10 days ago
ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ 300 ስደተኞች ታግተው ኩላሊታቸዉ እንደሚወጣ እንደተዛተባቸዉ ተሰማ
ባለፈው ክረምት ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ ከ300 በላይ ስደተኞች አፈና፣ድብደባ እና በግዳጅ የአካል ክፍሎችን እንደሚነጠቁ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።ወጣቶቹ ከኢራቅ ኩርዲስታን የመጡ ሲሆን ሁሉም በሊቢያ በሚኙ ሚሊሻዎች ከእያንዳንዳቸው ቤተሰቦቻቸው 5,000 ዶላር ለማስለቀቅ የተጠየቁ ሲሆን ገንዘቡን በፍጥነት ካልከፈሉ ኩላሊቶቻቸዉን እንደሚያጡ ተዝቶባቸዉ ነበር፡፡
ከእስር የተፈቱትን አንዳንድ ታጋቾች የግዳጅ ስራዎች መፈጸማቸውንም የሚያሳዩ የፎቶ ማስረጃዎችን አጋርተዋል፡፡የቀድሞዎቹ ምርኮኞች የደረሰባቸዉን የስቃይ ማስረጃ አሳይተዋል፡፡ ወደ 180 የሚጠጉ ሰዎች በአንድ ክፍል ውስጥ በጠባብ ሁኔታ ውስጥ እንደቆዩ ተናግረዋል፡፡ቢያንስ አንድ ታጋች የተገደለ ሲሆን ምን ያህሉ በምርኮ እንደሚቀሩ የታወቀ ነገር የለም።
ሚሊሻዎቹ በሊቢያ በኩል ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ድረስ ፍልሰተኞቹ እየመራቸው ነበር ተብሏል። ሆኖም የስደተኞቹን ጉዞ ካደራጀው ከኢራቅ የኩርድ ህዝብ-ህገ-ወጥ አዘዋዋሪ ኖህ አሮን ጋር በክፍያ ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር።አሮን አሁን በፈረንሳይ በተለያዩ የገንዘብ ማጭበርበር እና የኮንትሮባንድ ወንጀሎች የ10 አመት እስራት ተፈርዶበታል።
Via_dagu
Seledadotio
Seledadotio
ባለፈው ክረምት ወደ እንግሊዝ ሲያቀኑ የነበሩ ከ300 በላይ ስደተኞች አፈና፣ድብደባ እና በግዳጅ የአካል ክፍሎችን እንደሚነጠቁ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ተሰምቷል።ወጣቶቹ ከኢራቅ ኩርዲስታን የመጡ ሲሆን ሁሉም በሊቢያ በሚኙ ሚሊሻዎች ከእያንዳንዳቸው ቤተሰቦቻቸው 5,000 ዶላር ለማስለቀቅ የተጠየቁ ሲሆን ገንዘቡን በፍጥነት ካልከፈሉ ኩላሊቶቻቸዉን እንደሚያጡ ተዝቶባቸዉ ነበር፡፡
ከእስር የተፈቱትን አንዳንድ ታጋቾች የግዳጅ ስራዎች መፈጸማቸውንም የሚያሳዩ የፎቶ ማስረጃዎችን አጋርተዋል፡፡የቀድሞዎቹ ምርኮኞች የደረሰባቸዉን የስቃይ ማስረጃ አሳይተዋል፡፡ ወደ 180 የሚጠጉ ሰዎች በአንድ ክፍል ውስጥ በጠባብ ሁኔታ ውስጥ እንደቆዩ ተናግረዋል፡፡ቢያንስ አንድ ታጋች የተገደለ ሲሆን ምን ያህሉ በምርኮ እንደሚቀሩ የታወቀ ነገር የለም።
ሚሊሻዎቹ በሊቢያ በኩል ወደ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ድረስ ፍልሰተኞቹ እየመራቸው ነበር ተብሏል። ሆኖም የስደተኞቹን ጉዞ ካደራጀው ከኢራቅ የኩርድ ህዝብ-ህገ-ወጥ አዘዋዋሪ ኖህ አሮን ጋር በክፍያ ላይ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር።አሮን አሁን በፈረንሳይ በተለያዩ የገንዘብ ማጭበርበር እና የኮንትሮባንድ ወንጀሎች የ10 አመት እስራት ተፈርዶበታል።
Via_dagu
Seledadotio
Seledadotio
25 days ago
የወለደችውን ህፃን ልጅ መፀዳጃ ቤት ለመክተት ስትታገል የነበረች እናት በእስራት ተቀጣች
በቦረና ዞን ዲሎቲ ወረዳ ውስጥ የወለደችውን ልጅ መፀዳጃ ውስጥ ለመክተት የሞከረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች ።የቦረና ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ፅ/ቤት ሃላፊ ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ ለብስራት ሬዲዮ እንገለጹት ተከሳሽ መገርቱ ጋሹ የተባለች ተከሳሽ ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ሴት ልጅ በሰላም መገላገሏ ተገልጿል ።
ተከሳሿ በሰላም የወለደቻትን ሴት ልጅ ለተወሰኑ ቀናት አጠገቧ ካቆየቻት በኋላ ማንም ሳያያት መፀዳጃ ቤት በመግባት ህጻኗን ጉድጓድ ውስጥ በጭንቅላቷ ለመክተት ስትሞክር የህጻኗን ለቅሶ የሰሙት ሰዎች ህጻኗን ከሞት ማትረፋቸው ተገልጿል። ድርጊቱን ስትፈጽም የነበረችው ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ውላለች።ፖሊስም ህጻኗን ወዲያው ለህክምና ወደ ጤና ተቋም በመላክ ተከሳሿ ላይ በበቂ ማስረጃ የምርመራ መዝገቡን በማጣራት ለአቃቢ ህግ አስተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በተከሳሿ ላይ በህጻን ልጅ መግደል ወንጀል ሙከራ ክስ የመሰረተባት እንደሆነ ገልፀዋል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቦረና ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለ ችሎት ተከሳሽ መገርቱ ጋሻው አስባና አቅዳ የወለደቻትን ልጅ ለመግደል በመፀዳጃ ቤት ለመክተት ስትሞክር በመያዟ በአምስት አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ የተወሰነባት መሆኑን ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል። ህጻኗ በተደረጋላት የተፋጠነ የህክምና እርዳታ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደምትገኝና ወደፊት ህጉን በጠበቀ መሰረት ለአሳዳጊ እንደምትሰጥ ገልፀዋል።via_dagu
Seledadotio
Seledadotio
በቦረና ዞን ዲሎቲ ወረዳ ውስጥ የወለደችውን ልጅ መፀዳጃ ውስጥ ለመክተት የሞከረችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች ።የቦረና ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ፅ/ቤት ሃላፊ ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ ለብስራት ሬዲዮ እንገለጹት ተከሳሽ መገርቱ ጋሹ የተባለች ተከሳሽ ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ሴት ልጅ በሰላም መገላገሏ ተገልጿል ።
ተከሳሿ በሰላም የወለደቻትን ሴት ልጅ ለተወሰኑ ቀናት አጠገቧ ካቆየቻት በኋላ ማንም ሳያያት መፀዳጃ ቤት በመግባት ህጻኗን ጉድጓድ ውስጥ በጭንቅላቷ ለመክተት ስትሞክር የህጻኗን ለቅሶ የሰሙት ሰዎች ህጻኗን ከሞት ማትረፋቸው ተገልጿል። ድርጊቱን ስትፈጽም የነበረችው ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ውላለች።ፖሊስም ህጻኗን ወዲያው ለህክምና ወደ ጤና ተቋም በመላክ ተከሳሿ ላይ በበቂ ማስረጃ የምርመራ መዝገቡን በማጣራት ለአቃቢ ህግ አስተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በተከሳሿ ላይ በህጻን ልጅ መግደል ወንጀል ሙከራ ክስ የመሰረተባት እንደሆነ ገልፀዋል።
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቦረና ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለ ችሎት ተከሳሽ መገርቱ ጋሻው አስባና አቅዳ የወለደቻትን ልጅ ለመግደል በመፀዳጃ ቤት ለመክተት ስትሞክር በመያዟ በአምስት አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ የተወሰነባት መሆኑን ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል። ህጻኗ በተደረጋላት የተፋጠነ የህክምና እርዳታ በሙሉ ጤንነት ላይ እንደምትገኝና ወደፊት ህጉን በጠበቀ መሰረት ለአሳዳጊ እንደምትሰጥ ገልፀዋል።via_dagu
Seledadotio
Seledadotio
4 months ago
አጫጭር መረጃዎች
🇮🇱 🇱🇧የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ሰሜናዊ ትሪፖሊ ከተማ በወሰደው እርምጃ የሃማስ አዛዥ ዋሲም አታላህ አሊን ላይ ኢላማ በማድረግ መግደሉን አስታውቋል።
🇮🇷🇮🇱🇺🇸 በኢራን ቅዳሜ እለት በሚናብ ትምህርት ቤት ላይ በተፈጸመው የእስራኤል የሚሳኤል 175 ሴት ተማሪዎች እና ሰራተኞችን ጨምሮ ቢያንስ 1,230ዜጎቿ በጦርነቱ ተገድለውባታል። በእስራኤል በኩል እስካሁን 11 ሰዎች ሲገደሉ ስድስት የአሜሪካ ወታደሮችም ተገድለዋል።
🇮🇷🇰🇼 🇦🇪🇧🇭🇴🇲በኢራን የሚሳኤል ጥቃት በኩዌት ወታደሮችን ጨምሮ አራት ሰዎች ፣ በኢምሬትስ ሶስት ፣ በባህሬን እና ኦማን አንድ አንድ ሰዎች ተገድለዋል።
🇱🇧 የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር የእስራኤል የቦምብ ጥቃት ከሰኞ ጀምሮ ባስከተለው ጉዳት 102 ሰዎች ሲገደሉ 638 ሰዎች ቆስለዋል ሲል የሊባኖስ ብሄራዊ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።
🇦🇪🌍 የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የአለም ጤና ድርጅት በዱባይ በሚገኘው የአለም አቀፍ የድንገተኛ አደጋ ሎጂስቲክስ ማዕከል የሚያደርገውን ስራ እንዲያቆም አስገድዶታል ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገልፀዋል።
🇹🇷🇫🇷 የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እንደተናገሩት አንካራ በኢራን ጉዳይ ላይ ወደ ድርድር እንዲመለስ ግፊት እያደረገች ነው ብለዋል።
🇱🇧🇫🇷 የሊባኖስ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን የፈረንሳዩ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጣልቃ እንዲገቡ እና እስራኤል በቤይሩት ደቡባዊ ዳርቻ በዳሂህ ላይ የምታደርሰውን የጅምላ ፍንዳታ እንዲያስቆሙ ጠይቀዋል።
Dagu journal
seledadotio
seledadotio
🇮🇱 🇱🇧የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ሰሜናዊ ትሪፖሊ ከተማ በወሰደው እርምጃ የሃማስ አዛዥ ዋሲም አታላህ አሊን ላይ ኢላማ በማድረግ መግደሉን አስታውቋል።
🇮🇷🇮🇱🇺🇸 በኢራን ቅዳሜ እለት በሚናብ ትምህርት ቤት ላይ በተፈጸመው የእስራኤል የሚሳኤል 175 ሴት ተማሪዎች እና ሰራተኞችን ጨምሮ ቢያንስ 1,230ዜጎቿ በጦርነቱ ተገድለውባታል። በእስራኤል በኩል እስካሁን 11 ሰዎች ሲገደሉ ስድስት የአሜሪካ ወታደሮችም ተገድለዋል።
🇮🇷🇰🇼 🇦🇪🇧🇭🇴🇲በኢራን የሚሳኤል ጥቃት በኩዌት ወታደሮችን ጨምሮ አራት ሰዎች ፣ በኢምሬትስ ሶስት ፣ በባህሬን እና ኦማን አንድ አንድ ሰዎች ተገድለዋል።
🇱🇧 የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር የእስራኤል የቦምብ ጥቃት ከሰኞ ጀምሮ ባስከተለው ጉዳት 102 ሰዎች ሲገደሉ 638 ሰዎች ቆስለዋል ሲል የሊባኖስ ብሄራዊ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።
🇦🇪🌍 የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የአለም ጤና ድርጅት በዱባይ በሚገኘው የአለም አቀፍ የድንገተኛ አደጋ ሎጂስቲክስ ማዕከል የሚያደርገውን ስራ እንዲያቆም አስገድዶታል ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ገልፀዋል።
🇹🇷🇫🇷 የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እንደተናገሩት አንካራ በኢራን ጉዳይ ላይ ወደ ድርድር እንዲመለስ ግፊት እያደረገች ነው ብለዋል።
🇱🇧🇫🇷 የሊባኖስ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን የፈረንሳዩ አቻቸው ኢማኑኤል ማክሮን ጣልቃ እንዲገቡ እና እስራኤል በቤይሩት ደቡባዊ ዳርቻ በዳሂህ ላይ የምታደርሰውን የጅምላ ፍንዳታ እንዲያስቆሙ ጠይቀዋል።
Dagu journal
seledadotio
seledadotio
6 months ago
በናይጄሪያ መስጊድ በሶላት ወቅት ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ቢያንስ 5 ሰዎች ሲገደሉ 35 ሰዎች ቆሰሉ
#ethiopia | በናይጄሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ ቦርኖ ግዛት ሀሙስ በምሽት ሰላት ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ቢያንስ አምስት ሰዎች ሲገደሉ 35 ያህል ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባይ ኤኤስፒ ናሆም ዳሶ ኬኔት የማህበራዊ ሚዲያ ድረ-ገጽ በሆነዉ ፌስቡክ ላይ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
በመግለጫው መሰረት፣ ባለስልጣናት በግዛቱ ዋና ከተማ ማይዱጉሪ የተፈጸመው ፍንዳታ በአጥፍቶ ጠፊ ፍንዳታ ነው ብለው እንደሚጠረጥሩ በማንሳት ምስክሮች ከሰጡት ቃል እና በአጥፍቶ ጠፊነት ከተጠረጠረው ልብስ ውስጥ ቁርጥራጮች መገኘታቸውን ገልጸዋል።
ኃላፊዎቹ የችግሩን መንስኤና ሁኔታ ለማወቅ ምርመራውን ቀጥሏል ብለዋል ።የቦርኖ ግዛት ለዓመታት በታጣቂዉ ቦኮ ሃራም እና መሰል ቡድኖች ስትታመስ ቆይታለች። #dagu
#ethiopia | በናይጄሪያ ሰሜናዊ ምስራቅ ቦርኖ ግዛት ሀሙስ በምሽት ሰላት ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ ቢያንስ አምስት ሰዎች ሲገደሉ 35 ያህል ሰዎች ቆስለዋል ሲሉ የፖሊስ ቃል አቀባይ ኤኤስፒ ናሆም ዳሶ ኬኔት የማህበራዊ ሚዲያ ድረ-ገጽ በሆነዉ ፌስቡክ ላይ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡
በመግለጫው መሰረት፣ ባለስልጣናት በግዛቱ ዋና ከተማ ማይዱጉሪ የተፈጸመው ፍንዳታ በአጥፍቶ ጠፊ ፍንዳታ ነው ብለው እንደሚጠረጥሩ በማንሳት ምስክሮች ከሰጡት ቃል እና በአጥፍቶ ጠፊነት ከተጠረጠረው ልብስ ውስጥ ቁርጥራጮች መገኘታቸውን ገልጸዋል።
ኃላፊዎቹ የችግሩን መንስኤና ሁኔታ ለማወቅ ምርመራውን ቀጥሏል ብለዋል ።የቦርኖ ግዛት ለዓመታት በታጣቂዉ ቦኮ ሃራም እና መሰል ቡድኖች ስትታመስ ቆይታለች። #dagu
6 months ago
አብዛኛዎቹ ሩሲያውያን የዩክሬን ጦርነት በ2026 ያበቃል ብለው እንደሚጠብቁ አንድ ጥናት አረጋገጠ
#ethiopia | አብዛኛዎቹን ሩሲያውያን በዩክሬን ያለው ጦርነት በ2026 ያበቃል ብለው እንደሚጠብቁ የመንግስት የምርምር ማዕከል ያስታወቀ ሲሆን የሩስያ ሀይሎች በጦር ሜዳ ላይ የሚያደርጉት ግስጋሴ ቢቀጥልም በኪየቭ እና በሞስኮ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከሩሲያ ህዝብ የተሰበሰበዉ አስተያየት እንዳመላከተዉ በወጪው አመት ሩሲያውያን ጦርነቱ እንደሚያበቃ ብሩህ ተስፋ እንዳላቸዉ ተመላክቷል፡፡
