Logo
SeledaPost
በሰሜን ኢራቅ የሚገኘው የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ ስፍራ በድሮን ጥቃት ተመታ

በኢራቅ ኮሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ ስፍራ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት ተቋሙ ሥራውን እንዲያቆም አስገድዶታል፣ በሰሜናዊ ኢራቅ የኩርዲሽ ክልል አብዛኛው ኃይል እንዲቋረጥ አድርጓል ሲሉ የአካባቢዉ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።ጥቃቱ የተፈፀመው እሮብ ምሽት ላይ መሆኑን የሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። በርካታ የጋዝ ማከማቻ በመመታቱ ፍንዳታ እና ከፍተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱን ኤጀንሲው ገልጿል።

በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።የኢራቅ ማእከላዊ ወታደራዊ አዛዥ የጋራ ዘመቻ ኮማንድ እንደገለፀው የጥቃቱ ትኩረት የክልሉን "ደህንነት እና ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት" ማስተጓጎል ይመስላል ብሏል።እንደየአካባቢው ባለስልጣናት ገለጻ፣ 8 በመቶው የክልሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍርግርግ ተጎድቷል፣ በዚህም የተነሳ ከፊል ራስ ገዝ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ አስከትሏል።

ክሆር ሞር የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ኩባንያ ዳና ጋዝ የሚተዳደር ሲሆን በሰሜን ኢራቅ ውስጥ በኪርኩክ እና በሱሌማንያ ከተሞች መካከል ይገኛል።መሐንዲሶች የነዳጅ መሰረተ ልማቱን ለመጠገን ከሁለት እስከ ሶስት ቀናት እንደሚፈጅ ተናግረዋል፡፡ የኢራቅ መንግስት እና ዳና ጋዝ ደግሞ አደጋውን ለማጣራት አጣሪ ቡድኖችን ወደ ስፍራዉ ልከዋል።
Dagu
seledadotio
seledadotio
7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.