22 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሩሲያ ትልቁ የኦንላይን የገበያ መድረክ የሆነው 'ዋይልድቤሪስ' መጋዘኖች ላይ ዩክሬን እያደረሰች ያለው ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የሩሲያ አነስተኛ ንግዶችን ለከፍተኛ ኪሳራ እና መዘጋት እየዳረገ መሆኑ ተዘገበ።
ከጁላይ 18 ጀምሮ በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ወደ 20 በሚጠጉ የኩባንያው ግዙፍ ማከማቻዎች ላይ ቃጠሎ የተነሳ ሲሆን፣ የሳተላይት ምስሎች እንደሚያሳዩት ከ1.18 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ (ወይም ከኩባንያው አጠቃላይ አቅም አንድ አምስተኛው) የመጋዘን ቦታ ወድሟል። በዚህም ምክንያት የኩባንያው የሎጂስቲክስ መስመር ክፉኛ በመስተጓጎሉ፣ በገበያ መድረኩ ላይ ጥገኛ የሆኑ ቸርቻሪዎች ምርቶቻቸውን ማቅረብ ተስኗቸዋል።
በሞስኮ የዕቃ መቀበያ ጣቢያ የሚያስተዳድረው ቫሲሊ ክሊሞቭ የተባለ ነጋዴ፣ የዕቃ አቅርቦት በመቆሙ ምክንያት ሽያጭ በ50 በመቶ ማሽቆልቆሉን እና ንግዱን ለመሸጥ መገደዱን ተናግሯል። የችግሩን ስፋት በሚያሳይ መልኩ፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ሩሲያ ከ3,100 በላይ የዋይልድቤሪስ የፍራንቻይዝ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በኪሳራ ምክንያት በኦንላይን ገበያ ለሽያጭ ቀርበዋል።
የዚህ ጥቃት ጫና ከአነስተኛ ነጋዴዎች አልፎ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ስጋት ደቅኗል። የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ይህ የአቅርቦት መስተጓጎል የዋጋ ግሽበትን ሊያባብስ እንደሚችል ሲያስጠነቅቅ፣ ትልቁ የሀገሪቱ ባንክ 'ስበርባንክ' በበኩሉ የብድር መክፈል አቅማቸው በተዳከሙ የኦንላይን ቸርቻሪዎች ምክንያት ወደ 300 የሚጠጉ ኩባንያዎች የብድር መክፈያ ጊዜያቸው እንዲራዘምላቸው መጠየቃቸውን አሳውቋል።
ዩክሬን ኩባንያው የሌሊት እይታ መነጽሮችን እና የጥይት መያዣዎችን ጨምሮ ወታደራዊ አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ ቁሳቁሶችን በማቅረብ የሩሲያን ጦር ይደግፋል ስትል ትከሳለች። ይሁን እንጂ ዋይልድቤሪስም ሆነ የሩሲያ መንግስት ኩባንያው ለጦር ኃይሉ አቅርቦት እንደማያደርግ በማስታወቅ ክሱን ያስተባብላሉ። በአደጋው መጋዘን ውስጥ የነበሩ ቢያንስ 13 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ የሩሲያ መንግስት ኪሳራ ለደረሰባቸው ሻጮች የብድር እና የታክስ ድጋፍ ስለማድረግ እየመከረ መሆኑ ተገልጿል።
ከጁላይ 18 ጀምሮ በተከታታይ በተፈጸሙ ጥቃቶች ወደ 20 በሚጠጉ የኩባንያው ግዙፍ ማከማቻዎች ላይ ቃጠሎ የተነሳ ሲሆን፣ የሳተላይት ምስሎች እንደሚያሳዩት ከ1.18 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ (ወይም ከኩባንያው አጠቃላይ አቅም አንድ አምስተኛው) የመጋዘን ቦታ ወድሟል። በዚህም ምክንያት የኩባንያው የሎጂስቲክስ መስመር ክፉኛ በመስተጓጎሉ፣ በገበያ መድረኩ ላይ ጥገኛ የሆኑ ቸርቻሪዎች ምርቶቻቸውን ማቅረብ ተስኗቸዋል።
በሞስኮ የዕቃ መቀበያ ጣቢያ የሚያስተዳድረው ቫሲሊ ክሊሞቭ የተባለ ነጋዴ፣ የዕቃ አቅርቦት በመቆሙ ምክንያት ሽያጭ በ50 በመቶ ማሽቆልቆሉን እና ንግዱን ለመሸጥ መገደዱን ተናግሯል። የችግሩን ስፋት በሚያሳይ መልኩ፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ሩሲያ ከ3,100 በላይ የዋይልድቤሪስ የፍራንቻይዝ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በኪሳራ ምክንያት በኦንላይን ገበያ ለሽያጭ ቀርበዋል።
የዚህ ጥቃት ጫና ከአነስተኛ ነጋዴዎች አልፎ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ስጋት ደቅኗል። የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ይህ የአቅርቦት መስተጓጎል የዋጋ ግሽበትን ሊያባብስ እንደሚችል ሲያስጠነቅቅ፣ ትልቁ የሀገሪቱ ባንክ 'ስበርባንክ' በበኩሉ የብድር መክፈል አቅማቸው በተዳከሙ የኦንላይን ቸርቻሪዎች ምክንያት ወደ 300 የሚጠጉ ኩባንያዎች የብድር መክፈያ ጊዜያቸው እንዲራዘምላቸው መጠየቃቸውን አሳውቋል።
ዩክሬን ኩባንያው የሌሊት እይታ መነጽሮችን እና የጥይት መያዣዎችን ጨምሮ ወታደራዊ አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ ቁሳቁሶችን በማቅረብ የሩሲያን ጦር ይደግፋል ስትል ትከሳለች። ይሁን እንጂ ዋይልድቤሪስም ሆነ የሩሲያ መንግስት ኩባንያው ለጦር ኃይሉ አቅርቦት እንደማያደርግ በማስታወቅ ክሱን ያስተባብላሉ። በአደጋው መጋዘን ውስጥ የነበሩ ቢያንስ 13 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ የሩሲያ መንግስት ኪሳራ ለደረሰባቸው ሻጮች የብድር እና የታክስ ድጋፍ ስለማድረግ እየመከረ መሆኑ ተገልጿል።
6 days ago
ከወርቅ በእጅጉ ውድ የሆነ አዲስ ማዕድን በሩሲያ ተገኘ? ሳይንቲስቶች ምን አገኙ?
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
9 days ago
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ!
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
10 days ago
የዓለም የጸሐፍት ድርጅት (WOW) ዓለም አቀፍ ጉባኤ ዛሬ በአዲስ አበባ ይካሄዳል
ዕዝራ እጅጉ
#ethiopia | በኢትዮጵያውያን ደራሲያን እና በውጭ አገር የሥነ-ጽሑፍ ባለሙያዎች ተሳትፎ የሚካሄደው የዓለም የጸሐፍት ድርጅት (WOW) ዓለም አቀፍ ጉባኤ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል ይካሄዳል።
ጉባኤው "Africa in Shaping a Common Future" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ በአፍሪካ ሥነ-ጽሑፍ፣ ባህላዊ እሴቶች እና የደራሲያን ዓለም አቀፍ ትብብር ዙሪያ የሚያተኩሩ ርዕሰ ጉዳዮች ይቀርባሉ።
በመድረኩ ላይ በአፍሪካ ሥነ-ጽሑፍ ላይ ጥናት ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር አቢይ ዳንኤል የጥናት ወረቀት እንደሚያቀርቡ ሲገለጽ፣ ፀሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱም ከዋና የጽሑፍ አቅራቢዎች መካከል ይገኛሉ።
የድርጅቱ ፕሬዝዳንት ማርጋሪታ አል ለጉባኤው በተለይ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን፣ የጉባኤው ሁሉም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተገልጿል።
ጉባኤው በኢትዮጵያ መካሄዱ የኢትዮጵያ ደራሲያን ከዓለም አቀፍ የሥነ-ጽሑፍ ማኅበረሰብ ጋር ያላቸውን ትስስር በማጠናከር የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል።
በመጽሐፍ ዝግጅትና ሥነ-ጽሑፍ ሥራ ላይ የተሰማራው "ተወዳጅ ሚዲያ እና ኮምዩኒኬሽን" መሥራች ዕዝራ እጅጉን ጨምሮ የዝግጅት ኮሚቴው አባላትም በጉባኤው ይሳተፋሉ ተብሏል።
ስለ WOW
የዓለም የጸሐፍት ድርጅት (WOW) ዓለም አቀፍ ደራሲያንን ለማገናኘት፣ የሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችን ለማበረታታት እና በባህሎች መካከል ውይይትን ለማጠናከር የተቋቋመ ዓለም አቀፍ ማኅበር ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱ በሞስኮ የሚገኝ ሲሆን፣ በፕሬዝዳንት ማርጋሪታ አል ይመራል።
የድርጅቱ የምሥረታ ሀሳብ በ2019 በባኩ፣ አዘርባጃን የቀረበ ሲሆን፣ በ2023 በካይሮ፣ ግብፅ በስምምነት ሰነድ ተመስርቶ በዚያው ዓመት በይፋ ተመዝግቧል። የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ጉባኤውም በ2024 በዓቡጃ፣ ናይጄሪያ ተካሂዶ ነበር።
WOW በአሁኑ ጊዜ አባልነቱን በተለያዩ አገሮች እያስፋፋ ሲሆን፣ የፓናል ውይይቶችን፣ የልጆች የሥነ-ጽሑፍ መድረኮችን እና የጋራ የትርጉም ፕሮጀክቶችን በማካሄድ የዓለም አቀፍ የሥነ-ጽሑፍ ትብብርን ለማጠናከር እየሠራ ነው።
ዕዝራ እጅጉ
#ethiopia | በኢትዮጵያውያን ደራሲያን እና በውጭ አገር የሥነ-ጽሑፍ ባለሙያዎች ተሳትፎ የሚካሄደው የዓለም የጸሐፍት ድርጅት (WOW) ዓለም አቀፍ ጉባኤ ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ10:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ኢሊሊ ሆቴል ይካሄዳል።
ጉባኤው "Africa in Shaping a Common Future" በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ ሲሆን፣ በአፍሪካ ሥነ-ጽሑፍ፣ ባህላዊ እሴቶች እና የደራሲያን ዓለም አቀፍ ትብብር ዙሪያ የሚያተኩሩ ርዕሰ ጉዳዮች ይቀርባሉ።
በመድረኩ ላይ በአፍሪካ ሥነ-ጽሑፍ ላይ ጥናት ያካሄዱት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር አቢይ ዳንኤል የጥናት ወረቀት እንደሚያቀርቡ ሲገለጽ፣ ፀሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱም ከዋና የጽሑፍ አቅራቢዎች መካከል ይገኛሉ።
የድርጅቱ ፕሬዝዳንት ማርጋሪታ አል ለጉባኤው በተለይ ወደ አዲስ አበባ የመጡ ሲሆን፣ የጉባኤው ሁሉም የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸው ተገልጿል።
ጉባኤው በኢትዮጵያ መካሄዱ የኢትዮጵያ ደራሲያን ከዓለም አቀፍ የሥነ-ጽሑፍ ማኅበረሰብ ጋር ያላቸውን ትስስር በማጠናከር የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል።
በመጽሐፍ ዝግጅትና ሥነ-ጽሑፍ ሥራ ላይ የተሰማራው "ተወዳጅ ሚዲያ እና ኮምዩኒኬሽን" መሥራች ዕዝራ እጅጉን ጨምሮ የዝግጅት ኮሚቴው አባላትም በጉባኤው ይሳተፋሉ ተብሏል።
ስለ WOW
የዓለም የጸሐፍት ድርጅት (WOW) ዓለም አቀፍ ደራሲያንን ለማገናኘት፣ የሥነ-ጽሑፍ ሥራዎችን ለማበረታታት እና በባህሎች መካከል ውይይትን ለማጠናከር የተቋቋመ ዓለም አቀፍ ማኅበር ነው። ዋና መሥሪያ ቤቱ በሞስኮ የሚገኝ ሲሆን፣ በፕሬዝዳንት ማርጋሪታ አል ይመራል።
የድርጅቱ የምሥረታ ሀሳብ በ2019 በባኩ፣ አዘርባጃን የቀረበ ሲሆን፣ በ2023 በካይሮ፣ ግብፅ በስምምነት ሰነድ ተመስርቶ በዚያው ዓመት በይፋ ተመዝግቧል። የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ ጉባኤውም በ2024 በዓቡጃ፣ ናይጄሪያ ተካሂዶ ነበር።
WOW በአሁኑ ጊዜ አባልነቱን በተለያዩ አገሮች እያስፋፋ ሲሆን፣ የፓናል ውይይቶችን፣ የልጆች የሥነ-ጽሑፍ መድረኮችን እና የጋራ የትርጉም ፕሮጀክቶችን በማካሄድ የዓለም አቀፍ የሥነ-ጽሑፍ ትብብርን ለማጠናከር እየሠራ ነው።
15 days ago
ከ700 በላይ የዓለም መሪዎችንና ፈጣሪዎችን የሚያሰባስበው ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው!
