6 days ago
በምግብ ወለድ በሽታዎች በዓለም ላይ በየዓመቱ እስከ 1.5 ሚሊዮን ሕዝብ ይሞታል ተባለ!
#fastmereja I በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ 866 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በምግብ ወለድ በሽታዎች (Foodborne illnesses) የሚጠቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ሕይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) አዲስ ያወጣው መረጃ አመለከተ።
ይህ አስደንጋጭ የወረርሽኝ ጫና በተለይ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትን እና በማደግ ያሉ አገራትን በከፍተኛ ሁኔታ እያጠቃ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ከዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ጋር በመተባበር “ከምግብ ደህንነት ችግሮች ወደ መፍትሔዎች በሁሉም ቦታ ደህንነቱ የተጠበቀ ምግብ” በሚል መሪ ቃል በዛሬዉ እለት በስካይላይት ሆቴል ባዘጋጁት የዉይይት መድረክ ላይ ነው።
መድረኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የምግብ ደህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የደብሊውኤፍፒ (WFP) የሰፕላይ ቼይን ኃላፊ የሆኑት ክላራ ሲልቫ እንደገለፁት ፣ እነዚህ ቁጥሮች ዝም ብለው ቁጥር ብቻ ሳይሆኑ አስቸኳይ የድርጊት ጥሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ድርጅታቸው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ለ3 ሚሊዮን ተጋላጭ ወገኖች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከ2026 እስከ 2030 ባለው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ምግብን ከውጭ ከማስገባት ይልቅ ወደ ሀገር ውስጥ ምርት ግዢ (Local Sourcing) ለማሸጋገር እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን በበኩሉ የምግብ ቁጥጥር ሥርዓቱን "ከቅድመ-ገበያ እስከ ድኅረ‐ገበያ" ለማዘመን በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ይፋ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በኬላዎች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠናክር ግዙፍና ዘመናዊ የላቦራቶሪ ኮምፕሌክስ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያው መድረሱ ተገልጿል።
እንዲሁም ማንኛውም ያልታወቀ ወይም ያልተረጋገጠ የምግብ ምርት ወደ አገር ውስጥ እንዳይገባ፣ ይዘቱና የአመራረት ሂደቱ በጥልቀት የሚገመገምበት ዘመናዊ የሰነድ ምዝገባ ሥርዓት ወደ ሥራ መግባቱን አስታዉቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሄራን ገርባ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፣ ይህንን የጥራት ማረጋገጫና የቁጥጥር ሥርዓት ወደ ክልሎች፣ በተለይም የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደሚገኙባቸው አካባቢዎች የማውረድ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ አክለዉም ክልሎች የችርቻሮ ንግዱንና የአቅርቦት መስመሩን የሚቆጣጠሩ በመሆናቸው፣ በታችኛው መዋቅር ላይ የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት መዘርጋት "የመደራደሪያ ጉዳይ አይደለም" ሲሉ ገልፀዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍም የክትትል ሥርዓትን ማጠናከር፣ በሳይንስ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መውሰድ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) ጨምሮ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር ማሳደግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
እንዲሁም በመርሀ-ግብሩ ላይ ባለድርሻ አካላት በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ ገለፃዎችን ያቀረቡ ሲሆንየ2026 (እ.ኤ.አ) የዓለም የምግብ ደህንነት ቀን ዋና መሪ ቃል የሆነውን “ከችግር ወደ መፍትሄ - አስተማማኝ ምግብ በየትኛውም ቦታ” (From Burden to Solutions - Safe Food Everywhere) የሚለውን ሀሳብ መሰረት ያደረገ የፓናል ዉይይትም ተካሂዷል።
#fastmereja I በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ 866 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በምግብ ወለድ በሽታዎች (Foodborne illnesses) የሚጠቁ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ እስከ 1.5 ሚሊዮን የሚሆኑት ሕይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) አዲስ ያወጣው መረጃ አመለከተ።
ይህ አስደንጋጭ የወረርሽኝ ጫና በተለይ ዕድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትን እና በማደግ ያሉ አገራትን በከፍተኛ ሁኔታ እያጠቃ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ከዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ጋር በመተባበር “ከምግብ ደህንነት ችግሮች ወደ መፍትሔዎች በሁሉም ቦታ ደህንነቱ የተጠበቀ ምግብ” በሚል መሪ ቃል በዛሬዉ እለት በስካይላይት ሆቴል ባዘጋጁት የዉይይት መድረክ ላይ ነው።
መድረኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የምግብ ደህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የደብሊውኤፍፒ (WFP) የሰፕላይ ቼይን ኃላፊ የሆኑት ክላራ ሲልቫ እንደገለፁት ፣ እነዚህ ቁጥሮች ዝም ብለው ቁጥር ብቻ ሳይሆኑ አስቸኳይ የድርጊት ጥሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ድርጅታቸው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ለ3 ሚሊዮን ተጋላጭ ወገኖች ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ ከ2026 እስከ 2030 ባለው ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ምግብን ከውጭ ከማስገባት ይልቅ ወደ ሀገር ውስጥ ምርት ግዢ (Local Sourcing) ለማሸጋገር እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን በበኩሉ የምግብ ቁጥጥር ሥርዓቱን "ከቅድመ-ገበያ እስከ ድኅረ‐ገበያ" ለማዘመን በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ይፋ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በኬላዎች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠናክር ግዙፍና ዘመናዊ የላቦራቶሪ ኮምፕሌክስ ግንባታ ወደ ማጠናቀቂያው መድረሱ ተገልጿል።
እንዲሁም ማንኛውም ያልታወቀ ወይም ያልተረጋገጠ የምግብ ምርት ወደ አገር ውስጥ እንዳይገባ፣ ይዘቱና የአመራረት ሂደቱ በጥልቀት የሚገመገምበት ዘመናዊ የሰነድ ምዝገባ ሥርዓት ወደ ሥራ መግባቱን አስታዉቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሄራን ገርባ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፣ ይህንን የጥራት ማረጋገጫና የቁጥጥር ሥርዓት ወደ ክልሎች፣ በተለይም የተቀናጁ የግብርና ማቀነባበሪያና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደሚገኙባቸው አካባቢዎች የማውረድ ሥራ መጀመሩን ገልፀዋል።
ዋና ዳይሬክተሯ አክለዉም ክልሎች የችርቻሮ ንግዱንና የአቅርቦት መስመሩን የሚቆጣጠሩ በመሆናቸው፣ በታችኛው መዋቅር ላይ የጥራት ማረጋገጫ ሥርዓት መዘርጋት "የመደራደሪያ ጉዳይ አይደለም" ሲሉ ገልፀዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍም የክትትል ሥርዓትን ማጠናከር፣ በሳይንስ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መውሰድ፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) ጨምሮ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር ማሳደግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
እንዲሁም በመርሀ-ግብሩ ላይ ባለድርሻ አካላት በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ ገለፃዎችን ያቀረቡ ሲሆንየ2026 (እ.ኤ.አ) የዓለም የምግብ ደህንነት ቀን ዋና መሪ ቃል የሆነውን “ከችግር ወደ መፍትሄ - አስተማማኝ ምግብ በየትኛውም ቦታ” (From Burden to Solutions - Safe Food Everywhere) የሚለውን ሀሳብ መሰረት ያደረገ የፓናል ዉይይትም ተካሂዷል።
24 days ago
ኢትዮጵያ የሕክምና ሙከራና የቁጥጥር ሥርዓቷን ዲጂታል አደረገች!
#fastmereja I ኢትዮጵያ በሕክምና ምርምርና ክሊኒካዊ ሙከራዎች (Clinical Trials) ያላትን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የቁጥጥር ሥርዓቷን ዘመናዊ ለማድረግ ያለመ አዲስ የዲጂታል መረጃ ሥርዓት በይፋ ሥራ አስጀመረች።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ይፋ ያደረገው ይህ የኦንላይን ሥርዓት፣ ቀደም ሲል በወረቀትና በአካል ንክኪ ይከናወን የነበረውን የፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር ሂደት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚተካ ነው።
ይህንን አዲስ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ይፋ ለማድረግና ተያያዥ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክን ለመክፈት በተዘጋጀው ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ፍሬህይወት አበበ፣ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ተመራማሪዎች፣ የአካዳሚክ ማኅበረሰብ አባላትና የስፖንሰር ተወካዮች ተገኝተዋል።
አዲሱ ሥርዓት ተመራማሪዎች ባሉበት ሆነው በኦንላይን እንዲያመለክቱና የጉዳያቸውን ደረጃ በቀጥታ (Tracking) እንዲከታተሉ የሚያስችል ሲሆን ከዚህም ባሻገር ፈቃድ ከተሰጠ በኋላም ቢሆን የደኅንነት (Safety) ሪፖርቶች፣ የጂሲፒ (GCP) ኢንስፔክሽን መረጃዎች እና ተያያዥ ግብረ‐መልሶች በጥብቅ የቁጥጥር ሰንሰለት ውስጥ እንዲያልፉ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ፍሬህይወት አበበ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳመለከቱት፣ ድንገት የሚከሰቱ ወረርሽኞች፣ የፀረ-ተህዋሲያን መላመድ (Antimicrobial Resistance) ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በወቅቱ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን ማመንጨት የሚችል ጠንካራ የሕክምና ሙከራ ምርምር አቅምን ይሻል ሲሉ ገልፀዋል።
