Logo
SeledaPost
የመቂ ከተማ ነዋሪዋ የ10 ሚሊዮን ብር የሎተሪ ዕጣ አሸናፊ ሽልማታቸውን ተረከበች

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ባወጣው የ"ልዩ ዕድል" ሎተሪ የ10 ሚሊዮን ብር ከፍተኛ ዕጣ አሸናፊ የሆኑት የመቂ ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ስምረት ኢቲቻ፣ ሽልማታቸውን  በይፋ ተረክበዋል።

ወ/ሮ ስምረት ዕጣው የወጣበትን አጋጣሚ ሲያስታውሱ፣ መስከረም 21 ቀን ከቤተክርስቲያን መልስ ቢሮአቸው ተቀምጠው ሳለ የቆረጡት ትኬት የ10 ሚሊዮን ብር ባለቤት እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። አሸናፊዋ በደስታ ተውጠው በሰጡት አስተያየት "እናቴ እመቤቴ የ10 ሚሊዮን ብር አሸናፊ አድርጋኛለች" በማለት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በበኩሉ፣ ሽልማቱን ለአሸናፊዋ ማስረከቡን ገልጾ፣ መሰል የሎተሪ ዕጣዎች የማህበረሰቡን የኑሮ ሁኔታ ከመቀየር ባለፈ ለሀገር ኢኮኖሚ ያላቸውን ድርሻ ጠቁሟል።Dagu

seledadotio
seledadotio
6 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.