2 months ago
ማያ በጎ አድራጎት ድርጅት በህፃናት የአፈጣጠር ችግር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
3 months ago
በስፓይና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ግንዛቤ የፈጠረ የተማሪዎች ውድድር ተካሄደ
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
4 months ago
የነርቭ ዘንግ ክፍተትና ፎሊክ አሲድ ላይ ለጋዜጠኞች ስልጠና ተሰጠ
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia