15 days ago
በአፍሪካ ከፍተኛ የአርሰናል ደጋፊ ያላቸው 10 ቀዳሚ አገራት ደረጃ ይፋ ሆኑ!
መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የዘንድሮውን የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ ክለቡ በአፍሪካ አህጉር ያለው ግዙፍ ተፅዕኖ ዳግም ትኩረት ስቧል።
በቢቢሲ (BBC) የምርምር መረጃዎችና በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መስተጋብሮች መነሻነት የወጣው የአፍሪካ ቀዳሚ የአርሰናል ደጋፊዎች ደረጃ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስገራሚ ውጤቶችን አሳይቷል።
በዚሁ መረጃ መሠረት፣ አርሰናልን በከፍተኛ ስሜትና በብዛት በመደገፍ በአህጉሪቱ ቀዳሚ የሆኑት 10 አገራት የሚከተሉት ናቸው ተብሏል:-
1. 🇳🇬 ናይጄሪያ (Nigeria)
2. 🇰🇪 ኬንያ (Kenya)
3. 🇺🇬 ኡጋንዳ (Uganda)
4. 🇪🇹 ኢትዮጵያ (Ethiopia)
5. 🇹🇿 ታንዛኒያ (Tanzania)
6. 🇩🇿 አልጄሪያ (Algeria)
7. 🇬🇭 ጋና (Ghana)
8. 🇲🇦 ሞሮኮ (Morocco)
9. 🇹🇳 ቱኒዚያ (Tunisia)
10. 🇲🇼 ማላዊ (Malawi)
seledadotio
seledadotio
መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የዘንድሮውን የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ ክለቡ በአፍሪካ አህጉር ያለው ግዙፍ ተፅዕኖ ዳግም ትኩረት ስቧል።
በቢቢሲ (BBC) የምርምር መረጃዎችና በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መስተጋብሮች መነሻነት የወጣው የአፍሪካ ቀዳሚ የአርሰናል ደጋፊዎች ደረጃ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስገራሚ ውጤቶችን አሳይቷል።
በዚሁ መረጃ መሠረት፣ አርሰናልን በከፍተኛ ስሜትና በብዛት በመደገፍ በአህጉሪቱ ቀዳሚ የሆኑት 10 አገራት የሚከተሉት ናቸው ተብሏል:-
1. 🇳🇬 ናይጄሪያ (Nigeria)
2. 🇰🇪 ኬንያ (Kenya)
3. 🇺🇬 ኡጋንዳ (Uganda)
4. 🇪🇹 ኢትዮጵያ (Ethiopia)
5. 🇹🇿 ታንዛኒያ (Tanzania)
6. 🇩🇿 አልጄሪያ (Algeria)
7. 🇬🇭 ጋና (Ghana)
8. 🇲🇦 ሞሮኮ (Morocco)
9. 🇹🇳 ቱኒዚያ (Tunisia)
10. 🇲🇼 ማላዊ (Malawi)
seledadotio
seledadotio
2 months ago
ከፍተኛ ባለስልጣናት በአንድ አውቶቡስ እንዲጓዙ ተወሰነ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦትና ዋጋ ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና ተከትሎ፣ ታንዛኒያ የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስ ጥብቅ መመሪያ አወጣች።
የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን ባለስልጣኖቻቸው ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በየግል መኪኖቻቸው ከመሄድ ይልቅ በአንድ አውቶቡስ በጋራ እንዲጓዙ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ይህ ውሳኔ በጦርነቱ ምክንያት የተከሰተውን የነዳጅ ዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና ለመቋቋም ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንቷ በሰጡት መመሪያ፣ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ቀውስ ታንዛኒያንም እየፈተናት በመሆኑ የመንግሥትን ሀብት በከፍተኛ ዲሲፕሊን መጠቀም ግዴታ መሆኑን አሳስበዋል።
በዚህም መሰረት ባለስልጣናቱ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝቶችም ሆነ ለተለያዩ ስብሰባዎች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በተናጠል መኪና መጠቀም አቁመው በአንድ አውቶቡስ ተሰባስበው እንዲጓዙ ይደረጋል።
ከዚህ ቀደምም መንግሥት ወጪን ለመቆጠብ በሚያደርገው ጥረት፣ የፕሬዚዳንቷን አጀብ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እንዲቀነሱ ማድረጉ ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት በታንዛኒያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ3 ሺህ 820 የታንዛኒያ ሽልንግ እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ሀገሪቱ የነዳጅ ምርትን ሙሉ በሙሉ ከውጭ የምታስገባ በመሆኗ ለዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ተጋላጭ ሆና ትገኛለች።
ይህ የታንዛኒያ እርምጃ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነዳጅ ቀውሱን ለመቋቋም ተመሳሳይ የቁጠባ እርምጃዎችን ሊከተሉ እንደሚችሉ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #fmc #tanzania #samiasul #fuelcrisis #africanews #economy #fuelprice #tanzanianews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦትና ዋጋ ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና ተከትሎ፣ ታንዛኒያ የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስ ጥብቅ መመሪያ አወጣች።
የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን ባለስልጣኖቻቸው ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በየግል መኪኖቻቸው ከመሄድ ይልቅ በአንድ አውቶቡስ በጋራ እንዲጓዙ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ይህ ውሳኔ በጦርነቱ ምክንያት የተከሰተውን የነዳጅ ዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና ለመቋቋም ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ፕሬዚዳንቷ በሰጡት መመሪያ፣ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ቀውስ ታንዛኒያንም እየፈተናት በመሆኑ የመንግሥትን ሀብት በከፍተኛ ዲሲፕሊን መጠቀም ግዴታ መሆኑን አሳስበዋል።
በዚህም መሰረት ባለስልጣናቱ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝቶችም ሆነ ለተለያዩ ስብሰባዎች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በተናጠል መኪና መጠቀም አቁመው በአንድ አውቶቡስ ተሰባስበው እንዲጓዙ ይደረጋል።
ከዚህ ቀደምም መንግሥት ወጪን ለመቆጠብ በሚያደርገው ጥረት፣ የፕሬዚዳንቷን አጀብ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እንዲቀነሱ ማድረጉ ይታወሳል።
በአሁኑ ወቅት በታንዛኒያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ3 ሺህ 820 የታንዛኒያ ሽልንግ እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ሀገሪቱ የነዳጅ ምርትን ሙሉ በሙሉ ከውጭ የምታስገባ በመሆኗ ለዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ተጋላጭ ሆና ትገኛለች።
ይህ የታንዛኒያ እርምጃ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነዳጅ ቀውሱን ለመቋቋም ተመሳሳይ የቁጠባ እርምጃዎችን ሊከተሉ እንደሚችሉ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #fmc #tanzania #samiasul #fuelcrisis #africanews #economy #fuelprice #tanzanianews
4 months ago
የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ወደ 2028 ሊራዘም ይችላል? ኬንያ የጸጥታ ስጋት እንዳለባት ገለጸች
#ethiopia | በጋራ አዘጋጅነት የተረከቡት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ) ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጁ ቢሆንም፣ ውድድሩ የአንድ ዓመት መራዘም ሊገጥመው እንደሚችል ፍንጮች እየታዩ ነው።
ለምን ሊራዘም ይችላል?
ዋናው ምክንያት የኬንያ ሀገራዊ ምርጫ ነው። እ.ኤ.አ በ2027 ኬንያ ጠቅላይ ምርጫ የምታካሂድ በመሆኑ፣ የሀገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ለትልቅ ስፖርታዊ ውድድር አስተማማኝ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
የኬንያ የአዘጋጅ ኮሚቴ ሊቀመንበር ኒኮላስ ሙሶንዬ በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ፦
> "በምርጫ ወቅት የደህንነት ሁኔታው አስተማማኝ ስለማይሆን፣ ውድድሩ ወደ 2028 ቢራዘም ለኬንያ መልካም ነው" ብለዋል።
>
የካፍ (CAF) ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል?
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በታንዛኒያ ዳሬሰላም በሚያደርገው ስብሰባ በዚህ አጀንዳ ላይ በጥልቅ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። ካፍ የኬንያን ጥያቄ ተቀብሎ ውድድሩን ያራዝመዋል ወይንስ ሌሎች አማራጮችን ይፈልጋል? የሚለው ጉዳይ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ውድድሩ የሚራዘም ከሆነ በዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ዝግጅት ላይም የራሱ የሆነ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #afcon2027 #caf #kenya #tanzania #uganda #africanfootball #sportsnews #pamojabid #የአፍሪካዋንጫ #ኬንያ
#ethiopia | በጋራ አዘጋጅነት የተረከቡት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ) ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጁ ቢሆንም፣ ውድድሩ የአንድ ዓመት መራዘም ሊገጥመው እንደሚችል ፍንጮች እየታዩ ነው።
ለምን ሊራዘም ይችላል?
ዋናው ምክንያት የኬንያ ሀገራዊ ምርጫ ነው። እ.ኤ.አ በ2027 ኬንያ ጠቅላይ ምርጫ የምታካሂድ በመሆኑ፣ የሀገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ለትልቅ ስፖርታዊ ውድድር አስተማማኝ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
የኬንያ የአዘጋጅ ኮሚቴ ሊቀመንበር ኒኮላስ ሙሶንዬ በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ፦
> "በምርጫ ወቅት የደህንነት ሁኔታው አስተማማኝ ስለማይሆን፣ ውድድሩ ወደ 2028 ቢራዘም ለኬንያ መልካም ነው" ብለዋል።
>
የካፍ (CAF) ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል?
