Logo
Getu Temesgen
ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በአካል ለመወያየት ጥሪ አቀረቡ
#ethiopia | ዩክሬንና ሩሲያ በቀጥታ በመገናኘት ጦርነቱን እንዲያቆሙ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (ቪዲዮ) ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ በአካል ለመገናኘት ጥሪ ማቅረባቸው ተሰማ።

የአሜሪካ ትኩረት ሙሉ በሙሉ ወደ ኢራን ጉዳይ በዞረበት በዚህ ወቅት፣ ጦርነቱ እንደገና የአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እስኪሆን ድረስ ዝም ብሎ መጠበቅ ስህተት መሆኑን እና ሰላም ሊመጣ የሚችለው በሁለቱ አገራት ቀጥተኛ ንግግር ብቻ መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።

ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሚካሄደው ድርድር እንዲረዳ ሙሉ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ የጠየቁ ቢሆንም፣ ቭላድሚር ፑቲን ግን ከዚህ ቀደም የተኩስ አቁም ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል።

የክሬምሊን ቤተ መንግሥት ደብዳቤው እንደደረሰውና ለፑቲን ገለጻ እንደሚደረግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም ሩሲያ ዘለንስኪ ወደ ሞስኮ መጥተው መወያየት እንደሚችሉ ገልጻ ነበር።

ቭላድሚር ፑቲን ስምምነት ለማድረግ ፈቃደኛ መሆናቸውን ቢናገሩም፣ ዩክሬን ዶኔትስክ፣ ሉሃንስክ፣ ኬርሰን እና ዛፖሪዢያ ከተባሉ አራት ክልሎች እንድትወጣ እና የኔቶ አባል የመሆን ጥረቷን እንድታቆም የሚሉትን ጠንካራ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጠዋል፡፡

ዩክሬን ግን ይህንን ግዛቶቿን አሳልፋ መስጠት የሩሲያን ዳግም ወረራ የሚያበረታታ መሆኑን በመግለጽ የሩሲያን ቅድመ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ አድርጋለች።

በሌላ በኩል የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለቱ መሪዎች መገናኘት "በጣም ጥሩ ነገር ነው" ሲሉ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጋዜጣ + #russian #uk #peace #nowar

4 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.