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
Sponsored by
Surafel
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሴርጌይ ላቭሮቭ እና የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በፊሊፒንስ ማኒላ በተካሄደው የአሴያን ቀጠናዊ ፎረም ጎን ለጎን ባደረጉት ስብሰባ፣ በዩክሬን ግጭት እና በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ መደበኛ ሁኔታ በመመለስ ዙሪያ መምከራቸውን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ሴርጌይ ላቭሮቭ ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት በፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ዝግጁነት በድጋሚ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ሞስኮ በነሐሴ 2025 (እ.ኤ.አ.) በአላስካ በተካሄደው ጉባኤ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በፕሬዝዳንት ቪላዲሚር ፑቲን የቀረቡትን የመፍትሔ ሀሳቦች አሁንም እንደምትቀበልና እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
ሁለቱ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በቀጣይም በሁለቱ አገራት እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉትን ግንኙነትና ውይይት አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን መግለጫው አክሎ አመልክቷል።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ሴርጌይ ላቭሮቭ ሩሲያ የዩክሬንን ግጭት በፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ያላትን ዝግጁነት በድጋሚ ያረጋገጡ ሲሆን፤ ሞስኮ በነሐሴ 2025 (እ.ኤ.አ.) በአላስካ በተካሄደው ጉባኤ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በፕሬዝዳንት ቪላዲሚር ፑቲን የቀረቡትን የመፍትሔ ሀሳቦች አሁንም እንደምትቀበልና እንደምትደግፍ ገልጸዋል።
ሁለቱ ከፍተኛ ዲፕሎማቶች በቀጣይም በሁለቱ አገራት እና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉትን ግንኙነትና ውይይት አጠናክረው ለመቀጠል መስማማታቸውን መግለጫው አክሎ አመልክቷል።
17 days ago
የፑቲን "ስውሯ ልጅ" በፓሪስ መሸታ ቤቶች እየሰራች ነው ተባለ
#ethiopia | የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድብቅ ልጅ እንደሆነች የሚነገርላት ኤሊዛቬታ ክሪቮኖጊክ (ሉኢዛ ሮዞቫ) ከሞስኮ የሥልጣን ማዕከል ርቃ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ውስጥ ፍጹም የተለየ ሕይወት እየመራች ይገኛል።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በይፋ አባትነታቸውን አምነው ተቀብለው ባያውቁም እና ጉዳዩ በይፋ ባይረጋገጥም የተሾለኩ ሰነዶችና የምርመራ ዘገባዎች ግን የጉዞ መረጃዎቿን ዋቢ በማድረግ ደምድመዋል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ለጉዳዩ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ አለመስጠቱም የታሪኩን ምስጢራዊነት ይበልጥ አጉልቶታል።
ይህች አወዛጋቢ ወጣት በፓሪስ የስነ-ጥበብ እና የባህል አስተዳደር ትምህርቷን የተከታተለች ሲሆን በምሽት ቤቶች ውስጥ ከመስራቷም በላይ በተለያዩ ስሞች በዲጄነት የሙዚቃ አጫዋችነት ሙያ ላይ ተሰማርታ ትገኛለች።
አባቷ ተብሎ የሚገመቱት ፑቲን የዓለማችንን ኃያል ሀገር ሩሲያን ከክሬምሊን ሆነው በብረት እጅ ሲመሩ እሷ ግን ማንነቷን ደብቃ በፓሪስ የምሽት ክለቦችና በስነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ አዲስ ሕይወት መገንባቷ እጅግ አስደናቂ ንፅፅርን ፈጥሯል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ድብቅ ልጅ እንደሆነች የሚነገርላት ኤሊዛቬታ ክሪቮኖጊክ (ሉኢዛ ሮዞቫ) ከሞስኮ የሥልጣን ማዕከል ርቃ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ ውስጥ ፍጹም የተለየ ሕይወት እየመራች ይገኛል።
ምንም እንኳን ፕሬዝዳንቱ በይፋ አባትነታቸውን አምነው ተቀብለው ባያውቁም እና ጉዳዩ በይፋ ባይረጋገጥም የተሾለኩ ሰነዶችና የምርመራ ዘገባዎች ግን የጉዞ መረጃዎቿን ዋቢ በማድረግ ደምድመዋል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ለጉዳዩ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ አለመስጠቱም የታሪኩን ምስጢራዊነት ይበልጥ አጉልቶታል።
ይህች አወዛጋቢ ወጣት በፓሪስ የስነ-ጥበብ እና የባህል አስተዳደር ትምህርቷን የተከታተለች ሲሆን በምሽት ቤቶች ውስጥ ከመስራቷም በላይ በተለያዩ ስሞች በዲጄነት የሙዚቃ አጫዋችነት ሙያ ላይ ተሰማርታ ትገኛለች።
አባቷ ተብሎ የሚገመቱት ፑቲን የዓለማችንን ኃያል ሀገር ሩሲያን ከክሬምሊን ሆነው በብረት እጅ ሲመሩ እሷ ግን ማንነቷን ደብቃ በፓሪስ የምሽት ክለቦችና በስነ-ጥበብ ዓለም ውስጥ አዲስ ሕይወት መገንባቷ እጅግ አስደናቂ ንፅፅርን ፈጥሯል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
18 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሰሜን ኮሪያ እና የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሞስኮ ተገናኝተው መወያየታቸውን ተከትሎ፣ ፕዮንግያንግ በዩክሬን ላይ ለምታካሂደው ጦርነት ለሞስኮ ያላትን ሙሉና ፅኑ ድጋፍ በድጋሚ ማረጋገጧን የሀገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ይህ ስብሰባ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቅርቡ ክሬምሊንን ሊጎበኙ ይችላሉ የሚለውን ግምት ከፍ አድርጎታል።
በዲፕሎማሲው መስክ የተገለሉት ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ፣ እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ ወረራ ከሰነዘረችበት ጊዜ ጀምሮ በመካከላቸው ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር በከፍተኛ ፍጥነት እያሰፉት ይገኛሉ። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚያስረዱት፣ ፕዮንግያንግ የጦር ግንባር በሆነችው የሩሲያ ኩርስክ (Kursk) ግዛት ውስጥ የጦር ሰራዊት ያሰማራች ሲሆን፣ ለሞስኮም የተለያዩ የጦር መሣሪያ ሥርዓቶችን አቅርባለች። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ያደረገችው ከሩሲያ የምታገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ፣ የምግብ፣ የኃይል አቅርቦት እና የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋስትና ለማረጋገጥ ነው።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቾይ ሶን ሁዪ ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሞስኮ ካደረጉት ስብሰባ በኋላ፣ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት በረጅም ጊዜ እና በዘርፈ ብዙ መስኮች ይበልጥ ለማፋጠን ያላቸውን "የማይናወጥ የፖለቲካ ፍላጎት" በድጋሚ ማረጋገጣቸውን የፕዮንግያንግ መንግሥት ሚዲያ ዘግቧል። በሌላ በኩል ሩሲያ፣ ሰሜን ኮሪያ ሉዓላዊነቷን እና ደኅንነቷን ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት ሙሉ ድጋፏን መግለጿ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
በዲፕሎማሲው መስክ የተገለሉት ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ፣ እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ ወረራ ከሰነዘረችበት ጊዜ ጀምሮ በመካከላቸው ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር በከፍተኛ ፍጥነት እያሰፉት ይገኛሉ። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚያስረዱት፣ ፕዮንግያንግ የጦር ግንባር በሆነችው የሩሲያ ኩርስክ (Kursk) ግዛት ውስጥ የጦር ሰራዊት ያሰማራች ሲሆን፣ ለሞስኮም የተለያዩ የጦር መሣሪያ ሥርዓቶችን አቅርባለች። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ያደረገችው ከሩሲያ የምታገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ፣ የምግብ፣ የኃይል አቅርቦት እና የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋስትና ለማረጋገጥ ነው።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቾይ ሶን ሁዪ ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሞስኮ ካደረጉት ስብሰባ በኋላ፣ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት በረጅም ጊዜ እና በዘርፈ ብዙ መስኮች ይበልጥ ለማፋጠን ያላቸውን "የማይናወጥ የፖለቲካ ፍላጎት" በድጋሚ ማረጋገጣቸውን የፕዮንግያንግ መንግሥት ሚዲያ ዘግቧል። በሌላ በኩል ሩሲያ፣ ሰሜን ኮሪያ ሉዓላዊነቷን እና ደኅንነቷን ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት ሙሉ ድጋፏን መግለጿ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
21 days ago
ዩክሬይን በሁለት የሩስያ ግዛቶች ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃቶች 8 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የሩስያ ባለስላጣናት አስታወቁ።
በጥቃቱ ከ60 በላይ መቁሰላቸውንም አክሏል። ጥቃቱ ኮቶቭስክ በተባለች በዩክሬይን ድንበር አቅራቢያ በምትገኝ ከተማና ከሞስኮ በስተምስራቅ 50 ኪሎሜትሮችን ርቃ በምትገኝ ኤሌክትሮስታል በተባለች ከተማ ውስጥ ነው ተብሏል። ከከአካባቢው የወጡ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ከፍተኛ ፍንዳታና ቃጠሎ እንደነበረ አመላክቷል።የሞስኮ ክልል ገዥ አንድሬይ ቮሮቢዮቭ እንደገለፁት ጥቃቱ የተፈፀመው በከተማዋ ዋይልድቤሪ በተባለው የሩሲያ ኩባንያ መጋዘን ሲሆን የተጎዱትም የሌሊት ተረኛ የመጋዘን ሰራተኞችን ናቸው።የዋይልድቤሪስ ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ታትያና ኪም ለሩሲያ እና ለኩባንያው "አስፈሪ ምሽት" እንደነበር ተናግረዋል። ለተጎጂዎቹ ቤተሰቦችም ሀዘናቸውን ገልጸዋል።
ሮይተርስ የዜና ምንጭ እንደዘገበው የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ኪየቭ ሩሲያ ድሮን ለማምረት ፣ ለማሰስ እና መሳሪያዎችን ለማቅረብ የምትጠቀምባቸውን ሁለት የሎጂስቲክስ ተቋማት መምታቷን ዛሬ ቅዳሜ ገልፀዋል። በጥቃቱ የነዳጅ ተቋምም መመታቱን ዘለንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ ጽፈዋል።
DW Amharic
በጥቃቱ ከ60 በላይ መቁሰላቸውንም አክሏል። ጥቃቱ ኮቶቭስክ በተባለች በዩክሬይን ድንበር አቅራቢያ በምትገኝ ከተማና ከሞስኮ በስተምስራቅ 50 ኪሎሜትሮችን ርቃ በምትገኝ ኤሌክትሮስታል በተባለች ከተማ ውስጥ ነው ተብሏል። ከከአካባቢው የወጡ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ከፍተኛ ፍንዳታና ቃጠሎ እንደነበረ አመላክቷል።የሞስኮ ክልል ገዥ አንድሬይ ቮሮቢዮቭ እንደገለፁት ጥቃቱ የተፈፀመው በከተማዋ ዋይልድቤሪ በተባለው የሩሲያ ኩባንያ መጋዘን ሲሆን የተጎዱትም የሌሊት ተረኛ የመጋዘን ሰራተኞችን ናቸው።የዋይልድቤሪስ ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ታትያና ኪም ለሩሲያ እና ለኩባንያው "አስፈሪ ምሽት" እንደነበር ተናግረዋል። ለተጎጂዎቹ ቤተሰቦችም ሀዘናቸውን ገልጸዋል።
ሮይተርስ የዜና ምንጭ እንደዘገበው የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ኪየቭ ሩሲያ ድሮን ለማምረት ፣ ለማሰስ እና መሳሪያዎችን ለማቅረብ የምትጠቀምባቸውን ሁለት የሎጂስቲክስ ተቋማት መምታቷን ዛሬ ቅዳሜ ገልፀዋል። በጥቃቱ የነዳጅ ተቋምም መመታቱን ዘለንስኪ በኤክስ ገፃቸው ላይ ጽፈዋል።
DW Amharic
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹በሞስኮ 1000 ድሮን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል›› ሲሉ ዘለንስኪ ገለፁ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ከፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ከሩሲያ ጋር የሚደረገውን ጦርነት ውጤት የሚለውጠው በአየር የበላይነት መያዝ መሆኑን አስታወቁ፡፡
ፕሬዝደንቱ በጦርነቱ በባህር ሀይልና በምድር ጦር ድል መቀዳጀታቸውን ጠቅሰው ወሳኙና ቀጣዩ በአየር ሀይል የበላይነት መቀዳጀት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በዚህ ጦርነት አሸናፊ የሚሆነው ብልህ እንደሆነ አምናለሁ›› ያሉት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹በጦር ሜዳ ላይ ጠላት እንዳይንቀሳቀስ ካደረከው በምድር ጦር የበላይነት ይዘህ አቁመኸዋል ማለት ነው፡፡ የሩሲያን መርከቦች በባህር ድሮኖቻችን እንዳይንቀሳቀሱ እንዳደረግነው በባህር ሀይልም የበላይነትን ጨብጠናል፡፡ ስለዚህም አሁን የሚቀረን ሰማዩ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ‹‹በዚህ በሰማይ ላይ በሚደረግ ውድድር ማን ሰፊ ግዛት አለው የሚለው አይሰራም፡፡ በፊቱንም ተፎካካሪ እንደነበርነው ሁሉ አሁን ወደዚያ ገብተናል›› ካሉ በኋላ ዩክሬይን ረጅም ርቀት ላይ የማጥቃት አቅሟ እየተጠናከረ መምጣቱን ገልፀው አንድ ድክመት እንዳለባት ግን አልሸሸጉም፡፡ እንዳስረዱትም እሱም ፀረ ሚሳኤል መከላከያ ነው፡፡ ፓትሪዮት ፓክ 3 የተሰኙት እነዚህ መከላከያዎች እያጠሯቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹አውሮፓ በዚህ ረገድ የምታሳየውን ቸልተኝነት ማቆም አለባት፡፡ ቴክኖሎጂዎችንና የኢንዱስትሪ አቅሟን ከሌሎች አገራት ጋር መጋራት ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም ለሁሉም የሚበቃ ፓትሪዮት ሚሳኤል አይኖርም›› ብለዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳብራሩት ፓትሪዮት ሚሳኤሎችን የምታመርተው አሜሪካ ብቻ ስትሆን ይህ ሚሳኤል በአውሮፓ ውስጥ እንዲመረት ፈቃድ ልትሰጥ ይገባታል፡፡ አውሮፓውያንም ከአሜሪካ ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ጥያቄ ማቅረብና መወትወት እንዳለባቸው አሳስበው ዩክሬይን በራሷ መንገድ ለአሜሪካ ጥያቄውን ማቅረቧን አስታውቀዋል፡፡
አገራቸው በክሬሚያ ግዛት ውስጥ የምታደርገውን ረጅም ርቀት ጥቃት እንደምትቀጥል የገለፁት ዘለንስኪ ኢላማቸውም ወታደራዊ ማእከላት፣ የነዳጅ ዴፖዎች፣ የአየር መቃወሚያዎችና የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉትም ሩሲያ በሀይል ዘርፍና በወደብ መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት ከደረሰባት በኋላ ወታደራዊ ተቋሞቿን በክሬሚያ ስላሰፈረች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም በዋና ከተማ ሞስኮ ላይ ጥቃት የመቀጠል እቅድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ እንደፕሬዝደንቱ ገለፃ የክሬሚሊን መሪው ጥቃቱ ሞስኮና ሴንት ፒትስበርግ እስከሚደርስ ድረስ ብዙም አላሳሰባቸውም ነበር፡፡
ጨምረውም ‹‹ፑቲን ክሬሚሊን በጣም ሩቅ ቦታ እንደሆነ አስቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ሞስኮ ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን ሲሰማ ስሜቱ እየገባው መጥቷል›› ካሉ በኋላ በቀጣይነት የሚያደርጉት ጥቃት የበለጠ ፑቲን የጦርነቱን እውነታ እንዲጋፈጡ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አስከትለውም ‹‹በሞስኮ ላይ በመቶዎች አይደለም በሺህ የሚቆጠሩ ድሮኖችን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል፡፡ እኛ ወደሞስኮ እጅግ በቀረብን ቁጥር ጦርነቱን ለማቆም አዲስ ምእራፍ ይከፈታል፡፡ ፑቲንም የራሱን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል ሰላምን ይመርጣል›› በማለት አስረድተዋል፡፡
ፕሬዝደንቱ በጦርነቱ በባህር ሀይልና በምድር ጦር ድል መቀዳጀታቸውን ጠቅሰው ወሳኙና ቀጣዩ በአየር ሀይል የበላይነት መቀዳጀት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በዚህ ጦርነት አሸናፊ የሚሆነው ብልህ እንደሆነ አምናለሁ›› ያሉት ዘለንስኪ ጨምረውም ‹‹በጦር ሜዳ ላይ ጠላት እንዳይንቀሳቀስ ካደረከው በምድር ጦር የበላይነት ይዘህ አቁመኸዋል ማለት ነው፡፡ የሩሲያን መርከቦች በባህር ድሮኖቻችን እንዳይንቀሳቀሱ እንዳደረግነው በባህር ሀይልም የበላይነትን ጨብጠናል፡፡ ስለዚህም አሁን የሚቀረን ሰማዩ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ‹‹በዚህ በሰማይ ላይ በሚደረግ ውድድር ማን ሰፊ ግዛት አለው የሚለው አይሰራም፡፡ በፊቱንም ተፎካካሪ እንደነበርነው ሁሉ አሁን ወደዚያ ገብተናል›› ካሉ በኋላ ዩክሬይን ረጅም ርቀት ላይ የማጥቃት አቅሟ እየተጠናከረ መምጣቱን ገልፀው አንድ ድክመት እንዳለባት ግን አልሸሸጉም፡፡ እንዳስረዱትም እሱም ፀረ ሚሳኤል መከላከያ ነው፡፡ ፓትሪዮት ፓክ 3 የተሰኙት እነዚህ መከላከያዎች እያጠሯቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹አውሮፓ በዚህ ረገድ የምታሳየውን ቸልተኝነት ማቆም አለባት፡፡ ቴክኖሎጂዎችንና የኢንዱስትሪ አቅሟን ከሌሎች አገራት ጋር መጋራት ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም ለሁሉም የሚበቃ ፓትሪዮት ሚሳኤል አይኖርም›› ብለዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳብራሩት ፓትሪዮት ሚሳኤሎችን የምታመርተው አሜሪካ ብቻ ስትሆን ይህ ሚሳኤል በአውሮፓ ውስጥ እንዲመረት ፈቃድ ልትሰጥ ይገባታል፡፡ አውሮፓውያንም ከአሜሪካ ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ጥያቄ ማቅረብና መወትወት እንዳለባቸው አሳስበው ዩክሬይን በራሷ መንገድ ለአሜሪካ ጥያቄውን ማቅረቧን አስታውቀዋል፡፡
አገራቸው በክሬሚያ ግዛት ውስጥ የምታደርገውን ረጅም ርቀት ጥቃት እንደምትቀጥል የገለፁት ዘለንስኪ ኢላማቸውም ወታደራዊ ማእከላት፣ የነዳጅ ዴፖዎች፣ የአየር መቃወሚያዎችና የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች እንደሚሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህንን የሚያደርጉትም ሩሲያ በሀይል ዘርፍና በወደብ መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት ከደረሰባት በኋላ ወታደራዊ ተቋሞቿን በክሬሚያ ስላሰፈረች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም በዋና ከተማ ሞስኮ ላይ ጥቃት የመቀጠል እቅድ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ እንደፕሬዝደንቱ ገለፃ የክሬሚሊን መሪው ጥቃቱ ሞስኮና ሴንት ፒትስበርግ እስከሚደርስ ድረስ ብዙም አላሳሰባቸውም ነበር፡፡
ጨምረውም ‹‹ፑቲን ክሬሚሊን በጣም ሩቅ ቦታ እንደሆነ አስቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ሞስኮ ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን ሲሰማ ስሜቱ እየገባው መጥቷል›› ካሉ በኋላ በቀጣይነት የሚያደርጉት ጥቃት የበለጠ ፑቲን የጦርነቱን እውነታ እንዲጋፈጡ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አስከትለውም ‹‹በሞስኮ ላይ በመቶዎች አይደለም በሺህ የሚቆጠሩ ድሮኖችን ስናበር የፑቲን ካልኩሌሽን ይለወጣል፡፡ እኛ ወደሞስኮ እጅግ በቀረብን ቁጥር ጦርነቱን ለማቆም አዲስ ምእራፍ ይከፈታል፡፡ ፑቲንም የራሱን ደህንነት ለመጠበቅ ሲል ሰላምን ይመርጣል›› በማለት አስረድተዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢትዮጵያ በሩሲያ የቪዛ ነፃ የጉዞ ሥርዓት ድርድር ውስጥ ተካታ ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ
#ethiopia | የሩሲያ መንግሥት ከአፍሪካ አገራት ጋር ያለውን የዲፕሎማሲ፣ የንግድ እና የዜጎች የጉዞ ግንኙነት ይበልጥ ለማሳለጥ በማሰብ፣ ከበርካታ የአህጉሪቱ አገራት ጋር ከቪዛ ነፃ የጉዞ ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ውይይቶችን እያደረገ መሆኑን የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር አሌክሲ ክሊሞቭ ለስፑትኒክ የዜና ወኪል እንደገለጹት፤ ሩሲያ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ዕድልን ለማስፋፋት ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ጋር በድርድር ላይ ትገኛለች። ይሁን እንጂ ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ድረስ በይፋ የተጠናቀቀ እና ፊርማ ያረፈበት የስምምነት ሰነድ አለመኖሩን አብራርተዋል።
