17 days ago
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃጽዮን በሰጡት ማብራሪያ ፤ የኢትዮጵያ የልማት አስተዳደር ሪፎርም ሀገሪቱ የምታቅድበትን፣ ክትትል የምታደርግበትንና ውጤት የምታስመዘግብበትን አካሄድ መሠረታዊ በሆነ መልኩ እየቀየረው ይገኛል።
#ethiopia #digitalethiopia #digitaltransformation #governance #techethiopia
2 months ago
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ48.8 ሚሊዮን ዶላር የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱን እያፋጠነ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎችን የክፍያ ሥርዓት ወደ ዘመናዊ የዲጂታል መንገድ ለመቀየር የጀመረውን ግዙፍ ፕሮጀክት በስፋት እያከናወነ ይገኛል። ተቋሙ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለመግጠም ለጀመረው ለዚሁ ፕሮጀክት 48.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ማድረጉ ተገልጿል።
እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ከ67 ሺህ በላይ ደንበኞች የዘመናዊው ቆጣሪ ተጠቃሚ መሆን የጀመሩ ሲሆን፣
ዝርዝር አፈጻጸሙም 🔎
* 60,457 ነጠላ ፌዝ (Single Phase) ቆጣሪዎች፦ እስከ 7.5 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ መኖሪያና ንግድ ቤቶች አገልግሎት እየሰጡ ነው።
* 7,013 ባለ ሦስት ፌዝ (Three Phase) ቆጣሪዎች፦ ከ8 እስከ 24 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ አነስተኛ ኢንዱስትሪዎችና ቤቶች ተገጥመዋል።
ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ደንበኞች ቀደም ሲል የኤሌክትሪክ ቶክን ለመግዛት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በማቅናት ያባክኑት የነበረውን ጊዜና ጉልበት ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው።
ደንበኞች በፈለጉት ሰዓት (በ24 ሰዓት) ባሉበት ሆነው፦
* በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE Birr/App)
* በቴሌ ብር (telebirr)
* በአዋሽ ባንክ መተግበሪያዎች አማካኝነት
በቀላሉ ክፍያቸውን መፈጸም ይችላሉ።
ይህ እርምጃ የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ከማሳለጡ ባለፈ፣ ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነትና አስተማማኝነት ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianelectricutility #eeu #digitaltransformation #smartmeter #prepaidelectric #ethiopiatech #cbe #telebirr #awashbank #energyupdate
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቅድመ ክፍያ የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎችን የክፍያ ሥርዓት ወደ ዘመናዊ የዲጂታል መንገድ ለመቀየር የጀመረውን ግዙፍ ፕሮጀክት በስፋት እያከናወነ ይገኛል። ተቋሙ 500 ሺህ ስማርት የቅድመ ክፍያ ቆጣሪዎችን ለመግጠም ለጀመረው ለዚሁ ፕሮጀክት 48.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ማድረጉ ተገልጿል።
እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት ከ67 ሺህ በላይ ደንበኞች የዘመናዊው ቆጣሪ ተጠቃሚ መሆን የጀመሩ ሲሆን፣
ዝርዝር አፈጻጸሙም 🔎
* 60,457 ነጠላ ፌዝ (Single Phase) ቆጣሪዎች፦ እስከ 7.5 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ መኖሪያና ንግድ ቤቶች አገልግሎት እየሰጡ ነው።
