4 months ago
ማያ በጎ አድራጎት ድርጅት በህፃናት የአፈጣጠር ችግር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
4 months ago
በአዲስ አበባ የህፃናት የአፈጣጠር ችግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ !
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ህመሞች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሂዷል።
በኢትዮጵያ በአመት ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት እንደሚወለዱ የተገለጸ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ የእናቶች የፎሊክ አሲድ (ቫይታሚን ቢ9) እጥረት መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ ህፃናት በአፈጣጠር ችግሩ ሳቢያ ለዕድሜ ልክ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸውም ተመላክቷል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው በፎሊክ አሲድ ወይም በቫይታሚን ቢ9 የበለፀጉ ምግቦችን ለህብረተሰቡ የማቅረብ (Food Fortification) ስራ ያለውን ፋይዳ ማሳደግ እንደሚገባ ተገልጿል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገርአቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የአካቶ ትምህርት እና ተጠቃሚነት ከመከላከል ስራው ባሻገር፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት፣ የአካቶ ትምህርት (Inclusive Education) ተጠቃሚ የመሆን መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
መድረኩም በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይትም አካሂዷል።
በዛሬዉ መርሀ-ግብር የጤና ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች፣የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራሮች፣የጥበብ ባለሙያዎች እና የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው ተገኝተዋል
#fastmereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ህመሞች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር አካሂዷል።
በኢትዮጵያ በአመት ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት እንደሚወለዱ የተገለጸ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ የእናቶች የፎሊክ አሲድ (ቫይታሚን ቢ9) እጥረት መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ ህፃናት በአፈጣጠር ችግሩ ሳቢያ ለዕድሜ ልክ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸውም ተመላክቷል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው በፎሊክ አሲድ ወይም በቫይታሚን ቢ9 የበለፀጉ ምግቦችን ለህብረተሰቡ የማቅረብ (Food Fortification) ስራ ያለውን ፋይዳ ማሳደግ እንደሚገባ ተገልጿል።
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገርአቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
የአካቶ ትምህርት እና ተጠቃሚነት ከመከላከል ስራው ባሻገር፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት፣ የአካቶ ትምህርት (Inclusive Education) ተጠቃሚ የመሆን መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል፡፡
መድረኩም በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይትም አካሂዷል።
በዛሬዉ መርሀ-ግብር የጤና ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎች፣የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አመራሮች፣የጥበብ ባለሙያዎች እና የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው ተገኝተዋል
5 months ago
በኢትዮጵያ በየዓመቱ 41 ሺህ ህጻናት ከአፈጣጠር ችግር ጋር እንደሚወለዱ ተገለጸ፤ መፍትሄውስ ምን ይሆን?
#ethiopia | በኢትዮጵያ በየዓመቱ 41 ሺህ የሚጠጉ ህጻናት ከተለያዩ የአፈጣጠር የጤና ችግሮች ጋር እንደሚወለዱ የጤና ባለሙያዎች አስታወቁ። ከእነዚህ ችግሮች መካከል «ስፓይና ቢፊዳ» (Spina Bifida) እና ተያያዥነት ያለው የጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ወይም «ሃይድሮሴፋለስ» (Hydrocephalus) በዋናነት ይጠቀሳሉ።
የሴንትራል መላ ሮተሪ ክለብ፣ ሪችአናዘር ፋውንዴሽን፣ አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት እና የጤና ሚኒስቴር በመተባበር «የአፈጣጠር ችግሮችን መቆጣጠርና መንከባከብ» በሚል ርዕስ ባዘጋጁት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ እንደተገለጸው፥ እነዚህ የጤና እክሎች ሕጻናትን ለዕድሜ ልክ የአካል ጉዳትና ብሎም ለሞት ያጋልጧቸዋል።
የችግሩ ዋነኛ መንስኤ ምንድነው?
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት እስከ 70 በመቶ የሚሆነው የስፓይና ቢፊዳ (የአከርካሪ አጥንትና የህብለ ሰረሰር ክፍተት) ችግር የሚከሰተው በእናቶች የፎሊክ አሲድ (Folic Acid) እጥረት፣ በሌሎች ተጓዳኝ የጤና ችግሮች፣ እንዲሁም እናቶች በሚጠቀሟቸው አንዳንድ መድኃኒቶች ምክንያት ነው።
እንዴት መከላከል ይቻላል?
በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ባለሙያዎች እና ፖሊሲ አውጪዎች የሚከተሉትን የመፍትሄ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል
* የአመጋገብ ዘይቤ፡ እድሜያቸው ከ15 እስከ 49 ዓመት የሆኑ ሴቶች በተፈጥሮ ፎሊክ አሲድ ያላቸውን ምግቦች ማዘውተር አለባቸው።
* ቅድመ ዝግጅት፡ እርግዝና ከማቀድ 3 ወራት በፊት ጀምሮ እና በእርግዝና ወቅት የፎሊክ አሲድ እንክብሎችን መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።
* የበለፀጉ ምግቦች፡ በፎሊክ አሲድ የበለፀጉ የስንዴ ዱቄቶችን እና ዘይቶችን መጠቀም ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሰዋል።
ይህ አገር አቀፍ መድረክ፤ ከአፈጣጠር ችግር ጋር የሚኖሩ ህጻናትን የህይወት ጥራት ለማሻሻል የሚያስችሉ ስልቶች ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ ተጠናቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #healthnews #ethiopianhealth #ministryofhealth #spinabifidaawareness #folicacid #healthypregnancy #addisababa #የጤናመረጃ #ኢትዮጵያ
#ethiopia | በኢትዮጵያ በየዓመቱ 41 ሺህ የሚጠጉ ህጻናት ከተለያዩ የአፈጣጠር የጤና ችግሮች ጋር እንደሚወለዱ የጤና ባለሙያዎች አስታወቁ። ከእነዚህ ችግሮች መካከል «ስፓይና ቢፊዳ» (Spina Bifida) እና ተያያዥነት ያለው የጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ወይም «ሃይድሮሴፋለስ» (Hydrocephalus) በዋናነት ይጠቀሳሉ።
የሴንትራል መላ ሮተሪ ክለብ፣ ሪችአናዘር ፋውንዴሽን፣ አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት እና የጤና ሚኒስቴር በመተባበር «የአፈጣጠር ችግሮችን መቆጣጠርና መንከባከብ» በሚል ርዕስ ባዘጋጁት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ እንደተገለጸው፥ እነዚህ የጤና እክሎች ሕጻናትን ለዕድሜ ልክ የአካል ጉዳትና ብሎም ለሞት ያጋልጧቸዋል።
የችግሩ ዋነኛ መንስኤ ምንድነው?
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት እስከ 70 በመቶ የሚሆነው የስፓይና ቢፊዳ (የአከርካሪ አጥንትና የህብለ ሰረሰር ክፍተት) ችግር የሚከሰተው በእናቶች የፎሊክ አሲድ (Folic Acid) እጥረት፣ በሌሎች ተጓዳኝ የጤና ችግሮች፣ እንዲሁም እናቶች በሚጠቀሟቸው አንዳንድ መድኃኒቶች ምክንያት ነው።
እንዴት መከላከል ይቻላል?
በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ባለሙያዎች እና ፖሊሲ አውጪዎች የሚከተሉትን የመፍትሄ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል
* የአመጋገብ ዘይቤ፡ እድሜያቸው ከ15 እስከ 49 ዓመት የሆኑ ሴቶች በተፈጥሮ ፎሊክ አሲድ ያላቸውን ምግቦች ማዘውተር አለባቸው።
* ቅድመ ዝግጅት፡ እርግዝና ከማቀድ 3 ወራት በፊት ጀምሮ እና በእርግዝና ወቅት የፎሊክ አሲድ እንክብሎችን መውሰድ እጅግ አስፈላጊ ነው።
* የበለፀጉ ምግቦች፡ በፎሊክ አሲድ የበለፀጉ የስንዴ ዱቄቶችን እና ዘይቶችን መጠቀም ችግሩን በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሰዋል።
ይህ አገር አቀፍ መድረክ፤ ከአፈጣጠር ችግር ጋር የሚኖሩ ህጻናትን የህይወት ጥራት ለማሻሻል የሚያስችሉ ስልቶች ላይ ጥልቅ ውይይት በማድረግ ተጠናቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #healthnews #ethiopianhealth #ministryofhealth #spinabifidaawareness #folicacid #healthypregnancy #addisababa #የጤናመረጃ #ኢትዮጵያ
5 months ago
የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ!
