2 days ago
ለሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ የባህልና ጥበባት አምባሳደር ሞዴል ሩት ይርጋለም ሸኝት ተደረገላት።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለምትወክለው ሞዴል ሩት ይርጋለም የእንኳን ደስ አለሽና የሽኝት መርሃ ግብር አደረገ።
ክብርት ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ለሞዴሏ መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ በማስተዋወቅ በድል እንድትመለስ ተመኝተዋል።
ክብርት ሸዊት በንግግራቸው ሞዴሏ የባህል አምባሳደር ሆና ከተሾመች በኋላ የሀገሪቱን ብዝሃ ባህላዊ ዕሴቶች በቅርበት ለመረዳት በተለያዩ ቦታዎች ጉብኝት ማድረጓን አንስተዋል።
በዚሁ መሠረት በደቡብ ኢትዮጵያ በመገኘት የህዝቡን ባህል፣ በአማራ ክልል ጎንደር በመሄድ የክልሉን ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ባሌ በመገኘት የገዳ ስርዓትንና ድቅ ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን በበቂ ሁኔታ ጎብኝታለች ብለዋል።
ይህ በክልሎች ያደረገችው ቆይታ የሀገሪቱን ባህልና ጥበብ ጠልቃ እንድታውቅ የረዳት ሲሆን፣ ከ130 በላይ የዓለም ሀገራት ሞዴሎች በሚሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያን በብቃት ለማስተዋወቅና ገጽታዋን ከፍ ለማድረግ እንደሚያግዛት ገልፀዋል።
የገጠማትን ማንኛውንም ፈተና ተቋቁማ የሀገሯን ባህልና ጥበብ በዓለም አቀፍ አደባባይ ለማሳየት ቆርጣ የተነሳች ጠንካራ ወጣት በመሆኗ ትልቅ አድናቆትና ምስጋና እንደሚገባትም ክብርት ሸዊት ሻንካ አክለዋል።
ክብርት ሸዊት ለመላው ኢትዮጵያውያን ባስተላለፈው መልዕክት በመጪው ውድድር ላይ በሚፈጠረው የማህበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ (Link) አማካኝነት ሁሉም ድጋፉን እንዲሰጥና ለሞዴሏ ስኬት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ሞዴል ሩት ይርጋለም በበኩሏ ለተደረገላት የሸኝትና መልካም ምኞት መርሀ ግብር ምስጋና አቅርባለች።
ሞዴሏ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለማስጠራት ቆርጣ እንደተነሳች በመግለፅ የገጠማት ችግር ወደሗላ እንደማይመልሳት አንስታለች።
ከዓለም አቀፉ ውድድር በሗላም በሀገሯ ያሉ ባህላዊና ጥበባዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅ እደምሰራ ገልፃለች።
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደር የባህልና ስፖርት ሴክተር አመራሮች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች፣ የሙያ ማህበራት አመራሮችና የሞዴሏ ቤተሰቦች ተገኝተው ለሞዴሏ የሀገር አደራ ተሰጥቷል።
Via የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለምትወክለው ሞዴል ሩት ይርጋለም የእንኳን ደስ አለሽና የሽኝት መርሃ ግብር አደረገ።
ክብርት ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ለሞዴሏ መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ በማስተዋወቅ በድል እንድትመለስ ተመኝተዋል።
ክብርት ሸዊት በንግግራቸው ሞዴሏ የባህል አምባሳደር ሆና ከተሾመች በኋላ የሀገሪቱን ብዝሃ ባህላዊ ዕሴቶች በቅርበት ለመረዳት በተለያዩ ቦታዎች ጉብኝት ማድረጓን አንስተዋል።
በዚሁ መሠረት በደቡብ ኢትዮጵያ በመገኘት የህዝቡን ባህል፣ በአማራ ክልል ጎንደር በመሄድ የክልሉን ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ባሌ በመገኘት የገዳ ስርዓትንና ድቅ ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን በበቂ ሁኔታ ጎብኝታለች ብለዋል።
ይህ በክልሎች ያደረገችው ቆይታ የሀገሪቱን ባህልና ጥበብ ጠልቃ እንድታውቅ የረዳት ሲሆን፣ ከ130 በላይ የዓለም ሀገራት ሞዴሎች በሚሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያን በብቃት ለማስተዋወቅና ገጽታዋን ከፍ ለማድረግ እንደሚያግዛት ገልፀዋል።
የገጠማትን ማንኛውንም ፈተና ተቋቁማ የሀገሯን ባህልና ጥበብ በዓለም አቀፍ አደባባይ ለማሳየት ቆርጣ የተነሳች ጠንካራ ወጣት በመሆኗ ትልቅ አድናቆትና ምስጋና እንደሚገባትም ክብርት ሸዊት ሻንካ አክለዋል።
ክብርት ሸዊት ለመላው ኢትዮጵያውያን ባስተላለፈው መልዕክት በመጪው ውድድር ላይ በሚፈጠረው የማህበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ (Link) አማካኝነት ሁሉም ድጋፉን እንዲሰጥና ለሞዴሏ ስኬት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ሞዴል ሩት ይርጋለም በበኩሏ ለተደረገላት የሸኝትና መልካም ምኞት መርሀ ግብር ምስጋና አቅርባለች።
ሞዴሏ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለማስጠራት ቆርጣ እንደተነሳች በመግለፅ የገጠማት ችግር ወደሗላ እንደማይመልሳት አንስታለች።
ከዓለም አቀፉ ውድድር በሗላም በሀገሯ ያሉ ባህላዊና ጥበባዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅ እደምሰራ ገልፃለች።
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደር የባህልና ስፖርት ሴክተር አመራሮች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች፣ የሙያ ማህበራት አመራሮችና የሞዴሏ ቤተሰቦች ተገኝተው ለሞዴሏ የሀገር አደራ ተሰጥቷል።
Via የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) — በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል በተካሄደ ልዩ የዕውቅና እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ ጸደይ ባንክ አዲሱን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዮሐንስ አያሌውን ከተቀበለ በኋላ የፋይናንስ እና የአሰራር ለውጦችን ማስመዝገብ መቻሉን ገለጸ። ባንኩ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ይገጥመው የነበረውን የኪሳራ ታሪክ በመቀልበስ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 4.3 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘት መቻሉ ተገልጿል።
በባንክ ኢንዱስትሪው ትልቅ ማነቆ የሆነውን የተበላሸ ብድር (Non-Performing Loans - NPL) መጠን በመቀነስ ረገድ ጸደይ ባንክ የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገብም ተነግሯል። ባለፈው በጀት ዓመት ከፍተኛ አደጋ በሚያመለክተው የ21 በመቶ ደረጃ ላይ የነበረው የተበላሸ ብድር ምጣኔ፣ በስድስት ወራት ውስጥ ወደ 6 በመቶ ዝቅ ብሎ የነበረ ሲሆን፤ አሁን በጀት ዓመቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው አስገዳጅ የ5 በመቶ ጣሪያ በታች ማውረድ መቻሉ ተብራርቷል። ይህ ስኬት አዲሱ አመራር የብድር አመላለስ ሥርዓቱን ውጤታማ እና ጥብቅ በሆነ መንገድ በማሻሻሉ ነው ተብሏል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የባንኩን አጠቃላይ ግብ እና የሥራ ዕቅድ በማሳካት የላቀ ውጤት ላመጡ የሥራ ኃላፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ፕሮግራም ተካሂዷል። ከእነዚህም መካከል የፍኖተሰላም ዲስትሪክት ማናጀር የሆኑት አቶ ደሳለኝ ወንዳለ ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ደሳለኝ በሁሉም ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) ባስመዘገቡት አመርቂ ውጤት ልዩ ተሸላሚ መሆን ችለዋል።
በዕለቱ የቀድሞው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን የለውወሰንም የሽኝት ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸዋል። ለባንኩ ባለፉት 30 ዓመታት አበረከቱት ለተባለው አገልግሎት "ዕውቅና ለመስጠት" ቶዮታ RAV4 Hybrid 2026 ሞዴል መኪና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ሌሎች ጥቅማጥቅሞችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩላቸው መደረጉን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ የውስጥ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ባንኩ በዚሁ መድረክ ላይ የረዥም ጊዜ የስትራቴጂክ ዕቅዱን እና ራዕዩንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት የባንኩ ቀጣይ ትልልቅ ግቦቼ የሚከተሉት ናቸው ብሏል፦
በአውሮፓውያኑ 2030 በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግዙፍ 4 የንግድ ባንኮች አንዱ መሆን።
በአውሮፓውያኑ 2040 ደግሞ የሀገር ውስጥ ገበያን አልፎ በመላው አፍሪካ ከሚገኙ 40 ምርጥ የንግድ ባንኮች ተርታ መሰለፍ።
በባንክ ኢንዱስትሪው ትልቅ ማነቆ የሆነውን የተበላሸ ብድር (Non-Performing Loans - NPL) መጠን በመቀነስ ረገድ ጸደይ ባንክ የተሻለ ውጤት እንዳስመዘገብም ተነግሯል። ባለፈው በጀት ዓመት ከፍተኛ አደጋ በሚያመለክተው የ21 በመቶ ደረጃ ላይ የነበረው የተበላሸ ብድር ምጣኔ፣ በስድስት ወራት ውስጥ ወደ 6 በመቶ ዝቅ ብሎ የነበረ ሲሆን፤ አሁን በጀት ዓመቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው አስገዳጅ የ5 በመቶ ጣሪያ በታች ማውረድ መቻሉ ተብራርቷል። ይህ ስኬት አዲሱ አመራር የብድር አመላለስ ሥርዓቱን ውጤታማ እና ጥብቅ በሆነ መንገድ በማሻሻሉ ነው ተብሏል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የባንኩን አጠቃላይ ግብ እና የሥራ ዕቅድ በማሳካት የላቀ ውጤት ላመጡ የሥራ ኃላፊዎች የሽልማት አሰጣጥ ፕሮግራም ተካሂዷል። ከእነዚህም መካከል የፍኖተሰላም ዲስትሪክት ማናጀር የሆኑት አቶ ደሳለኝ ወንዳለ ተጠቃሽ ናቸው። አቶ ደሳለኝ በሁሉም ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያዎች (KPIs) ባስመዘገቡት አመርቂ ውጤት ልዩ ተሸላሚ መሆን ችለዋል።
በዕለቱ የቀድሞው ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን የለውወሰንም የሽኝት ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸዋል። ለባንኩ ባለፉት 30 ዓመታት አበረከቱት ለተባለው አገልግሎት "ዕውቅና ለመስጠት" ቶዮታ RAV4 Hybrid 2026 ሞዴል መኪና ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ሌሎች ጥቅማጥቅሞችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩላቸው መደረጉን ለዘ-ሐበሻ የደረሱ የውስጥ መረጃዎች ጠቁመዋል።
ባንኩ በዚሁ መድረክ ላይ የረዥም ጊዜ የስትራቴጂክ ዕቅዱን እና ራዕዩንም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት የባንኩ ቀጣይ ትልልቅ ግቦቼ የሚከተሉት ናቸው ብሏል፦
በአውሮፓውያኑ 2030 በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ግዙፍ 4 የንግድ ባንኮች አንዱ መሆን።
በአውሮፓውያኑ 2040 ደግሞ የሀገር ውስጥ ገበያን አልፎ በመላው አፍሪካ ከሚገኙ 40 ምርጥ የንግድ ባንኮች ተርታ መሰለፍ።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደር (FAA) የቦይንግ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ አነስተኛው ሞዴል የሆነውን ቦይንግ 737 ማክስ 7 ለንግድ በረራ አገልግሎት እንዲውል ሰኞ ዕለት ማጽደቁን አስታውቋል። አውሮፕላኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ከተደረገ ከአስር ዓመታት ገደማ በኋላ የተሰጠው ይህ የእውቅና ማረጋገጫ፣ ኩባንያው ለዓመታት ሲገጥሙት የነበሩትን የደህንነት፣ የጥራት እና የምርት ተግዳሮቶች በማለፍ ረገድ እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተቆጥሯል። ለረጅም ጊዜ የዘገየው ይህ ማክስ 7 አውሮፕላን የቦይንግ 737 የንግድ አውሮፕላኖች ቤተሰብ አካል ሲሆን፣ ይህ ሞዴል ለኩባንያው ከፍተኛ የገቢ ምንጭ ቢሆንም ላለፉት ተከታታይ ዓመታት የበርካታ ቀውሶች ማዕከል ሆኖ ቆይቷል።
የዚህ አውሮፕላን ማረጋገጫ ሂደት እጅግ ሊዘገይ የቻለው፣ በ2018 እና 2019 በኢንዶኔዥያ እና በኢትዮጵያ 346 ንጹሃን ዜጎችን የቀጠፈውን ትልቁን የማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ ተከትሎ በተፈጠረው ከፍተኛ የቁጥጥር ማዕቀፍ እና የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት ነው። ኤፍ ኤ ኤ (FAA) ማረጋገጫውን የሰጠው ለዓመታት ተጨማሪ ሙከራዎችን፣ የዲዛይን ለውጦችን እና በደህንነት ስርዓቶች ላይ ጥብቅ ግምገማ ካደረገ በኋላ መሆኑን አስታውቋል። ከእነዚህም አሳዛኝ አደጋዎች በኋላ አስተዳደሩ የቦይንግ አውሮፕላኖችን የሚያጸድቅበትን አሰራር ሙሉ በሙሉ የቀየረ ሲሆን፣ በኩባንያው ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትል ከማክስ 7 ፈቃድ አሰጣጥ በኋላም እንደሚቀጥል አሳስቧል።
የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደሩ አውሮፕላኑ ወደ በረራ ከመመለሱ በፊት ቦይንግ ወሳኝ የደህንነት ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ አስገድዶ ነበር። ከእነዚህም መካከል የበረራ መቆጣጠሪያ ሶፍትዌርን ማዘመን፣ ለአብራሪዎች የሚሰጠውን የማስጠንቀቂያ ስርዓት ማሻሻል፣ እና ከመጠን በላይ ሙቀትን ለመከላከል የሞተር ፀረ-በረዶ (anti-ice) ስርዓትን እንደገና ዲዛይን ማድረግ ይገኙበታል። በተጨማሪም የደህንነት ተቆጣጣሪዎች የኩባንያውን የደህንነት አስተዳደር ስርዓት እና አጠቃላይ የደህንነት ባህልን ጨምሮ የአመራረት ሂደቱን ለመከታተል በቦይንግ የማምረቻ ተቋማት ውስጥ በቋሚነት እንደሚቆዩ አስተዳደሩ ገልጿል።
የቦይንግ የንግድ አውሮፕላኖች ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ስቴፋኒ ፖፕ በበኩላቸው፣ የኩባንያው መሃንዲሶች እና የሙከራ ባለሙያዎች ወረርሽኙን እና አዳዲስ የማረጋገጫ ሂደቶችን ጨምሮ በርካታ ተግዳሮቶችን በጽናት ማለፋቸውን ተናግረዋል። ይህ አዲሱ ማክስ 7 አውሮፕላን በዋናነት ለአጭር እና መካከለኛ ርቀት በረራዎች ጥቅም ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ሳውዝ ዌስት ኤርላይንስን ጨምሮ በርካታ አየር መንገዶች ቀደም ብለው ባዘዙት መሰረት አውሮፕላኑን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
የዚህ አውሮፕላን ማረጋገጫ ሂደት እጅግ ሊዘገይ የቻለው፣ በ2018 እና 2019 በኢንዶኔዥያ እና በኢትዮጵያ 346 ንጹሃን ዜጎችን የቀጠፈውን ትልቁን የማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ ተከትሎ በተፈጠረው ከፍተኛ የቁጥጥር ማዕቀፍ እና የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት ነው። ኤፍ ኤ ኤ (FAA) ማረጋገጫውን የሰጠው ለዓመታት ተጨማሪ ሙከራዎችን፣ የዲዛይን ለውጦችን እና በደህንነት ስርዓቶች ላይ ጥብቅ ግምገማ ካደረገ በኋላ መሆኑን አስታውቋል። ከእነዚህም አሳዛኝ አደጋዎች በኋላ አስተዳደሩ የቦይንግ አውሮፕላኖችን የሚያጸድቅበትን አሰራር ሙሉ በሙሉ የቀየረ ሲሆን፣ በኩባንያው ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትል ከማክስ 7 ፈቃድ አሰጣጥ በኋላም እንደሚቀጥል አሳስቧል።
የፌደራል አቪዬሽን አስተዳደሩ አውሮፕላኑ ወደ በረራ ከመመለሱ በፊት ቦይንግ ወሳኝ የደህንነት ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ አስገድዶ ነበር። ከእነዚህም መካከል የበረራ መቆጣጠሪያ ሶፍትዌርን ማዘመን፣ ለአብራሪዎች የሚሰጠውን የማስጠንቀቂያ ስርዓት ማሻሻል፣ እና ከመጠን በላይ ሙቀትን ለመከላከል የሞተር ፀረ-በረዶ (anti-ice) ስርዓትን እንደገና ዲዛይን ማድረግ ይገኙበታል። በተጨማሪም የደህንነት ተቆጣጣሪዎች የኩባንያውን የደህንነት አስተዳደር ስርዓት እና አጠቃላይ የደህንነት ባህልን ጨምሮ የአመራረት ሂደቱን ለመከታተል በቦይንግ የማምረቻ ተቋማት ውስጥ በቋሚነት እንደሚቆዩ አስተዳደሩ ገልጿል።
የቦይንግ የንግድ አውሮፕላኖች ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ስቴፋኒ ፖፕ በበኩላቸው፣ የኩባንያው መሃንዲሶች እና የሙከራ ባለሙያዎች ወረርሽኙን እና አዳዲስ የማረጋገጫ ሂደቶችን ጨምሮ በርካታ ተግዳሮቶችን በጽናት ማለፋቸውን ተናግረዋል። ይህ አዲሱ ማክስ 7 አውሮፕላን በዋናነት ለአጭር እና መካከለኛ ርቀት በረራዎች ጥቅም ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ሳውዝ ዌስት ኤርላይንስን ጨምሮ በርካታ አየር መንገዶች ቀደም ብለው ባዘዙት መሰረት አውሮፕላኑን ለመረከብ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የ'ሪያል ማድሪድ ፋውንዴሽን' በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በመላው አፍሪካ ካከናወናቸው ስኬታማ ተግባራት መካከል በኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መክፈቱ በዋና ማሳያነት ተጠቅሷል። ፋውንዴሽኑ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ 52 የማህበራዊ ስፖርት ፕሮጀክቶችን ያካሄደ ሲሆን፣ በዚህም 10,628 የሚሆኑ ህጻናትን፣ ታዳጊዎችን እና ወጣቶችን የዕድሉ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
በዘመኑ ከተመዘገቡት ትልልቅ ስኬቶች አንዱ በሀገራችን ኢትዮጵያ አዲስ የማህበራዊ ስፖርት አካዳሚ መከፈቱ ነው። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም አንጎላ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ሴኔጋል እና ግብጽን ጨምሮ በ23 የአፍሪካ ሀገራት ፕሮጀክቱ ተደራሽ ሆኗል።
በአካታችነት በኩል ፋውንዴሽኑ ሴት ታዳጊዎች በስፖርቱ ያላቸውን ተሳትፎ በማሳደግ እና ሴት አሰልጣኞችን በማበረታታት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቷል። ከዚህም በተጨማሪ አካል ጉዳተኛ ህጻናት፣ ወጣት ስደተኞች እንዲሁም በከባድ ድህነት እና በግጭት የተጎዱ ማህበረሰቦችን የዕድሉ ተጠቃሚ አድርጓል። ከስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ባሻገር ትምህርታዊ ድጋፍን፣ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን፣ የህጻናት ጥበቃን፣ የጾታ እኩልነትን እና ማህበረሰባዊ ትስስርን ማጠናከር የትምህርት ቤቶቹ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው።
የአካባቢውን አሰልጣኞች አቅም በስልጠና፣ በክትትል እና በተሞክሮ ልውውጥ ማሳደግ የፕሮጀክቱ ሌላኛው ስኬት ነው። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የነበሩ ወጣቶች አሁን ላይ ለተተኪው ትውልድ አሰልጣኝ እና አርአያ የሚሆኑበትን ቀጣይነት ያለው ሞዴል ለመፍጠር አስችሏል።
ፋውንዴሽኑ ይህንን ዘላቂ እና አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማምጣት ከተለያዩ ማህበራዊ ተቋማት፣ የኃይማኖት ተቋማት፣ ሌሎች ፋውንዴሽኖች፣ ኩባንያዎች እና የአካባቢው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውቋል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለመደብ መቅረታቸውን ኤስቢኤስ ራድዮ ከአውስትራሊያ ዘግበ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፤ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመረው የንግድ እንቅስቃሴ እንደሚካተቱ ተናግረዋል።
ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ደግሞ ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ እየተከናወነ ነው። በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ መቀሌ እና መሰል ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዎች ማሳያ ይሆናል ተብሏል።
ፎርቹን ጋዜጣ እንደዘገበው ደግሞ ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ እየተከናወነ ነው። በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ መቀሌ እና መሰል ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዎች ማሳያ ይሆናል ተብሏል።
5 days ago
AAU ከ500 በላይ ሰራተኞቹን አሰናበተ‼️
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለ ምደባ ቀርተዋል።
ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፣ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመሩ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል።
ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ ነው።
በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጂማ፣ መቐለ፣ ባህር ዳር እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙሉ የራስ-ገዝነት መብቱን ለመተግበር ባደረገው የመዋቅር ማስተካከያ ምክንያት ከ500 በላይ አስተዳደራዊ ሰራተኞች እና 50 መምህራን ያለ ምደባ ቀርተዋል።
ይሁን እንጂ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ማንም ሰራተኛ እንዳልተባረረ ገልጸው፣ የተጎዱት በጡረታ፣ በካሳ ወይም በቅርቡ በሚጀመሩ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደሚካተቱ አረጋግጠዋል።
ምደባው ለአስተዳደር ሰራተኞች በፈተና፣ ለመምህራን ደግሞ በትምህርት ዝግጅት አግባብነት ላይ ተመስርቶ የተከናወነ ነው።
በሀገሪቱ ከሚገኙ 46 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መካከል የመጀመሪያው ሞዴል የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም እርምጃ፣ ቀጣይ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ ለሚዘጋጁት እንደ ጂማ፣ መቐለ፣ ባህር ዳር እና ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ትልቅ ማሳያ እንደሚሆን ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
ታይላንድን እንዳየኋት፤ የ"Destination" ሳይሆን የ"Experience Economy" አገር
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
8 days ago
ቱርክ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል ገነባች
#ethiopia | የቱርክ ትብብርና ቅንጅት ኤጀንሲ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቡና እና የፍራፍሬ ችግኞችን የሚያፈራ ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል በኢትዮጵያ ገነባ።
ይህ የችግኝ ማዕከል የተገነባው የኢትዮጵያ የፍራፍሬ ልማት ድጋፍ ፕሮጀክት አካል ሲሆን ዓላማውም የአካባቢውን የግብርና አቅም በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን መቋቋም የሚያስችሉ የልማት አሰራሮችን ማስፋፋት ነው።
ይህ ሞዴል የግሪን ሃውስ ማዕከል በየዓመቱ ዘመናዊ የማባዛትና የመቀላቀል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ የተሻሻሉ የቡና፣ የአቮካዶ እና የሌሎች ፍራፍሬዎች ችግኞችን ያመርታል።
ማዕከሉ ከችግኝ ማፍላት ባለፈ የተግባር ስልጠና የሚሰጥበት፣ የግብርና ምርምሮች የሚካሄዱበት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት ዋነኛ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቱርክ ትብብርና ቅንጅት ኤጀንሲ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገሩ ቡና እና የፍራፍሬ ችግኞችን የሚያፈራ ዘመናዊ የችግኝ ማዕከል በኢትዮጵያ ገነባ።
ይህ የችግኝ ማዕከል የተገነባው የኢትዮጵያ የፍራፍሬ ልማት ድጋፍ ፕሮጀክት አካል ሲሆን ዓላማውም የአካባቢውን የግብርና አቅም በማሳደግ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን መቋቋም የሚያስችሉ የልማት አሰራሮችን ማስፋፋት ነው።
ይህ ሞዴል የግሪን ሃውስ ማዕከል በየዓመቱ ዘመናዊ የማባዛትና የመቀላቀል ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ የተሻሻሉ የቡና፣ የአቮካዶ እና የሌሎች ፍራፍሬዎች ችግኞችን ያመርታል።
ማዕከሉ ከችግኝ ማፍላት ባለፈ የተግባር ስልጠና የሚሰጥበት፣ የግብርና ምርምሮች የሚካሄዱበት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት ዋነኛ ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሜታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ማርክ ዙከርበርግ፣ በዓለማችን ከፍተኛ ዋጋ ካላቸው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኩባንያዎች መካከል የሆኑትን አንትሮፒክ እና ኦፕን ኤአይ የኤአይ ቴክኖሎጂን የሚያለሙበትን የተዘጋ መንገድ አጥብቀው ተቹ። ዙከርበርግ ይህ ዓይነቱ አካሄድ ስልጣንና ኃይልን በአንድ ማዕከል እንዲከማች እንደሚያደርግና ሰዎች ከዚህ ለውጥ አምጪ ቴክኖሎጂ የሚያገኙትን ተጠቃሚነት እንደሚያጠብ አስጠንቅቀዋል።
የ42 ዓመቱ ዙከርበርግ ማክሰኞ ዕለት ከኒውዮርክ ታይምስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ የኩባንያዎቹን ስም በቀጥታ ባይጠቅሱም፤ ግንባር ቀደም የጥናት ተቋማት የኤአይ ቴክኖሎጂን በጥብቅ ቁጥጥር ስር ለማልማት የሚያደርጉት ጥረት የአሜሪካን የቴክኖሎጂ እሴቶች ከመተው ጋር እኩል መሆኑንና ፈጠራን እንደሚያዳፍን ገልጸዋል። በዘርፉ "ከመጠን ያለፈ የጥፋት ትርክት" እንደሚስተዋል የገለጹት ዙከርበርግ፣ ለውይይቱ "እውነታን" የሚያመጡ ድምጾች እንደሚያስፈልጉ አሳስበዋል።
በሲሊከን ቫሊ የተፈጠረው የሐሳብ ልዩነት የዙከርበርግ አስተያየት በሲሊከን ቫሊ የቴክኖሎጂ መሪዎች መካከል የተፈጠረውን ክፍፍል ይበልጥ አጉልቶታል። የአንትሮፒክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳሪዮ አሞዴይ እና የኦፕን ኤአይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳም አልትማን የኤአይ ሞዴሎች እጅግ አደገኛ በመሆናቸው ያለ ጥብቅ ቁጥጥር ሊለሙና ሊጋሩ አይገባም የሚል አቋም አላቸው። በሌላ በኩል ማይክሮሶፍት፣ ኤንቪዲያ (Nvidia)፣ ጉግል እና ሜታ ይህንን ሀሳብ በመቃወም፣ ቴክኖሎጂው እንዲያድግ እና አዳዲስ የንግድ ዘርፎች እንዲፈጠሩ አብዛኛዎቹ የኤአይ ሞዴሎች በክፍት መንገድ መለማት አለባቸው ብለው ይከራከራሉ።