ሚኒስትር ዲኤታዋ አክለዉም ይህ ሥርዓት ጊዜን፣ ወጪን እና ጉልበትን በመቆጠብ ረገድ የጎላ ሚና እንዳለዉ አስረድተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ የሕክምና ሙከራ ሥርዓቷን በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ለማሟላት ባደረገችው መጠነ-ሰፊ የአደረጃጀትና የአሰራር ለውጥ፣ በዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የሕክምና ሙከራ የቁጥጥር ሥርዓት የብስለት ደረጃ 3 (Maturity Level 3 – ML3)ማግኘት መቻሏ በዕለቱ ተገልጿል።
ቀጣዩ ግብ ባለሥልጣኑን የልህቀት ማዕከልና የብስለት ደረጃ ወደላቀ ደረጃ ማድረስ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ ማንኛውም በሰው ልጅ ላይ የሚደረግ የሕክምና ወይም የመድኃኒት ሙከራ ከባለሥልጣኑ ይፋዊ ፈቃድ ውጪ ሊጀመር እንደማይችልና ያለ ፈቃድ የሚከናወኑ ማናቸውም ሙከራዎች በሕግ “ሕገ-ወጥ” ተብለው በጥብቅ እንደሚቀጡ አስገንዝቧል።
አዲሱ ሥርዓት የቢል ኤንድ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በጋራ ድጋፍ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
#fastmereja I ኢትዮጵያ በሕክምና ምርምርና ክሊኒካዊ ሙከራዎች (Clinical Trials) ያላትን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የቁጥጥር ሥርዓቷን ዘመናዊ ለማድረግ ያለመ አዲስ የዲጂታል መረጃ ሥርዓት በይፋ ሥራ አስጀመረች።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ይፋ ያደረገው ይህ የኦንላይን ሥርዓት፣ ቀደም ሲል በወረቀትና በአካል ንክኪ ይከናወን የነበረውን የፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር ሂደት ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚተካ ነው።
ይህንን አዲስ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ይፋ ለማድረግና ተያያዥ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክን ለመክፈት በተዘጋጀው ታላቅ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ፍሬህይወት አበበ፣ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ተመራማሪዎች፣ የአካዳሚክ ማኅበረሰብ አባላትና የስፖንሰር ተወካዮች ተገኝተዋል።
አዲሱ ሥርዓት ተመራማሪዎች ባሉበት ሆነው በኦንላይን እንዲያመለክቱና የጉዳያቸውን ደረጃ በቀጥታ (Tracking) እንዲከታተሉ የሚያስችል ሲሆን ከዚህም ባሻገር ፈቃድ ከተሰጠ በኋላም ቢሆን የደኅንነት (Safety) ሪፖርቶች፣ የጂሲፒ (GCP) ኢንስፔክሽን መረጃዎች እና ተያያዥ ግብረ‐መልሶች በጥብቅ የቁጥጥር ሰንሰለት ውስጥ እንዲያልፉ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ፍሬህይወት አበበ በመክፈቻ ንግግራቸው እንዳመለከቱት፣ ድንገት የሚከሰቱ ወረርሽኞች፣ የፀረ-ተህዋሲያን መላመድ (Antimicrobial Resistance) ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በወቅቱ ሳይንሳዊ ማስረጃዎችን ማመንጨት የሚችል ጠንካራ የሕክምና ሙከራ ምርምር አቅምን ይሻል ሲሉ ገልፀዋል።
ሚኒስትር ዲኤታዋ አክለዉም ይህ ሥርዓት ጊዜን፣ ወጪን እና ጉልበትን በመቆጠብ ረገድ የጎላ ሚና እንዳለዉ አስረድተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ የሕክምና ሙከራ ሥርዓቷን በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ለማሟላት ባደረገችው መጠነ-ሰፊ የአደረጃጀትና የአሰራር ለውጥ፣ በዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የሕክምና ሙከራ የቁጥጥር ሥርዓት የብስለት ደረጃ 3 (Maturity Level 3 – ML3)ማግኘት መቻሏ በዕለቱ ተገልጿል።
ቀጣዩ ግብ ባለሥልጣኑን የልህቀት ማዕከልና የብስለት ደረጃ ወደላቀ ደረጃ ማድረስ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል።
ባለሥልጣኑ ማንኛውም በሰው ልጅ ላይ የሚደረግ የሕክምና ወይም የመድኃኒት ሙከራ ከባለሥልጣኑ ይፋዊ ፈቃድ ውጪ ሊጀመር እንደማይችልና ያለ ፈቃድ የሚከናወኑ ማናቸውም ሙከራዎች በሕግ “ሕገ-ወጥ” ተብለው በጥብቅ እንደሚቀጡ አስገንዝቧል።
አዲሱ ሥርዓት የቢል ኤንድ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽንን ጨምሮ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት በጋራ ድጋፍ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
2 months ago
እነዚህን 69 ደረጃቸውን ያልጠበቁ የምግብ ምርቶች እንዳትጠቀሙ!
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ባደረገው የገበያ ቁጥጥርና ፍተሻ፣ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ እንዲሁም አስገዳጅ መስፈርቶችን ያላሟሉ 69 የምግብ ምርቶችን ለይቶ ይፋ አድርጓል።
በ570 የንግድ ተቋማት ላይ በተደረገ ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤ፣ 6 የማር ዓይነቶች እንዲሁም ከረሜላና የሕፃናት ምግቦች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሆነው ተገኝተዋል።
ማንኛውንም ምርት ሲገዙ የገላጭ ጽሑፍ፣ የአምራች መረጃ፣ የመለያ ቁጥር (Batch Number) እና የጥራት ምልክት መኖሩን ማረጋገጥ ይገባል።
ባለስልጣኑ እንዳትጠቀሟቸው የከለከላቸው ዋና ዋና ምርቶች፦
የገበታ ጨው ዓይነቶች (ከፊሉ)፦
ሰይፋ፣ ቲና፣ እሙሹ፣ ቃሊ፣ አዮዲን፣ እኑ፣ አራዳ፣ ንጉስ፣ ሀሮት፣ ኩል፣ አሜን፣ ሰቦኑማ፣ እቱ፣ መክሊት፣ ዳግም፣ መርሰን፣ ኒሀል፣ ሊቅ፣ ስካይ፣ ናፊ፣ አቤ፣ ሳሮማ፣ ፀሐይ፣ ማሩ፣ እንቁ፣ ሰኒ፣ ሚያዋ፣ ስኬት፣ ሔራል፣ ቤዝ፣ ገዳ።
የምግብ ዘይት ዓይነቶች፦