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በታንዛኒያ ዳሬሰላም በሚያደርገው ስብሰባ በዚህ አጀንዳ ላይ በጥልቅ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። ካፍ የኬንያን ጥያቄ ተቀብሎ ውድድሩን ያራዝመዋል ወይንስ ሌሎች አማራጮችን ይፈልጋል? የሚለው ጉዳይ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ውድድሩ የሚራዘም ከሆነ በዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ዝግጅት ላይም የራሱ የሆነ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #afcon2027 #caf #kenya #tanzania #uganda #africanfootball #sportsnews #pamojabid #የአፍሪካዋንጫ #ኬንያ
6 months ago
35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር በሞሮኮ 24 ሀገራት 6 ምድቦች 52 ጨዋታዎች!
ምድብ 1. ሞሮኮ 🇲🇦, ማሊ 🇲🇱, ዛምቢያ 🇿🇲, ኮሞሮስ 🇰🇲
ሞሮኮ በ 2030 የዓለም ዋንጫን በማዘጋጀት በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሀገር ለመሆን እየተዘጋጀች ነው:: ጥራታቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማቶች ላይ ኢንቨስት እያደረገች ነው:: ከዚያም በላይ ደግሞ ቶፕ ክላስ ቡድን መገንባት:: ለዚያም ነው በዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ከ favorite ቡድኖች አንዷ ሆና ግምት የተሰጣት:: ዋና አሰልጣኙ Walid Regragui በቡድኑ አስደናቂ የሚባል ትራክ ሪከርድ አለው:: የሞሮኮ ቡድን በ elite-level ያሉ ተጫዋቾችን የያዘ ስብስብ ነው::
በዚህ ምድብ ሌላኛዋ ሀገር ማሊ ናት:: የማሊ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ Tom Saintfiet , እኚህ ሰው በኢትዮጵያ ብ.ቡድን ነበሩ (July 2011-Oct 2011)
13 የተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖችን የማሰልጠን ልምድ , ከ underdogs ቡድኖች ጋር ኦቨርአቺቭ የማድረግ ስምና ዝና :: የማሊ ቡድን ወጣት ባለተሰጥኦ ተጫዋቾች ያሉት ነው::
ዛምቢያ ከቀድሞው አሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች, ከቶርናመንቱ ሁለት ወራት በፊት (የቀድሞው የቼልሲ አሰልጣኝ Avram Grant) ታድያ ረዳታቸው የነበረው Moses Sichone የዋና አሰልጣኝነት ሚናውን ተረክቧል:: የ 2012 ቻምፒየኖቹ በ2025 በዚህስ ውድድር?
ኮሞሮስ ዝቅተኛ ግምት ከሚሰጣቸው ሀገራት ናት, በውድድሩ ከሚሳተፉ ሃገራት አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት:: በጣልያናዊው አሰልጣኝ Stefano Cusin ትመራለች::
ምድብ 2. ግብጽ 🇪🇬 , ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 , አንጎላ 🇦🇴 , ዚምባብዌ 🇿🇼
በአፍሪካ ዋንጫ በጣም ስኬታማዋ ሀገር ግብጽ, 7 ዋንጫዎች:: ይሁን እንጂ በቅርብ ዓመታት የዋንጫ ድርቅ መቷታል ከ 2010 በሗላ ዋንጫ አላሸነፈችም:: ሞሃመድ ሳላህ የመጀመሪያ International title ለማሳካት:: ይህ ቡድን ሌሎችም የሚጠበቁ ተጫዋቾች አሉት ኦማር ማርሙሽ እና ሞስታፋ ሞሃመድ:: በተጫዋችነትም በአሰልጣኝነትም ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ልምድ ያለው ሆሳም ሀሳን በውድድሩ ይጠበቃል::
ደቡብ አፍሪካ ስድስት በአውሮፓ የሚጫወቱ ሁለት ደግሞ በሳውዲ አራቢያ የሚጫወቱ እና ሌሎች ከዚያው ከሀገር ውስጥ የተሰባሰቡ:: ይህ ቡድን በ Hugo Broos ስር በታክቲካል ኢንተለጀንሱ ይታወቃል:: ምርጥ ፐርፎርማንስ እንደሚያሳይ እና ለየትኛውም ቡድን ከባድ ተጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል::
አንጎላ በቅርብ ዓመታት በተከታታይ ኦቨርአቺቨር ሆናለች:: ስብስቧ የወጣት እና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ውህድ ነው:: ፈረንሳዊው አሰልጣኝ Patrice Beaumelle ቡድኑን ረዘም ላለ ጊዜ ይዘውት ከቆዩት Pedro Gonçalves ኅላፊነቱን ተረክበዋል::