የቻይና ስጋት እና የዋሽንግተን ሎቢ በዚህ ወር የቻይና የኤአይ ሞዴሎች ያሳዩት ፈጣን እድገት የአሜሪካ ኩባንያዎች የነበራቸውን ብልጫ እየቀነሰው መምጣቱ ክርክሩን አባብሶታል። አርብ ዕለት የኤንቪዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጄንሰን ሁዋንግ ክፍት የሶፍትዌር ልማትን የሚደግፍ ደብዳቤ ያወጡ ሲሆን፣ ከ SpaceX እና IBM ጋር በመሆን በክፍት የኤአይ ደህንነት ላይ የሚሰራ ጥምረት ማቋቋማቸውን ይፋ አድርገዋል። ሁዋንግ እና አልትማንን ጨምሮ የቴክኖሎጂ መሪዎች ጉዳዩን ከትራምፕ አስተዳደር ጋር ለመወያየት በዚህ ሳምንት ወደ ዋሽንግተን እያቀኑ ይገኛሉ።
"ግላዊ ሱፐር-ኢንተለጀንስ" ከማዕከላዊ ቁጥጥር ይልቅ አንትሮፒክ የኤአይ ሞዴሎች ለሰው ልጅ ደህንነት ስጋት እንዳይሆኑ "የአሰላለፍ አደጋን" ለመፍታት ሲሞክር፤ ዙከርበርግ ግን አንድ ወጥ የሆነ እና ለሁሉም በእኩል የሚስማማ "ደግ" ሱፐር-ኢንተለጀንስ መፍጠር ፈጽሞ የማይቻል መሆኑን ይከራከራሉ። በምትኩ የሰዎችን ግላዊ ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል "ግላዊ ሱፐር-ኢንተለጀንስ" ለሁሉም ሰው መድረስ አለበት ብለዋል።
ለዓመታት የኦፕን ኤአይ አቀንቃኝ የነበረችው እና ሞዴሎቿን በነጻ ስታድል የቆየችው ሜታ፣ በቅርቡ የስትራቴጂ ለውጥ አድርጋለች። በአንትሮፒክ እና ኦፕን ኤአይ ተቀድማ የነበረችው ሜታ፣ 14.3 ቢሊዮን ዶላር ScaleAI በተባለ ኩባንያ ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና መስራቹን አሌክሳንደር ዋንግን በመቅጠር 'Meta Superintelligence Labs'ን አቋቁማለች። ኩባንያው 'Muse Spark' የተሰኘ አዲስ ዝግ (Closed) ሞዴል በማልማት በዚህ ወር መሸጥ መጀመሩም ተገልጿል፤ ምንም እንኳ የክፍት ሞዴል ልማቱን ጎን ለጎን እያስኬደ ቢሆንም።
ዙከርበርግ በዎል ስትሪት ጆርናል ላይ ባወጡት ጽሁፍ የኤአይ ኃይል ማዕከላዊነትን አጥብቀው በመንቀፍ፣ የኢንዱስትሪው ታሪካዊ ጉዞ የቴክኖሎጂን ኃይል በጥቂቶች እጅ ከመሰብሰብ ይልቅ ክፍት በማድረግ ወደ ብዙሃኑ እጅ ማስገባት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቀናቃኞቹ አንትሮፒክ እና ኦፕን ኤአይ በበኩላቸው የኤአይ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ትብብር እንዲኖር የሚጠይቅ ግልጽ ደብዳቤ ከሌሎች ተመራማሪዎች ጋር ፈርመው አውጥተዋል።
የ42 ዓመቱ ዙከርበርግ ማክሰኞ ዕለት ከኒውዮርክ ታይምስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ የኩባንያዎቹን ስም በቀጥታ ባይጠቅሱም፤ ግንባር ቀደም የጥናት ተቋማት የኤአይ ቴክኖሎጂን በጥብቅ ቁጥጥር ስር ለማልማት የሚያደርጉት ጥረት የአሜሪካን የቴክኖሎጂ እሴቶች ከመተው ጋር እኩል መሆኑንና ፈጠራን እንደሚያዳፍን ገልጸዋል። በዘርፉ "ከመጠን ያለፈ የጥፋት ትርክት" እንደሚስተዋል የገለጹት ዙከርበርግ፣ ለውይይቱ "እውነታን" የሚያመጡ ድምጾች እንደሚያስፈልጉ አሳስበዋል።
በሲሊከን ቫሊ የተፈጠረው የሐሳብ ልዩነት የዙከርበርግ አስተያየት በሲሊከን ቫሊ የቴክኖሎጂ መሪዎች መካከል የተፈጠረውን ክፍፍል ይበልጥ አጉልቶታል። የአንትሮፒክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳሪዮ አሞዴይ እና የኦፕን ኤአይ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳም አልትማን የኤአይ ሞዴሎች እጅግ አደገኛ በመሆናቸው ያለ ጥብቅ ቁጥጥር ሊለሙና ሊጋሩ አይገባም የሚል አቋም አላቸው። በሌላ በኩል ማይክሮሶፍት፣ ኤንቪዲያ (Nvidia)፣ ጉግል እና ሜታ ይህንን ሀሳብ በመቃወም፣ ቴክኖሎጂው እንዲያድግ እና አዳዲስ የንግድ ዘርፎች እንዲፈጠሩ አብዛኛዎቹ የኤአይ ሞዴሎች በክፍት መንገድ መለማት አለባቸው ብለው ይከራከራሉ።
የቻይና ስጋት እና የዋሽንግተን ሎቢ በዚህ ወር የቻይና የኤአይ ሞዴሎች ያሳዩት ፈጣን እድገት የአሜሪካ ኩባንያዎች የነበራቸውን ብልጫ እየቀነሰው መምጣቱ ክርክሩን አባብሶታል። አርብ ዕለት የኤንቪዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጄንሰን ሁዋንግ ክፍት የሶፍትዌር ልማትን የሚደግፍ ደብዳቤ ያወጡ ሲሆን፣ ከ SpaceX እና IBM ጋር በመሆን በክፍት የኤአይ ደህንነት ላይ የሚሰራ ጥምረት ማቋቋማቸውን ይፋ አድርገዋል። ሁዋንግ እና አልትማንን ጨምሮ የቴክኖሎጂ መሪዎች ጉዳዩን ከትራምፕ አስተዳደር ጋር ለመወያየት በዚህ ሳምንት ወደ ዋሽንግተን እያቀኑ ይገኛሉ።
"ግላዊ ሱፐር-ኢንተለጀንስ" ከማዕከላዊ ቁጥጥር ይልቅ አንትሮፒክ የኤአይ ሞዴሎች ለሰው ልጅ ደህንነት ስጋት እንዳይሆኑ "የአሰላለፍ አደጋን" ለመፍታት ሲሞክር፤ ዙከርበርግ ግን አንድ ወጥ የሆነ እና ለሁሉም በእኩል የሚስማማ "ደግ" ሱፐር-ኢንተለጀንስ መፍጠር ፈጽሞ የማይቻል መሆኑን ይከራከራሉ። በምትኩ የሰዎችን ግላዊ ፍላጎት ሊያሟላ የሚችል "ግላዊ ሱፐር-ኢንተለጀንስ" ለሁሉም ሰው መድረስ አለበት ብለዋል።
ለዓመታት የኦፕን ኤአይ አቀንቃኝ የነበረችው እና ሞዴሎቿን በነጻ ስታድል የቆየችው ሜታ፣ በቅርቡ የስትራቴጂ ለውጥ አድርጋለች። በአንትሮፒክ እና ኦፕን ኤአይ ተቀድማ የነበረችው ሜታ፣ 14.3 ቢሊዮን ዶላር ScaleAI በተባለ ኩባንያ ላይ ኢንቨስት በማድረግ እና መስራቹን አሌክሳንደር ዋንግን በመቅጠር 'Meta Superintelligence Labs'ን አቋቁማለች። ኩባንያው 'Muse Spark' የተሰኘ አዲስ ዝግ (Closed) ሞዴል በማልማት በዚህ ወር መሸጥ መጀመሩም ተገልጿል፤ ምንም እንኳ የክፍት ሞዴል ልማቱን ጎን ለጎን እያስኬደ ቢሆንም።
ዙከርበርግ በዎል ስትሪት ጆርናል ላይ ባወጡት ጽሁፍ የኤአይ ኃይል ማዕከላዊነትን አጥብቀው በመንቀፍ፣ የኢንዱስትሪው ታሪካዊ ጉዞ የቴክኖሎጂን ኃይል በጥቂቶች እጅ ከመሰብሰብ ይልቅ ክፍት በማድረግ ወደ ብዙሃኑ እጅ ማስገባት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ተቀናቃኞቹ አንትሮፒክ እና ኦፕን ኤአይ በበኩላቸው የኤአይ ልማት ደህንነትን ለማረጋገጥ ዓለም አቀፍ ትብብር እንዲኖር የሚጠይቅ ግልጽ ደብዳቤ ከሌሎች ተመራማሪዎች ጋር ፈርመው አውጥተዋል።
12 days ago
ቱሪዝም፦ የመደመር እሳቤ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ኢኮኖሚ ሞተርነት የለወጠበት ተጨባጭ ማሳያ
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአንድ በኩል የሀገርን ስም በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ ለማድረግ የሚደረግ ብሩህ የደስታ ዝግጅት፤ በሌላ በኩል ደግሞ ድንገት ቤትን የሚያንኳኳ የሞት ጥላ። የ2026ቱ የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊ እና የባህል አምባሳደር የሆነችው ሞዴል ሩት ይርጋለም ቤተሰብ፣ መቼም ቢሆን ጠብቀውት በማያውቁት ጥልቅ የሀዘን ማዕበል ተመተዋል።
ለዘ-ሐበሻ እንደደረሰው መረጃ ከሆነ... የዚህ ልብ ሰባሪ ታሪክ ሰለባ የሆነችው የሩት ታላቅ እህት፣ ወጣት ቅዱሳን ይርጋለም ነች። በመሐል አዲስ አበባ፣ ቤተል አካባቢ በሰላም ትኖርበት ከነበረው ሞቃታማ ቤቷ በተንኮል ተጠርታ ከወጣች በኋላ፣ ዳግም ወደማትመለስበት የጨለማ መንገድ ታፍና ተወሰደች። አጋቾቿ የሰውነትን ክብር እና ርህራሄን ወደ ጎን በመተው፣ የዚችን ወጣት ህይወት በገንዘብ ተመን ቆረጡ፤ ለቤተሰቦቿም የሁለት ሚሊዮን ብር የቤዛ ጥያቄ አቀረቡ። ቤተሰብ በጭንቀትና በስጋት መሃል ሆኖ የሚወዷትን ልጅ ህይወት ለማትረፍ ሲንገዳገድ፣ እነዚያ ጨካኝ አጋቾች ግን አንዳች ርህራሄ በልባቸው አልነበረም። ገንዘቡን ቢጠይቁም፣ ምንም ሳያቅማሙ የቅዱሳንን ለጋ ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ቀጭተውታል።
ይህ መሪር እውነት የተረጋገጠው፣ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ባደረጉት ከፍተኛ እና የተቀናጀ ክትትል፣ ወንጀለኞቹን ከህግ ለማምለጥ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ካዋሏቸው በኋላ ነው። አጋቾቹ በቁጥጥር ስር ውለው በተደረገባቸው ምርመራ፣ ያቺን ንጹህ ነፍስ ያጠፉበትን እና አስክሬኗን የጣሉበትን ስፍራ ለፖሊስ ጠቆሙ። የፖሊስ ቡድንም ወጣቷን በህይወት ለማግኘት የነበረው ተስፋ ተሟጦ፣ በምትኩ በጭካኔ የተገደለውን ቀዝቃዛ አስክሬኗን ሊያገኝ ችሏል።
ለሀገሯ ትልቅ ራዕይ ሰንቃ.. የኢትዮጵያን ቱሪዝምና እሴት ለዓለም ለማስተዋወቅ በዝግጅት ላይ የነበረችው ሩት ይርጋለም፣ ይህ የሞት መርዶ ሲያጋጥማት ሁሉንም ሀገራዊ ተልዕኮዋን እና ህልሟን ወደ ጎን በመተው፣ እያለቀሰች ወደ ቤተሰቧ ጉያ ተመልሳለች። የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አዘጋጅ ኮሚቴም የደረሰውን አሰቃቂ ድርጊት በከፍተኛ ሀዘን በመግለጽ፣ ለሞዴል ሩት፣ ለቤተሰቧና ለወዳጅ ዘመዶቿ ልባዊ መጽናናትን ተመኝቷል፤ ፖሊስ ላደረገው የተቀናጀ ጥረትም ምስጋናውን አቅርቧል።
የወጣት ቅዱሳን ይርጋለም የቀብር ሥነ-ሥርዓት፣ ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ቤተል በሚገኘው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል። ከቤቷ በሰላም ወጥታ በጭካኔ የተገደለችው የቅዱሳን አስክሬን ወደ ቀዝቃዛው መቃብር ሲወርድ፣ የቤ=
ለዘ-ሐበሻ እንደደረሰው መረጃ ከሆነ... የዚህ ልብ ሰባሪ ታሪክ ሰለባ የሆነችው የሩት ታላቅ እህት፣ ወጣት ቅዱሳን ይርጋለም ነች። በመሐል አዲስ አበባ፣ ቤተል አካባቢ በሰላም ትኖርበት ከነበረው ሞቃታማ ቤቷ በተንኮል ተጠርታ ከወጣች በኋላ፣ ዳግም ወደማትመለስበት የጨለማ መንገድ ታፍና ተወሰደች። አጋቾቿ የሰውነትን ክብር እና ርህራሄን ወደ ጎን በመተው፣ የዚችን ወጣት ህይወት በገንዘብ ተመን ቆረጡ፤ ለቤተሰቦቿም የሁለት ሚሊዮን ብር የቤዛ ጥያቄ አቀረቡ። ቤተሰብ በጭንቀትና በስጋት መሃል ሆኖ የሚወዷትን ልጅ ህይወት ለማትረፍ ሲንገዳገድ፣ እነዚያ ጨካኝ አጋቾች ግን አንዳች ርህራሄ በልባቸው አልነበረም። ገንዘቡን ቢጠይቁም፣ ምንም ሳያቅማሙ የቅዱሳንን ለጋ ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ቀጭተውታል።
ይህ መሪር እውነት የተረጋገጠው፣ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ባደረጉት ከፍተኛ እና የተቀናጀ ክትትል፣ ወንጀለኞቹን ከህግ ለማምለጥ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ካዋሏቸው በኋላ ነው። አጋቾቹ በቁጥጥር ስር ውለው በተደረገባቸው ምርመራ፣ ያቺን ንጹህ ነፍስ ያጠፉበትን እና አስክሬኗን የጣሉበትን ስፍራ ለፖሊስ ጠቆሙ። የፖሊስ ቡድንም ወጣቷን በህይወት ለማግኘት የነበረው ተስፋ ተሟጦ፣ በምትኩ በጭካኔ የተገደለውን ቀዝቃዛ አስክሬኗን ሊያገኝ ችሏል።
ለሀገሯ ትልቅ ራዕይ ሰንቃ.. የኢትዮጵያን ቱሪዝምና እሴት ለዓለም ለማስተዋወቅ በዝግጅት ላይ የነበረችው ሩት ይርጋለም፣ ይህ የሞት መርዶ ሲያጋጥማት ሁሉንም ሀገራዊ ተልዕኮዋን እና ህልሟን ወደ ጎን በመተው፣ እያለቀሰች ወደ ቤተሰቧ ጉያ ተመልሳለች። የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አዘጋጅ ኮሚቴም የደረሰውን አሰቃቂ ድርጊት በከፍተኛ ሀዘን በመግለጽ፣ ለሞዴል ሩት፣ ለቤተሰቧና ለወዳጅ ዘመዶቿ ልባዊ መጽናናትን ተመኝቷል፤ ፖሊስ ላደረገው የተቀናጀ ጥረትም ምስጋናውን አቅርቧል።
የወጣት ቅዱሳን ይርጋለም የቀብር ሥነ-ሥርዓት፣ ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ቤተል በሚገኘው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል። ከቤቷ በሰላም ወጥታ በጭካኔ የተገደለችው የቅዱሳን አስክሬን ወደ ቀዝቃዛው መቃብር ሲወርድ፣ የቤ=
20 days ago
#እንድታውቁት
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል።
ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ልጆች ዕድል እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎችም በውድድር ተደራሽ ይሆናል ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመስጠት ያቀደው 5 ኪሎ (በቀድሞው ድህረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) ሲሆን ምዝገባውም ማክሰኞ ሐምሌ 14 - ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።
ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ?
- የመመዝገቢያ ክፍያ 1,000 ብር፤
- የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ እንዲሁም ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት፤
- 2 የወላጅ እና 4 የልጅ ፎቶግራፍ እንዲሁም ወላጆች ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል የሰው ሀብት ቢሮ የተመዝጋቢው ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ፤
- የመመዝገቢያ ክላሰር እና የክፍያ ደረሰኝ
ዩኒቨረሲቲው በማኅበራዊ ሚዲያው ባወጣው መረጃ ወርኃዊ የተማሪዎች ክፍያን አላሳወቀም።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል።
ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ልጆች ዕድል እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎችም በውድድር ተደራሽ ይሆናል ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመስጠት ያቀደው 5 ኪሎ (በቀድሞው ድህረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) ሲሆን ምዝገባውም ማክሰኞ ሐምሌ 14 - ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።
ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ?