ጥናቱን የሰራዉ ቪቲሲኦኤም የተሰኘዉ ማዕከል ምክትል ኃላፊ ሚካሂል ማሞኖቭ በዓመት መጨረሻ ላይ ሆነዉ እንደተናገሩ በጥናቱ ከተካሄደባቸው 1,600 ሰዎች መካከል 70 በመቶው ለሩሲያ 2026 “የተሳካ” ዓመት እንደሆነ አድርገው ይመለከታሉ ብለዋል።
ለብሩህ ተስፋ ዋናው ምክንያት በፕሬዚዳንት ፑቲን ከተገለጹት ብሄራዊ ጥቅሞች ጋር በተገናኘ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻውን ማጠናቀቅ እና የተገለጹትን ዓላማዎች ማሳካት ይቻላል የሚል ተስፋ አድርገዋል፡፡
ማሞኖቭ እንዳሉት የሩስያ ጦር በዩክሬን እያካሄደ ያለውን ጥቃት፣ ዋሽንግተን የዩክሬንን ጦርነት ለመደገፍ ፈቃደኛ አለመሆኗ እና የአውሮፓ ህብረት በዩክሬን ውስጥ የዩናይትድ ስቴትስ ሚናን ሙሉ በሙሉ ለመተካት አለመቻሉ በገንዘብ እና በወታደራዊ ድጋፍ እጥረት ጦርነቱን ለማቆም የመጨረሻው ስምምነት ከሚጠበቀው ቁልፍ ምክንያቶች በስተጀርባ ይገኛል ሲሉ ጠቁመዋል ።
በግጭቱ ማጠቃለያ ላይ የሩሲያ ወታደራዊ ዘማቾችን ወደ ህብረተሰብ መመለስ እና በሩሲያ ቁጥጥር ስር ያሉ የዩክሬን ክልሎችን እንዲሁም የሩሲያ የድንበር አካባቢዎችን እንደገና መገንባት ዋና ዋና ጉዳዮች ይሆናሉ ሲሉ ማሞኖቭ አክለዋል። #dagu
#ethiopia | አብዛኛዎቹን ሩሲያውያን በዩክሬን ያለው ጦርነት በ2026 ያበቃል ብለው እንደሚጠብቁ የመንግስት የምርምር ማዕከል ያስታወቀ ሲሆን የሩስያ ሀይሎች በጦር ሜዳ ላይ የሚያደርጉት ግስጋሴ ቢቀጥልም በኪየቭ እና በሞስኮ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከሩሲያ ህዝብ የተሰበሰበዉ አስተያየት እንዳመላከተዉ በወጪው አመት ሩሲያውያን ጦርነቱ እንደሚያበቃ ብሩህ ተስፋ እንዳላቸዉ ተመላክቷል፡፡
ጥናቱን የሰራዉ ቪቲሲኦኤም የተሰኘዉ ማዕከል ምክትል ኃላፊ ሚካሂል ማሞኖቭ በዓመት መጨረሻ ላይ ሆነዉ እንደተናገሩ በጥናቱ ከተካሄደባቸው 1,600 ሰዎች መካከል 70 በመቶው ለሩሲያ 2026 “የተሳካ” ዓመት እንደሆነ አድርገው ይመለከታሉ ብለዋል።
ለብሩህ ተስፋ ዋናው ምክንያት በፕሬዚዳንት ፑቲን ከተገለጹት ብሄራዊ ጥቅሞች ጋር በተገናኘ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻውን ማጠናቀቅ እና የተገለጹትን ዓላማዎች ማሳካት ይቻላል የሚል ተስፋ አድርገዋል፡፡
ማሞኖቭ እንዳሉት የሩስያ ጦር በዩክሬን እያካሄደ ያለውን ጥቃት፣ ዋሽንግተን የዩክሬንን ጦርነት ለመደገፍ ፈቃደኛ አለመሆኗ እና የአውሮፓ ህብረት በዩክሬን ውስጥ የዩናይትድ ስቴትስ ሚናን ሙሉ በሙሉ ለመተካት አለመቻሉ በገንዘብ እና በወታደራዊ ድጋፍ እጥረት ጦርነቱን ለማቆም የመጨረሻው ስምምነት ከሚጠበቀው ቁልፍ ምክንያቶች በስተጀርባ ይገኛል ሲሉ ጠቁመዋል ።
በግጭቱ ማጠቃለያ ላይ የሩሲያ ወታደራዊ ዘማቾችን ወደ ህብረተሰብ መመለስ እና በሩሲያ ቁጥጥር ስር ያሉ የዩክሬን ክልሎችን እንዲሁም የሩሲያ የድንበር አካባቢዎችን እንደገና መገንባት ዋና ዋና ጉዳዮች ይሆናሉ ሲሉ ማሞኖቭ አክለዋል። #dagu
6 months ago
ሩሲያ በአስር ዓመታት ውስጥ በጨረቃ ላይ የኒውክሌር ሀይል ማመንጫ ለመትከል ማቀዷን አስታወቀች
#ethiopia | ሩሲያ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ውስጥ የጨረቃን የጠፈር መርሃ ግብሯን በማስቀጠል የኒውክሌር ሃይል ማመንጫ ጣቢያን በጨረቃ ላይ ለመትከል አቅዳለች። ዋናዎቹ የዓለም ኃያል ሀገራት የምድርን ብቸኛ የተፈጥሮ ሳተላይት ለመቃኘት እየተጣደፉ ይገኛል።
እ.ኤ.አ. በ 1961 የሶቪየት ኮስሞናዊት ዩሪ ጋጋሪን ወደ ህዋ በመላክ የመጀመሪያው ሰው ከሆነ ወዲህ ሩሲያ በህዋ ምርምር ላይ ቀዳሚ ሃይል ነበረች።
ከቅርብ አስርት አመታት ወዲህ ግን ከአሜሪካ እና ቻይና ስር ለመከተል ተገዳለች።እ.ኤ.አ. ነሐሴ 2023 የራሺያ ፍላጎት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ሲሆን ሰው አልባው ሉና-25 ተልእኮ ወደ ጨረቃ ላይ ለማረፍ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።
በአንፃሩ ኤሎን ማስክ የጠፈር ተሽከርካሪዎችን በማምጠቅ ላይ ለውጥ አሳይቷል። የሩሲያ ግዛት የጠፈር ኮርፖሬሽን ሮስኮስሞስ በ2036 የጨረቃ ሃይል ማመንጫ ለመገንባት አቅዶ ከላቮችኪን ማህበር ኤሮስፔስ ኩባንያ ጋር ውል መፈራረሙን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ሮስስኮስሞስ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫው አላማ የሩስያን የጨረቃ መርሃ ግብር ማለትም ሮቨርስ፣ ኦብዘርቫቶሪ እና የጋራ የሩሲያ-ቻይና አለም አቀፍ የጨረቃ ምርምር ጣቢያ መሠረተ ልማትን ማጎልበት ነው ብሏል።
"ፕሮጀክቱ በቋሚነት የሚሰራ ሳይንሳዊ የጨረቃ ጣቢያን ለመፍጠር እና ከአንድ ጊዜ ተልዕኮዎች ወደ የረጅም ጊዜ የጨረቃ ፍለጋ መርሃ ግብር ለመሸጋገር ጠቃሚ እርምጃ ነው" ሲል በመግለጫው አክሏል።
#dagu
#ethiopia | ሩሲያ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ውስጥ የጨረቃን የጠፈር መርሃ ግብሯን በማስቀጠል የኒውክሌር ሃይል ማመንጫ ጣቢያን በጨረቃ ላይ ለመትከል አቅዳለች። ዋናዎቹ የዓለም ኃያል ሀገራት የምድርን ብቸኛ የተፈጥሮ ሳተላይት ለመቃኘት እየተጣደፉ ይገኛል።
እ.ኤ.አ. በ 1961 የሶቪየት ኮስሞናዊት ዩሪ ጋጋሪን ወደ ህዋ በመላክ የመጀመሪያው ሰው ከሆነ ወዲህ ሩሲያ በህዋ ምርምር ላይ ቀዳሚ ሃይል ነበረች።
ከቅርብ አስርት አመታት ወዲህ ግን ከአሜሪካ እና ቻይና ስር ለመከተል ተገዳለች።እ.ኤ.አ. ነሐሴ 2023 የራሺያ ፍላጎት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ሲሆን ሰው አልባው ሉና-25 ተልእኮ ወደ ጨረቃ ላይ ለማረፍ ያደረገው ሙከራ አልተሳካም።
በአንፃሩ ኤሎን ማስክ የጠፈር ተሽከርካሪዎችን በማምጠቅ ላይ ለውጥ አሳይቷል። የሩሲያ ግዛት የጠፈር ኮርፖሬሽን ሮስኮስሞስ በ2036 የጨረቃ ሃይል ማመንጫ ለመገንባት አቅዶ ከላቮችኪን ማህበር ኤሮስፔስ ኩባንያ ጋር ውል መፈራረሙን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ሮስስኮስሞስ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫው አላማ የሩስያን የጨረቃ መርሃ ግብር ማለትም ሮቨርስ፣ ኦብዘርቫቶሪ እና የጋራ የሩሲያ-ቻይና አለም አቀፍ የጨረቃ ምርምር ጣቢያ መሠረተ ልማትን ማጎልበት ነው ብሏል።
"ፕሮጀክቱ በቋሚነት የሚሰራ ሳይንሳዊ የጨረቃ ጣቢያን ለመፍጠር እና ከአንድ ጊዜ ተልዕኮዎች ወደ የረጅም ጊዜ የጨረቃ ፍለጋ መርሃ ግብር ለመሸጋገር ጠቃሚ እርምጃ ነው" ሲል በመግለጫው አክሏል።
#dagu
Sponsored by
Surafel
6 months ago
አቶ አርሰናል ፤ የትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ሆነው ተሾሙ
ከሰሞኑ የሀረሪ ክልል መንግስት ባካሄደው የአመራር ሽግሽግ አቶ አርሰናል አብዲ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ሆነዉ ሹመት ማግኘታቸውን ዳጉ ጆርናል ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።
በተጨማሪም ክልሉ አቶ ሳዳም መሀመድን የክልሉ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ሀላፊ በማድረግ ሹመት ሰጥቷል።
የእንግሊዙ አርሰናልስ በዚህ አመት የዋንጫ ሹመት ያገኝ ይሆን?(dagu)
seledadotio
seledadotio
ከሰሞኑ የሀረሪ ክልል መንግስት ባካሄደው የአመራር ሽግሽግ አቶ አርሰናል አብዲ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ሆነዉ ሹመት ማግኘታቸውን ዳጉ ጆርናል ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል ።
በተጨማሪም ክልሉ አቶ ሳዳም መሀመድን የክልሉ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ሀላፊ በማድረግ ሹመት ሰጥቷል።
የእንግሊዙ አርሰናልስ በዚህ አመት የዋንጫ ሹመት ያገኝ ይሆን?(dagu)
seledadotio
seledadotio
6 months ago
አሜሪካ በማያሚ ከሩሲያ እና ዩክሬን ጋር የተደረገው ውይይት ገንቢና ውጤታማ ነበር ስትል ተናገረች
#ethiopia | የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ በፍሎሪዳ ግዛት ከዩክሬን ፣ አውሮፓውያንፈ እና ሩሲያውያን ተደራዳሪዎች ጋር የተለያዩ ስብሰባዎችን ካደረጉ በኋላ የሞስኮን ጦርነት በዩክሬን ለማስቆም የሚደረገውን ንግግር “አመርቂ እና ገንቢ” ነው ሲሉ አድንቀዋል።
እሁድ እለት በማያሚ የተካሄደው ድርድር በአሜሪካ፣ ሩሲያ እና ዩክሬን መካከል በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለአራት ዓመታት የተቃረበውን ጦርነት ለማቆም ባቀረቡት ባለ 20 ነጥብ እቅድ ላይ የተደረገው ተከታታይ ስብሰባ የመጨረሻው ነው።
ምንም እንኳን በአሜሪካ ወገን ግጭት እንደሚያበቃ ብሩህ ተስፋ ቢኖርም ፣ በግጭቱ ወቅት ሩሲያ በኃይል የያዘቻቸውን ግዛት ጉዳይ ጨምሮ ቁልፍ በሆኑ ነጥቦች ላይ በቅርቡ መፍትሄ እንደሚሰጥ ግልጽ ምልክቶች አልታዩም ።
ቅዳሜ ዕለት ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ ጋር የተገናኙት ዊትኮፍ እሁድ እለት ከዩክሬን እና ከአውሮፓ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተዋል።
ከዚያም በከፍተኛ ባለስልጣን ሩስቴም ኡሜሮቭ ከሚመራው የዩክሬን ልዑካን ጋር የተለየ ውይይት አድርገዋል። የትራምፕ አማች ያሬድ ኩሽነርም በስብሰባው ተሳታፊ ነበሩ።
ዊትኮፍ ከኡሜሮቭ ጋር በጋራ በሰጡት መግለጫ ያደረግነው ንግግር "አመርቂ እና ገንቢ" ብለው በመጥራት "በዩክሬን፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በአውሮፓ መካከል የጋራ ስትራቴጂካዊ አቀራረብ ላይ ያተኮሩ ናቸው ብለዋል።
"የጊዜ ሰሌዳዎችን እና የቀጣይ እርምጃዎችን ቅደም ተከተል ለመወያየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል" ሲሉ አክለዋል። የተደረገው የሁለትዮሽ ውይይቶች በቁልፍ ሰነዶች ላይ አቋሞችን በማዘጋጀት እና በማጣጣም ላይ ያተኮረ ሲሆን ይህም ባለ 20 ነጥብ የሰላም እቅድ ፣ “ባለብዙ ወገን የደህንነት ዋስትና ማዕቀፍ” ፣ “የአሜሪካ የደህንነት ዋስትና ማዕቀፍ ለዩክሬን” እና “የኢኮኖሚ እና የብልጽግና እቅድ” ላይ ያተኮረ ነበር።#dagu
#ethiopia | የዩናይትድ ስቴትስ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ በፍሎሪዳ ግዛት ከዩክሬን ፣ አውሮፓውያንፈ እና ሩሲያውያን ተደራዳሪዎች ጋር የተለያዩ ስብሰባዎችን ካደረጉ በኋላ የሞስኮን ጦርነት በዩክሬን ለማስቆም የሚደረገውን ንግግር “አመርቂ እና ገንቢ” ነው ሲሉ አድንቀዋል።
እሁድ እለት በማያሚ የተካሄደው ድርድር በአሜሪካ፣ ሩሲያ እና ዩክሬን መካከል በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለአራት ዓመታት የተቃረበውን ጦርነት ለማቆም ባቀረቡት ባለ 20 ነጥብ እቅድ ላይ የተደረገው ተከታታይ ስብሰባ የመጨረሻው ነው።
ምንም እንኳን በአሜሪካ ወገን ግጭት እንደሚያበቃ ብሩህ ተስፋ ቢኖርም ፣ በግጭቱ ወቅት ሩሲያ በኃይል የያዘቻቸውን ግዛት ጉዳይ ጨምሮ ቁልፍ በሆኑ ነጥቦች ላይ በቅርቡ መፍትሄ እንደሚሰጥ ግልጽ ምልክቶች አልታዩም ።
ቅዳሜ ዕለት ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ልዩ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ ጋር የተገናኙት ዊትኮፍ እሁድ እለት ከዩክሬን እና ከአውሮፓ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተዋል።
ከዚያም በከፍተኛ ባለስልጣን ሩስቴም ኡሜሮቭ ከሚመራው የዩክሬን ልዑካን ጋር የተለየ ውይይት አድርገዋል። የትራምፕ አማች ያሬድ ኩሽነርም በስብሰባው ተሳታፊ ነበሩ።
ዊትኮፍ ከኡሜሮቭ ጋር በጋራ በሰጡት መግለጫ ያደረግነው ንግግር "አመርቂ እና ገንቢ" ብለው በመጥራት "በዩክሬን፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በአውሮፓ መካከል የጋራ ስትራቴጂካዊ አቀራረብ ላይ ያተኮሩ ናቸው ብለዋል።
"የጊዜ ሰሌዳዎችን እና የቀጣይ እርምጃዎችን ቅደም ተከተል ለመወያየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል" ሲሉ አክለዋል። የተደረገው የሁለትዮሽ ውይይቶች በቁልፍ ሰነዶች ላይ አቋሞችን በማዘጋጀት እና በማጣጣም ላይ ያተኮረ ሲሆን ይህም ባለ 20 ነጥብ የሰላም እቅድ ፣ “ባለብዙ ወገን የደህንነት ዋስትና ማዕቀፍ” ፣ “የአሜሪካ የደህንነት ዋስትና ማዕቀፍ ለዩክሬን” እና “የኢኮኖሚ እና የብልጽግና እቅድ” ላይ ያተኮረ ነበር።#dagu
6 months ago
የእርሻ ማሳ ውስጥ የገባ ዝሆን የ76 ዓመቱን አዛውንት ሕይወት ሲያጠፋ በአንድ ሰው ላይ ጉዳት አደረሰ
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሀረማያ ወረዳ እርሻ ማሳ ውስጥ የገባው ዝሆን የአንድ ሰው ሕይወት ሲያጠፋ በአንድ ሰው ላይ ጉዳት ማድረሱን ፖሊስ አስታውቅቋል።የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮምንኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፍ ምክትል ኢንስፔክተር ካሲዬ አበበ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በዞኑ ሐረማያ ወረዳ በሊና ቀበሌ ውስጥ ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የእርሻ ማሳ ውስጥ የገባው ዝሆን አቶ መሐመድ አሕመድ ቱሌ የተባሉትን የስምንት ልጆች አባት በኩንቢው ጠልፎ የጣላቸው ከእርሻ ማሳቸው ውስጥ ዝሆኑን ለማውጣት ባደረጉት ጥረት እንደሆነ ገልፀዋል። በኩቢው አዛውንቱን ጠቅልሎ ከጣላቸው በኃላ በእግሩ ሲረጋግጣቸው የተመለከተው የሀያ አመት ወጣት አዛውንቱን ከዝሆኑ ጥቃት ለመታደግ ጥረት ሲያደርግ ዝሆኑ ጉዳት አድርሶበት እንደ ሄደ ገልፀዋል።