ምስራቅ ፀሐይ፣ ቃል፣ አፍራን፣ ኒያ፣ ሪሃ፣ ኤአይ ሻኪር፣ ኤ1-ኑር፣ ጥራ፣ ረዲ፣ አያን፣ ሳፊያ፣ እሰይ፣ አማን፣ ላምሮት ኬኬ፣ እድገት፣ ራኒያ፣ ሸገር፣ ሀይላለ፣ ፍፁም የተጣራ።
ማርና የለውዝ ቅቤ፦
ሀራ፣ ሶራ፣ ብሉ፣ ስዊት ክሬም፣ ሉሲ፣ ስንቅ (ለውዝ ቅቤ)፤ ቤዛ ማር፣ ውብሸት የማር ጠጅ፣ ጂጂ ማር፣ አምባሰል ነጭ ማር፣ የኢሉባቦር ማር።
ከረሜላ፦
ቡርቃ ሎሊፖፕ፣ አዩ ፓፕ፣ አፍሪ፣ ዴሉክሴ።
#getu #efda #foodsafetyethiopia #publichealth #addisababa #ethiopia #consumerprotection #healthyeating #alert #ጥራትቁጥጥር #ጤና #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ባደረገው የገበያ ቁጥጥርና ፍተሻ፣ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ እንዲሁም አስገዳጅ መስፈርቶችን ያላሟሉ 69 የምግብ ምርቶችን ለይቶ ይፋ አድርጓል።
በ570 የንግድ ተቋማት ላይ በተደረገ ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤ፣ 6 የማር ዓይነቶች እንዲሁም ከረሜላና የሕፃናት ምግቦች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሆነው ተገኝተዋል።
ማንኛውንም ምርት ሲገዙ የገላጭ ጽሑፍ፣ የአምራች መረጃ፣ የመለያ ቁጥር (Batch Number) እና የጥራት ምልክት መኖሩን ማረጋገጥ ይገባል።
ባለስልጣኑ እንዳትጠቀሟቸው የከለከላቸው ዋና ዋና ምርቶች፦
የገበታ ጨው ዓይነቶች (ከፊሉ)፦
ሰይፋ፣ ቲና፣ እሙሹ፣ ቃሊ፣ አዮዲን፣ እኑ፣ አራዳ፣ ንጉስ፣ ሀሮት፣ ኩል፣ አሜን፣ ሰቦኑማ፣ እቱ፣ መክሊት፣ ዳግም፣ መርሰን፣ ኒሀል፣ ሊቅ፣ ስካይ፣ ናፊ፣ አቤ፣ ሳሮማ፣ ፀሐይ፣ ማሩ፣ እንቁ፣ ሰኒ፣ ሚያዋ፣ ስኬት፣ ሔራል፣ ቤዝ፣ ገዳ።
የምግብ ዘይት ዓይነቶች፦
ምስራቅ ፀሐይ፣ ቃል፣ አፍራን፣ ኒያ፣ ሪሃ፣ ኤአይ ሻኪር፣ ኤ1-ኑር፣ ጥራ፣ ረዲ፣ አያን፣ ሳፊያ፣ እሰይ፣ አማን፣ ላምሮት ኬኬ፣ እድገት፣ ራኒያ፣ ሸገር፣ ሀይላለ፣ ፍፁም የተጣራ።
ማርና የለውዝ ቅቤ፦
ሀራ፣ ሶራ፣ ብሉ፣ ስዊት ክሬም፣ ሉሲ፣ ስንቅ (ለውዝ ቅቤ)፤ ቤዛ ማር፣ ውብሸት የማር ጠጅ፣ ጂጂ ማር፣ አምባሰል ነጭ ማር፣ የኢሉባቦር ማር።
ከረሜላ፦
ቡርቃ ሎሊፖፕ፣ አዩ ፓፕ፣ አፍሪ፣ ዴሉክሴ።
#getu #efda #foodsafetyethiopia #publichealth #addisababa #ethiopia #consumerprotection #healthyeating #alert #ጥራትቁጥጥር #ጤና #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
10ኛው "ኢትዮ ኸልዝ" ዓለምአቀፍ አውደርዕይ እና ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው
#fastmereja I በአስርተ ዓመታት የጤናው ዘርፍ ጉዞ ታላቅ ስም ያተረፈው ኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደርዕይና ጉባኤ፣ ለ10ኛ ጊዜ ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) እንደሚካሄድ ዛሬ መጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ፕራና ኢቨንትስ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያቀርባሉ።
የዘንድሮው ኹነት 2ኛው የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ጎን ለጎን የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ማሳየትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከ20 በላይ ከሚሆኑ የሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር፣ ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎች ለጤና ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
2ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ፎረም፣ የጤና አመራር ጉባኤ እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶን በኹነቱ ውስጥ የተካተቱ አቢይ መድረኮች ናቸው።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከባንግላዴሽ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እና አሜሪካ የመጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ።
ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን፣ የንግድ ትስስር እንዲጎለብትና የሕክምና አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም ተቋማት ሙሉ ዕውቅና የተሰጠው ይህ አውደርዕይ፣ የዘርፉ ተዋናዮች የሚገናኙበት ትልቁ ሀገራዊ መድረክ ነው።
#ኹነት
#fastmereja I በአስርተ ዓመታት የጤናው ዘርፍ ጉዞ ታላቅ ስም ያተረፈው ኢትዮ ኸልዝ ዓለምአቀፍ አውደርዕይና ጉባኤ፣ ለ10ኛ ጊዜ ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC) እንደሚካሄድ ዛሬ መጋቢት 08 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል በተሰጠ መግለጫ ተገልጿል።
ፕራና ኢቨንትስ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ ከ8 ሀገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያቀርባሉ።
የዘንድሮው ኹነት 2ኛው የሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ጎን ለጎን የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም ማሳየትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከ20 በላይ ከሚሆኑ የሙያ ማኅበራት ጋር በመተባበር፣ ከ40 በላይ የሙያ ማጎልበቻ ስልጠናዎች ለጤና ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
2ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ፎረም፣ የጤና አመራር ጉባኤ እና 3ኛው የዲጂታል ኸልዝ ሃካቶን በኹነቱ ውስጥ የተካተቱ አቢይ መድረኮች ናቸው።
ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከባንግላዴሽ፣ ቻይና፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቱርክ፣ የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እና አሜሪካ የመጡ ኩባንያዎች ይሳተፋሉ።
ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የጤናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፋጠን፣ የንግድ ትስስር እንዲጎለብትና የሕክምና አገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል። በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም ተቋማት ሙሉ ዕውቅና የተሰጠው ይህ አውደርዕይ፣ የዘርፉ ተዋናዮች የሚገናኙበት ትልቁ ሀገራዊ መድረክ ነው።
#ኹነት
3 months ago
10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ለማዘመንና የሕክምና ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳለጥ ያለመው 10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ፣ እንዲሁም 2ኛው የአገር ውስጥ የሕክምና ግብዓቶች ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
በዚህ መድረክ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት እና በፕራና ኤቨንትስ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ከስምንት አገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ለታዳሚዎች ያቀርባሉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከእንግሊዝ፣ ከቻይና፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከታይላንድ፣ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ከአሜሪካ የመጡ ታዋቂ ድርጅቶች የሚሳተፉ በመሆኑ፣ የውጭውን ቴክኖሎጂ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለማስተሳሰርና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከንግድ ትርኢቱ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ከ40 በላይ ቀጣይነት ያለው የሙያ ማሳደጊያ (CPD) ስልጠናዎች የሚሰጡ ሲሆን፣ ከ20 በላይ የሚሆኑ የዘርፉ የሙያ ማህበራትም በዝግጅቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የጤና አመራር ጉባኤ፣ የዲጂታል ሄልዝ ፎረም እና የሳይንሳዊ መድረኮች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በጤናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን በምርምርና በቴክኖሎጂ ለመፍታት የሚያስችሉ ምክክሮች የሚደረጉባቸው መድረኮች ይሆናሉ።
ይህ ዝግጅት በተለይም የሀገር ውስጥ የሕክምና መሣሪያዎችና የመድኃኒት አምራቾች ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ድርሻ እንዲያሳድጉና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም መንግስታዊ ተቋማት ሙሉ እውቅናና ድጋፍ የሚደረግለት ይህ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiohealth2026 #healthcareethiopia #medicalexhibition #pranaevents #ahri #digitalhealth #medicalinnovation #ethiopiahealthconference
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ለማዘመንና የሕክምና ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳለጥ ያለመው 10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ፣ እንዲሁም 2ኛው የአገር ውስጥ የሕክምና ግብዓቶች ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
በዚህ መድረክ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት እና በፕራና ኤቨንትስ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ከስምንት አገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ለታዳሚዎች ያቀርባሉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከእንግሊዝ፣ ከቻይና፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከታይላንድ፣ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ከአሜሪካ የመጡ ታዋቂ ድርጅቶች የሚሳተፉ በመሆኑ፣ የውጭውን ቴክኖሎጂ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለማስተሳሰርና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከንግድ ትርኢቱ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ከ40 በላይ ቀጣይነት ያለው የሙያ ማሳደጊያ (CPD) ስልጠናዎች የሚሰጡ ሲሆን፣ ከ20 በላይ የሚሆኑ የዘርፉ የሙያ ማህበራትም በዝግጅቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የጤና አመራር ጉባኤ፣ የዲጂታል ሄልዝ ፎረም እና የሳይንሳዊ መድረኮች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በጤናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን በምርምርና በቴክኖሎጂ ለመፍታት የሚያስችሉ ምክክሮች የሚደረጉባቸው መድረኮች ይሆናሉ።