- የመመዝገቢያ ክፍያ 1,000 ብር፤
- የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ እንዲሁም ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት፤
- 2 የወላጅ እና 4 የልጅ ፎቶግራፍ እንዲሁም ወላጆች ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል የሰው ሀብት ቢሮ የተመዝጋቢው ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ፤
- የመመዝገቢያ ክላሰር እና የክፍያ ደረሰኝ
ዩኒቨረሲቲው በማኅበራዊ ሚዲያው ባወጣው መረጃ ወርኃዊ የተማሪዎች ክፍያን አላሳወቀም።
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
የታሪክ ስህተቶችን በማረም ለነገይቱ ጠንካራ ኢትዮጵያ መሠረት የሚጥለው ሀገራዊ ምክክር
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
25 days ago
3.69 ቢሊዮን ብር ያባከነው ተቋም‼
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
የፌዴራል ዋና ኦዲተር በ2018-2025 እ.ኤ.አ በመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ስር በተከናወኑት የዌልመል እና የጨልጨል የመስኖ ፕሮጀክቶች ላይ ባካሄደው የክዋኔ ኦዲት፣ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ ብክነትና የውል ጥሰት መፈጸሙን ይፋ አደረገ።
ዋና ዋና የኦዲት ግኝቶች፦
📌የገንዘብ ብክነት፦ "የዋጋ ማስተካከያ አይፈቀድም" የሚለው የውል ድንጋጌ ተጥሶ በተደረጉ ማሻሻያዎች 3.69 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ህገ-ወጥ ተጨማሪ ወጪ ተደርጓል።
📌የቅንጡ መኪናዎች ግዢ፦ በጨልጨል ፕሮጀክት ውስጥ በውል ያልተካተቱ፣ ከ132 ሚሊዮን ብር በላይ የፈጁ የ2023 ሞዴል ቅንጡ ተሽከርካሪዎች (V6 እና Toyota Prado) ተገዝተው በተቋራጩ እጅ እንዲገቡ ተደርጓል።
📌የሰነድ ማጭበርበር፦ የ75 ሚሊዮን ብር የመስክ ተሽከርካሪዎች ግዢ የተጠናቀቀ ግንባታ ተደርጎ በተጭበረበረ ጊዜያዊ የክፍያ ማረጋገጫ ተፈጽሟል።
📌 ከፍተኛ መዘግየት፦ ፕሮጀክቶቹ ያለ አዋጭነት ጥናት በመጀመራቸውና በደካማ ክትትል ምክንያት ከ38 ወራት በላይ የዘገዩ ቢሆንም፣ በሚኒስቴሩ በኩል ምንም ዓይነት የመዘግየት ቅጣት አልተጣለም።
👉👉ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የተሰጡትን የማስተካከያ ምክረ-ሃሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ ካላደረገ፣ ጉዳዩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የሕግና የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ዋና ኦዲተሩ ማስጠንቀቁን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
28 days ago
ከ7.6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የሻማ ጦንጊ ቀበሌ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት በይፋ ተመረቀ
በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ሻማ ጦንጊ ቀበሌ ከ7.6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተገነባው ዘመናዊ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት፣ በክልል፣ በዞንና በወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ህፃናት ከመሠረቱ ጀምሮ በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነ-ምግባር የታነፁ ዜጎች እንዲሆኑ በማለም፣ በክልሉ ርዕስ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት፣ በማረቃ ወረዳ መንግስት፣ በጌንዶ ማዘጋጃ ቤት፣ በትምህርት ተቋማት እና በአካባቢው ህብረተሰብ የጋራ ትብብርና ንቁ ተሳትፎ የተገነባ ነው።
የተገነባው ይህ ዘመናዊ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ለህፃናት ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የመማሪያ አካባቢ በመፍጠር፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ተደራሽነትና ጥራት በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል::
ዘገባው የማረቃ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው
በዳውሮ ዞን ማረቃ ወረዳ ሻማ ጦንጊ ቀበሌ ከ7.6 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተገነባው ዘመናዊ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት፣ በክልል፣ በዞንና በወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ህፃናት ከመሠረቱ ጀምሮ በዕውቀት፣ በክህሎትና በሥነ-ምግባር የታነፁ ዜጎች እንዲሆኑ በማለም፣ በክልሉ ርዕስ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ኢኒሼቲቭ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት፣ በማረቃ ወረዳ መንግስት፣ በጌንዶ ማዘጋጃ ቤት፣ በትምህርት ተቋማት እና በአካባቢው ህብረተሰብ የጋራ ትብብርና ንቁ ተሳትፎ የተገነባ ነው።
የተገነባው ይህ ዘመናዊ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ትምህርት ቤት ለህፃናት ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የመማሪያ አካባቢ በመፍጠር፣ የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ተደራሽነትና ጥራት በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል::
ዘገባው የማረቃ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው
28 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በታይላንድ ባንኮክ በተካሄደው ታላቅ የውበትና የሞዴሊንግ ውድድር ላይ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ የተሳተፈችው ሞዴል ሩት ሸዋታጠቅ የ"Miss Classy Model Earth 2026" አሸናፊ በመሆን አኩሪ ስኬት አስመዝግባለች።
ይህ ስኬት ለሩት የመጀመሪያዋ አይደለም። ከዚህ ቀደም የ"Miss Popularity" አሸናፊ መሆን የቻለች ሲሆን፣ በ"Miss International Ethiopia" እና በ"Miss ውበት Ethiopia" የውበት ውድድሮች ላይም ተሳትፋ የክብር ዘውድ ለመድፋት በቅታለች።
ሩት ሸዋታጠቅ ለስኬቶቿ ሁሉ መሠረት የሆኑትን ሁለገብ ስብዕናዎቿን ስታብራራ፣ በፈጣሪ ላይ ያላት ጠንካራ እምነት፣ በታዋቂው የናዝሬት ትምህርት ቤት ያሳለፈችው የትምህርት ቆይታ፣ በልጅነቷ በጀርመን ሀገር መኖሯ፣ እንዲሁም ሁለቱም ዶክተር ከሆኑት እናት እና አባቷ ያገኘችው አስተዳደግና ድጋፍ ለዛሬ ማንነቷ መገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ለዘ-ሐበሻ ገልጻለች።
ከተሳካው የሞዴሊንግ ህይወቷ ባሻገር በትምህርቷ እጅግ አስደናቂ ውጤት ያላት ሩት፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርቷን በማዕረግ ያጠናቀቀች ሲሆን፣ በሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ላይም ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የህግ ዲግሪ ባለቤት መሆን ችላለች። አሁን ላይም የህክምና ባለሙያ የሆነውን የአባቷን ፈለግ በመከተል በህክምና ትምህርት ዘርፍ የ"C2" ተማሪ ሆና ትምህርቷን እየተከታተለች ትገኛለች። በቆይታዋም የህክምና ተማሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን በምርጫ ተሰይማ በተሳካ ሁኔታ አገልግላለች።
ከእነዚህ ሙያዎቿ በተጨማሪ በስነ-ጥበብ ዘርፍ የዘፈንና የቅኔ (ግጥም) ተሰጥኦ ያላት ሲሆን፣ በተለይም በማህበራዊ ኃላፊነት ላይ በንቃት እየተሳተፈች ትገኛለች። ሩት "Ruth Drops" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ተቋም በመመስረት በርካታ የህክምና እና ማህበራዊ ድጋፎችን ለህብረተሰቡ እያበረከተች ሲሆን፣ ከተግባራቶቿም መካከል በተስፋ አዲስ የካንሰር ማዕከል፣ በብሔራዊ የደም ባንክ እና በተለያዩ ሆስፒታሎች የሚገኙ ህሙማንን በቁርጠኝነት መርዳቷ በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
እንኳን ደስ ያለሽ፣ ሩት!
ይህ ስኬት ለሩት የመጀመሪያዋ አይደለም። ከዚህ ቀደም የ"Miss Popularity" አሸናፊ መሆን የቻለች ሲሆን፣ በ"Miss International Ethiopia" እና በ"Miss ውበት Ethiopia" የውበት ውድድሮች ላይም ተሳትፋ የክብር ዘውድ ለመድፋት በቅታለች።
ሩት ሸዋታጠቅ ለስኬቶቿ ሁሉ መሠረት የሆኑትን ሁለገብ ስብዕናዎቿን ስታብራራ፣ በፈጣሪ ላይ ያላት ጠንካራ እምነት፣ በታዋቂው የናዝሬት ትምህርት ቤት ያሳለፈችው የትምህርት ቆይታ፣ በልጅነቷ በጀርመን ሀገር መኖሯ፣ እንዲሁም ሁለቱም ዶክተር ከሆኑት እናት እና አባቷ ያገኘችው አስተዳደግና ድጋፍ ለዛሬ ማንነቷ መገንባት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ለዘ-ሐበሻ ገልጻለች።
ከተሳካው የሞዴሊንግ ህይወቷ ባሻገር በትምህርቷ እጅግ አስደናቂ ውጤት ያላት ሩት፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርቷን በማዕረግ ያጠናቀቀች ሲሆን፣ በሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ላይም ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የህግ ዲግሪ ባለቤት መሆን ችላለች። አሁን ላይም የህክምና ባለሙያ የሆነውን የአባቷን ፈለግ በመከተል በህክምና ትምህርት ዘርፍ የ"C2" ተማሪ ሆና ትምህርቷን እየተከታተለች ትገኛለች። በቆይታዋም የህክምና ተማሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን በምርጫ ተሰይማ በተሳካ ሁኔታ አገልግላለች።
ከእነዚህ ሙያዎቿ በተጨማሪ በስነ-ጥበብ ዘርፍ የዘፈንና የቅኔ (ግጥም) ተሰጥኦ ያላት ሲሆን፣ በተለይም በማህበራዊ ኃላፊነት ላይ በንቃት እየተሳተፈች ትገኛለች። ሩት "Ruth Drops" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ተቋም በመመስረት በርካታ የህክምና እና ማህበራዊ ድጋፎችን ለህብረተሰቡ እያበረከተች ሲሆን፣ ከተግባራቶቿም መካከል በተስፋ አዲስ የካንሰር ማዕከል፣ በብሔራዊ የደም ባንክ እና በተለያዩ ሆስፒታሎች የሚገኙ ህሙማንን በቁርጠኝነት መርዳቷ በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው።
እንኳን ደስ ያለሽ፣ ሩት!
Sponsored by
Surafel
29 days ago
የኢትዮጵያው የቴክኖሎጂ ስታርትአፕ ከአፍሪካ ምርጥ 15 ውስጥ ተካተተ
#ethiopia | በአለማየሁ ሰይፉ የተመሠረተውና በኢንተርፕራይዝ ሶፍትዌር መፍትሔዎች ላይ የሚሠራው ማራኪሶፍት (Marakisoft) የተባለው የኢትዮጵያ ስታርትአፕ፣ በመላው አፍሪካ ከ500 በላይ አመልካቾች መካከል ተመርጦ በአህጉሪቱ ምርጥ 15 ስታርትአፖች ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ተገለጸ።
ምርጫውን ያካሄደው ፓን-አፍሪካዊው የኢንቨስትመንት ተቋም ሪኒው ካፒታል (Renew Capital) ሲሆን፣ በመጀመሪያው "Renew Venture Lab" መርሃ ግብር ከ48 የአፍሪካ አገራት የቀረቡ ኩባንያዎችን አወዳድሯል። ከእነዚህም 47 ኩባንያዎች ለፒች (Pitch) ውድድር ከተመረጡ በኋላ፣ 10 አገራትን የሚወክሉ 15 ስታርትአፖች ለላቀ ቴክኒካዊ ስልጠናና ለቀጣይ የኢንቨስትመንት ግምገማ ተመርጠዋል።
ውድድሩ በEmbedded Finance ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ይህም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እንደ ብድር፣ ኢንሹራንስ እና የክፍያ አገልግሎቶችን በቀጥታ በራሳቸው ዲጂታል መድረኮች ላይ በማቀናጀት ለአነስተኛና መካከለኛ ንግዶች እንዲደርሱ የሚያስችል የፋይናንስ ሞዴል ነው።
ሪኒው ካፒታል እንደገለጸው፣ የአፍሪካ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በየዓመቱ 330 ቢሊዮን ዶላር የብድር ክፍተት ያጋጥማቸዋል። እንደ ማራኪሶፍት ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የደንበኞቻቸውን የንግድ መረጃ በመጠቀም ይህንን የፋይናንስ ክፍተት ለመቀነስ አስፈላጊ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉም አመልክቷል።
ማራኪሶፍት በ17 ዓመታት የሥራ ልምዱ ከ5,000 በላይ ደንበኞችን በማገልገል፣ የERP እና POS ሶፍትዌር መፍትሔዎችን በኢትዮጵያ በማልማት የሚታወቅ ኩባንያ ነው።
በመጨረሻ ዙር የደረሱት 47 ስታርትአፖች እያንዳንዳቸው ከ250,000 ዶላር በላይ ዋጋ ያለውን የድጋፍ ፓኬጅና የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ምክር ያገኙ ሲሆን፣ አሁን በምርጥ 15 ውስጥ የተካተቱት ኩባንያዎች ለቀጣይ የፋይናንስ ኢንቨስትመንት ምዘና ሂደት ላይ ይገኛሉ።
EBR
#ethiopiantech #marakisoft #renewcapital #embeddedfinance #startupethiopia #africatech #smes #getutemesgen
#ethiopia | በአለማየሁ ሰይፉ የተመሠረተውና በኢንተርፕራይዝ ሶፍትዌር መፍትሔዎች ላይ የሚሠራው ማራኪሶፍት (Marakisoft) የተባለው የኢትዮጵያ ስታርትአፕ፣ በመላው አፍሪካ ከ500 በላይ አመልካቾች መካከል ተመርጦ በአህጉሪቱ ምርጥ 15 ስታርትአፖች ዝርዝር ውስጥ መካተቱ ተገለጸ።
ምርጫውን ያካሄደው ፓን-አፍሪካዊው የኢንቨስትመንት ተቋም ሪኒው ካፒታል (Renew Capital) ሲሆን፣ በመጀመሪያው "Renew Venture Lab" መርሃ ግብር ከ48 የአፍሪካ አገራት የቀረቡ ኩባንያዎችን አወዳድሯል። ከእነዚህም 47 ኩባንያዎች ለፒች (Pitch) ውድድር ከተመረጡ በኋላ፣ 10 አገራትን የሚወክሉ 15 ስታርትአፖች ለላቀ ቴክኒካዊ ስልጠናና ለቀጣይ የኢንቨስትመንት ግምገማ ተመርጠዋል።
ውድድሩ በEmbedded Finance ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ይህም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እንደ ብድር፣ ኢንሹራንስ እና የክፍያ አገልግሎቶችን በቀጥታ በራሳቸው ዲጂታል መድረኮች ላይ በማቀናጀት ለአነስተኛና መካከለኛ ንግዶች እንዲደርሱ የሚያስችል የፋይናንስ ሞዴል ነው።
ሪኒው ካፒታል እንደገለጸው፣ የአፍሪካ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በየዓመቱ 330 ቢሊዮን ዶላር የብድር ክፍተት ያጋጥማቸዋል። እንደ ማራኪሶፍት ያሉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የደንበኞቻቸውን የንግድ መረጃ በመጠቀም ይህንን የፋይናንስ ክፍተት ለመቀነስ አስፈላጊ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉም አመልክቷል።
ማራኪሶፍት በ17 ዓመታት የሥራ ልምዱ ከ5,000 በላይ ደንበኞችን በማገልገል፣ የERP እና POS ሶፍትዌር መፍትሔዎችን በኢትዮጵያ በማልማት የሚታወቅ ኩባንያ ነው።
በመጨረሻ ዙር የደረሱት 47 ስታርትአፖች እያንዳንዳቸው ከ250,000 ዶላር በላይ ዋጋ ያለውን የድጋፍ ፓኬጅና የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ምክር ያገኙ ሲሆን፣ አሁን በምርጥ 15 ውስጥ የተካተቱት ኩባንያዎች ለቀጣይ የፋይናንስ ኢንቨስትመንት ምዘና ሂደት ላይ ይገኛሉ።
EBR
#ethiopiantech #marakisoft #renewcapital #embeddedfinance #startupethiopia #africatech #smes #getutemesgen
29 days ago
ትውልድን ከመሠረት ማነጽ፦ በመዋቅራዊ ሽግግር ላይ የሚገኘው የሀገራችን የትምህርት ዘርፍ
***********************
በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ማደጉ በራሱ ትልቅ ስኬት ቢሆንም፣ የትምህርት መሠረት በሆነው የመጀመሪያ ደረጃ ጥራት ላይ ትልቅ ክፍተት እንደነበር ይታወቃል።
የቀድሞው የትምህርት ሥርዓት ትኩረት በዋናነት በየክልሉ ዩኒቨርሲቲዎችን ማስፋፋት እና የተመራቂዎችን ቁጥር ማብዛት ነበር።
ከመሠረቱ በትኩረት ያልተሠራባቸውን ተማሪዎች አስመርቆ ማውጣቱ ለትምህርት ጥራቱ ማሽቆልቆል ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርላማ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ንግግሮች እና በተግባር ባካሄዷቸው ንቅናቄዎች፣ “ከላይ ወደ ታች” የነበረውን የተዛባ አካሄድ በመቀየር “ከታች ወደ ላይ” የሆነ ስትራቴጂ መከተላቸውን አመልክተዋል።
ከለውጡ ወዲህ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችም ይህንኑ የትምህርት ጥራት ችግር ከመሠረቱ ለመፍታት ያለሙ ናቸው።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአፀደ ሕፃናት ትኩረት የሰጡ የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች እና ማዕከላት በስፋት መገንባት ነው።
ቀደም ሲል የቅድመ-መደበኛ ትምህርት የግል ትምህርት ቤቶች ብቻ የሚያከናውኑት ተግባር አድርጎ ይመለከት የነበረውን የተዛባ አተያይ በመስበር ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረጉ መዋዕለ ሕፃናት በስፋት ተገንብተዋል።
በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአፀደ ሕፃናት ክፍሎች በነፃ እንዲካተቱ መደረጉ፣ ማኅበረሰቡ ልጆቹን ያለምንም ክፍያ እንዲያስተምር ሰፊ ዕድል ፈጥሯል።
በዚሁ መሠረት ባለፉት 7 ዓመታት ብቻ ከ35 ሺህ በላይ መዋዕለ ሕፃናትን መገንባት ተችሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ፣ “እነዚህ ሕፃናት ከ20 ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕልውና መሆናቸውን ስለምናውቅ ነው ከመሠረቱ የምንሠራው” ማለታቸው የተደረገውን መሠረታዊ ለውጥ ያመላክታል።
የትምህርት ቤት ምገባ ለትምህርት ጥራት ያለውን ጉልህ ፋይዳ ታሳቢ በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትን የመርሐ ግብሩ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
ይህ ስትራቴጂ ሕፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲቆዩ፣ መጠነ ማቋረጥ እንዲቀንስ እንዲሁም በአካልም በአእምሮም ጤናማ ሆነው እንዲያድጉ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
ከሥር በአግባቡ ተኮትኩተው የመጡ ተማሪዎች ትክክለኛ እና በቂ ዕውቀት የሚያገኙበትን ተቋም በማዘጋጀት በኩልም መንግሥት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።
የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከመደመር መጽሐፍ ሽያጭ እና መሰል ገቢ ማሰባሰቢያ ኢኒሼቲቮች በተገኘ በጀት በሁሉም ክልሎች 35 የሁለተኛ ደረጃ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ገንብቷል።
ከዚህ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በየአካባቢው እየተገነቡ ይገኛሉ። ደረጃቸውን የጠበቁ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት ላይም በትኩረት እየተሠራ ነው።
መንግሥት ከመሠረቱ የጀመረውን ይህን የትምህርት ጥራትን የማሻሻል ሥራ ሀገር አቀፍ የጥራት መለኪያ ሥርዓት በማውጣት ጭምር እየተከታተለው ይገኛል።
ተግባራዊ የተደረገው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) እንዲሁም በ8ኛ ክፍል ክልላዊ እና በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናዎች አሰጣጥ የተዘረጋው ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓት የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ሥራው አካል ነው።
በአንድ ሀገር የትምህርት ጥራት የሚለካው በዩኒቨርሲቲዎች ብዛት ወይም ከተቋማቱ በሚወጡ ተመራቂዎች ቁጥር ብቻ ሳይሆን፣ ተማሪዎቹ ከመነሻው በሚቀስሙት ዕውቀት እና ክህሎት እንዲሁም በተግባር በሚያሳዩት ብቃት ነው።
ሀገራችንም “ከታች ወደ ላይ” ስትራቴጂዋን በመከተል የትምህርት ተደራሽነትን ከጥራት ጋር ለማስማማት እያደረገችው ያለው ጥረት እጅግ ተስፋ ሰጪ ነው።
አፀደ ሕፃናትን ከማስፋፋት ጀምሮ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር፣ ጥብቅ የምዘና ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም በርካታ ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶችን መገንባት የነገውን ጠንካራ ትውልድ በቅድሚያ የማነጽ ሥራ ነው።
በጥቅሉ ኢትዮጵያ የመጻኢው የቴክኖሎጂ ዓለም ዋና ተዋናይ እንድትሆን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲን (AI University) ጨምሮ የነገውን ትውልድ የሚያንጹ ተግባራትን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ትውልድን የመገንባት ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ ጉዞ ሀገራችን ለወደፊት ሕልውናዋ እና ዘላቂ ዕድገቷ ያዋለችው ትልቁ እና አስተማማኙ ኢንቨስትመንት ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
በንፍታሌም እንግዳወርቅ
#ethiopia #education #reform #quality #ebc
***********************
በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ማደጉ በራሱ ትልቅ ስኬት ቢሆንም፣ የትምህርት መሠረት በሆነው የመጀመሪያ ደረጃ ጥራት ላይ ትልቅ ክፍተት እንደነበር ይታወቃል።
የቀድሞው የትምህርት ሥርዓት ትኩረት በዋናነት በየክልሉ ዩኒቨርሲቲዎችን ማስፋፋት እና የተመራቂዎችን ቁጥር ማብዛት ነበር።
ከመሠረቱ በትኩረት ያልተሠራባቸውን ተማሪዎች አስመርቆ ማውጣቱ ለትምህርት ጥራቱ ማሽቆልቆል ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በፓርላማ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ንግግሮች እና በተግባር ባካሄዷቸው ንቅናቄዎች፣ “ከላይ ወደ ታች” የነበረውን የተዛባ አካሄድ በመቀየር “ከታች ወደ ላይ” የሆነ ስትራቴጂ መከተላቸውን አመልክተዋል።
ከለውጡ ወዲህ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችም ይህንኑ የትምህርት ጥራት ችግር ከመሠረቱ ለመፍታት ያለሙ ናቸው።
ባለፉት የለውጥ ዓመታት የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል ከተከናወኑ ሥራዎች መካከል በሀገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአፀደ ሕፃናት ትኩረት የሰጡ የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ቤቶች እና ማዕከላት በስፋት መገንባት ነው።
ቀደም ሲል የቅድመ-መደበኛ ትምህርት የግል ትምህርት ቤቶች ብቻ የሚያከናውኑት ተግባር አድርጎ ይመለከት የነበረውን የተዛባ አተያይ በመስበር ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች ታሳቢ ያደረጉ መዋዕለ ሕፃናት በስፋት ተገንብተዋል።
በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአፀደ ሕፃናት ክፍሎች በነፃ እንዲካተቱ መደረጉ፣ ማኅበረሰቡ ልጆቹን ያለምንም ክፍያ እንዲያስተምር ሰፊ ዕድል ፈጥሯል።
በዚሁ መሠረት ባለፉት 7 ዓመታት ብቻ ከ35 ሺህ በላይ መዋዕለ ሕፃናትን መገንባት ተችሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ማብራሪያ፣ “እነዚህ ሕፃናት ከ20 ዓመት በኋላ የኢትዮጵያ ሕልውና መሆናቸውን ስለምናውቅ ነው ከመሠረቱ የምንሠራው” ማለታቸው የተደረገውን መሠረታዊ ለውጥ ያመላክታል።
የትምህርት ቤት ምገባ ለትምህርት ጥራት ያለውን ጉልህ ፋይዳ ታሳቢ በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕፃናትን የመርሐ ግብሩ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
ይህ ስትራቴጂ ሕፃናት በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዲቆዩ፣ መጠነ ማቋረጥ እንዲቀንስ እንዲሁም በአካልም በአእምሮም ጤናማ ሆነው እንዲያድጉ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
ከሥር በአግባቡ ተኮትኩተው የመጡ ተማሪዎች ትክክለኛ እና በቂ ዕውቀት የሚያገኙበትን ተቋም በማዘጋጀት በኩልም መንግሥት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።
የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከመደመር መጽሐፍ ሽያጭ እና መሰል ገቢ ማሰባሰቢያ ኢኒሼቲቮች በተገኘ በጀት በሁሉም ክልሎች 35 የሁለተኛ ደረጃ ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ገንብቷል።
ከዚህ በተጨማሪ በአሁኑ ወቅት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በየአካባቢው እየተገነቡ ይገኛሉ። ደረጃቸውን የጠበቁ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን መገንባት ላይም በትኩረት እየተሠራ ነው።
መንግሥት ከመሠረቱ የጀመረውን ይህን የትምህርት ጥራትን የማሻሻል ሥራ ሀገር አቀፍ የጥራት መለኪያ ሥርዓት በማውጣት ጭምር እየተከታተለው ይገኛል።
ተግባራዊ የተደረገው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና (Exit Exam) እንዲሁም በ8ኛ ክፍል ክልላዊ እና በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናዎች አሰጣጥ የተዘረጋው ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓት የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ሥራው አካል ነው።
በአንድ ሀገር የትምህርት ጥራት የሚለካው በዩኒቨርሲቲዎች ብዛት ወይም ከተቋማቱ በሚወጡ ተመራቂዎች ቁጥር ብቻ ሳይሆን፣ ተማሪዎቹ ከመነሻው በሚቀስሙት ዕውቀት እና ክህሎት እንዲሁም በተግባር በሚያሳዩት ብቃት ነው።
ሀገራችንም “ከታች ወደ ላይ” ስትራቴጂዋን በመከተል የትምህርት ተደራሽነትን ከጥራት ጋር ለማስማማት እያደረገችው ያለው ጥረት እጅግ ተስፋ ሰጪ ነው።
አፀደ ሕፃናትን ከማስፋፋት ጀምሮ የትምህርት ቤት ምገባ ፕሮግራምን ማጠናከር፣ ጥብቅ የምዘና ሥርዓት መዘርጋት እንዲሁም በርካታ ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶችን መገንባት የነገውን ጠንካራ ትውልድ በቅድሚያ የማነጽ ሥራ ነው።
በጥቅሉ ኢትዮጵያ የመጻኢው የቴክኖሎጂ ዓለም ዋና ተዋናይ እንድትሆን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲን (AI University) ጨምሮ የነገውን ትውልድ የሚያንጹ ተግባራትን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ትውልድን የመገንባት ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ ጉዞ ሀገራችን ለወደፊት ሕልውናዋ እና ዘላቂ ዕድገቷ ያዋለችው ትልቁ እና አስተማማኙ ኢንቨስትመንት ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
በንፍታሌም እንግዳወርቅ
#ethiopia #education #reform #quality #ebc
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በታይላንድ ዋና ከተማ ባንኮክ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሞዴሊንግ ውድድር (Mister Classy Model International) ላይ የተካፈለው ኢትዮጵያዊው ሞዴል ዘላለም ተድላ መስፍን በቅጽል ስሙ ሞዴል ዞላ አሸናፊ በመሆን የሀገሩን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጓል።
ወጣቱ ሞዴል በዚህ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ አምስት የተለያዩ ዘርፎችን በበላይነት አጠናቋል። ባሸነፈባቸው ዘርፎችም የዓመቱ ሞዴል አሸናፊ፣ የምርጥ አረማመድ አሸናፊ፣ የእጅግ አስተዋይ ተወዳዳሪ አሸናፊ፣ የምርጥ መደበኛ አለባበስ አሸናፊ እንዲሁም የውድድሩ የሶስተኛ ደረጃ (3rd Runner Up) አሸናፊ በመሆን ዋንጫዎችን ጠቅልሏል። የውድድሩን ርዕሶች እና አጠራሮች ሙሉ በሙሉ ወደ አማርኛ ለመመለስ አስቸጋሪ ቢሆንም፣ ሞዴሉ በሁሉም የውድድሩ መመዘኛዎች ብልጫ ወስዷል።
1. CLASSY MODEL EARTH WINNER
2. BEST CATWALK WINNER
3. MOST INTELLIGENT WINNER
4. BEST IN FORMAL WEAR WINNER
5. 3RD RUNNER UP
ይህ ተደጋጋሚ ድል ለወጣቱ ሞዴል የመጀመሪያው አይደለም። ከአንድ ወር በፊት በኢንዶኔዥያ ጃካርታ በተካሄደው ሌላ ዓለም አቀፍ የባህል ሞዴሊንግ ውድድር ላይ ተሳትፎ በተመሳሳይ አራት የተለያዩ ሽልማቶችን ይዞ መመለሱ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በተከታታይ እና በተደራራቢ ውጤት በማስመዝገብ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ወንድ ሞዴል ለመሆን በቅቷል። ይህን ታላቅ ድል ያስመዘገበው ሞዴል ዘላለም ተድላ፣ የፊታችን አርብ ጠዋት 2፡00 ሰዓት ላይ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ ይጠበቃል።
ወጣቱ ሞዴል በዚህ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ አምስት የተለያዩ ዘርፎችን በበላይነት አጠናቋል። ባሸነፈባቸው ዘርፎችም የዓመቱ ሞዴል አሸናፊ፣ የምርጥ አረማመድ አሸናፊ፣ የእጅግ አስተዋይ ተወዳዳሪ አሸናፊ፣ የምርጥ መደበኛ አለባበስ አሸናፊ እንዲሁም የውድድሩ የሶስተኛ ደረጃ (3rd Runner Up) አሸናፊ በመሆን ዋንጫዎችን ጠቅልሏል። የውድድሩን ርዕሶች እና አጠራሮች ሙሉ በሙሉ ወደ አማርኛ ለመመለስ አስቸጋሪ ቢሆንም፣ ሞዴሉ በሁሉም የውድድሩ መመዘኛዎች ብልጫ ወስዷል።
1. CLASSY MODEL EARTH WINNER
2. BEST CATWALK WINNER
3. MOST INTELLIGENT WINNER
4. BEST IN FORMAL WEAR WINNER
5. 3RD RUNNER UP
ይህ ተደጋጋሚ ድል ለወጣቱ ሞዴል የመጀመሪያው አይደለም። ከአንድ ወር በፊት በኢንዶኔዥያ ጃካርታ በተካሄደው ሌላ ዓለም አቀፍ የባህል ሞዴሊንግ ውድድር ላይ ተሳትፎ በተመሳሳይ አራት የተለያዩ ሽልማቶችን ይዞ መመለሱ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በተከታታይ እና በተደራራቢ ውጤት በማስመዝገብ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ወንድ ሞዴል ለመሆን በቅቷል። ይህን ታላቅ ድል ያስመዘገበው ሞዴል ዘላለም ተድላ፣ የፊታችን አርብ ጠዋት 2፡00 ሰዓት ላይ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ ይጠበቃል።
1 month ago
ተግባራዊ ቅቡልነት፦ በቃላት ሳይሆን በውጤት የሚለካው አዲሱ የሀገር ግንባታ
*****************************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለዘመናት በማይፈጸሙ የተስፋ ቃላት እና በብሔር ማንነት አጀንዳ ሲታመስ ቆይቷል። አሁን ግን ሀገራችን ከዚህ የቃላት እና የተስፋ ፖለቲካ ወጥታ የመንግሥት ቅቡልነት በሚያወራው ሳይሆን በተግባር በሚሠራው ሥራ እና በሚያመጣው ተጨባጭ ውጤት ወደሚሆንበት አዲስ አሠራር እየተሸጋገረች ነው።
ይህ አሠራር በሚመጡ ተጨባጭ ለውጦች ለመለካት የሚሻ አዲስ የሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በአጽንዖት እንደገለጹት፣ የሀገራችን አዲሱ የታሪክ ምዕራፍ በተስፋ ቃላት ላይ ሳይሆን በተግባራዊ ክንውን እና በጥራት ላይ የተመሠረተ ነው።
ይህ "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው መርሕ ከተራ መፈክር በላይ በመሆን፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ያላትን የማስፈጸም አቅም እና የሥልጣኔ ልክ የምታሳይበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኗል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን እየታዩ ያሉ ስኬቶች መንግሥት ውጤት የማምጣት አቅሙን በተግባር ያረጋገጠባቸው ማሳያዎች ናቸው።
ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከማጠናቀቅ እና ኃይል ማመንጨት ጀምሮ፣ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው የስንዴ ኤክስፖርት እና የመስኖ ልማት ስኬት፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የክልል ከተሞችን ገጽታ የቀየሩት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዚሁ ተግባራዊ ሕጋዊነት ውጤቶች ናቸው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እና የኢትዮጵያ ታምርት የኢንዱስትሪ ንቅናቄም ሀገራችን ትላልቅ ዕቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም እንዳላት በተጨባጭ እያሳዩ ነው።
ዋናው ማዕቀፍ ግን የእነዚህ ፕሮጀክቶች መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ጥቅሞቻቸው በሁሉም ክልሎች፣ ማንነቶች እና የፖለቲካ አመለካከቶች ውስጥ እኩል ሊሰርጹ መቻላቸው ላይ ነው። መንገዶች፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ልማታዊ ውጤቶች ብቻ ሳይሆኑ፣ የፌዴራል ሥርዓቱን ልዩነቶች አቀናጅተው የጋራ ብሔራዊ ልምድን የሚፈጥሩ ሥልታዊ ድልድዮች ናቸው።
ይህ አካሄድ ቀደም ሲል ከነበረው እና ሥልጣኑን በረጅም ጊዜ ተስፋዎች ላይ ብቻ ይመሠርት ከነበረው "ልማታዊ መንግሥት" አስተሳሰብ በእጅጉ የላቀ ነው።
የአሁኑ የመፈጸም ሞዴል ሊለኩ በሚችሉ ውጤቶች፣ በትግበራ ፍጥነት እና በተቋማዊ ብቃት ላይ የተመሠረተ ነው። የሲንጋፖር፣ የቪየትናም እና የማሌዢያ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ውል የሚገነባው እና ቢሮክራሲው የሚቀናጀው በተግባር በሚታይ የድህነት ቅነሳ እና የዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻል ላይ ነው።
መንግሥት ለኢኮኖሚ ችግሮች የሚሰጠው መፍትሔ በርዕዮተ ዓለም የታጠረ ሳይሆን፣ በተግባር በሚታይ ውጤት ላይ የተመሠረተ ገቢር ነበብ የኢኮኖሚ ፍልስፍና ነው።
ከለውጡ በፊት ኢኮኖሚው በከፍተኛ ዕዳ ተሸብቦ እና በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ተፈትኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ይህን የውድቀት ታሪክ መቀየር ተችሏል።
"ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያ በችግሮቿ እንጂ በእምቅ አቅሟ ስትገለጽ አልኖረችም፤ ዛሬ ግን የተለየ ታሪክ ብቅ እያለ ነው" ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገራችንን አዲስ ምዕራፍ ያበሰሩት።
ይህ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የሚለው መንፈስ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ መስክም በጉልህ እየታየ ይገኛል። በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አማካኝነት የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ማቅረብ፣ የ“መሶብ” የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መተግበሪያን መዘርጋት እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ሥልጠና ንቅናቄን መተግበር ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ እና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት እያሸጋገሯት ነው።
እነዚህ የዲጂታል መሠረቶች የቢሮክራሲውን ቅልጥፍና ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ፍጹም ዘመናዊ እና ግልጽ ያደርጉታል።
ይህ የተግባር ስኬት እና የማስፈጸም አቅም በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ሳይሆን በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ እና በጂኦ-ፖለቲካ አቋማችን ላይም ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አካባቢ ያላትን የባሕር በር የማግኘት ሕጋዊ መብት ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የሰላም እና የፀጥታ ሚና እንዲሁም የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቶቿን የማጠናከር ሥራ የዲፕሎማሲያዊ ቁመቷን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል።
የሀገር ውስጥ የልማት አቅም ሲጎለብት የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነትም አብሮ እንደሚገነባ ይህ አካሄድ ሕያው ማሳያ ነው።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው ይፋዊ እውነት በተግባር እየተረጋገጠ በሄደ ቁጥር፣ ልማት ለብሔራዊ ትሥሥር እንደ ትሥሥር ገመድ ማገልገሉን ይቀጥላል። ይሄ የአፈጻጸም ሥልጣኔ ከተራ ፍልስፍና በላይ በመሆን አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጠንካራ ዐለት ላይ የሚገነባ ተግባራዊ መሠረት ሆኖ ሊጸና ይገባል።
