3 months ago
ጠ/ሚ'ሯ የተሾሙሏት ኢትዮጵያ AI በጤና ዘርፍ ላይ ምን ያህል ድርሻ አለው?
#ethiopia | ኢትዮጵያ በሕክምናው ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ሲፈታተኗት የነበሩትን የባለሙያ እጥረት፣ የምርመራ መዘግየት እና የመረጃ አያያዝ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) እንደ ዋነኛ መፍትሔ መጠቀም ጀምራለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንደገለጹት፤ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ የግድ አስፈላጊ መሠረታዊ ግብዓት ነው።
ቀደም ባሉት ጊዜያት የራጅ ወይም የሲቲ ስካን ውጤቶችን ለመተርጎም ቀናትን አልፎ ተርፎም ሳምንታትን ይፈጅ የነበረ ሲሆን፣ ይህ መዘግየት ሀገራችን ወደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አማራጭ እንድትመለከት አስገድዷታል።
በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በራሷ ባለሙያዎች የበለጸጉ እና ከነባራዊ ሁኔታዎቿ ጋር የተቃኙ የAI መተግበሪያዎች ባለቤት መሆን ችላለች።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያበለጸገው "መላ" የተሰኘው መተግበሪያ በዘርፉ የታየ ትልቅ እመርታ ነው።
መተግበሪያው ፈጣን የምርመራ ውጤቶችን በመስጠት የሳንባ ነቀርሳን (TB) እና የሳንባ ምችን (Pneumonia) ከራጅ ምስሎች ላይ በሰከንዶች ውስጥ በመለየት ለሐኪሞች የውሳኔ ድጋፍ ይሰጣል።
ከዚህ በተጨማሪ የጡት ካንሰር ምርመራ የራጅ (Mammography) ምስሎችን በመተንተን የሕመሙን ምልክቶች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት የመለየት ተግባር ያከናውናል።
ካንሰርን ገና በጅምሩ ለመለየት ያለው አቅም የብዙዎችን ሕይወት ለማዳን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በሌላ በኩል የደረት ራጅ ምስሎችን በማንበብ የሳንባ ነቀርሳና ቲቢን የሚለየው ቴክኖሎጂ (CXR-based Diagnosis) የራጅ ባለሙያዎች በሌሉባቸው አካባቢዎች ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት እያስቻለ ነው።
ይህ አገልግሎት በየካ ኮቲቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና በተመረጡ የክልል ሆስፒታሎች ተግባራዊ ተደርጓል።
የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ (Cervical Cancer Screening) በምስል ትንተና አማካኝነት ምልክቶችን ቀድሞ መለየት የሚያስችል ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልና በአንዳንድ የጤና ጣቢያዎች በሙከራ ሂደት ላይ ይገኛል።
በተመሳሳይ የልብ ምትን (ECG) በመተንተን የሕመም ዓይነቶችን የሚለየው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መተግበሪያ የልብ ስፔሻሊስቶች በሌሉባቸው ሆስፒታሎች ለጠቅላላ ሐኪሞች እንደ ረዳት መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው።
እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በዋናነት በመንግሥት ከፍተኛ የሪፈራል ሆስፒታሎች የተጀመሩ ቢሆንም፣ ቀስ በቀስ ወደ ሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የማስፋፋት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጤና ሚኒስቴር በቅንጅት እያከናወኑት ያለው ይህ ተግባር የምርመራ ጥራትን በማሻሻል የሀገራችንን የጤና አገልግሎት ወደ አዲስ ከፍታ እያሸጋገረው ይገኛል።
ማስታወሻ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu via#ebc #ethiopia #aiinhealth #healthtech #digitalhealth #melaai #ethiopianaiinstitute