* 7,013 ባለ ሦስት ፌዝ (Three Phase) ቆጣሪዎች፦ ከ8 እስከ 24 ኪሎ ዋት ለሚጠቀሙ አነስተኛ ኢንዱስትሪዎችና ቤቶች ተገጥመዋል።
ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ደንበኞች ቀደም ሲል የኤሌክትሪክ ቶክን ለመግዛት ወደ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በማቅናት ያባክኑት የነበረውን ጊዜና ጉልበት ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር ነው።
ደንበኞች በፈለጉት ሰዓት (በ24 ሰዓት) ባሉበት ሆነው፦
* በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE Birr/App)
* በቴሌ ብር (telebirr)
* በአዋሽ ባንክ መተግበሪያዎች አማካኝነት
በቀላሉ ክፍያቸውን መፈጸም ይችላሉ።
ይህ እርምጃ የሀገሪቱን የዲጂታል ኢኮኖሚ ጉዞ ከማሳለጡ ባለፈ፣ ለኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነትና አስተማማኝነት ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianelectricutility #eeu #digitaltransformation #smartmeter #prepaidelectric #ethiopiatech #cbe #telebirr #awashbank #energyupdate
3 months ago
አዋሽ ባንክ ሦስት አዳዲስ የዲጂታል መተግበሪያዎችን ሥራ ማስጀመሩን አስታወቀ
#ethiopia | አዋሽ ባንክ ለደንበኞቹ የሚሰጠውን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘና ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ሦስት አዳዲስ የዲጂታል መተግበሪያዎችን በይፋ ሥራ ማስጀመሩን አስታወቀ።
ባንኩ ዛሬ መጋቢት 03 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል ይፋ ያደረጋቸው መተግበሪያዎች
👉 “አዋሽ ሬሚት”፣
👉 “አዋሽ ኢ-ቲኬቲንግ” እና
👉 “አዋሽ ኢ-ፕሮፐርቲ ማኔጅመንት” የተሰኙ መተግበሪያዎችን ማስተዋወቁን ገልጿል።
ባንኩ እነዚህን የዲጂታል አገልግሎቶች በዝርዝር እንደሚከተለው አብራርቷል፡-
1. አዋሽ ሬሚት (Awash Remit)
ይህ መተግበሪያ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ፈጣንና ደህንነቱ የተጠበቀ የገንዘብ ዝውውር እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው። ደንበኞች የቪዛ (Visa) ወይም የማስተር ካርድ (MasterCard) በመጠቀም በቀጥታ ወደ አዋሽ ባንክ አካውንት፣ ወደ አዋሽ ብር ፕሮ ዋሌት ወይም በቅርንጫፎች በኩል የሚከፈል ገንዘብ በቀላሉ መላክ ይችላሉ።
2. አዋሽ ኢ-ቲኬቲንግ (Awash e-Ticketing)
ይህ አገልግሎት ኮንሰርቶችን ጨምሮ ማንኛውንም ሁነት (Event) የሚያዘጋጁ አካላት ትኬቶቻቸውን በኢንተርኔት አማካኝነት እንዲሸጡና እንዲያስተዳድሩ የሚያስችል ነው። የወረቀት ትኬቶችን በQR ኮድ በመተካት ለአዘጋጆችም ሆነ ለታዳሚዎች ምቹ፣ ግልጽና ደህንነቱ የተጠበቀ አሠራርን ይፈጥራል። አገልግሎቱ ለኮንፈረንሶች፣ ለስፖርታዊ ኩነቶችና ለሃይማኖታዊ ስብሰባዎች እጅግ ጠቃሚ መሆኑ ተገልጿል።
3. አዋሽ ኢ-ፕሮፐርቲ ማኔጅመንት (Awash e-Property Management)
ይህ መተግበሪያ የህንጻ ባለቤቶችና ተከራዮች ግንኙነትን በዲጂታል መንገድ የሚያቀላጥፍ ነው። የቤት ኪራይ አሰባሰብን፣ የፋይናንስ ክትትልንና የውል ስምምነቶችን በዘመናዊ መልኩ ለማስተዳደር ይረዳል። በተጨማሪም የሚከራዩ ክፍሎችን፣ የንግድ ቦታዎችንና የመኪና ማቆሚያዎችን በዝርዝር ለመለየትና ለማስተዳደር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተመላክቷል።