ይህ የሩሲያ እንቅስቃሴ ሞስኮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትስስር ለማሳደግ የምታደርገው ሰፋ ያለ ስትራቴጂ አካል መሆኑን የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
በአሁኑ ወቅት ለሩሲያ ዜጎች ከቪዛ ነፃ የሆኑ የአፍሪካ አገራት አሁን ባለው መረጃ መሠረት 11 የአፍሪካ አገራት ለሩሲያ ዜጎች ከቪዛ ነፃ የመጓዝ ዕድልን ፈቅደዋል። እነዚህም አገራት የሚከተሉት ናቸው፡-
🇲🇦 ሞሮኮ
🇹🇳 ቱኒዚያ
🇳🇦 ናሚቢያ
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇧🇼 ቦትስዋና
🇦🇴 አንጎላ
🇲🇺 ሞሪሸስ
🇸🇨 ሲሼልስ
🇨🇻 ኬፕ ቨርዴ
🇸🇹 ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ
🇸🇿 ኤስዋቲኒ
Credit : spuntik
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የሩሲያ መንግሥት ከአፍሪካ አገራት ጋር ያለውን የዲፕሎማሲ፣ የንግድ እና የዜጎች የጉዞ ግንኙነት ይበልጥ ለማሳለጥ በማሰብ፣ ከበርካታ የአህጉሪቱ አገራት ጋር ከቪዛ ነፃ የጉዞ ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ውይይቶችን እያደረገ መሆኑን የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር አሌክሲ ክሊሞቭ ለስፑትኒክ የዜና ወኪል እንደገለጹት፤ ሩሲያ ከቪዛ ነፃ የጉዞ ዕድልን ለማስፋፋት ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ጋር በድርድር ላይ ትገኛለች። ይሁን እንጂ ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ድረስ በይፋ የተጠናቀቀ እና ፊርማ ያረፈበት የስምምነት ሰነድ አለመኖሩን አብራርተዋል።
ይህ የሩሲያ እንቅስቃሴ ሞስኮ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ትስስር ለማሳደግ የምታደርገው ሰፋ ያለ ስትራቴጂ አካል መሆኑን የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
በአሁኑ ወቅት ለሩሲያ ዜጎች ከቪዛ ነፃ የሆኑ የአፍሪካ አገራት አሁን ባለው መረጃ መሠረት 11 የአፍሪካ አገራት ለሩሲያ ዜጎች ከቪዛ ነፃ የመጓዝ ዕድልን ፈቅደዋል። እነዚህም አገራት የሚከተሉት ናቸው፡-
🇲🇦 ሞሮኮ
🇹🇳 ቱኒዚያ
🇳🇦 ናሚቢያ
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇧🇼 ቦትስዋና
🇦🇴 አንጎላ
🇲🇺 ሞሪሸስ
🇸🇨 ሲሼልስ
🇨🇻 ኬፕ ቨርዴ
🇸🇹 ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ
🇸🇿 ኤስዋቲኒ
Credit : spuntik
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
ጋዜጠኛ ያልተቀጠረለት ምስጥራዊው የሩሲያ የሬዲዮ ጣቢያ
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዘለንስኪ በ‹‹ፍላሚንጎ›› ሚሳኤል ሩሲያ ውስጥ ዘልቀው ገብተው ጥቃት ማድረሳቸውን አስታወቁ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በምስራቃዊ ሞስኮ በሚገኝ አንድ ወታደራዊ ፋብሪካ ላይ ጥቃት መፈፀማቸውን ገለፁ፡፡ ፕሬዝደንቱ እንዳሉት ይህ ጥቃት የተፈፀመው ዩክሬይን በአገር ውስጥ በሰራችው ሚሳኤል ነው፡፡
ሲናገሩም ‹‹ለሊቱን ዩክሬይን ሰራሽ በሆነው ኤፍፒ 5 ፍላሚንጎ ሚሳኤል በቼቦስካሪ ከተማ ያለ ወታደራዊ ፋብሪካ ላይ ጥቃት አድርሰናል፡፡ ይህ ፋብሪካ ለሩሲያ መከላከያ ሀይል የድሮንና ሚሳኤል መለዋወጫዎችን የሚያመርት ነው›› ብለዋል፡፡ አያይዘውም ወደዚህ ፋብሪካ አንድ ሚሳኤል ሲወነጨፍ የሚያሳይና የቃጠሎ ምስሎችን አቅርበዋል፡፡ ቼቦስካሪ ከተማ ከዩክሬይን ድንበር በ1000 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህንን ጥቃት የአካባቢው ባለስልጣናት አረጋግጠው የደረሰውን ጉዳት እያጣሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ሲናገሩም ‹‹ለሊቱን ዩክሬይን ሰራሽ በሆነው ኤፍፒ 5 ፍላሚንጎ ሚሳኤል በቼቦስካሪ ከተማ ያለ ወታደራዊ ፋብሪካ ላይ ጥቃት አድርሰናል፡፡ ይህ ፋብሪካ ለሩሲያ መከላከያ ሀይል የድሮንና ሚሳኤል መለዋወጫዎችን የሚያመርት ነው›› ብለዋል፡፡ አያይዘውም ወደዚህ ፋብሪካ አንድ ሚሳኤል ሲወነጨፍ የሚያሳይና የቃጠሎ ምስሎችን አቅርበዋል፡፡ ቼቦስካሪ ከተማ ከዩክሬይን ድንበር በ1000 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህንን ጥቃት የአካባቢው ባለስልጣናት አረጋግጠው የደረሰውን ጉዳት እያጣሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
2 months ago
የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል በሮምና ሞስኮ...
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።
አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።
አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡
በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።
የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ÷ አትሌት ሂርኮ ኃይሉ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል።
የ2026 ዳይመንድ ሊግ 4ኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የመጀመሪያዎቹን ሰባት ደረጃዎች በመቆጣጠር ጨርሰዋል፡፡
አትሌት ልቅና አምባው 14፡18፡41 የሆነ የወቅቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ባለድል ሆናለች።
FBC
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።
አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።
አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡
በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።
የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ÷ አትሌት ሂርኮ ኃይሉ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል።
የ2026 ዳይመንድ ሊግ 4ኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የመጀመሪያዎቹን ሰባት ደረጃዎች በመቆጣጠር ጨርሰዋል፡፡
አትሌት ልቅና አምባው 14፡18፡41 የሆነ የወቅቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ባለድል ሆናለች።
FBC
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የኢትዮጵያ አትሌቶች በሞስኮ የደመቀ ድል አስመዘገቡ
#ethiopia | በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በተካሄደው የ2026 የዝናሜንስኪ ሜሞሪያል የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ከፍተኛ የበላይነት በመቀዳጀት አራት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ስምንት ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው አበርክተዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ፉክክር አትሌት ብርቄ ኃይሎም አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ስታሸንፍ ሳሮን በርሔ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በተመሳሳይ በሴቶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ፈንታዬ ጫኔ፣ ቤተልሄም ኦላና እና ሰላማዊት ሻምበል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር የሀገራቸውን የበላይነት አስመስክረዋል።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር የመስመር ውድድር አትሌት እዮብ ስመኝ የሩሲያ አትሌቶችን አስከራሪ ፉክክር በመስበር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን የቻለ ሲሆን ሽመልስ ንጉሴ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ የወጣበት ነበር።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ዲንቃ ፍቃዱ ቀዳሚ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያጠልቅ ሂርኮ ኃይሉ ሶስተኛ ሆኖ አጠናቋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ የብር ሜዳሊያ ያስገኘች ሲሆን በ800 ሜትር የሴቶች ማጣሪያ ሀብታም ገበየሁ ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ፈጽማለች።
#ethiopianathletics #znamenskymemorial2026 #ethiopianpride #runningchampions #greenflood #moscow2026 #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በተካሄደው የ2026 የዝናሜንስኪ ሜሞሪያል የዓለም አትሌቲክስ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ከፍተኛ የበላይነት በመቀዳጀት አራት የወርቅ፣ ሁለት የብር እና ሁለት የነሐስ በድምሩ ስምንት ሜዳሊያዎችን ለሀገራቸው አበርክተዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ፉክክር አትሌት ብርቄ ኃይሎም አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ስታሸንፍ ሳሮን በርሔ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በተመሳሳይ በሴቶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ፈንታዬ ጫኔ፣ ቤተልሄም ኦላና እና ሰላማዊት ሻምበል ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ያለውን ደረጃ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር የሀገራቸውን የበላይነት አስመስክረዋል።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር የመስመር ውድድር አትሌት እዮብ ስመኝ የሩሲያ አትሌቶችን አስከራሪ ፉክክር በመስበር የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን የቻለ ሲሆን ሽመልስ ንጉሴ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ የወጣበት ነበር።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ዲንቃ ፍቃዱ ቀዳሚ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ሲያጠልቅ ሂርኮ ኃይሉ ሶስተኛ ሆኖ አጠናቋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ የብር ሜዳሊያ ያስገኘች ሲሆን በ800 ሜትር የሴቶች ማጣሪያ ሀብታም ገበየሁ ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ፈጽማለች።