ዚምባብዌ ከወር በፊት ነው አዲስ አሰልጣኝ የሾመችው Mario Marinică . የዎልቭሱ አማካይ Marshall Munetsi ከጉዳቱ አገግሞ ይህንን ስብስብ ተቀላቅሏል::
ምድብ 3. ናይጄሪያ 🇳🇬 , ቱኒዚያ 🇹🇳 , ዩጋንዳ(ኡጋንዳ) 🇺🇬 , ታንዛኒያ 🇹🇿
ያለፈው ውድድር የፍጻሜ ተፋላሚ , ለዓለም ዋንጫ ውድድር ማለፍ ያልቻለችው ሀገር ከዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ብዙ ትጠብቃለች, ቁጭትም አለ:: ማጥቃት ላይ ቅንጦት ያለው ቡድን Victor Osimhen እና Lookman በስብስቧ አሉ:: Tolu Arokodare እና Victor Boniface በዚህ ስብስብ ውስጥ አልተካተቱም:: በዚህ ቡድን ፈተናው የሚድፊልዱን ሚዛን መፈለግ ነው:: Eric Chelle አይቮሪ ኮስት ተወልዶ ለማሊ የተጫወተው ይህ ሰው ናይጄሪያን በዋና አሰልጣኝነት ይመራል::
ቱኒዚያ የ Sami Trabelsi ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በ 10 ጨዋታዎች ክሊን ሺት የጠበቀ , ማንም ሊገጥመው የማይፈልገው ግን ደግሞ በማጥቃት ደካማ:: ይህ ቡድን ከፊት መስመር ተጫዋቾች ድጋፍ ይፈልጋል::
ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) አሰልጣኝ Paul Put ለተጫዋቾች ጥሪ ያቀረቡት ከሁልም ዓለማት ነው:: ከ USL ቻምፒየንሺፕ አሜሪካ, Thailand, Tanzania, Rwanda, Romania , Czechia እና ከእንግሊዝ 3ተኛ ቲር Burton Albion. ልዩ ልዩ ዓይነት ተጫዋቾችን የያዘውን ስብስብ እንደ ቡድን ፎርም ማድረግ ለአሰልጣኙ ከባድ ስራ::
ታንዛኒያ ካለፉት አራት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለሶስተኛ ጊዜ ስትሳተፍ ነው:: በሚቀጥለውም ስለመሳተፏ ዋስትና አላት, ከኬንያ እና ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) ጋር በጋራ ውድድሩን ስለምታዘጋጅ:: የአዲሱ አሰልጣኝ (አርጀንቲናዊው Miguel Gamondi) ቀዳሚ ዋና ነገር ቡድኑን የጨዋታዎች አሸናፊ ማድረግ ነው:: እኚህ አሰልጣኝ ያለፉትን 25 ዓመታት በአህጉሪቱ አሳልፈዋል, የተለያዩ ክለቦችን በማሰልጠን, ብሔራዊ ቡድን ሲይዙ ግን የመጀመሪያቸው ነው::
ምድብ 4. ሴኔጋል 🇸🇳 , ዲ.ኮንጎ 🇨🇩, ቤኒን 🇧🇯 , ቦትስዋና 🇧🇼
የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ ቻምፒየን ሴኔጋል ለአሰልጣኟ Pape Thaiw የመጀመሪያው ሜጀር ቶርናመንት ነው:: ሴኔጋል ባለፉት 23 competitive ጨዋታዎች አልተሸነፈችም, በጣም ጥሩ ስብስብ አላት::
ዲ.ኮንጎ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የነበራት ደካማ ብቃት በዚህም ውድድር ዝቅተኛ ግምት እንዲሰጣት ያደርጋል:: ቁልፍ የፊት መስመር ተጫዋቿ Yoane Wissa በስብስቡ የለም::
ቤኒን ባለፉት ሁለት ውድድሮች ካለመሳተፍ በሗላ ተመልሳለች, ለአራተኛ ጊዜ በውድድሩ ትካፈላለች: ጀርመናዊው አሰልጣኝ Gernot Rohr በዉድድሩ የቡድኑን የመሸነፍ ታሪክ ወደ አሸናፊነት የመቀየር ዕድል አላቸው::
ቦትስዋና በዚህ ውድድር ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው ቡድን የያዘች ሀገር:: ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ ትሳተፋለች::
ምድብ 5. አልጄሪያ 🇩🇿 , ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫, ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇬🇶, ሱዳን 🇸🇩
አልጄሪያ በውድድሩ ዋነኛ የዋንጫ ተፎካካሪ ነገር ግን የምድብ ጨዋታዎች ላይ መበርታት , ከምድብ ማለፍ ይቀድማል:: Vladimir Petković ቡድኑን በጥሩ ስኬት ይዘውታል, እውነተኛ ፈተናቸው ግን የሚጀምረው አሁን ነው:: የቡድኑን መከላከል ማጠንከር ከአጥቂ ተጫዋቾች ምርጣቸውን ማውጣት::
