8 hours ago
“በህዳሴ ግድቡ ያሳረፍነውን አሻራ በሀገራዊ ምክክሩም እንደግማለን”
********************
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያሳዩትን የታሪክ አሻራ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ በመድገም ጠንካራ ሀገር በመገንባት ለትውልድ ለማስተላለፍ የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ በምክክር ጉባኤው ላይ እየተመካከሩ የሚገኙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጎብኘት የተሰማቸውን ደስታና ኩራት ገልፀዋል፡፡
ከሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ የመጡት ተመካካሪ አድጎልኝ መኮንን በሰጡት አስተያየት፤ ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኛ በነበሩበት ወቅት የ400 ብር ቦንድ ገዝተው አስተዋጽኦ ያደረጉበት ግድብ ተጠናቆ በማየታቸው ጥልቅ የደስታ ስሜት እንደተሰማቸው ተናግረዋል።
"ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል" መባሉ ቀርቶ ዛሬ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ትልቅ የብርሃን ምንጭ መሆን መቻሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
አሁን ደግሞ ከመላ ኢትዮጵያና ከውጭ ሀገር የተውጣጡ አራት ሺህ ዜጎች በመካከር ላይ መሆናቸውን አውስተው፤ በምክክር ጉባኤው ላይ ስለሀገራቸው ጉዳይ በነጻነት የሚመካከሩበትን ትልቅ ታሪካዊ ዕድል ለመጀመሪያ ጊዜ አግኝተናል ሲሉ ገልፀዋል።
ዜጎች በመመካከር ጠንካራ ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚደረገው የሰለጠነ የምክክር ሂደት የሚያስደስት ሆኖ እንዳገኙትም ጠቅሰዋል፡፡
ከሰዊድን የመጡት ተመካካሪ መቅደስ ወርቁ በበኩላቸው፤ በግድቡ ግንባታ ወቅት በውጭ ሀገር ሲያስተባብሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ አሁን ግድቡ ተጠናቆ በአካል ማየት በመቻላቸው ደስታና ኩራት እንደተሰማቸው ተናግረዋል።
በግድቡ የተሰራው ድንቅ ተግባር የኢትዮጵያውያንን ገድል እና ዳግማዊ ዓድዋ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ከእንግሊዝ ሀገር የመጡት ተመካካሪ ኡስታዝ ሙክታር ጀማል፣ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉብኝት ወቅት የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል።
ከካናዳ ቶሮንቶ የመጡት ተመካካሪ ጌትነት ሃይሉ በበኩላቸው፤ በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የወር ደመወዛቸውን ሳይቀር በማዋጣት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
በግድቡ ግንባታ ወቅት ዓለም አቀፍ ተቋማት ብድር በመከልከል ጫና ቢፈጥሩም፣ ኢትዮጵያውያን ግን በጋራ በመተባበር ግድቡን በራሳቸው አቅም መገንባታቸው ታሪካዊ ድል መሆኑን መናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
በአሁኑ ወቅት ለትውልድ ጠንካራ ሀገር ለማስተላለፍ የሚያስችላቸውን የምክክር ሂደት መሳተፍ በመቻላቸውም ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
የምክክር ሂደቱ ውጤት አብሮነታችንን በማጽናት በተጠናከረ መልኩ በጋራ ለልማት መነሳሳት እንደሚቻል እምነታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ቦንድ በመግዛት፣ በስጦታ እና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስለግድቡ በመከራከር ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ግድቡ የኤሌትሪክ ሃይል ያልደረሳቸው ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ ለከባድ ኢንዱስትሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በንጋት ሐይቅ ዙሪያ የተፈጠሩትን ደሴቶች እና የቱሪዝም ፀጋዎች በመመልከት በቱሪዝም ኢንቨስትመንት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
********************
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያሳዩትን የታሪክ አሻራ በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ በመድገም ጠንካራ ሀገር በመገንባት ለትውልድ ለማስተላለፍ የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉ በምክክር ጉባኤው ላይ እየተመካከሩ የሚገኙ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በመሳተፍ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጎብኘት የተሰማቸውን ደስታና ኩራት ገልፀዋል፡፡
ከሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ የመጡት ተመካካሪ አድጎልኝ መኮንን በሰጡት አስተያየት፤ ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኛ በነበሩበት ወቅት የ400 ብር ቦንድ ገዝተው አስተዋጽኦ ያደረጉበት ግድብ ተጠናቆ በማየታቸው ጥልቅ የደስታ ስሜት እንደተሰማቸው ተናግረዋል።
"ዓባይ ግንድ ይዞ ይዞራል" መባሉ ቀርቶ ዛሬ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ትልቅ የብርሃን ምንጭ መሆን መቻሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
አሁን ደግሞ ከመላ ኢትዮጵያና ከውጭ ሀገር የተውጣጡ አራት ሺህ ዜጎች በመካከር ላይ መሆናቸውን አውስተው፤ በምክክር ጉባኤው ላይ ስለሀገራቸው ጉዳይ በነጻነት የሚመካከሩበትን ትልቅ ታሪካዊ ዕድል ለመጀመሪያ ጊዜ አግኝተናል ሲሉ ገልፀዋል።
ዜጎች በመመካከር ጠንካራ ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚደረገው የሰለጠነ የምክክር ሂደት የሚያስደስት ሆኖ እንዳገኙትም ጠቅሰዋል፡፡
ከሰዊድን የመጡት ተመካካሪ መቅደስ ወርቁ በበኩላቸው፤ በግድቡ ግንባታ ወቅት በውጭ ሀገር ሲያስተባብሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ አሁን ግድቡ ተጠናቆ በአካል ማየት በመቻላቸው ደስታና ኩራት እንደተሰማቸው ተናግረዋል።
በግድቡ የተሰራው ድንቅ ተግባር የኢትዮጵያውያንን ገድል እና ዳግማዊ ዓድዋ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
ከእንግሊዝ ሀገር የመጡት ተመካካሪ ኡስታዝ ሙክታር ጀማል፣ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉብኝት ወቅት የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል።
ከካናዳ ቶሮንቶ የመጡት ተመካካሪ ጌትነት ሃይሉ በበኩላቸው፤ በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የወር ደመወዛቸውን ሳይቀር በማዋጣት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
በግድቡ ግንባታ ወቅት ዓለም አቀፍ ተቋማት ብድር በመከልከል ጫና ቢፈጥሩም፣ ኢትዮጵያውያን ግን በጋራ በመተባበር ግድቡን በራሳቸው አቅም መገንባታቸው ታሪካዊ ድል መሆኑን መናገራቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።
በአሁኑ ወቅት ለትውልድ ጠንካራ ሀገር ለማስተላለፍ የሚያስችላቸውን የምክክር ሂደት መሳተፍ በመቻላቸውም ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል።
የምክክር ሂደቱ ውጤት አብሮነታችንን በማጽናት በተጠናከረ መልኩ በጋራ ለልማት መነሳሳት እንደሚቻል እምነታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ፤ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ቦንድ በመግዛት፣ በስጦታ እና በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ስለግድቡ በመከራከር ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል።
በአሁኑ ወቅት ግድቡ የኤሌትሪክ ሃይል ያልደረሳቸው ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ ለከባድ ኢንዱስትሪዎች እና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠሩን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በንጋት ሐይቅ ዙሪያ የተፈጠሩትን ደሴቶች እና የቱሪዝም ፀጋዎች በመመልከት በቱሪዝም ኢንቨስትመንት እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
23 hours ago
ጽኑ የሕዝብ አንድነት እና ብቁ የጸጥታ ተቋማት፡ የኢትዮጵያ ከፍታ ዋስትና
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ሥርዓተ መንግሥት ያላት ታላቅ ሀገር በመሆኗ ምንም ዓይነት የጥፋት ኃይል ሰላሟን በቀላሉ ማናጋት እንደማይችል በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
ኢትዮጵያ የሚለው ስም ለችግሮች አለመንበርከክ፣ በፈተና ሳይበገሩ የማለፍ እና እንቅፋቶችን ተሻግሮ ድል የማድረግ የክብር ማህተም ነው።
ሀገራችን በታሪኳ ያለፈተና ያሳለፈቻቸው ዘመናት እጅግ ጥቂት ቢሆኑም፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ታሪካዊ ክብራችንን እያስጠበቅን ነው።
በተለይም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ወደ ኋላ የማይደራደር ጠንካራ መንግሥት መኖሩን የተረዱ በዓባይና በአፍሪካ ቀንድ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የጥፋት ናዳቸውን ሲያወርዱ ቆይተዋል።