የአካባቢ ሰዎች ዝሆኑ ስፍራውን ለቆ ከሄደ በኋላ ሲደርሱ የአዛውንቱ ሕይወት ያለፈ ሲሆን ጉዳት የደረሰበትን ወጣት ደግሞ በሕይወት ያለ በመሆኑ ወዲያው ወደ ሀረማያ ሆስፒታል በማድረስ የሕክምና እርዳታ አግኝቶ በጤንነት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ዝሆኖች አንዳንዴ ከባብሌ ፖርክ በመውጣት በሰብል ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሲሆን ይህንኑ ለመከላከል በሚደረግ ሙከራም በሰው ላይ ጉዳት እንደሚያደርሱ ምክትል ኢኒስፔክተር ካሲዪ አበበ ጨምረው ገልፀዋል።dagu
seledadotio
seledadotio
በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሀረማያ ወረዳ እርሻ ማሳ ውስጥ የገባው ዝሆን የአንድ ሰው ሕይወት ሲያጠፋ በአንድ ሰው ላይ ጉዳት ማድረሱን ፖሊስ አስታውቅቋል።የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮምንኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፍ ምክትል ኢንስፔክተር ካሲዬ አበበ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት በዞኑ ሐረማያ ወረዳ በሊና ቀበሌ ውስጥ ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የእርሻ ማሳ ውስጥ የገባው ዝሆን አቶ መሐመድ አሕመድ ቱሌ የተባሉትን የስምንት ልጆች አባት በኩንቢው ጠልፎ የጣላቸው ከእርሻ ማሳቸው ውስጥ ዝሆኑን ለማውጣት ባደረጉት ጥረት እንደሆነ ገልፀዋል። በኩቢው አዛውንቱን ጠቅልሎ ከጣላቸው በኃላ በእግሩ ሲረጋግጣቸው የተመለከተው የሀያ አመት ወጣት አዛውንቱን ከዝሆኑ ጥቃት ለመታደግ ጥረት ሲያደርግ ዝሆኑ ጉዳት አድርሶበት እንደ ሄደ ገልፀዋል።
የአካባቢ ሰዎች ዝሆኑ ስፍራውን ለቆ ከሄደ በኋላ ሲደርሱ የአዛውንቱ ሕይወት ያለፈ ሲሆን ጉዳት የደረሰበትን ወጣት ደግሞ በሕይወት ያለ በመሆኑ ወዲያው ወደ ሀረማያ ሆስፒታል በማድረስ የሕክምና እርዳታ አግኝቶ በጤንነት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ዝሆኖች አንዳንዴ ከባብሌ ፖርክ በመውጣት በሰብል ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሲሆን ይህንኑ ለመከላከል በሚደረግ ሙከራም በሰው ላይ ጉዳት እንደሚያደርሱ ምክትል ኢኒስፔክተር ካሲዪ አበበ ጨምረው ገልፀዋል።dagu
seledadotio
seledadotio
6 months ago
በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ማምሻውን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አለፈ
#ethiopia | በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቀርሳ ወረዳ ማምሻውን በደረሰ የተሽከርካሪ መገልበጥ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።
የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት አመሻሽ ላይ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የተሽከርካሪው ረዳት ጨምሮ የሰባት ወንድ እና የሁለት ሴቶች በአጠቃላይ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አልፏል።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 06860 ድሬ የሆነ የጭነት ተሽከርካሪ ለግዜው በውል ያልታወቀ ተሳፋሪን አሳፍሮ ከቀርሳ ከተማ ወደ ማያ ከተማ ሲጓዝ ቀርሳ ወረዳ አዋ መራ ቀበሌ ሲደርስ ቀርሳ ድልድይ ውስጥ ገብቶ አደጋው መድረሱ ተገልጿል ።
ህይወታቸውን ካጡ ዘጠኝ ሰዎች በተጨማሪ በአራት ሰዎች ላይ ከባድ ፣በሶስት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ መድረሱን ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ቢሆንም አሽከርካሪው ተሳፋሪን ከእቃ ጋር ከመጠን በላይ በመጫን የተከሰተ ሳይሆን እንዳልቀረ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ጨምረው ገልፀዋል ። አሽከርካሪው ከአደጋው ቦታ ተሰውሮ ያመለጠ ሲሆን ፖሊስም በክትትል ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። #dagu
#ethiopia | በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቀርሳ ወረዳ ማምሻውን በደረሰ የተሽከርካሪ መገልበጥ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።
የምስራቅ ሀረርጌ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት አመሻሽ ላይ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የተሽከርካሪው ረዳት ጨምሮ የሰባት ወንድ እና የሁለት ሴቶች በአጠቃላይ የዘጠኝ ሰዎች ህይወት አልፏል።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 06860 ድሬ የሆነ የጭነት ተሽከርካሪ ለግዜው በውል ያልታወቀ ተሳፋሪን አሳፍሮ ከቀርሳ ከተማ ወደ ማያ ከተማ ሲጓዝ ቀርሳ ወረዳ አዋ መራ ቀበሌ ሲደርስ ቀርሳ ድልድይ ውስጥ ገብቶ አደጋው መድረሱ ተገልጿል ።
ህይወታቸውን ካጡ ዘጠኝ ሰዎች በተጨማሪ በአራት ሰዎች ላይ ከባድ ፣በሶስት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል አደጋ መድረሱን ገልፀዋል።
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ቢሆንም አሽከርካሪው ተሳፋሪን ከእቃ ጋር ከመጠን በላይ በመጫን የተከሰተ ሳይሆን እንዳልቀረ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ጨምረው ገልፀዋል ። አሽከርካሪው ከአደጋው ቦታ ተሰውሮ ያመለጠ ሲሆን ፖሊስም በክትትል ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል። #dagu
6 months ago
የመቂ ከተማ ነዋሪዋ የ10 ሚሊዮን ብር የሎተሪ ዕጣ አሸናፊ ሽልማታቸውን ተረከበች
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ባወጣው የ"ልዩ ዕድል" ሎተሪ የ10 ሚሊዮን ብር ከፍተኛ ዕጣ አሸናፊ የሆኑት የመቂ ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ስምረት ኢቲቻ፣ ሽልማታቸውን በይፋ ተረክበዋል።
ወ/ሮ ስምረት ዕጣው የወጣበትን አጋጣሚ ሲያስታውሱ፣ መስከረም 21 ቀን ከቤተክርስቲያን መልስ ቢሮአቸው ተቀምጠው ሳለ የቆረጡት ትኬት የ10 ሚሊዮን ብር ባለቤት እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። አሸናፊዋ በደስታ ተውጠው በሰጡት አስተያየት "እናቴ እመቤቴ የ10 ሚሊዮን ብር አሸናፊ አድርጋኛለች" በማለት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በበኩሉ፣ ሽልማቱን ለአሸናፊዋ ማስረከቡን ገልጾ፣ መሰል የሎተሪ ዕጣዎች የማህበረሰቡን የኑሮ ሁኔታ ከመቀየር ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚ ያላቸውን ድርሻ ጠቁሟል።Dagu
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ባወጣው የ"ልዩ ዕድል" ሎተሪ የ10 ሚሊዮን ብር ከፍተኛ ዕጣ አሸናፊ የሆኑት የመቂ ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ስምረት ኢቲቻ፣ ሽልማታቸውን በይፋ ተረክበዋል።
ወ/ሮ ስምረት ዕጣው የወጣበትን አጋጣሚ ሲያስታውሱ፣ መስከረም 21 ቀን ከቤተክርስቲያን መልስ ቢሮአቸው ተቀምጠው ሳለ የቆረጡት ትኬት የ10 ሚሊዮን ብር ባለቤት እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። አሸናፊዋ በደስታ ተውጠው በሰጡት አስተያየት "እናቴ እመቤቴ የ10 ሚሊዮን ብር አሸናፊ አድርጋኛለች" በማለት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በበኩሉ፣ ሽልማቱን ለአሸናፊዋ ማስረከቡን ገልጾ፣ መሰል የሎተሪ ዕጣዎች የማህበረሰቡን የኑሮ ሁኔታ ከመቀየር ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚ ያላቸውን ድርሻ ጠቁሟል።Dagu
seledadotio
seledadotio
6 months ago
በኢትዮጵያ በሴቶች ላይ ከሚደርሱ ጥቃቶች 35.2 በመቶ በትዳር አጋሮቻቸው ወይም አብረዋቸው በሚኖሩ ወንዶች የሚፈጸም መሆኑ ተነገረ
#ethiopia ||የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም “ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ጊዜ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ጾታዊ ጥቃት ቀን አስቦ ውሏል።
በኢትዮጵያ በተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማያያዝ ፆታዊ ጥቃትን በጊዜና በቦታ ሳይወሰን ሁሉም ዜጋ መከላከል እንዳለበት የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንለይ ወርቄ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ፆታን መሰረት አድርጎ በሴቶች፣ ህፃናትና አካል ጉዳተኞች ላይ የሚፈጸሙ በርካታ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ጾታዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶች መኖራቸውን ተጠቁሟል፡፡
በኢትዮጵያ ከሚደርሱት ጥቃቶች ከ15 እስከ 49 በሆኑ ሴቶች ላይ 24.9 በመቶ አካላዊ፣ 24 በመቶ ስነልቦናዊ፣ 11.1 በመቶ ወሲባዊ፣ 28 በመቶ ወሲባዊ እና አካላዊ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል መባሉን በተቋሙ የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንለይ ወርቄ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም 35.2.በመቶ በትዳር አጋሮቻቸው ወይም አብረዋቸው በሚኖሩ ወንዶች ጥቃት ይፈጸምባቸዋል።#dagu
#ethiopia ||የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም “ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ ለትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ34ኛ ጊዜ፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ20ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ጾታዊ ጥቃት ቀን አስቦ ውሏል።
በኢትዮጵያ በተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማያያዝ ፆታዊ ጥቃትን በጊዜና በቦታ ሳይወሰን ሁሉም ዜጋ መከላከል እንዳለበት የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንለይ ወርቄ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
ፆታን መሰረት አድርጎ በሴቶች፣ ህፃናትና አካል ጉዳተኞች ላይ የሚፈጸሙ በርካታ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ጾታዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶች መኖራቸውን ተጠቁሟል፡፡
በኢትዮጵያ ከሚደርሱት ጥቃቶች ከ15 እስከ 49 በሆኑ ሴቶች ላይ 24.9 በመቶ አካላዊ፣ 24 በመቶ ስነልቦናዊ፣ 11.1 በመቶ ወሲባዊ፣ 28 በመቶ ወሲባዊ እና አካላዊ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል መባሉን በተቋሙ የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አንለይ ወርቄ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በተጨማሪም 35.2.በመቶ በትዳር አጋሮቻቸው ወይም አብረዋቸው በሚኖሩ ወንዶች ጥቃት ይፈጸምባቸዋል።#dagu
6 months ago
3 መቶ ሺ ብር በባንክ ካላስገባህ በመተት በቤተሰብህ ላይ ጉዳት አደርሳለሁ እያለች ስታስፈራራ የነበረችን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች
ተጠርጣሪዋ አለምነሽ አጉማስ፤ ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለው ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ/ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ወሎ ሰፈር አካባቢ ከሚገኝ አንድ ፕላዛ ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በፕላዛው በጽዳት ሰራተኝነት እና በአሳንሰር ተቆጣጣሪነት ተቀጥራ የምትሰራ ሲሆን የግል ተበዳይ በዚሁ ህንጻ ላይ ከሚገኝ የአንድ የግል ድርጅት የፋይናስ ኃላፊ ናቸው።
የግል ተበዳይ አቶ ግሩም ነጋሽ ለፖሊስ በሰጡት ቃል እንዳስረዱት የኔሰው የሚባል ግለሰብ ከአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ቢኮሎ ከሚባል አካባቢ እንደሚደውል ገልጸው 3መቶ ሺ ብር በባንክ ካላስገባህ ልጅህን የሰይጣን መሳቢያ አደርጋታለሁ የሚል የማስፈራሪያ መልዕክት በማያውቁት ስልክ ተደውሎ እንደደረሳቸው ተናግረዋል።
የግል ተበዳዩ ያቀረቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እና የተደወለበትን ስልክ እንዲሁም የማስፈራሪያ መልዕክት ያስተላለፈውን ሰው ድምፅ ማንነት ለመለየት በተደረገ ጥረት ተጠርጣሪዋ የግል ተበዳይን በመከታተል ካጠናች በኋላ ማንነቷን በመደበቅ እና ድምጿን በመቀየር አስፈራርታ 25ሺ ብር በባንክ እንዲያስገቡላት ካደረገች በኋላ ቀሪ 275ሺ ብር ለማስላክ ስትሞክር የግል ተበዳይ ለፖሊስ በሰጡት መረጃና ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ምርመራ ተጠርጣሪዋ ለመላክ ካዘጋጀችው የማስፈራሪያ ጽሑፍ የእጅ ስልኳ ላይ በመገኘቱ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት መሆኑን የላንቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።
