16 hours ago
"በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምርጫ ሰኔ 2 ይካሄዳል" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
16 hours ago
ፊፋ የስፒድን ዜማ በአልበሙ አካተተ !
#ethiopia | እውቁ አሜሪካዊ ' ስትሪመር ' አይ ሾው ስፒድ ለ 2026 ዓለም ዋንጫ የራሱን ዜማ ይፋ አድርጎ ነበር።
ስፒድ ይፋ ያደረገው ዜማ ከፍተኛ ተቀባይነት ሲያገኝ ሲሆን በ ዩቲዩብ በርካታ ተመልካቾች ተመልክተውታል።
ፊፋ አሁን ላይ የስፒድን ዜማ በዓለም ዋንጫ አልበም ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን አሳውቆታል።
ስፒድ ፊፋ በይፋ ማረጋገጫ እንደሰጠው በቀጥታ ስርጭት ለአድናቂዎቹ የፅሁፍ ማረጋገጫ መልዕክቱን አሳይቷል።
ዜማው ' Champions ' የሚል መጠርያ ያለው ሲሆን ዩቲዩብ ላይ 11 ሚልዮን እይታ አግኝቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sport #ethiopia #getutemesgen #getu
#ethiopia | እውቁ አሜሪካዊ ' ስትሪመር ' አይ ሾው ስፒድ ለ 2026 ዓለም ዋንጫ የራሱን ዜማ ይፋ አድርጎ ነበር።
ስፒድ ይፋ ያደረገው ዜማ ከፍተኛ ተቀባይነት ሲያገኝ ሲሆን በ ዩቲዩብ በርካታ ተመልካቾች ተመልክተውታል።
ፊፋ አሁን ላይ የስፒድን ዜማ በዓለም ዋንጫ አልበም ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን አሳውቆታል።
ስፒድ ፊፋ በይፋ ማረጋገጫ እንደሰጠው በቀጥታ ስርጭት ለአድናቂዎቹ የፅሁፍ ማረጋገጫ መልዕክቱን አሳይቷል።
ዜማው ' Champions ' የሚል መጠርያ ያለው ሲሆን ዩቲዩብ ላይ 11 ሚልዮን እይታ አግኝቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sport #ethiopia #getutemesgen #getu
16 hours ago
የንፁሃን ደም መፍሰስ ይብቃ፡ ለዘላቂ ሰላም በጋራ እንምከር!
#ethiopia | በሀገራች የዜጎች ሞት ስፍራ አየቀያየረ ቀጥሏል።ዛሬ ደግሞ በተደጋጋሚ ሞት እየተሰማበት ባለው በምስራቅ አርሲ ዞን በንፁሃን በኦርቶዶክስ ከርስትያን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና የአማኞች መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ከሚዲያዎች ዘገባ መረዳት ችያለሁ። መሰል ጥቃቶች ራስን በተጠቂዎች ቦታ አድርገን ካየን በእጅጉ ልብን በኃዘን ይሰብራል።
የንፁሃን ደም ያለአግባብ መፍሰስ እና የዜጎች መገደል በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል።ግና እንዴትና መቼ? እንዴትስ ላለፉት ዓመታት በንጹሃን ዜጎችና በቤተ እምነቶች(መስጊድና ቤተክርስቲያን) ላይ የደረሱት ጥቃቶች የአንዱ ፈጻሚዎች እንኳ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋልና ተጠያቂ ማድረግ ሳይቻል ቀረ? ከድርጊቱ በላይ መደጋገሙ፣ከመደጋገሙ በላይ ፈጻሚዎቹ ሁሌም ያልታወቁ እየተባሉ መፍትሄ ማምጣት አለመቻል አደገኛ ነው።
ዘላቂ መፍትሄ ይገኝ ዘንድ ቆም ብሎ ማሰብ፣በ ስሜት ተጽዕኖ ስር ከመውደቅ በራቀ መልኩ ነገሮችን መመርመር፣መምከርና በጋራ መፍትሄ መፈለግ ግድ ይላል።
ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ነፍስ እንዲህ መርከሱ እጅግ አደገኛ ነገር ነው።አላህ በቁርኣን እንዲህ ይለናል።
مِنۡ أَجۡلِ ذَٰلِكَ كَتَبۡنَا عَلَىٰ بَنِيٓ إِسۡرَـٰٓءِيلَ أَنَّهُۥ مَن قَتَلَ نَفۡسَۢا بِغَيۡرِ نَفۡسٍ أَوۡ فَسَادٖ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ ٱلنَّاسَ جَمِيعٗا وَمَنۡ أَحۡيَاهَا فَكَأَنَّمَآ أَحۡيَا ٱلنَّاسَ جَمِيعٗاۚ وَلَقَدۡ جَآءَتۡهُمۡ رُسُلُنَا بِٱلۡبَيِّنَٰتِ ثُمَّ إِنَّ كَثِيرٗا مِّنۡهُم بَعۡدَ ذَٰلِكَ فِي ٱلۡأَرۡضِ لَمُسۡرِفُونَ
— سورة المائدة (5:32)
"በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው፡፡"
— አል-ማኢዳህ (5:32)
ይህ ቁርኣናዊ መለኮታዊ መመሪያ የሰው ልጅ ሕይወት ነፍስ በማለት በመጥራት ያለ ምንም የዘር፣ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት ፍጹም የተከበረና የማይደፈር መሆኑን ያረጋግጣል።
በአንቀጹ መሠረት አንዲትን ንጹሕ ነፍስ ያለ አግባብ መቅጠፍ መላውን የሰውን ዘር እንደ ማጥፋት የሚቆጠር እጅግ ከባድ ወንጀል ሲሆን፣ በተቃራኒው ደግሞ አንዲትን ነፍስ ከአደጋ መታደግና ማዳን መላውን የሰው ልጅ ሕይወት እንደ ማኖር የሚቆጠር ታላቅ ሰብአዊ በጎነት ነው።
እንደ ዜጋ ማድረግ የምንችለው ለሟች ቤተሰቦችና ወገኖቻች መጽናናትን መመኘት ብቻ በመሆኑ እያዘንኩ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁ።
ህዝባችንና ሀገራችንን ከጥፋትና ከእልቂት ጠብቅልን።አላህ ሆይ! እውነቱ እንዲወጣ፣ የንጹዃን ደምም አፍሳሾች መቀጣጫ ይሆኑ ዘንድ የእጃቸውን እንዲያገኙ አድርግልን።አላህ በቃችሁ በለን!
ኡዝታዝ አህመዲን ጀበል
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በሀገራች የዜጎች ሞት ስፍራ አየቀያየረ ቀጥሏል።ዛሬ ደግሞ በተደጋጋሚ ሞት እየተሰማበት ባለው በምስራቅ አርሲ ዞን በንፁሃን በኦርቶዶክስ ከርስትያን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና የአማኞች መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ከሚዲያዎች ዘገባ መረዳት ችያለሁ። መሰል ጥቃቶች ራስን በተጠቂዎች ቦታ አድርገን ካየን በእጅጉ ልብን በኃዘን ይሰብራል።
የንፁሃን ደም ያለአግባብ መፍሰስ እና የዜጎች መገደል በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል።ግና እንዴትና መቼ? እንዴትስ ላለፉት ዓመታት በንጹሃን ዜጎችና በቤተ እምነቶች(መስጊድና ቤተክርስቲያን) ላይ የደረሱት ጥቃቶች የአንዱ ፈጻሚዎች እንኳ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋልና ተጠያቂ ማድረግ ሳይቻል ቀረ? ከድርጊቱ በላይ መደጋገሙ፣ከመደጋገሙ በላይ ፈጻሚዎቹ ሁሌም ያልታወቁ እየተባሉ መፍትሄ ማምጣት አለመቻል አደገኛ ነው።
ዘላቂ መፍትሄ ይገኝ ዘንድ ቆም ብሎ ማሰብ፣በ ስሜት ተጽዕኖ ስር ከመውደቅ በራቀ መልኩ ነገሮችን መመርመር፣መምከርና በጋራ መፍትሄ መፈለግ ግድ ይላል።
ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ነፍስ እንዲህ መርከሱ እጅግ አደገኛ ነገር ነው።አላህ በቁርኣን እንዲህ ይለናል።
مِنۡ أَجۡلِ ذَٰلِكَ كَتَبۡنَا عَلَىٰ بَنِيٓ إِسۡرَـٰٓءِيلَ أَنَّهُۥ مَن قَتَلَ نَفۡسَۢا بِغَيۡرِ نَفۡسٍ أَوۡ فَسَادٖ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ ٱلنَّاسَ جَمِيعٗا وَمَنۡ أَحۡيَاهَا فَكَأَنَّمَآ أَحۡيَا ٱلنَّاسَ جَمِيعٗاۚ وَلَقَدۡ جَآءَتۡهُمۡ رُسُلُنَا بِٱلۡبَيِّنَٰتِ ثُمَّ إِنَّ كَثِيرٗا مِّنۡهُم بَعۡدَ ذَٰلِكَ فِي ٱلۡأَرۡضِ لَمُسۡرِفُونَ
— سورة المائدة (5:32)
"በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው፡፡"
— አል-ማኢዳህ (5:32)
ይህ ቁርኣናዊ መለኮታዊ መመሪያ የሰው ልጅ ሕይወት ነፍስ በማለት በመጥራት ያለ ምንም የዘር፣ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት ፍጹም የተከበረና የማይደፈር መሆኑን ያረጋግጣል።
በአንቀጹ መሠረት አንዲትን ንጹሕ ነፍስ ያለ አግባብ መቅጠፍ መላውን የሰውን ዘር እንደ ማጥፋት የሚቆጠር እጅግ ከባድ ወንጀል ሲሆን፣ በተቃራኒው ደግሞ አንዲትን ነፍስ ከአደጋ መታደግና ማዳን መላውን የሰው ልጅ ሕይወት እንደ ማኖር የሚቆጠር ታላቅ ሰብአዊ በጎነት ነው።
እንደ ዜጋ ማድረግ የምንችለው ለሟች ቤተሰቦችና ወገኖቻች መጽናናትን መመኘት ብቻ በመሆኑ እያዘንኩ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁ።
ህዝባችንና ሀገራችንን ከጥፋትና ከእልቂት ጠብቅልን።አላህ ሆይ! እውነቱ እንዲወጣ፣ የንጹዃን ደምም አፍሳሾች መቀጣጫ ይሆኑ ዘንድ የእጃቸውን እንዲያገኙ አድርግልን።አላህ በቃችሁ በለን!
ኡዝታዝ አህመዲን ጀበል
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
18 hours ago
የም/ቤቱ 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል
#ethiopia | ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄዳል።
ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተፈረሙትን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም የኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል ያለው መናኸሪያ ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄዳል።
ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተፈረሙትን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም የኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።
በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል ያለው መናኸሪያ ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
18 hours ago
ሪያል ማድሪድ ለውሾች ማልያ አዘጋጀ !