ይህ ዝግጅት በተለይም የሀገር ውስጥ የሕክምና መሣሪያዎችና የመድኃኒት አምራቾች ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ድርሻ እንዲያሳድጉና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም መንግስታዊ ተቋማት ሙሉ እውቅናና ድጋፍ የሚደረግለት ይህ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiohealth2026 #healthcareethiopia #medicalexhibition #pranaevents #ahri #digitalhealth #medicalinnovation #ethiopiahealthconference
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የኔ ሄልዝ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሴቶችን የጤና አገልግሎት እና የመድኃኒት አቅርቦት ስርአትን ለማቃለል በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ የጀመረው "የኔ ሄልዝ" ፣ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርጉ አዳዲስ አሰራሮችን ይፋ አደረገ።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ቅድስት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ "የኔ ሄልዝ" ባለፉት አራት ዓመታት በሴቶች ጤና እና በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ድርጅቱ በተለይ በሞባይል መተግበሪያው (App) አማካኝነት ለሴቶች ሦስት ዋና ዋና አገልግሎቶችን ይሰጣል፡
* የጤና መረጃ፡ ስለ እርግዝና፣ ስለ የወር አበባ ዑደትና ስለ ተለያዩ መድኃኒቶች ግንዛቤ የሚሰጡ መረጃዎች።
* የቴሌ ሄልዝ (Tele-Health) አገልግሎት፡ ታካሚዎች በቪዲዮ፣ በቻት ወይም በስልክ ከሐኪሞችና ከፋርማሲስቶች ጋር በቀጥታ በመገናኘት ምክክር የሚያደርጉበትና መድኃኒት የሚታዘዝበት ሥርዓት።
* የኦንላይን ፋርማሲ፡ የታዘዘላቸውን መድኃኒት ወይም የውጭ አገር የሕክምና ትዕዛዝ (Prescription) በመተግበሪያው ላይ በመጫን መድኃኒቱን ባሉበት ቦታ ድረስ እንዲመጣላቸው የሚያደርግ አገልግሎት።
ድርጅቱ አሁን ላይ አገልግሎቱን በማስፋት ከባንኮች ጋር በመተባበር ለፋርማሲዎችና ለጤና ተቋማት የብድር አቅርቦት ማመቻቸት መጀመሩን ገልጿል። ይህ አሰራር ፋርማሲዎች የገንዘብ እጥረት ሳይገጥማቸው መድኃኒቶችን በቋሚነት እንዲያቀርቡና ህብረተሰቡ የመድኃኒት እጥረት እንዳይገጥመው ለማድረግ ያለመ ነው።
በተጨማሪም "የኔ ሄልዝ" ከ60 በላይ ከሚሆኑ አምራቾች፣ አስመጪዎችና የጤና ተቋማት ጋር የጅምላ ግብይት ትስስር (Online Wholesale Platform) መፍጠሩ ተጠቁሟል።
በአገሪቱ ያለውን ዝቅተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንዛቤ (Digital Literacy) ለመቅረፍ፣ ድርጅቱ ለጤና ባለሙያዎች፣ ለተማሪዎችና ለተጠቃሚዎች መተግበሪያውን እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን መተግበሪያውም ተጠቃሚዎች እንዳይሰላቹ በቀላልና ምቹ በሆነ መንገድ (User Friendly) እንዲዘጋጅ ተደርጓል።
"የኔ ሄልዝ" ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የውይይት መድረክ ላይ ከመንግሥት አካላት (ከኢትዮጵያ መድኃኒትና ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን - EFDA) እና ከኢትዮጵያ መድኃኒት ማህበር ጋር በመሆን የኦንላይን መድኃኒት ግብይትና አቅርቦት ሕጋዊ ማዕቀፎች እንዲጠናከሩ ውይይቶችን አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #የኔ_ሄልዝ #የሴቶች_ጤና #ቴክኖሎጂ #ጤና #ኢትዮጵያ #yenehealth #telehealth #digitalhealth
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሴቶችን የጤና አገልግሎት እና የመድኃኒት አቅርቦት ስርአትን ለማቃለል በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ የጀመረው "የኔ ሄልዝ" ፣ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርጉ አዳዲስ አሰራሮችን ይፋ አደረገ።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ቅድስት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ "የኔ ሄልዝ" ባለፉት አራት ዓመታት በሴቶች ጤና እና በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ድርጅቱ በተለይ በሞባይል መተግበሪያው (App) አማካኝነት ለሴቶች ሦስት ዋና ዋና አገልግሎቶችን ይሰጣል፡
* የጤና መረጃ፡ ስለ እርግዝና፣ ስለ የወር አበባ ዑደትና ስለ ተለያዩ መድኃኒቶች ግንዛቤ የሚሰጡ መረጃዎች።
* የቴሌ ሄልዝ (Tele-Health) አገልግሎት፡ ታካሚዎች በቪዲዮ፣ በቻት ወይም በስልክ ከሐኪሞችና ከፋርማሲስቶች ጋር በቀጥታ በመገናኘት ምክክር የሚያደርጉበትና መድኃኒት የሚታዘዝበት ሥርዓት።
* የኦንላይን ፋርማሲ፡ የታዘዘላቸውን መድኃኒት ወይም የውጭ አገር የሕክምና ትዕዛዝ (Prescription) በመተግበሪያው ላይ በመጫን መድኃኒቱን ባሉበት ቦታ ድረስ እንዲመጣላቸው የሚያደርግ አገልግሎት።
ድርጅቱ አሁን ላይ አገልግሎቱን በማስፋት ከባንኮች ጋር በመተባበር ለፋርማሲዎችና ለጤና ተቋማት የብድር አቅርቦት ማመቻቸት መጀመሩን ገልጿል። ይህ አሰራር ፋርማሲዎች የገንዘብ እጥረት ሳይገጥማቸው መድኃኒቶችን በቋሚነት እንዲያቀርቡና ህብረተሰቡ የመድኃኒት እጥረት እንዳይገጥመው ለማድረግ ያለመ ነው።