አንዳንድ ግለሰቦች ሰዎችን በማጥናትና በባዕድ አምልኮ በማስፈራራት በቀላሉ ለመበልፀግ ጥረት እንደሚያደርጉ መገንዘብ እንደሚገባ ያሳሰበው ፖሊስ መሰል ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ነገሩን ከመደባበቅ ይልቅ በአስቸኳይ ወደ ፖሊስ በመሄድና መረጃ በመስጠት አጥፊዎች በህግ አግባብ እንዲጠየቁ ማድረግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።dagu
seledadotio
seledadotio
ተጠርጣሪዋ አለምነሽ አጉማስ፤ ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለው ህዳር 22 ቀን 2018 ዓ/ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ወሎ ሰፈር አካባቢ ከሚገኝ አንድ ፕላዛ ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በፕላዛው በጽዳት ሰራተኝነት እና በአሳንሰር ተቆጣጣሪነት ተቀጥራ የምትሰራ ሲሆን የግል ተበዳይ በዚሁ ህንጻ ላይ ከሚገኝ የአንድ የግል ድርጅት የፋይናስ ኃላፊ ናቸው።
የግል ተበዳይ አቶ ግሩም ነጋሽ ለፖሊስ በሰጡት ቃል እንዳስረዱት የኔሰው የሚባል ግለሰብ ከአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ቢኮሎ ከሚባል አካባቢ እንደሚደውል ገልጸው 3መቶ ሺ ብር በባንክ ካላስገባህ ልጅህን የሰይጣን መሳቢያ አደርጋታለሁ የሚል የማስፈራሪያ መልዕክት በማያውቁት ስልክ ተደውሎ እንደደረሳቸው ተናግረዋል።
የግል ተበዳዩ ያቀረቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ቴክኖሎጂን በመጠቀም እና የተደወለበትን ስልክ እንዲሁም የማስፈራሪያ መልዕክት ያስተላለፈውን ሰው ድምፅ ማንነት ለመለየት በተደረገ ጥረት ተጠርጣሪዋ የግል ተበዳይን በመከታተል ካጠናች በኋላ ማንነቷን በመደበቅ እና ድምጿን በመቀየር አስፈራርታ 25ሺ ብር በባንክ እንዲያስገቡላት ካደረገች በኋላ ቀሪ 275ሺ ብር ለማስላክ ስትሞክር የግል ተበዳይ ለፖሊስ በሰጡት መረጃና ፖሊስ ባደረገው ጠንካራ ምርመራ ተጠርጣሪዋ ለመላክ ካዘጋጀችው የማስፈራሪያ ጽሑፍ የእጅ ስልኳ ላይ በመገኘቱ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት መሆኑን የላንቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።
አንዳንድ ግለሰቦች ሰዎችን በማጥናትና በባዕድ አምልኮ በማስፈራራት በቀላሉ ለመበልፀግ ጥረት እንደሚያደርጉ መገንዘብ እንደሚገባ ያሳሰበው ፖሊስ መሰል ወንጀሎች ሲያጋጥሙ ነገሩን ከመደባበቅ ይልቅ በአስቸኳይ ወደ ፖሊስ በመሄድና መረጃ በመስጠት አጥፊዎች በህግ አግባብ እንዲጠየቁ ማድረግ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።dagu
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
6 months ago
አሸዋ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ ባደረሰዉ አደጋ የአንድ ቤተሠብ አባላት የሆኑ አራት ሕፃናት እና የአሽከርካሪው ህይወት አለፈ
የባሌ ዞን ዲንሾ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የትራፊክ ደህንነት እና ቁጥጥር አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ያሬድ ታደሰ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ከአርባ ላይ አሸዋ የጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ የአንድ ቤተሠብ አባላት አራት ሕፃናት እና አሽከርካሪው ሕይወታቸው ማለፉን ገለፁ።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ3 52420 ኢቲ የሆነ ዩዲ የጭነት ከባድ ተሽከርካሪ ከአሳሳ ከተማ አሸዋ ጭኖ ወደ ባሌ ዲንሾ ወረዳ ሀዋ ቀበሌ በተባለ ስፍራ መንገዱን ስቶ የሰው ግቢ ውስጥ በመግባት ሶስት ወንድ እና አንድ ሴት ልጅን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት የአንድ ቤተሰብ ላይ ባደረሰው አደጋ አሽከርካሪውን ጨምሮ የአምስት ሠው ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።dagu
seledadotio
seledadotio
የባሌ ዞን ዲንሾ ወረዳ ፖሊስ ፅህፈት ቤት የትራፊክ ደህንነት እና ቁጥጥር አስተባባሪ ምክትል ኢንስፔክተር ያሬድ ታደሰ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ አስራ አንድ ሰዓት ከአርባ ላይ አሸዋ የጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ የአንድ ቤተሠብ አባላት አራት ሕፃናት እና አሽከርካሪው ሕይወታቸው ማለፉን ገለፁ።
የሰሌዳ ቁጥር ኮድ3 52420 ኢቲ የሆነ ዩዲ የጭነት ከባድ ተሽከርካሪ ከአሳሳ ከተማ አሸዋ ጭኖ ወደ ባሌ ዲንሾ ወረዳ ሀዋ ቀበሌ በተባለ ስፍራ መንገዱን ስቶ የሰው ግቢ ውስጥ በመግባት ሶስት ወንድ እና አንድ ሴት ልጅን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት የአንድ ቤተሰብ ላይ ባደረሰው አደጋ አሽከርካሪውን ጨምሮ የአምስት ሠው ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።dagu
seledadotio
seledadotio
6 months ago
ናይጄሪያዊዉ ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ ከነዳጅ ተቆጣጣሪ አካል ጋር ግጭት ዉስጥ ገቡ
#ethiopia | የናይጄሪያ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት አሊኮ ዳንጎቴ እሁድ እለት ከነዳጅ ተቆጣጠሪ አካል ጋር ያለውን ውዝግብ ጋር ተባብሶ ቀጥሏል፡፡
በናይጄሪያ የሚገኙ የነዳጅ ማጣሪያዎችን አደጋ ላይ የሚጥል ርካሽ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ አድርገዋል ሲሉ ዳንጎቴ ከተቆጣጣሪዉ አካል ጋር ያላቸዉን ልዩነት ገልጸዋል፡፡ናይጄሪያ በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ዘይት አምራች ሀገር ብትሆን ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ጥገኛ ናት፡
፡ይህንኑ ችግር ለመቀየት የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ቁጥጥር ካልተደረገባቸው ለሥራ፣ ለኢንቨስትመንትና ለኢነርጂ ደህንነት ስጋት ይሆናሉ ብለዋል።
በሌጎስ በሚገኘዉ እና በቀን 650 ሺ በርሜል የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ላይ ንግግር ያደረጉት ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች “የአገር ውስጥ አቅምን ለመፈተሽ” ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው፣ ይህም ናይጄሪያ ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገዉ ሽግግር ፈተና እየሆነ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዳንጎቴ የናይጄሪያ ሚድ ስትሪም እና ዳውንስትሪም ፔትሮሊየም ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ኃላፊ ፋሩክ አህመድን በተመለከተ በዘርፉ ያላቸውን የአስተዳደር ስጋት እና የግል ወጪዎች ከህጋዊ ገቢ በላይ ናቸው በሚል ክስ ላይ ይፋዊ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
አህመድ በሚመሩት ተቋማት ላይ ለቀረበዉ አስተያየት ወዲያውኑ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀደም የዳንጎቴ ማጣሪያ በፔትሮሊየም ምርቶች ሽያጭ ላይ በብቸኝነት መያዝ እንደሚፈልግ ተናግረዉ ነበረ፡፡ የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካው ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ሊያሟላ አይችልም ሲሉ ተደምጠዋል።
#dagu
#ethiopia | የናይጄሪያ ቁጥር አንድ ባለሀብት የሆኑት አሊኮ ዳንጎቴ እሁድ እለት ከነዳጅ ተቆጣጠሪ አካል ጋር ያለውን ውዝግብ ጋር ተባብሶ ቀጥሏል፡፡
በናይጄሪያ የሚገኙ የነዳጅ ማጣሪያዎችን አደጋ ላይ የሚጥል ርካሽ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ አድርገዋል ሲሉ ዳንጎቴ ከተቆጣጣሪዉ አካል ጋር ያላቸዉን ልዩነት ገልጸዋል፡፡ናይጄሪያ በአፍሪካ ትልቁ የነዳጅ ዘይት አምራች ሀገር ብትሆን ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ጥገኛ ናት፡
፡ይህንኑ ችግር ለመቀየት የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ቁጥጥር ካልተደረገባቸው ለሥራ፣ ለኢንቨስትመንትና ለኢነርጂ ደህንነት ስጋት ይሆናሉ ብለዋል።
በሌጎስ በሚገኘዉ እና በቀን 650 ሺ በርሜል የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ ላይ ንግግር ያደረጉት ዳንጎቴ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች “የአገር ውስጥ አቅምን ለመፈተሽ” ጥቅም ላይ እየዋሉ ነው፣ ይህም ናይጄሪያ ወደ ኢንዱስትሪ ለምታደርገዉ ሽግግር ፈተና እየሆነ ይገኛል ብለዋል፡፡
ዳንጎቴ የናይጄሪያ ሚድ ስትሪም እና ዳውንስትሪም ፔትሮሊየም ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ኃላፊ ፋሩክ አህመድን በተመለከተ በዘርፉ ያላቸውን የአስተዳደር ስጋት እና የግል ወጪዎች ከህጋዊ ገቢ በላይ ናቸው በሚል ክስ ላይ ይፋዊ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቀዋል።
አህመድ በሚመሩት ተቋማት ላይ ለቀረበዉ አስተያየት ወዲያውኑ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀደም የዳንጎቴ ማጣሪያ በፔትሮሊየም ምርቶች ሽያጭ ላይ በብቸኝነት መያዝ እንደሚፈልግ ተናግረዉ ነበረ፡፡ የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካው ምርት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ሊያሟላ አይችልም ሲሉ ተደምጠዋል።
#dagu
6 months ago
ሚያሚ በሦስት አስርት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ዲሞክራት ከንቲባ መረጠች
#ethiopia | ዴሞክራቷ ኢሊን ሂጊንስ ለሚያሚ ከንቲባ ሆና ስትመረጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በኋላ የዲሞክራት ፓርቲ የመጀመሪያ አባል ሆናለች።
የትራምፕ ጠንካራ ድጋፍ ባለባት ፍሎሪዳ እንዲሁም የሂስፓኒክ ነዋሪዎች በሚበዙባት ከተማ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሚደገፉትን ሪፐብሊካን አሸንፋለች።
ሲ ኤን ኤን እና አሶሺየትድ ፕሬስ ምርጫው ከተጠናቀቀ ከአንድ ሰአት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሂጊንስ ማሸነፏን ዘግበዋል።
የቀድሞዋ ሚያሚ-ዴድ ካውንቲ ኮሚሽነር የሪፐብሊካን ተቀናቃኛቸውን ኤሚሊዮ ጎንዛሌዝን በ18 በመቶ ብልጫ አዲሷ ከንቲባ አግኝታለች።
ይህ ውጤይ በ2026 የአጋማሽ ዘመን ምርጫዎች በኮንግረሱ ውስጥ የትራምፕን ብቸኛ የበላይነት ለማስጠበቅ ሪፓብሊካን ያላቸውን ተስፋ አደብዟል።
የሂጊንስ ወሳኝ ድል ዲሞክራቶች ባለፈው ወር በምርጫ ካሳኩት ድል ቀጥሎ በፍጥነት የመጣ ስኬት ነው።
እ.ኤ.አ. በ 2024 ትራምፕ ከዴሞክራቶች የነጠቁት የሂስፓኒክ ድጋፍ ከዚያን ጊዜ ወዲህ እየከሰመ ስለመሆኑ ሪፓብሊካኑ ያላቸውን ስጋት ያጠነክራል።
የ61 ዓመቷ ሂጊንስ በፌስ ቡክ አካውንቷ ላይ ባጋራችው መግለጫ የድሏን ሀገራዊ እንድምታ አልተናገረችም ይልቁንም ውጤቱን በአገር ውስጥ ደረጃ "የአመታት ትርምስ እና ሙስና ላይ አዲስ ምዕራፍ " ነው በማለት ገልጻለች። #dagu
#ethiopia | ዴሞክራቷ ኢሊን ሂጊንስ ለሚያሚ ከንቲባ ሆና ስትመረጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በኋላ የዲሞክራት ፓርቲ የመጀመሪያ አባል ሆናለች።
የትራምፕ ጠንካራ ድጋፍ ባለባት ፍሎሪዳ እንዲሁም የሂስፓኒክ ነዋሪዎች በሚበዙባት ከተማ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሚደገፉትን ሪፐብሊካን አሸንፋለች።
ሲ ኤን ኤን እና አሶሺየትድ ፕሬስ ምርጫው ከተጠናቀቀ ከአንድ ሰአት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ሂጊንስ ማሸነፏን ዘግበዋል።
የቀድሞዋ ሚያሚ-ዴድ ካውንቲ ኮሚሽነር የሪፐብሊካን ተቀናቃኛቸውን ኤሚሊዮ ጎንዛሌዝን በ18 በመቶ ብልጫ አዲሷ ከንቲባ አግኝታለች።
ይህ ውጤይ በ2026 የአጋማሽ ዘመን ምርጫዎች በኮንግረሱ ውስጥ የትራምፕን ብቸኛ የበላይነት ለማስጠበቅ ሪፓብሊካን ያላቸውን ተስፋ አደብዟል።
የሂጊንስ ወሳኝ ድል ዲሞክራቶች ባለፈው ወር በምርጫ ካሳኩት ድል ቀጥሎ በፍጥነት የመጣ ስኬት ነው።
እ.ኤ.አ. በ 2024 ትራምፕ ከዴሞክራቶች የነጠቁት የሂስፓኒክ ድጋፍ ከዚያን ጊዜ ወዲህ እየከሰመ ስለመሆኑ ሪፓብሊካኑ ያላቸውን ስጋት ያጠነክራል።
የ61 ዓመቷ ሂጊንስ በፌስ ቡክ አካውንቷ ላይ ባጋራችው መግለጫ የድሏን ሀገራዊ እንድምታ አልተናገረችም ይልቁንም ውጤቱን በአገር ውስጥ ደረጃ "የአመታት ትርምስ እና ሙስና ላይ አዲስ ምዕራፍ " ነው በማለት ገልጻለች። #dagu
6 months ago
በጋምቤላ ክልል የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት መቀነሱ ተነገረ
#ethiopia | በጋምቤላ ክልል የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት ቀደም ካሉት ጊዜያት አንፃር አሁን ላይ መቀነሱን የክልሉ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት አስታውቋል።በጽህፈት ቤቱ የዘርፈ ብዙ ምላሽ የኤች አይ ቪ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አቡላ ድንጉር ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም በክልሉ የነበረው የቫይረሱ ስርጭት ምጣኔ በከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኝ ነበር።