#ethiopia | ኢትዮጵያ በሕክምናው ዘርፍ ለበርካታ ዓመታት ሲፈታተኗት የነበሩትን የባለሙያ እጥረት፣ የምርመራ መዘግየት እና የመረጃ አያያዝ ክፍተቶችን ለመቅረፍ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን (AI) እንደ ዋነኛ መፍትሔ መጠቀም ጀምራለች።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት እንደገለጹት፤ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለኢትዮጵያ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ የግድ አስፈላጊ መሠረታዊ ግብዓት ነው።
ቀደም ባሉት ጊዜያት የራጅ ወይም የሲቲ ስካን ውጤቶችን ለመተርጎም ቀናትን አልፎ ተርፎም ሳምንታትን ይፈጅ የነበረ ሲሆን፣ ይህ መዘግየት ሀገራችን ወደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ አማራጭ እንድትመለከት አስገድዷታል።
በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በራሷ ባለሙያዎች የበለጸጉ እና ከነባራዊ ሁኔታዎቿ ጋር የተቃኙ የAI መተግበሪያዎች ባለቤት መሆን ችላለች።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ያበለጸገው "መላ" የተሰኘው መተግበሪያ በዘርፉ የታየ ትልቅ እመርታ ነው።
መተግበሪያው ፈጣን የምርመራ ውጤቶችን በመስጠት የሳንባ ነቀርሳን (TB) እና የሳንባ ምችን (Pneumonia) ከራጅ ምስሎች ላይ በሰከንዶች ውስጥ በመለየት ለሐኪሞች የውሳኔ ድጋፍ ይሰጣል።
ከዚህ በተጨማሪ የጡት ካንሰር ምርመራ የራጅ (Mammography) ምስሎችን በመተንተን የሕመሙን ምልክቶች በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት የመለየት ተግባር ያከናውናል።
ካንሰርን ገና በጅምሩ ለመለየት ያለው አቅም የብዙዎችን ሕይወት ለማዳን ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በሌላ በኩል የደረት ራጅ ምስሎችን በማንበብ የሳንባ ነቀርሳና ቲቢን የሚለየው ቴክኖሎጂ (CXR-based Diagnosis) የራጅ ባለሙያዎች በሌሉባቸው አካባቢዎች ፈጣን ውሳኔ ለመስጠት እያስቻለ ነው።
ይህ አገልግሎት በየካ ኮቲቤ አጠቃላይ ሆስፒታል እና በተመረጡ የክልል ሆስፒታሎች ተግባራዊ ተደርጓል።
የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ (Cervical Cancer Screening) በምስል ትንተና አማካኝነት ምልክቶችን ቀድሞ መለየት የሚያስችል ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልና በአንዳንድ የጤና ጣቢያዎች በሙከራ ሂደት ላይ ይገኛል።
በተመሳሳይ የልብ ምትን (ECG) በመተንተን የሕመም ዓይነቶችን የሚለየው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መተግበሪያ የልብ ስፔሻሊስቶች በሌሉባቸው ሆስፒታሎች ለጠቅላላ ሐኪሞች እንደ ረዳት መሣሪያ ሆኖ እያገለገለ ነው።
እነዚህ የቴክኖሎጂ ውጤቶች በዋናነት በመንግሥት ከፍተኛ የሪፈራል ሆስፒታሎች የተጀመሩ ቢሆንም፣ ቀስ በቀስ ወደ ሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የማስፋፋት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የጤና ሚኒስቴር በቅንጅት እያከናወኑት ያለው ይህ ተግባር የምርመራ ጥራትን በማሻሻል የሀገራችንን የጤና አገልግሎት ወደ አዲስ ከፍታ እያሸጋገረው ይገኛል።
ማስታወሻ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu via#ebc #ethiopia #aiinhealth #healthtech #digitalhealth #melaai #ethiopianaiinstitute
5 months ago
10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ለማዘመንና የሕክምና ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳለጥ ያለመው 10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ፣ እንዲሁም 2ኛው የአገር ውስጥ የሕክምና ግብዓቶች ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