ይህ የሆፕ ኤስቢኤች ጥሪ ነው።
ይህን ያለው ደግሞ በ2026 ብሔራዊ የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ ከጤና ጥበቃ ጋር ያደረገውን ንቅናቄ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
በተለይ በህብለሰረሰር ዘንግ ክፍተት የአፈጣጠር ችግር( Spina Bifida and Hydrocephalus) ያለባቸውን ከ6000 በላይ ህፃናት ድጋፍ እያደረገ ያለው HOPE-SBH ልጆቼ መ ማር እየቻሉ እድሉን አለማግኘታቸው እንደአገር ሊታሰብበት ይገባል ብሏል።
HOPE-SBH (ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች) ባለፉት ሳምንታት ብቻ
በብሔራዊ ደረጃ
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ሀገር አቀፍ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር
በአዲስ አበባ
- ከሶስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ200 የሚበልጡ ተማሪዎችን ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፓርላማ አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከአርቲስቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አዘጋጅቷል።
- በስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ የተጎዱ ቤተሰቦች ከፊዚዮቴራፒ፣ ከአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና የባለሙያዎች አገልግሎት ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ውስጥ ሁለገብ እንክብካቤ ድጋፍ ጊዜ አካሂዷል።
- በአዲስ አበባ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የአዲስ አበባን የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ መክፈቻ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አድርጓል።
በአፋር ክልል
- በክልሉ ስላሉት ስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ችግር እና ሊወሰዱ የሚገቡ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች ላይ ለመወያየት ከዋና ዋና ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
- በዱብቲ 1500 የትምህርት ሰጪ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሂዷል።
የኦሮሚያ ክልል
- ከኦሮሚያ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በክልል ደተጃ የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ አካሂዷል።
-በጅማ ከተማ ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲሁም 1,500 የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል።
- የነርቭ ዘንግ ክፍተቶችን የመከላከል እና የመንከባከብ ስራን በማጠናከር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በጅማ ከተማ አዘጋጅቷል።
በሲዳማ ክልል
- ከሲዳማ ጤና ጥበቃ ቢሮ ጋር በመተባበር የወሊድ መጓደል/የአፈጣጠር ችግ ዘመቻ ክልላዊ የመክፈቻና መዝጊያ ዝግጅቶችን አድርጓል።
የአማራ ክልል
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ክልላዊ የመዝጊያ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከአማራ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር
- በዘመቻው ወቅት ለተደረጉ ቀዶ ጥገናዎች በአይነት ድጋፍ ተደረገ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
- በዘመቻው ወቅት የአከርካሪ አጥንት እና የሃይድሮሴፋለስ ጉዳቶችን እና አራት የነርቭ ቀዶ ጥገና ዎች እንዲካሄዱ አመቻችቷል።
- ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ በርካታ ተሳታፊዎችን ያሳተፈ በSpina Bifida እና Hydrocephalus ዙሪያ አውደ ጥናት አካሂዷል።
-በከተማው በሚገኙ ሁለት አካባቢዎች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የህዝብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሰርቷል። 2,000 የትምህርት መስጫ ቁሳቁሶችን በሶስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች አከፋፍሏል።
በዝግጅቱ ማጠቃለያ ላይ የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራችና ባለራእይ ወ/ሮ ቤዛ በሻህ የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ! የሚል መፈክር አሰምተዋል።
ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች አሁንም በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የጠቆመ ሲሆን ለዚሁና መሰል ድጋፎች ላደረገው አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተርክቶለታል።
ይህ የሆፕ ኤስቢኤች ጥሪ ነው።
ይህን ያለው ደግሞ በ2026 ብሔራዊ የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ ከጤና ጥበቃ ጋር ያደረገውን ንቅናቄ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