#ethiopia | ሪያል ማድሪድ በዛሬው ዕለት በሚቀጥለው የውድድር ዘመን የሚጠቀመውን ማልያ ይፋ አድርጓል።
ሎስ ብላንኮዎቹ በአዱስ ማልያቸው ለውሻ የሚሆንም ማዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።
የክለቡ ደጋፊዎች ለውሾቻቸው በአዲዳስ የተዘጋጀውን ልዩ ማልያ ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
ማልያው ለእንስሳቱ እንደሚመች ሆኖ በልዩነት መዘጋጀቱ ተነግሯል።
በዛሬው ዕለት በ 150 ዩሮ ለሽያጭ የቀረቡት የውሻ ማልያዎች ተሸጠው መጠናቀቃቸውን የክለቡ ይፋዊ ድረገጽ ያሳያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sports #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ሪያል ማድሪድ በዛሬው ዕለት በሚቀጥለው የውድድር ዘመን የሚጠቀመውን ማልያ ይፋ አድርጓል።
ሎስ ብላንኮዎቹ በአዱስ ማልያቸው ለውሻ የሚሆንም ማዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።
የክለቡ ደጋፊዎች ለውሾቻቸው በአዲዳስ የተዘጋጀውን ልዩ ማልያ ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።
ማልያው ለእንስሳቱ እንደሚመች ሆኖ በልዩነት መዘጋጀቱ ተነግሯል።
በዛሬው ዕለት በ 150 ዩሮ ለሽያጭ የቀረቡት የውሻ ማልያዎች ተሸጠው መጠናቀቃቸውን የክለቡ ይፋዊ ድረገጽ ያሳያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sports #ጌጡተመስገን
1 day ago
ዩናይትድ ተጨዋች ለማስፈረም ተስማማ !
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ኤደርሰን ከአታላንታ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።
ቀያዮቹ ሰይጣኖች ተጫዋቹን ተጨማሪ ክፍያን ጨምሮ በ 4️⃣5️⃣ ሚልዮን ዩሮ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
ተጨዋቹ በማንችስተር ዩናይትድ ለተጨማሪ አንድ አመት የመቆየት አማራጭ ያካተተ የአራት አመት ውል ይፈርማል።
የ 26ዓመቱ አማካይ ኤደርሰን በቀጣይ የህክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ ተዘግቧል።
ተጨዋቹ በሌሎች ታላላቅ ክለቦች ኢላማ ቢደረግም ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል መምረጡ ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #new #ethiopia #addisababa
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ኤደርሰን ከአታላንታ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።
ቀያዮቹ ሰይጣኖች ተጫዋቹን ተጨማሪ ክፍያን ጨምሮ በ 4️⃣5️⃣ ሚልዮን ዩሮ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
ተጨዋቹ በማንችስተር ዩናይትድ ለተጨማሪ አንድ አመት የመቆየት አማራጭ ያካተተ የአራት አመት ውል ይፈርማል።
የ 26ዓመቱ አማካይ ኤደርሰን በቀጣይ የህክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ ተዘግቧል።
ተጨዋቹ በሌሎች ታላላቅ ክለቦች ኢላማ ቢደረግም ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል መምረጡ ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #new #ethiopia #addisababa
1 day ago
ቀዝቀዝ ሞቅ የሚለው የሩስያ ዩክሬን ጦርነት ዛሬ ሌላ እልቂት አስመዝግቧል
#ethiopia | በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት፣ ሩሲያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በዩክሬን ላይ የሰነዘረችው እጅግ ከፍተኛ የተባለው የአየር ጥቃት የ18 ሰዎችን ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
ከተጎጂዎቹ መካከል የስምንት ዓመት ህጻን እና አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በድኒፕሮ 12 እንዲሁም በዋና ከተማዋ ኪየቭ 6 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፣ የሩሲያ ኢላማዎች በመላው ዩክሬን የሚገኙ የሲቪል መሰረተ ልማቶችና የኃይል ማመንጫ ተቋማት የነበሩ ሲሆን፣ ከሟቾቹ በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በሌላ በኩል ሩሲያ ጥቃቱን የፈጸመችው ቀደም ሲል 21 ተማሪዎች ለተገደሉበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን አስታውቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሩሲያ_ዩክሬን_ጦርነት #የአየር_ጥቃት #ዩክሬን #ሩሲያ #ሰብአዊ_ቀውስ
#ethiopia | በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት፣ ሩሲያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በዩክሬን ላይ የሰነዘረችው እጅግ ከፍተኛ የተባለው የአየር ጥቃት የ18 ሰዎችን ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል።
ከተጎጂዎቹ መካከል የስምንት ዓመት ህጻን እና አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በድኒፕሮ 12 እንዲሁም በዋና ከተማዋ ኪየቭ 6 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፣ የሩሲያ ኢላማዎች በመላው ዩክሬን የሚገኙ የሲቪል መሰረተ ልማቶችና የኃይል ማመንጫ ተቋማት የነበሩ ሲሆን፣ ከሟቾቹ በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
በሌላ በኩል ሩሲያ ጥቃቱን የፈጸመችው ቀደም ሲል 21 ተማሪዎች ለተገደሉበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን አስታውቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የሩሲያ_ዩክሬን_ጦርነት #የአየር_ጥቃት #ዩክሬን #ሩሲያ #ሰብአዊ_ቀውስ
2 days ago
የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።
በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።
እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦
° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 days ago
ምርጫው የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ነው፦ የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።
ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።
ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።
በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።
ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።
በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።
በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።
የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ
2 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀመሩ
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት መርቀው በይፋ ሥራ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ይህ ትልቅ ተነሣሽነት፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በዘመናዊ የአፈር ጥበቃ እና በወንዝ ማጣራት ወደ አረንጓዴ ስፍራዎች በመቀየር፣ የፍራፍሬ ፓርኮችን ከእግር ጉዞ እና ከብስክሌት መንገዶች ጋር በማቀናጀት መዲናችንን አድሷል ብለዋል።
በአጠቃላይ 22.25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት፣ የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ሕያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አክለዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት መርቀው በይፋ ሥራ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ይህ ትልቅ ተነሣሽነት፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በዘመናዊ የአፈር ጥበቃ እና በወንዝ ማጣራት ወደ አረንጓዴ ስፍራዎች በመቀየር፣ የፍራፍሬ ፓርኮችን ከእግር ጉዞ እና ከብስክሌት መንገዶች ጋር በማቀናጀት መዲናችንን አድሷል ብለዋል።
በአጠቃላይ 22.25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት፣ የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ሕያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አክለዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ዝነኛው AFTV (Arsenal Fan TV) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!
#ethiopia | የዓለማችን ትልቁና ተፅዕኖ ፈጣሪው የክለብ ደጋፊዎች ሚዲያ AFTV፣ በኢትዮጵያ የሚገኘውን እጅግ በርካታ የአርሰናል ደጋፊ ማህበረሰብ ለመጎብኘትና ልዩ ዝግጅቶችን ለማድረግ ጉዞውን ወደ አዲስ አበባ ሊያደርግ መሆኑ ታውቋል።
ይህ ጉብኝት በኢትዮጵያ ስፖርታዊ ሚዲያና በደጋፊዎች መካከል አዲስ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ የለንደኑ ክለብ በሀገራችን ያለውን ታላቅ ተወዳጅነት ለዓለም ይበልጥ የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#aftv #arsenalfantv #arsenalethiopia #coyg #addisababa #gooners #ethiopiangooners #aftvinethiopia
#ethiopia | የዓለማችን ትልቁና ተፅዕኖ ፈጣሪው የክለብ ደጋፊዎች ሚዲያ AFTV፣ በኢትዮጵያ የሚገኘውን እጅግ በርካታ የአርሰናል ደጋፊ ማህበረሰብ ለመጎብኘትና ልዩ ዝግጅቶችን ለማድረግ ጉዞውን ወደ አዲስ አበባ ሊያደርግ መሆኑ ታውቋል።
ይህ ጉብኝት በኢትዮጵያ ስፖርታዊ ሚዲያና በደጋፊዎች መካከል አዲስ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ የለንደኑ ክለብ በሀገራችን ያለውን ታላቅ ተወዳጅነት ለዓለም ይበልጥ የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#aftv #arsenalfantv #arsenalethiopia #coyg #addisababa #gooners #ethiopiangooners #aftvinethiopia
3 days ago
ምርጫዉ እስከ ለሊት ስድስት ሰዓት በአንዳንድ ቦታዎች መራዘሙን ቦርዱ ገለጸ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል።
በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።
ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ አስታውሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል።
በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።
ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ አስታውሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
የገዥው ቦታ አዲስ ሰው ተሾመበት
#ethiopia | እዮብ ተካልኝ (ፒኤችዲ) ወደ ብሄራዊ ባንክ ገዥነት መስከረም ላይ ከሄዱ በኋላ ወሳኝ የሚባለው የገንዘብ ሚኒስቴር የፊሲካል ፖሊሲ እና ፐብሊክ ፋይናንስ አስተዳደር ሚኒስትር ደኤታ መደብ ክፍት ሆኖ ነበር።
አሁን ከረጅም ቆይታ በኋላ አቶ ፍቃዱ ሆረታ ተመድበውበታል ያለው ቅዳሜገበያ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | እዮብ ተካልኝ (ፒኤችዲ) ወደ ብሄራዊ ባንክ ገዥነት መስከረም ላይ ከሄዱ በኋላ ወሳኝ የሚባለው የገንዘብ ሚኒስቴር የፊሲካል ፖሊሲ እና ፐብሊክ ፋይናንስ አስተዳደር ሚኒስትር ደኤታ መደብ ክፍት ሆኖ ነበር።
አሁን ከረጅም ቆይታ በኋላ አቶ ፍቃዱ ሆረታ ተመድበውበታል ያለው ቅዳሜገበያ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
ማንችስተር ዩናይትድ ቹዋሜኒን ያስፈርም ይሆን ?