ቡርኪና ፋሶ Brama Traoré በብሔራዊ ቡድኑ ዙሪያ ቆይቷል ረዳት አሰልጣኝ እና የታዳጊዎች አሰልጣኝ ሆኖ, አሁን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋና አሰልጣኝነት:: ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አሉት Bertrand Traoré, Edmond Tapsoba, እና Hervè Koffi ወጣቶቹን Dango Ouattara እና Cyriaque Irié ጨምሮ::
ኢኳቶሪያል ጊኒ ያለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ሰርፕራይዚንግ ቡድን የፍጻሜ ተፋላሚዎች ከነበሩት ናይጄሪያ እና አይቮሪ ኮስትም በላይ ምድቡን በበላይነት:: አሁንም ጥራት እና ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በስብስቧ ይዛለች::
ሱዳን ባለፋት አስር ዓመታት ለሁለተኛ ጊዜ , ከ 1976 ጀምሮ ለአራተኛ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር:: Kwesi Appiah ሱዳን አቅሟን እንድትጠቀም ያስቻለ አሰልጣኝ ነው:: ሱዳን እዚህ ስኬት ላይ የደረሰችው በጦርነት ውስጥ አልፋ ነው እናም በሜዳ ላይ እያንዳንዱ ጨዋታ ከእግር ኳስም በላይ ትርጉም አለው::
ምድብ 6. አይቮሪ ኮስት 🇨🇮 , ካሜሩን 🇨🇲 , ጋቦን 🇬🇦, ሞዛምቢክ 🇲🇿
Defending champion አይቮሪ ኮስት ለሶስተኛ ጊዜ ዋንጫውን ስታሸንፍ በውድድሩ ታሪክ አስገራሚ ክስተቶች ነበሩ:: በምድብ ጨዋታ ሁለቱን ተሸንፋ, በውድድሩ መሀል የአሰልጣኝ ለውጥ አድርጋ, በጥሎ ማለፍ ውጤቶችን ቀልብሳ ድል በማድረግ:: አሰልጣኙ Emerse Faé ተስፋ አለው በስብስቡ ምርጫ ላይም ቦልድ ውሳኔዎችንም አሳልፏል Nicolas Pépé እና Simon Adingra በመተው ወጣቶቹ Yan Diomande እና Bazoumana Touré ተካተዋል:: ልምድ እና ጥራት ያላቸው ተጫዋቾች ያሉት ብርቱ የtitle defence ስብስብ::
ካሜሩን የአምስት ጊዜ የዋንጫው ባለክብር አሁን ላይ ግን የእግር ኳስ አመራሯ ችግር ውስጥ የተጠመደ የተወሳሰበ ነው ብጥብጥ, ሁከት ያለበት:: ያልተረጋጋ! ለውድድሩ ሁለት የተለያየ ስብስብ ያላት አንደኛው የእግር ኳስ ማህበሩን እና አዲስ የተቀጠረውን አሰልጣኝ David Pagouን ወክሎ , ሌላኛው ደግሞ በቡድኑ አሰልጣኝነት ውል ካለው ከ Marc Brys ወገን:: የችግሩ ምንጭ የ Brys እና የ FA ፕሬዝዳንቱ Samuel Etò ግጭት ነው::
ጋቦን ባለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር አልነበረችም አሁን ተመልሳለች::
ሞዛምቢክ በውድድሩ ላይ ለስድስተኛ ጊዜ ትሳተፋለች , በጨዋታ የመጀመሪያ አሸናፊነት ለማግኘት:: የአሰልጣኙ Chiquinho Conde ስብስብ ያልተቀየረ, አብሮ የቆየ ነው:: የ 42 ዓመቱ Domingues ጨዋታ የሚያደርግ ከሆነ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ በእድሜ ትልቁ outfield player ይሆናል::
ሰላም ጎሳዬ ለፋስት መረጃ
ምድብ 1. ሞሮኮ 🇲🇦, ማሊ 🇲🇱, ዛምቢያ 🇿🇲, ኮሞሮስ 🇰🇲
ሞሮኮ በ 2030 የዓለም ዋንጫን በማዘጋጀት በአፍሪካ ሁለተኛዋ ሀገር ለመሆን እየተዘጋጀች ነው:: ጥራታቸውን የጠበቁ መሰረተ ልማቶች ላይ ኢንቨስት እያደረገች ነው:: ከዚያም በላይ ደግሞ ቶፕ ክላስ ቡድን መገንባት:: ለዚያም ነው በዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ከ favorite ቡድኖች አንዷ ሆና ግምት የተሰጣት:: ዋና አሰልጣኙ Walid Regragui በቡድኑ አስደናቂ የሚባል ትራክ ሪከርድ አለው:: የሞሮኮ ቡድን በ elite-level ያሉ ተጫዋቾችን የያዘ ስብስብ ነው::
በዚህ ምድብ ሌላኛዋ ሀገር ማሊ ናት:: የማሊ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ Tom Saintfiet , እኚህ ሰው በኢትዮጵያ ብ.ቡድን ነበሩ (July 2011-Oct 2011)
13 የተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖችን የማሰልጠን ልምድ , ከ underdogs ቡድኖች ጋር ኦቨርአቺቭ የማድረግ ስምና ዝና :: የማሊ ቡድን ወጣት ባለተሰጥኦ ተጫዋቾች ያሉት ነው::
ዛምቢያ ከቀድሞው አሰልጣኟ ጋር ተለያይታለች, ከቶርናመንቱ ሁለት ወራት በፊት (የቀድሞው የቼልሲ አሰልጣኝ Avram Grant) ታድያ ረዳታቸው የነበረው Moses Sichone የዋና አሰልጣኝነት ሚናውን ተረክቧል:: የ 2012 ቻምፒየኖቹ በ2025 በዚህስ ውድድር?