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፤ በሕዝቦቿ ጥረት፣ በጠንካራ ሀገራዊ ተቋማት ግንባታ እና በዲጂታል ዘመን በሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎች በመታገዝ የተሻለ እና ብሩህ ነገን ትቀርጻለች።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #nationalinterest
*****************************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለዘመናት በማይፈጸሙ የተስፋ ቃላት እና በብሔር ማንነት አጀንዳ ሲታመስ ቆይቷል። አሁን ግን ሀገራችን ከዚህ የቃላት እና የተስፋ ፖለቲካ ወጥታ የመንግሥት ቅቡልነት በሚያወራው ሳይሆን በተግባር በሚሠራው ሥራ እና በሚያመጣው ተጨባጭ ውጤት ወደሚሆንበት አዲስ አሠራር እየተሸጋገረች ነው።
ይህ አሠራር በሚመጡ ተጨባጭ ለውጦች ለመለካት የሚሻ አዲስ የሀገር ግንባታ ማዕቀፍ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በአጽንዖት እንደገለጹት፣ የሀገራችን አዲሱ የታሪክ ምዕራፍ በተስፋ ቃላት ላይ ሳይሆን በተግባራዊ ክንውን እና በጥራት ላይ የተመሠረተ ነው።
ይህ "ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው መርሕ ከተራ መፈክር በላይ በመሆን፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ያላትን የማስፈጸም አቅም እና የሥልጣኔ ልክ የምታሳይበት ዋነኛ መሣሪያ ሆኗል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን እየታዩ ያሉ ስኬቶች መንግሥት ውጤት የማምጣት አቅሙን በተግባር ያረጋገጠባቸው ማሳያዎች ናቸው።
ከታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከማጠናቀቅ እና ኃይል ማመንጨት ጀምሮ፣ በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው የስንዴ ኤክስፖርት እና የመስኖ ልማት ስኬት፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች፣ እንዲሁም የአዲስ አበባ እና የክልል ከተሞችን ገጽታ የቀየሩት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የዚሁ ተግባራዊ ሕጋዊነት ውጤቶች ናቸው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እና የኢትዮጵያ ታምርት የኢንዱስትሪ ንቅናቄም ሀገራችን ትላልቅ ዕቅዶችን በተግባር የመለወጥ አቅም እንዳላት በተጨባጭ እያሳዩ ነው።
ዋናው ማዕቀፍ ግን የእነዚህ ፕሮጀክቶች መፈጸም ብቻ ሳይሆን፣ ጥቅሞቻቸው በሁሉም ክልሎች፣ ማንነቶች እና የፖለቲካ አመለካከቶች ውስጥ እኩል ሊሰርጹ መቻላቸው ላይ ነው። መንገዶች፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ልማታዊ ውጤቶች ብቻ ሳይሆኑ፣ የፌዴራል ሥርዓቱን ልዩነቶች አቀናጅተው የጋራ ብሔራዊ ልምድን የሚፈጥሩ ሥልታዊ ድልድዮች ናቸው።
ይህ አካሄድ ቀደም ሲል ከነበረው እና ሥልጣኑን በረጅም ጊዜ ተስፋዎች ላይ ብቻ ይመሠርት ከነበረው "ልማታዊ መንግሥት" አስተሳሰብ በእጅጉ የላቀ ነው።
የአሁኑ የመፈጸም ሞዴል ሊለኩ በሚችሉ ውጤቶች፣ በትግበራ ፍጥነት እና በተቋማዊ ብቃት ላይ የተመሠረተ ነው። የሲንጋፖር፣ የቪየትናም እና የማሌዢያ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ውል የሚገነባው እና ቢሮክራሲው የሚቀናጀው በተግባር በሚታይ የድህነት ቅነሳ እና የዜጎች የዕለት ተዕለት ሕይወት መሻሻል ላይ ነው።
መንግሥት ለኢኮኖሚ ችግሮች የሚሰጠው መፍትሔ በርዕዮተ ዓለም የታጠረ ሳይሆን፣ በተግባር በሚታይ ውጤት ላይ የተመሠረተ ገቢር ነበብ የኢኮኖሚ ፍልስፍና ነው።
ከለውጡ በፊት ኢኮኖሚው በከፍተኛ ዕዳ ተሸብቦ እና በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ተፈትኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ይህን የውድቀት ታሪክ መቀየር ተችሏል።
"ለረጅም ጊዜ ኢትዮጵያ በችግሮቿ እንጂ በእምቅ አቅሟ ስትገለጽ አልኖረችም፤ ዛሬ ግን የተለየ ታሪክ ብቅ እያለ ነው" ሲሉ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሀገራችንን አዲስ ምዕራፍ ያበሰሩት።
ይህ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” የሚለው መንፈስ በቴክኖሎጂ እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽኑ መስክም በጉልህ እየታየ ይገኛል። በ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አማካኝነት የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ማቅረብ፣ የ“መሶብ” የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መተግበሪያን መዘርጋት እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ሥልጠና ንቅናቄን መተግበር ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊ እና ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት እያሸጋገሯት ነው።
እነዚህ የዲጂታል መሠረቶች የቢሮክራሲውን ቅልጥፍና ከማሳደግ ባለፈ ዜጎች ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ግንኙነት ፍጹም ዘመናዊ እና ግልጽ ያደርጉታል።
ይህ የተግባር ስኬት እና የማስፈጸም አቅም በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ ሳይሆን በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ እና በጂኦ-ፖለቲካ አቋማችን ላይም ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር አካባቢ ያላትን የባሕር በር የማግኘት ሕጋዊ መብት ለማረጋገጥ የምታደርገው ጥረት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያላት የሰላም እና የፀጥታ ሚና እንዲሁም የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ አጋርነቶቿን የማጠናከር ሥራ የዲፕሎማሲያዊ ቁመቷን በእጅጉ እያሳደገው ይገኛል።
የሀገር ውስጥ የልማት አቅም ሲጎለብት የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነትም አብሮ እንደሚገነባ ይህ አካሄድ ሕያው ማሳያ ነው።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" የሚለው ይፋዊ እውነት በተግባር እየተረጋገጠ በሄደ ቁጥር፣ ልማት ለብሔራዊ ትሥሥር እንደ ትሥሥር ገመድ ማገልገሉን ይቀጥላል። ይሄ የአፈጻጸም ሥልጣኔ ከተራ ፍልስፍና በላይ በመሆን አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጠንካራ ዐለት ላይ የሚገነባ ተግባራዊ መሠረት ሆኖ ሊጸና ይገባል።
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፤ በሕዝቦቿ ጥረት፣ በጠንካራ ሀገራዊ ተቋማት ግንባታ እና በዲጂታል ዘመን በሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎች በመታገዝ የተሻለ እና ብሩህ ነገን ትቀርጻለች።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #nationalinterest
Sponsored by
Surafel
1 month ago
“እናት ፈር ቀዳጅና ለሌሎችም ተሞክሮ የሚሆን ብቸኛው የቀጠናው ሞዴል አካዳሚ ነው” ስንትአየሁ ንብረት
በእንጅባራ ከተማ የሚገኘው አንጋፋው "እናት አካዳሚ" ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
" እናት አካዳሚ" (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎቹን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።
በምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የእንጅባራ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ስንታየሁ ንብረት ፥በእንጅባራ ከተማ ከሚገኙት 12 አካዳሚዎች መካከል "እናት " የነገ አገር ተረካቢ ህፃናትን በትክክለኛው የዕውቀትና የሥነ-ምግባር ማዕቀፍ በመቅረጽ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።
እናት ኬጂ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጥራት ባለው ትምህርት ላይ በመረባረብ በተለይም በትውልድ ግንባታ ሂደት ውስጥ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛና ለሌሎችም አርአያ የሚሆን መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቱ ህጻናትን ከመንከባከብ ባለፈ ለአገር የሚጠቅም ስነ-ምግባር ያለው ትውልድ ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጋዥ አካላት ሁሉ ሊደግፉት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የእናት አካዳሚ መስራችና ባለቤት ጥሩወርቅ ደባሱ፥በዛሬው ዕለት በ3ቱም የአካዳሚው ት/ቤቶች ኬጅ(ቅድመ መደበኛ) ያጠናቀቁ 240 ተማሪዎች ተመርቀዋል።
ትምህርት ቤቱ መደበኛውን የማስተማር ሂደት ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችን ስብዕና፣ የቋንቋ ክህሎትና የባህል እሴት ማሳደግ ላይ መስራቱ የነገ አገር ተረካቢ እያፈራ መሆኑ ተናግረዋል ።
አካዳሚው በ2000 ዓ. ም መማር ማስተማር የጀመረ መሆኑን ያስታወሱት ወ/ሮ ጥሩወርቅ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ 6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ክልላዊ ፈተና ማስፈተኑ የዘንድሮን ምረቃት የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።
በ2018 ዓ.ም ከ1ሽ 600 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማሩንም ተናግረዋል።
በቀጣዩ የትምህርት ዘመንም የተሻሻሉ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በማሟላት በርካታ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስ
ተማርና ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የተማሪ ወላጆች በሰጡት አስተያየት እናት ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተማሪዎች ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል ።
ተቋም በተጠናከረ መልኩ እያሳየ ያለው ጥንካሬና ለትምህርት ጥራት የሚሰጠው ትኩረት ይበልጥ ሊጎላና ሊደገፍ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የዛሬ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢዎች አለም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከዚህ በላይ ቅደመ መደበኛ ላይ መሰራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በተማሪዎች የቀረቡ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የምረቃ ስነስርዓቱን አድምቀውታል።
በእንጅባራ ከተማ የሚገኘው አንጋፋው "እናት አካዳሚ" ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
" እናት አካዳሚ" (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎቹን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።
በምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የእንጅባራ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ስንታየሁ ንብረት ፥በእንጅባራ ከተማ ከሚገኙት 12 አካዳሚዎች መካከል "እናት " የነገ አገር ተረካቢ ህፃናትን በትክክለኛው የዕውቀትና የሥነ-ምግባር ማዕቀፍ በመቅረጽ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።
እናት ኬጂ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጥራት ባለው ትምህርት ላይ በመረባረብ በተለይም በትውልድ ግንባታ ሂደት ውስጥ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛና ለሌሎችም አርአያ የሚሆን መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቱ ህጻናትን ከመንከባከብ ባለፈ ለአገር የሚጠቅም ስነ-ምግባር ያለው ትውልድ ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጋዥ አካላት ሁሉ ሊደግፉት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የእናት አካዳሚ መስራችና ባለቤት ጥሩወርቅ ደባሱ፥በዛሬው ዕለት በ3ቱም የአካዳሚው ት/ቤቶች ኬጅ(ቅድመ መደበኛ) ያጠናቀቁ 240 ተማሪዎች ተመርቀዋል።
ትምህርት ቤቱ መደበኛውን የማስተማር ሂደት ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችን ስብዕና፣ የቋንቋ ክህሎትና የባህል እሴት ማሳደግ ላይ መስራቱ የነገ አገር ተረካቢ እያፈራ መሆኑ ተናግረዋል ።
አካዳሚው በ2000 ዓ. ም መማር ማስተማር የጀመረ መሆኑን ያስታወሱት ወ/ሮ ጥሩወርቅ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ 6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ክልላዊ ፈተና ማስፈተኑ የዘንድሮን ምረቃት የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።
በ2018 ዓ.ም ከ1ሽ 600 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማሩንም ተናግረዋል።
በቀጣዩ የትምህርት ዘመንም የተሻሻሉ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በማሟላት በርካታ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስ
ተማርና ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የተማሪ ወላጆች በሰጡት አስተያየት እናት ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተማሪዎች ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል ።
ተቋም በተጠናከረ መልኩ እያሳየ ያለው ጥንካሬና ለትምህርት ጥራት የሚሰጠው ትኩረት ይበልጥ ሊጎላና ሊደገፍ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የዛሬ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢዎች አለም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከዚህ በላይ ቅደመ መደበኛ ላይ መሰራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በተማሪዎች የቀረቡ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የምረቃ ስነስርዓቱን አድምቀውታል።
1 month ago
እናት " ፈር ቀዳጅና ለሌሎችም ተሞክሮ የሚሆን ብቸኛው የቀጠናው ሞዴል አካዳሚ ነው -ስንትአየሁ ንብረት
#ethiopia | በእንጅባራ ከተማ የሚገኘው አንጋፋው "እናት አካዳሚ" ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
" እናት አካዳሚ" (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎቹን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።
በምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የእንጅባራ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ስንታየሁ ንብረት ፥በእንጅባራ ከተማ ከሚገኙት 12 አካዳሚዎች መካከል "እናት " የነገ አገር ተረካቢ ህፃናትን በትክክለኛው የዕውቀትና የሥነ-ምግባር ማዕቀፍ በመቅረጽ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።
እናት ኬጂ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጥራት ባለው ትምህርት ላይ በመረባረብ በተለይም በትውልድ ግንባታ ሂደት ውስጥ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛና ለሌሎችም አርአያ የሚሆን መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቱ ህጻናትን ከመንከባከብ ባለፈ ለአገር የሚጠቅም ስነ-ምግባር ያለው ትውልድ ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጋዥ አካላት ሁሉ ሊደግፉት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የእናት አካዳሚ መስራችና ባለቤት ጥሩወርቅ ደባሱ፥በዛሬው ዕለት በ3ቱም የአካዳሚው ት/ቤቶች ኬጅ(ቅድመ መደበኛ) ያጠናቀቁ 240 ተማሪዎች ተመርቀዋል።
ትምህርት ቤቱ መደበኛውን የማስተማር ሂደት ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችን ስብዕና፣ የቋንቋ ክህሎትና የባህል እሴት ማሳደግ ላይ መስራቱ የነገ አገር ተረካቢ እያፈራ መሆኑ ተናግረዋል ።
አካዳሚው በ2000 ዓ. ም መማር ማስተማር የጀመረ መሆኑን ያስታወሱት ወ/ሮ ጥሩወርቅ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ 6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ክልላዊ ፈተና ማስፈተኑ የዘንድሮን ምረቃት የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።
በ2018 ዓ.ም ከ1ሽ 600 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማሩንም ተናግረዋል።
በቀጣዩ የትምህርት ዘመንም የተሻሻሉ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በማሟላት በርካታ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስ
ተማርና ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የተማሪ ወላጆች በሰጡት አስተያየት እናት ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተማሪዎች ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል ።
ተቋም በተጠናከረ መልኩ እያሳየ ያለው ጥንካሬና ለትምህርት ጥራት የሚሰጠው ትኩረት ይበልጥ ሊጎላና ሊደገፍ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የዛሬ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢዎች አለም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከዚህ በላይ ቅደመ መደበኛ ላይ መሰራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በተማሪዎች የቀረቡ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የምረቃ ስነስርዓቱን አድምቀውታል።