#ethiopianathletics #znamenskymemorial2026 #ethiopianpride #runningchampions #greenflood #moscow2026 #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።
የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።
የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።
ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡
ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar
2 months ago
"ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእኔ ጋር ፊት ለፊት ይወያዩ" - ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
3 months ago
አትሌት አበባ አረጋዊ በኦታዋ ማራቶን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጻፈች
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
Sponsored by
Surafel
3 months ago
#ethiopia | የኢህአፓና የምርጫ ቦርድ ፍጥጫ | ለመንግስት ፍትሕ የጠየቁት አባት | የጀርመን ማስጠንቀቂያ | የሞስኮና ቤጂንግ ወዳጅነት
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ፣ ሞስኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለሚደረጉ ማናቸውም የሰላም ድርድሮች አስፈላጊውን እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሰርጌይ ራያብኮቭ አስታወቁ።
ምክትል ሚኒስትሩ አክለውም ሩሲያ ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ቢኖራትም፣ ፍላጎቷን ግን በሁለቱ ወገኖች ላይ በግድ የመጫን እቅድ እንደሌላት በግልጽ ተናግረዋል።
ሰርጌይ ራያብኮቭ ከሀገሪቱ የመንግስት የዜና ወኪል ታስ (TASS) ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ፣ "ይህንን ግጭት ለመፍታት ሩሲያ ሊደረግ የሚችለውን ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተፋላሚዎቹ ወገኖች በሚገባ ያውቃሉ። በተመሳሳይ ጊዜ እኛ አገልግሎታችንን በነሱ ላይ በፍጹም ጭነን አናውቅም፤ የመጫንም ፍላጎት የለንም። ነገር ግን ተገቢው ጥያቄ ከቀረበልን የመርጃ እጃችንን እንዘረጋለን" ብለዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ ሞስኮ ሁልጊዜም ቢሆን ለችግሮች መፍትሄ የሚገኘው በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ ነው የሚል ፅኑ እምነት እንዳላት እና አሁንም ለዚህ ቁርጠኛ መሆኗን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን የድርድር ሂደቱን ለመቀጠል እያደረጉ ያሉትን ሙከራዎች ሩሲያ እንደምትደግፍ የገለጹት ራያብኮቭ፣ በተለይም በአካባቢው መረጋጋት እንዲሰፍን እና ለዘላቂ ሰላም ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የፓኪስታን ወገን እያጫወተ ያለውን ንቁ እና አዎንታዊ ሚና አድንቀዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ አክለውም ሩሲያ ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ቢኖራትም፣ ፍላጎቷን ግን በሁለቱ ወገኖች ላይ በግድ የመጫን እቅድ እንደሌላት በግልጽ ተናግረዋል።
ሰርጌይ ራያብኮቭ ከሀገሪቱ የመንግስት የዜና ወኪል ታስ (TASS) ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ፣ "ይህንን ግጭት ለመፍታት ሩሲያ ሊደረግ የሚችለውን ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተፋላሚዎቹ ወገኖች በሚገባ ያውቃሉ። በተመሳሳይ ጊዜ እኛ አገልግሎታችንን በነሱ ላይ በፍጹም ጭነን አናውቅም፤ የመጫንም ፍላጎት የለንም። ነገር ግን ተገቢው ጥያቄ ከቀረበልን የመርጃ እጃችንን እንዘረጋለን" ብለዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ ሞስኮ ሁልጊዜም ቢሆን ለችግሮች መፍትሄ የሚገኘው በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ ነው የሚል ፅኑ እምነት እንዳላት እና አሁንም ለዚህ ቁርጠኛ መሆኗን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን የድርድር ሂደቱን ለመቀጠል እያደረጉ ያሉትን ሙከራዎች ሩሲያ እንደምትደግፍ የገለጹት ራያብኮቭ፣ በተለይም በአካባቢው መረጋጋት እንዲሰፍን እና ለዘላቂ ሰላም ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የፓኪስታን ወገን እያጫወተ ያለውን ንቁ እና አዎንታዊ ሚና አድንቀዋል።
3 months ago
ዩክሬን ድሮኔ መንገድ ስቶ ኢስቶኒያ በመግባቱ ይቅታ ጠይቃለሁ አለች
#ethiopia | የዩክሬን የጦር ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) በስህተት የኢስቶኒያን የአየር ክልል ጥሶ መግባቱን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ያስታወቀ ሲሆን፥ ድሮኑም በኔቶ የፀረ-አየር መከላከያ መትቶ መጣሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄሮይሂ ትይኪ በኤክስ (X) ማህበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “ኢስቶኒያን ይቅርታ እንጠይቃለን” በማለት ይፋዊ ይቅርታ ጠይቀዋል።
ነገር ግን ለተፈጠረው የቴክኒክ ስህተት ሩሲያን ተጠያቂ ያደረጉት ሚኒስትሩ፥ “ሞስኮ ሆን ብላ የድሮኑን አቅጣጫ እንዲቀይር አድርጋለች” ሲሉ ክስ ሰንዝረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ዩክሬን #ኢስቶኒያ #ኔቶ #ሩሲያ #የአየር_ክልል_ጥሰት #meduza #thiqaheth
#ethiopia | የዩክሬን የጦር ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) በስህተት የኢስቶኒያን የአየር ክልል ጥሶ መግባቱን የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ያስታወቀ ሲሆን፥ ድሮኑም በኔቶ የፀረ-አየር መከላከያ መትቶ መጣሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄሮይሂ ትይኪ በኤክስ (X) ማህበራዊ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “ኢስቶኒያን ይቅርታ እንጠይቃለን” በማለት ይፋዊ ይቅርታ ጠይቀዋል።
ነገር ግን ለተፈጠረው የቴክኒክ ስህተት ሩሲያን ተጠያቂ ያደረጉት ሚኒስትሩ፥ “ሞስኮ ሆን ብላ የድሮኑን አቅጣጫ እንዲቀይር አድርጋለች” ሲሉ ክስ ሰንዝረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ዩክሬን #ኢስቶኒያ #ኔቶ #ሩሲያ #የአየር_ክልል_ጥሰት #meduza #thiqaheth
3 months ago
ሩሲያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀች‼️
የዩክሬን ድሮኖች በራይዛን የነዳጅ ማጣሪያ ላይ በፈጸሙት ጥቃት ከፍተኛ ውድመት መድረሱንና ስትራቴጂካዊ በሆኑ ቀጠናዎች ላይ የእሳት አደጋ መከሰቱን ተከትሎ፣ የሩሲያ ባለሥልጣናት በአንዱ ተጎጂ ከተማ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጀዋል።
በተመሳሳይ ወቅት ሞስኮ በዩክሬን ይዞታዎች ላይ አዳዲስ ጥቃቶችን የሰነዘረች ሲሆን፣ ሁለቱም ወገኖች ከጠላት የጦር ግንባር በስተጀርባ ባሉ ጥልቅ ይዞታዎች ላይ ረጅም ርቀት በሚጓዙ ድሮኖችና ትክክለኛ ኢላማቸውን በሚመቱ ጥቃቶች ላይ ይበልጥ መተማመናቸውን ተከትሎ በተለያዩ ግንባሮች ላይ ያለው ጫና በርትቷል።
እየተባባሰ የመጣው የጥቃት ማዕበል ግጭቱ መሠረተ ልማትን ወደ ማውደም ሰፊ ጦርነት እየተቀየረ መምጣቱን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለቱም አገራት የሎጂስቲክስ፣ የነዳጅ ማጠራቀሚያዎች፣ የአየር መከላከያ ሥርዓቶች እና የወታደራዊ አቅርቦት መረቦችን መዳረሻ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
የዩክሬን ድሮኖች በራይዛን የነዳጅ ማጣሪያ ላይ በፈጸሙት ጥቃት ከፍተኛ ውድመት መድረሱንና ስትራቴጂካዊ በሆኑ ቀጠናዎች ላይ የእሳት አደጋ መከሰቱን ተከትሎ፣ የሩሲያ ባለሥልጣናት በአንዱ ተጎጂ ከተማ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጀዋል።
በተመሳሳይ ወቅት ሞስኮ በዩክሬን ይዞታዎች ላይ አዳዲስ ጥቃቶችን የሰነዘረች ሲሆን፣ ሁለቱም ወገኖች ከጠላት የጦር ግንባር በስተጀርባ ባሉ ጥልቅ ይዞታዎች ላይ ረጅም ርቀት በሚጓዙ ድሮኖችና ትክክለኛ ኢላማቸውን በሚመቱ ጥቃቶች ላይ ይበልጥ መተማመናቸውን ተከትሎ በተለያዩ ግንባሮች ላይ ያለው ጫና በርትቷል።
እየተባባሰ የመጣው የጥቃት ማዕበል ግጭቱ መሠረተ ልማትን ወደ ማውደም ሰፊ ጦርነት እየተቀየረ መምጣቱን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለቱም አገራት የሎጂስቲክስ፣ የነዳጅ ማጠራቀሚያዎች፣ የአየር መከላከያ ሥርዓቶች እና የወታደራዊ አቅርቦት መረቦችን መዳረሻ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
ሩሲያ ሰይጣን ሁለት ከተሰኘዉ ሚሳኤል የበለጠና በዓለም ላይ እጅግ ኃይለኛ የተባለዉን የሚሳኤል ሙከራ አደረገች
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌርን አቅም ያለው ሳርማት መሳሪያ የአለም "ኃይለኛ" ሚሳኤል ሙከራን ሩሲያ አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ተናገሩ።ሞስኮ ማክሰኞ እለት በተሳካ ሁኔታ ሙከራዉ መደረጉን የሩስያ የስትራቴጂክ ሚሳኤል ጦር አዛዥ ሰርጌይ ካራካዬቭን ለፑቲን ሪፖርተ ማቅረባቸዉን የመንግስት ቴሌቪዥን በምስል ባወጣዉ ዘገባ አሰራጭቷል።
ፑቲን የሳርማት ሚሳኤል በዓመቱ መጨረሻ ወደ ፍልሚያ አገልግሎት እንደሚገባ ተናግረዋል። በቴሌቭዥን ዘገባዉ ላይ "ይህ በዓለም ላይ በጣም ኃይለኛው ሚሳኤል ነው" በማለት የጦርነት መጠን ላይ ከምዕራባውያን አቻዎች በአራት እጥፍ እንደሚበልጥ ተመላክቷል፡፡ፑቲን ሳርማት ከ 35,000 ኪ.ሜ የሚበልጥ ርቀት በመጓዝ የከርሰ ምድር በረራ ችሎታ እንዳለው እና "ወደ ሁሉም ነባር እና የወደፊት የፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ውስጥ ዘልቆ መግባት ይችላል" ብለዋል ።