ኮሞሮስ ዝቅተኛ ግምት ከሚሰጣቸው ሀገራት ናት, በውድድሩ ከሚሳተፉ ሃገራት አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላት:: በጣልያናዊው አሰልጣኝ Stefano Cusin ትመራለች::
ምድብ 2. ግብጽ 🇪🇬 , ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 , አንጎላ 🇦🇴 , ዚምባብዌ 🇿🇼
በአፍሪካ ዋንጫ በጣም ስኬታማዋ ሀገር ግብጽ, 7 ዋንጫዎች:: ይሁን እንጂ በቅርብ ዓመታት የዋንጫ ድርቅ መቷታል ከ 2010 በሗላ ዋንጫ አላሸነፈችም:: ሞሃመድ ሳላህ የመጀመሪያ International title ለማሳካት:: ይህ ቡድን ሌሎችም የሚጠበቁ ተጫዋቾች አሉት ኦማር ማርሙሽ እና ሞስታፋ ሞሃመድ:: በተጫዋችነትም በአሰልጣኝነትም ከብሔራዊ ቡድኑ ጋር ልምድ ያለው ሆሳም ሀሳን በውድድሩ ይጠበቃል::
ደቡብ አፍሪካ ስድስት በአውሮፓ የሚጫወቱ ሁለት ደግሞ በሳውዲ አራቢያ የሚጫወቱ እና ሌሎች ከዚያው ከሀገር ውስጥ የተሰባሰቡ:: ይህ ቡድን በ Hugo Broos ስር በታክቲካል ኢንተለጀንሱ ይታወቃል:: ምርጥ ፐርፎርማንስ እንደሚያሳይ እና ለየትኛውም ቡድን ከባድ ተጋጣሚ እንደሚሆን ይጠበቃል::
አንጎላ በቅርብ ዓመታት በተከታታይ ኦቨርአቺቨር ሆናለች:: ስብስቧ የወጣት እና ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ውህድ ነው:: ፈረንሳዊው አሰልጣኝ Patrice Beaumelle ቡድኑን ረዘም ላለ ጊዜ ይዘውት ከቆዩት Pedro Gonçalves ኅላፊነቱን ተረክበዋል::
ዚምባብዌ ከወር በፊት ነው አዲስ አሰልጣኝ የሾመችው Mario Marinică . የዎልቭሱ አማካይ Marshall Munetsi ከጉዳቱ አገግሞ ይህንን ስብስብ ተቀላቅሏል::
ምድብ 3. ናይጄሪያ 🇳🇬 , ቱኒዚያ 🇹🇳 , ዩጋንዳ(ኡጋንዳ) 🇺🇬 , ታንዛኒያ 🇹🇿
ያለፈው ውድድር የፍጻሜ ተፋላሚ , ለዓለም ዋንጫ ውድድር ማለፍ ያልቻለችው ሀገር ከዚህ የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ብዙ ትጠብቃለች, ቁጭትም አለ:: ማጥቃት ላይ ቅንጦት ያለው ቡድን Victor Osimhen እና Lookman በስብስቧ አሉ:: Tolu Arokodare እና Victor Boniface በዚህ ስብስብ ውስጥ አልተካተቱም:: በዚህ ቡድን ፈተናው የሚድፊልዱን ሚዛን መፈለግ ነው:: Eric Chelle አይቮሪ ኮስት ተወልዶ ለማሊ የተጫወተው ይህ ሰው ናይጄሪያን በዋና አሰልጣኝነት ይመራል::
ቱኒዚያ የ Sami Trabelsi ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በ 10 ጨዋታዎች ክሊን ሺት የጠበቀ , ማንም ሊገጥመው የማይፈልገው ግን ደግሞ በማጥቃት ደካማ:: ይህ ቡድን ከፊት መስመር ተጫዋቾች ድጋፍ ይፈልጋል::
ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) አሰልጣኝ Paul Put ለተጫዋቾች ጥሪ ያቀረቡት ከሁልም ዓለማት ነው:: ከ USL ቻምፒየንሺፕ አሜሪካ, Thailand, Tanzania, Rwanda, Romania , Czechia እና ከእንግሊዝ 3ተኛ ቲር Burton Albion. ልዩ ልዩ ዓይነት ተጫዋቾችን የያዘውን ስብስብ እንደ ቡድን ፎርም ማድረግ ለአሰልጣኙ ከባድ ስራ::