በዚህ መድረክ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት እና በፕራና ኤቨንትስ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ከስምንት አገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ለታዳሚዎች ያቀርባሉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከእንግሊዝ፣ ከቻይና፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከታይላንድ፣ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ከአሜሪካ የመጡ ታዋቂ ድርጅቶች የሚሳተፉ በመሆኑ፣ የውጭውን ቴክኖሎጂ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለማስተሳሰርና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከንግድ ትርኢቱ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ከ40 በላይ ቀጣይነት ያለው የሙያ ማሳደጊያ (CPD) ስልጠናዎች የሚሰጡ ሲሆን፣ ከ20 በላይ የሚሆኑ የዘርፉ የሙያ ማህበራትም በዝግጅቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የጤና አመራር ጉባኤ፣ የዲጂታል ሄልዝ ፎረም እና የሳይንሳዊ መድረኮች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በጤናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን በምርምርና በቴክኖሎጂ ለመፍታት የሚያስችሉ ምክክሮች የሚደረጉባቸው መድረኮች ይሆናሉ።
ይህ ዝግጅት በተለይም የሀገር ውስጥ የሕክምና መሣሪያዎችና የመድኃኒት አምራቾች ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ድርሻ እንዲያሳድጉና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም መንግስታዊ ተቋማት ሙሉ እውቅናና ድጋፍ የሚደረግለት ይህ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiohealth2026 #healthcareethiopia #medicalexhibition #pranaevents #ahri #digitalhealth #medicalinnovation #ethiopiahealthconference
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤናውን ዘርፍ ለማዘመንና የሕክምና ግብዓቶችን አቅርቦት ለማሳለጥ ያለመው 10ኛው የኢትዮ ሄልዝ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ጉባኤ፣ እንዲሁም 2ኛው የአገር ውስጥ የሕክምና ግብዓቶች ምርትና ኢኖቬሽን ኤግዚቢሽን ከመጋቢት 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ገልጸዋል።
በዚህ መድረክ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት እና በፕራና ኤቨንትስ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ከስምንት አገራት የተውጣጡ ከ90 በላይ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ኩባንያዎች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ለታዳሚዎች ያቀርባሉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከእንግሊዝ፣ ከቻይና፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከታይላንድ፣ ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስና ከአሜሪካ የመጡ ታዋቂ ድርጅቶች የሚሳተፉ በመሆኑ፣ የውጭውን ቴክኖሎጂ ከአገር ውስጥ አምራቾች ጋር ለማስተሳሰርና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከንግድ ትርኢቱ ጎን ለጎን የጤና ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚረዱ ከ40 በላይ ቀጣይነት ያለው የሙያ ማሳደጊያ (CPD) ስልጠናዎች የሚሰጡ ሲሆን፣ ከ20 በላይ የሚሆኑ የዘርፉ የሙያ ማህበራትም በዝግጅቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም የጤና አመራር ጉባኤ፣ የዲጂታል ሄልዝ ፎረም እና የሳይንሳዊ መድረኮች የሚካሄዱ ሲሆን፣ እነዚህም በጤናው ዘርፍ ያሉ ችግሮችን በምርምርና በቴክኖሎጂ ለመፍታት የሚያስችሉ ምክክሮች የሚደረጉባቸው መድረኮች ይሆናሉ።