#ethiopia | በእንጅባራ ከተማ የሚገኘው አንጋፋው "እናት አካዳሚ" ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ2018 ዓ.ም ተማሪዎቹን በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
" እናት አካዳሚ" (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 የትምህርት ዘመን ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎቹን፣ የተማሪ ወላጆች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶችና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት አስመርቋል።
በምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የእንጅባራ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ ስንታየሁ ንብረት ፥በእንጅባራ ከተማ ከሚገኙት 12 አካዳሚዎች መካከል "እናት " የነገ አገር ተረካቢ ህፃናትን በትክክለኛው የዕውቀትና የሥነ-ምግባር ማዕቀፍ በመቅረጽ ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው።
እናት ኬጂ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ጥራት ባለው ትምህርት ላይ በመረባረብ በተለይም በትውልድ ግንባታ ሂደት ውስጥ እያበረከተ ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛና ለሌሎችም አርአያ የሚሆን መሆኑን ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቱ ህጻናትን ከመንከባከብ ባለፈ ለአገር የሚጠቅም ስነ-ምግባር ያለው ትውልድ ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጋዥ አካላት ሁሉ ሊደግፉት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የእናት አካዳሚ መስራችና ባለቤት ጥሩወርቅ ደባሱ፥በዛሬው ዕለት በ3ቱም የአካዳሚው ት/ቤቶች ኬጅ(ቅድመ መደበኛ) ያጠናቀቁ 240 ተማሪዎች ተመርቀዋል።
ትምህርት ቤቱ መደበኛውን የማስተማር ሂደት ብቻ ሳይሆን የተማሪዎችን ስብዕና፣ የቋንቋ ክህሎትና የባህል እሴት ማሳደግ ላይ መስራቱ የነገ አገር ተረካቢ እያፈራ መሆኑ ተናግረዋል ።
አካዳሚው በ2000 ዓ. ም መማር ማስተማር የጀመረ መሆኑን ያስታወሱት ወ/ሮ ጥሩወርቅ በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ 6ኛ ክፍል ተማሪዎችን ክልላዊ ፈተና ማስፈተኑ የዘንድሮን ምረቃት የተለየ ያደርገዋል ብለዋል።
በ2018 ዓ.ም ከ1ሽ 600 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማሩንም ተናግረዋል።
በቀጣዩ የትምህርት ዘመንም የተሻሻሉ አሰራሮችንና ግብዓቶችን በማሟላት በርካታ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስ
ተማርና ሙሉ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቀዋል።
የተማሪ ወላጆች በሰጡት አስተያየት እናት ኬጂ (KG) እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተማሪዎች ላይ የሚያደርገው ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል ።
ተቋም በተጠናከረ መልኩ እያሳየ ያለው ጥንካሬና ለትምህርት ጥራት የሚሰጠው ትኩረት ይበልጥ ሊጎላና ሊደገፍ እንደሚገባም ተናግረዋል ።
የዛሬ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢዎች አለም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ከዚህ በላይ ቅደመ መደበኛ ላይ መሰራት እንደሚገባም ጠቁመዋል።
በተማሪዎች የቀረቡ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች የምረቃ ስነስርዓቱን አድምቀውታል።
1 month ago
ከነዳጅ ወደ ኤሌክትሪክ፡ የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ አስደናቂ የቴክኖሎጂ ስኬት
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ በሀገር ውስጥ የታየ ትልቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ማብሰሪያ የሆነ አዲስ የፈጠራ ስኬት ይፋ አድርጓል።
ተቋሙ ቀደም ሲል በነዳጅ (በቤንዚን) ይንቀሳቀስ የነበረውን 'Sandstorm S24' የተሰኘ የፒክአፕ ተሽከርካሪ ሞዴል ሙሉ በሙሉ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪነት (EV) የመቀየር ሥራን በስኬት አጠናቋል።
ይህ አረንጓዴ እና ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክት በዩኒቨርሲቲው የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ ተመራማሪዎች ቡድን በግንባር ቀደምትነት የተመራ ነው።
ወደ ኤሌክትሪክ የተቀየረው ይህ ተሽከርካሪ በአንድ ጊዜ ሙሉ ቻርጅ እስከ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት የመጓዝ ከፍተኛ አቅም አለው።
ከዚህም በላይ አሠራሩ ሙሉ በሙሉ ለአካባቢ ተስማሚ በመሆኑ ምንም ዓይነት የጭስ ልቀት (Zero Emission) የማያስመዘግብና የአየር ብክለትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚከላከል ነው።
የዚህ ፕሮጀክት ትልቁ ስኬት በኢኮኖሚ ረገድ የሚሰጠው ጥቅም ሲሆን፥ የተሽከርካሪውን የሥራ ማስኬጃ እና የነዳጅ ወጪ በ88 በመቶ ያህል በከፍተኛ መጠን ይቀንሳል። ለለውጥ ሥራው የወጣው ጠቅላላ የፕሮጀክት ወጪም ተሽከርካሪው በሚሰጠው አገልግሎትና በሚያስገኘው ቁጠባ አማካኝነት ከ4 እስከ 5 ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ መሆን ይችላል።
ለዚህ አስደናቂ የፈጠራ ውጤት ተመራማሪዎቹ 70 ኪሎዋት የPMSM ኤሌክትሪክ ሞተር እና 65 ኪሎዋት ሰዓት የሊቲየም-አዮን ባትሪ በውስጡ ገጥመዋል።
በተጨማሪም ቀልጣፋ የ3.3 ኪሎዋት AC/DC የቻርጂንግ ሥርዓት እና በሚያዝበት ጊዜ ኃይል የሚቆጥብ የRegenerative Braking ቴክኖሎጂ በጥንቃቄ ተተግብሮበታል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ በሀገር ውስጥ የታየ ትልቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር ማብሰሪያ የሆነ አዲስ የፈጠራ ስኬት ይፋ አድርጓል።
ተቋሙ ቀደም ሲል በነዳጅ (በቤንዚን) ይንቀሳቀስ የነበረውን 'Sandstorm S24' የተሰኘ የፒክአፕ ተሽከርካሪ ሞዴል ሙሉ በሙሉ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪነት (EV) የመቀየር ሥራን በስኬት አጠናቋል።
ይህ አረንጓዴ እና ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክት በዩኒቨርሲቲው የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ ተመራማሪዎች ቡድን በግንባር ቀደምትነት የተመራ ነው።
ወደ ኤሌክትሪክ የተቀየረው ይህ ተሽከርካሪ በአንድ ጊዜ ሙሉ ቻርጅ እስከ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት የመጓዝ ከፍተኛ አቅም አለው።
ከዚህም በላይ አሠራሩ ሙሉ በሙሉ ለአካባቢ ተስማሚ በመሆኑ ምንም ዓይነት የጭስ ልቀት (Zero Emission) የማያስመዘግብና የአየር ብክለትን በከፍተኛ ሁኔታ የሚከላከል ነው።
የዚህ ፕሮጀክት ትልቁ ስኬት በኢኮኖሚ ረገድ የሚሰጠው ጥቅም ሲሆን፥ የተሽከርካሪውን የሥራ ማስኬጃ እና የነዳጅ ወጪ በ88 በመቶ ያህል በከፍተኛ መጠን ይቀንሳል። ለለውጥ ሥራው የወጣው ጠቅላላ የፕሮጀክት ወጪም ተሽከርካሪው በሚሰጠው አገልግሎትና በሚያስገኘው ቁጠባ አማካኝነት ከ4 እስከ 5 ዓመታት ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ መሆን ይችላል።
ለዚህ አስደናቂ የፈጠራ ውጤት ተመራማሪዎቹ 70 ኪሎዋት የPMSM ኤሌክትሪክ ሞተር እና 65 ኪሎዋት ሰዓት የሊቲየም-አዮን ባትሪ በውስጡ ገጥመዋል።
በተጨማሪም ቀልጣፋ የ3.3 ኪሎዋት AC/DC የቻርጂንግ ሥርዓት እና በሚያዝበት ጊዜ ኃይል የሚቆጥብ የRegenerative Braking ቴክኖሎጂ በጥንቃቄ ተተግብሮበታል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
የኢትዮጵያ የገጠር ኮሪደር ልማትና የአርሶ አደሩ ሁለንተናዊ የኑሮ ሽግግር
******************
የመደመር መንግሥት በከተሞች የጀመረውን ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስኬቶች ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለመቀየር የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊ የልማት ሪፎርም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና አነሳሽነት ተግባራዊ በማድረግ በየክልሎቹ አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ ንቅናቄ በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የዕድገት ልዩነት በማጥበብ የዘላቂ ብልጽግናን መሠረት ለመጣል ያለመ ነው።
የጥንታዊ ሥልጣኔ የዘመናት ታሪካዊ ክብር ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የትናንቱን የአክሱም ሐውልቶች ዘመን አይሽሬ የኢንጂነሪንግ ጥበብ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና የጀጎል ግንብ የኪነ-ሕንጻ ምጥቀት ከነገው የብልጽግና ተስፋ ጋር በማገመድ፣ አቅዶ የመፈጸም ባህልን በተጨባጭ ምድር ላይ እያረጋገጠችና ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የታሪክ አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች።
ይህ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት መሠረተ ልማትን ከማዘመን ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ሥራዎችን በተጨባጭ መሬት ላይ ማሳየት የጀመረ የመደመር መንግሥት ቁልፍ የለውጥ እሳቤ ነው። ልማቱ የከተማ ውበትና የኮሪደር ልማት ስኬቶችን ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየሠራ ይገኛል።
ልማቱ የገጠር ነዋሪዎችን ከተበታተነ አሰፋፈር ወደ ተቀናጁ የገጠር መንደሮች በማምጣት ንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ መብራት፣ ጤና እና ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ፤ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማት አካባቢውን ለቱሪዝምና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
ቀደም ሲል የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ሰዓታት በእግር ይጓዙ የነበሩ የገጠር መንደሮች፣ አሁን ላይ ደረጃቸውን በጠበቁ የጠጠርና የአስፋልት መንገዶች መገናኘት ችለዋል።
በዚህም በእናቶችና ሕፃናት የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የገጠር አባወራዎች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም አማራጭ የኢነርጂ እና የፀሐይ ብርሃን መብራቶች በየመንደሮቹ በመስፋፋታቸው የገጠሩን የምሽት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር ላይ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ የልማት ስልት አነስተኛ ወጪ በሚጠይቁና በአካባቢው በሚገኑ ግብዓቶች የሚገነቡ፣ ነገር ግን ምቹና ሞዴል በሆኑ መኖሪያ ቤቶች የአርሶ አደሮችን ሕይወት የሚለውጥ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ባዮ ጋዝን በማሟላት ለሕይወት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስችላል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተተከሉ የፍራፍሬና የጓሮ አትክልቶችን ከንብ እርባታ፣ ከእንቁላል፣ ከወተትና ከሥጋ ምርት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት እንዲኖረውና ምርታማነቱ አድጎ ለራሱ ፍጆታ ከመብቃቱ ባለፈ፣ ለገበያ በማቅረብ ገቢውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያሳድግ ይረዳል።
ይህ የመሠረተ ልማትና የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ለልጆች ትምህርትና ለቤተሰብ ዘመናዊ መረጃ ተደራሽነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፤ በገጠር የተሻለ የኑሮ ሁኔታ በመፈጠሩ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን የኢትዮጵያን ገጠር መልክ የሚቀይር የትውልድ ፕሮጀክት በመሆኑ፣ የተጀመረው ዘላቂ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ይበልጥ እንዲያሳድግ አመራሩ፣ አርሶ አደሩ እና ባለሀብቶች በጋራና በቁርጠኝነት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #ruralcorridordevelopment #ruraldevelopment #infrastructure
******************
የመደመር መንግሥት በከተሞች የጀመረውን ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስኬቶች ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለመቀየር የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊ የልማት ሪፎርም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና አነሳሽነት ተግባራዊ በማድረግ በየክልሎቹ አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ ንቅናቄ በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የዕድገት ልዩነት በማጥበብ የዘላቂ ብልጽግናን መሠረት ለመጣል ያለመ ነው።
የጥንታዊ ሥልጣኔ የዘመናት ታሪካዊ ክብር ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የትናንቱን የአክሱም ሐውልቶች ዘመን አይሽሬ የኢንጂነሪንግ ጥበብ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና የጀጎል ግንብ የኪነ-ሕንጻ ምጥቀት ከነገው የብልጽግና ተስፋ ጋር በማገመድ፣ አቅዶ የመፈጸም ባህልን በተጨባጭ ምድር ላይ እያረጋገጠችና ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የታሪክ አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች።
ይህ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት መሠረተ ልማትን ከማዘመን ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ሥራዎችን በተጨባጭ መሬት ላይ ማሳየት የጀመረ የመደመር መንግሥት ቁልፍ የለውጥ እሳቤ ነው። ልማቱ የከተማ ውበትና የኮሪደር ልማት ስኬቶችን ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየሠራ ይገኛል።
ልማቱ የገጠር ነዋሪዎችን ከተበታተነ አሰፋፈር ወደ ተቀናጁ የገጠር መንደሮች በማምጣት ንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ መብራት፣ ጤና እና ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ፤ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማት አካባቢውን ለቱሪዝምና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
ቀደም ሲል የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ሰዓታት በእግር ይጓዙ የነበሩ የገጠር መንደሮች፣ አሁን ላይ ደረጃቸውን በጠበቁ የጠጠርና የአስፋልት መንገዶች መገናኘት ችለዋል።
በዚህም በእናቶችና ሕፃናት የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የገጠር አባወራዎች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም አማራጭ የኢነርጂ እና የፀሐይ ብርሃን መብራቶች በየመንደሮቹ በመስፋፋታቸው የገጠሩን የምሽት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር ላይ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ የልማት ስልት አነስተኛ ወጪ በሚጠይቁና በአካባቢው በሚገኑ ግብዓቶች የሚገነቡ፣ ነገር ግን ምቹና ሞዴል በሆኑ መኖሪያ ቤቶች የአርሶ አደሮችን ሕይወት የሚለውጥ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ባዮ ጋዝን በማሟላት ለሕይወት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስችላል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተተከሉ የፍራፍሬና የጓሮ አትክልቶችን ከንብ እርባታ፣ ከእንቁላል፣ ከወተትና ከሥጋ ምርት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት እንዲኖረውና ምርታማነቱ አድጎ ለራሱ ፍጆታ ከመብቃቱ ባለፈ፣ ለገበያ በማቅረብ ገቢውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያሳድግ ይረዳል።
ይህ የመሠረተ ልማትና የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ለልጆች ትምህርትና ለቤተሰብ ዘመናዊ መረጃ ተደራሽነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፤ በገጠር የተሻለ የኑሮ ሁኔታ በመፈጠሩ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን የኢትዮጵያን ገጠር መልክ የሚቀይር የትውልድ ፕሮጀክት በመሆኑ፣ የተጀመረው ዘላቂ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ይበልጥ እንዲያሳድግ አመራሩ፣ አርሶ አደሩ እና ባለሀብቶች በጋራና በቁርጠኝነት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #ruralcorridordevelopment #ruraldevelopment #infrastructure
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት፤ ከልቀት ማዕከልነት እስከ ዘመናዊ ግብርና እና ዲጂታላይዜሽን
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
1 month ago
የኢትዮጵያ የማዕድን አብዮት - ከ0.2 በመቶ የኢኮኖሚ ድርሻ ወደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ሞተርነት
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
1 month ago