በተለይ በህብለሰረሰር ዘንግ ክፍተት የአፈጣጠር ችግር( Spina Bifida and Hydrocephalus) ያለባቸውን ከ6000 በላይ ህፃናት ድጋፍ እያደረገ ያለው HOPE-SBH ልጆቼ መ ማር እየቻሉ እድሉን አለማግኘታቸው እንደአገር ሊታሰብበት ይገባል ብሏል።
HOPE-SBH (ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች) ባለፉት ሳምንታት ብቻ
በብሔራዊ ደረጃ
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ሀገር አቀፍ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር
በአዲስ አበባ
- ከሶስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ200 የሚበልጡ ተማሪዎችን ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፓርላማ አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከአርቲስቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አዘጋጅቷል።
- በስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ የተጎዱ ቤተሰቦች ከፊዚዮቴራፒ፣ ከአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና የባለሙያዎች አገልግሎት ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ውስጥ ሁለገብ እንክብካቤ ድጋፍ ጊዜ አካሂዷል።
- በአዲስ አበባ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የአዲስ አበባን የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ መክፈቻ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አድርጓል።
በአፋር ክልል
- በክልሉ ስላሉት ስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ችግር እና ሊወሰዱ የሚገቡ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች ላይ ለመወያየት ከዋና ዋና ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
- በዱብቲ 1500 የትምህርት ሰጪ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሂዷል።
የኦሮሚያ ክልል
- ከኦሮሚያ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በክልል ደተጃ የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ አካሂዷል።
-በጅማ ከተማ ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲሁም 1,500 የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል።
- የነርቭ ዘንግ ክፍተቶችን የመከላከል እና የመንከባከብ ስራን በማጠናከር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በጅማ ከተማ አዘጋጅቷል።
በሲዳማ ክልል
- ከሲዳማ ጤና ጥበቃ ቢሮ ጋር በመተባበር የወሊድ መጓደል/የአፈጣጠር ችግ ዘመቻ ክልላዊ የመክፈቻና መዝጊያ ዝግጅቶችን አድርጓል።
የአማራ ክልል
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ክልላዊ የመዝጊያ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከአማራ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር
- በዘመቻው ወቅት ለተደረጉ ቀዶ ጥገናዎች በአይነት ድጋፍ ተደረገ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
- በዘመቻው ወቅት የአከርካሪ አጥንት እና የሃይድሮሴፋለስ ጉዳቶችን እና አራት የነርቭ ቀዶ ጥገና ዎች እንዲካሄዱ አመቻችቷል።
- ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ በርካታ ተሳታፊዎችን ያሳተፈ በSpina Bifida እና Hydrocephalus ዙሪያ አውደ ጥናት አካሂዷል።
-በከተማው በሚገኙ ሁለት አካባቢዎች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የህዝብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሰርቷል። 2,000 የትምህርት መስጫ ቁሳቁሶችን በሶስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች አከፋፍሏል።
በዝግጅቱ ማጠቃለያ ላይ የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራችና ባለራእይ ወ/ሮ ቤዛ በሻህ የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ! የሚል መፈክር አሰምተዋል።
ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች አሁንም በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የጠቆመ ሲሆን ለዚሁና መሰል ድጋፎች ላደረገው አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተርክቶለታል።
Sponsored by
Surafel
5 months ago
በስፓይና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ግንዛቤ የፈጠረ የተማሪዎች ውድድር ተካሄደ
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
6 months ago
በአመት ከ44,000 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ከአፈጣጠር ችግር ጋር ይወለዳሉ!