ታንዛኒያ ካለፉት አራት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድሮች ለሶስተኛ ጊዜ ስትሳተፍ ነው:: በሚቀጥለውም ስለመሳተፏ ዋስትና አላት, ከኬንያ እና ዩጋንዳ (ኡጋንዳ) ጋር በጋራ ውድድሩን ስለምታዘጋጅ:: የአዲሱ አሰልጣኝ (አርጀንቲናዊው Miguel Gamondi) ቀዳሚ ዋና ነገር ቡድኑን የጨዋታዎች አሸናፊ ማድረግ ነው:: እኚህ አሰልጣኝ ያለፉትን 25 ዓመታት በአህጉሪቱ አሳልፈዋል, የተለያዩ ክለቦችን በማሰልጠን, ብሔራዊ ቡድን ሲይዙ ግን የመጀመሪያቸው ነው::
ምድብ 4. ሴኔጋል 🇸🇳 , ዲ.ኮንጎ 🇨🇩, ቤኒን 🇧🇯 , ቦትስዋና 🇧🇼
የ 2021 የአፍሪካ ዋንጫ ቻምፒየን ሴኔጋል ለአሰልጣኟ Pape Thaiw የመጀመሪያው ሜጀር ቶርናመንት ነው:: ሴኔጋል ባለፉት 23 competitive ጨዋታዎች አልተሸነፈችም, በጣም ጥሩ ስብስብ አላት::
ዲ.ኮንጎ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የነበራት ደካማ ብቃት በዚህም ውድድር ዝቅተኛ ግምት እንዲሰጣት ያደርጋል:: ቁልፍ የፊት መስመር ተጫዋቿ Yoane Wissa በስብስቡ የለም::
ቤኒን ባለፉት ሁለት ውድድሮች ካለመሳተፍ በሗላ ተመልሳለች, ለአራተኛ ጊዜ በውድድሩ ትካፈላለች: ጀርመናዊው አሰልጣኝ Gernot Rohr በዉድድሩ የቡድኑን የመሸነፍ ታሪክ ወደ አሸናፊነት የመቀየር ዕድል አላቸው::
ቦትስዋና በዚህ ውድድር ዝቅተኛ ግምት የተሰጠው ቡድን የያዘች ሀገር:: ለሁለተኛ ጊዜ በውድድሩ ትሳተፋለች::
ምድብ 5. አልጄሪያ 🇩🇿 , ቡርኪና ፋሶ 🇧🇫, ኢኳቶሪያል ጊኒ 🇬🇶, ሱዳን 🇸🇩
አልጄሪያ በውድድሩ ዋነኛ የዋንጫ ተፎካካሪ ነገር ግን የምድብ ጨዋታዎች ላይ መበርታት , ከምድብ ማለፍ ይቀድማል:: Vladimir Petković ቡድኑን በጥሩ ስኬት ይዘውታል, እውነተኛ ፈተናቸው ግን የሚጀምረው አሁን ነው:: የቡድኑን መከላከል ማጠንከር ከአጥቂ ተጫዋቾች ምርጣቸውን ማውጣት::
ቡርኪና ፋሶ Brama Traoré በብሔራዊ ቡድኑ ዙሪያ ቆይቷል ረዳት አሰልጣኝ እና የታዳጊዎች አሰልጣኝ ሆኖ, አሁን ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋና አሰልጣኝነት:: ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አሉት Bertrand Traoré, Edmond Tapsoba, እና Hervè Koffi ወጣቶቹን Dango Ouattara እና Cyriaque Irié ጨምሮ::
ኢኳቶሪያል ጊኒ ያለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ሰርፕራይዚንግ ቡድን የፍጻሜ ተፋላሚዎች ከነበሩት ናይጄሪያ እና አይቮሪ ኮስትም በላይ ምድቡን በበላይነት:: አሁንም ጥራት እና ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች በስብስቧ ይዛለች::
ሱዳን ባለፋት አስር ዓመታት ለሁለተኛ ጊዜ , ከ 1976 ጀምሮ ለአራተኛ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ ውድድር:: Kwesi Appiah ሱዳን አቅሟን እንድትጠቀም ያስቻለ አሰልጣኝ ነው:: ሱዳን እዚህ ስኬት ላይ የደረሰችው በጦርነት ውስጥ አልፋ ነው እናም በሜዳ ላይ እያንዳንዱ ጨዋታ ከእግር ኳስም በላይ ትርጉም አለው::
ምድብ 6. አይቮሪ ኮስት 🇨🇮 , ካሜሩን 🇨🇲 , ጋቦን 🇬🇦, ሞዛምቢክ 🇲🇿