ይህ ዝግጅት በተለይም የሀገር ውስጥ የሕክምና መሣሪያዎችና የመድኃኒት አምራቾች ምርቶቻቸውን ለገበያ በማቅረብ በጤናው ዘርፍ ያላቸውን ድርሻ እንዲያሳድጉና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣ በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) እና በሌሎችም መንግስታዊ ተቋማት ሙሉ እውቅናና ድጋፍ የሚደረግለት ይህ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያን የጤና አገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ ሚና ይጫወታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiohealth2026 #healthcareethiopia #medicalexhibition #pranaevents #ahri #digitalhealth #medicalinnovation #ethiopiahealthconference
5 months ago
የኔ ሄልዝ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሴቶችን የጤና አገልግሎት እና የመድኃኒት አቅርቦት ስርአትን ለማቃለል በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ የጀመረው "የኔ ሄልዝ" ፣ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርጉ አዳዲስ አሰራሮችን ይፋ አደረገ።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ቅድስት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ "የኔ ሄልዝ" ባለፉት አራት ዓመታት በሴቶች ጤና እና በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ድርጅቱ በተለይ በሞባይል መተግበሪያው (App) አማካኝነት ለሴቶች ሦስት ዋና ዋና አገልግሎቶችን ይሰጣል፡
* የጤና መረጃ፡ ስለ እርግዝና፣ ስለ የወር አበባ ዑደትና ስለ ተለያዩ መድኃኒቶች ግንዛቤ የሚሰጡ መረጃዎች።
* የቴሌ ሄልዝ (Tele-Health) አገልግሎት፡ ታካሚዎች በቪዲዮ፣ በቻት ወይም በስልክ ከሐኪሞችና ከፋርማሲስቶች ጋር በቀጥታ በመገናኘት ምክክር የሚያደርጉበትና መድኃኒት የሚታዘዝበት ሥርዓት።
* የኦንላይን ፋርማሲ፡ የታዘዘላቸውን መድኃኒት ወይም የውጭ አገር የሕክምና ትዕዛዝ (Prescription) በመተግበሪያው ላይ በመጫን መድኃኒቱን ባሉበት ቦታ ድረስ እንዲመጣላቸው የሚያደርግ አገልግሎት።
ድርጅቱ አሁን ላይ አገልግሎቱን በማስፋት ከባንኮች ጋር በመተባበር ለፋርማሲዎችና ለጤና ተቋማት የብድር አቅርቦት ማመቻቸት መጀመሩን ገልጿል። ይህ አሰራር ፋርማሲዎች የገንዘብ እጥረት ሳይገጥማቸው መድኃኒቶችን በቋሚነት እንዲያቀርቡና ህብረተሰቡ የመድኃኒት እጥረት እንዳይገጥመው ለማድረግ ያለመ ነው።
በተጨማሪም "የኔ ሄልዝ" ከ60 በላይ ከሚሆኑ አምራቾች፣ አስመጪዎችና የጤና ተቋማት ጋር የጅምላ ግብይት ትስስር (Online Wholesale Platform) መፍጠሩ ተጠቁሟል።
በአገሪቱ ያለውን ዝቅተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንዛቤ (Digital Literacy) ለመቅረፍ፣ ድርጅቱ ለጤና ባለሙያዎች፣ ለተማሪዎችና ለተጠቃሚዎች መተግበሪያውን እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን መተግበሪያውም ተጠቃሚዎች እንዳይሰላቹ በቀላልና ምቹ በሆነ መንገድ (User Friendly) እንዲዘጋጅ ተደርጓል።
"የኔ ሄልዝ" ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የውይይት መድረክ ላይ ከመንግሥት አካላት (ከኢትዮጵያ መድኃኒትና ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን - EFDA) እና ከኢትዮጵያ መድኃኒት ማህበር ጋር በመሆን የኦንላይን መድኃኒት ግብይትና አቅርቦት ሕጋዊ ማዕቀፎች እንዲጠናከሩ ውይይቶችን አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #የኔ_ሄልዝ #የሴቶች_ጤና #ቴክኖሎጂ #ጤና #ኢትዮጵያ #yenehealth #telehealth #digitalhealth
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሴቶችን የጤና አገልግሎት እና የመድኃኒት አቅርቦት ስርአትን ለማቃለል በቴክኖሎጂ የታገዘ ስራ የጀመረው "የኔ ሄልዝ" ፣ አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርጉ አዳዲስ አሰራሮችን ይፋ አደረገ።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ቅድስት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ "የኔ ሄልዝ" ባለፉት አራት ዓመታት በሴቶች ጤና እና በፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል። ድርጅቱ በተለይ በሞባይል መተግበሪያው (App) አማካኝነት ለሴቶች ሦስት ዋና ዋና አገልግሎቶችን ይሰጣል፡