ከፍተኛ የቫይረስ ስርጭትን በማስመዝገብ ክልሉ ቀዳሚ እንደነበር ገልፀው ከሁለት አመታት ወዲህ ግን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ እንደቻለ አስረድተዋል።
ስርጭቱ እ.አ.አ በ2023 ላይ ከነበረበት 3 ነጥብ 14 በመቶ ባለፈዉ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ባደረገው የዳሰሳ ጥናት መሰረት ወደ 3ነጥብ 09 በመቶ መቀነሱ ተረጋግጧል።
የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ ልዮ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱ፣ የቫይረሱን ስርጭት በመግታት በኩል የአጋር አካላት ድጋፍ መኖር እንዲሁም ለማህበረሰቡ የግንዛቤ መፍጠር ስራዎች መሰራታቸው ለዚህ ውጤት አስተዋፅኦ አበርክቷል።
አሁን ላይ በክልሉ ያለው የበሽታው ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ ቢያሳይም በሚፈለገው ልክ መሻሻሎች አላሳየም። በክልሉ የኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት አምራች ኃይል በሆኑት ወጣቶች ላይ እያስከተለ ያለው ጉዳት አሁንም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
#dagu
#ethiopia | በጋምቤላ ክልል የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት ቀደም ካሉት ጊዜያት አንፃር አሁን ላይ መቀነሱን የክልሉ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽህፈት አስታውቋል።በጽህፈት ቤቱ የዘርፈ ብዙ ምላሽ የኤች አይ ቪ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አቡላ ድንጉር ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም በክልሉ የነበረው የቫይረሱ ስርጭት ምጣኔ በከፍተኛ ደረጃ ላይ ይገኝ ነበር።
ከፍተኛ የቫይረስ ስርጭትን በማስመዝገብ ክልሉ ቀዳሚ እንደነበር ገልፀው ከሁለት አመታት ወዲህ ግን ከአዲስ አበባ በመቀጠል በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ እንደቻለ አስረድተዋል።
ስርጭቱ እ.አ.አ በ2023 ላይ ከነበረበት 3 ነጥብ 14 በመቶ ባለፈዉ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዮት ባደረገው የዳሰሳ ጥናት መሰረት ወደ 3ነጥብ 09 በመቶ መቀነሱ ተረጋግጧል።
የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ ልዮ ትኩረት ሰጥቶ መስራቱ፣ የቫይረሱን ስርጭት በመግታት በኩል የአጋር አካላት ድጋፍ መኖር እንዲሁም ለማህበረሰቡ የግንዛቤ መፍጠር ስራዎች መሰራታቸው ለዚህ ውጤት አስተዋፅኦ አበርክቷል።
አሁን ላይ በክልሉ ያለው የበሽታው ስርጭት የመቀነስ አዝማሚያ ቢያሳይም በሚፈለገው ልክ መሻሻሎች አላሳየም። በክልሉ የኤችአይቪ ኤድስ ቫይረስ ስርጭት አምራች ኃይል በሆኑት ወጣቶች ላይ እያስከተለ ያለው ጉዳት አሁንም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
#dagu
Sponsored by
Surafel
6 months ago
በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን መካከል የድንበር ጦርነት ተቀሰቀሰ
#ethiopia | በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን ታሊባን ሃይሎች መካከል የድንበር ግጭት እንደገና ተቀስቅሷል ፣እያንዳንዱ ወገን ሌላኛውን አካል ደካማ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነቱን አፍርሷል በሚል እየተካሰሱ ይገኛሉ።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው 2,600 ኪሜ ድንበር ላይ የምትገኘውን የአፍጋኒስታን ከተማ ስፒን ቦልዳክን ነዋሪዎች ጥቃትን ፈርተው ተሰደዋል።
በአቅራቢያው በምትገኘው የካንዳሃር ከተማ የህክምና ሰራተኛ ለቢቢሲ ፓሽቶ አገልግሎት እንደተናገሩት አራት አስከሬኖች በአካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል ገብተዋል። ሌሎች አራት ሰዎች ቆስለዋል። በፓኪስታን በኩል ደግሞ 3 ሰዎች ቆስለዋል ተብሏል።
ባለፉት ወራት በሁለቱ ሀገራት መካከል አልፎ አልፎ ጦርነት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፥ የአፍጋኒስታኑ የታሊባን መንግስት ፓኪስታን በሀገሪቱ ውስጥ የአየር ድብደባ ትፈጽማለች ሲል ከሷል።
ሁለቱም ወገኖች የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ቢያረጋግጡም ለአራት ሰአታት የፈጀውን ጦርነት በተመለከተ አንዳው ሌላኛውን ለጥቃቱ ወቅሰዋል።
የፓኪስታን ጠቅላይ ሚንስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ቃል አቀባይ ሞሻራፍ ዛዲ ታሊባንን “ያለምክንያት ተኩስ ከፍቷል” ሲሉ ከሰዋል። ይህንኑ ተከትሎ “አፋጣኝ፣ ተገቢ እና ጠንከር ያለ ምላሽ በታጣቂ ሃይሎቻችን ተሰጥቷል ብለዋል። ፓኪስታን ግዛቷን እና የዜጎቻችንን ደህንነት ለማረጋገጥ ቁርጠኛ ነች ሲሉ አክለዋል።#dagu
#ethiopia | በፓኪስታን እና በአፍጋኒስታን ታሊባን ሃይሎች መካከል የድንበር ግጭት እንደገና ተቀስቅሷል ፣እያንዳንዱ ወገን ሌላኛውን አካል ደካማ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነቱን አፍርሷል በሚል እየተካሰሱ ይገኛሉ።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው 2,600 ኪሜ ድንበር ላይ የምትገኘውን የአፍጋኒስታን ከተማ ስፒን ቦልዳክን ነዋሪዎች ጥቃትን ፈርተው ተሰደዋል።
በአቅራቢያው በምትገኘው የካንዳሃር ከተማ የህክምና ሰራተኛ ለቢቢሲ ፓሽቶ አገልግሎት እንደተናገሩት አራት አስከሬኖች በአካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል ገብተዋል። ሌሎች አራት ሰዎች ቆስለዋል። በፓኪስታን በኩል ደግሞ 3 ሰዎች ቆስለዋል ተብሏል።
ባለፉት ወራት በሁለቱ ሀገራት መካከል አልፎ አልፎ ጦርነት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፥ የአፍጋኒስታኑ የታሊባን መንግስት ፓኪስታን በሀገሪቱ ውስጥ የአየር ድብደባ ትፈጽማለች ሲል ከሷል።
ሁለቱም ወገኖች የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ቢያረጋግጡም ለአራት ሰአታት የፈጀውን ጦርነት በተመለከተ አንዳው ሌላኛውን ለጥቃቱ ወቅሰዋል።
የፓኪስታን ጠቅላይ ሚንስትር ሸህባዝ ሻሪፍ ቃል አቀባይ ሞሻራፍ ዛዲ ታሊባንን “ያለምክንያት ተኩስ ከፍቷል” ሲሉ ከሰዋል። ይህንኑ ተከትሎ “አፋጣኝ፣ ተገቢ እና ጠንከር ያለ ምላሽ በታጣቂ ሃይሎቻችን ተሰጥቷል ብለዋል። ፓኪስታን ግዛቷን እና የዜጎቻችንን ደህንነት ለማረጋገጥ ቁርጠኛ ነች ሲሉ አክለዋል።#dagu
7 months ago
የአራት ወር ህፃን ላይ የፈላ ውሃ በመድፋት ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረገችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን በካራት ከተማ ሚሊኒየም ሰፈር በአቶ ኩሲያ ካላሌ መኖርያ ቤት ግቢ ውስጥ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
ሊባን ኤርሚያስ የተባለች የ4 ወር ዕድሜ ያላት ህፃን በእናቷ ወይዘሮ ካይሎቴ አማሬ ታቅፋ እያለ ተከሳሽ የፈላ ውሃ በብረት ድስት በማድረግ እናት በታቀፈቻት ልጅ ፣በእናትየው እና በሌላ በ3 ዓመት ከ5 ወር ልጅ ላይ በመድፋት ጉዳት ማድረሷ ተገልፆል፡
በዚህም የአራት ወር እድሜ ያለት ህፃን ወዲያኑ ህይወቷ ሲያልፍ የ3 ዓመት ከ5 ወር ህፃን እና ወላጅ እናት በህክምና ህይዉታቸው ማትረፍ ተችሏል ሲሉ በኮንሶ ዞን የቀና ወረዳ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገመቹ ገለገሎ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በዚህም ፖሊስ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል በወንጀለኛ ህግ አንቀጽ 27/1 58/1/ሀ እና 539/1 ጠቅሶ ክስ መሰርቷል፡፡ተከሳሽ የወንጀሉን ድርጊት አምና ተበዳይ ስለምትሰድባትና ስለምታንቋሽሻት ወንጀሉን የፈፀመች መሆኗን ገልፃ ችሎቱም የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ከሰማ በኋላ በክስ አንድ በወንጀል ህግ አንቀጽ 58/1/ለ እና 540 ስር እና በክስ 2 እና 3 በወንጄል ህግ አንቀጽ 58/1/ለ እና 555/ሀ እንድትከላከል ብይን ሰጥቷል።
ተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ እንደሌላት ለችሎት የገለፀች በመሆኑ ችሎቱም እንዲትከላከል ብይን በሰጠበት የህግ አንቀጽ ስር ጥፋተኛ በማድረግ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን በኮንሶ ዞን የቀና ወረዳ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገመቹ ገለገሎ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡#dagu
seledadotio
seledadotio
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ዞን በካራት ከተማ ሚሊኒየም ሰፈር በአቶ ኩሲያ ካላሌ መኖርያ ቤት ግቢ ውስጥ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
ሊባን ኤርሚያስ የተባለች የ4 ወር ዕድሜ ያላት ህፃን በእናቷ ወይዘሮ ካይሎቴ አማሬ ታቅፋ እያለ ተከሳሽ የፈላ ውሃ በብረት ድስት በማድረግ እናት በታቀፈቻት ልጅ ፣በእናትየው እና በሌላ በ3 ዓመት ከ5 ወር ልጅ ላይ በመድፋት ጉዳት ማድረሷ ተገልፆል፡
በዚህም የአራት ወር እድሜ ያለት ህፃን ወዲያኑ ህይወቷ ሲያልፍ የ3 ዓመት ከ5 ወር ህፃን እና ወላጅ እናት በህክምና ህይዉታቸው ማትረፍ ተችሏል ሲሉ በኮንሶ ዞን የቀና ወረዳ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገመቹ ገለገሎ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
በዚህም ፖሊስ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር በማዋል በወንጀለኛ ህግ አንቀጽ 27/1 58/1/ሀ እና 539/1 ጠቅሶ ክስ መሰርቷል፡፡ተከሳሽ የወንጀሉን ድርጊት አምና ተበዳይ ስለምትሰድባትና ስለምታንቋሽሻት ወንጀሉን የፈፀመች መሆኗን ገልፃ ችሎቱም የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ከሰማ በኋላ በክስ አንድ በወንጀል ህግ አንቀጽ 58/1/ለ እና 540 ስር እና በክስ 2 እና 3 በወንጄል ህግ አንቀጽ 58/1/ለ እና 555/ሀ እንድትከላከል ብይን ሰጥቷል።
ተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ እንደሌላት ለችሎት የገለፀች በመሆኑ ችሎቱም እንዲትከላከል ብይን በሰጠበት የህግ አንቀጽ ስር ጥፋተኛ በማድረግ በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን በኮንሶ ዞን የቀና ወረዳ ፍትህ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ገመቹ ገለገሎ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡#dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago
የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ዓብይ ጉባኤ ለ117 ዳኞች ሹመት ለክልሉ ምክር ቤት ኡቀረበ
👉 የሁለት ዳኞች ያለመከሰስ ከለላ ተነስቷል
#ethiopia | የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ዐቢይ ጉባኤ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔ መስጠቱ ተገልጿል። በዚህም 169 የወረዳ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች እና 5 የአዲስ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች በድምሩ የ174 ዳኞች ሹመት ለክልሉ ምክር ቤት እንዲቀርብ መወሰኑ ተገልጿል፡፡
አራት የከፍተኛ ፍርድ ቤት ሸሪዓ ዳኞች እና 25 የወረዳ ፍርድ ቤት ሸሪዓ ዳኞች ሹመት ሰጥቷል። እንዲሁም የጠቅላይ ፍርድ ቤት ደሴ እና ጎንደር ምድብ ችሎት አስተባባሪዎች ከኃላፊነት እንዲነሱ ወስኗል።
የአንድ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የተጠረጠሩበትን ሃሰተኛ ሰነድ እና የአንድ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የተጠረጠሩበትን የአካል ጉዳት ማድረስ እና ዛቻ ወንጀል መነሻ በማድረግ ከተወያየ በኋላ ያለመከሰስ ከለላቸዉን ማንሳቱ ተገልጿል።
እንዲሁም የፀባይ እና የስነስርዐት ጉዳዮችን መርምሮ ሁለት የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች ከኃላፊነት እንዲነሱና ውሳኔው በክልሉ ምክር ቤት እንዲጸድቅ የውሳኔ ሀሳብ መስጠቱ ተገልጿል፡፡
እንዲሁም በሌሎች የዲሲፕሊን ጉዳዮች ላይ መክሮ የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ሌሎች የቅሬታ ይግባኞችን መርምሮ ውሳኔ የሰጠ ሲሆን ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልጋቸው የዲሲፒሊን ጉዳዮች በቀጣይ ጉባኤ ተጣርተው እንዲቀርቡ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
በተጨማሪም የቀረበለትን የዝውውር መረጃ መርምሮ ለኅብረተሰቡ የተሻለ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ሲባል በጥናት ላይ የተመሰረተ የመመሪያ ማሻሻያ ተደርጎ እስኪተገበር ድረስ መደበኛ ዝውውር ለጊዜዉ ታግዶ እንዲቆይ እና በሚወጣው መመሪያ መሰረት ውድድር ተደርጎ እንዲተገበር ሆኖም እንደአስፈላጊነቱ በልዩ ዝውውር የሚቀርቡ የዝውውር ጥያቄዎች እንዲስተናገዱ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡#dagu
👉 የሁለት ዳኞች ያለመከሰስ ከለላ ተነስቷል