Defending champion አይቮሪ ኮስት ለሶስተኛ ጊዜ ዋንጫውን ስታሸንፍ በውድድሩ ታሪክ አስገራሚ ክስተቶች ነበሩ:: በምድብ ጨዋታ ሁለቱን ተሸንፋ, በውድድሩ መሀል የአሰልጣኝ ለውጥ አድርጋ, በጥሎ ማለፍ ውጤቶችን ቀልብሳ ድል በማድረግ:: አሰልጣኙ Emerse Faé ተስፋ አለው በስብስቡ ምርጫ ላይም ቦልድ ውሳኔዎችንም አሳልፏል Nicolas Pépé እና Simon Adingra በመተው ወጣቶቹ Yan Diomande እና Bazoumana Touré ተካተዋል:: ልምድ እና ጥራት ያላቸው ተጫዋቾች ያሉት ብርቱ የtitle defence ስብስብ::
ካሜሩን የአምስት ጊዜ የዋንጫው ባለክብር አሁን ላይ ግን የእግር ኳስ አመራሯ ችግር ውስጥ የተጠመደ የተወሳሰበ ነው ብጥብጥ, ሁከት ያለበት:: ያልተረጋጋ! ለውድድሩ ሁለት የተለያየ ስብስብ ያላት አንደኛው የእግር ኳስ ማህበሩን እና አዲስ የተቀጠረውን አሰልጣኝ David Pagouን ወክሎ , ሌላኛው ደግሞ በቡድኑ አሰልጣኝነት ውል ካለው ከ Marc Brys ወገን:: የችግሩ ምንጭ የ Brys እና የ FA ፕሬዝዳንቱ Samuel Etò ግጭት ነው::
ጋቦን ባለፈው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር አልነበረችም አሁን ተመልሳለች::
ሞዛምቢክ በውድድሩ ላይ ለስድስተኛ ጊዜ ትሳተፋለች , በጨዋታ የመጀመሪያ አሸናፊነት ለማግኘት:: የአሰልጣኙ Chiquinho Conde ስብስብ ያልተቀየረ, አብሮ የቆየ ነው:: የ 42 ዓመቱ Domingues ጨዋታ የሚያደርግ ከሆነ በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ በእድሜ ትልቁ outfield player ይሆናል::
ሰላም ጎሳዬ ለፋስት መረጃ
Sponsored by
Surafel
10 months ago
ኢትዮጵያ ፌስቡክም ሆነ ዩቲዩብ ሞኒታይዝ የማይደረግባት ሀገር ነች።ይህ ችግር እንዲፈታ የሚመለከተው የመንግስት አካል መፍትሄ ቢፈጥር መልካም ነው።በቅርቡ ዩቲዩብ ተጀምሮ ነበር ቆመ ምክንያቱ አይታወቅም።
ለምሳሌ ፌስቡክ እነዚህ የአፍሪካ ሃገራት ሞነታይዝ ይደረጋሉ።ዜጎቻቸው በፌስቡክ ገንዘብ እንዲሰሩ ተፈቅዶላቸዋል።
1. Egypt 🇪🇬
2. Democratic Republic of Congo 🇨🇩
3. Ghana 🇬🇭
4. Kenya 🇰🇪
5. Morocco 🇲🇦
6. Nigeria 🇳🇬
7. Tanzania 🇹🇿
8. South Africa 🇿🇦
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ኢትዮጵያ ስለምን ዜጎች በዘርፉ ሰርተው የሚጠቀሙበት የዲጅታል ዘርፍ እንዲያድግ አልፈለገችም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።መታለፍ ያለባቸው ሂደቶች ታልፈው ተግባራዊ ቢሆን መልካም ነው።
ለምሳሌ ፌስቡክ እነዚህ የአፍሪካ ሃገራት ሞነታይዝ ይደረጋሉ።ዜጎቻቸው በፌስቡክ ገንዘብ እንዲሰሩ ተፈቅዶላቸዋል።
1. Egypt 🇪🇬
2. Democratic Republic of Congo 🇨🇩
3. Ghana 🇬🇭
4. Kenya 🇰🇪
5. Morocco 🇲🇦
6. Nigeria 🇳🇬
7. Tanzania 🇹🇿
8. South Africa 🇿🇦
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ ኢትዮጵያ ስለምን ዜጎች በዘርፉ ሰርተው የሚጠቀሙበት የዲጅታል ዘርፍ እንዲያድግ አልፈለገችም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።መታለፍ ያለባቸው ሂደቶች ታልፈው ተግባራዊ ቢሆን መልካም ነው።