* የጤና መረጃ፡ ስለ እርግዝና፣ ስለ የወር አበባ ዑደትና ስለ ተለያዩ መድኃኒቶች ግንዛቤ የሚሰጡ መረጃዎች።
* የቴሌ ሄልዝ (Tele-Health) አገልግሎት፡ ታካሚዎች በቪዲዮ፣ በቻት ወይም በስልክ ከሐኪሞችና ከፋርማሲስቶች ጋር በቀጥታ በመገናኘት ምክክር የሚያደርጉበትና መድኃኒት የሚታዘዝበት ሥርዓት።
* የኦንላይን ፋርማሲ፡ የታዘዘላቸውን መድኃኒት ወይም የውጭ አገር የሕክምና ትዕዛዝ (Prescription) በመተግበሪያው ላይ በመጫን መድኃኒቱን ባሉበት ቦታ ድረስ እንዲመጣላቸው የሚያደርግ አገልግሎት።
ድርጅቱ አሁን ላይ አገልግሎቱን በማስፋት ከባንኮች ጋር በመተባበር ለፋርማሲዎችና ለጤና ተቋማት የብድር አቅርቦት ማመቻቸት መጀመሩን ገልጿል። ይህ አሰራር ፋርማሲዎች የገንዘብ እጥረት ሳይገጥማቸው መድኃኒቶችን በቋሚነት እንዲያቀርቡና ህብረተሰቡ የመድኃኒት እጥረት እንዳይገጥመው ለማድረግ ያለመ ነው።
በተጨማሪም "የኔ ሄልዝ" ከ60 በላይ ከሚሆኑ አምራቾች፣ አስመጪዎችና የጤና ተቋማት ጋር የጅምላ ግብይት ትስስር (Online Wholesale Platform) መፍጠሩ ተጠቁሟል።
በአገሪቱ ያለውን ዝቅተኛ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ግንዛቤ (Digital Literacy) ለመቅረፍ፣ ድርጅቱ ለጤና ባለሙያዎች፣ ለተማሪዎችና ለተጠቃሚዎች መተግበሪያውን እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ስልጠናዎችን እየሰጠ ሲሆን መተግበሪያውም ተጠቃሚዎች እንዳይሰላቹ በቀላልና ምቹ በሆነ መንገድ (User Friendly) እንዲዘጋጅ ተደርጓል።
"የኔ ሄልዝ" ዛሬ ባካሄደው ዓመታዊ የውይይት መድረክ ላይ ከመንግሥት አካላት (ከኢትዮጵያ መድኃኒትና ምግብ ቁጥጥር ባለሥልጣን - EFDA) እና ከኢትዮጵያ መድኃኒት ማህበር ጋር በመሆን የኦንላይን መድኃኒት ግብይትና አቅርቦት ሕጋዊ ማዕቀፎች እንዲጠናከሩ ውይይቶችን አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #የኔ_ሄልዝ #የሴቶች_ጤና #ቴክኖሎጂ #ጤና #ኢትዮጵያ #yenehealth #telehealth #digitalhealth
5 months ago
የኢትዮጵያ የጤና ደህንነት ወደ ዲጂታል ምዕራፍ ተሸጋገረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የሀገሪቱን የጤና ስጋቶች በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችለውን ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ዛሬ በይፋ አስመርቋል። ይህ አዲስ "የቁጥጥር ማዕከል" ኢትዮጵያ ለወረርሽኞችና ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ያላትን ምላሽ ፈጣንና መረጃን መሰረት ያደረገ ያደርገዋል።
🚀 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ከወረዳ እስከ ማዕከል፦ አዲሱ አሰራር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚታዩ የጤና ስጋቶችን በቅርበት ለመለየትና መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥ ያስችላል።
800 ሚሊዮን ብር ድጋፍ፦ ዲጂታላይዜሽኑን እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ፣ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የICT መሣሪያዎች ለክልል ጤና ቢሮዎች ተከፋፍለዋል።
የልህቀት ማዕከል፦ ይህ እርምጃ ተቋሙን በምስራቅ አፍሪካ የጤና ዘርፍ ግንባር ቀደም የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ያሳካል።
እንደ ኮቪድ-19 ያሉ ወረርሽኞች በገጠሙን ጊዜ ትልቁ ፈተና የነበረው የተበታተነና የዘገየ የመረጃ ልውውጥ ነበር። አሁን ግን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወረርሽኞችን ገና በጅምራቸው መለየትና የቅድመ ማስጠንቀቂያ እርምጃዎችን መውሰድ ይቻላል።