ባንኩ በመግለጫው እንዳመለከተው፣ ከሐምሌ እስከ ታኅሣሥ 2025 ባሉት ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ በዲጂታል የክፍያ ሥርዓት የተከናወነው የገንዘብ ልውውጥ መጠን ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጿል።
ይህም ባንኩ ከመንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመሥራቱ የተመዘገበ ውጤት መሆኑ ተጠቅሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#awashbank #digitalbanking #fintechethiopia #awashremit #eticketing #propertymanagement #ethiopiabanking #digitaltransformation #financialinnovation #cashlessethiopia
#ethiopia | አዋሽ ባንክ ለደንበኞቹ የሚሰጠውን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘና ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ሦስት አዳዲስ የዲጂታል መተግበሪያዎችን በይፋ ሥራ ማስጀመሩን አስታወቀ።
ባንኩ ዛሬ መጋቢት 03 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል ይፋ ያደረጋቸው መተግበሪያዎች
👉 “አዋሽ ሬሚት”፣
👉 “አዋሽ ኢ-ቲኬቲንግ” እና
👉 “አዋሽ ኢ-ፕሮፐርቲ ማኔጅመንት” የተሰኙ መተግበሪያዎችን ማስተዋወቁን ገልጿል።
ባንኩ እነዚህን የዲጂታል አገልግሎቶች በዝርዝር እንደሚከተለው አብራርቷል፡-
1. አዋሽ ሬሚት (Awash Remit)
ይህ መተግበሪያ በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ፈጣንና ደህንነቱ የተጠበቀ የገንዘብ ዝውውር እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው። ደንበኞች የቪዛ (Visa) ወይም የማስተር ካርድ (MasterCard) በመጠቀም በቀጥታ ወደ አዋሽ ባንክ አካውንት፣ ወደ አዋሽ ብር ፕሮ ዋሌት ወይም በቅርንጫፎች በኩል የሚከፈል ገንዘብ በቀላሉ መላክ ይችላሉ።
2. አዋሽ ኢ-ቲኬቲንግ (Awash e-Ticketing)
ይህ አገልግሎት ኮንሰርቶችን ጨምሮ ማንኛውንም ሁነት (Event) የሚያዘጋጁ አካላት ትኬቶቻቸውን በኢንተርኔት አማካኝነት እንዲሸጡና እንዲያስተዳድሩ የሚያስችል ነው። የወረቀት ትኬቶችን በQR ኮድ በመተካት ለአዘጋጆችም ሆነ ለታዳሚዎች ምቹ፣ ግልጽና ደህንነቱ የተጠበቀ አሠራርን ይፈጥራል። አገልግሎቱ ለኮንፈረንሶች፣ ለስፖርታዊ ኩነቶችና ለሃይማኖታዊ ስብሰባዎች እጅግ ጠቃሚ መሆኑ ተገልጿል።
3. አዋሽ ኢ-ፕሮፐርቲ ማኔጅመንት (Awash e-Property Management)
ይህ መተግበሪያ የህንጻ ባለቤቶችና ተከራዮች ግንኙነትን በዲጂታል መንገድ የሚያቀላጥፍ ነው። የቤት ኪራይ አሰባሰብን፣ የፋይናንስ ክትትልንና የውል ስምምነቶችን በዘመናዊ መልኩ ለማስተዳደር ይረዳል። በተጨማሪም የሚከራዩ ክፍሎችን፣ የንግድ ቦታዎችንና የመኪና ማቆሚያዎችን በዝርዝር ለመለየትና ለማስተዳደር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተመላክቷል።
ባንኩ በመግለጫው እንዳመለከተው፣ ከሐምሌ እስከ ታኅሣሥ 2025 ባሉት ስድስት ወራት ውስጥ ብቻ በዲጂታል የክፍያ ሥርዓት የተከናወነው የገንዘብ ልውውጥ መጠን ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ መድረሱን ገልጿል።
ይህም ባንኩ ከመንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመሥራቱ የተመዘገበ ውጤት መሆኑ ተጠቅሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#awashbank #digitalbanking #fintechethiopia #awashremit #eticketing #propertymanagement #ethiopiabanking #digitaltransformation #financialinnovation #cashlessethiopia
3 months ago
AI የሰው ልጅን ከሥራ አያፈናቅልም፤ ይልቁንም አቅምን ያሳድጋል!