#fastmereja I እሊያንስ ፎር በርዝ ድፌክት (አብዲ) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽንና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በነርቭ ዘንግ ክፍተት እና ሀይድሮሴፋለስ(Spina Bifida and Hydrocephalus) በሽታ ዙሪያ ላይ ያተኮረ የጋዜጠኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬዉ እለት በሞናርክ ሆቴል ተካሂዷል።
ስፓይና ቢፊዳ (የነርቨ ዘንግ አፈጣጠር ) ችግሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን የአከርካሪ አጥንትና የህብለ ሰረሰር በአግባቡ አለመዘጋት/ክፍተት ነው፡፡
ሃይድሮሴፋለስ (የጭንቅላት ውስጥ ከመጠን በላይ የፈሳሽ ክምችት) ሲሆን ይህም የአዕምሮ ግፊት እንዲጨምርና የራስ ቅል ላይ መሰንጠቅን ሊያስከትል ይችላል።
ስልጠናዉ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን ለመከላከል እና ስለችግሩ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለዉን ግንዛቤ ለማሳደግ ታልሞ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በመሆኑም እነዚህ ህፃናት በዚሁ ህመም ምክንያት ለእድሜ ልክ የመንቀሳቀስ ችግር እና እራሳቸውን ችለው የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸዉ ነዉ የተገለፀዉ፡፡
ፎሊክ አሲድ እጥረትን ለመከላከል እናቶች በመጀመሪያ የእርግዝና ወራቶች በእንክብል መልክ የሚሰጥ መድሃኒት መውሰድ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ስንዴ፣ ዘይት፣ ጨው የበለፀጉ ምግቦችን መውሰድ የፎሊክአሲድ ችግርን ለመቅረፍ ወሳኝ ነው ተብሏል።
በተጨማሪም በችግሩ የተጎዱ ህጻናት እና ቤተሰቦቻቸው ጥራቱን የጠበቀ ህክምና እንዲሁም የእለት ተእለት ህይወታቸዉን በአግባቡ እንዲመሩ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር እንደሚገባ ነዉ የተገለፀዉ።
#fastmereja I እሊያንስ ፎር በርዝ ድፌክት (አብዲ) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽንና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በነርቭ ዘንግ ክፍተት እና ሀይድሮሴፋለስ(Spina Bifida and Hydrocephalus) በሽታ ዙሪያ ላይ ያተኮረ የጋዜጠኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬዉ እለት በሞናርክ ሆቴል ተካሂዷል።
ስፓይና ቢፊዳ (የነርቨ ዘንግ አፈጣጠር ) ችግሮች ውስጥ አንዱ ሲሆን የአከርካሪ አጥንትና የህብለ ሰረሰር በአግባቡ አለመዘጋት/ክፍተት ነው፡፡
ሃይድሮሴፋለስ (የጭንቅላት ውስጥ ከመጠን በላይ የፈሳሽ ክምችት) ሲሆን ይህም የአዕምሮ ግፊት እንዲጨምርና የራስ ቅል ላይ መሰንጠቅን ሊያስከትል ይችላል።
ስልጠናዉ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን ለመከላከል እና ስለችግሩ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለዉን ግንዛቤ ለማሳደግ ታልሞ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በመሆኑም እነዚህ ህፃናት በዚሁ ህመም ምክንያት ለእድሜ ልክ የመንቀሳቀስ ችግር እና እራሳቸውን ችለው የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸዉ ነዉ የተገለፀዉ፡፡
ፎሊክ አሲድ እጥረትን ለመከላከል እናቶች በመጀመሪያ የእርግዝና ወራቶች በእንክብል መልክ የሚሰጥ መድሃኒት መውሰድ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ስንዴ፣ ዘይት፣ ጨው የበለፀጉ ምግቦችን መውሰድ የፎሊክአሲድ ችግርን ለመቅረፍ ወሳኝ ነው ተብሏል።
በተጨማሪም በችግሩ የተጎዱ ህጻናት እና ቤተሰቦቻቸው ጥራቱን የጠበቀ ህክምና እንዲሁም የእለት ተእለት ህይወታቸዉን በአግባቡ እንዲመሩ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር እንደሚገባ ነዉ የተገለፀዉ።
6 months ago
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት እንደሚጠቁ ተገለጸ
አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ እንደተገለጸው፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ 44,000 በላይ ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተት (Spina Bifida) እና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት (Hydrocephalus) ተጠቂ ይሆናሉ።
የመከላከያ መንገዶች፡ እንደ ዱቄትና ዘይት ያሉ የምግብ ምርቶችን በፎሊክ አሲድ (Folic Acid) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን እስከ 70% መቀነስ እንደሚቻል ተጠቁሟል።
የሕክምና ዕድል፡ ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት በወቅቱ የቀዶ ጥገና ሕክምናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ፣ የተሻለና ውጤታማ ሕይወት የመምራት ዕድል እንዳላቸው ተመላክቷል።
የሚዲያ ሚና፡ ጋዜጠኞች ስለ በሽታው መከላከልና ፈላጊዎች ሊያገኙት ስለሚገባው ድጋፍ ለህዝቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ትልቅ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ ቀርቧል።
ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ ምን አሉ?