#publichealth #digitalhealth #ethiopia #healthtech #ephi #diseasesurveillance #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የሀገሪቱን የጤና ስጋቶች በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችለውን ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ዛሬ በይፋ አስመርቋል። ይህ አዲስ "የቁጥጥር ማዕከል" ኢትዮጵያ ለወረርሽኞችና ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ያላትን ምላሽ ፈጣንና መረጃን መሰረት ያደረገ ያደርገዋል።
🚀 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ከወረዳ እስከ ማዕከል፦ አዲሱ አሰራር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚታዩ የጤና ስጋቶችን በቅርበት ለመለየትና መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥ ያስችላል።
800 ሚሊዮን ብር ድጋፍ፦ ዲጂታላይዜሽኑን እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ፣ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የICT መሣሪያዎች ለክልል ጤና ቢሮዎች ተከፋፍለዋል።
የልህቀት ማዕከል፦ ይህ እርምጃ ተቋሙን በምስራቅ አፍሪካ የጤና ዘርፍ ግንባር ቀደም የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ያሳካል።
እንደ ኮቪድ-19 ያሉ ወረርሽኞች በገጠሙን ጊዜ ትልቁ ፈተና የነበረው የተበታተነና የዘገየ የመረጃ ልውውጥ ነበር። አሁን ግን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወረርሽኞችን ገና በጅምራቸው መለየትና የቅድመ ማስጠንቀቂያ እርምጃዎችን መውሰድ ይቻላል።
#publichealth #digitalhealth #ethiopia #healthtech #ephi #diseasesurveillance #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
💎 ቪዥን የጤና አገልግሎት የ"ዳይመንድ ደረጃ" የክብር ዋንጫ ተሸላሚ ሆነ! 🇪🇹🏥
#ethiopia | "ለዚህ ሁሉ ዓመት ስኬት ያበቃን ሙያችንንና ሕሙማንን ማስቀደማችን ነው" — ቪዥን የጤና አገልግሎት
ባለፉት 15 ዓመታት በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በምሳሌነት የሚጠቀስ ሥራ ሲያከናውን የቆየው ቪዥን የጤና አገልግሎት፣ በግራንድ አፍሪካ ሽልማት ከፍተኛው የዳይመንድ ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ተቋሙ ለሽልማት የበቃባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች፦
⭐ ልዩ ትኩረት፦
ለታካሚዎች ለሚሰጠው ልዩ እንክብካቤ እና ለአገልግሎት ጥራት ያለው ጽኑ አቋም።
💻 ዲጂታል ጤና (Digital Healthcare)፦
አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሲስተም በመደገፍ፣ የታካሚዎችን መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ መያዝ እና የጥበቃ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ በመቻሉ።
🤝 ማህበራዊ ኃላፊነት፦
አቅም ለሌላቸው ዜጎች በሚያደርገው የዋጋ ቅናሽ እና በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ተሳትፎ።
🚀 የሥራ ዕድል፦
በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የክሊኒካል፣ የፋርማሲ፣ የማማከርና የላቀ የላብራቶሪ ምርመራዎችን እየሰጠ ይገኛል።
የወደፊት ራዕይ፦
የድርጅቱ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ስምዖን ሀብተአብ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ወደፊት የተቀናጀ የቴሌ-መድኃኒት (Telemedicine) ኔትወርክን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተደገፉ የሕክምና ውሳኔ ረዳት ሥርዓቶችን ለመዘርጋት እየሰራ ይገኛል።
በ2011 (እ.ኤ.አ) የተመሰረተው ይህ ተቋም ለደረሰበት ከፍተኛ ደረጃ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!
