በኢንዶኔዥያ፣ ሲሪላንካና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወት አለፈ
ባለፉት ቀናት በተከሰቱት አውሎ ነፋስ በኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ እና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በአስከፊ የአየር ሁኔታ የተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እየተሰራ ይገኛል። ሰኞ እለት ወደ ሰሜን ሱማትራ ያቀኑት የኢንዶኔዥያ ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ መንግስት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ "አስፈላጊውን እርዳታ እንዴት ወዲያውኑ መላክ እንደሚቻል" ነው ብለዋል ።
“ፈጣሪ ቢፈቅድ ልንደርስባቸው የሚገቡ በርካታ ሩቅ መንደሮች አሉ” ያሉት ፕራቦዎ፣ መንግስት የእርዳታ ጥረቱን ለማገዝ ሄሊኮፕተሮችን እና አውሮፕላኖችን እያሰማራ መሆኑን ተናግረዋል።ፕራቦዎ ቢያንስ በኢንዶኔዥያ 442 ሰዎችን ለገደለው እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የደረሱበት አልታወቀም ለተባለዉ ከባድ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ምላሽ ብሄራዊ ድንገተኛ ሁኔታ አዋጅ እንዲያውጁ ከፍተኛ ጫና በአስተዳደራቸዉ ላይ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከስሪላንካ አቻቸው አኑራ ኩማራ ዲሳናያኬ በተለየ መልኩ ፕራቦዎ እስካሁን ድረስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እርዳታ እንዲሰጣቸዉ በይፋ ከመጠየቅ ተቆጥበዋል።የኢንዶኔዥያ መንግስት ሁለት የሆስፒታል መርከቦችን እና ሶስት የጦር መርከቦችን እርዳታ የጫኑ ድጋፎችን በጣም አስከፊ ወደሆኑ አካባቢዎች ልኳል፡፡የስሪላንካ መንግስት አለም አቀፍ ዕርዳታን በመጠየቅ በአደጋዉ ለታገቱ ሰዎች ወታደራዊ ሄሊኮፕተሮችን እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ቢያንስ 334 ሰዎች መሞታቸውን የሲሪላንካ የአደጋ ኤጀንሲ ያስታወቀ ሲሆን በርካቶች አሁንም ጠፍተዋል።
የታይላንድ ባለስልጣናት በበኩላቸዉ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በቀጠለው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 176 ደርሷል ብለዋል።መንግስት የእርዳታ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ቢገልጽም በጎርፉ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ህዝባዊ ትችት እየጨመረ ይገኛል፡፡ ሁለት የአካባቢው ባለስልጣናት በደካማ ምላሽ አሰጣጣቸዉ የተነሳ ከስራ ታግደዋል ሲል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
ባለፉት ቀናት በተከሰቱት አውሎ ነፋስ በኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ እና ታይላንድ በደረሰ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ ከ1 ሺ በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በአስከፊ የአየር ሁኔታ የተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመርዳት እየተሰራ ይገኛል። ሰኞ እለት ወደ ሰሜን ሱማትራ ያቀኑት የኢንዶኔዥያ ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ መንግስት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ "አስፈላጊውን እርዳታ እንዴት ወዲያውኑ መላክ እንደሚቻል" ነው ብለዋል ።
“ፈጣሪ ቢፈቅድ ልንደርስባቸው የሚገቡ በርካታ ሩቅ መንደሮች አሉ” ያሉት ፕራቦዎ፣ መንግስት የእርዳታ ጥረቱን ለማገዝ ሄሊኮፕተሮችን እና አውሮፕላኖችን እያሰማራ መሆኑን ተናግረዋል።ፕራቦዎ ቢያንስ በኢንዶኔዥያ 442 ሰዎችን ለገደለው እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የደረሱበት አልታወቀም ለተባለዉ ከባድ የጎርፍ አደጋ እና የመሬት መንሸራተት ምላሽ ብሄራዊ ድንገተኛ ሁኔታ አዋጅ እንዲያውጁ ከፍተኛ ጫና በአስተዳደራቸዉ ላይ እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከስሪላንካ አቻቸው አኑራ ኩማራ ዲሳናያኬ በተለየ መልኩ ፕራቦዎ እስካሁን ድረስ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እርዳታ እንዲሰጣቸዉ በይፋ ከመጠየቅ ተቆጥበዋል።የኢንዶኔዥያ መንግስት ሁለት የሆስፒታል መርከቦችን እና ሶስት የጦር መርከቦችን እርዳታ የጫኑ ድጋፎችን በጣም አስከፊ ወደሆኑ አካባቢዎች ልኳል፡፡የስሪላንካ መንግስት አለም አቀፍ ዕርዳታን በመጠየቅ በአደጋዉ ለታገቱ ሰዎች ወታደራዊ ሄሊኮፕተሮችን እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ቢያንስ 334 ሰዎች መሞታቸውን የሲሪላንካ የአደጋ ኤጀንሲ ያስታወቀ ሲሆን በርካቶች አሁንም ጠፍተዋል።
የታይላንድ ባለስልጣናት በበኩላቸዉ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በቀጠለው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 176 ደርሷል ብለዋል።መንግስት የእርዳታ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ቢገልጽም በጎርፉ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ህዝባዊ ትችት እየጨመረ ይገኛል፡፡ ሁለት የአካባቢው ባለስልጣናት በደካማ ምላሽ አሰጣጣቸዉ የተነሳ ከስራ ታግደዋል ሲል አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago