3 days ago
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
5 months ago
6ኛው ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 22 ዓመታት የንባብ ባህልን ለማስፋፋትና ትምህርትን ለመደገፍ ሲሠራ የቆየው ኢትዮጵያ ሪድስ (Ethiopia Reads)፣ ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ ያዘጋጀውን ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
"የንባብ ችግኝ በቀዳማይ ልጅነት መትከል" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ በሕፃናት የንባብ ዕድገትና በትምህርት ጥራት ዙሪያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የሚከናወን ታላቅ መድረክ ነው።
በዚህ ጉባኤ ላይ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የትምህርት ዘርፍ ተመራማሪዎች፣ መምህራን፣ ደራሲያን፣ የአሳታሚ ድርጅቶች ተወካዮች እንዲሁም ከውጭ አገር የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
መድረኩ በዋናነት በሕፃናት የንባብ ልምድ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት፣ የፓናል ውይይቶች የሚካሄዱበትና ልምድ የሚለዋወጥበት ሰፊ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣትና የንባብ ባህልን ከልጅነት ጀምሮ ለማዳበር ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ሪድስ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ከ70 በላይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቤተ-መጻሕፍትን በማቋቋም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎችና ሕፃናት የንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ችሏል።
በተጨማሪም ድርጅቱ ከ"Open Hearts Big Dreams" ጋር በመተባበር "ሬዲ-ሴት-ሪድ" በሚል መጠሪያ የሕፃናት መጻሕፍትን በአሥር አገር በቀል ቋንቋዎች በማዘጋጀትና በማሰራጨት ሕፃናት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤታቸው ከወላጆቻቸው ጋር ሆነው እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅትም ድርጅቱ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቤት መሄድ ለማይችሉ ከ14 ሺህ በላይ ሕፃናት በፈረስና በአህያ በታገዘ ተንቀሳቃሽ የንባብ አገልግሎት መጻሕፍትን እስከ መንደራቸው ድረስ በማድረስ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ይህ የስድስተኛው ዓመታዊ ጉባኤም ድርጅቱ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ከመገምገም ባለፈ፣ ለወደፊቱ የተሻለ የእውቀት ትውልድ ለመቅረጽ የሚያስችሉ ጠቃሚ ግብዓቶችና ምክረ-ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopiareads #childrensliteracy #readingculture #ethiopiaeducation #earlychildhoodeducation #bookfair #literacyconference #readysetread
#ethiopia | በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 22 ዓመታት የንባብ ባህልን ለማስፋፋትና ትምህርትን ለመደገፍ ሲሠራ የቆየው ኢትዮጵያ ሪድስ (Ethiopia Reads)፣ ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ ያዘጋጀውን ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
"የንባብ ችግኝ በቀዳማይ ልጅነት መትከል" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ በሕፃናት የንባብ ዕድገትና በትምህርት ጥራት ዙሪያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የሚከናወን ታላቅ መድረክ ነው።
በዚህ ጉባኤ ላይ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የትምህርት ዘርፍ ተመራማሪዎች፣ መምህራን፣ ደራሲያን፣ የአሳታሚ ድርጅቶች ተወካዮች እንዲሁም ከውጭ አገር የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
መድረኩ በዋናነት በሕፃናት የንባብ ልምድ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት፣ የፓናል ውይይቶች የሚካሄዱበትና ልምድ የሚለዋወጥበት ሰፊ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣትና የንባብ ባህልን ከልጅነት ጀምሮ ለማዳበር ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ሪድስ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ከ70 በላይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቤተ-መጻሕፍትን በማቋቋም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎችና ሕፃናት የንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ችሏል።
በተጨማሪም ድርጅቱ ከ"Open Hearts Big Dreams" ጋር በመተባበር "ሬዲ-ሴት-ሪድ" በሚል መጠሪያ የሕፃናት መጻሕፍትን በአሥር አገር በቀል ቋንቋዎች በማዘጋጀትና በማሰራጨት ሕፃናት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤታቸው ከወላጆቻቸው ጋር ሆነው እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅትም ድርጅቱ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቤት መሄድ ለማይችሉ ከ14 ሺህ በላይ ሕፃናት በፈረስና በአህያ በታገዘ ተንቀሳቃሽ የንባብ አገልግሎት መጻሕፍትን እስከ መንደራቸው ድረስ በማድረስ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ይህ የስድስተኛው ዓመታዊ ጉባኤም ድርጅቱ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ከመገምገም ባለፈ፣ ለወደፊቱ የተሻለ የእውቀት ትውልድ ለመቅረጽ የሚያስችሉ ጠቃሚ ግብዓቶችና ምክረ-ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopiareads #childrensliteracy #readingculture #ethiopiaeducation #earlychildhoodeducation #bookfair #literacyconference #readysetread
Comments