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ የሪያል ማድሪዱን አማካይ ኦርሊየን ቹዋሜኒ የማስፈረም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሰይጣኖች ቹዋሜኒን የካሴሚሮ ሁነኛ ተተኪ አድርገው እንደሚመለከቱት ፋብሪዝዮ ርማኖ ዘግቧል።
ማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋቹን ለማስፈረም የጓጓ ቢሆንም ለዝውውሩ መሰናክሎች መኖራቸው ተገልጿል።
ተጨዋቹ በሪያል ማድሪድ የሚያገኘው ከፍተኛ ደሞዝ አንዱ የዝውውሩ መሰናክል መሆኑ ተዘግቧል።
በተጨማሪም ሪያል ማድሪድ እሱን የመልቀቅ ፍላጎት የሌላቸው መሆኑ ዝውውሩን ሊያከብደው ይችላል ተብሏል።
ለማንችስተር ዩናይትድ ዝውውሩን ማሳካት ከባድ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #getutemesgen #ሰበርዜና #sport #uk
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ የሪያል ማድሪዱን አማካይ ኦርሊየን ቹዋሜኒ የማስፈረም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል።
ቀያዮቹ ሰይጣኖች ቹዋሜኒን የካሴሚሮ ሁነኛ ተተኪ አድርገው እንደሚመለከቱት ፋብሪዝዮ ርማኖ ዘግቧል።
ማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋቹን ለማስፈረም የጓጓ ቢሆንም ለዝውውሩ መሰናክሎች መኖራቸው ተገልጿል።
ተጨዋቹ በሪያል ማድሪድ የሚያገኘው ከፍተኛ ደሞዝ አንዱ የዝውውሩ መሰናክል መሆኑ ተዘግቧል።
በተጨማሪም ሪያል ማድሪድ እሱን የመልቀቅ ፍላጎት የሌላቸው መሆኑ ዝውውሩን ሊያከብደው ይችላል ተብሏል።
ለማንችስተር ዩናይትድ ዝውውሩን ማሳካት ከባድ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #getutemesgen #ሰበርዜና #sport #uk
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በሥርዓት እየተካሄደ ነው - የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ
#ethiopia | የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክን የሚመሩት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋ።
አሁሩ ኬንያታ በመራጮች ማዕከላት የተመለከቱትን ሁኔታ ሲገልጹ፣ የድምፅ አሰጣጡ ሂደቱ በሥርዓት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው፣ ቀኑን ሙሉ በተመሳሳይ መንፈስ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
"ድምፅ መስጠት ዜጎች የሚወክሏቸውን መሪዎች እና ተወካዮች በነፃነት የሚመርጡበት መሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው" ያሉት ኬንያታ፣ የአፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ እውነተኛ ውክልና፣ አካታችነት እና ሕዝቦች የራሳቸውን መሪዎች የመምረጥ አቅም እንዲጠናከር እንደሚሠራ አስታውቀዋል።
በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት የምርጫ ሂደቶች ፈተናዎች እንዳሉ ቢገልጹም፣ ከእያንዳንዱ ምርጫ በኋላ የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ባህል ለመገንባት ዕድል እንዳለ ጠቅሰዋል።
"ኢትዮጵያ የዚህች ታላቅ አህጉር ዋና ከተማ ናት፤ በዚህች ሀገር የሚገኝ ስኬት በመላው አፍሪካ ውስጥ ይንጸባረቃል" ሲሉ የተናገሩት ኬንያታ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም ምኞታቸውን ገልጸው የምርጫው ሂደት በሥርዓት እና በሰላም እንዲጠናቀቅ ያላቸውን እምነት አረጋግጠዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #ebcdotstream #democracy #africanunion
#ethiopia | የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክን የሚመሩት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሰላማዊ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸዋ።
አሁሩ ኬንያታ በመራጮች ማዕከላት የተመለከቱትን ሁኔታ ሲገልጹ፣ የድምፅ አሰጣጡ ሂደቱ በሥርዓት እየተካሄደ መሆኑን ጠቁመው፣ ቀኑን ሙሉ በተመሳሳይ መንፈስ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
"ድምፅ መስጠት ዜጎች የሚወክሏቸውን መሪዎች እና ተወካዮች በነፃነት የሚመርጡበት መሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ መብት ነው" ያሉት ኬንያታ፣ የአፍሪካ ኅብረት በአህጉሪቱ እውነተኛ ውክልና፣ አካታችነት እና ሕዝቦች የራሳቸውን መሪዎች የመምረጥ አቅም እንዲጠናከር እንደሚሠራ አስታውቀዋል።
በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት የምርጫ ሂደቶች ፈተናዎች እንዳሉ ቢገልጹም፣ ከእያንዳንዱ ምርጫ በኋላ የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ባህል ለመገንባት ዕድል እንዳለ ጠቅሰዋል።
"ኢትዮጵያ የዚህች ታላቅ አህጉር ዋና ከተማ ናት፤ በዚህች ሀገር የሚገኝ ስኬት በመላው አፍሪካ ውስጥ ይንጸባረቃል" ሲሉ የተናገሩት ኬንያታ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ መልካም ምኞታቸውን ገልጸው የምርጫው ሂደት በሥርዓት እና በሰላም እንዲጠናቀቅ ያላቸውን እምነት አረጋግጠዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #ebcdotstream #democracy #africanunion
4 days ago
ዴሞክራሲን ለማፅናት የአፍሪካ ሀገራት አንዱ ከሌላው ሊማር ይገባል – ኡሁሩ ኬንያታ
#ethiopia | በአፍሪካ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርና የምርጫ ስርዓትን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት አንዳቸው ከሌላቸው ልምድ መቅሰም አለባቸው አሉ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ፡፡
ነገ የሚካሄደውን ምርጫ ለመታዘብ አዲስ አበባ የሚገኙት ኡሁሩ ኬንያታ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የተካሄዱ ምርጫን የመታዘብ ተግባራት የምርጫ ሂደቶችን ከመከታተል ያለፈ አስተዋጽኦ አላቸው።
ምርጫ የመታዘብ ተግባራቱ በአባል ሀገራቱ መካከል የልምድ ልውውጥና መልካም ተሞክሮዎችን በመቅሰም ዴሞክራሲያዊ ልማትን ለማስፈን ጭምር የተነደፉ ናቸው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት የዴሞክራሲ ስርዓትን የበለጠ ለማጎልበት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የአቻ ለአቻ ትምህርትን ለማበረታታት የሚደረገው ጥረት አካል በመሆኑ በአህጉሪቱ በሚደረጉ ምርጫዎች በታዛቢነት እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።
የምርጫ ታዛቢነት ተልዕኮዎች እና ሌሎች የአፍሪካ ህብረት አሰራሮች ሀገራት ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ስኬታማ አካሄዶችን እንዲለዩ እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ትምህርቶችን እንዲለማመዱ እድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
የአፍሪካ ሀገራት በሌሎች አህጉራት/አካባቢዎች የተዘጋጁ የአስተዳደር ስልቶችን ለመተግበር በአህጉሪቱ ነባራዊ ሁኔታ እና ልምድ የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የተሞክሮ ልውውጥ ሀገር በቀል ዴሞክራሲዊ ልምምዶችን ያመጣል ብለዋል፡፡
አፍሪካዊያን መር የሆነ ዴሞክራሲን የማጠናከር አካሄድ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎች” ለሚለው መርህ ማዕከል ሆኖ እንደሚቀጥል አፅንዖት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
#ethiopia | በአፍሪካ ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርና የምርጫ ስርዓትን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት አንዳቸው ከሌላቸው ልምድ መቅሰም አለባቸው አሉ የኬንያ የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ ኡሁሩ ኬንያታ፡፡
ነገ የሚካሄደውን ምርጫ ለመታዘብ አዲስ አበባ የሚገኙት ኡሁሩ ኬንያታ እንዳሉት፤ በአፍሪካ ህብረት ስር የተካሄዱ ምርጫን የመታዘብ ተግባራት የምርጫ ሂደቶችን ከመከታተል ያለፈ አስተዋጽኦ አላቸው።
ምርጫ የመታዘብ ተግባራቱ በአባል ሀገራቱ መካከል የልምድ ልውውጥና መልካም ተሞክሮዎችን በመቅሰም ዴሞክራሲያዊ ልማትን ለማስፈን ጭምር የተነደፉ ናቸው ብለዋል፡፡
የአፍሪካ ህብረት የዴሞክራሲ ስርዓትን የበለጠ ለማጎልበት እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል የአቻ ለአቻ ትምህርትን ለማበረታታት የሚደረገው ጥረት አካል በመሆኑ በአህጉሪቱ በሚደረጉ ምርጫዎች በታዛቢነት እንደሚሳተፍ ጠቁመዋል።
የምርጫ ታዛቢነት ተልዕኮዎች እና ሌሎች የአፍሪካ ህብረት አሰራሮች ሀገራት ልምድ እንዲለዋወጡ፣ ስኬታማ አካሄዶችን እንዲለዩ እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ሊያጠናክሩ የሚችሉ ትምህርቶችን እንዲለማመዱ እድል ይፈጥራል ነው ያሉት።
የአፍሪካ ሀገራት በሌሎች አህጉራት/አካባቢዎች የተዘጋጁ የአስተዳደር ስልቶችን ለመተግበር በአህጉሪቱ ነባራዊ ሁኔታ እና ልምድ የተደገፈ ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአፍሪካ ሀገራት መካከል የሚደረግ የተሞክሮ ልውውጥ ሀገር በቀል ዴሞክራሲዊ ልምምዶችን ያመጣል ብለዋል፡፡
አፍሪካዊያን መር የሆነ ዴሞክራሲን የማጠናከር አካሄድ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎች” ለሚለው መርህ ማዕከል ሆኖ እንደሚቀጥል አፅንዖት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc
4 days ago
ቲክቶክ ለነገው ምርጫ መዘጋጀቱን ገለጸ
#ethiopia | ቲክቶክ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሚናፈሱ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት እና የፕላትፎርሙን ደህንነት ለመጠበቅ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ይፋ አደረገ።
ማህበራዊ ሚዲያው ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እና ከተለያዩ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቀ ሲሆን፤ የዚሁ ስራ አካል በሆነው የማጣራት እርምጃ በ2025 ማጠናቀቂያ ላይ ብቻ ደንቡን የጣሱ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ የተቀረጹ ቪዲዮዎችን ማስወገዱን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#tiktok #ethiopiaelection #fakenews #nebe #ethiopia #digitalsafety #medialiteracy #ቅዳሜገበያ
#ethiopia | ቲክቶክ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሚናፈሱ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት እና የፕላትፎርሙን ደህንነት ለመጠበቅ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ይፋ አደረገ።
ማህበራዊ ሚዲያው ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እና ከተለያዩ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቀ ሲሆን፤ የዚሁ ስራ አካል በሆነው የማጣራት እርምጃ በ2025 ማጠናቀቂያ ላይ ብቻ ደንቡን የጣሱ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ የተቀረጹ ቪዲዮዎችን ማስወገዱን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#tiktok #ethiopiaelection #fakenews #nebe #ethiopia #digitalsafety #medialiteracy #ቅዳሜገበያ
4 days ago
ዋይት ሀውስ ስደተኞችን ከባዕዳን ፍጥረታት (Aliens) ጋር ያገናኘ አነጋጋሪ ድረ-ገጽ ይፋ ማድረጉ ተነገረ
#ethiopia | የአሜሪካው ዋይት ሀውስ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ በሚል ሳይንሳዊ ልብ-ወለድ እና የባዕዳን ፍጥረታትን (Aliens) ጭብጥ ያደረገ “Aliens.gov” የተሰኘ አዲስ የኢሚግሬሽን መከታተያ ድረ-ገጽ ይፋ ማድረጉ ከፍተኛ መነጋጋሪያ ሆኗል።
ይህ አዲስ ድረ-ገጽ በሀገሪቱ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ ስደተኞችን መረጃ፣ የእስር ቁጥሮችን እና የድንበር ላይ እገዳዎችን በቀጥታ የሚያሳይና በካርታ የታገዘ መረጃ ለህዝብ ይፋ የሚያደርግ ነው።
የድረ-ገጹ መግቢያ መልዕክት “በመካከላችን ይመላለሳሉ!” በሚል አስገራሚ የአጻጻፍ ስልት የተሞላ ሲሆን፣ ማስተዋወቂያ ቪዲዮውም የበረራ ሳህን (UFO) ሰውን አንስቶ ከድንበር ማዶ ሲጥል የሚያሳይ የፈጠራ ምስልን ያካተተ ነው።
ድረ-ገጹ ህብረተሰቡ ጥርጣሬ ያደረባቸውን ስደተኞች በቀጥታ ለኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ አስከባሪ (ICE) ሪፖርት የሚያደርግበት የጥቆማ መስመርም አብሮ የተካተተበት መሆኑ ታውቋል።
የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት አካሄዱን የህዝብን ግንዛቤ ለማሳደግ የተመረጠ የፈጠራ መንገድ ነው ቢሉም፣ የስደተኞች መብት ተሟጋቾች ግን ስደተኞችን ከሰው ልጅ ውጭ አድርጎ መሳል ጥላቻንና ሰብአዊ መብት መጣስን ያባብሳል በሚል በፅኑ እየኮነኑት ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የአሜሪካኢሚግሬሽን #ዋይትሀውስ #aliensgov #የስደተኞችመብት #ሰበርዜና #ufo #ኢሚግሬሽንዜና
#ethiopia | የአሜሪካው ዋይት ሀውስ የህዝብን ትኩረት ለመሳብ በሚል ሳይንሳዊ ልብ-ወለድ እና የባዕዳን ፍጥረታትን (Aliens) ጭብጥ ያደረገ “Aliens.gov” የተሰኘ አዲስ የኢሚግሬሽን መከታተያ ድረ-ገጽ ይፋ ማድረጉ ከፍተኛ መነጋጋሪያ ሆኗል።
ይህ አዲስ ድረ-ገጽ በሀገሪቱ ውስጥ በህገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ ስደተኞችን መረጃ፣ የእስር ቁጥሮችን እና የድንበር ላይ እገዳዎችን በቀጥታ የሚያሳይና በካርታ የታገዘ መረጃ ለህዝብ ይፋ የሚያደርግ ነው።
የድረ-ገጹ መግቢያ መልዕክት “በመካከላችን ይመላለሳሉ!” በሚል አስገራሚ የአጻጻፍ ስልት የተሞላ ሲሆን፣ ማስተዋወቂያ ቪዲዮውም የበረራ ሳህን (UFO) ሰውን አንስቶ ከድንበር ማዶ ሲጥል የሚያሳይ የፈጠራ ምስልን ያካተተ ነው።
ድረ-ገጹ ህብረተሰቡ ጥርጣሬ ያደረባቸውን ስደተኞች በቀጥታ ለኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ አስከባሪ (ICE) ሪፖርት የሚያደርግበት የጥቆማ መስመርም አብሮ የተካተተበት መሆኑ ታውቋል።
የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት አካሄዱን የህዝብን ግንዛቤ ለማሳደግ የተመረጠ የፈጠራ መንገድ ነው ቢሉም፣ የስደተኞች መብት ተሟጋቾች ግን ስደተኞችን ከሰው ልጅ ውጭ አድርጎ መሳል ጥላቻንና ሰብአዊ መብት መጣስን ያባብሳል በሚል በፅኑ እየኮነኑት ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የአሜሪካኢሚግሬሽን #ዋይትሀውስ #aliensgov #የስደተኞችመብት #ሰበርዜና #ufo #ኢሚግሬሽንዜና
4 days ago
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን የቅድመ ምርጫ ትዝብትና የሴቶች ተሳትፎ ሪፖርት ይፋ አደረገ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ዙሪያ ሲያከናውን የቆየውን ሰፊ የቅድመ ምርጫ ትዝብትና የሴቶች ተሳትፎ የዳሰሰበትን አጠቃላይ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
ፌዴሬሽኑ እንደገለጸው፣ በምርጫው ሂደት የሴቶች መራጭነት ተሳትፎ ከፍተኛ ታሪካዊ ውጤት የታየበት ቢሆንም፣ በዕጩነት የመቅረብ እና የመወዳደር ምጣኔያቸው ግን አሁንም ሰፊ ክፍተት ያለበትና ትኩረት የሚሻ መሆኑን አመልክቷል።
በዚሁ ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፣ በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ከተመዘገቡት 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 አጠቃላይ መራጮች ውስጥ 26 ሚሊዮን 667 ሺህ 132 ማለትም 49.3 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ታውቋል ።
ይህ ከፍተኛ የመራጭነት ቁጥር የታየ ቢሆንም፣ በዕጩነት ደረጃ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረቡት ሴቶች ግን 23.1 በመቶ ብቻ ሲሆኑ፣ ለአጠቃላይ ብሔራዊ ምክር ቤት ደግሞ የሴቶች ዕጩዎች ድርሻ 25.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ አኃዝ በሴቶች መራጭነትና ዕጩነት መካከል የ23.5 በመቶ ሰፊ የአሳታፊነት ልዩነት ወይም ክፍተት መኖሩን በግልጽ እንደሚያሳይ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
የሴቶች ፌዴሬሽን የዜጎችን ንቃተ ህሊና ለማሳደግና መራጮችን ለማስተማር ሰፊ የቴክኖሎጂና የሚዲያ ዘመቻዎችን ማካሄዱን በዝርዝር አስረድቷል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በተደረገ ስምምነት 255 ሚሊዮን የፅሁፍ መልዕክቶች በነፃ የተላኩ ሲሆን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ6 ቋንቋዎች የተዘጋጁ መልዕክቶች 42 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሴቶችና 87 ሚሊዮን ለሚሆኑ አጠቃላይ ተመዝጋቢዎች መድረስ መቻላቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በኤፍ ኤም ሬዲዮና በቴሌግራም ቦት አማካኝነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች የምርጫ ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ባልተደጋገመ ስሌት ከ90 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ዘመቻውን መድረስ መቻሉ ተረጋግጧል።
ሂደቱን በታዛቢነት ከመከታተል አንፃርም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉንና 5 ሺህ 432 ታዛቢዎችን ለማሰማራት አቅዶ እንደነበር አስታውቋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ 267 የረጅም ጊዜ ታዛቢ አሰልጣኞች በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስልጠና የወሰዱ ሲሆን፣ እነዚህ አሰልጣኞች በተራቸው 5 ሺህ 165 የሚሆኑ የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን በየደረጃው ማሰልጠን መቻላቸው በስራ አፈፃፀሙ ላይ ተገልጿል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ለቀጣይ ምርጫዎች መሻሻል የሚረዱ በርካታ የውሳኔ ሐሳቦችንና ምክረ ሐሳቦችን ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቅርቧል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዲጂታል ምዝገባ ስርዓቱን ይበልጥ እንዲያሻሽልና የታዛቢዎችን የገንዘብና የዕቃዎች አቅርቦት በወቅቱ እንዲያደርስ የጠየቀው ፌዴሬሽኑ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቢያንስ 30 በመቶ የሴቶች ዕጩ ተሳትፎን የሚያረጋግጥ ውስጣዊ ደንብ እንዲያወጡና የሴቶችን በራስ የመተማመን አቅም የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉ በፅኑ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ዙሪያ ሲያከናውን የቆየውን ሰፊ የቅድመ ምርጫ ትዝብትና የሴቶች ተሳትፎ የዳሰሰበትን አጠቃላይ ሪፖርት ዛሬ ይፋ አድርጓል።
ፌዴሬሽኑ እንደገለጸው፣ በምርጫው ሂደት የሴቶች መራጭነት ተሳትፎ ከፍተኛ ታሪካዊ ውጤት የታየበት ቢሆንም፣ በዕጩነት የመቅረብ እና የመወዳደር ምጣኔያቸው ግን አሁንም ሰፊ ክፍተት ያለበትና ትኩረት የሚሻ መሆኑን አመልክቷል።
በዚሁ ይፋ በተደረገው መረጃ መሠረት፣ በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት ከተመዘገቡት 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 አጠቃላይ መራጮች ውስጥ 26 ሚሊዮን 667 ሺህ 132 ማለትም 49.3 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸው ታውቋል ።
ይህ ከፍተኛ የመራጭነት ቁጥር የታየ ቢሆንም፣ በዕጩነት ደረጃ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረቡት ሴቶች ግን 23.1 በመቶ ብቻ ሲሆኑ፣ ለአጠቃላይ ብሔራዊ ምክር ቤት ደግሞ የሴቶች ዕጩዎች ድርሻ 25.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ አኃዝ በሴቶች መራጭነትና ዕጩነት መካከል የ23.5 በመቶ ሰፊ የአሳታፊነት ልዩነት ወይም ክፍተት መኖሩን በግልጽ እንደሚያሳይ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
የሴቶች ፌዴሬሽን የዜጎችን ንቃተ ህሊና ለማሳደግና መራጮችን ለማስተማር ሰፊ የቴክኖሎጂና የሚዲያ ዘመቻዎችን ማካሄዱን በዝርዝር አስረድቷል።
ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በተደረገ ስምምነት 255 ሚሊዮን የፅሁፍ መልዕክቶች በነፃ የተላኩ ሲሆን፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ በ6 ቋንቋዎች የተዘጋጁ መልዕክቶች 42 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሴቶችና 87 ሚሊዮን ለሚሆኑ አጠቃላይ ተመዝጋቢዎች መድረስ መቻላቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም በኤፍ ኤም ሬዲዮና በቴሌግራም ቦት አማካኝነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች የምርጫ ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ባልተደጋገመ ስሌት ከ90 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ዘመቻውን መድረስ መቻሉ ተረጋግጧል።
ሂደቱን በታዛቢነት ከመከታተል አንፃርም ፌዴሬሽኑ ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉንና 5 ሺህ 432 ታዛቢዎችን ለማሰማራት አቅዶ እንደነበር አስታውቋል። ለዚህም ይረዳ ዘንድ 267 የረጅም ጊዜ ታዛቢ አሰልጣኞች በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስልጠና የወሰዱ ሲሆን፣ እነዚህ አሰልጣኞች በተራቸው 5 ሺህ 165 የሚሆኑ የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን በየደረጃው ማሰልጠን መቻላቸው በስራ አፈፃፀሙ ላይ ተገልጿል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ለቀጣይ ምርጫዎች መሻሻል የሚረዱ በርካታ የውሳኔ ሐሳቦችንና ምክረ ሐሳቦችን ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቅርቧል።
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዲጂታል ምዝገባ ስርዓቱን ይበልጥ እንዲያሻሽልና የታዛቢዎችን የገንዘብና የዕቃዎች አቅርቦት በወቅቱ እንዲያደርስ የጠየቀው ፌዴሬሽኑ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ቢያንስ 30 በመቶ የሴቶች ዕጩ ተሳትፎን የሚያረጋግጥ ውስጣዊ ደንብ እንዲያወጡና የሴቶችን በራስ የመተማመን አቅም የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉ በፅኑ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
4 days ago
ፒኤስጂ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ በፓሪስ ሁከት ተቀሰቀሰ
#ethiopia | የፓሪሰን ዠርሜን (PSG) የሻምፒዮናነት ድልን ተከትሎ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ እና በተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ ስርዓት አልበኝነት እስካሁን 416 ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከታሰሩት ደጋፊዎች መካከል 283ቱ በፓሪስ ከተማ ውስጥ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ ድርጊቱን ለማስቆም በነበረው ግጭት ሰባት የፖሊስ አባላት ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል።
የክለቡ ደጋፊዎች በደስታ ስሜት ውስጥ ሆነው አራት ዋና ዋና የቀለበት መንገዶችን ለመዝጋት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን፥ በፓሪስ ጎዳናዎች ላይ የነበረው የእልልታና የደስታ አገላለጽ እስከ ንጋት ድረስ ቀጥሎ አድሯል።
በሌላ በኩል ፒኤስጂ ይፋዊ የዋንጫ ድሉን በፓሪስ በሚገኘው "Champ-de-Mars" ክፍት የሕዝብ መናፈሻ በጎዳና ላይ እንደሚያከብር ታውቋል።
በዚህ ታላቅ የጎዳና ላይ የድል ክብረ በዓል ላይ እስከ 90,000 የሚደርሱ የክለቡ አድናቂዎችና ነዋሪዎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#psg #paris #ligue1 #footballnews #france #breakingnews
#ethiopia | የፓሪሰን ዠርሜን (PSG) የሻምፒዮናነት ድልን ተከትሎ በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ እና በተለያዩ አካባቢዎች በተቀሰቀሰ ስርዓት አልበኝነት እስካሁን 416 ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከታሰሩት ደጋፊዎች መካከል 283ቱ በፓሪስ ከተማ ውስጥ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ ድርጊቱን ለማስቆም በነበረው ግጭት ሰባት የፖሊስ አባላት ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል።
የክለቡ ደጋፊዎች በደስታ ስሜት ውስጥ ሆነው አራት ዋና ዋና የቀለበት መንገዶችን ለመዝጋት ሙከራ ያደረጉ ሲሆን፥ በፓሪስ ጎዳናዎች ላይ የነበረው የእልልታና የደስታ አገላለጽ እስከ ንጋት ድረስ ቀጥሎ አድሯል።
በሌላ በኩል ፒኤስጂ ይፋዊ የዋንጫ ድሉን በፓሪስ በሚገኘው "Champ-de-Mars" ክፍት የሕዝብ መናፈሻ በጎዳና ላይ እንደሚያከብር ታውቋል።
በዚህ ታላቅ የጎዳና ላይ የድል ክብረ በዓል ላይ እስከ 90,000 የሚደርሱ የክለቡ አድናቂዎችና ነዋሪዎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#psg #paris #ligue1 #footballnews #france #breakingnews
4 days ago
ፔዤ ዳግም ሻምፒዮን
መድፉ በክብር ተሸንፏል ! OHO BIG GABI ...
እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች መሃል ! Champions League Classic .