ሆኖም እነዚህ የክፋት ኃይላት በሀገራችን ላይ የሚረባረቡት መጪውን ብሩህ ዘመናችንን አይተው እንጂ ተስፋ ቢስ ድሆች መሆናችን አስጨንቋቸው አይደለም።
ዓላማ የሌላቸው አጥፊዎች የሚያደርሱትን የውስጥ ፈተና እና የውጭ ጫና ተቋቁመን በድል ላይ ድል የምንቀዳጀውም በሕዝባችን አንድነት እና በጸጥታ ተቋሞቻችን ብቃት ነው።
ይህ የጸጥታ ተቋማት ብቃት ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከተከናወኑ መጠነ-ሰፊ ሀገራዊ ሪፎርሞች የተገኘ ፍሬ ነው።
ተቋማቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት የጸዱ፣ ለሕገ-መንግሥቱና ለሕዝብ ብቻ ታማኝ የሆኑ እንዲሁም የሀገራችንን ሉዓላዊነት በጽናት የሚያስጠብቁ ሆነው ተገንብተዋል።
በዚህም መሠረት የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአየር ኃይል የላቁ የረጅም ርቀት ሚሳኤሎችን እና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስልታዊ ድሮኖችን በመታጠቅ የአየር ክልላችንን ፍጹም የማይደፈር አድርገውታል።
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይልም የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም እና ቀጣናዊ ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ ሌት ተቀን እየተጋ የሚገኝ ተቋም ሆኗል።
የዘመኑ ጦርነት በቴክኖሎጂ የሚመራ በመሆኑ በሳይበር ምህዳር ሀገርን ለመጠበቅ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር እንዲሁም ስትራቴጂያዊ መረጃዎችን አስቀድሞ በመተንተን ሴራዎችን የሚያከሽፈው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ወደር የለሽ አቅም ገንብተዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ አቅሙን በፎረንሲክና በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን የአሻጥር፣ የሌብነት፣ የኮንትሮባንድ፣ የሙስና እንዲሁም ሕገ-ወጥ የሰዎችና የገንዘብ ዝውውር ወንጀሎችን በመከላከል የሕዝቡን ሰላም እያስከበረ ይገኛል።
እነዚህ ተቋማት ጠላቶች የሚነዙትን የሥነ-ልቦና ጦርነት እና ድብቅ ሴራዎች አስቀድመው በማምከን የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንቶች መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል።
የኢትዮጵያ ጂኦ-ፖለቲካዊ ኩስምና ባከተመበትና አቋሟ እየተስተካከለ በመጣበት በዚህ ወቅት የጸጥታ ተቋሞቻችን የሀገራችንን ሉዓላዊነት፣ ዳር ድንበርና የብልጽግና ጉዞ ለማስከበር በሚያስችል አስተማማኝ የወትሮ ዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ይህንኑ ዝግጁነት ይበልጥ በማጠናከር እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማረጋገጥ የውስጥና የውጭ ችግር ፈጣሪዎችን አደብ ማስገዛት የህልውናችን መሠረት ነው።
የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት ሀገርና ሕዝብን በማስቀደም በጀግንነት የሚከፍሉት መስዋዕትነት፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥበብ እና ጽናት የምትመራ፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ ፈተናዎችን አልፋ ለትውልድ የምትተርፍ የኩራት ምንጭ መሆኗን ያረጋግጣል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የረጅም ዘመን ሥርዓተ መንግሥት ያላት ታላቅ ሀገር በመሆኗ ምንም ዓይነት የጥፋት ኃይል ሰላሟን በቀላሉ ማናጋት እንደማይችል በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
ኢትዮጵያ የሚለው ስም ለችግሮች አለመንበርከክ፣ በፈተና ሳይበገሩ የማለፍ እና እንቅፋቶችን ተሻግሮ ድል የማድረግ የክብር ማህተም ነው።
ሀገራችን በታሪኳ ያለፈተና ያሳለፈቻቸው ዘመናት እጅግ ጥቂት ቢሆኑም፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ የውስጥና የውጭ ፈተናዎችን በድል ተሻግረን ታሪካዊ ክብራችንን እያስጠበቅን ነው።
በተለይም የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ወደ ኋላ የማይደራደር ጠንካራ መንግሥት መኖሩን የተረዱ በዓባይና በአፍሪካ ቀንድ ላይ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የጥፋት ናዳቸውን ሲያወርዱ ቆይተዋል።
ሆኖም እነዚህ የክፋት ኃይላት በሀገራችን ላይ የሚረባረቡት መጪውን ብሩህ ዘመናችንን አይተው እንጂ ተስፋ ቢስ ድሆች መሆናችን አስጨንቋቸው አይደለም።
ዓላማ የሌላቸው አጥፊዎች የሚያደርሱትን የውስጥ ፈተና እና የውጭ ጫና ተቋቁመን በድል ላይ ድል የምንቀዳጀውም በሕዝባችን አንድነት እና በጸጥታ ተቋሞቻችን ብቃት ነው።
ይህ የጸጥታ ተቋማት ብቃት ባለፉት ጥቂት ዓመታት ከተከናወኑ መጠነ-ሰፊ ሀገራዊ ሪፎርሞች የተገኘ ፍሬ ነው።
ተቋማቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት የጸዱ፣ ለሕገ-መንግሥቱና ለሕዝብ ብቻ ታማኝ የሆኑ እንዲሁም የሀገራችንን ሉዓላዊነት በጽናት የሚያስጠብቁ ሆነው ተገንብተዋል።
በዚህም መሠረት የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአየር ኃይል የላቁ የረጅም ርቀት ሚሳኤሎችን እና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስልታዊ ድሮኖችን በመታጠቅ የአየር ክልላችንን ፍጹም የማይደፈር አድርገውታል።
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይልም የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም እና ቀጣናዊ ደኅንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ ሌት ተቀን እየተጋ የሚገኝ ተቋም ሆኗል።
የዘመኑ ጦርነት በቴክኖሎጂ የሚመራ በመሆኑ በሳይበር ምህዳር ሀገርን ለመጠበቅ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር እንዲሁም ስትራቴጂያዊ መረጃዎችን አስቀድሞ በመተንተን ሴራዎችን የሚያከሽፈው የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ወደር የለሽ አቅም ገንብተዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ አቅሙን በፎረንሲክና በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን የአሻጥር፣ የሌብነት፣ የኮንትሮባንድ፣ የሙስና እንዲሁም ሕገ-ወጥ የሰዎችና የገንዘብ ዝውውር ወንጀሎችን በመከላከል የሕዝቡን ሰላም እያስከበረ ይገኛል።
እነዚህ ተቋማት ጠላቶች የሚነዙትን የሥነ-ልቦና ጦርነት እና ድብቅ ሴራዎች አስቀድመው በማምከን የኢትዮጵያ የጀርባ አጥንቶች መሆናቸውን በተግባር አስመስክረዋል።
የኢትዮጵያ ጂኦ-ፖለቲካዊ ኩስምና ባከተመበትና አቋሟ እየተስተካከለ በመጣበት በዚህ ወቅት የጸጥታ ተቋሞቻችን የሀገራችንን ሉዓላዊነት፣ ዳር ድንበርና የብልጽግና ጉዞ ለማስከበር በሚያስችል አስተማማኝ የወትሮ ዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ይህንኑ ዝግጁነት ይበልጥ በማጠናከር እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማረጋገጥ የውስጥና የውጭ ችግር ፈጣሪዎችን አደብ ማስገዛት የህልውናችን መሠረት ነው።
የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት ሀገርና ሕዝብን በማስቀደም በጀግንነት የሚከፍሉት መስዋዕትነት፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥበብ እና ጽናት የምትመራ፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ ፈተናዎችን አልፋ ለትውልድ የምትተርፍ የኩራት ምንጭ መሆኗን ያረጋግጣል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን እንድትገነባ «አልፈቅድም» ስትል አስጠነቀቀች
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን እንድትገነባ «አልፈቅድም» ስትል አስጠነቀቀች
#fastmereja I ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
#fastmereja I ግብፅ ኢትዮጵያ በዓባይ (ብሉ ናይል) ወንዝ ላይ ተጨማሪ የውሃ ግድቦችን እንድትገነባ በፍፁም የማትፈቅድ መሆኑን የሀገሪቱ የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም አስታወቁ። ሚኒስትሩ ይፋዊ መግለጫ የሰጡት ኢትዮጵያ በወንዙ ላይ ተጨማሪ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ልትገነባ ነው መባሉን ተከተሎ ካይሮ በውሃ ደህንነቷ ላይ ያደገባትን ስጋት በድጋሚ ባንጸባረቀችበት ወቅት ነው።
ሚኒስትር ሀኒ ሴዊላም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በአጠቃላይ አራት ግድቦችን በወንዙ ላይ ለመገንባት ያወጣችው እቅድ አዲስ አለመሆኑን እና ግብፅ ቀደሞውኑ የምታውቀው ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም «የግብፅ መንግስት እነዚህ ተጨማሪ ፕሮጀክቶች ወደፊት እንዲገፉ እና እንዲተገበሩ ይፈቅዳል ወይ? መልሱ አይሆንም ነው» ሲሉ ካይሮ የተፋሰሱን የታችኛ ሀገራት መብት የማይጠብቅ እና ህጋዊ አሰሪ ውል የሌለውን ማንኛውንም ተቋም አጥብቃ የምትቃወም መሆኗን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትሩ ወቅታዊውን የአባይ ወንዝ የውሃ ፍሰት አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ፣ እስከ ነሐሴ ወር መጀመሪያ ድረስ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች ወደ ግብፅ የሚፈሰው የውሃ መጠን ከመደበኛው ወቅታዊ አማካይ መጠን በጥቂቱ ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ሆኖም በኢትዮጵያ ደጋማ ቦታዎች ያለው የዝናብ ወቅት ገና በጅምር ላይ ያለ እና እስከ ነሐሴ እና መስከረም ወራት ድረስ የሚቀጥል በመሆኑ ሁኔታው የከፋ ድርቅ መከሰቱን የሚያሳይ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል።