#ብዙዎቻችን "አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሥራዬን ይነጥቀኝ ይሆን?" የሚል ስጋት ነበረብን። ሆኖም የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ያወጣው አዲስ ጥናት ይህንን ስጋት የሚቀይር አስገራሚ ውጤት ይፋ አድርጓል።
AIን መጠቀም የሚያስገኘው ትርፍ በቁጥር፦
ጥናቱ AIን በሥራቸው ላይ የጨመሩ ሠራተኞች ካልተጠቀሙት በተሻለ የሚከተሉትን ለውጦች እንዳሳዩ አረጋግጧል፦
የፈጠራ ችሎታ (Creativity)፦ በ 40% ጨምሯል!
የሥራ ፍጥነት (Efficiency)፦ በ 25% አድጓል!
የሥራ ጥራት (Quality)፦ በ 18% መሻሻል አሳይቷል!
AI አድካሚና ተደጋጋሚ ሥራዎችን በፍጥነት ቢሰራም፣ የሚከተሉት የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክህሎቶች ግን በማሽኖች ሊተኩ እንደማይችሉ ጥናቱ ይገልጻል፦
ሂሳዊ አስተሳሰብ (Critical Thinking)
ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ (Ethics)
ጥልቅ ስሜታዊ ግንኙነት (Emotional Intelligence)
እንደ ዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም (WEF) ትንበያ፣ በቴክኖሎጂው ምክንያት አንዳንድ ነባር ሥራዎች ቢቀየሩም፣ 97 ሚሊዮን የሚደርሱ አዳዲስና ዘመናዊ የሥራ ዕድሎች ይፈጠራሉ። ቁልፉ ያለው ራስን ከቴክኖሎጂው ጋር በማላመድና አዳዲስ ዲጂታል ክህሎቶችን በማዳበር ላይ ነው።
AIን በዕለት ተዕለት ሥራዎ ወይም ትምህርትዎ ላይ መጠቀም ጀምረዋል? የሥራ ጫናዎን ቀንሶልዎታል ወይስ ይበልጥ አሳስቦዎታል? ራስዎን ለነገው የሥራ ገበያ እንዴት እያዘጋጁ ነው?
#artificialintelligence #ai #futureofwork #technology #productivity #digitaltransformation #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ብዙዎቻችን "አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሥራዬን ይነጥቀኝ ይሆን?" የሚል ስጋት ነበረብን። ሆኖም የጆንስ ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ያወጣው አዲስ ጥናት ይህንን ስጋት የሚቀይር አስገራሚ ውጤት ይፋ አድርጓል።
AIን መጠቀም የሚያስገኘው ትርፍ በቁጥር፦
ጥናቱ AIን በሥራቸው ላይ የጨመሩ ሠራተኞች ካልተጠቀሙት በተሻለ የሚከተሉትን ለውጦች እንዳሳዩ አረጋግጧል፦
የፈጠራ ችሎታ (Creativity)፦ በ 40% ጨምሯል!
የሥራ ፍጥነት (Efficiency)፦ በ 25% አድጓል!
የሥራ ጥራት (Quality)፦ በ 18% መሻሻል አሳይቷል!
AI አድካሚና ተደጋጋሚ ሥራዎችን በፍጥነት ቢሰራም፣ የሚከተሉት የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ክህሎቶች ግን በማሽኖች ሊተኩ እንደማይችሉ ጥናቱ ይገልጻል፦
ሂሳዊ አስተሳሰብ (Critical Thinking)
ሥነ-ምግባራዊ ውሳኔ አሰጣጥ (Ethics)
ጥልቅ ስሜታዊ ግንኙነት (Emotional Intelligence)
እንደ ዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም (WEF) ትንበያ፣ በቴክኖሎጂው ምክንያት አንዳንድ ነባር ሥራዎች ቢቀየሩም፣ 97 ሚሊዮን የሚደርሱ አዳዲስና ዘመናዊ የሥራ ዕድሎች ይፈጠራሉ። ቁልፉ ያለው ራስን ከቴክኖሎጂው ጋር በማላመድና አዳዲስ ዲጂታል ክህሎቶችን በማዳበር ላይ ነው።
AIን በዕለት ተዕለት ሥራዎ ወይም ትምህርትዎ ላይ መጠቀም ጀምረዋል? የሥራ ጫናዎን ቀንሶልዎታል ወይስ ይበልጥ አሳስቦዎታል? ራስዎን ለነገው የሥራ ገበያ እንዴት እያዘጋጁ ነው?