#ethiopia | የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ዐቢይ ጉባኤ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔ መስጠቱ ተገልጿል። በዚህም 169 የወረዳ ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች እና 5 የአዲስ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች በድምሩ የ174 ዳኞች ሹመት ለክልሉ ምክር ቤት እንዲቀርብ መወሰኑ ተገልጿል፡፡
አራት የከፍተኛ ፍርድ ቤት ሸሪዓ ዳኞች እና 25 የወረዳ ፍርድ ቤት ሸሪዓ ዳኞች ሹመት ሰጥቷል። እንዲሁም የጠቅላይ ፍርድ ቤት ደሴ እና ጎንደር ምድብ ችሎት አስተባባሪዎች ከኃላፊነት እንዲነሱ ወስኗል።
የአንድ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የተጠረጠሩበትን ሃሰተኛ ሰነድ እና የአንድ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የተጠረጠሩበትን የአካል ጉዳት ማድረስ እና ዛቻ ወንጀል መነሻ በማድረግ ከተወያየ በኋላ ያለመከሰስ ከለላቸዉን ማንሳቱ ተገልጿል።
እንዲሁም የፀባይ እና የስነስርዐት ጉዳዮችን መርምሮ ሁለት የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች ከኃላፊነት እንዲነሱና ውሳኔው በክልሉ ምክር ቤት እንዲጸድቅ የውሳኔ ሀሳብ መስጠቱ ተገልጿል፡፡
እንዲሁም በሌሎች የዲሲፕሊን ጉዳዮች ላይ መክሮ የገንዘብ ቅጣት ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ሌሎች የቅሬታ ይግባኞችን መርምሮ ውሳኔ የሰጠ ሲሆን ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልጋቸው የዲሲፒሊን ጉዳዮች በቀጣይ ጉባኤ ተጣርተው እንዲቀርቡ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
በተጨማሪም የቀረበለትን የዝውውር መረጃ መርምሮ ለኅብረተሰቡ የተሻለ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ሲባል በጥናት ላይ የተመሰረተ የመመሪያ ማሻሻያ ተደርጎ እስኪተገበር ድረስ መደበኛ ዝውውር ለጊዜዉ ታግዶ እንዲቆይ እና በሚወጣው መመሪያ መሰረት ውድድር ተደርጎ እንዲተገበር ሆኖም እንደአስፈላጊነቱ በልዩ ዝውውር የሚቀርቡ የዝውውር ጥያቄዎች እንዲስተናገዱ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡#dagu
7 months ago
ለኩላሊት እጥበት ህክምና አገልግሎት የጤና መድህን ሽፋን አይሰጥም ተባለ
👉 በኢትዮጵያ 84 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና ተጠቃሚ ሆኗል
በተለያዩ አጋጣሚዎች ለውጪ ሀገር ህክምና ፤በስራ ተቋማት ውስጥ ለሚያጋጥሙ አደጋዎች ፤ሶስተኛ ወገን ሽፋን ያላቸው ፤ ለኩላሊት እጥበት ታካሚዎች እና ለውበት መጠበቂያ ለሚወጡ ህክምናዎች በጤና መድህን ሽፋን ማግኘት እንደማይቻል የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት አስታውቋል ፡፡
የጤና እክል አጋጥሞት ወደ ውጪ ሀገር ሄዶ እንዲታከም ለሚደረግ ታካሚ በጤና መድህን የተሰበሰበውን ገንዘብ አንድ ሰው ላይ ማዋል እንደሆነ እና ፍትሀዊ አገልግሎት አሰጣጥ እንደማይሆን ለብስራት ሬዲዮ የተናገሩት በኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳምጠው ጥላሁን ናቸው፡፡እንዲሁም ለኩላሊት ህመምተኞች ለሚደረግ የእጥበት አገልግሎት ላይም የጤና አገልግሎት የጤና መድህን ሽፋን መስጠት አስቸ ጋሪ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ከእነዚህ ህክምናዎች ውጪ ግን ምንም አይነት የገንዘብ ገደብ ሳይደረግ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች የህክምና አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ 84 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የማህበረሰብ አቀፍ ተጠቃሚ ሆኗል፡፡የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት በ1ሺ195 ወረዳዎች ስር ከ4ሺ347 ጤና ተቋማት ጋር ውል በማሰር የጤና ተቋማቱ ለማህበራዊ ጤና መድህን ተጠቃሚዎች የዱቤ አገልግሎት እንዲሰጡ ያደርጋል፡፡ በመጨረሻም ኦዲት ተደርጎ ለጤና ተቋማቱ ክፍያው እንደሚፈፀምላቸው ገልፀዋል ፡፡በ2018 ዓ.ም ደግሞ የወረዳ ሽፋኑን አሳድጎ ለ1ሺ320 ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ማቀዱን በኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዳምጠው ጥላሁን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
Dagu
seledadotio
seledadotio
👉 በኢትዮጵያ 84 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና ተጠቃሚ ሆኗል
በተለያዩ አጋጣሚዎች ለውጪ ሀገር ህክምና ፤በስራ ተቋማት ውስጥ ለሚያጋጥሙ አደጋዎች ፤ሶስተኛ ወገን ሽፋን ያላቸው ፤ ለኩላሊት እጥበት ታካሚዎች እና ለውበት መጠበቂያ ለሚወጡ ህክምናዎች በጤና መድህን ሽፋን ማግኘት እንደማይቻል የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት አስታውቋል ፡፡
የጤና እክል አጋጥሞት ወደ ውጪ ሀገር ሄዶ እንዲታከም ለሚደረግ ታካሚ በጤና መድህን የተሰበሰበውን ገንዘብ አንድ ሰው ላይ ማዋል እንደሆነ እና ፍትሀዊ አገልግሎት አሰጣጥ እንደማይሆን ለብስራት ሬዲዮ የተናገሩት በኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ዳምጠው ጥላሁን ናቸው፡፡እንዲሁም ለኩላሊት ህመምተኞች ለሚደረግ የእጥበት አገልግሎት ላይም የጤና አገልግሎት የጤና መድህን ሽፋን መስጠት አስቸ ጋሪ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ከእነዚህ ህክምናዎች ውጪ ግን ምንም አይነት የገንዘብ ገደብ ሳይደረግ የጤና መድህን ተጠቃሚዎች የህክምና አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ 84 በመቶ የሚሆነው ህዝብ የማህበረሰብ አቀፍ ተጠቃሚ ሆኗል፡፡የኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት በ1ሺ195 ወረዳዎች ስር ከ4ሺ347 ጤና ተቋማት ጋር ውል በማሰር የጤና ተቋማቱ ለማህበራዊ ጤና መድህን ተጠቃሚዎች የዱቤ አገልግሎት እንዲሰጡ ያደርጋል፡፡ በመጨረሻም ኦዲት ተደርጎ ለጤና ተቋማቱ ክፍያው እንደሚፈፀምላቸው ገልፀዋል ፡፡በ2018 ዓ.ም ደግሞ የወረዳ ሽፋኑን አሳድጎ ለ1ሺ320 ወረዳ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ማቀዱን በኢትዮጵያ የጤና መድህን አገልግሎት የዋና ዳይሬክተር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዳምጠው ጥላሁን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
Dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago
በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን ልጆች አባታችን በህይወት ይኑር ይሙት አናዉቅም አሉ
#ethiopia | በፓኪስታን በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን ልጆች ከሶስት ሳምንታት በላይ በህይወት ስለመኖራቸዉ ምንም ማስረጃ እንዳላገኙ ባለስልጣናቱ ስለሁኔታው እየደበቁ ነው ብለው እንደሚፈሩ ተናግረዋል፡፡
በፍርድ ቤት የተፈቀደ የእስር ቤት ጉብኝቶች ሲታገዱ እና የእስር ቤት ዝውውሮች ሊደረጉ ይችላሉ በሚል ዉዝግብ ዉስጥ መግባታቸዉን ገልጸዋል፡፡
የኢምራሃን ካን ልጅ ቃሲም ካን ለሮይተርስ እንደተናገረው ለሳምንታዊ መገናኘትን የፍርድ ትእዛዝ ቢሰጥም ቤተሰቡ ከካን ጋር ቀጥተኛ ወይም የተረጋገጠ ግንኙነት አልነበረውም ብሏል።
አባቴ ደህና ይሁን ቆስሎ ወይም በህይወት እንዳለ አለማወቅ የስነ ልቦና ጉዳት ነው" ሲል በማከል ለሁለት ወራት ያህል የተረጋገጠ ግንኙነት አልነበረንም ሲል ተናግሯል።
ዛሬ ስለ ህመሙ ምንም የተረጋገጠ መረጃ የለንም። ትልቁ ፍርሃታችን የማይቀለበስ ነገር እየተደበቀብን መሆኑን ነው።ቤተሰቡ ከአንድ አመት በላይ የካን የግል ሀኪም እንዲገናኙ ደጋግሞ ጠይቋል ሲሉ አክለዋል።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተያየት እንዲሰጥ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የእስር ቤቱ ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደተናገሩት ካን በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዉ ወደ ከፍተኛ የጸጥታ ተቋም ለማዘዋወር ምንም አይነት እቅድ እንደሌለ ገልጸዋል። #dagu
#ethiopia | በፓኪስታን በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኢምራን ካን ልጆች ከሶስት ሳምንታት በላይ በህይወት ስለመኖራቸዉ ምንም ማስረጃ እንዳላገኙ ባለስልጣናቱ ስለሁኔታው እየደበቁ ነው ብለው እንደሚፈሩ ተናግረዋል፡፡
በፍርድ ቤት የተፈቀደ የእስር ቤት ጉብኝቶች ሲታገዱ እና የእስር ቤት ዝውውሮች ሊደረጉ ይችላሉ በሚል ዉዝግብ ዉስጥ መግባታቸዉን ገልጸዋል፡፡
የኢምራሃን ካን ልጅ ቃሲም ካን ለሮይተርስ እንደተናገረው ለሳምንታዊ መገናኘትን የፍርድ ትእዛዝ ቢሰጥም ቤተሰቡ ከካን ጋር ቀጥተኛ ወይም የተረጋገጠ ግንኙነት አልነበረውም ብሏል።
አባቴ ደህና ይሁን ቆስሎ ወይም በህይወት እንዳለ አለማወቅ የስነ ልቦና ጉዳት ነው" ሲል በማከል ለሁለት ወራት ያህል የተረጋገጠ ግንኙነት አልነበረንም ሲል ተናግሯል።
ዛሬ ስለ ህመሙ ምንም የተረጋገጠ መረጃ የለንም። ትልቁ ፍርሃታችን የማይቀለበስ ነገር እየተደበቀብን መሆኑን ነው።ቤተሰቡ ከአንድ አመት በላይ የካን የግል ሀኪም እንዲገናኙ ደጋግሞ ጠይቋል ሲሉ አክለዋል።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተያየት እንዲሰጥ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የእስር ቤቱ ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደተናገሩት ካን በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዉ ወደ ከፍተኛ የጸጥታ ተቋም ለማዘዋወር ምንም አይነት እቅድ እንደሌለ ገልጸዋል። #dagu
7 months ago
በኢንዶኔዥያ፣ ሲሪላንካና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወት አለፈ
ባለፉት ቀናት በተከሰቱት አውሎ ነፋስ በኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ እና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በአስከፊ የአየር ሁኔታ የተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እየተሰራ ይገኛል። ሰኞ እለት ወደ ሰሜን ሱማትራ ያቀኑት የኢንዶኔዥያ ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ መንግስት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ "አስፈላጊውን እርዳታ እንዴት ወዲያውኑ መላክ እንደሚቻል" ነው ብለዋል ።
“ፈጣሪ ቢፈቅድ ልንደርስባቸው የሚገቡ በርካታ ሩቅ መንደሮች አሉ” ያሉት ፕራቦዎ፣ መንግስት የእርዳታ ጥረቱን ለማገዝ ሄሊኮፕተሮችን እና አውሮፕላኖችን እያሰማራ መሆኑን ተናግረዋል።ፕራቦዎ ቢያንስ በኢንዶኔዥያ 442 ሰዎችን ለገደለው እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የደረሱበት አልታወቀም ለተባለዉ ከባድ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ምላሽ ብሄራዊ ድንገተኛ ሁኔታ አዋጅ እንዲያውጁ ከፍተኛ ጫና በአስተዳደራቸዉ ላይ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከስሪላንካ አቻቸው አኑራ ኩማራ ዲሳናያኬ በተለየ መልኩ ፕራቦዎ እስካሁን ድረስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እርዳታ እንዲሰጣቸዉ በይፋ ከመጠየቅ ተቆጥበዋል።የኢንዶኔዥያ መንግስት ሁለት የሆስፒታል መርከቦችን እና ሶስት የጦር መርከቦችን እርዳታ የጫኑ ድጋፎችን በጣም አስከፊ ወደሆኑ አካባቢዎች ልኳል፡፡የስሪላንካ መንግስት አለም አቀፍ ዕርዳታን በመጠየቅ በአደጋዉ ለታገቱ ሰዎች ወታደራዊ ሄሊኮፕተሮችን እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ቢያንስ 334 ሰዎች መሞታቸውን የሲሪላንካ የአደጋ ኤጀንሲ ያስታወቀ ሲሆን በርካቶች አሁንም ጠፍተዋል።
የታይላንድ ባለስልጣናት በበኩላቸዉ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በቀጠለው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 176 ደርሷል ብለዋል።መንግስት የእርዳታ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ቢገልጽም በጎርፉ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ህዝባዊ ትችት እየጨመረ ይገኛል፡፡ ሁለት የአካባቢው ባለስልጣናት በደካማ ምላሽ አሰጣጣቸዉ የተነሳ ከስራ ታግደዋል ሲል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
ባለፉት ቀናት በተከሰቱት አውሎ ነፋስ በኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ እና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በአስከፊ የአየር ሁኔታ የተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እየተሰራ ይገኛል። ሰኞ እለት ወደ ሰሜን ሱማትራ ያቀኑት የኢንዶኔዥያ ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ መንግስት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ "አስፈላጊውን እርዳታ እንዴት ወዲያውኑ መላክ እንደሚቻል" ነው ብለዋል ።