ግብፅ የሀገሪቱን የውሃ ደህንነት ለማስጠበቅ የዓባይ ወንዝ የጎርፍ ሁኔታን፣ የዝናብ ስርጭትን እና የውሃ ፍሰቱን በላቀ የሳተላይት እና የሃይድሮሎጂ መረጃ መከታተያ ስርአት በየዕለቱ እየተከታተለች መሆኗንም ሚኒስትሩ አክለው ገልጸዋል።
10 days ago
Sponsored by
Surafel
13 days ago
ያከተመው የዓባይ ብቸኛ ባለቤትነት ትርክት
*******************
ሰሞኑን እያየነው ያለነው የግብፅ ውኃ-ተኮር ሩጫ ሀገሪቱ ለዘመናት ራሷን ስታሞኝበት የኖረችው የውሸት ትርክት ወደ ፍጻሜው መቃረቡን የሚያሳይ ነው።
ካይሮ ሤራዋ በዲፕሎማሲው መድረክ ውኃ አላነሳ ሲላት፣ የቀጣናውን ሀገራት መሠረት ያደረጉ አዳዲስ ወታደራዊ እና የጸጥታ ትብብሮችን ለመፍጠር በመፍጨርጨር ጊዜዋን እያባከነች ነው።
የሰሞኑ ሩጫዋ ያረጀ እና ያፈጀ የውኃ የበላይነቷን በማወናበድ ለማስቀጠል የምታደርገው የመጨረሻ ሙከራዋ ይመስላል።
ሆኖም ይህ እርምጃዋ አንድን መሠረታዊ እውነት ዘንግቷል፤ እርሱም ኢትዮጵያ በገዛ ሀብቷ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊ እና ሉዓላዊ መብት ወደኋላ መመለስ የማይቻል መሆኑን ነው።
የዓባይ ወንዝ በዓለም ታሪክ ውስጥ የሥልጣኔ መገኛ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ይሁን እንጂ የዚህ ታላቅ ወንዝ የ85 በመቶ ውኃ ምንጭ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በተዛባ ትርክት በገዛ ወንዟ ላይ ባይተዋር እንድትሆን ተደርጋ ኖራለች። ይህም የተዛባ ትርክት እንዴት ታሪክን ሊያዛባ እንደሚችል ትልቅ ማሳያ ነው።
ከ2 ሺህ 500 ዓመታት በፊት በግሪኩ የታሪክ ጸሐፊ ሄሮዶተስ የተሰነዘረው “ግብፅ የዓባይ ስጦታ ናት” የሚለው ብሒል ወንዙን ከምንጩ በማላቀቅ ግብፅን ብቸኛ ባለቤት አድርጎ ለመቅረጽ መሠረት ጥሏል።
ግብፅም ይህን የፈጠራ ትርክት እንደ ፍጹም እውነት ወስዳ፣ ያለ ኢትዮጵያ ፈቃድ ዓባይን በብቸኝነት ጠቅልላ ለመያዝ ራሷን ስታሞኝ ኖራለች። ይህንኑ የተዛባ ትርክት በትውልዶች ቅብብሎሽ ስታስተላልፍም እዚህ ደርሳለች።
ይህ በጥንታዊው ዓለም የተፈጠረው የትርክት መዛባት በሕግ እና በፖለቲካዊ መዋቅር ውስጥ ሰርጎ በመግባት የቅኝ ግዛት ስምምነቶችን ለመቅረጽ መንገድ ከፍቷል። በዚህም መሠረት የወንዙ የላይኛው ተፋሰስ ሀገራትን መብት የገፈፈው የ1929 የአንግሎ-ግብፅ ስምምነት እና የዓባይን ወንዝ ዓመታዊ ፍሰት ሙሉ በሙሉ በግብፅ እና በሱዳን መካከል ብቻ ያከፋፈለው የ1959 ስምምነት ተፈረሙ። እነዚህ ስምምነቶች ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ያገለሉ እና በወንዟ ላይ ባይተዋር ያደረጓት ነበሩ።
ይህ የተዛባ ትርክት ያስከተለውን ጥልቅ የዲፕሎማሲ ጫና አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፣ "ላገኘሁት የዓለም መሪ ሁሉ ማስረዳት የሚከብደኝ ‘ዓባይ የሚመነጨው ከኢትዮጵያ ነው' የሚለውን እውነታ ነው" ብለዋል። ይህም የዓለም መሪዎች በአካዳሚክ ምርምሮች እና በመገናኛ ብዙኃን የተመገቡት መረጃ ዓባይን ከግብፅ ጋር ብቻ ያቆራኘ እንደነበር ያሳያል።
ግብፅ የዓባይን ጉዳይ "የሕልውና ሥጋት" አድርጋ ቀርጻዋለች። በዚህም ኢትዮጵያ ከ130 ሚሊዮን በላይ ለሚሆነው ሕዝቧ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታላቁ ሕዳሴ ግድብን ስትገነባ፣ ግብፅ ግንባታውን ለማስተጓጎል ያልፈነቀለችው ድንጋይ አልነበረም። ይህን የምታደርገው ደግሞ የኢትዮጵያን የልማት ጥረትን፣ ቀጣናውን ወደ ቀውስ የሚመራ የደኅንነት ሥጋት አስመስላ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማቅረብ ነው።
ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ የመጠቀም መብቷን በተግባር እንዳታውል የውስጥ ሰላሟን ማወክ ዋነኛው የግብፅ ስትራቴጂ ሆኖ ዘልቋል። ኢትዮጵያ ስለ ዓባይ ውኃ ልማት እንዳታስብ ለማድረግ የውስጥ አለመረጋጋቶችን በገንዘብ እና በሥልጠና መደገፍ፣ እንዲሁም በድንበር አካባቢ ወታደራዊ ውጥረቶችን መፍጠር ሀገራችን ለዘመናት የብጥብጥ እና የድህነት ሰለባ እንድትሆን ታላቅ ዕንቅፋት ሆነው ኖረዋል። የሰሞኑ የግብፅ የአፍሪካ ቀንድ ዙረትም የዚሁ ኋላቀር የቀውስ አዙሪት ስትራቴጂዋ አካል ነው።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተሳካ ሁኔታ መገንባት እና ውኃ መያዝ ለኢትዮጵያውያን የአንድ ፕሮጀክት ስኬት ሳይሆን እውነተኛ ታሪክ ወደ ባለቤቱ የተመለሰበት ታላቅ የብሔራዊ ሉዓላዊነት ማረጋገጫ ነው።
ግብፅ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ላይ ባደረገችው ጫና ምክንያት ኢትዮጵያ የውጭ ብድር እንዳታገኝ ተደርጋ የኖረች ቢሆንም፣ ግድቡ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን ዐቅም ተገንብቶ የነፃነት ምልክት ለመሆን በቅቷል።
አሁን ላይ ግብፅ እየተከተለችው ያለው የማስፈራራት እና በጎረቤት ሀገራት በኩል አዲስ ጫና የመፍጠር አካሄድ፣ በሕዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ክፉኛ የተመታውን እና የፈረሰውን የውኃ የበላይነቷን ለመጠገን የሚደረግ ከንቱ ጥረት ነው።
ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በዓባይ ላይ የተሰራጨውን የዘመናት የተዛባ ትርክት ከማምከኑም በላይ፣ መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በድል አድራጊነት ግዘፍ ነስቶ የቆመበት የትውልዳችን አዲስ ምዕራፍ ነው።
ኢትዮጵያ አሁንም ቢሆን የጋራ ተጠቃሚነትን እና ቀጣናዊ ትብብርን የምትሻ ሲሆን፣ ግብፅ ግን ከቅዠት ዓለሟ ነቅታ አዲሱን እውነት መቀበል ግድ ይላታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #abay #bluenile #nile #egypt #gerd #ebc
*******************
ሰሞኑን እያየነው ያለነው የግብፅ ውኃ-ተኮር ሩጫ ሀገሪቱ ለዘመናት ራሷን ስታሞኝበት የኖረችው የውሸት ትርክት ወደ ፍጻሜው መቃረቡን የሚያሳይ ነው።
ካይሮ ሤራዋ በዲፕሎማሲው መድረክ ውኃ አላነሳ ሲላት፣ የቀጣናውን ሀገራት መሠረት ያደረጉ አዳዲስ ወታደራዊ እና የጸጥታ ትብብሮችን ለመፍጠር በመፍጨርጨር ጊዜዋን እያባከነች ነው።
የሰሞኑ ሩጫዋ ያረጀ እና ያፈጀ የውኃ የበላይነቷን በማወናበድ ለማስቀጠል የምታደርገው የመጨረሻ ሙከራዋ ይመስላል።
ሆኖም ይህ እርምጃዋ አንድን መሠረታዊ እውነት ዘንግቷል፤ እርሱም ኢትዮጵያ በገዛ ሀብቷ ላይ ያላትን ተፈጥሯዊ እና ሉዓላዊ መብት ወደኋላ መመለስ የማይቻል መሆኑን ነው።
የዓባይ ወንዝ በዓለም ታሪክ ውስጥ የሥልጣኔ መገኛ ተደርጎ የሚወሰድ ነው። ይሁን እንጂ የዚህ ታላቅ ወንዝ የ85 በመቶ ውኃ ምንጭ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በተዛባ ትርክት በገዛ ወንዟ ላይ ባይተዋር እንድትሆን ተደርጋ ኖራለች። ይህም የተዛባ ትርክት እንዴት ታሪክን ሊያዛባ እንደሚችል ትልቅ ማሳያ ነው።
ከ2 ሺህ 500 ዓመታት በፊት በግሪኩ የታሪክ ጸሐፊ ሄሮዶተስ የተሰነዘረው “ግብፅ የዓባይ ስጦታ ናት” የሚለው ብሒል ወንዙን ከምንጩ በማላቀቅ ግብፅን ብቸኛ ባለቤት አድርጎ ለመቅረጽ መሠረት ጥሏል።
ግብፅም ይህን የፈጠራ ትርክት እንደ ፍጹም እውነት ወስዳ፣ ያለ ኢትዮጵያ ፈቃድ ዓባይን በብቸኝነት ጠቅልላ ለመያዝ ራሷን ስታሞኝ ኖራለች። ይህንኑ የተዛባ ትርክት በትውልዶች ቅብብሎሽ ስታስተላልፍም እዚህ ደርሳለች።
ይህ በጥንታዊው ዓለም የተፈጠረው የትርክት መዛባት በሕግ እና በፖለቲካዊ መዋቅር ውስጥ ሰርጎ በመግባት የቅኝ ግዛት ስምምነቶችን ለመቅረጽ መንገድ ከፍቷል። በዚህም መሠረት የወንዙ የላይኛው ተፋሰስ ሀገራትን መብት የገፈፈው የ1929 የአንግሎ-ግብፅ ስምምነት እና የዓባይን ወንዝ ዓመታዊ ፍሰት ሙሉ በሙሉ በግብፅ እና በሱዳን መካከል ብቻ ያከፋፈለው የ1959 ስምምነት ተፈረሙ። እነዚህ ስምምነቶች ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ያገለሉ እና በወንዟ ላይ ባይተዋር ያደረጓት ነበሩ።
ይህ የተዛባ ትርክት ያስከተለውን ጥልቅ የዲፕሎማሲ ጫና አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት፣ "ላገኘሁት የዓለም መሪ ሁሉ ማስረዳት የሚከብደኝ ‘ዓባይ የሚመነጨው ከኢትዮጵያ ነው' የሚለውን እውነታ ነው" ብለዋል። ይህም የዓለም መሪዎች በአካዳሚክ ምርምሮች እና በመገናኛ ብዙኃን የተመገቡት መረጃ ዓባይን ከግብፅ ጋር ብቻ ያቆራኘ እንደነበር ያሳያል።
ግብፅ የዓባይን ጉዳይ "የሕልውና ሥጋት" አድርጋ ቀርጻዋለች። በዚህም ኢትዮጵያ ከ130 ሚሊዮን በላይ ለሚሆነው ሕዝቧ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ታላቁ ሕዳሴ ግድብን ስትገነባ፣ ግብፅ ግንባታውን ለማስተጓጎል ያልፈነቀለችው ድንጋይ አልነበረም። ይህን የምታደርገው ደግሞ የኢትዮጵያን የልማት ጥረትን፣ ቀጣናውን ወደ ቀውስ የሚመራ የደኅንነት ሥጋት አስመስላ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማቅረብ ነው።
ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ የመጠቀም መብቷን በተግባር እንዳታውል የውስጥ ሰላሟን ማወክ ዋነኛው የግብፅ ስትራቴጂ ሆኖ ዘልቋል። ኢትዮጵያ ስለ ዓባይ ውኃ ልማት እንዳታስብ ለማድረግ የውስጥ አለመረጋጋቶችን በገንዘብ እና በሥልጠና መደገፍ፣ እንዲሁም በድንበር አካባቢ ወታደራዊ ውጥረቶችን መፍጠር ሀገራችን ለዘመናት የብጥብጥ እና የድህነት ሰለባ እንድትሆን ታላቅ ዕንቅፋት ሆነው ኖረዋል። የሰሞኑ የግብፅ የአፍሪካ ቀንድ ዙረትም የዚሁ ኋላቀር የቀውስ አዙሪት ስትራቴጂዋ አካል ነው።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተሳካ ሁኔታ መገንባት እና ውኃ መያዝ ለኢትዮጵያውያን የአንድ ፕሮጀክት ስኬት ሳይሆን እውነተኛ ታሪክ ወደ ባለቤቱ የተመለሰበት ታላቅ የብሔራዊ ሉዓላዊነት ማረጋገጫ ነው።
ግብፅ በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ላይ ባደረገችው ጫና ምክንያት ኢትዮጵያ የውጭ ብድር እንዳታገኝ ተደርጋ የኖረች ቢሆንም፣ ግድቡ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን ዐቅም ተገንብቶ የነፃነት ምልክት ለመሆን በቅቷል።
አሁን ላይ ግብፅ እየተከተለችው ያለው የማስፈራራት እና በጎረቤት ሀገራት በኩል አዲስ ጫና የመፍጠር አካሄድ፣ በሕዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ክፉኛ የተመታውን እና የፈረሰውን የውኃ የበላይነቷን ለመጠገን የሚደረግ ከንቱ ጥረት ነው።
ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በዓባይ ላይ የተሰራጨውን የዘመናት የተዛባ ትርክት ከማምከኑም በላይ፣ መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ እውነት በድል አድራጊነት ግዘፍ ነስቶ የቆመበት የትውልዳችን አዲስ ምዕራፍ ነው።
ኢትዮጵያ አሁንም ቢሆን የጋራ ተጠቃሚነትን እና ቀጣናዊ ትብብርን የምትሻ ሲሆን፣ ግብፅ ግን ከቅዠት ዓለሟ ነቅታ አዲሱን እውነት መቀበል ግድ ይላታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #abay #bluenile #nile #egypt #gerd #ebc
14 days ago
የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የግብጽ የሞኝ ብልጠት አካሄድ ዳግም ሲጋለጥ
********************
ኢትዮጵያ የዓባይን ውኃ 85 በመቶ የምታመነጭ እና ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሕይወት እስትንፋስ የሆነች ሀገር ነች።
ይሁን እንጂ ግብጽ ይህንን የማይካድ የተፈጥሮ እውነት ወደ ጎን በመተው ለረጅም ዘመናት "የዓባይ ውኃ ብቸኛ ባለቤት እኔ ነኝ" የሚል የሞኝ ብልጠት ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ካይሮ ይህንን የውኃ ሞኖፖል ለማስቀጠል መሠረት የምታደርገው ኢትዮጵያን ያገለሉትን እና ጊዜ ያለፈባቸውን የ1929 እና የ1959 የቅኝ ግዛት ዘመን 'ስምምነቶች'ን ነው።
ከዚህም አልፋ የውኃ ድርሻዬ የምትለውን ለማረጋገጥ በቀጣናው የውክልና ፖለቲካን በመጠቀም ሀገራት እርስ በርስ እንዲጋጩ፣ ትርምስ እንዲፈጠር እና ኢትዮጵያ በውስጥ ችግር ተተብትባ የራሷን ጸጋ እንዳትጠቀም የተለያዩ የሴራ ድሮችን ስታደራ መኖሯ የአደባባይ ምሥጢር ነው።
ለዘመናት የዓባይ ወንዝን በብቸኝነት ለመጠቀም ስትከተለው የቆየው ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በዜሮ ድምር ስሌት የምትመራ እና ከመጠን ያለፈ ራስ ወዳድ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
ኢትዮጵያ ከደጇ የሚመነጨውን ተፈጥሯዊ ሀብቷን የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን ስታነሣ አምርራ የምትቃወመው ግብጽ፣ በቀይ ባሕር የባሕር ላይ ደኅንነት ዙሪያ ፍጹም ተቃራኒ የሆነ እና "ዐይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ" የሚል ሌላ የሴራ አካሄድ ይዛ ብቅ ማለቷ ነው።
የታችኛው ተፋሰስ ሀገር የሆነችው ግብጽ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ "የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ድምፅ እና ይሁንታ ሊኖራቸው ይገባል" በማለት የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መብት ስትገዳደር ኖራለች።
በተቃራኒው ግን በቀይ ባሕር ጉዳይ ላይ ስትጠየቅ "ውይይት እና ውሳኔው የሚመለከተው የባሕሩ ተዋሳኝ ሀገራትን ብቻ ነው" የሚል የሞኝ ዜማ ማቀንቀን ከጀመረች ውላ አድራለች። ይህ ተቃራኒ እና ሚዛን የሳተ አካሄድ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማወናበድ እና የማይመስሉ ጥያቄዎችን በማንሣት ኢትዮጵያን ከጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ ለማግለል ያሰላችው ያረጀ ስትራቴጂዋ ነው።
ይህንን የካይሮን የሚጣረስ እና የተፈጥሮ ሕግን የሚቃረን አካሄድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁለት ዓመታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ታሪካዊ ማብራሪያ በግልጽ አስቀምጠውታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀይ ባሕር እና ዓባይ ከኢትዮጵያ ዕድገት እና ሕልውና ጋር በቀጥታ የተሣሠሩ መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን በመጠቆም፣ ተፈጥሯዊ ትሥሥራቸውን አብራርተዋል።
ዓባይ ከኢትዮጵያ እየፈለቀ ለግብጽ የሕልውና ጉዳይ ከሆነ እና ስለ እርሱ በግልጽ መነጋገር ከቻለች ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ታሥራ መኖር ስለማትችል ስለ ቀይ ባሕር መነጋገርም ሆነ መደራደር ነውር ሊሆንባት አይገባም ነው ያሉት።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አባባል፣ ተፈጥሮ በውኃ አዙሪት ያስተሣሠረቻቸውን እነዚህን ሁለት የውኃ አካላት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታዎች አንዱን የብቸኝነት ንብረት አድርጎ ሌላውን መከልከል ከፍትሕ እና ከተፈጥሮ ሕግ ጋር ፈጽሞ የሚጣረስ ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ይህንኑ ጽኑ አቋም እና የግብጽን ግብዝነት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በሚገባ መረዳት ጀምሯል።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቀድሞው የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ቲቦር ናዥ ይህንን የግብጽን ጨፍኑ ላሞኛችሁ አካሄድ ሰሞኑን በጥልቅ አመክንዮአዊ መልዕክት አጋልጠውታል።
አምባሳደሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ግብጽ እና ኤርትራ በቀይ ባሕር ላይ መወሰን ያለባቸው ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ናቸው ካሉ፤ እንግዲያውስ በአመክንዮ ደረጃ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይም መወሰን ያለባቸው ውኃውን የሚያመነጩት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ብቻ ናቸው" በማለት የካይሮን ክርክር መሠረተ ቢስነት በአደባባይ አሳይተዋል።
አምባሳደሩ ከዚህ ቀደምም ግብጽ ጊዜ ያለፈበትን አካሄድ ትታ መሬት ላይ ወዳለው እውነታ መምጣት እንዳለባት በተደጋጋሚ አሳስበዋል። ኢትዮጵያን በዛቻ እና በግፊት ማንበርከክ እንደማይቻል የገለጹት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ የቀይ ባሕር ደኅንነት ያለ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ሙሉ ሊሆን እንደማይችል በግልጽ አስምረውበታል።
ግብጽ በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ስትገነባ "የታችኛው ተፋሰስ ፈቃድ ያስፈልጋል" እያለች አቤቱታ ስታሰማ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እ.አ.አ በ2020 በሪያድ የተቋቋመውን "የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ሀገራት ምክር ቤት" በመጠቀም ኢትዮጵያን ከባሕር ደኅንነት ውይይቶች ለማግለል ስትሠራ ቆይታለች።
ይህ የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የብልጠት ስትራቴጂ አሁን ላይ ጊዜው አልፎበታል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ፍትሐዊ የልማት ጥያቄዋን በአግባቡ መጠየቅ እና በውኃዋም ሆነ በባሕር በር አማራጮቿ ተጠቃሚ ለመሆን መንቀሳቀስ በመጀመሯ፣ የግብጽ ያረጀ የሞኖፖል እና የሴራ አካሄድ ፈጽሞ እንደማያዋጣ በተግባር እየተረጋገጠ መጥቷል።
ለግብጽ የሚበጃት ብቸኛ መንገድ ወደ እውነታው መምጣት እና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ የትብብር ማዕቀፍን መቀበል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን የልማት እና የደኅንነት ዋስትና ለማረጋገጥ የጀመረችውን የሰላም እና የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ጉዞ ማንም አያስቆመውም።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redsea #nilebasin #geopolitics #hornofafrica #diplomacy
********************
ኢትዮጵያ የዓባይን ውኃ 85 በመቶ የምታመነጭ እና ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሕይወት እስትንፋስ የሆነች ሀገር ነች።
ይሁን እንጂ ግብጽ ይህንን የማይካድ የተፈጥሮ እውነት ወደ ጎን በመተው ለረጅም ዘመናት "የዓባይ ውኃ ብቸኛ ባለቤት እኔ ነኝ" የሚል የሞኝ ብልጠት ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ካይሮ ይህንን የውኃ ሞኖፖል ለማስቀጠል መሠረት የምታደርገው ኢትዮጵያን ያገለሉትን እና ጊዜ ያለፈባቸውን የ1929 እና የ1959 የቅኝ ግዛት ዘመን 'ስምምነቶች'ን ነው።
ከዚህም አልፋ የውኃ ድርሻዬ የምትለውን ለማረጋገጥ በቀጣናው የውክልና ፖለቲካን በመጠቀም ሀገራት እርስ በርስ እንዲጋጩ፣ ትርምስ እንዲፈጠር እና ኢትዮጵያ በውስጥ ችግር ተተብትባ የራሷን ጸጋ እንዳትጠቀም የተለያዩ የሴራ ድሮችን ስታደራ መኖሯ የአደባባይ ምሥጢር ነው።
ለዘመናት የዓባይ ወንዝን በብቸኝነት ለመጠቀም ስትከተለው የቆየው ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በዜሮ ድምር ስሌት የምትመራ እና ከመጠን ያለፈ ራስ ወዳድ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
ኢትዮጵያ ከደጇ የሚመነጨውን ተፈጥሯዊ ሀብቷን የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን ስታነሣ አምርራ የምትቃወመው ግብጽ፣ በቀይ ባሕር የባሕር ላይ ደኅንነት ዙሪያ ፍጹም ተቃራኒ የሆነ እና "ዐይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ" የሚል ሌላ የሴራ አካሄድ ይዛ ብቅ ማለቷ ነው።
የታችኛው ተፋሰስ ሀገር የሆነችው ግብጽ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ "የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ድምፅ እና ይሁንታ ሊኖራቸው ይገባል" በማለት የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መብት ስትገዳደር ኖራለች።
በተቃራኒው ግን በቀይ ባሕር ጉዳይ ላይ ስትጠየቅ "ውይይት እና ውሳኔው የሚመለከተው የባሕሩ ተዋሳኝ ሀገራትን ብቻ ነው" የሚል የሞኝ ዜማ ማቀንቀን ከጀመረች ውላ አድራለች። ይህ ተቃራኒ እና ሚዛን የሳተ አካሄድ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማወናበድ እና የማይመስሉ ጥያቄዎችን በማንሣት ኢትዮጵያን ከጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ ለማግለል ያሰላችው ያረጀ ስትራቴጂዋ ነው።
ይህንን የካይሮን የሚጣረስ እና የተፈጥሮ ሕግን የሚቃረን አካሄድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁለት ዓመታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ታሪካዊ ማብራሪያ በግልጽ አስቀምጠውታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀይ ባሕር እና ዓባይ ከኢትዮጵያ ዕድገት እና ሕልውና ጋር በቀጥታ የተሣሠሩ መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን በመጠቆም፣ ተፈጥሯዊ ትሥሥራቸውን አብራርተዋል።
ዓባይ ከኢትዮጵያ እየፈለቀ ለግብጽ የሕልውና ጉዳይ ከሆነ እና ስለ እርሱ በግልጽ መነጋገር ከቻለች ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ታሥራ መኖር ስለማትችል ስለ ቀይ ባሕር መነጋገርም ሆነ መደራደር ነውር ሊሆንባት አይገባም ነው ያሉት።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አባባል፣ ተፈጥሮ በውኃ አዙሪት ያስተሣሠረቻቸውን እነዚህን ሁለት የውኃ አካላት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታዎች አንዱን የብቸኝነት ንብረት አድርጎ ሌላውን መከልከል ከፍትሕ እና ከተፈጥሮ ሕግ ጋር ፈጽሞ የሚጣረስ ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ይህንኑ ጽኑ አቋም እና የግብጽን ግብዝነት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በሚገባ መረዳት ጀምሯል።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቀድሞው የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ቲቦር ናዥ ይህንን የግብጽን ጨፍኑ ላሞኛችሁ አካሄድ ሰሞኑን በጥልቅ አመክንዮአዊ መልዕክት አጋልጠውታል።
አምባሳደሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ግብጽ እና ኤርትራ በቀይ ባሕር ላይ መወሰን ያለባቸው ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ናቸው ካሉ፤ እንግዲያውስ በአመክንዮ ደረጃ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይም መወሰን ያለባቸው ውኃውን የሚያመነጩት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ብቻ ናቸው" በማለት የካይሮን ክርክር መሠረተ ቢስነት በአደባባይ አሳይተዋል።
አምባሳደሩ ከዚህ ቀደምም ግብጽ ጊዜ ያለፈበትን አካሄድ ትታ መሬት ላይ ወዳለው እውነታ መምጣት እንዳለባት በተደጋጋሚ አሳስበዋል። ኢትዮጵያን በዛቻ እና በግፊት ማንበርከክ እንደማይቻል የገለጹት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ የቀይ ባሕር ደኅንነት ያለ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ሙሉ ሊሆን እንደማይችል በግልጽ አስምረውበታል።
ግብጽ በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ስትገነባ "የታችኛው ተፋሰስ ፈቃድ ያስፈልጋል" እያለች አቤቱታ ስታሰማ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እ.አ.አ በ2020 በሪያድ የተቋቋመውን "የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ሀገራት ምክር ቤት" በመጠቀም ኢትዮጵያን ከባሕር ደኅንነት ውይይቶች ለማግለል ስትሠራ ቆይታለች።
ይህ የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የብልጠት ስትራቴጂ አሁን ላይ ጊዜው አልፎበታል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ፍትሐዊ የልማት ጥያቄዋን በአግባቡ መጠየቅ እና በውኃዋም ሆነ በባሕር በር አማራጮቿ ተጠቃሚ ለመሆን መንቀሳቀስ በመጀመሯ፣ የግብጽ ያረጀ የሞኖፖል እና የሴራ አካሄድ ፈጽሞ እንደማያዋጣ በተግባር እየተረጋገጠ መጥቷል።
ለግብጽ የሚበጃት ብቸኛ መንገድ ወደ እውነታው መምጣት እና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ የትብብር ማዕቀፍን መቀበል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን የልማት እና የደኅንነት ዋስትና ለማረጋገጥ የጀመረችውን የሰላም እና የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ጉዞ ማንም አያስቆመውም።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redsea #nilebasin #geopolitics #hornofafrica #diplomacy
14 days ago
u12d3u1263u12ed u12dbu122c u1240u12ed u1263u1215u122d u1290u1308 #ethiopia #redsea #gerd #assab ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ዓባይ ዛሬ ቀይ ባሕር ነገ #ethiopia #redsea #gerd #assab
15 days ago
የታዳሽ ኃይል ልማት ጉዞዋን ያጠናከረችው ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማትና የቀጣናው ትስስር ጉዞ እየተሻሻለ እና ወደ አስተማማኝ አጋርነት እያደገ ይገኛል፡፡
ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ይህንን እውነት በመረዳት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሪነት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሰፉና የሚያዘምኑ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ስትራቴጂካዊ ጉዞ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከጨለማ ከማውጣት ባለፈ ሀገሪቱን የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል ለማድረግ ያለመ ታላቅ ብሔራዊ ራዕይ ነው።
የዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም ተምሳሌት የሆነው የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጽናት፣ የጥበብ፣ የአብሮነትና የመተባበር መገለጫ ነው።
ግድቡ የዓባይን ወንዝ ተፈጥሯዊ ፍሰት ሳይገታና የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም ሳይነካ የውሃውን ኃይል ወደ ንጹህ የኤሌክትሪክ ብርሃንነት በመቀየር ረገድ ታሪካዊ ምዕራፍ እየፈጠረ ይገኛል።
የውሃ አሞላልና የግንባታ ምዕራፎቹን በተሳካ ሁኔታ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ተቋም፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ለማሳደግ ታላቅ አቅም ሆኗል።
ግድቡ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ለከተሞች መስፋፋትና ለገጠር አካባቢዎች የብርሃን ምንጭ በመሆን የኢኮኖሚውን ሞተር በማንቀሳቀስ ላይ ነው።
ነገር ግን የኢትዮጵያ የኃይል ስትራቴጂ በውሃ ሀይል ወይም በሕዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም።ሀገሪቱ የኃይል ምንጮቿን ከማስፋት ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
በውሃ ኃይል ረገድ እንደ ኮይሻ፣ ግልገል ጊቤ እና ሌሎች የወንዝ ተፋሰሶች ላይ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ሜጋ ዋት ሀይልን ለብሔራዊ ኃይል ቋት እያበረከቱ ናቸው።
ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ጸጋ በመነሳት የንፋስ ኃይል፣ የፀሐይ ብርሃን ኃይል እና የምድር ውስጥ እንፋሎት ልማቶችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
እንደ አሸጎዳ እና አዳማ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የአሉቶ ላንጋኖ የምድር ውስጥ እንፋሎት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ታዳሽ ኃይል ይበልጥ አስተማማኝ እና ከተፈጥሮ መዛባት የተጠበቀ እያደረጉት ይገኛሉ።
ይህ በሀገር ውስጥ የሚመነጨው ግዙፍ የኃይል አቅም ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር ትልቅ መሣሪያ እየሆነ ነው።
ኢትዮጵያ "የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ" የመሆን ራዕይዋን ለማሳካት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋት ላይ ትገኛለች።
በአሁኑ ወቅት ለጎረቤት ሀገራት እንደ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ የምትገኝ ሲሆን÷ ይህ ትስስር ወደ ታንዛኒያ እና ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት እንዲደርስ ሰፊ የዲፕሎማሲና የቴክኒክ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፤ የሙከራ ሸያጭ የተጀመረባቸው ሀገራትም አሉ።
ይህ የኃይል ሽያጭ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ በቀጣናው ሀገራት መካከል ያለውን የሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ ማጠናከሪያ የዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በሌሎች ዘርፈ ብዙ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ላይ እያደረገችው ያለው ርብርብ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሟላት ብቻ ሳይሆን ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዕድገት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ የሃይል ምንጮች 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
የኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማትና የቀጣናው ትስስር ጉዞ እየተሻሻለ እና ወደ አስተማማኝ አጋርነት እያደገ ይገኛል፡፡
ለአንድ ሀገር የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢንዱስትሪ ሽግግር እንዲሁም ሁለንተናዊ ብልጽግና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ይህንን እውነት በመረዳት በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መሪነት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚያሰፉና የሚያዘምኑ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
ይህ ስትራቴጂካዊ ጉዞ በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከጨለማ ከማውጣት ባለፈ ሀገሪቱን የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል ለማድረግ ያለመ ታላቅ ብሔራዊ ራዕይ ነው።
የዚህ ግዙፍ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም ተምሳሌት የሆነው የሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን የጽናት፣ የጥበብ፣ የአብሮነትና የመተባበር መገለጫ ነው።
ግድቡ የዓባይን ወንዝ ተፈጥሯዊ ፍሰት ሳይገታና የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጥቅም ሳይነካ የውሃውን ኃይል ወደ ንጹህ የኤሌክትሪክ ብርሃንነት በመቀየር ረገድ ታሪካዊ ምዕራፍ እየፈጠረ ይገኛል።
የውሃ አሞላልና የግንባታ ምዕራፎቹን በተሳካ ሁኔታ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ተቋም፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በእጥፍ ለማሳደግ ታላቅ አቅም ሆኗል።
ግድቡ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ለከተሞች መስፋፋትና ለገጠር አካባቢዎች የብርሃን ምንጭ በመሆን የኢኮኖሚውን ሞተር በማንቀሳቀስ ላይ ነው።
ነገር ግን የኢትዮጵያ የኃይል ስትራቴጂ በውሃ ሀይል ወይም በሕዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የተገደበ አይደለም።ሀገሪቱ የኃይል ምንጮቿን ከማስፋት ረገድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነች ትገኛለች።
በውሃ ኃይል ረገድ እንደ ኮይሻ፣ ግልገል ጊቤ እና ሌሎች የወንዝ ተፋሰሶች ላይ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ሜጋ ዋት ሀይልን ለብሔራዊ ኃይል ቋት እያበረከቱ ናቸው።
ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ ካላት የተፈጥሮ ጸጋ በመነሳት የንፋስ ኃይል፣ የፀሐይ ብርሃን ኃይል እና የምድር ውስጥ እንፋሎት ልማቶችን በስፋት እያከናወነች ትገኛለች።
እንደ አሸጎዳ እና አዳማ ያሉ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች እንዲሁም የአሉቶ ላንጋኖ የምድር ውስጥ እንፋሎት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ታዳሽ ኃይል ይበልጥ አስተማማኝ እና ከተፈጥሮ መዛባት የተጠበቀ እያደረጉት ይገኛሉ።
ይህ በሀገር ውስጥ የሚመነጨው ግዙፍ የኃይል አቅም ከኢትዮጵያ ድንበር አልፎ ቀጣናዊ ትስስርን ለመፍጠር ትልቅ መሣሪያ እየሆነ ነው።
ኢትዮጵያ "የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ" የመሆን ራዕይዋን ለማሳካት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመዘርጋት ላይ ትገኛለች።
በአሁኑ ወቅት ለጎረቤት ሀገራት እንደ ኬንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ላይ የምትገኝ ሲሆን÷ ይህ ትስስር ወደ ታንዛኒያ እና ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ቀጣና ሀገራት እንዲደርስ ሰፊ የዲፕሎማሲና የቴክኒክ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፤ የሙከራ ሸያጭ የተጀመረባቸው ሀገራትም አሉ።
ይህ የኃይል ሽያጭ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኝ ከመሆኑም በላይ በቀጣናው ሀገራት መካከል ያለውን የሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር ይበልጥ ማጠናከሪያ የዲፕሎማሲ መሳሪያ ሆኖ ያገለግላል።
ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብና በሌሎች ዘርፈ ብዙ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ላይ እያደረገችው ያለው ርብርብ የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ፍላጎትን ለማሟላት ብቻ ሳይሆን ለአካባቢ ጥበቃና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዕድገት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከተለያዩ የሃይል ምንጮች 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች፡፡
በእመቤት ሲሳይ
Sponsored by
Surafel
17 days ago
አረንጓዴ አሻራ ለታችኞቹ የናይል ተፋሰስ ሀገራት ያለው ፋይዳ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለማችንን በአሁኑ ወቅት እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተላቸው ጫናዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
የአየር ንብረት ለውጥ በሚያስከትላቸው ቀውሶች በእጅጉ ከሚፈተኑት የተፈጥሮ ሀብቶች መካከል ውሃ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
በድርቅም ሆነ በጎርፍ እንዲሁም የገጸ ምድር ውሃ በደለል መሞላት በዘላቂነት የውሃ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሃብት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ምላሽ ለመስጠት ተግባራዊ ርምጃ በመውሰድ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
ከእነዚህ ተግባራት መካከል ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ የሚገኘው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ስሟ በጉልህ እንዲጠቀስ አድርጓል።
በመንግሥት ቆራጥነት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያንን ልብና ጉልበት በአንድነት ያስተሳሰረ ታላቅ ሀገራዊ ተግባር ሆኖ ቀጥሏል።
ይህ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ የተጀመረው መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል ባሻገር ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሀብቶቻችን ዋስትና የሰጠ ውጤት አስመዝግቧል።