ይህዉ ቴክኖሎጂ ከዓመታት ውድቀት በኋላ የመጣ ስኬት ነዉ፡፡የሳርማት ልማት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ20111 ሲሆን ሚሳኤሉ አንድ የታወቀ የተሳካ ሙከራ ብቻ ተደርጎለታል፤ በ 2024 ዓመት በሙከራ ወቅት ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡በምዕራቡ ዓለም "ሰይጣን ሁለት" ተብሎ የተሰየመው ሳርማት ወደ 40 የሚጠጉ በሶቪየት የተሰሩ የቮዬቮዳ ሚሳኤሎችን ለመተካት ታስቦ ነው። ፑቲን እንዳሉት ሳርማት እንደ ቮዬቮዳ ኃይለኛ ቢሆንም ከፍተኛ እና ትክክለኛነት አለው ብለዋል፡፡
በስምዖን ደረጄ
seledadotio
seledadotio
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የኒውክሌርን አቅም ያለው ሳርማት መሳሪያ የአለም "ኃይለኛ" ሚሳኤል ሙከራን ሩሲያ አዲስ አህጉር አቀፍ ባሊስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አድርጋለች ሲሉ ተናገሩ።ሞስኮ ማክሰኞ እለት በተሳካ ሁኔታ ሙከራዉ መደረጉን የሩስያ የስትራቴጂክ ሚሳኤል ጦር አዛዥ ሰርጌይ ካራካዬቭን ለፑቲን ሪፖርተ ማቅረባቸዉን የመንግስት ቴሌቪዥን በምስል ባወጣዉ ዘገባ አሰራጭቷል።
ፑቲን የሳርማት ሚሳኤል በዓመቱ መጨረሻ ወደ ፍልሚያ አገልግሎት እንደሚገባ ተናግረዋል። በቴሌቭዥን ዘገባዉ ላይ "ይህ በዓለም ላይ በጣም ኃይለኛው ሚሳኤል ነው" በማለት የጦርነት መጠን ላይ ከምዕራባውያን አቻዎች በአራት እጥፍ እንደሚበልጥ ተመላክቷል፡፡ፑቲን ሳርማት ከ 35,000 ኪ.ሜ የሚበልጥ ርቀት በመጓዝ የከርሰ ምድር በረራ ችሎታ እንዳለው እና "ወደ ሁሉም ነባር እና የወደፊት የፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ውስጥ ዘልቆ መግባት ይችላል" ብለዋል ።
ይህዉ ቴክኖሎጂ ከዓመታት ውድቀት በኋላ የመጣ ስኬት ነዉ፡፡የሳርማት ልማት የጀመረው እ.ኤ.አ. በ20111 ሲሆን ሚሳኤሉ አንድ የታወቀ የተሳካ ሙከራ ብቻ ተደርጎለታል፤ በ 2024 ዓመት በሙከራ ወቅት ከፍተኛ ፍንዳታ ደርሶበት እንደነበር ይታወሳል፡፡በምዕራቡ ዓለም "ሰይጣን ሁለት" ተብሎ የተሰየመው ሳርማት ወደ 40 የሚጠጉ በሶቪየት የተሰሩ የቮዬቮዳ ሚሳኤሎችን ለመተካት ታስቦ ነው። ፑቲን እንዳሉት ሳርማት እንደ ቮዬቮዳ ኃይለኛ ቢሆንም ከፍተኛ እና ትክክለኛነት አለው ብለዋል፡፡
በስምዖን ደረጄ
seledadotio
seledadotio
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፣ አዲሱ ስትራቴጂካዊ የኒውክሌር አህጉር አቋራጭ ባለስቲክ ሚሳኤል 'ሳርማት' በዚህ አመት መጨረሻ ላይ ይፋዊ ስምሪት እንደሚያገኝ አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት ማክሰኞ ዕለት የተካሄደውን የሚሳኤሉን የሙከራ ትርኢት ተከትሎ በሰጡት መግለጫ ነው።
ሳርማት (በኔቶ መጠሪያ "ሰይጣን ዳግማዊ" የሚባለው፣ ሩሲያ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ካመረተቻቸው አህጉር አቋራጭ ሚሳኤሎች መካከል "እጅግ ከባድ" በሚል ምድብ የተመደበው የመጀመሪያው ነው።
በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ በሺዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኙ ኢላማዎችን በኒውክሌር አረር ለመምታት የተነደፈው ይህ ሚሳኤል፣ ለዓመታት ባጋጠመው መጓተት እና መዘግየት ምክንያት ስምሪቱ ሲራዘም መቆየቱ ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን በቴሌቪዥን መስኮት በሰጡት ቃል፣ የሳርማት የኒውክሌር አረር የማፈንዳት አቅም ከማንኛውም የምዕራባውያን አቻው ከአራት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ፣ እና ከ35,000 ኪ.ሜ (21,750 ማይል) በላይ ርቀት መምታት እንደሚችል አስረድተዋል።
"አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚመጡትን ፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ጥሶ የመግባት አቅም አለው" ያሉት ፑቲን፣ የጦር መሳሪያውን "በአለም ላይ እጅግ ሀይለኛው የሚሳኤል ስርዓት" ሲሉ በከፍተኛ ኩራት ገልጸውታል።
የምዕራባውያን የፀጥታ ተንታኞች ግን ፑቲን በ2018 እ.ኤ.አ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳወቁትን የጦር መሳሪያ ዘመናዊ የማድረግ ፕሮግራም አካል የሆኑትን አዳዲስ የኒውክሌር መሳሪያዎች አቅም አጋንነው እየገለፁ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። ባለሙያዎቹ እንደሚሉት፣ ሳርማት ከዚህ ቀደም ውድቀቶች አጋጥመውታል፤ ለአብነትም በመስከረም 2024 የተደረገው ሙከራ በሚሳኤል ማስወንጨፊያው ላይ ጥልቅ ጉድጓድ ጥሎ ማለፉን ያስታውሳሉ።
ይሁን እንጂ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የሚሳኤል ሃይሎች አዛዥ የሆኑት ሰርጌይ ካራካዬቭ፣ የማክሰኞው የሳርማት ሙከራ የተሳካ እንደነበር ለፑቲን ሪፖርት ሲያደርጉ በመንግስት ቴሌቪዥን ታይተዋል። ካራካዬቭ እንዳሉት፣ "ሳርማት የሚሳኤል ስርዓት የተገጠመላቸው ማስወንጨፊያዎች መሰማራታቸው... የስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሃይሎችን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል።"
እ.ኤ.አ በ2022 የዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ ፑቲን የሩሲያን የኒውክሌር መሳሪያ ብዛት እና ሀይል ለአለም በተደጋጋሚ ሲያስታውሱ ቆይተዋል። ይህ አካሄዳቸው ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ለማስፈራራት ያለመ መሆኑ ይነገራል።
የተባበሩት መንግስታት ትጥቅ ማስፈታት ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ፓቬል ፖድቪግ በበኩላቸው፣ የሩሲያ "ትልቁ ሚሳኤል" በዚህ ዓመት መሰማራቱ እውን መሆኑን ቢያምኑም፣ ይህ ግን "የሩሲያን ስትራቴጂካዊ ሃይሎች የመከላከል አቅም ላይ ጉልህ ለውጥ ያመጣል" ብለው እንደማያስቡ ተናግረዋል።
የሩሲያው የዜና ወኪል እንደዘገበው፣ ክሬምሊን ለሚሳኤል ሙከራው አሜሪካን አስቀድሞ አሳውቆ ነበር። ሆኖም፣ ሞስኮ እና ዋሽንግተን የ 'ኒው ስታርት' የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ቁጥጥር ስምምነት ጊዜው ካበቃ በኋላ ከፍተኛ ወታደራዊ ውይይት እንደገና ለመጀመር ቢስማሙም፣ እስካሁን ወደ ተግባር አልገቡም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ አዲስ ስምምነት የጦር መሳሪያዋ እያደገ የመጣችውን ቻይናንም ሊያካትት ይገባል በማለት በተደጋጋሚ ጫና ቢያደርጉም፣ ቤይጂንግ ግን ይህንን ውድቅ አድርጋዋለች። በሌላ በኩል፣ ሩሲያ 'ኒው ስታርት' እንዲራዘም ለምታቀርበው ጥያቄ ትራምፕ ዝምታን የመረጡ ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት በተደጋጋሚ አንዱ ሌላውን ስምምነቱን አላከበረም ሲሉ ይወነጃጀላሉ።
ሳርማት (በኔቶ መጠሪያ "ሰይጣን ዳግማዊ" የሚባለው፣ ሩሲያ ከሶቪየት ህብረት ውድቀት በኋላ ካመረተቻቸው አህጉር አቋራጭ ሚሳኤሎች መካከል "እጅግ ከባድ" በሚል ምድብ የተመደበው የመጀመሪያው ነው።
በአሜሪካ ወይም በአውሮፓ በሺዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ርቀት ላይ የሚገኙ ኢላማዎችን በኒውክሌር አረር ለመምታት የተነደፈው ይህ ሚሳኤል፣ ለዓመታት ባጋጠመው መጓተት እና መዘግየት ምክንያት ስምሪቱ ሲራዘም መቆየቱ ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ፑቲን በቴሌቪዥን መስኮት በሰጡት ቃል፣ የሳርማት የኒውክሌር አረር የማፈንዳት አቅም ከማንኛውም የምዕራባውያን አቻው ከአራት እጥፍ በላይ እንደሚበልጥ፣ እና ከ35,000 ኪ.ሜ (21,750 ማይል) በላይ ርቀት መምታት እንደሚችል አስረድተዋል።
"አሁን ያሉትንም ሆነ ወደፊት የሚመጡትን ፀረ-ሚሳኤል መከላከያ ስርዓቶች ጥሶ የመግባት አቅም አለው" ያሉት ፑቲን፣ የጦር መሳሪያውን "በአለም ላይ እጅግ ሀይለኛው የሚሳኤል ስርዓት" ሲሉ በከፍተኛ ኩራት ገልጸውታል።
የምዕራባውያን የፀጥታ ተንታኞች ግን ፑቲን በ2018 እ.ኤ.አ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳወቁትን የጦር መሳሪያ ዘመናዊ የማድረግ ፕሮግራም አካል የሆኑትን አዳዲስ የኒውክሌር መሳሪያዎች አቅም አጋንነው እየገለፁ ነው ሲሉ ይሞግታሉ። ባለሙያዎቹ እንደሚሉት፣ ሳርማት ከዚህ ቀደም ውድቀቶች አጋጥመውታል፤ ለአብነትም በመስከረም 2024 የተደረገው ሙከራ በሚሳኤል ማስወንጨፊያው ላይ ጥልቅ ጉድጓድ ጥሎ ማለፉን ያስታውሳሉ።
ይሁን እንጂ የሩሲያ ስትራቴጂካዊ የሚሳኤል ሃይሎች አዛዥ የሆኑት ሰርጌይ ካራካዬቭ፣ የማክሰኞው የሳርማት ሙከራ የተሳካ እንደነበር ለፑቲን ሪፖርት ሲያደርጉ በመንግስት ቴሌቪዥን ታይተዋል። ካራካዬቭ እንዳሉት፣ "ሳርማት የሚሳኤል ስርዓት የተገጠመላቸው ማስወንጨፊያዎች መሰማራታቸው... የስትራቴጂካዊ የኒውክሌር ሃይሎችን የውጊያ አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድጋል።"
እ.ኤ.አ በ2022 የዩክሬን ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ ፑቲን የሩሲያን የኒውክሌር መሳሪያ ብዛት እና ሀይል ለአለም በተደጋጋሚ ሲያስታውሱ ቆይተዋል። ይህ አካሄዳቸው ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ለማስፈራራት ያለመ መሆኑ ይነገራል።
የተባበሩት መንግስታት ትጥቅ ማስፈታት ጥናት ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ፓቬል ፖድቪግ በበኩላቸው፣ የሩሲያ "ትልቁ ሚሳኤል" በዚህ ዓመት መሰማራቱ እውን መሆኑን ቢያምኑም፣ ይህ ግን "የሩሲያን ስትራቴጂካዊ ሃይሎች የመከላከል አቅም ላይ ጉልህ ለውጥ ያመጣል" ብለው እንደማያስቡ ተናግረዋል።
የሩሲያው የዜና ወኪል እንደዘገበው፣ ክሬምሊን ለሚሳኤል ሙከራው አሜሪካን አስቀድሞ አሳውቆ ነበር። ሆኖም፣ ሞስኮ እና ዋሽንግተን የ 'ኒው ስታርት' የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ቁጥጥር ስምምነት ጊዜው ካበቃ በኋላ ከፍተኛ ወታደራዊ ውይይት እንደገና ለመጀመር ቢስማሙም፣ እስካሁን ወደ ተግባር አልገቡም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህ አዲስ ስምምነት የጦር መሳሪያዋ እያደገ የመጣችውን ቻይናንም ሊያካትት ይገባል በማለት በተደጋጋሚ ጫና ቢያደርጉም፣ ቤይጂንግ ግን ይህንን ውድቅ አድርጋዋለች። በሌላ በኩል፣ ሩሲያ 'ኒው ስታርት' እንዲራዘም ለምታቀርበው ጥያቄ ትራምፕ ዝምታን የመረጡ ሲሆን፣ ሁለቱም ሀገራት በተደጋጋሚ አንዱ ሌላውን ስምምነቱን አላከበረም ሲሉ ይወነጃጀላሉ።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
"የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው እየተቃረበ ነው"፦ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን
*************************
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በሩሲያና በመላው ዓለም የተከበረውን የ79ኛው የድል ቀን በዓል ተከትሎ በሞስኮ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
ፕሬዚዳንት ፑቲን በሰጡት ማብራሪያ "ጉዳዩ ወደ ዩክሬን ግጭት ማጠቃለያ እያመራ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም በሩሲያና በዩክሬን መካከል የመጨረሻው የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ፣ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሦስተኛ ሀገር ለመገናኘትና ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሞስኮ በተካሄደው የድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ከመጡ የውጭ ሀገራት መሪዎች ጋር ተከታታይ ስብሰባዎችን ያደረጉት ፑቲን፣ ስለ ሩሲያ-ቻይና ግንኙነትና ስለ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችም ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ግጭቱን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ስምምነቶች ላይ መድረስ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በብሌን ደምበሎ
#russia #ukraine #vladimirputin #globalnews #peacetalks
*************************
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የዩክሬን ግጭት ወደ ማብቂያው ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት በሩሲያና በመላው ዓለም የተከበረውን የ79ኛው የድል ቀን በዓል ተከትሎ በሞስኮ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው።
ፕሬዚዳንት ፑቲን በሰጡት ማብራሪያ "ጉዳዩ ወደ ዩክሬን ግጭት ማጠቃለያ እያመራ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም በሩሲያና በዩክሬን መካከል የመጨረሻው የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ ከተቻለ፣ ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሦስተኛ ሀገር ለመገናኘትና ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በሞስኮ በተካሄደው የድል ቀን በዓል ላይ ለመሳተፍ ከመጡ የውጭ ሀገራት መሪዎች ጋር ተከታታይ ስብሰባዎችን ያደረጉት ፑቲን፣ ስለ ሩሲያ-ቻይና ግንኙነትና ስለ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችም ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
ፕሬዚዳንቱ በንግግራቸው ግጭቱን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ስምምነቶች ላይ መድረስ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በብሌን ደምበሎ
#russia #ukraine #vladimirputin #globalnews #peacetalks
3 months ago
የዩክሬን ግጭት 'እየተጠናቀቀ ነው' ብለው እንደሚያስቡ ፑቲን ተናገሩ
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አገራቸው ከዩክሬን ጋር እያካሄደች ያለችው ጦርነት እያበቃ ነው ብለው እንደሚያስቡ ተናገሩ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን ያሉት ሶቪየት ኅብረት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረገችበትን በዓል ካከበረች በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ወቅት ነው።
"ጉዳዩ እየተጠናቀቀ ነው ብዬ አስባለሁ" ሲሉ በዩክሬን እየተካሄደ ስለሚገኘው "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ተናግረው ምዕራባውያን ለኪዬቭ መንግሥትን የሚያደርጉትን ድጋፍ ኮንነዋል።
የሩሲያ ዓመታዊ የድል በዓል ዩክሬን በቀዩ አደባባይ በድሮኖች ጥቃት ልታደርስ ትችላለች በሚል ስጋት የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ሠልፍ አላካሄዱም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በመጨረሻ ደቂቃ ባደራደሩት እና በሞስኮ እና በኪየቭ መካከል በተደረገ የተኩስ አቁም ስምምነት የጥቃት ስጋቱ ቀንሶ ሠልፉ ያለ ምንም አደጋ ተጠናቋል።
ፑቲን አስተያየትቱን የሰጡት የድል ቀን ንግግራቸውን ጦርነቱን ምክንያታዊነት ለማረጋገጥ ከተጠቀሙ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
በንግግራቸውም ሩሲያ "ፍትሃዊ" ጦርነት እየተዋጋች እንደሆነ እና ዩክሬንን "በኔቶ የሚታጠቀ እና የሚደገፍ ጠበኛ ኃይል" ብለው ጠርተዋታል።
ምዕራባውያን ዩክሬንን ስለመርዳታቸው በተመለከተ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት የተጠየቁት ፑቲን "እርዳታ ቃል ገብተው እስከ ዛሬ ድረስም ከሩሲያ ጋር ግጭቱን ማቀጣጠል ጀመሩ። ጉዳዩ እያበቃ ነው ብዬ ባስብም ግን ከባድ ጉዳይ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
የሩሲያ ኃይሎች በ2014 ክሬሚያን እና የምሥራቅ ዩክሬን ክፍሎችን የተቆጣጠሩ ሲሆን እአአ በየካቲት 2022 የዩክሬን ሙሉ ወረራን ጀመሩ።
ፑቲን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዜሌንስኪን የሚያገኙት ዘላቂ የሰላም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ ብቻ እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሦስተኛ አገር መገናኘትም ቢቻልም ግን በዚህ ዝግጅት ላይ ለመሳተፍ እና ለመፈረም የረዥም ጊዜ ታሪካዊ እይታን ለመፍጠር የሰላም ስምምነት ላይ የመጨረሻ ስምምነቶች ከተደረሱ በኋላ ብቻ ነው። ይህም የመጨረሻ እርምጃ መሆን አለበት" ሲሉ አክለዋል።
ዜሌንስኪ በግል ሊያገኟቸው ዝግጁ መሆናቸውን ቢሰሙም "እንዲህ አይነት መግለጫዎችን ስንሰማ ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም" ብለዋል ፑቲን።
ፑቲን ለአውሮፓ አዲስ የደህንነት ስምምነቶችን ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ እና የሚመርጡት የድርድር አጋር የጀርመን የቀድሞ ቻንስለር ጄርሃርድ ሽሮደር እንደሆኑ ጠቅሰዋል።
የቀድሞው ቻንስለር የፑቲን የረዠም ጊዜ ወዳጅ ሲሆኑ በሩሲያ መንግሥት ባለቤትነት ስር ላሉ የኤነርጂ ኩባንያዎች ላይ በመሥራታቸው ምክንያት አወዛጋቢ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ የአውሮፓ ኅብረት ከሩሲያ ጋር ለመደራደር "ተስፋ" እንዳለው እና ዜሌንስኪ እንዲህ ዓይነት እርምጃን እንደሚደግፉ እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
በፋይናንሺያል ታይምስ በተጠቀሰው የኮስታ ንግግር መሠረት የአውሮፓ ኅብረት መሪዎች "ይህንን ለማድረግ ትክክለኛው ጊዜ ሲመጣ ከሩሲያ ጋር በብቃት ለመወያየት ምን እንደሚያስፈልገን" እየተማከሩ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በአሜሪካ በተመራው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት ኪዬቭ እና ሞስኮ አንድ ሺህ እስረኞችን ለመለዋወጥም ተስማምተዋል። ፑቲን ቅዳሜ ዕለት ሩሲያ ስለልውውጡ ምንም ዓይነት መረጃ ከዩክሬን በኩል እስካሁን እንዳልሰማች ተናግረዋል።
በሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'ቀዩ አደባባይ' ሠልፍ ላይ ምንም ዓይነት ወታደራዊ መሳሪያ ያልታየ ሲሆን ክሪምሊን በተለምዶ የሩሲያን ወታደራዊ ኃይል ለዓለም አቀፍ መድረክ የምታሳይበት ሰልፍ ነው።
በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉት ጋዜጠኞች በጣም ጥቂት የነበሩ ሲሆን ብዙ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ፈቃድ አልተሰጣቸውም።
BBC
3 months ago
ሩሲያ 81ኛውን የድል በዓሏን በታላቅ ወታደራዊ ትርዒት እያከበረች ነው
#ethiopia | መላው የሩሲያ ህዝብና መንግስት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረጉበትን 81ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት እያከበሩ ይገኛሉ። በሞስኮ የቀዩ አደባባይ (Red Square) በተካሄደው ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፣ የሀገሪቱ ወታደራዊ ጥንካሬ የታየበትና የታሪክ ጀግኖች የታሰቡበት ነበር።
ፕሬዚዳንቱ በክብር እንግድነት ለተገኙ የጦር አርበኞችና ለዓለም መሪዎች ባደረጉት ንግግር፣ የሶቪየት ህብረት ወታደሮች ለሰው ልጅ ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት በዝርዝር አንስተዋል። "ዓለምን ከናዚ አስከፊ አገዛዝ የታደጉትና ለአውሮፓውያን ነጻነትን ያመጡት የሶቪየት ልጆች ናቸው" ሲሉ የአያቶቻቸውን ጀግንነት አውስተዋል።
በዓሉን ለየት የሚያደርገው በዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች የታጀበው ሰልፍ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች፣ ታንኮችና ዘመናዊ ሚሳኤሎች በአደባባዩ ላይ የተመለከቱ ሲሆን፣ የሩሲያ የአየር ኃይልም በሰማይ ላይ አስደናቂ ትርዒት አሳይቷል።
ፑቲን ባስተላለፉት መልእክት፣ ይህ ድል ለሩሲያውያን የኩራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ትውልድ የሰላምና የጥንካሬ ትምህርት መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።
ይህ 81ኛው የድል በዓል ሩሲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ዳግም ለማሳየት የተጠቀመችበት አጋጣሚ ሆኖ አልፏል። በበዓሉ ላይ የተለያዩ የሀገራት መሪዎች መገኘታቸውም ለክብረ በዓሉ የላቀ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ሰጥቶታል።