“ፈጣሪ ቢፈቅድ ልንደርስባቸው የሚገቡ በርካታ ሩቅ መንደሮች አሉ” ያሉት ፕራቦዎ፣ መንግስት የእርዳታ ጥረቱን ለማገዝ ሄሊኮፕተሮችን እና አውሮፕላኖችን እያሰማራ መሆኑን ተናግረዋል።ፕራቦዎ ቢያንስ በኢንዶኔዥያ 442 ሰዎችን ለገደለው እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የደረሱበት አልታወቀም ለተባለዉ ከባድ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ምላሽ ብሄራዊ ድንገተኛ ሁኔታ አዋጅ እንዲያውጁ ከፍተኛ ጫና በአስተዳደራቸዉ ላይ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከስሪላንካ አቻቸው አኑራ ኩማራ ዲሳናያኬ በተለየ መልኩ ፕራቦዎ እስካሁን ድረስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እርዳታ እንዲሰጣቸዉ በይፋ ከመጠየቅ ተቆጥበዋል።የኢንዶኔዥያ መንግስት ሁለት የሆስፒታል መርከቦችን እና ሶስት የጦር መርከቦችን እርዳታ የጫኑ ድጋፎችን በጣም አስከፊ ወደሆኑ አካባቢዎች ልኳል፡፡የስሪላንካ መንግስት አለም አቀፍ ዕርዳታን በመጠየቅ በአደጋዉ ለታገቱ ሰዎች ወታደራዊ ሄሊኮፕተሮችን እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ቢያንስ 334 ሰዎች መሞታቸውን የሲሪላንካ የአደጋ ኤጀንሲ ያስታወቀ ሲሆን በርካቶች አሁንም ጠፍተዋል።
የታይላንድ ባለስልጣናት በበኩላቸዉ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በቀጠለው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 176 ደርሷል ብለዋል።መንግስት የእርዳታ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ቢገልጽም በጎርፉ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ህዝባዊ ትችት እየጨመረ ይገኛል፡፡ ሁለት የአካባቢው ባለስልጣናት በደካማ ምላሽ አሰጣጣቸዉ የተነሳ ከስራ ታግደዋል ሲል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
7 months ago
በሰሜን ኢራቅ የሚገኘው የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ ስፍራ በድሮን ጥቃት ተመታ
በኢራቅ ኮሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ ስፍራ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ተቋሙ ሥራውን እንዲያቆም አስገድዶታል፣ በሰሜናዊ ኢራቅ የኩርዲሽ ክልል አብዛኛው ኃይል እንዲቋረጥ አድርጓል ሲሉ የአካባቢዉ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው እሮብ ምሽት ላይ መሆኑን የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። በርካታ የጋዝ ማከማቻ በመመታቱ ፍንዳታ እና ከፍተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱን ኤጀንሲው ገልጿል።
በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።የኢራቅ ማእከላዊ ወታደራዊ አዛዥ የጋራ ዘመቻ ኮማንድ እንደገለፀው የጥቃቱ ትኩረት የክልሉን "ደህንነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት" ማስተጓጎል ይመስላል ብሏል።እንደየአካባቢው ባለስልጣናት ገለጻ፣ 8 በመቶው የክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍርግርግ ተጎድቷል፣ በዚህም የተነሳ ከፊል ራስ ገዝ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ አስከትሏል።
ክሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ኩባንያ ዳና ጋዝ የሚተዳደር ሲሆን በሰሜን ኢራቅ ውስጥ በኪርኩክ እና በሱሌማንያ ከተሞች መካከል ይገኛል።መሐንዲሶች የነዳጅ መሰረተ ልማቱን ለመጠገን ከሁለት እስከ ሶስት ቀናት እንደሚፈጅ ተናግረዋል፡፡ የኢራቅ መንግስት እና ዳና ጋዝ ደግሞ አደጋውን ለማጣራት አጣሪ ቡድኖችን ወደ ስፍራዉ ልከዋል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
በኢራቅ ኮሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ ስፍራ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ተቋሙ ሥራውን እንዲያቆም አስገድዶታል፣ በሰሜናዊ ኢራቅ የኩርዲሽ ክልል አብዛኛው ኃይል እንዲቋረጥ አድርጓል ሲሉ የአካባቢዉ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው እሮብ ምሽት ላይ መሆኑን የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። በርካታ የጋዝ ማከማቻ በመመታቱ ፍንዳታ እና ከፍተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱን ኤጀንሲው ገልጿል።
በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።የኢራቅ ማእከላዊ ወታደራዊ አዛዥ የጋራ ዘመቻ ኮማንድ እንደገለፀው የጥቃቱ ትኩረት የክልሉን "ደህንነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት" ማስተጓጎል ይመስላል ብሏል።እንደየአካባቢው ባለስልጣናት ገለጻ፣ 8 በመቶው የክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍርግርግ ተጎድቷል፣ በዚህም የተነሳ ከፊል ራስ ገዝ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ አስከትሏል።
ክሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ኩባንያ ዳና ጋዝ የሚተዳደር ሲሆን በሰሜን ኢራቅ ውስጥ በኪርኩክ እና በሱሌማንያ ከተሞች መካከል ይገኛል።መሐንዲሶች የነዳጅ መሰረተ ልማቱን ለመጠገን ከሁለት እስከ ሶስት ቀናት እንደሚፈጅ ተናግረዋል፡፡ የኢራቅ መንግስት እና ዳና ጋዝ ደግሞ አደጋውን ለማጣራት አጣሪ ቡድኖችን ወደ ስፍራዉ ልከዋል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago
በአስር ዓመት ታዳጊ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸመው ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የአስር ዓመት ታዳጊ ናትናኤል ማይክልን በማገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ ወርቅነህ አሰፋ በሞት እንዲቀጣ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወስኗል።
ተከሳሹ የቀድሞ የመምህርነት ሥራውን ተጠቅሞ ታዳጊውን ናትናኤል ማይክልን ከትምህርት ቤት ሲመለስ ጠልፎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ወሰዷል።
ተከሳሹ ልጁን በቦክስ ከመምታት በኋላ በአፍና አፍንጫው ላይ በፕላስተር በማሸግ አፍኖታል። ልጁ ለማምለጥ ሲታገል ተመልሶ በመምጣት በአንሶላ አንቆ ሕይወቱን ካጠፋ በኋላ አስከሬኑን መፀዳጃ ቤት ውስጥ በመደበቅ ለመሰወር ሞክሯል።
የወንጀል ሕግ አንቀጽ 539(1)(ሐ) እና 590/2/(ሠ)ን የተላለፈው ተከሳሽ፣ አስቀድሞ በሕፃኑ ቤተሰብ ላይ ገንዘብ የመጠየቅና የራሱን ኑሮ የመቀየር አደገኛ አስተሳሰብ አንግቦ መሆኑ በክሱ ተገልጿል።
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዐቃቤ ሕግን ክስና ማስረጃዎች አጥጋቢ ሆኖ በማግኘቱ፣ ተከሳሹ በጭካኔ በተሞላበት መንገድ የፈጸመው አስቦ የመግደልና ታዳጊን የመጥለፍ ወንጀል ተረጋግጦበት፣ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የአስር ዓመት ታዳጊ ናትናኤል ማይክልን በማገት እና በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ተከሳሽ ወርቅነህ አሰፋ በሞት እንዲቀጣ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወስኗል።
ተከሳሹ የቀድሞ የመምህርነት ሥራውን ተጠቅሞ ታዳጊውን ናትናኤል ማይክልን ከትምህርት ቤት ሲመለስ ጠልፎ ወደ መኖሪያ ቤቱ ወሰዷል።
ተከሳሹ ልጁን በቦክስ ከመምታት በኋላ በአፍና አፍንጫው ላይ በፕላስተር በማሸግ አፍኖታል። ልጁ ለማምለጥ ሲታገል ተመልሶ በመምጣት በአንሶላ አንቆ ሕይወቱን ካጠፋ በኋላ አስከሬኑን መፀዳጃ ቤት ውስጥ በመደበቅ ለመሰወር ሞክሯል።
የወንጀል ሕግ አንቀጽ 539(1)(ሐ) እና 590/2/(ሠ)ን የተላለፈው ተከሳሽ፣ አስቀድሞ በሕፃኑ ቤተሰብ ላይ ገንዘብ የመጠየቅና የራሱን ኑሮ የመቀየር አደገኛ አስተሳሰብ አንግቦ መሆኑ በክሱ ተገልጿል።
የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዐቃቤ ሕግን ክስና ማስረጃዎች አጥጋቢ ሆኖ በማግኘቱ፣ ተከሳሹ በጭካኔ በተሞላበት መንገድ የፈጸመው አስቦ የመግደልና ታዳጊን የመጥለፍ ወንጀል ተረጋግጦበት፣ በሞት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago
በማርበርግ ቫይረስ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ
👉 የሟቾች ቁጥር 6 ደርሷል
ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች በሽታው የመያዝ እድላቸውን ለመቀነስ የሚያግዝ Remsedevir የተባለ የፀረ ህዋስ መድኃኒት ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የመጀመሪያው የበሽታው ታማሚ ከተገኘበት ቀን ጀምሮ እስከ ህዳር 17 ድረስ በበሽታው ለተጠረጠሩ ለ73 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ መደረጉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። 11 በሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ቫይረሱ እንደተገኘ መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። እነዚህ ታማሚዎች አስፈላጊው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ቢሆንም የ6ቱ ህይወት ያለፈ ሲሆን የተቀሩት 5ቱ ደግሞ በህክምና ጣቢያ ወስጥ ሕክምናቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡
የበሽታው ምልክቶች ከታየባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ የነበራቸው 349 ሰዎች ተለይተው ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 119ኙ የክትትል ጊዜያቸውን ጨርሰው ከለይቶ ማቆያ እንዲወጡ ተደርጓል።
ከዚህ በተጨማሪም በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ከነበራቸው የማህበረሰብ አካላት ጋር በበሽታው የመያዝ እድላቸውን ለመቀነስ የሚያግዝ Remsedevir የተባለ የፀረ ህዋስ መድኃኒት ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት እስካሁን 16 ለሚሆኑ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ ሊሆን ይችላል ተብለው ለታሰቡ የህክምና ባለሙያዎችን እና ለታማሚዎች ለማድረስ ስለመቻሉ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡via.dagu
seledadotio
seledadotio
👉 የሟቾች ቁጥር 6 ደርሷል
ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች በሽታው የመያዝ እድላቸውን ለመቀነስ የሚያግዝ Remsedevir የተባለ የፀረ ህዋስ መድኃኒት ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
የመጀመሪያው የበሽታው ታማሚ ከተገኘበት ቀን ጀምሮ እስከ ህዳር 17 ድረስ በበሽታው ለተጠረጠሩ ለ73 ሰዎች የላብራቶሪ ምርመራ መደረጉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። 11 በሚሆኑ ግለሰቦች ላይ ቫይረሱ እንደተገኘ መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል። እነዚህ ታማሚዎች አስፈላጊው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ቢሆንም የ6ቱ ህይወት ያለፈ ሲሆን የተቀሩት 5ቱ ደግሞ በህክምና ጣቢያ ወስጥ ሕክምናቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ፡፡
የበሽታው ምልክቶች ከታየባቸው ሰዎች ጋር ንክኪ የነበራቸው 349 ሰዎች ተለይተው ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 119ኙ የክትትል ጊዜያቸውን ጨርሰው ከለይቶ ማቆያ እንዲወጡ ተደርጓል።
ከዚህ በተጨማሪም በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ከነበራቸው የማህበረሰብ አካላት ጋር በበሽታው የመያዝ እድላቸውን ለመቀነስ የሚያግዝ Remsedevir የተባለ የፀረ ህዋስ መድኃኒት ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት እስካሁን 16 ለሚሆኑ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ ሊሆን ይችላል ተብለው ለታሰቡ የህክምና ባለሙያዎችን እና ለታማሚዎች ለማድረስ ስለመቻሉ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡via.dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago
ኢትዮጵያ የተቀቀለ የበግና የፍየል ስጋን ወደ ቻይና ልትልክ ነው
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያሏትን ውስን የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዮት አስታውቋል።በኢንስቲትዮቱ የማህበራዊ ኢኮኖሚክስና እሴት ሰንሰለት አስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ ታቀርባለች።