በኤፍሬም የማነ
#ethiopia | በእነዛ ሽርፍራፊ ሰከንዶች የፔናሊቲ ድራማ ራያ ኤዜን አዳነ ። ራያ አርሰናል አዳነ ። መድፉ ሞቶ ተነሳ ። የፔናሊቲው ድራማ ከቡዳፔስት ቀጠለ ። ከሜንዴዝ መሳት በኋላ ፔዤ ብልጫውን ወሰደ ። የመድፉ ለ120 ደቂቃ የዘለቀ የጀግንነት ተጋድሎ በBig Gabi አምስተኛዋ ወሳኝ ፔናሊቲ ላይ ተወሰነ ። መድፈኞቹ ተጨነቁ ። ዓለም በስሜት ከፍ ዝቅ አለ ። የመድፉ የድል አባት አርሴን ቬንገር ከማጋሊሽ ወሳኝ ፔናሊቲ ጋር በጭንቅ ታጥፈው ታዩ ። ንጉስ ኦነሪ በCBS ስቱዱዮ አርሰናል ከተባለ እናት ሀገሩ ጋር በስሜት ተንቆራጠጠ ። ማጋሊሽ በቀጥታ ፔናሊቲ ተመቶበት ካላዳነው የፔዤው በረኛ ሳፋኖቭ ተፈጠጠ ። ፀንቶ ለአርሰናል ድል ሲዋደቅ የዋለው ብራዚላዊ የመድፉ ግድግዳ ወሳኝ ፔናሊቲ በዛች አጋጣሚ ከቡዳፔስት ሰማይ ስር በረረች ። ፔዤ ሻምፒዮን ሆነ ። አርሰናል በጀግንነት ተዋድቆ ተሸነፈ ። እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች ተሞላች ። የፀናው የመድፉ የድል ምኞት ትጋት በመጨረሻ ከብቃት ባሻገር እንደ ሎተሪም በሆነው ፔናሊቲ ታጠፈ ። አርሰናል ሁለት ወደ ፎሪና ሰማይ በለቀቃቸው ፔናሊቲዎች አማካኝነት የህይወት ዘመን ወደር አልባው የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ህልሙን ሳያሳካ ቀረ ። መድፉ በክብር ተሸነፈ ። መድፉ በክብር ተዋድቆ ተረታ ። ከፑሽካሽ አሬና እግር ኳስ በሁለቱ ኋያላን ፍጥጫ ለ120 ደቂቃ ዘልቆ ለፔናሊቲ በተዳረገ የህይወት ገፅ ተመሠለ ። ስሜት ከፍ አለ ። ተስፋ ነገሰ ። መውጣት መውረድ መውደቅ መነሳት ፀፀት ደስታ ቁጭት እንባ ከቡዳፔስት ተፈራረቁ ። ማግኘት ማጣት መሳት ማዳን በሚሊዮኖች ላይ በእነዛ የፔናሊቲ ቅፅበቶች ተፈራረቁ ። በመጨረሻም 120 ደቂቃዎች ተሻግሮ ለፔናሊቲ የደረሰው ድራማ ፓሬዚያኑን ዳግም አነገሰ ። አርሰናል በክብር እጅ የሰጠው አሳዛኙ ተሸናፊ ሆነ ። እግር ኳስ ኳስ ይዞ መሽከርከር ብቻ እንዳልሆነ መድፉ በፀና ተደናቂ የመከላከል ቅርፁ አረጋገጠ ።
በላቀ የጨዋታ ዝግጅነት የዳበረው በታክቲክ የታጠረው ትንቅንቅ የዘመናዊው እግር ኳስ ሁለት የእግር ኳስ ቀለሞችን አሳየ ። እግር ኳስ በመድፉ የመከላከል ከፍታ ውስጥ የፔዤ የማጥቃት አቅምን አፈዘዘ ። ፓሬዚያኑ ከመድፉ ካቴና ፊት ተቆልፈው ዋሉ ። ድራማ ከቡዳፔስት ክዋክብቶቹ ከሜዳው ለድል ተዋደቁ ። ከመድፉ ግድግዳ ፊት እንደወትሮው እንደልቡ መንፈላሰስ ለፓሬዚያኑ ብርቅም ሆነ ። የመድፉ ባስ ከፓሬዚያኑ ፊት ፀንቶ ቆመ ። አርቴታ ከመጀመሪያ ቋሚ አሰላለፉ አንስቶ የመረጠው የጨዋታ ስትራቴጂው በአግባቡ ሲያዋጣው ታየ ። የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አውራ ጆዜን መሰለ ። አርሰናል የጣሊያንን አዙሪ ካቴናን አስናቀ ። ፔዤ እንደወትሮው መንቀሳቀስ ተሳነው ። ፓሬዚያኑ የአቻ ጎል ለማግኘት ያውም በፔናሊቲ 65 ደቂቃ ታተሩ ። የመድፉ የደረጀ የመከላከል ቅርፅ የፔዤ የማጥቃት ጥራትን ለአፋልጉኝ ማስታወቂያ አበቃ ። የመድፉ ካቴና ጀገነ ። የመጫወቺያ ቦታ የተነፈጉት የፔዤ ኮኮቦች እንደ ወትሮው ማንፀባረቅ ተሳናቸው ። ዘንድሮ ብቻ በቻምፒዮንስ ሊጉ 44 ጎል አዝንቦ ለቡዳፔስት ፍፃሜ የደረሰው ፔዤ ከመድፉ ግድግዳ ፊት ህይወት ከበደው ። ተጋጣሚዎቹ ላይ እንደ ልቡ በጎሎቹ የሚዘንጠው ፔዤ የአቻዋን ጎል በዴምቤሌ ፔናሊቲ አገኘ ። ፔዤ 75 በመቶ ኳስ ተቆጣጥሮ በዘለቀው ጨዋታ የመድፉ የዳበረ አጥርን መጣስም ተሳነው ። ለጨዋታው ቀልብ ገዢ ፉክክር የሚያዋጣውን የጨዋታ ቅኝት በቡድኑ ዓመቱን ሙሉ በነበረ ጥንካሬ ላይ ተመርኩዞ ተግባራዊ ያደረገው አርቴታ የፓሬዚያኑ የተለመደ ህበረ ትርዒትን አከሰመ ። ፔዤ 21 ወደ ጎል ሞክሮ 4 ብቻ ታርጌታቸውን የጠበቁ ሆኑ ። የመድፉ የፀና የLow Block ኮንክሪትን ጥሶ ማለፍ ለእነ ክቫራ ዴምቤሌ ዱዌ ብርቅ ሆነ ። ተቀይሮ የገባው ብራኮላ የተሻለ ራያን ቀረበ ። ያለ ኳስ ቁጥጥር ተጋጣሚው አርሰናል በጨዋታ መሃል ያለውን ጥንካሬ ከጨዋታው በፊትም የመሰከረው ሉዊስ ኤኔሪኬ ምርጡ ስብስቡ ከመድፉ ኮንክሪት ፊት ከመቼውም ግዜ በላይ የማጥቃት ሀሳቦች ተፋልሰው ታዩ ።
የተፈራው ክቫራ በማስኬራ ተቆለፈ ። ዱዌ ዴምቤሌ ፈዘዙ ። የፔዤ ፍሬ አልባ የኳስ ቁጥጥር ፉርሽ ሆነ ። መከላከል ጀገነ ። አርሰናል ፔዤን አሰረ ። ከሰሜን ለንደን ቡዳፔስት የደረሰው የመድፉ አውቶብስም በjose park the Bus ስታይል ሉዊስ ኤኔሪኬን አቁነጠነጠ ። የመድፉ እንደ አለት የጠነከሩ የፀኑ አጥሮች የሆኑት ማጋሊሽና ሳሊባ በራይስ እና ስኬሊ ሽፋን ለፓሬዚያኑ ፈተና ሆነ ። ጉዳት ያጋጠመው ሄንካፔ ቅያሪ ቀድሞ በጨረሰው አርቴታ እስከመጨረሻው በጀግንነት ተሰዋ ። እንደ ጨዋታ ዕቅዱ ጥሩ አጀማመሩ የመጨረሻዎቹ የጨዋታ ሂደቶች ላይ ጠንቃቃው አርቴታ በቁልፍ የጨዋታው ቅያሪ ውሳኔዎቹ ተፈተነ ። አርቴታ ከ120 ደቂቃ በኋላ ተጋድሎ በኋላ ከመጨረሻው የፔናሊቲ መቺ ምርጫ ውሳኔዎቹ የመዱፉ የክብር ሽንፈት አይረሴው ቁጭት ሆኑ ። ከፔናሊቲው ድራማ በፊት በተጨማሪው 30 ደቂቃ ዴክላን ራይስን ጨርቅ ያስጣለች ማይክ አርቴታን ያሳበደች የሜንዴዝ ማዱኬ ፋወል ከVAR የዳኛው ዕይታ መታለፍ ጋር ሌላው አነጋጋሪም ነበር ። ይህ የመድፉ አርሰናል ወርቃማው የውድድር ዓመት መልክ ነው ። ይህ የፓሬዚያኑ እንደ ልብ ከኳስ ጋር የሚፈነጩ ክዋክብቶችን ከጎሉ ፊት ቆልፎ የዋለው የመድፉ ካቴና ታላቁ ተጋድሎ ነው ። ይህ አርሰናል ወደ ፎሪ እና ወደ ሰማይ በላካቸው ሁለት ፔናሊቲዎች ፀፀት ታጅቦ በጀግንነት እስከ መጨረሻው ተዋድቆ እጅ የሰጠበት የመድፉ የህይወት ከፍታ ጉዞ አሳዛኙ ሌላኛው የቻምፒየንስ ሊግ ምሽት የክብር ገፁ ነው ። ፔዤ ሻምፒዮን ። ናስር አልከሊፋ የፔዤው ቢሊየነር አባት ሉዊስ ኤኔሪኬ ቀምሞ ባወቀረው ቡድናቸው እንደፎከሩት ሁለተኛውን የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ በተከታታይ ድል ነስተዋል ። የፈረንሳይ ሊግም ምስጋና ለፓሬዚያኑ እያለ በድጋሜ በትልቁ የክዋክብቶች መድረክ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ላይ ዳግም ነግሷል ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
መድፉ በክብር ተሸንፏል ! OHO BIG GABI ...
እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች መሃል ! Champions League Classic .