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በቅንጅት በመስራት በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት መቀነስ ይቻላል።
ስለ ፎሊክ አሲድ ጠቃሚ መረጃዎች
ፎሊክ አሲድ ለሴሎች እድገትና ለፅንስ የነርቭ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ የሆነ የቢ-ቪታሚን (B9) አይነት ነው። አንዲት ሴት እርግዝና ከመከሰቱ ቢያንስ 3 ወራት በፊትና በእርግዝና የመጀመሪያዎቹ ወራት መውሰድ ይኖርባታል። እንደ አረንጓዴ ቅጠላቅጠል፣ ባቄላ፣ አተርና ብርቱካን ያሉ ምግቦች ተፈጥሯዊ የፎሊክ አሲድ ምንጮች ናቸው።
የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
ድርጅቱ በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና መላው ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።
አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ እንደተገለጸው፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ 44,000 በላይ ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተት (Spina Bifida) እና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት (Hydrocephalus) ተጠቂ ይሆናሉ።
የመከላከያ መንገዶች፡ እንደ ዱቄትና ዘይት ያሉ የምግብ ምርቶችን በፎሊክ አሲድ (Folic Acid) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን እስከ 70% መቀነስ እንደሚቻል ተጠቁሟል።
የሕክምና ዕድል፡ ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት በወቅቱ የቀዶ ጥገና ሕክምናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ፣ የተሻለና ውጤታማ ሕይወት የመምራት ዕድል እንዳላቸው ተመላክቷል።
የሚዲያ ሚና፡ ጋዜጠኞች ስለ በሽታው መከላከልና ፈላጊዎች ሊያገኙት ስለሚገባው ድጋፍ ለህዝቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ ትልቅ ሚና እንዲጫወቱ ጥሪ ቀርቧል።
ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ ምን አሉ?
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በቅንጅት በመስራት በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና የጨቅላ ሕፃናትን ሞት መቀነስ ይቻላል።
ስለ ፎሊክ አሲድ ጠቃሚ መረጃዎች
ፎሊክ አሲድ ለሴሎች እድገትና ለፅንስ የነርቭ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ የሆነ የቢ-ቪታሚን (B9) አይነት ነው። አንዲት ሴት እርግዝና ከመከሰቱ ቢያንስ 3 ወራት በፊትና በእርግዝና የመጀመሪያዎቹ ወራት መውሰድ ይኖርባታል። እንደ አረንጓዴ ቅጠላቅጠል፣ ባቄላ፣ አተርና ብርቱካን ያሉ ምግቦች ተፈጥሯዊ የፎሊክ አሲድ ምንጮች ናቸው።
የገቢ ማሰባሰቢያ ጥሪ
ድርጅቱ በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና መላው ማህበረሰብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።
6 months ago
የነርቭ ዘንግ ክፍተትና ፎሊክ አሲድ ላይ ለጋዜጠኞች ስልጠና ተሰጠ
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia
12 months ago
የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ውሃ ክምችት ህመሞችን በእርግዝና እቅድ መከላከል ይቻላል ተባለ
#ethiopia | በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ20 ሺህ እስከ 50 ሺህ የሚደርሱ ሕፃናት የነርቭ ዘንግ ክፍተት (Spina Bifida) እና ከልክ ያለፈ የጭንቅላት ውሃ ክምችት (Hydrocephalus) በሚባሉ የአፈጣጠር ችግሮች እንደሚወለዱ ተገለጸ።
ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ይህ አሃዝ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ነው። እነዚህ ህመሞች በዋነኝነት የሚከሰቱት የፎሊክ አሲድ እጥረት በመኖሩ ሲሆን፣ በእርግዝና እቅድ አማካይነት መከላከል እንደሚቻል በዘርፉ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው የሆፕ ኤስቢኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ቤዛ በሻ ተናግረዋል።
የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ውሃ ክምችት ህመሞች በዋነኝነት የሚከሰቱት የቫይታሚን B9 ወይም ፎሊክ አሲድ እጥረት ሲሆን፣ ይህ የአፈጣጠር ችግር የሚፈጠረው በእርግዝና የመጀመሪያ ወር ውስጥ ነው። በዚያ ወሳኝ ወቅት የፅንሱ የነርቭ ዘንግ እድገት ስለሚካሄድ፣ በእናቲቱ ደም ውስጥ በቂ የፎሊክ አሲድ መጠን መኖር ወሳኝ ነው።
የሕመሙ ስርጭት በኢትዮጵያ ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ከ70 እስከ 75 በመቶ የሚሆኑት ሕፃናት በእነዚህ ችግሮች እንደሚወለዱ ወ/ሮ ቤዛ ተናግረዋል። ይህ ችግር ያለባቸው ሰዎች ለሕይወት ዘመን የአካል እና የአእምሮ ጤና ችግሮች ይጋለጣሉ ተብሏል።
ወ/ሮ ቤዛ እንዳብራሩት፣ የነርቭ ዘንግ ክፍተት ህመምን ለመከላከል ከሁሉ በፊት እርግዝናን ማቀድ ወሳኝ ነው ያሉ ሲሆን የእናትየው የነርቭ ዘንግ እድገት የሚፈጠረው ፅንስ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ እስከ 28ኛው ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ስለሆነ፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ በቂ የፎሊክ አሲድ ክምችት በእናት ደም ውስጥ መኖር አለበት።
ይህን ለማረጋገጥ፣ ለእርግዝና የምትዘጋጅ ሴት ከመፀነሷ ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ በቂ የፎሊክ አሲድ እና ሌሎች ጠቃሚ የምግብ ንጥረ ነገሮችን መውሰድ እና በአመጋገብዋ ላይ ትኩረት መስጠት ይኖርባታል። የህመሙን ስርጭት ለመግታት፣ በዘርፉ በቂ ትኩረት እና ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን በዘርፉ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በትናንትናው እለት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ ውይይት ተገልጿል።
📷 Sisay Guzay
#ethiopia | በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ20 ሺህ እስከ 50 ሺህ የሚደርሱ ሕፃናት የነርቭ ዘንግ ክፍተት (Spina Bifida) እና ከልክ ያለፈ የጭንቅላት ውሃ ክምችት (Hydrocephalus) በሚባሉ የአፈጣጠር ችግሮች እንደሚወለዱ ተገለጸ።
ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ይህ አሃዝ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ነው። እነዚህ ህመሞች በዋነኝነት የሚከሰቱት የፎሊክ አሲድ እጥረት በመኖሩ ሲሆን፣ በእርግዝና እቅድ አማካይነት መከላከል እንደሚቻል በዘርፉ ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራው የሆፕ ኤስቢኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ቤዛ በሻ ተናግረዋል።
የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ውሃ ክምችት ህመሞች በዋነኝነት የሚከሰቱት የቫይታሚን B9 ወይም ፎሊክ አሲድ እጥረት ሲሆን፣ ይህ የአፈጣጠር ችግር የሚፈጠረው በእርግዝና የመጀመሪያ ወር ውስጥ ነው። በዚያ ወሳኝ ወቅት የፅንሱ የነርቭ ዘንግ እድገት ስለሚካሄድ፣ በእናቲቱ ደም ውስጥ በቂ የፎሊክ አሲድ መጠን መኖር ወሳኝ ነው።
የሕመሙ ስርጭት በኢትዮጵያ ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ከ70 እስከ 75 በመቶ የሚሆኑት ሕፃናት በእነዚህ ችግሮች እንደሚወለዱ ወ/ሮ ቤዛ ተናግረዋል። ይህ ችግር ያለባቸው ሰዎች ለሕይወት ዘመን የአካል እና የአእምሮ ጤና ችግሮች ይጋለጣሉ ተብሏል።
ወ/ሮ ቤዛ እንዳብራሩት፣ የነርቭ ዘንግ ክፍተት ህመምን ለመከላከል ከሁሉ በፊት እርግዝናን ማቀድ ወሳኝ ነው ያሉ ሲሆን የእናትየው የነርቭ ዘንግ እድገት የሚፈጠረው ፅንስ ከተፈጠረበት ቀን ጀምሮ እስከ 28ኛው ቀን ባለው ጊዜ ውስጥ ስለሆነ፣ በዚህ ጊዜ ውስጥ በቂ የፎሊክ አሲድ ክምችት በእናት ደም ውስጥ መኖር አለበት።
ይህን ለማረጋገጥ፣ ለእርግዝና የምትዘጋጅ ሴት ከመፀነሷ ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ በቂ የፎሊክ አሲድ እና ሌሎች ጠቃሚ የምግብ ንጥረ ነገሮችን መውሰድ እና በአመጋገብዋ ላይ ትኩረት መስጠት ይኖርባታል። የህመሙን ስርጭት ለመግታት፣ በዘርፉ በቂ ትኩረት እና ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን በዘርፉ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በትናንትናው እለት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ ውይይት ተገልጿል።
📷 Sisay Guzay
Sponsored by
Surafel
Comments