2 months ago
የቮሊቦል ባለውለታው ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ተጠናቀቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ቮሊቦል ስፖርት ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ150 በላይ በሚሆኑ ሀገራት የአሰልጣኝነት ስልጠና የሰጡት የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ ሦስት ዓመታት የሞላቸው ሲሆን፣ ይህንን የቀድሞ ውጤታማ ስፖርተኛና የዘርፉ ባለውለታ ለመዘከር ሲካሄድ የሰነበተው ውድድር ላለፈው አንድ ሳምንት በበርካታ ክለቦች መካከል ሲካሄድ ቆይቷል።
በኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከመጋቢት 5 እሰከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ሲደረግ የነበረው ይህ ውድድር በዛሬው የፍጻሜ ጨዋታ በወንዶች መቻል ስፖርት ክለብ እንዲሁም በሴቶች ብሔራዊ አልኮል ስፖርት ክለብ የዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን
አረጋግጠዋል።
በመዝጊያ መርሐግብር ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አበባ አማረ ፣ በባህልና ስፖርት የስፖርት ማህበራት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ዳኜ ፣ የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብ ስራ አስፈፃሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ፣የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ባለቤት ወይዘሮ ትዝታ አባተ ጫኔ እና የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አመራሮች በመገኘት ለአሸናፊዎች የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዶች ለኮከብ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ልዩ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ ውድድሩ የኢንስትራክተሩን ሙያዊ ተጋድሎ ከማስታወስ ባለፈ በክለቦች መካከል ያለውን የተቀናጀ ስፖርታዊ መንፈስ ይበልጥ እንዲጎለብት ማድረጉ ተገልጿል።
በተለይም በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና በቮሊቦል ፌዴሬሽን በኩል የተገኙት ከፍተኛ አመራሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን ያስጠሩ ባለሙያዎችን እንዲህ ባለ ደማቅ መድረክ መዘከር ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopianvolleyball #instructoralemayehu #volleyballethiopia #sportsnews #addisababa #ethiopia #mechal #nationalalcohol
#ethiopia | በኢትዮጵያ ቮሊቦል ስፖርት ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ150 በላይ በሚሆኑ ሀገራት የአሰልጣኝነት ስልጠና የሰጡት የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ ሦስት ዓመታት የሞላቸው ሲሆን፣ ይህንን የቀድሞ ውጤታማ ስፖርተኛና የዘርፉ ባለውለታ ለመዘከር ሲካሄድ የሰነበተው ውድድር ላለፈው አንድ ሳምንት በበርካታ ክለቦች መካከል ሲካሄድ ቆይቷል።
በኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከመጋቢት 5 እሰከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ሲደረግ የነበረው ይህ ውድድር በዛሬው የፍጻሜ ጨዋታ በወንዶች መቻል ስፖርት ክለብ እንዲሁም በሴቶች ብሔራዊ አልኮል ስፖርት ክለብ የዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን
አረጋግጠዋል።
በመዝጊያ መርሐግብር ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አበባ አማረ ፣ በባህልና ስፖርት የስፖርት ማህበራት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ዳኜ ፣ የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብ ስራ አስፈፃሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ፣የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ባለቤት ወይዘሮ ትዝታ አባተ ጫኔ እና የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አመራሮች በመገኘት ለአሸናፊዎች የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዶች ለኮከብ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ልዩ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ ውድድሩ የኢንስትራክተሩን ሙያዊ ተጋድሎ ከማስታወስ ባለፈ በክለቦች መካከል ያለውን የተቀናጀ ስፖርታዊ መንፈስ ይበልጥ እንዲጎለብት ማድረጉ ተገልጿል።
በተለይም በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና በቮሊቦል ፌዴሬሽን በኩል የተገኙት ከፍተኛ አመራሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን ያስጠሩ ባለሙያዎችን እንዲህ ባለ ደማቅ መድረክ መዘከር ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopianvolleyball #instructoralemayehu #volleyballethiopia #sportsnews #addisababa #ethiopia #mechal #nationalalcohol