በተጨማሪም "የኔ ሄልዝ" ከ60 በላይ ከሚሆኑ አምራቾች፣ አስመጪዎችና የጤና ተቋማት ጋር የጅምላ ግብይት ትስስር (Online Wholesale Platform) መፍጠሩ ተጠቁሟል።
በአገሪቱ ያለውን ዝቅተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንዛቤ (Digital Literacy) ለመቅረፍ፣ ድርጅቱ ለጤና ባለሙያዎች፣ ለተማሪዎችና ለተጠቃሚዎች መተግበሪያውን እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን መተግበሪያውም ተጠቃሚዎች እንዳይሰላቹ በቀላልና ምቹ በሆነ መንገድ (User Friendly) እንዲዘጋጅ ተደርጓል።
"የኔ ሄልዝ" ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የውይይት መድረክ ላይ ከመንግሥት አካላት (ከኢትዮጵያ መድኃኒትና ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን - EFDA) እና ከኢትዮጵያ መድኃኒት ማህበር ጋር በመሆን የኦንላይን መድኃኒት ግብይትና አቅርቦት ሕጋዊ ማዕቀፎች እንዲጠናከሩ ውይይቶችን አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #የኔ_ሄልዝ #የሴቶች_ጤና #ቴክኖሎጂ #ጤና #ኢትዮጵያ #yenehealth #telehealth #digitalhealth
4 months ago
''NAN" የተሰኘው የህፃናት ወተት የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በገበያ ላይ ቁጥጥር እያደረገ መሆኑን ገለጸ
#ethiopia | "Nestle" የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት በህፃናት ምግብ ምርቶቹ ላይ ብክለት መገኘቱን ተከትሎ ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ጥንቃቄ የሚሻው የምርት ዝርዝር
ብክለት ተገኝቶባቸዋል ተብለው ለሽያጭ እንዳይቀርቡ የተከለከሉት ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፦
* የምርት መለያ፦ NAN special pro HA 0-12
* የባች ቁጥር፦ 51660742F3
* የተመረተበት ቀን፦ 15 June 2025
* የሚያበቃበት ቀን፦ 15 December 2026
* ክብደት፦ 800 ግራም
የባለስልጣኑ የቁጥጥር ስራና የሰጠው ምላሽ
የባለስልጣኑ የምግብ ኢንስፔክሽንና የህግ ማስፈጸም መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙላቱ ተስፋዬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት፣ ምርቱ በይፋዊ የገበያ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ባይገባም በተለያዩ መንገዶች ሊገባ ስለሚችል በሱፐር ማርኬቶችና በማከፋፈያዎች ላይ ፍተሻ ተደርጓል። እስካሁን ባለው መረጃ ምርቱ በገበያ ላይ ባይገኝም ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የድርጅቱ ኃላፊነት፦ የድርጅቱ ተወካዮች ምርቱን በራሳቸው ወጪ የመሰብሰብና የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው።
* የነጋዴው ድርሻ፦ ማንኛውም ነጋዴ ይህ ምርት እጁ ላይ ካለ ከመሸጥና ከማከፋፈል እንዲቆጠብ ጥሪ ቀርቧል።
* የህብረተሰቡ ጥንቃቄ፦ ህብረተሰቡ የተጠቀሰውን የባች ቁጥርና የምርት መለያ በማየት ጥንቃቄ እንዲያደርግና ካገኘም ለባለስልጣኑ እንዲጠቁም ተጠይቋል።
ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ደረጃውን የጠበቀ ምርት ማቅረብ የአምራችና የአስመጭ ግዴታ መሆኑን አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #nestle #babyfoodsafety #ethiopia #efda #healthalert #nan #የምግብደህንነት #ኢትዮጵያ
#ethiopia | "Nestle" የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት በህፃናት ምግብ ምርቶቹ ላይ ብክለት መገኘቱን ተከትሎ ባስተላለፈው ማስጠንቀቂያ መሠረት፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ጥብቅ ክትትል እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ጥንቃቄ የሚሻው የምርት ዝርዝር
ብክለት ተገኝቶባቸዋል ተብለው ለሽያጭ እንዳይቀርቡ የተከለከሉት ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፦
* የምርት መለያ፦ NAN special pro HA 0-12
* የባች ቁጥር፦ 51660742F3
* የተመረተበት ቀን፦ 15 June 2025
* የሚያበቃበት ቀን፦ 15 December 2026
* ክብደት፦ 800 ግራም
የባለስልጣኑ የቁጥጥር ስራና የሰጠው ምላሽ
የባለስልጣኑ የምግብ ኢንስፔክሽንና የህግ ማስፈጸም መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሙላቱ ተስፋዬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት፣ ምርቱ በይፋዊ የገበያ ፈቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ባይገባም በተለያዩ መንገዶች ሊገባ ስለሚችል በሱፐር ማርኬቶችና በማከፋፈያዎች ላይ ፍተሻ ተደርጓል። እስካሁን ባለው መረጃ ምርቱ በገበያ ላይ ባይገኝም ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የድርጅቱ ኃላፊነት፦ የድርጅቱ ተወካዮች ምርቱን በራሳቸው ወጪ የመሰብሰብና የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው።
* የነጋዴው ድርሻ፦ ማንኛውም ነጋዴ ይህ ምርት እጁ ላይ ካለ ከመሸጥና ከማከፋፈል እንዲቆጠብ ጥሪ ቀርቧል።
* የህብረተሰቡ ጥንቃቄ፦ ህብረተሰቡ የተጠቀሰውን የባች ቁጥርና የምርት መለያ በማየት ጥንቃቄ እንዲያደርግና ካገኘም ለባለስልጣኑ እንዲጠቁም ተጠይቋል።
ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ደረጃውን የጠበቀ ምርት ማቅረብ የአምራችና የአስመጭ ግዴታ መሆኑን አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #nestle #babyfoodsafety #ethiopia #efda #healthalert #nan #የምግብደህንነት #ኢትዮጵያ
5 months ago
ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ለማይበገር የጤና ሥርዓት
#ethiopia | የሕብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅና የጤና ሥርዓቱን ጥራት ለማረጋገጥ ያለመ የመጀመሪያው አገራዊ የጤና ቁጥጥር ፎረም ንቅናቄ መድረክ "ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ለማይበገር የጤና ሥርዓት" በሚል መሪ ቃል ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
📋 የሥርዓት ማዘመንና የፖሊሲ ድጋፍ
በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፣ የሕብረተሰቡን ጤና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የወጡ አገራዊ ደረጃዎችንና የአሠራር ሥርዓቶችን ማዘመን ወሳኝ ነው። መንግሥት ለዚህ ተግባር እንዲረዳ የፖሊሲና የአሠራር ማዕቀፎችን መዘርጋቱን የገለጹት ሚኒስትሯ፣ ይህም ደረጃዎችን ከፌደራል እስከ ታችኛው መዋቅር ወጥ በሆነ መንገድ ለማስፈጸም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
💻 ዲጂታላይዜሽን እና የጥራት መሠረተ ልማት
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሔራን ገርባ በበኩላቸው፣ የተቋሙን ስኬቶችና ተግዳሮቶች ለጉባኤው አቅርበዋል። ባለሥልጣኑ የቁጥጥር ሥርዓቱን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የጀመረውን ዲጂታላይዝ የማድረግ ሥራ እንዲሁም የጥራት መሠረተ ልማት ዝርጋታን በተመለከተ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
🔍 ሕገ-ወጥ ምርቶችን የመቆጣጠር ስኬት
በፎረሙ ላይ በልዩ ሁኔታ የቀረበው የኤግዚቢሽን መድረክ፣ ባለሥልጣኑ ቁጥጥር ያደረገባቸውንና ከሥርጭት ያገዳቸውን ሕገ-ወጥ የጤና ግብዓቶች ለተሳታፊዎች አሳይቷል። ይህም ተቋሙ የሕብረተሰቡን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ምርቶችን ለመቆጣጠር እያከናወነ ያለውን ጠንካራ ሥራ በተግባር ያሳየ ሆኗል።
በዚህ የንቅናቄ መድረክ ላይ፦
* ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች
* የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወካዮች
* የክልል ተቆጣጣሪ ባለሥልጣናት እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ፎረሙ በዘርፉ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ትልቅ መድረክ ሆኖ አገልግሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #ጤናሚኒስቴር #የጤናቁጥጥር #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጤና #ethiopia #healthregulation #efda #moh
#ethiopia | የሕብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅና የጤና ሥርዓቱን ጥራት ለማረጋገጥ ያለመ የመጀመሪያው አገራዊ የጤና ቁጥጥር ፎረም ንቅናቄ መድረክ "ጠንካራ የጤና ቁጥጥር ለማይበገር የጤና ሥርዓት" በሚል መሪ ቃል ዛሬ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
📋 የሥርዓት ማዘመንና የፖሊሲ ድጋፍ
በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ እንደገለጹት፣ የሕብረተሰቡን ጤና በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የወጡ አገራዊ ደረጃዎችንና የአሠራር ሥርዓቶችን ማዘመን ወሳኝ ነው። መንግሥት ለዚህ ተግባር እንዲረዳ የፖሊሲና የአሠራር ማዕቀፎችን መዘርጋቱን የገለጹት ሚኒስትሯ፣ ይህም ደረጃዎችን ከፌደራል እስከ ታችኛው መዋቅር ወጥ በሆነ መንገድ ለማስፈጸም ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
💻 ዲጂታላይዜሽን እና የጥራት መሠረተ ልማት
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሔራን ገርባ በበኩላቸው፣ የተቋሙን ስኬቶችና ተግዳሮቶች ለጉባኤው አቅርበዋል። ባለሥልጣኑ የቁጥጥር ሥርዓቱን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የጀመረውን ዲጂታላይዝ የማድረግ ሥራ እንዲሁም የጥራት መሠረተ ልማት ዝርጋታን በተመለከተ ሰፊ ገለጻ አድርገዋል።
🔍 ሕገ-ወጥ ምርቶችን የመቆጣጠር ስኬት
በፎረሙ ላይ በልዩ ሁኔታ የቀረበው የኤግዚቢሽን መድረክ፣ ባለሥልጣኑ ቁጥጥር ያደረገባቸውንና ከሥርጭት ያገዳቸውን ሕገ-ወጥ የጤና ግብዓቶች ለተሳታፊዎች አሳይቷል። ይህም ተቋሙ የሕብረተሰቡን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ምርቶችን ለመቆጣጠር እያከናወነ ያለውን ጠንካራ ሥራ በተግባር ያሳየ ሆኗል።
በዚህ የንቅናቄ መድረክ ላይ፦
* ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች
* የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወካዮች
* የክልል ተቆጣጣሪ ባለሥልጣናት እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ፎረሙ በዘርፉ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ትልቅ መድረክ ሆኖ አገልግሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #ጤናሚኒስቴር #የጤናቁጥጥር #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጤና #ethiopia #healthregulation #efda #moh
Comments