#artificialintelligence #ai #futureofwork #technology #productivity #digitaltransformation #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
ሳውዲ አረቢያ ለግመሎቿ "ዲጂታል ፓስፖርት" አዘጋጀች
#ethiopia | ሳውዲ አረቢያ በባህላዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፏ ትልቅ ድርሻ ያለውን የግመል ሃብት አያያዝ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ ዘመናዊ የዲጂታል ፓስፖርት አሰራርን በይፋ አስጀመረች።
ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ እርምጃ በሀገሪቱ የሚገኙ ግመሎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ለመሰብሰብ፣ ለመቆጣጠር እና የግብይት ሂደቱን አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ ነው።
በአካባቢ፣ ውሃ እና ግብርና ሚኒስቴር ስር በተካሄደው እና የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት ብሔራዊ ፕሮግራም አካል በሆነው በዚህ ፕሮጀክት፤ እያንዳንዱ ግመል የራሱ የሆነ ዲጂታል መታወቂያ ወይም "ፓስፖርት" ይኖረዋል። ይህ አሰራር የግመሎቹን የዘር ሐረግ፣ የባለቤትነት መብት እና የጤና ታሪክ በአንድ ቋት ውስጥ በማካተት የመረጃ ፍሰቱን ቀልጣፋ ያደርገዋል ተብሏል።
የፕሮጀክቱን ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የመሩት ምክትል ሚኒስትሩ ማንሱር አል-ሙሻይቲ እንደገለጹት፣ ይህ የዲጂታል ሽግግር ለዘርፉ ተዋንያን ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ነው። በተለይም በእንስሳት ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅልጥፍናን ከመፍጠሩም ባሻገር፣ በግመሎች ግብይት ወቅት የሚነሱ የባለቤትነት ውዝግቦችን በመፍታት እና የገበያ ተዓማኒነትን በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ይህ እርምጃ ሳውዲ አረቢያ ባህላዊ የግመል እርባታን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር ለማስተሳሰር የጀመረችው ሰፊ ዕቅድ አንድ አካል ሲሆን፣ በመላው የንጉሳዊው መንግስት ግዛቶች ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሳውዲአረቢያ #ግመል #ዲጂታል_ፓስፖርት #ቴክኖሎጂ #ግብርና #saudiarabia #camelpassport #digitaltransformation
#ethiopia | ሳውዲ አረቢያ በባህላዊ እና ኢኮኖሚያዊ ዘርፏ ትልቅ ድርሻ ያለውን የግመል ሃብት አያያዝ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር፣ ዘመናዊ የዲጂታል ፓስፖርት አሰራርን በይፋ አስጀመረች።
ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ እርምጃ በሀገሪቱ የሚገኙ ግመሎችን መረጃ በዘመናዊ መንገድ ለመሰብሰብ፣ ለመቆጣጠር እና የግብይት ሂደቱን አስተማማኝ ለማድረግ ያለመ ነው።
በአካባቢ፣ ውሃ እና ግብርና ሚኒስቴር ስር በተካሄደው እና የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት ብሔራዊ ፕሮግራም አካል በሆነው በዚህ ፕሮጀክት፤ እያንዳንዱ ግመል የራሱ የሆነ ዲጂታል መታወቂያ ወይም "ፓስፖርት" ይኖረዋል። ይህ አሰራር የግመሎቹን የዘር ሐረግ፣ የባለቤትነት መብት እና የጤና ታሪክ በአንድ ቋት ውስጥ በማካተት የመረጃ ፍሰቱን ቀልጣፋ ያደርገዋል ተብሏል።
