በይርጋጨፌ የአረቄ ንግድ ቢከለከልም 65 ጀሪካን አረቄ በድብቅ ሲጓጓዝ በቁጥጥር ስር ዋለ
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌከተማ ፖሊስ የተከለከለ 65 ጀሪካን የአረቄ መጠጥ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል ።
በቁጥጥር ስር የዋለዉ 65 ጀሪካን አረቄ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻዉን ከነገሌ አድርጎ በይርጋጨፌ ከተማ ዉስጥ ጨለማን ተገን በማድረግ ለአረቄ ቤቶች እየተራገፈ እያለ በዕለቱ ተረኛ ሮንድ ፖሊሶች ከእነ መኪናዉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ፍቃዱ ሲሳይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
አረቄ ባህላዊ መጠጥ ተብሎ ቢነገድም ከስሪቱ አንፃር የተለያዩ ባዕድ ነገሮች እየተጨመረበት በዜጎች ላይ ከፍተኛ የጤና እክል እየፈጠረ በመሆኑ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጎበት በይርጋጨፌ ከተማ የአረቄ ንግድ ክልከላ መደረጉ ይታወሳል ።
በእጃቸዉ ላይ ያለዉን ጨርሰዉ እንዲያቆሙ በተሰጣቸዉ የቀን ገደብ መሠረት አብዛኛዎቹ አረቄ ቤቶች ይህን ተግባራዊ ቢያደርጉትም በድብቅ የሚሸጡ ስለመኖራቸዉ በቁጥጥር ስር የዋለዉ አረቄ ማሳያ ነዉ ተብሏል ።አዛዡ ከድርጊታቸው በማይቆጠቡ አካላት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል ።
Dagu
Addis_News
Addis_News
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌከተማ ፖሊስ የተከለከለ 65 ጀሪካን የአረቄ መጠጥ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል ።
በቁጥጥር ስር የዋለዉ 65 ጀሪካን አረቄ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻዉን ከነገሌ አድርጎ በይርጋጨፌ ከተማ ዉስጥ ጨለማን ተገን በማድረግ ለአረቄ ቤቶች እየተራገፈ እያለ በዕለቱ ተረኛ ሮንድ ፖሊሶች ከእነ መኪናዉ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ፍቃዱ ሲሳይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።
አረቄ ባህላዊ መጠጥ ተብሎ ቢነገድም ከስሪቱ አንፃር የተለያዩ ባዕድ ነገሮች እየተጨመረበት በዜጎች ላይ ከፍተኛ የጤና እክል እየፈጠረ በመሆኑ ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጎበት በይርጋጨፌ ከተማ የአረቄ ንግድ ክልከላ መደረጉ ይታወሳል ።
በእጃቸዉ ላይ ያለዉን ጨርሰዉ እንዲያቆሙ በተሰጣቸዉ የቀን ገደብ መሠረት አብዛኛዎቹ አረቄ ቤቶች ይህን ተግባራዊ ቢያደርጉትም በድብቅ የሚሸጡ ስለመኖራቸዉ በቁጥጥር ስር የዋለዉ አረቄ ማሳያ ነዉ ተብሏል ።አዛዡ ከድርጊታቸው በማይቆጠቡ አካላት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል ።
Dagu
Addis_News
Addis_News
7 months ago