ይህም ሊሆን የቻለዉ የእነዚህን ሀገራት የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን ብቻ በማሟላቷ እንደሆነ ተናግረዉ ችግሩን ለመፍታት ሌሎች ሰፋፊ የገበያ መዳረሻዎችን ለማፈላለግ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።በአሁኑ ወቅት ይህን ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ሲሉ የተናገሩት ዶክተር ሳህሉ በተለይም እንደ ቻይና ወደሚገኙ የሩቅ ምስራቅ ሀገራት ምርቱን ለመላክ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ከአምናና ካቻምና ጀምሮ የተቀቀለ ስጋን ወደ ቻይና ለመላክ የሚያስችሉ አካሄዶችን በመከተል የተለያዪ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን የገለፁት ዶክተር ሳህሉ ይህ ሂደት ከጫፍ መድረሱን አብራርተዋል። በያዝነው ሳምንት የመጨረሻው የፕሮቶኮል ፊርማ ወይንም ስምምነት ከተደረገ በኋላ ምርቶቹን ወደ ቻይና ገበያ መላክ እንደሚቻል ተገልጿል።የተቀቀለ የበግና ፍየል ስጋ ለጊዜው ወደ ቻይና ለመላክ የተፈቀደ ሲሆን አምራቾችንና ላኪዎችን የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡በዘርፋ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በማቀነባበር ሂደት ውስጥ አስፈላጊውን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ኢንስቲትዮቱ አስታውቋል።dagu
seledadotio
seledadotio
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያሏትን ውስን የስጋ ምርት ተቀባይ ሀገራትን ቁጥር ለመጨመር እና ከዘርፋ ያላትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ አቅዳ እየሰራች ትገኛለች ሲል የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዮት አስታውቋል።በኢንስቲትዮቱ የማህበራዊ ኢኮኖሚክስና እሴት ሰንሰለት አስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ በአብዛኛዉ የስጋ ምርቷን ጥቂተ በሆኑ የገልፍ ሀገራት ላይ ለሽያጭ ታቀርባለች።
ይህም ሊሆን የቻለዉ የእነዚህን ሀገራት የምርት ጥራትና ደህንነት መስፈርትን ብቻ በማሟላቷ እንደሆነ ተናግረዉ ችግሩን ለመፍታት ሌሎች ሰፋፊ የገበያ መዳረሻዎችን ለማፈላለግ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።በአሁኑ ወቅት ይህን ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ሲሉ የተናገሩት ዶክተር ሳህሉ በተለይም እንደ ቻይና ወደሚገኙ የሩቅ ምስራቅ ሀገራት ምርቱን ለመላክ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
ከአምናና ካቻምና ጀምሮ የተቀቀለ ስጋን ወደ ቻይና ለመላክ የሚያስችሉ አካሄዶችን በመከተል የተለያዪ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን የገለፁት ዶክተር ሳህሉ ይህ ሂደት ከጫፍ መድረሱን አብራርተዋል። በያዝነው ሳምንት የመጨረሻው የፕሮቶኮል ፊርማ ወይንም ስምምነት ከተደረገ በኋላ ምርቶቹን ወደ ቻይና ገበያ መላክ እንደሚቻል ተገልጿል።የተቀቀለ የበግና ፍየል ስጋ ለጊዜው ወደ ቻይና ለመላክ የተፈቀደ ሲሆን አምራቾችንና ላኪዎችን የማዘጋጀት ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡በዘርፋ የተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች በማቀነባበር ሂደት ውስጥ አስፈላጊውን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀሙ ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ኢንስቲትዮቱ አስታውቋል።dagu
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
7 months ago
የልጅነት እርግዝናን ማስቆም እንዳልተቻለ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ
#ethiopia | የልጅነት እርግዝና ሴቶችን ለተለያዩ ተያያዥ የጤና ችግሮች ከማጋለጥ በተጨማሪ ያለ ዕድሜያቸው ሲያረግዙ ከትምህርት ገበታቸው ማቋረጥና ለሌሎችም ማህበራዊ ህይወታቸዉ መናጋት ምክንያት ነዉ።
በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእርግዝና ምርመራ ከተደረገላቸው 11ሺህ 767 አፍላ ወጣቶች ዉስጥ 1ሺህ 843 ሴቶች ለልጅነት እሮግዝና መጋለጣቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የቤተሰብ ዕቅድ ፣የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች የጤና ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብረሀም ከብስራት ሬዳዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልፀዋል ።
ይህም የልጅነት እርግዝናን ለመቀነስ የሚሰሩ ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አመላካች ናቸዉ ያሉት አስተባባሪው የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና አገልግሎትን ለወጣቶች በማመቻቸት እንዲሁም ከመደበኛ የስራ ሰዓት ዉጪ ሰዓት በመመደብ የሚያዘወትሩባቸዉን ስፍራዎች በመለየት መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ያሳያል ብለዋል ።
ከባለድርሻ አካላት በተለይም ከትምህርት ቤቶች ፣ወጣቶችና ስፖርት ፣ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ከሀይማኖት ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አለብን ሲሉ አቶ አብረሀም ለጣቢያችን ተናግረዋል ።#dagu
#ethiopia | የልጅነት እርግዝና ሴቶችን ለተለያዩ ተያያዥ የጤና ችግሮች ከማጋለጥ በተጨማሪ ያለ ዕድሜያቸው ሲያረግዙ ከትምህርት ገበታቸው ማቋረጥና ለሌሎችም ማህበራዊ ህይወታቸዉ መናጋት ምክንያት ነዉ።
በ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእርግዝና ምርመራ ከተደረገላቸው 11ሺህ 767 አፍላ ወጣቶች ዉስጥ 1ሺህ 843 ሴቶች ለልጅነት እሮግዝና መጋለጣቸውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የቤተሰብ ዕቅድ ፣የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች የጤና ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ አብረሀም ከብስራት ሬዳዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ ገልፀዋል ።
ይህም የልጅነት እርግዝናን ለመቀነስ የሚሰሩ ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አመላካች ናቸዉ ያሉት አስተባባሪው የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና አገልግሎትን ለወጣቶች በማመቻቸት እንዲሁም ከመደበኛ የስራ ሰዓት ዉጪ ሰዓት በመመደብ የሚያዘወትሩባቸዉን ስፍራዎች በመለየት መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ያሳያል ብለዋል ።
ከባለድርሻ አካላት በተለይም ከትምህርት ቤቶች ፣ወጣቶችና ስፖርት ፣ሴቶችና ህፃናት እንዲሁም ከሀይማኖት ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት አለብን ሲሉ አቶ አብረሀም ለጣቢያችን ተናግረዋል ።#dagu
7 months ago
በይርጋጨፌ የአረቄ ንግድ ቢከለከልም 65 ጀሪካን አረቄ በድብቅ ሲጓጓዝ በቁጥጥር ስር ዋለ
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌከተማ ፖሊስ የተከለከለ 65 ጀሪካን የአረቄ መጠጥ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል ።
በቁጥጥር ስር የዋለዉ 65 ጀሪካን አረቄ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻዉን ከነገሌ አድርጎ በይርጋጨፌ ከተማ ዉስጥ ጨለማን ተገን በማድረግ ለአረቄ ቤቶች እየተራገፈ እያለ በዕለቱ ተረኛ ሮንድ ፖሊሶች ከእነ መኪናዉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ፍቃዱ ሲሳይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
አረቄ ባህላዊ መጠጥ ተብሎ ቢነገድም ከስሪቱ አንፃር የተለያዩ ባዕድ ነገሮች እየተጨመረበት በዜጎች ላይ ከፍተኛ የጤና እክል እየፈጠረ በመሆኑ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጎበት በይርጋጨፌ ከተማ የአረቄ ንግድ ክልከላ መደረጉ ይታወሳል ።
በእጃቸዉ ላይ ያለዉን ጨርሰዉ እንዲያቆሙ በተሰጣቸዉ የቀን ገደብ መሠረት አብዛኛዎቹ አረቄ ቤቶች ይህን ተግባራዊ ቢያደርጉትም በድብቅ የሚሸጡ ስለመኖራቸዉ በቁጥጥር ስር የዋለዉ አረቄ ማሳያ ነዉ ተብሏል ።አዛዡ ከድርጊታቸው በማይቆጠቡ አካላት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል ።
Dagu
Addis_News
Addis_News
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌከተማ ፖሊስ የተከለከለ 65 ጀሪካን የአረቄ መጠጥ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል ።
በቁጥጥር ስር የዋለዉ 65 ጀሪካን አረቄ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻዉን ከነገሌ አድርጎ በይርጋጨፌ ከተማ ዉስጥ ጨለማን ተገን በማድረግ ለአረቄ ቤቶች እየተራገፈ እያለ በዕለቱ ተረኛ ሮንድ ፖሊሶች ከእነ መኪናዉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ፍቃዱ ሲሳይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
አረቄ ባህላዊ መጠጥ ተብሎ ቢነገድም ከስሪቱ አንፃር የተለያዩ ባዕድ ነገሮች እየተጨመረበት በዜጎች ላይ ከፍተኛ የጤና እክል እየፈጠረ በመሆኑ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጎበት በይርጋጨፌ ከተማ የአረቄ ንግድ ክልከላ መደረጉ ይታወሳል ።
በእጃቸዉ ላይ ያለዉን ጨርሰዉ እንዲያቆሙ በተሰጣቸዉ የቀን ገደብ መሠረት አብዛኛዎቹ አረቄ ቤቶች ይህን ተግባራዊ ቢያደርጉትም በድብቅ የሚሸጡ ስለመኖራቸዉ በቁጥጥር ስር የዋለዉ አረቄ ማሳያ ነዉ ተብሏል ።አዛዡ ከድርጊታቸው በማይቆጠቡ አካላት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል ።
Dagu
Addis_News
Addis_News
8 months ago
የ12 ዓመቷን የእንጀራ ልጃቸዉ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸሙት የ75 ዓመቱ አዛዉንት በእስራት ተቀጡ
የወንጀል ድርጊቱ በጅማ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ጅሬን ቀበሌ መፈጸሙን ፖሊስ አስታዉቋል። የጅማ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ፖሊስ ፅህፈት ቤት የሴቶች እና ሕፃናት የወንጀል ምርመራ መርማሪ ሣጅን ሲፍቱ በላይ እንደገለፁት ተከሣሽ ናስር አባ ቡልጉ የተባሉት የ75 ዓመት አዛዉንት ድርጊቱን በ12 ዓመቷ የእንጀራ ልጃቸዉ ላይ ፈጽመዋል፡፡
መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓም ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ ጥቃቱን ሊፈጹሙ የቻሉት የታዳጊዋ እናት ጎረቤት ለቅሶ ለማስተዛዘን ባመሹበት ወቅት በነዉ።ወላጅ እናት ከለቅሶ ቤት ሲመለሱ ታዳጊዋ ልጅም በደረሠበት ጥቃት ደም በደም ሆና በመመልከታቸው ወዲያው ጎረቤት ጠርተው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳዉቀዋል፡፡
ታዳጊዋ ጥቃቱን ማን እንፈጸመባት ለፖሊስ በሰጠችው መረጃ መሠረት ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡ በተጨማሪም በሕክምና ምርመራ ተደርጎላት ውጤቱን ፖሊስ በማያያዝ መዝገቡን ለአቃቤ ሕግ ልኳል።ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው አቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ በወንጀል ሕግ ቁጥር 627 መሠረት ክስ መስርቷል።
በአቃቤ ሕግ የተመሠረተውን ክስ የተመለከተው የጅማ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ናስር አባ ቡልጉ ጥፋተኛ በማለት በ18 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል።Via : dagu
seledadotio
seledadotio
የወንጀል ድርጊቱ በጅማ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ጅሬን ቀበሌ መፈጸሙን ፖሊስ አስታዉቋል። የጅማ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ፖሊስ ፅህፈት ቤት የሴቶች እና ሕፃናት የወንጀል ምርመራ መርማሪ ሣጅን ሲፍቱ በላይ እንደገለፁት ተከሣሽ ናስር አባ ቡልጉ የተባሉት የ75 ዓመት አዛዉንት ድርጊቱን በ12 ዓመቷ የእንጀራ ልጃቸዉ ላይ ፈጽመዋል፡፡
መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓም ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ ጥቃቱን ሊፈጹሙ የቻሉት የታዳጊዋ እናት ጎረቤት ለቅሶ ለማስተዛዘን ባመሹበት ወቅት በነዉ።ወላጅ እናት ከለቅሶ ቤት ሲመለሱ ታዳጊዋ ልጅም በደረሠበት ጥቃት ደም በደም ሆና በመመልከታቸው ወዲያው ጎረቤት ጠርተው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳዉቀዋል፡፡
ታዳጊዋ ጥቃቱን ማን እንፈጸመባት ለፖሊስ በሰጠችው መረጃ መሠረት ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡ በተጨማሪም በሕክምና ምርመራ ተደርጎላት ውጤቱን ፖሊስ በማያያዝ መዝገቡን ለአቃቤ ሕግ ልኳል።ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው አቃቤ ሕግ በተከሳሹ ላይ በወንጀል ሕግ ቁጥር 627 መሠረት ክስ መስርቷል።
በአቃቤ ሕግ የተመሠረተውን ክስ የተመለከተው የጅማ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ናስር አባ ቡልጉ ጥፋተኛ በማለት በ18 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል።Via : dagu
seledadotio
seledadotio
Comments