"ወታደሮቻችን ለመላው አውሮፓውያን ነጻነትና ክብር የህይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል" — ቭላድሚር ፑቲን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #የድልበዓል #victoryday81 #ሞስኮ #ታሪክ #ወታደራዊትርዒት #ናዚድል #ፑቲን
#ethiopia | መላው የሩሲያ ህዝብና መንግስት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ድል ያደረጉበትን 81ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት እያከበሩ ይገኛሉ። በሞስኮ የቀዩ አደባባይ (Red Square) በተካሄደው ደማቅ ስነ-ስርዓት ላይ፣ የሀገሪቱ ወታደራዊ ጥንካሬ የታየበትና የታሪክ ጀግኖች የታሰቡበት ነበር።
ፕሬዚዳንቱ በክብር እንግድነት ለተገኙ የጦር አርበኞችና ለዓለም መሪዎች ባደረጉት ንግግር፣ የሶቪየት ህብረት ወታደሮች ለሰው ልጅ ነጻነት የከፈሉትን መስዋዕትነት በዝርዝር አንስተዋል። "ዓለምን ከናዚ አስከፊ አገዛዝ የታደጉትና ለአውሮፓውያን ነጻነትን ያመጡት የሶቪየት ልጆች ናቸው" ሲሉ የአያቶቻቸውን ጀግንነት አውስተዋል።
በዓሉን ለየት የሚያደርገው በዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች የታጀበው ሰልፍ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ወታደሮች፣ ታንኮችና ዘመናዊ ሚሳኤሎች በአደባባዩ ላይ የተመለከቱ ሲሆን፣ የሩሲያ የአየር ኃይልም በሰማይ ላይ አስደናቂ ትርዒት አሳይቷል።
ፑቲን ባስተላለፉት መልእክት፣ ይህ ድል ለሩሲያውያን የኩራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ትውልድ የሰላምና የጥንካሬ ትምህርት መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።
ይህ 81ኛው የድል በዓል ሩሲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላትን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ዳግም ለማሳየት የተጠቀመችበት አጋጣሚ ሆኖ አልፏል። በበዓሉ ላይ የተለያዩ የሀገራት መሪዎች መገኘታቸውም ለክብረ በዓሉ የላቀ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ሰጥቶታል።
"ወታደሮቻችን ለመላው አውሮፓውያን ነጻነትና ክብር የህይወት መስዋዕትነት ከፍለዋል" — ቭላድሚር ፑቲን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #የድልበዓል #victoryday81 #ሞስኮ #ታሪክ #ወታደራዊትርዒት #ናዚድል #ፑቲን
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዛሬው ዕለት በሞስኮ ቀይ አደባባይ የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ማጓጓዣዎችን ትዕይንት የቀነሰ የድል ቀን በዓል አክብረዋል። ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ያሸነፈችበትን 81ኛ ዓመት ለማሰብ በተዘጋጀው በዚህ በዓል ላይ ወታደራዊ ትርኢቱ እንዲቀነስ የተደረገው፣ በዩክሬን ባለው "ወቅታዊ የጦርነት ሁኔታ" እና ኪየቭ በምታስወነጭፋቸው የረጅም ርቀት ድሮኖች ስጋት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
3 months ago
የቅዱስ ጊዮርጊስ ሪባን እገዳ ውዝግብ አስነሳ
#ethiopia | በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የናዚ ጀርመን የተሸነፈበትን ዕለት ለማሰብ የሚደረገው በዓል፣ ዘንድሮም በጀርመን አውራ ጎዳናዎች ላይ የጦዘ የፖለቲካ ክርክር አስነስቷል።
ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የጀርመን ባለስልጣናት በበዓሉ ላይ የሶቪየት ባንዲራዎችን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ሪባን እንዳይታዩ ማገዳቸው ነው።
"ግልጽ አድልዎ ነው" — ጉናር ቤክ
የተቃዋሚው 'AfD' ፓርቲ አባልና የቀድሞው የአውሮፓ ፓርላማ አባል ጉናር ቤክ፣ ይህን የበርሊን ውሳኔ "ፖለቲካዊ እና አድልዎ የተሞላበት" ሲሉ ኮንነውታል። ቤክ ለሚዲያዎች በሰጡት አስተያየት የገለጿቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
-ጀርመን በሌሎች አሸናፊ አገራት ተወካዮች ላይ ያልጣለችውን ክልከላ በሩሲያ ላይ ብቻ ማድረጓ ፍትሃዊ አይደለም።
-ይህ እርምጃ ሩሲያ ናዚዝምን ለማጥፋት የከፈለችውን እጅግ ከፍተኛ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት መስዋዕትነት ሆን ብሎ ችላ የሚል ነው።
ጉዳዩን ለሚመለከት ለማንኛውም የታሪክ ተመራማሪ፣ የጀርመን መንግስት ታሪክን ለወቅታዊ ፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገው መሆኑ ግልጽ ነው ብለዋል።
በጉዳዩ ላይ ጠንከር ያለ ምላሽ የሰጠችው ሞስኮ፣ ምዕራባውያን የሶቪየት ህብረትን የድል ታሪክ ከታሪክ ገጽ ላይ ለመደምሰስ "የታሪክ በቀል" እያካሄዱ ነው ስትል ከሳለች። በተጨማሪም፣ እንዲህ ያሉ ምልክቶችን ማገድ በአውሮፓ ውስጥ የናዚ ርዕዮተ ዓለም ዳግም እንዲያንሰራራ በር ይከፍታል ስትል አስጠንቅቃለች።
ለዓመታት የናዚዝም ሽንፈት ምልክት የነበሩት ሪባኖችና ባንዲራዎች፣ ዛሬ ላይ በምዕራባውያን እና በሩሲያ መካከል ላለው የዲፕሎማሲ ፍጥጫ አዲስ የጦር አውድማ ሆነዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#victoryday #germany #russia #stgeorgeribbon #history #politics #gunnarbeck
#ethiopia | በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የናዚ ጀርመን የተሸነፈበትን ዕለት ለማሰብ የሚደረገው በዓል፣ ዘንድሮም በጀርመን አውራ ጎዳናዎች ላይ የጦዘ የፖለቲካ ክርክር አስነስቷል።
ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የጀርመን ባለስልጣናት በበዓሉ ላይ የሶቪየት ባንዲራዎችን እና የቅዱስ ጊዮርጊስ ሪባን እንዳይታዩ ማገዳቸው ነው።
"ግልጽ አድልዎ ነው" — ጉናር ቤክ
የተቃዋሚው 'AfD' ፓርቲ አባልና የቀድሞው የአውሮፓ ፓርላማ አባል ጉናር ቤክ፣ ይህን የበርሊን ውሳኔ "ፖለቲካዊ እና አድልዎ የተሞላበት" ሲሉ ኮንነውታል። ቤክ ለሚዲያዎች በሰጡት አስተያየት የገለጿቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
-ጀርመን በሌሎች አሸናፊ አገራት ተወካዮች ላይ ያልጣለችውን ክልከላ በሩሲያ ላይ ብቻ ማድረጓ ፍትሃዊ አይደለም።
-ይህ እርምጃ ሩሲያ ናዚዝምን ለማጥፋት የከፈለችውን እጅግ ከፍተኛ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት መስዋዕትነት ሆን ብሎ ችላ የሚል ነው።
ጉዳዩን ለሚመለከት ለማንኛውም የታሪክ ተመራማሪ፣ የጀርመን መንግስት ታሪክን ለወቅታዊ ፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገው መሆኑ ግልጽ ነው ብለዋል።
በጉዳዩ ላይ ጠንከር ያለ ምላሽ የሰጠችው ሞስኮ፣ ምዕራባውያን የሶቪየት ህብረትን የድል ታሪክ ከታሪክ ገጽ ላይ ለመደምሰስ "የታሪክ በቀል" እያካሄዱ ነው ስትል ከሳለች። በተጨማሪም፣ እንዲህ ያሉ ምልክቶችን ማገድ በአውሮፓ ውስጥ የናዚ ርዕዮተ ዓለም ዳግም እንዲያንሰራራ በር ይከፍታል ስትል አስጠንቅቃለች።
ለዓመታት የናዚዝም ሽንፈት ምልክት የነበሩት ሪባኖችና ባንዲራዎች፣ ዛሬ ላይ በምዕራባውያን እና በሩሲያ መካከል ላለው የዲፕሎማሲ ፍጥጫ አዲስ የጦር አውድማ ሆነዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#victoryday #germany #russia #stgeorgeribbon #history #politics #gunnarbeck
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያን የድል በአል አስመልክቶ ውጥረት ተፈጠረ፡፡ የሩሲያ የድል በአል የፊታችን ቅዳሜ የሚከበር ሲሆን ይህንን አስመልክቶ ነገና ከነገ ወዲያ የተኩስ አቁም እንደሚደረግ ቢገለፅም ውጥረቱ ግን ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ቀናት በሁለቱም አገራት ዋና ከተሞች ላይ የተካሄደው ጥቃት የተኩስ አቁሙ እውን መሆኑን አጠራጣሪ አድርጎታል፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ከረቡእ ሜይ 6 ቀን አንስቶ የተኩስ አቁም እንደሚያደርጉ አስታውቀው የነበረ ቢሆንም ለዚህ ግን ሩሲያ መልስ አልሰጠችም ነበር፡፡
በመሆኑም ሁለቱም አገራት ጥቃት መሰንዘራቸውን የቀጠሉ ሲሆን የክሬሚሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ግን ተኩስ አቁሙ አርብና ቅዳሜ ማለትም ሜይ 8 እና 9 መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከደህንነት ስጋት አኳያ በሞስኮ ይከናወን የነበረው ወታደራዊ ትርኢትም እንደወትሮው በቀይ አደባባይ እንደማይደረግ ገልፀው ትርኢቱ ሱሮቭ በተሰኘ ወታደራዊ ትምህርት ቤት እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም የጦር መሳሪያ ትርኢቱ በኦንላይን የሚቀርብ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ከሞስኮ ለቀረበው የተኩስ አቁም ጥሪ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በሰጡት መልስ ‹‹እያንዳንዱ ቀን ለሩሲያ ይህንን ጦርነት ለማቆም እድል የሚፈጥር ነው፡፡ ለወታደራዊ ትርኢት ብቻ የእኛን ፈቃድ ለሰአታት መጠበቅ ምንም ዋጋ የለውም›› በማለት የገለፁ ሲሆን ይህም የተኩስ አቁሙን ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡
በመሆኑም ሁለቱም አገራት ጥቃት መሰንዘራቸውን የቀጠሉ ሲሆን የክሬሚሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ግን ተኩስ አቁሙ አርብና ቅዳሜ ማለትም ሜይ 8 እና 9 መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከደህንነት ስጋት አኳያ በሞስኮ ይከናወን የነበረው ወታደራዊ ትርኢትም እንደወትሮው በቀይ አደባባይ እንደማይደረግ ገልፀው ትርኢቱ ሱሮቭ በተሰኘ ወታደራዊ ትምህርት ቤት እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም የጦር መሳሪያ ትርኢቱ በኦንላይን የሚቀርብ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ከሞስኮ ለቀረበው የተኩስ አቁም ጥሪ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በሰጡት መልስ ‹‹እያንዳንዱ ቀን ለሩሲያ ይህንን ጦርነት ለማቆም እድል የሚፈጥር ነው፡፡ ለወታደራዊ ትርኢት ብቻ የእኛን ፈቃድ ለሰአታት መጠበቅ ምንም ዋጋ የለውም›› በማለት የገለፁ ሲሆን ይህም የተኩስ አቁሙን ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡
Sponsored by
Surafel
Comments