በኤፍሬም የማነ
#ethiopia | በእነዛ ሽርፍራፊ ሰከንዶች የፔናሊቲ ድራማ ራያ ኤዜን አዳነ ። ራያ አርሰናል አዳነ ። መድፉ ሞቶ ተነሳ ። የፔናሊቲው ድራማ ከቡዳፔስት ቀጠለ ። ከሜንዴዝ መሳት በኋላ ፔዤ ብልጫውን ወሰደ ። የመድፉ ለ120 ደቂቃ የዘለቀ የጀግንነት ተጋድሎ በBig Gabi አምስተኛዋ ወሳኝ ፔናሊቲ ላይ ተወሰነ ። መድፈኞቹ ተጨነቁ ። ዓለም በስሜት ከፍ ዝቅ አለ ። የመድፉ የድል አባት አርሴን ቬንገር ከማጋሊሽ ወሳኝ ፔናሊቲ ጋር በጭንቅ ታጥፈው ታዩ ። ንጉስ ኦነሪ በCBS ስቱዱዮ አርሰናል ከተባለ እናት ሀገሩ ጋር በስሜት ተንቆራጠጠ ። ማጋሊሽ በቀጥታ ፔናሊቲ ተመቶበት ካላዳነው የፔዤው በረኛ ሳፋኖቭ ተፈጠጠ ። ፀንቶ ለአርሰናል ድል ሲዋደቅ የዋለው ብራዚላዊ የመድፉ ግድግዳ ወሳኝ ፔናሊቲ በዛች አጋጣሚ ከቡዳፔስት ሰማይ ስር በረረች ። ፔዤ ሻምፒዮን ሆነ ። አርሰናል በጀግንነት ተዋድቆ ተሸነፈ ። እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች ተሞላች ። የፀናው የመድፉ የድል ምኞት ትጋት በመጨረሻ ከብቃት ባሻገር እንደ ሎተሪም በሆነው ፔናሊቲ ታጠፈ ። አርሰናል ሁለት ወደ ፎሪና ሰማይ በለቀቃቸው ፔናሊቲዎች አማካኝነት የህይወት ዘመን ወደር አልባው የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ህልሙን ሳያሳካ ቀረ ። መድፉ በክብር ተሸነፈ ። መድፉ በክብር ተዋድቆ ተረታ ። ከፑሽካሽ አሬና እግር ኳስ በሁለቱ ኋያላን ፍጥጫ ለ120 ደቂቃ ዘልቆ ለፔናሊቲ በተዳረገ የህይወት ገፅ ተመሠለ ። ስሜት ከፍ አለ ። ተስፋ ነገሰ ። መውጣት መውረድ መውደቅ መነሳት ፀፀት ደስታ ቁጭት እንባ ከቡዳፔስት ተፈራረቁ ። ማግኘት ማጣት መሳት ማዳን በሚሊዮኖች ላይ በእነዛ የፔናሊቲ ቅፅበቶች ተፈራረቁ ። በመጨረሻም 120 ደቂቃዎች ተሻግሮ ለፔናሊቲ የደረሰው ድራማ ፓሬዚያኑን ዳግም አነገሰ ። አርሰናል በክብር እጅ የሰጠው አሳዛኙ ተሸናፊ ሆነ ። እግር ኳስ ኳስ ይዞ መሽከርከር ብቻ እንዳልሆነ መድፉ በፀና ተደናቂ የመከላከል ቅርፁ አረጋገጠ ።
በላቀ የጨዋታ ዝግጅነት የዳበረው በታክቲክ የታጠረው ትንቅንቅ የዘመናዊው እግር ኳስ ሁለት የእግር ኳስ ቀለሞችን አሳየ ። እግር ኳስ በመድፉ የመከላከል ከፍታ ውስጥ የፔዤ የማጥቃት አቅምን አፈዘዘ ። ፓሬዚያኑ ከመድፉ ካቴና ፊት ተቆልፈው ዋሉ ። ድራማ ከቡዳፔስት ክዋክብቶቹ ከሜዳው ለድል ተዋደቁ ። ከመድፉ ግድግዳ ፊት እንደወትሮው እንደልቡ መንፈላሰስ ለፓሬዚያኑ ብርቅም ሆነ ። የመድፉ ባስ ከፓሬዚያኑ ፊት ፀንቶ ቆመ ። አርቴታ ከመጀመሪያ ቋሚ አሰላለፉ አንስቶ የመረጠው የጨዋታ ስትራቴጂው በአግባቡ ሲያዋጣው ታየ ። የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አውራ ጆዜን መሰለ ። አርሰናል የጣሊያንን አዙሪ ካቴናን አስናቀ ። ፔዤ እንደወትሮው መንቀሳቀስ ተሳነው ። ፓሬዚያኑ የአቻ ጎል ለማግኘት ያውም በፔናሊቲ 65 ደቂቃ ታተሩ ። የመድፉ የደረጀ የመከላከል ቅርፅ የፔዤ የማጥቃት ጥራትን ለአፋልጉኝ ማስታወቂያ አበቃ ። የመድፉ ካቴና ጀገነ ። የመጫወቺያ ቦታ የተነፈጉት የፔዤ ኮኮቦች እንደ ወትሮው ማንፀባረቅ ተሳናቸው ። ዘንድሮ ብቻ በቻምፒዮንስ ሊጉ 44 ጎል አዝንቦ ለቡዳፔስት ፍፃሜ የደረሰው ፔዤ ከመድፉ ግድግዳ ፊት ህይወት ከበደው ። ተጋጣሚዎቹ ላይ እንደ ልቡ በጎሎቹ የሚዘንጠው ፔዤ የአቻዋን ጎል በዴምቤሌ ፔናሊቲ አገኘ ። ፔዤ 75 በመቶ ኳስ ተቆጣጥሮ በዘለቀው ጨዋታ የመድፉ የዳበረ አጥርን መጣስም ተሳነው ። ለጨዋታው ቀልብ ገዢ ፉክክር የሚያዋጣውን የጨዋታ ቅኝት በቡድኑ ዓመቱን ሙሉ በነበረ ጥንካሬ ላይ ተመርኩዞ ተግባራዊ ያደረገው አርቴታ የፓሬዚያኑ የተለመደ ህበረ ትርዒትን አከሰመ ። ፔዤ 21 ወደ ጎል ሞክሮ 4 ብቻ ታርጌታቸውን የጠበቁ ሆኑ ። የመድፉ የፀና የLow Block ኮንክሪትን ጥሶ ማለፍ ለእነ ክቫራ ዴምቤሌ ዱዌ ብርቅ ሆነ ። ተቀይሮ የገባው ብራኮላ የተሻለ ራያን ቀረበ ። ያለ ኳስ ቁጥጥር ተጋጣሚው አርሰናል በጨዋታ መሃል ያለውን ጥንካሬ ከጨዋታው በፊትም የመሰከረው ሉዊስ ኤኔሪኬ ምርጡ ስብስቡ ከመድፉ ኮንክሪት ፊት ከመቼውም ግዜ በላይ የማጥቃት ሀሳቦች ተፋልሰው ታዩ ።
የተፈራው ክቫራ በማስኬራ ተቆለፈ ። ዱዌ ዴምቤሌ ፈዘዙ ። የፔዤ ፍሬ አልባ የኳስ ቁጥጥር ፉርሽ ሆነ ። መከላከል ጀገነ ። አርሰናል ፔዤን አሰረ ። ከሰሜን ለንደን ቡዳፔስት የደረሰው የመድፉ አውቶብስም በjose park the Bus ስታይል ሉዊስ ኤኔሪኬን አቁነጠነጠ ። የመድፉ እንደ አለት የጠነከሩ የፀኑ አጥሮች የሆኑት ማጋሊሽና ሳሊባ በራይስ እና ስኬሊ ሽፋን ለፓሬዚያኑ ፈተና ሆነ ። ጉዳት ያጋጠመው ሄንካፔ ቅያሪ ቀድሞ በጨረሰው አርቴታ እስከመጨረሻው በጀግንነት ተሰዋ ። እንደ ጨዋታ ዕቅዱ ጥሩ አጀማመሩ የመጨረሻዎቹ የጨዋታ ሂደቶች ላይ ጠንቃቃው አርቴታ በቁልፍ የጨዋታው ቅያሪ ውሳኔዎቹ ተፈተነ ። አርቴታ ከ120 ደቂቃ በኋላ ተጋድሎ በኋላ ከመጨረሻው የፔናሊቲ መቺ ምርጫ ውሳኔዎቹ የመዱፉ የክብር ሽንፈት አይረሴው ቁጭት ሆኑ ። ከፔናሊቲው ድራማ በፊት በተጨማሪው 30 ደቂቃ ዴክላን ራይስን ጨርቅ ያስጣለች ማይክ አርቴታን ያሳበደች የሜንዴዝ ማዱኬ ፋወል ከVAR የዳኛው ዕይታ መታለፍ ጋር ሌላው አነጋጋሪም ነበር ። ይህ የመድፉ አርሰናል ወርቃማው የውድድር ዓመት መልክ ነው ። ይህ የፓሬዚያኑ እንደ ልብ ከኳስ ጋር የሚፈነጩ ክዋክብቶችን ከጎሉ ፊት ቆልፎ የዋለው የመድፉ ካቴና ታላቁ ተጋድሎ ነው ። ይህ አርሰናል ወደ ፎሪ እና ወደ ሰማይ በላካቸው ሁለት ፔናሊቲዎች ፀፀት ታጅቦ በጀግንነት እስከ መጨረሻው ተዋድቆ እጅ የሰጠበት የመድፉ የህይወት ከፍታ ጉዞ አሳዛኙ ሌላኛው የቻምፒየንስ ሊግ ምሽት የክብር ገፁ ነው ። ፔዤ ሻምፒዮን ። ናስር አልከሊፋ የፔዤው ቢሊየነር አባት ሉዊስ ኤኔሪኬ ቀምሞ ባወቀረው ቡድናቸው እንደፎከሩት ሁለተኛውን የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ በተከታታይ ድል ነስተዋል ። የፈረንሳይ ሊግም ምስጋና ለፓሬዚያኑ እያለ በድጋሜ በትልቁ የክዋክብቶች መድረክ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ላይ ዳግም ነግሷል ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
በደርግ ዘመነ መንግሥት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመምራት የሚታወቁት አቶ ካሳ ገብሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው።
ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።
ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል።
በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል።
የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል።
የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ።
በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ።
አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል።
አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።
በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው።
ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።
ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል።
በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል።
የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል።
የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ።
በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ።
አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል።
አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።
በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል ሶላት በመጠናቀቁ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶች ተከፍተዋል
#ethiopia | የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሶላት ስነ- ስርዓት አካሂደዋል።
የኃይማኖት አባቶች እና የእምነቱ ተከታዮች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የሶላት ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡
የሶላት ስነ-ስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ተብሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶቸ መከፈታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋፆኦ ላደረጉ አካላት፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና አባላት ዋና ጠቅላይ መምሪያው ምስጋናውን በማቅረብ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሠላም እና የደስታ እንዲሆንም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሶላት ስነ- ስርዓት አካሂደዋል።
የኃይማኖት አባቶች እና የእምነቱ ተከታዮች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የሶላት ፕሮግራም ተጠናቋል፡፡
የሶላት ስነ-ስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ተብሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶቸ መከፈታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋፆኦ ላደረጉ አካላት፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና አባላት ዋና ጠቅላይ መምሪያው ምስጋናውን በማቅረብ ለመላው የእምነቱ ተከታዮች በዓሉ የሠላም እና የደስታ እንዲሆንም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀዳሚው ተወዳጅ የፋይናንስ ተቋም ተብሎ ተመረጠ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገሪቱ ቀዳሚው ተወዳጅ የፋይናንስ ተቋም ተብሎ መመረጡን ብራንድ አፍሪካ (Brand Africa) ይፋ አድርጓል።
ተቋሙ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የእንኳን ደስ አለዎት ይፋዊ ደብዳቤ ልኳል።
ይህ ዓመታዊ የ"Africa's Best Brands" የሽልማት ስነ-ስርዓት ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደ ልዩ መርሃ-ግብር ላይ ይፋ ያደረገ ሲሆን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክቱን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትን በመወከል የባንኩ የኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አልሰን አሰፋ ተቀብለዋል።
ጥናቱን ያካሄደው ብራንድ አፍሪካ ከአፍሪካ ቢዝነስ መጽሔት እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ሲሆን፣ በ30 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ከ85% በላይ የሚሆነውን የአህጉሪቱን ህዝብ እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሸፈነ ጥናት መሆኑ ተገልጿል። በጂኦፖል (GeoPoll) አማካኝነት በተሰበሰበው ይፋዊ መረጃ መሰረት ከ5,947 በላይ ልዩ ልዩ ብራንዶች በጥናቱ ውስጥ ተካትቷል።
በውጤቱ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሸማቾች ዘንድ ያለውን ጠንካራ ተቀባይነት ፣ የህዝብ እምነት እና የፋይናንስ መሪነት ለሽልማት እንዳበቃው በመድረኩ ተገልጿል።
በ2010 እ.ኤ.አ. የተመሰረተው ብራንድ አፍሪካ የአህጉሪቱን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ አፍሪካን እርስ በእርስ ለማገናኘት እና ለቀጣናው አዎንታዊ ገጽታን ለመገንባት በብራንድ-መር የአፍሪካ ህዳሴን ለማነሳሳት የተቋቋመ የትውልዶች ንቅናቄ ነው።
በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩት ተቋማትን ተመሳሳይ የ"Africa's Best Brands" ሽልማት በመስጠት የ16 ዓመታት ልምድ አካብቷል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትና የማኔጅመንት አባላት በተገኘው ውጤት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አለን መልእክት አስተላልፈዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc #cbe
#ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገሪቱ ቀዳሚው ተወዳጅ የፋይናንስ ተቋም ተብሎ መመረጡን ብራንድ አፍሪካ (Brand Africa) ይፋ አድርጓል።
ተቋሙ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የእንኳን ደስ አለዎት ይፋዊ ደብዳቤ ልኳል።
ይህ ዓመታዊ የ"Africa's Best Brands" የሽልማት ስነ-ስርዓት ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደ ልዩ መርሃ-ግብር ላይ ይፋ ያደረገ ሲሆን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክቱን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትን በመወከል የባንኩ የኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አልሰን አሰፋ ተቀብለዋል።
ጥናቱን ያካሄደው ብራንድ አፍሪካ ከአፍሪካ ቢዝነስ መጽሔት እና ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ሲሆን፣ በ30 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ከ85% በላይ የሚሆነውን የአህጉሪቱን ህዝብ እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሸፈነ ጥናት መሆኑ ተገልጿል። በጂኦፖል (GeoPoll) አማካኝነት በተሰበሰበው ይፋዊ መረጃ መሰረት ከ5,947 በላይ ልዩ ልዩ ብራንዶች በጥናቱ ውስጥ ተካትቷል።
በውጤቱ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሸማቾች ዘንድ ያለውን ጠንካራ ተቀባይነት ፣ የህዝብ እምነት እና የፋይናንስ መሪነት ለሽልማት እንዳበቃው በመድረኩ ተገልጿል።
በ2010 እ.ኤ.አ. የተመሰረተው ብራንድ አፍሪካ የአህጉሪቱን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ፣ አፍሪካን እርስ በእርስ ለማገናኘት እና ለቀጣናው አዎንታዊ ገጽታን ለመገንባት በብራንድ-መር የአፍሪካ ህዳሴን ለማነሳሳት የተቋቋመ የትውልዶች ንቅናቄ ነው።
በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩት ተቋማትን ተመሳሳይ የ"Africa's Best Brands" ሽልማት በመስጠት የ16 ዓመታት ልምድ አካብቷል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንትና የማኔጅመንት አባላት በተገኘው ውጤት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእንኳን ደስ አለን መልእክት አስተላልፈዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc #cbe
9 days ago
“ የአርቴታ ንግግር ግልጽ ትዕቢት ነው ” ሮይ ኪን
#ethiopia | የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል አባላት የግል የውስጥ የደስታ ዝግጅት አዘጋጅተው ነበር።
በዝግጅቱ ላይ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ለድግሱ ታዳሚያን ያደረጉት ንግግር ሾልኮ ወጥቷል።
አሰልጣኙ ባሰሙት ንግግር “ ቅዳሜ ደግሞ በእርግጠኝነት የአውሮፓ ሻምፒዮን እንሆናለን “ ሲሉ ይደመጣሉ።
የአርቴታ ንግግር ቪዲዮ በኋላም እንዲጠፋ ቢደረግም በርካቶች ተቀባብለውት በማህበራዊ ሚዲያው በስፋት ተሰራጭቷል።
በክለቡ ውስጥ አርቴታ ስህተት ሰርተዋል የሚል እምነት ባይኖርም ንግግሩ የፒኤስጂ ተጨዋቾች ጋር ደርሶ ተጨማሪ ተነሳሽነት ይፈጥርላቸዋል የሚል እምነት እንዳለ ተገልጿል።
በዚህም የአርቴታ ንግግር የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ታሪካዊ ተጨዋች ሮይ ኪን ሾልኮ የወጣውን የሚኬል አርቴታ ንግግር " ትዕቢት " ሲል ገልጿል።
“ ግልጽ ትዕቢት ነው ” ሲል የገለፀው ሮይ ኪን ” እኔ በፒኤስጂ ቦታ ብሆን እና ይሄን ንግግር ብሰማ ወዲያው ነበር የመልበሻ ቤቱ ግድግዳ ላይ የምፅፈው " ሲል ተናግሯል።
አክሎም “ አርቴታ ለእነሱ ነፀ የማነቃቂያ ንግግር አበርክቶላቸዋል “ ሲል ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport
#ethiopia | የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አርሰናል አባላት የግል የውስጥ የደስታ ዝግጅት አዘጋጅተው ነበር።
በዝግጅቱ ላይ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ለድግሱ ታዳሚያን ያደረጉት ንግግር ሾልኮ ወጥቷል።
አሰልጣኙ ባሰሙት ንግግር “ ቅዳሜ ደግሞ በእርግጠኝነት የአውሮፓ ሻምፒዮን እንሆናለን “ ሲሉ ይደመጣሉ።
የአርቴታ ንግግር ቪዲዮ በኋላም እንዲጠፋ ቢደረግም በርካቶች ተቀባብለውት በማህበራዊ ሚዲያው በስፋት ተሰራጭቷል።
በክለቡ ውስጥ አርቴታ ስህተት ሰርተዋል የሚል እምነት ባይኖርም ንግግሩ የፒኤስጂ ተጨዋቾች ጋር ደርሶ ተጨማሪ ተነሳሽነት ይፈጥርላቸዋል የሚል እምነት እንዳለ ተገልጿል።
በዚህም የአርቴታ ንግግር የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ታሪካዊ ተጨዋች ሮይ ኪን ሾልኮ የወጣውን የሚኬል አርቴታ ንግግር " ትዕቢት " ሲል ገልጿል።
“ ግልጽ ትዕቢት ነው ” ሲል የገለፀው ሮይ ኪን ” እኔ በፒኤስጂ ቦታ ብሆን እና ይሄን ንግግር ብሰማ ወዲያው ነበር የመልበሻ ቤቱ ግድግዳ ላይ የምፅፈው " ሲል ተናግሯል።
አክሎም “ አርቴታ ለእነሱ ነፀ የማነቃቂያ ንግግር አበርክቶላቸዋል “ ሲል ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport
9 days ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ የመስጠት መብት ለሁሉም የሀገሪቱ የንግድ ባንኮች መፍቀዱን አስታወቀ
#ethiopia | ቀደም ሲል ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ (Export Permit) የመስጠት ስልጣን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው አሰራር ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል።
ማዕከላዊ ባንኩ ይህንን እርምጃ የወሰደው በወጪ ንግድ ላይ ያሉ ቢሮክራሲዎችን ለማቃለል፣ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለመጨመር እና ለላኪዎች ምቹና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ነው።
ሁሉም ፈቃድ ያላቸው የንግድ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ ከተለመዱት የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሬ መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ አገልግሎቱን ለደንበኞቻቸው መስጠት እንዲጀምሩ በጥብቅ ታዟል።
ይህ አዲስ መመሪያ ላኪዎች የመረጡት ባንክ ዘንድ ሄደው ጉዳያቸውን እንዲያስፈጽሙ በር የሚከፍት በመሆኑ፣ የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በእጅጉ ያነቃቃል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የኢትዮጵያብሔራዊባንክ #የወጪንግድ #ቻይና #ኢትዮጵያ #ባንክ #ቢዝነስ #ethiopianeconomy #nbe
#ethiopia | ቀደም ሲል ወደ ቻይና ለሚላኩ ምርቶች የወጪ ንግድ ፈቃድ (Export Permit) የመስጠት ስልጣን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው አሰራር ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል።
ማዕከላዊ ባንኩ ይህንን እርምጃ የወሰደው በወጪ ንግድ ላይ ያሉ ቢሮክራሲዎችን ለማቃለል፣ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለመጨመር እና ለላኪዎች ምቹና ፈጣን የባንክ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ነው።
ሁሉም ፈቃድ ያላቸው የንግድ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ ከተለመዱት የወጪ ንግድና የውጭ ምንዛሬ መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ አገልግሎቱን ለደንበኞቻቸው መስጠት እንዲጀምሩ በጥብቅ ታዟል።
ይህ አዲስ መመሪያ ላኪዎች የመረጡት ባንክ ዘንድ ሄደው ጉዳያቸውን እንዲያስፈጽሙ በር የሚከፍት በመሆኑ፣ የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ በእጅጉ ያነቃቃል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የኢትዮጵያብሔራዊባንክ #የወጪንግድ #ቻይና #ኢትዮጵያ #ባንክ #ቢዝነስ #ethiopianeconomy #nbe
9 days ago
የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የሀገረ-መንግሥት ሥርዓታችን መሠረት ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓት የሚጠነክርበትና የዴሞክራሲ ልምምድ አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ነው።
የዐረፋ በዓል ማኅበረሰባዊ በዓል መሆኑን፣ ሰዎች በግላቸው ሳይሆን ከቤተሰብ፣ ጎረቤትና ማኅበረሰብ ጋር በመተሳሰብና በመተጋገዝ የሚያከብሩት መሆኑን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ማኅበራዊ ትስስር ለዜጎችና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
ከዚሁ ማኅበራዊ ኃላፊነት ጋር በማያያዝም ምርጫን ዋነኛው የማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታ መወጫ መሣሪያ አድርገው አቅርበውታል።
"ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መጪው ምርጫ ብዝሃ-ድምፅ የሚሰማበትና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የሚመሰረትበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝበ ሙስሊም በዓሉን ሲያከብር ማኅበራዊ ግዴታውን በመወጣት ብቻ ሳይወሰን፣ በመጪው ምርጫ በድምፅ መስጫ ካርዱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለማረጋገጥ ዝግጅት እንዲያደርግ ሀገራዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #pmabiyahmed #democracy #ethiopianelection #civicduty #ethiopianbroadcastingcorporation
#ethiopia | የዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓት የሚጠነክርበትና የዴሞክራሲ ልምምድ አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት ወሳኝ አጋጣሚ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ላይ ነው።
የዐረፋ በዓል ማኅበረሰባዊ በዓል መሆኑን፣ ሰዎች በግላቸው ሳይሆን ከቤተሰብ፣ ጎረቤትና ማኅበረሰብ ጋር በመተሳሰብና በመተጋገዝ የሚያከብሩት መሆኑን ያወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ማኅበራዊ ትስስር ለዜጎችና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
ከዚሁ ማኅበራዊ ኃላፊነት ጋር በማያያዝም ምርጫን ዋነኛው የማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታ መወጫ መሣሪያ አድርገው አቅርበውታል።
"ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ መጪው ምርጫ ብዝሃ-ድምፅ የሚሰማበትና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት የሚመሰረትበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን አብራርተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝበ ሙስሊም በዓሉን ሲያከብር ማኅበራዊ ግዴታውን በመወጣት ብቻ ሳይወሰን፣ በመጪው ምርጫ በድምፅ መስጫ ካርዱ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለማረጋገጥ ዝግጅት እንዲያደርግ ሀገራዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #pmabiyahmed #democracy #ethiopianelection #civicduty #ethiopianbroadcastingcorporation
Sponsored by
Surafel
9 days ago
ቢሊየነሮች ወደ ውጪ ማየት ጀመሩ
#ethiopia | በሕንድ የአገር ውስጥ
የኢኮኖሚ ዕድገት ፍጥነት መቀነሱንና የንግድ እንቅስቃሴው መዳከሙን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ታዋቂ ቢሊየነሮች በውጭ አገራት የሚገኙ ትልልቅ ኩባንያዎችን በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በስፋት በመግዛት ላይ ይገኛሉ።
የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ የሕንዳውያን ባለሀብቶች ከፍተኛ የካፒታል ሽግግር በአገር ውስጥ ሊገጥማቸው የሚችለውን የገበያ ስጋት ለመቀነስና አዳዲስ ዓለም አቀፍ የቢዝነስ ዕድሎችን ለመጠቀም ያለመ መሆኑን ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#indiaeconomy #globalbusiness #billionaires #investment Shift #economicgrowth #bbcnews #marketexpansion
#ethiopia | በሕንድ የአገር ውስጥ
የኢኮኖሚ ዕድገት ፍጥነት መቀነሱንና የንግድ እንቅስቃሴው መዳከሙን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ታዋቂ ቢሊየነሮች በውጭ አገራት የሚገኙ ትልልቅ ኩባንያዎችን በከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በስፋት በመግዛት ላይ ይገኛሉ።
የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ የሕንዳውያን ባለሀብቶች ከፍተኛ የካፒታል ሽግግር በአገር ውስጥ ሊገጥማቸው የሚችለውን የገበያ ስጋት ለመቀነስና አዳዲስ ዓለም አቀፍ የቢዝነስ ዕድሎችን ለመጠቀም ያለመ መሆኑን ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#indiaeconomy #globalbusiness #billionaires #investment Shift #economicgrowth #bbcnews #marketexpansion
9 days ago
የነፍስ ተናፋቂው ጥሪ፤ ሐጅ የሙስሊሞች የሕይወት ዘመን ታላቅ መንፈሳዊ ሕልምና የዒባዳ ማዕዘን
#ethiopia | ሐጅ... የአላህ (ሱ.ወ) ቤት ወደሆነችውና የሙዕሚኖች ልብ ዘወትር ወደምትናፍቃት ቅድስት መካ የሚደረግ፣ በአካል ለቻለና አቅም ላለው ሙስሊም ሁሉ በሕይወት ዘመን አንድ ጊዜ የመፈጸም ግዴታ ያለበት አምስተኛው የእስልምና ማዕዘን ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ የግል መንፈሳዊ ጥንካሬን ማደሻ ብቻ ሳይሆን፣ የታማኝነት እና የዓለም አቀፋዊ የእስልምና አንድነት ከፍተኛ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ምድራዊ ማዕረግና የሀብት ልዩነትን ሁሉ አውልቀው፣ ተመሳሳይ ነጭ ኢሕራም ለብሰው በአንድነት ሲቆሙ ፍጹም የእኩልነት እና የወንድማማችነት ትርጉም በተግባር ይገለጻል።
ይህ ሥርዓት ከዘመናት በፊት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩትን መንገዶች በመከተል የሚከናወን ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተግባር ከነቢዩ ኢብራሂምና (ረ.ወ) ከነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ጋር የተያያዘ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው።
ጉዞው በእስልምና የጨረቃ አቆጣጠር 12ኛው ወር "ዙል-ሒጃ" ላይ የሚፈጸም ሲሆን፣ የጨረቃ አቆጣጠር ከግሪጎሪያን አቆጣጠር ጋር ሲነጻጸር በየዓመቱ ወደ 11 ቀናት ገደማ ወደ ኋላ ስለሚሽከረከር የሐጅ ወቅት በተለያዩ የአየር ንብረቶች (በበጋ፣ በክረምትና በጸደይ) ላይ እንዲያርፍ ያደርገዋል።
የዚህ ታላቅ የሐጅ ሥርዓት ማጠናቀቂያ በመላው ዓለም በታላቅ ድምቀት በሚከበረው ዒድ አል-አድሃ (የአረፋ በዓል) ላይ ይደርሳል።
አማኞች መስዋዕት በማቅረብ፣ ያረዱትን አንድ ሦስተኛ ለቤተሰቦቻቸው፣ አንድ ሦስተኛ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ቀሪውን አንድ ሦስተኛ ለድሆች በማካፈል አጋርነታቸውንና እስላማዊ ፍቅራቸውን ይገልጻሉ።
በአካል ደክሞ በመንፈስ ታድሶ የሚመለስበት ሐጅ የትዕግስት፣ የትሕትናና የአንድነት ትምህርት ቤት ነው። አላህ (ሱ.ወ) ለሁላችንም ይህንን የአላህን ምሕረትና በረከት የምንቀበልበትን ልዩ የሕይወት አጋጣሚ ይወፍቀን።
በኢቲሃድ አብራር(ebc)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #hajj #makkah #eidaladha #islam #muslimummah #faith
#ethiopia | ሐጅ... የአላህ (ሱ.ወ) ቤት ወደሆነችውና የሙዕሚኖች ልብ ዘወትር ወደምትናፍቃት ቅድስት መካ የሚደረግ፣ በአካል ለቻለና አቅም ላለው ሙስሊም ሁሉ በሕይወት ዘመን አንድ ጊዜ የመፈጸም ግዴታ ያለበት አምስተኛው የእስልምና ማዕዘን ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ የግል መንፈሳዊ ጥንካሬን ማደሻ ብቻ ሳይሆን፣ የታማኝነት እና የዓለም አቀፋዊ የእስልምና አንድነት ከፍተኛ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ምድራዊ ማዕረግና የሀብት ልዩነትን ሁሉ አውልቀው፣ ተመሳሳይ ነጭ ኢሕራም ለብሰው በአንድነት ሲቆሙ ፍጹም የእኩልነት እና የወንድማማችነት ትርጉም በተግባር ይገለጻል።
ይህ ሥርዓት ከዘመናት በፊት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩትን መንገዶች በመከተል የሚከናወን ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተግባር ከነቢዩ ኢብራሂምና (ረ.ወ) ከነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ጋር የተያያዘ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው።
ጉዞው በእስልምና የጨረቃ አቆጣጠር 12ኛው ወር "ዙል-ሒጃ" ላይ የሚፈጸም ሲሆን፣ የጨረቃ አቆጣጠር ከግሪጎሪያን አቆጣጠር ጋር ሲነጻጸር በየዓመቱ ወደ 11 ቀናት ገደማ ወደ ኋላ ስለሚሽከረከር የሐጅ ወቅት በተለያዩ የአየር ንብረቶች (በበጋ፣ በክረምትና በጸደይ) ላይ እንዲያርፍ ያደርገዋል።
የዚህ ታላቅ የሐጅ ሥርዓት ማጠናቀቂያ በመላው ዓለም በታላቅ ድምቀት በሚከበረው ዒድ አል-አድሃ (የአረፋ በዓል) ላይ ይደርሳል።
አማኞች መስዋዕት በማቅረብ፣ ያረዱትን አንድ ሦስተኛ ለቤተሰቦቻቸው፣ አንድ ሦስተኛ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ቀሪውን አንድ ሦስተኛ ለድሆች በማካፈል አጋርነታቸውንና እስላማዊ ፍቅራቸውን ይገልጻሉ።
በአካል ደክሞ በመንፈስ ታድሶ የሚመለስበት ሐጅ የትዕግስት፣ የትሕትናና የአንድነት ትምህርት ቤት ነው። አላህ (ሱ.ወ) ለሁላችንም ይህንን የአላህን ምሕረትና በረከት የምንቀበልበትን ልዩ የሕይወት አጋጣሚ ይወፍቀን።
በኢቲሃድ አብራር(ebc)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #hajj #makkah #eidaladha #islam #muslimummah #faith
9 days ago
ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ አራተኛው ኩባንያ ሆኖ ተመዘገበ።
#ethiopia | ተቋሙ በዚህ ገበያ ላይ መመዝገቡን ይፋ ያደረገው ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ጋር በመተባበር በሰጠው የጋራ መግለጫ ነው።
እስካሁን በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ብቸኛው የተደራጀ የካፒታል ማርኬት የሆነው እና በመንግሥትና በግል አጋርነት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ በይፋ ተመዝግበው ተሳታፊ የሆኑት ሦስት የፋይናንስ ተቋማት ብቻ ነበሩ።
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋም በሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መድረክ ላይ ከመመዝገቡ አስቀድሞ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖቹን ለሽያጭ ገበያ አውጥቶ ነበር።
ኩባንያው ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣው መግለጫ ለአራት ወራት ያህል ክፍት ሆኖ በቆየው በዚህ የሽያጭ ሂደት ለሽያጭ ካቀረበው የ10 በመቶ የኩባንያው ድርሻ ውስጥ 10.7 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ብቻ የተሸጡ ሲሆን፤ቀሪዎቹ 89.3 ሚሊዮን አክሲዮኖች ግን ሳይሸጡ ቀርተዋል።
በተመሳሳይ ተቋሙ ከአክሲዮን ሽያጩ 30 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም ማሳካት የቻለው ግን 3.2 ቢሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።
በዚህ የሽያጭ ሂደት ላይ ከ47 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን አክሲዮን መግዛታቸውን ተቋሙ አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ዜጎች ውስጥ 45,336 የሚሆኑት “የባለቤትነት ማረጋገጫ” እና “አክሲዮኖችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሂደታቸውን ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቃቸው በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገልጿል።
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሂደታቸውን ያጠናቀቁ ዜጎች አክሲዮኖች በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መሆናቸውንም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ባለሀብቶች ውስጥ 3.7 በመቶ የሚሆኑት የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ባለማቅረባቸው እና ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው በመሆኑ፤ ለአክሲዮን ግዢ የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንደሚደረግላቸው የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ተቋሙ በዚህ ገበያ ላይ መመዝገቡን ይፋ ያደረገው ከኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ጋር በመተባበር በሰጠው የጋራ መግለጫ ነው።
እስካሁን በሀገሪቱ የመጀመሪያውና ብቸኛው የተደራጀ የካፒታል ማርኬት የሆነው እና በመንግሥትና በግል አጋርነት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ ላይ በይፋ ተመዝግበው ተሳታፊ የሆኑት ሦስት የፋይናንስ ተቋማት ብቻ ነበሩ።
መንግስታዊው የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ ተቋም በሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ መድረክ ላይ ከመመዝገቡ አስቀድሞ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖቹን ለሽያጭ ገበያ አውጥቶ ነበር።
ኩባንያው ባለፈው ሚያዝያ ወር ባወጣው መግለጫ ለአራት ወራት ያህል ክፍት ሆኖ በቆየው በዚህ የሽያጭ ሂደት ለሽያጭ ካቀረበው የ10 በመቶ የኩባንያው ድርሻ ውስጥ 10.7 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ብቻ የተሸጡ ሲሆን፤ቀሪዎቹ 89.3 ሚሊዮን አክሲዮኖች ግን ሳይሸጡ ቀርተዋል።
በተመሳሳይ ተቋሙ ከአክሲዮን ሽያጩ 30 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም ማሳካት የቻለው ግን 3.2 ቢሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።
በዚህ የሽያጭ ሂደት ላይ ከ47 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን አክሲዮን መግዛታቸውን ተቋሙ አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ዜጎች ውስጥ 45,336 የሚሆኑት “የባለቤትነት ማረጋገጫ” እና “አክሲዮኖችን ወደ ዲጂታል የመቀየር ሂደታቸውን ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቃቸው በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተገልጿል።
የባለቤትነት ማረጋገጫ ሂደታቸውን ያጠናቀቁ ዜጎች አክሲዮኖች በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መሆናቸውንም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።
አክሲዮን ከገዙ ባለሀብቶች ውስጥ 3.7 በመቶ የሚሆኑት የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ባለማቅረባቸው እና ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌላቸው በመሆኑ፤ ለአክሲዮን ግዢ የከፈሉት ገንዘብ ተመላሽ እንደሚደረግላቸው የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