የፕሮጀክቱን ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የመሩት ምክትል ሚኒስትሩ ማንሱር አል-ሙሻይቲ እንደገለጹት፣ ይህ የዲጂታል ሽግግር ለዘርፉ ተዋንያን ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ነው። በተለይም በእንስሳት ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ቅልጥፍናን ከመፍጠሩም ባሻገር፣ በግመሎች ግብይት ወቅት የሚነሱ የባለቤትነት ውዝግቦችን በመፍታት እና የገበያ ተዓማኒነትን በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ይህ እርምጃ ሳውዲ አረቢያ ባህላዊ የግመል እርባታን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር ለማስተሳሰር የጀመረችው ሰፊ ዕቅድ አንድ አካል ሲሆን፣ በመላው የንጉሳዊው መንግስት ግዛቶች ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሳውዲአረቢያ #ግመል #ዲጂታል_ፓስፖርት #ቴክኖሎጂ #ግብርና #saudiarabia #camelpassport #digitaltransformation
4 months ago
ኢትዮ ቴሌኮም በስድስት ወራት ውስጥ የ85 ቢሊዮን ብር ገቢ አስመዘገበ
#ethiopia | ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ የሥራ አፈጻጸሙን ይፋ ባደረገበት መግለጫ፣ በስድስት ወራት ውስጥ 85 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በገቢውም ሆነ በደንበኞች ቁጥር በኩል ከፍተኛ መሻሻል አሳይቷል።
የአፈጻጸሙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የደንበኞች ቁጥር፦ አጠቃላይ የቴሌኮም ተጠቃሚዎች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8.2 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
* የቴሌብር ስኬት፦ የቴሌብር ደንበኞች ቁጥር 58.6 ሚሊዮን ያለፈ ሲሆን፣ በግማሽ ዓመቱ ብቻ በዘርፉ 1.9 ትሪሊዮን ብር ማንቀሳቀስ ተችሏል።
* ስትራቴጂያዊ እቅድ፦ ኩባንያው ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚተገበር ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ አስደናቂ ውጤት ተቋሙ የጀመረውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ እንደሚያፋጥነው ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
📸 ከበደ መክብብ
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #ኢትዮቴሌኮም #ኢትዮጵያ #ዲጂታልኢትዮጵያ #ቴሌብር #ኢኮኖሚ #ethiotelecom #telebirr #ethiopia #digitaltransformation
#ethiopia | ኢትዮ ቴሌኮም የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ የሥራ አፈጻጸሙን ይፋ ባደረገበት መግለጫ፣ በስድስት ወራት ውስጥ 85 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል። የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በገቢውም ሆነ በደንበኞች ቁጥር በኩል ከፍተኛ መሻሻል አሳይቷል።
የአፈጻጸሙ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የደንበኞች ቁጥር፦ አጠቃላይ የቴሌኮም ተጠቃሚዎች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ8.2 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።
* የቴሌብር ስኬት፦ የቴሌብር ደንበኞች ቁጥር 58.6 ሚሊዮን ያለፈ ሲሆን፣ በግማሽ ዓመቱ ብቻ በዘርፉ 1.9 ትሪሊዮን ብር ማንቀሳቀስ ተችሏል።
* ስትራቴጂያዊ እቅድ፦ ኩባንያው ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚተገበር ስትራቴጂ በመቅረጽ፣ የዲጂታል ኢትዮጵያን ጉዞ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ አስደናቂ ውጤት ተቋሙ የጀመረውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ እንደሚያፋጥነው ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
📸 ከበደ መክብብ
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #ኢትዮቴሌኮም #ኢትዮጵያ #ዲጂታልኢትዮጵያ #ቴሌብር #ኢኮኖሚ #ethiotelecom #telebirr #ethiopia #digitaltransformation
Sponsored by
Surafel