#visionhealth #healthcareethiopia #awardwinning #digitalhealth #grandafricaaward #medicalexcellence #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "ለዚህ ሁሉ ዓመት ስኬት ያበቃን ሙያችንንና ሕሙማንን ማስቀደማችን ነው" — ቪዥን የጤና አገልግሎት
ባለፉት 15 ዓመታት በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በምሳሌነት የሚጠቀስ ሥራ ሲያከናውን የቆየው ቪዥን የጤና አገልግሎት፣ በግራንድ አፍሪካ ሽልማት ከፍተኛው የዳይመንድ ደረጃ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
ተቋሙ ለሽልማት የበቃባቸው ዋና ዋና ምክንያቶች፦
⭐ ልዩ ትኩረት፦
ለታካሚዎች ለሚሰጠው ልዩ እንክብካቤ እና ለአገልግሎት ጥራት ያለው ጽኑ አቋም።
💻 ዲጂታል ጤና (Digital Healthcare)፦
አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሲስተም በመደገፍ፣ የታካሚዎችን መረጃ በአስተማማኝ ሁኔታ መያዝ እና የጥበቃ ጊዜን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ በመቻሉ።
🤝 ማህበራዊ ኃላፊነት፦
አቅም ለሌላቸው ዜጎች በሚያደርገው የዋጋ ቅናሽ እና በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ተሳትፎ።
🚀 የሥራ ዕድል፦
በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የክሊኒካል፣ የፋርማሲ፣ የማማከርና የላቀ የላብራቶሪ ምርመራዎችን እየሰጠ ይገኛል።
የወደፊት ራዕይ፦
የድርጅቱ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ስምዖን ሀብተአብ እንደገለጹት፤ ተቋሙ ወደፊት የተቀናጀ የቴሌ-መድኃኒት (Telemedicine) ኔትወርክን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተደገፉ የሕክምና ውሳኔ ረዳት ሥርዓቶችን ለመዘርጋት እየሰራ ይገኛል።
በ2011 (እ.ኤ.አ) የተመሰረተው ይህ ተቋም ለደረሰበት ከፍተኛ ደረጃ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን!
#visionhealth #healthcareethiopia #awardwinning #digitalhealth #grandafricaaward #medicalexcellence #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
12 months ago
🌼እንኳን አደረሳችሁ🌼
ዊኬር ዲጂታል ሄልዝ 🌼 አዲስ ዓመትን በማስመልከት ለሚቀጥሉት 14 ቀናት በሀገራችን አሉ ከሚባሉ ስፔሻሊስት አና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞች ጋር በነፃ የሕክምና ምክክር አገልግሎት አዘጋጅቶላችኋል።
ያሉት ስፔሻሊስቶች
🟥 የሕፃናት
🟥 የውስጥ ደዌ
🟥 የማህፀን፣ ፅንስ እና መካንነት
🟥 የካንሰር
🟥 የቆዳ
🟥 ከአንገት በላይ
🟥 የቀዶ ጥገና
🟥 የአአምሮ
🟥 የስነልቦና
🟥 የስነ ወሲብ እና ሌሎችንም በነፃ ያናግሩ
የዙህ አድል ተጠቃሚ ለመሆን ማድረግ ያለባችሁ
👉 የዊኬር የ ስልክ መተግበሪያን ከፕለይ ስቶር ማውረድ አና መመዝገብ
https://play.google.com/st...
👉 በመቀጠል 9394 📞 ላይ መደወል ብቻ ነዉ።
አንዳያመልጣችሁ!!!!!!
🌼 መልካም በዓል! 🌼
#freeconsultation #wecareet #doctors #medicine #ethiopia #newyear #digitalhealth
ዊኬር ዲጂታል ሄልዝ 🌼 አዲስ ዓመትን በማስመልከት ለሚቀጥሉት 14 ቀናት በሀገራችን አሉ ከሚባሉ ስፔሻሊስት አና ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞች ጋር በነፃ የሕክምና ምክክር አገልግሎት አዘጋጅቶላችኋል።
ያሉት ስፔሻሊስቶች
🟥 የሕፃናት
🟥 የውስጥ ደዌ
🟥 የማህፀን፣ ፅንስ እና መካንነት
🟥 የካንሰር
🟥 የቆዳ
🟥 ከአንገት በላይ
🟥 የቀዶ ጥገና
🟥 የአአምሮ
🟥 የስነልቦና
🟥 የስነ ወሲብ እና ሌሎችንም በነፃ ያናግሩ
የዙህ አድል ተጠቃሚ ለመሆን ማድረግ ያለባችሁ
👉 የዊኬር የ ስልክ መተግበሪያን ከፕለይ ስቶር ማውረድ አና መመዝገብ
https://play.google.com/st...
👉 በመቀጠል 9394 📞 ላይ መደወል ብቻ ነዉ።
አንዳያመልጣችሁ!!!!!!
🌼 መልካም በዓል! 🌼
#freeconsultation #wecareet #doctors #medicine #ethiopia #newyear #digitalhealth
Comments