Logo
SeledaPost
የወለደችውን ህፃን ልጅ መፀዳጃ ቤት ለመክተት ስትታገል የነበረች እናት  በእስራት ተቀጣች
 
በቦረና ዞን ዲሎቲ ወረዳ ውስጥ የወለደችውን ልጅ መፀዳጃ ውስጥ ለመክተት  የሞከረችው ግለሰብ  በእስራት ተቀጣች ።የቦረና ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የሴቶች እና ህጻናት ጉዳዮች ፅ/ቤት ሃላፊ ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ  ለብስራት ሬዲዮ እንገለጹት ተከሳሽ መገርቱ ጋሹ የተባለች ተከሳሽ ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ  ሴት ልጅ በሰላም መገላገሏ ተገልጿል ።
 
ተከሳሿ በሰላም የወለደቻትን  ሴት ልጅ ለተወሰኑ ቀናት አጠገቧ ካቆየቻት በኋላ ማንም ሳያያት መፀዳጃ ቤት  በመግባት ህጻኗን  ጉድጓድ ውስጥ በጭንቅላቷ ለመክተት ስትሞክር የህጻኗን ለቅሶ የሰሙት  ሰዎች  ህጻኗን  ከሞት ማትረፋቸው ተገልጿል። ድርጊቱን ስትፈጽም የነበረችው ተከሳሽ  በቁጥጥር ስር ውላለች።ፖሊስም ህጻኗን ወዲያው ለህክምና ወደ ጤና ተቋም በመላክ ተከሳሿ ላይ በበቂ ማስረጃ የምርመራ መዝገቡን  በማጣራት ለአቃቢ ህግ አስተላልፏል። አቃቢ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በተከሳሿ ላይ በህጻን ልጅ መግደል ወንጀል ሙከራ ክስ የመሰረተባት እንደሆነ ገልፀዋል።
 
በአቃቢ ህግ የተመሰረተውን ክስ የተመለከተው የቦረና ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለ ችሎት ተከሳሽ መገርቱ ጋሻው አስባና አቅዳ የወለደቻትን ልጅ ለመግደል በመፀዳጃ ቤት ለመክተት ስትሞክር በመያዟ በአምስት አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ የተወሰነባት መሆኑን ኮማንደር ወጋዬ ዲዶ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ገልፀዋል። ህጻኗ በተደረጋላት የተፋጠነ የህክምና እርዳታ  በሙሉ ጤንነት ላይ እንደምትገኝና ወደፊት ህጉን በጠበቀ መሰረት ለአሳዳጊ እንደምትሰጥ  ገልፀዋል።via_dagu

Seledadotio
Seledadotio
25 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.