የኮሪደር ልማት ከከተማ ወደ ገጠር፡ የፍትሐዊነት እና የዜጎች ክብር አዲሱ ምዕራፍ
************************
ኢትዮጵያን የሚመጥን ዘመናዊ ገጽታን ለመገንባት እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ መንግሥት በአዲስ አበባ የጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ዛሬ ላይ የሀገራችን ከተሞች ዋነኛ መገለጫና አዲስ የልማት ባህል ሆኖ ተሻግሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከኮሪደር ልማቱ በፊት የነበራትን ገጽታ እና የመጀመሪያው ዙር ልማት ከተጠናቀቀ በኋላ ያገኘችውን አስደናቂ ውበትና ምቾት እንደ አብነት በመውሰድ፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች የኮሪደር ልማት በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህ የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ከመሆኑም በላይ፣ ሁሉንም ዜጋ ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማትን ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ በመሆኑ ለሌሎች ሀገራት ጭምር አርዓያና ምሳሌ ሊሆን በሚችል መልኩ እየተተገበረ ይገኛል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የሚኖረው በገጠር አካባቢዎች በመሆኑ፣ የዜጎችን ሕይወት በተሟላ መልኩ ለመቀየር እና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ በከተሞች ላይ ብቻ የሚሠራው የኮሪደር ልማት በቂ ሊሆን አይችልም።
በከተሞች የታየው አመርቂ እና ተጨባጭ ውጤት በገጠርም መደገም አለበት ከሚል ጽኑ ሀገራዊ ራዕይ በመነሳት፣ ልማቱ አድማሱን በማስፋት የገጠሩን ማኅበረሰብ አኗኗር ወደሚያሻሽል የገጠር ኮሪደር ልማት ተሸጋግሮ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሞዴል የገጠር መንደሮች ግንባታን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2017 ዓ.ም ግንቦት ወር መጨረሻ ላይ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ዋነኛ ግቡም የተስተካከለ የኑሮ ዘይቤን እና ዘመናዊ ከተሜነትን ወደ ገጠር ማምጣት ሲሆን፣ የሚገነቡት ሞዴል መንደሮችም ቀላል ወጪ የሚጠይቁ እና በአካባቢው በሚገኙ ሀገር በቀል ግብዓቶች የሚገነቡ መሆናቸው ልዩ ያደርጋቸዋል።
ይህም አርሶ አደሩ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ጤናማ፣ ፅዱ እና ክብሩን የጠበቀ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
ልማቱ በውጤት ደረጃ የኅብረተሰብ ሽግግርን የሚያመጣ እና የመሠረተ ልማት ተጠቃሚነትን በፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ነው።
በሌላ በኩል ከለውጡ በፊት የሀገራችን የኢኮኖሚ ዋነኛ ምንጭ የሆነው የገጠሩ አካባቢ ተገቢውን ትኩረት አጥቶ በመቆየቱ ምክንያት፣ የተሻለ ኑሮን ፍለጋ ወደ ከተሞች የሚሰደደው የወጣት ቁጥር ከፍተኛ ነበር።
የገጠር ኮሪደር ልማት ግን፣ የተመጣጠነ የሀገር ዕድገትን በሁሉም አካባቢ በማምጣት ይህንን ፍልሰት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል።
ወጣቶችም የተሻለ ሕይወት ፍለጋ መሰደድ ሳይጠበቅባቸው በሚኖሩበት አካባቢ ተረጋግተው በተለያዩ የልማት ዘርፎች እንዲሰማሩ እንዲሁም በግብርና ውጤቶች ላይ እሴት በመጨመር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ በመፍጠርም ላይ ይገኛል።
ይህ ሥራ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ፋይዳ ያለው ዘርፈ-ብዙ ስትራቴጂ ሲሆን፣ አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆን እና ዘመናዊ ስልተ-ምርትን እንዲከተል በማድረግ አዲስ የአኗኗር ባህል በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ይተክላል።
ይህም በሀገር ደረጃ የምግብ ሉዓላዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት እና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር የሚያስችል ምቹ ዐውድ እየፈጠረ ይገኛል።
የኮሪደር ልማቱ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ገጽታና አኗኗር የሚቀይር ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በዚህም በገጠር የሀገሪቱ አካባቢዎች ዘመናዊ አኗኗርን በመፍጠር፣ የአርሶ አደሩን ሕይወት በማሻሻል እና የከተማና የገጠርን የኑሮ ልዩነት በማጥበብ ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #corriderdevelopment #ruralcorriderdevelopment #ruraltransformation
************************
ኢትዮጵያን የሚመጥን ዘመናዊ ገጽታን ለመገንባት እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ መንግሥት በአዲስ አበባ የጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ዛሬ ላይ የሀገራችን ከተሞች ዋነኛ መገለጫና አዲስ የልማት ባህል ሆኖ ተሻግሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከኮሪደር ልማቱ በፊት የነበራትን ገጽታ እና የመጀመሪያው ዙር ልማት ከተጠናቀቀ በኋላ ያገኘችውን አስደናቂ ውበትና ምቾት እንደ አብነት በመውሰድ፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ የተለያዩ ከተሞች የኮሪደር ልማት በተጠናከረ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህ የኮሪደር ልማት ከከተሜነት ዕድገት ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ከመሆኑም በላይ፣ ሁሉንም ዜጋ ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ ልማትን ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ በመሆኑ ለሌሎች ሀገራት ጭምር አርዓያና ምሳሌ ሊሆን በሚችል መልኩ እየተተገበረ ይገኛል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የሚኖረው በገጠር አካባቢዎች በመሆኑ፣ የዜጎችን ሕይወት በተሟላ መልኩ ለመቀየር እና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ዕውን ለማድረግ በከተሞች ላይ ብቻ የሚሠራው የኮሪደር ልማት በቂ ሊሆን አይችልም።
በከተሞች የታየው አመርቂ እና ተጨባጭ ውጤት በገጠርም መደገም አለበት ከሚል ጽኑ ሀገራዊ ራዕይ በመነሳት፣ ልማቱ አድማሱን በማስፋት የገጠሩን ማኅበረሰብ አኗኗር ወደሚያሻሽል የገጠር ኮሪደር ልማት ተሸጋግሮ ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም የገጠር ኮሪደር ልማት እና ሞዴል የገጠር መንደሮች ግንባታን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ2017 ዓ.ም ግንቦት ወር መጨረሻ ላይ በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ዋነኛ ግቡም የተስተካከለ የኑሮ ዘይቤን እና ዘመናዊ ከተሜነትን ወደ ገጠር ማምጣት ሲሆን፣ የሚገነቡት ሞዴል መንደሮችም ቀላል ወጪ የሚጠይቁ እና በአካባቢው በሚገኙ ሀገር በቀል ግብዓቶች የሚገነቡ መሆናቸው ልዩ ያደርጋቸዋል።
ይህም አርሶ አደሩ ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ጤናማ፣ ፅዱ እና ክብሩን የጠበቀ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
ልማቱ በውጤት ደረጃ የኅብረተሰብ ሽግግርን የሚያመጣ እና የመሠረተ ልማት ተጠቃሚነትን በፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ነው።
በሌላ በኩል ከለውጡ በፊት የሀገራችን የኢኮኖሚ ዋነኛ ምንጭ የሆነው የገጠሩ አካባቢ ተገቢውን ትኩረት አጥቶ በመቆየቱ ምክንያት፣ የተሻለ ኑሮን ፍለጋ ወደ ከተሞች የሚሰደደው የወጣት ቁጥር ከፍተኛ ነበር።
የገጠር ኮሪደር ልማት ግን፣ የተመጣጠነ የሀገር ዕድገትን በሁሉም አካባቢ በማምጣት ይህንን ፍልሰት በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል።
ወጣቶችም የተሻለ ሕይወት ፍለጋ መሰደድ ሳይጠበቅባቸው በሚኖሩበት አካባቢ ተረጋግተው በተለያዩ የልማት ዘርፎች እንዲሰማሩ እንዲሁም በግብርና ውጤቶች ላይ እሴት በመጨመር ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፤ በመፍጠርም ላይ ይገኛል።
ይህ ሥራ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ሥነ-ምህዳራዊ ፋይዳ ያለው ዘርፈ-ብዙ ስትራቴጂ ሲሆን፣ አርሶ አደሩ የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆን እና ዘመናዊ ስልተ-ምርትን እንዲከተል በማድረግ አዲስ የአኗኗር ባህል በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ይተክላል።
ይህም በሀገር ደረጃ የምግብ ሉዓላዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት እና የተረጋጋ ኅብረተሰብ ለመፍጠር የሚያስችል ምቹ ዐውድ እየፈጠረ ይገኛል።
የኮሪደር ልማቱ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ገጽታና አኗኗር የሚቀይር ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ሲሆን፣ በዚህም በገጠር የሀገሪቱ አካባቢዎች ዘመናዊ አኗኗርን በመፍጠር፣ የአርሶ አደሩን ሕይወት በማሻሻል እና የከተማና የገጠርን የኑሮ ልዩነት በማጥበብ ለነገዋ የበለጸገች ኢትዮጵያ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #corriderdevelopment #ruralcorriderdevelopment #ruraltransformation
1 month ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
የኮሪደር ልማት...ከከተማ እስከ ገጠር
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ በስፋት እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በጥቂት ዓመታት ውስጥ የከተሞችና የገጠራማ አካባቢዎችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት በከፍተኛ ደረጃ እያሻሻለ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንዳሉት፥ ከተሜነት በዕቅድና በእውቀት ካልተመራ ከተሞች ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ ይሆናሉ፡፡
ለዚህም ነባሩን የዘፈቀደ አሠራር በማስቀረት ነገን ታሳቢ ያደረገና ሁሉን አቀፍ ብልጽግናን የሚያረጋገጥ የኮሪደር ልማት ሥራ በስፋት እያተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።
አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ከተሞች የተመሠረቱት በጦር ካምፕነት እንጂ በተጠና ማስተር ፕላን ባለመሆኑ ከተሞቹ እያደጉ በሚመጡበት ወቅት በርካታ ችግሮች እያጋጠማቸው ይገኛል።
አሁን ላይ እየተከናወነ ያለው የከተማ ኮሪደር ልማት ይህንን እቅድ አልባ ጉዞ በመቀየር ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ ለአብነትም በመዲናዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች እጅግ ማራኪ አድርገዋታል።
ይህ ጅማሮ የሀገሪቱን የኮንፈረንስ ቱሪዝም አድማስ በከፍተኛ ደረጃ በማስፋት በዚህ በጀት ዓመት ብቻ ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን የውጭ ጎብኚዎችን ማስተናገድ አስችሏል።
በዚሁ ጊዜ ውስጥ በቱሪዝም ፍሰት ከ5 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ መገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ አድርገዋል፡፡
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ማዕከል በዓለም ፈጣን የቱሪዝም ዕድገት እያሳዩ ካሉ ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
አሁን ላይ አስደናቂ ውጤት እያስመዘገበ የሚገኘውና በከተማ የተጀመረው ስኬታማ የኮሪደር ልማት ተሞክሮ ወደ ገጠር በመስፋፋት የአርሶና አርብቶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ እያሻሻለ ይገኛል።
የገጠር ኮሪደር ሀገራዊ ልማት ዋና ዓላማ የእያንዳንዱን አርሶ እና አርብቶ አደር አኗኗር በማሻሻል እንደ ሀገር የሚታሰበውን ብልጽግና ማረጋገጥ ነው።
በተጨማሪም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር በማዘመን ከተማ ሄደው የሚያገኟቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች ባሉበት አካባቢ እንዲያገኙ ማድረግ የኮሪደር ልማት ግብ ነው።
ከአካባቢ በሚገኙ ግብዓቶች፣ በባሕላዊ የግንባታ ዘዴ፣ በተደራጀ ዕቅድና በህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተገነቡት ሞዴል የገጠር መንደሮች ለየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች የተሻሻለ የአኗኗር ዘይቤ ጠንካራ እድል ፈጥረዋል።
ለአብነትም ሀማሳ፣ ጎሮ ወረዳ፣ ሀረሪ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ጉራፈርዳ እንዲሁም በሀላባ፣ ከምባታ፣ ሀዲያ እና ስልጤ ዞኖች የተገነቡና በሀገር ደረጃ እንደ ተሞክሮ ሊወሰዱ የሚችሉ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራዎችን መጥቀስ ይቻላል።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማን ከማስዋብና ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ የገጠሩን ማህበረሰብ የኑሮ ደረጃ ወደ ላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር ሁለንተናዊ የብልጽግና መሣሪያ በመሆን እያገለገለ ይገኛል።
በአነስተኛ ወጪና የአካባቢን የተፈጥሮ ጸጋ በመጠቀም የእያንዳንዱን ዜጋ ሕይወት አኗኗር መቀየር እንደሚቻል በተግባር የታየበትን ይህንን ልማት አጠናክሮ ማስቀጠል ለዘላቂ ሀገራዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የኮሪደር ልማት...ከከተማ እስከ ገጠር
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ በስፋት እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት በጥቂት ዓመታት ውስጥ የከተሞችና የገጠራማ አካባቢዎችን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይወት በከፍተኛ ደረጃ እያሻሻለ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንዳሉት፥ ከተሜነት በዕቅድና በእውቀት ካልተመራ ከተሞች ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ ይሆናሉ፡፡
ለዚህም ነባሩን የዘፈቀደ አሠራር በማስቀረት ነገን ታሳቢ ያደረገና ሁሉን አቀፍ ብልጽግናን የሚያረጋገጥ የኮሪደር ልማት ሥራ በስፋት እያተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።
አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ከተሞች የተመሠረቱት በጦር ካምፕነት እንጂ በተጠና ማስተር ፕላን ባለመሆኑ ከተሞቹ እያደጉ በሚመጡበት ወቅት በርካታ ችግሮች እያጋጠማቸው ይገኛል።
አሁን ላይ እየተከናወነ ያለው የከተማ ኮሪደር ልማት ይህንን እቅድ አልባ ጉዞ በመቀየር ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ ለአብነትም በመዲናዋ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ከተማዋን ለነዋሪዎች ምቹና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች እጅግ ማራኪ አድርገዋታል።
ይህ ጅማሮ የሀገሪቱን የኮንፈረንስ ቱሪዝም አድማስ በከፍተኛ ደረጃ በማስፋት በዚህ በጀት ዓመት ብቻ ኢትዮጵያ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን የውጭ ጎብኚዎችን ማስተናገድ አስችሏል።
በዚሁ ጊዜ ውስጥ በቱሪዝም ፍሰት ከ5 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ መገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ አድርገዋል፡፡
ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ማዕከል በዓለም ፈጣን የቱሪዝም ዕድገት እያሳዩ ካሉ ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ የኮሪደር ልማት ስራዎች ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
አሁን ላይ አስደናቂ ውጤት እያስመዘገበ የሚገኘውና በከተማ የተጀመረው ስኬታማ የኮሪደር ልማት ተሞክሮ ወደ ገጠር በመስፋፋት የአርሶና አርብቶ አደሩን የአኗኗር ዘዬ እያሻሻለ ይገኛል።
የገጠር ኮሪደር ሀገራዊ ልማት ዋና ዓላማ የእያንዳንዱን አርሶ እና አርብቶ አደር አኗኗር በማሻሻል እንደ ሀገር የሚታሰበውን ብልጽግና ማረጋገጥ ነው።
በተጨማሪም የገጠሩን ማህበረሰብ አኗኗር በማዘመን ከተማ ሄደው የሚያገኟቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች ባሉበት አካባቢ እንዲያገኙ ማድረግ የኮሪደር ልማት ግብ ነው።
ከአካባቢ በሚገኙ ግብዓቶች፣ በባሕላዊ የግንባታ ዘዴ፣ በተደራጀ ዕቅድና በህብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተገነቡት ሞዴል የገጠር መንደሮች ለየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች የተሻሻለ የአኗኗር ዘይቤ ጠንካራ እድል ፈጥረዋል።
ለአብነትም ሀማሳ፣ ጎሮ ወረዳ፣ ሀረሪ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ጉራፈርዳ እንዲሁም በሀላባ፣ ከምባታ፣ ሀዲያ እና ስልጤ ዞኖች የተገነቡና በሀገር ደረጃ እንደ ተሞክሮ ሊወሰዱ የሚችሉ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራዎችን መጥቀስ ይቻላል።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከተማን ከማስዋብና ለኑሮ ምቹ እንዲሆኑ ከማድረግ ባለፈ የገጠሩን ማህበረሰብ የኑሮ ደረጃ ወደ ላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር ሁለንተናዊ የብልጽግና መሣሪያ በመሆን እያገለገለ ይገኛል።
በአነስተኛ ወጪና የአካባቢን የተፈጥሮ ጸጋ በመጠቀም የእያንዳንዱን ዜጋ ሕይወት አኗኗር መቀየር እንደሚቻል በተግባር የታየበትን ይህንን ልማት አጠናክሮ ማስቀጠል ለዘላቂ ሀገራዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
Sponsored by
Surafel
Comments