መንግሥት ለመርሐ ግብሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በባለቤትነት በመምራትና ህዝቡም ጥሪውን ተቀብሎ በነቂስ በመውጣት ላለፉት ዓመታት ያሳዩት ቁርጠኝነት የሀገሪቱን ደን ሽፋን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ ውስጥ 18 ነጥብ 7 ቢሊየኑ በዓባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተተከለ ነው።
ይህም 40 በመቶ ድርሻ እንዳለው ያሳያል፥ ሆኖም ኢትዮጵያ በዓባይ ተፋሰስ ውሃውን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራም እየሠራች ማለት ያስችላል።
በዚህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በደን መራቆት ምክንያት የሚከሰት ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ስጋታቸው ይቀረፋል። በተጨማሪም ዓመቱን ሙሉ አስተማማኝ የሆነ የውሃ ፍሰት ተጠቃሚ ይሆናሉ።
በዓባይ ተፋሰስ ላይ የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ በወንዞች ላይ የሚፈጠረው ደለል እንዲቀንስ እና በወንዞች ላይ ይከማች የነበረውን ከፍተኛ ደለል እንዲቀንስ በማድረግ ለውሃ ሀብት ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
አረንጓዴ ዐሻራ ከላይ ከተጠቀሱት ጥቅሞች በተጨማሪ ለዘላቂ የውሃ ሀብት ጥበቃ በርካታ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ማየት ይቻላል።
ደን ማልማት የዝናብ ውሃ ወደ መሬት ውስጥ እንዲሰርግ በማድረግ የውሃ ምንጮችን ያጠናክራል፣ የአፈር መሸርሸርን ይቀንሳል፣ የዛፍ ሥር አፈርን በማቆየት ወደ ውሃ አካላት የሚደርሰውን ደለል ይቀንሳል።
ይህም የውሃ ጥራት ይጠብቃል፣ የጎርፍ አደጋ ይቀንሳል።
ደን ድንገተኛ ጎርፍን ስለሚቀንስ የውሃ አካላት በዘላቂነት ያገለግላሉ፤ ዝናብን በማመጣጠን የውሃ ሀብት ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ያግዛል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለማችንን በአሁኑ ወቅት እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተላቸው ጫናዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
የአየር ንብረት ለውጥ በሚያስከትላቸው ቀውሶች በእጅጉ ከሚፈተኑት የተፈጥሮ ሀብቶች መካከል ውሃ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
በድርቅም ሆነ በጎርፍ እንዲሁም የገጸ ምድር ውሃ በደለል መሞላት በዘላቂነት የውሃ ልማትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ያደናቅፋል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሃብት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ምላሽ ለመስጠት ተግባራዊ ርምጃ በመውሰድ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
ከእነዚህ ተግባራት መካከል ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ የሚገኘው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም መድረክ ስሟ በጉልህ እንዲጠቀስ አድርጓል።
በመንግሥት ቆራጥነት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የኢትዮጵያውያንን ልብና ጉልበት በአንድነት ያስተሳሰረ ታላቅ ሀገራዊ ተግባር ሆኖ ቀጥሏል።
ይህ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በይፋ የተጀመረው መርሐ ግብር ዛፍ ከመትከል ባሻገር ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሀብቶቻችን ዋስትና የሰጠ ውጤት አስመዝግቧል።
መንግሥት ለመርሐ ግብሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በባለቤትነት በመምራትና ህዝቡም ጥሪውን ተቀብሎ በነቂስ በመውጣት ላለፉት ዓመታት ያሳዩት ቁርጠኝነት የሀገሪቱን ደን ሽፋን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ብቻ ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞች ተተክለዋል። ከዚህ ውስጥ 18 ነጥብ 7 ቢሊየኑ በዓባይ ተፋሰስ ላይ ብቻ የተተከለ ነው።
ይህም 40 በመቶ ድርሻ እንዳለው ያሳያል፥ ሆኖም ኢትዮጵያ በዓባይ ተፋሰስ ውሃውን መጠቀም ብቻ ሳይሆን የመንከባከብ ስራም እየሠራች ማለት ያስችላል።
በዚህም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በደን መራቆት ምክንያት የሚከሰት ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ስጋታቸው ይቀረፋል። በተጨማሪም ዓመቱን ሙሉ አስተማማኝ የሆነ የውሃ ፍሰት ተጠቃሚ ይሆናሉ።
በዓባይ ተፋሰስ ላይ የተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ችግኝ ተከላ በወንዞች ላይ የሚፈጠረው ደለል እንዲቀንስ እና በወንዞች ላይ ይከማች የነበረውን ከፍተኛ ደለል እንዲቀንስ በማድረግ ለውሃ ሀብት ጥበቃ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
አረንጓዴ ዐሻራ ከላይ ከተጠቀሱት ጥቅሞች በተጨማሪ ለዘላቂ የውሃ ሀብት ጥበቃ በርካታ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ ማየት ይቻላል።
ደን ማልማት የዝናብ ውሃ ወደ መሬት ውስጥ እንዲሰርግ በማድረግ የውሃ ምንጮችን ያጠናክራል፣ የአፈር መሸርሸርን ይቀንሳል፣ የዛፍ ሥር አፈርን በማቆየት ወደ ውሃ አካላት የሚደርሰውን ደለል ይቀንሳል።
ይህም የውሃ ጥራት ይጠብቃል፣ የጎርፍ አደጋ ይቀንሳል።
ደን ድንገተኛ ጎርፍን ስለሚቀንስ የውሃ አካላት በዘላቂነት ያገለግላሉ፤ ዝናብን በማመጣጠን የውሃ ሀብት ቀጣይነት ያለው እንዲሆን ያግዛል።
18 days ago
የድሮን ጥቃት‼️
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
Seledadotio
Seledadotio
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ “በመካነ ሰላም ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም በድሮን ጥቃት የመነኮሳት ህይወት አለፈ”‼️
በዛሬው ዕለት ሐምሌ 15/2018 ዓ.ም በምዕራብ ወሎ በመካነ ሰላም በዓባይ ወንዝ ዳርቻ በሚገኘው ዓባይ ገዳመ አስቀጤስ የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ምክንያት በገዳሙ ውስጥ የሚኖሩ 2 ሴቶች ወዲያው ህይወታቸው ማለፉን እና ሌሎች መቁሰላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በአካባቢው የፋኖ ሀይሎች ከትመዋል በሚል ነው ተብሏል።
ሰላም ለሀገራችን🕊🕊
Seledadotio
Seledadotio
19 days ago
ውኃ የሚወቅጠው የግብጽ ዲፕሎማሲ እና የማይቀለበሰው የኢትዮጵያ ልማት
*********************
የግብፅ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር “በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ የውኃ መብቴን ለማስከበር ቁርጠኛ ነኝ” በሚል ያወጣው መግለጫ፣ የካይሮ ፖለቲከኞች ለዘመናት ሲያላምጡት የኖሩትና አሁንም መላቀቅ ያቃታቸው የተለመደ የሚዲያ ፍጆታ ነው።
ይህ መግለጫ መሬት ላይ ካለው ነባራዊ እውነት ጋር የማይገናኝ ነው፡፡ ዋናው ዓላማውም ኢትዮጵያ በውኃ ሀብቷ እያስመዘገበች ያለው የልማት ስኬት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ሚዛን ለውጥ የፈጠረባቸውን የሥነ-ልቦና መረበሽ ለመሸፈን የሚደረግ መፍጨርጨር ነው።
ካይሮ ዓለም አቀፍ ሕግን እንደ ሽፋን ብትጠቀምም፣ ትክክለኛው የውስጥ ሕመሟ የውኃ እጥረት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማንሰራራት እንደ ስጋት የመመልከትና የተፈጥሮ ሃብቷን ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት ለመግታት ያለመ ነው።
ግብፅ በረሃን እያለማች፣ ቶሽካን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ውኃ የሚጠይቁ ሰብሎችን በበረሃ እያመረተች፣ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዋን ተጠቅማ ዜጎቿን ከድህነት ለማውጣት የምታደርገውን ጥረት እንደ ሥጋት መመልከቷ የፖለቲካ ግብዝነቷ ማሳያ ነው።
ታሪካዊ ዳራዎችን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንፈትሽ ግብፅ ኢትዮጵያን በውኃ ሀብቷ እንዳትጠቀም ስትጎነጉነው የኖረችው ሤራ ዘርፈ ብዙ ነው። በአንድ በኩል ኢትዮጵያ ፈፅሞ ዕውቅና ያልሰጠቻቸውን የ1929 እና የ1959 (እ.አ.አ) የቅኝ ግዛት ውሎችን እንደ ብቸኛ የሕግ ማዕቀፍ እያነሳች ለማስፈራራት ትሞክራለች።
በሌላ በኩል ደግሞ፣ ኢትዮጵያ የውኃ ሃብቷን ለማልማት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እና እርዳታ እንዳይሰጧት ያልቆፈረችው የዲፕሎማሲ ጉድጓድ አልነበረም።
ከዚህም አልፎ ኢትዮጵያ ዕረፍት አግኝታ ወደ ልማቷ እንዳታተኩር የውስጥ ግጭቶችን በሎጂስቲክስ እና በፋይናንስ በመደገፍ እንዲሁም ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በማሰባሰብ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ይሁን እንጂ ይህ የዘመናት ሤራ ከሽፎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ የፋይናንስ በሮች መዘጋትን በገዛ ዜጎቿ አቅምና ላብ ተክታ ልማቷን እውን ስታደርግ ማየቷ ካይሮን ወደ ያልተገባ መደናገጥ ከትቷታል። የአሁኑ መሠረተ ቢስ መግለጫም የዚሁ ድንጋጤ ማስተጋቢያ ነው።
የኢትዮጵያ በዓባይ ውኃ ላይ ያላት አቋም ከመቼውም ጊዜ በላይ የጠራ፣ ዓለም አቀፍ የውኃ ሕግጋትን ያከበረ እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ነው።
ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስትገነባም ሌሎች የተፋሰሱን ሀገራት በማግለል ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ ተመስርታ ነው። ለዚህም ማሳያው ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ያደረገችው ተከታታይ ውይይት እና ያሳየችው ግልፅነት ነው።
ከዚህም ባሻገር የናይል ተፋሰስ ሀገራት የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በቅርቡ ወደ ትግበራ መግባቱ የጋራ ተጠቃሚነትን በተግባር ያረጋገጠ እና የግብፅን የብቻ የበላይነት ፍላጎት ሕገ-ወጥነት ያጋለጠ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ሕጋዊ ድል ነው።
የግብፅ የአሁኑ ጥያቄ እና ጩኸት ጊዜ ያለፈበት እና አዲሱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነው። ካይሮ ጉዳዩ ፈፅሞ የማይመለከታቸውን የሩቅ ኃይሎችና ተቋማት ደቦ በመሰብሰብ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ዛሬ ላይ ውኃ አያነሳም።
የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መንግሥት በዲፕሎማሲ ጫና እጁ የማይጠመዘዝ መሆኑን በሕዳሴው ግድብ ስኬት በተግባር አሳይቷል።
በመሆኑም ለግብፅ የሚበጃት ብቸኛው አዋጭ አማራጭ ከንቱ ከሆነው የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የደቦ ዲፕሎማሲ ወጥታ፣ አዲሱን የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በመቀበል ከኢትዮጵያ እና ከተቀሩት የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መሥራት ብቻ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ebc #ethiopia #gerd #nilebasin #africansolutions #abay #diplomacy
*********************
የግብፅ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር “በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ የውኃ መብቴን ለማስከበር ቁርጠኛ ነኝ” በሚል ያወጣው መግለጫ፣ የካይሮ ፖለቲከኞች ለዘመናት ሲያላምጡት የኖሩትና አሁንም መላቀቅ ያቃታቸው የተለመደ የሚዲያ ፍጆታ ነው።
ይህ መግለጫ መሬት ላይ ካለው ነባራዊ እውነት ጋር የማይገናኝ ነው፡፡ ዋናው ዓላማውም ኢትዮጵያ በውኃ ሀብቷ እያስመዘገበች ያለው የልማት ስኬት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ሚዛን ለውጥ የፈጠረባቸውን የሥነ-ልቦና መረበሽ ለመሸፈን የሚደረግ መፍጨርጨር ነው።
ካይሮ ዓለም አቀፍ ሕግን እንደ ሽፋን ብትጠቀምም፣ ትክክለኛው የውስጥ ሕመሟ የውኃ እጥረት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማንሰራራት እንደ ስጋት የመመልከትና የተፈጥሮ ሃብቷን ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት ለመግታት ያለመ ነው።
ግብፅ በረሃን እያለማች፣ ቶሽካን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ውኃ የሚጠይቁ ሰብሎችን በበረሃ እያመረተች፣ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዋን ተጠቅማ ዜጎቿን ከድህነት ለማውጣት የምታደርገውን ጥረት እንደ ሥጋት መመልከቷ የፖለቲካ ግብዝነቷ ማሳያ ነው።
ታሪካዊ ዳራዎችን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንፈትሽ ግብፅ ኢትዮጵያን በውኃ ሀብቷ እንዳትጠቀም ስትጎነጉነው የኖረችው ሤራ ዘርፈ ብዙ ነው። በአንድ በኩል ኢትዮጵያ ፈፅሞ ዕውቅና ያልሰጠቻቸውን የ1929 እና የ1959 (እ.አ.አ) የቅኝ ግዛት ውሎችን እንደ ብቸኛ የሕግ ማዕቀፍ እያነሳች ለማስፈራራት ትሞክራለች።
በሌላ በኩል ደግሞ፣ ኢትዮጵያ የውኃ ሃብቷን ለማልማት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እና እርዳታ እንዳይሰጧት ያልቆፈረችው የዲፕሎማሲ ጉድጓድ አልነበረም።
ከዚህም አልፎ ኢትዮጵያ ዕረፍት አግኝታ ወደ ልማቷ እንዳታተኩር የውስጥ ግጭቶችን በሎጂስቲክስ እና በፋይናንስ በመደገፍ እንዲሁም ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በማሰባሰብ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ይሁን እንጂ ይህ የዘመናት ሤራ ከሽፎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ የፋይናንስ በሮች መዘጋትን በገዛ ዜጎቿ አቅምና ላብ ተክታ ልማቷን እውን ስታደርግ ማየቷ ካይሮን ወደ ያልተገባ መደናገጥ ከትቷታል። የአሁኑ መሠረተ ቢስ መግለጫም የዚሁ ድንጋጤ ማስተጋቢያ ነው።
የኢትዮጵያ በዓባይ ውኃ ላይ ያላት አቋም ከመቼውም ጊዜ በላይ የጠራ፣ ዓለም አቀፍ የውኃ ሕግጋትን ያከበረ እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ነው።
ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስትገነባም ሌሎች የተፋሰሱን ሀገራት በማግለል ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ ተመስርታ ነው። ለዚህም ማሳያው ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ያደረገችው ተከታታይ ውይይት እና ያሳየችው ግልፅነት ነው።
ከዚህም ባሻገር የናይል ተፋሰስ ሀገራት የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በቅርቡ ወደ ትግበራ መግባቱ የጋራ ተጠቃሚነትን በተግባር ያረጋገጠ እና የግብፅን የብቻ የበላይነት ፍላጎት ሕገ-ወጥነት ያጋለጠ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ሕጋዊ ድል ነው።
የግብፅ የአሁኑ ጥያቄ እና ጩኸት ጊዜ ያለፈበት እና አዲሱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነው። ካይሮ ጉዳዩ ፈፅሞ የማይመለከታቸውን የሩቅ ኃይሎችና ተቋማት ደቦ በመሰብሰብ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ዛሬ ላይ ውኃ አያነሳም።
የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መንግሥት በዲፕሎማሲ ጫና እጁ የማይጠመዘዝ መሆኑን በሕዳሴው ግድብ ስኬት በተግባር አሳይቷል።
በመሆኑም ለግብፅ የሚበጃት ብቸኛው አዋጭ አማራጭ ከንቱ ከሆነው የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የደቦ ዲፕሎማሲ ወጥታ፣ አዲሱን የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በመቀበል ከኢትዮጵያ እና ከተቀሩት የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መሥራት ብቻ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ebc #ethiopia #gerd #nilebasin #africansolutions #abay #diplomacy
1 month ago
በምክክሩ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሴራ ይከሽፋል!
***********************
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት በድንበሯ ምሰሶዎች እና በጦር ኃይሏ ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በሕዝቦቿ ልብ ውስጥ በሚታነጸው የጋራ መግባባት እና በማይናወጠው የአንድነት ዐለት ላይ የቆመ ነው። ታላቋ ኢትዮጵያ፣ የዘመናት ፈተናዎችን ተሻግራ፣ በታሪክ አውሎ ንፋስ ውስጥ አልፋ ዛሬ ላይ የደረሰችው፣ በልጆቿ ደም እና አጥንት በተከፈለ መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ ከልዩነት ማዕበል በላይ በገነነ የውስጥ መተባበር እና የሕብረት ጸጋ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገራችን ቀና ብላ እንዳትራመድ፣ የጋራ ቋንቋ እና አንድ የልብ ትርታ እንዳይኖራት የባቢሎንን የመከፋፈል እርግማን ሲያዘንቡባት ኖረዋል። አንድ ሆነን የብልጽግናን ግንብ እንዳንገነባ ቋንቋችንን በማዘበራረቅ፣ አንዱን ወገን በመደለልና ሌላውን በማግለል ከጥንት ጀምሮ የልዩነት እና የጥላቻ መርዝ ሲግቱን ቆይተዋል።
የጠላቶቻችን ሴራ ጊዜና መልኩን ይቀይራል እንጂ ዓላማው አንድ እና ጥርት ያለ ነው፤ እርሱም ኢትዮጵያን የእርስ በርስ ጦርነት አውድማ ማድረግ፤ ከሁለቱ ውሃዎቿ ማራቅ ነው። ወንድም በወንድሙ ላይ ጠመንጃ እንዲያነሳ፣ እልህ አስጨራሽ እና ትውልድ አምካኝ የእርስ በርስ መተላለቅ ውስጥ እንድንዘፈቅ ጠላቶቻችን ያልሸረቡት አሻጥር፣ ያልቆፈሩት የጥፋት ጉድጓድ አልነበረም። አንዱን ወገን በስውር በማስታጠቅ፣ ሌላውን በማዳከም ለዘመናት በወንድማማቾች ደም ሲነግዱ ኖረዋል። ከዚህም አልፎ የኢትዮጵያን ጂኦፖለቲካዊ ጡንቻ በማዛል፣ ተፈጥሯዊ እና ታሪካዊ የባህር በሯን በማሳጣት፣ የውሃ ላይ እትብቷን በመበጠስ፣ በየብስ እንድትታጠር አድርገዋል። በኢኮኖሚ ደቅቃ፣ በፖለቲካ ተከፋፍላ እንደ ምስጥ በውስጧ በምትበላ ሀገር ላይ የራሳቸውን የባንዳ ዙፋን ለመትከል ያልፈነቀሉት ቋጥኝ አልነበረም።
ሆኖም የኢትዮጵያ የእምቢተኝነት፣ የአልደፈር ባይነት መንፈስ በመከራ ውስጥ የሚጠነክር፣ በእሳት የሚፈተን ወርቅ ነው! ጠላቶቻችን "ተበታተኑ፣ ፈረሱ፣ አከተመላቸው" ሲሉን፣ እኛ ግን ከውድቀታችን አፈር ውስጥ ዳግም እንመዘዛለን። እነሆ የፊታችን ሐምሌ 8 የሚጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የፖለቲካ ስብራታችንን የምንጠግንበት፣ የዘመናት ቁስላችንን በይቅርታ የምናክምበት የሕልውና እና የሉዓላዊነታችን ዋነኛ ምሰሶ ነው። ይህ ጉባዔ ተራ የፖለቲካ ልሂቃን የቃላት ጦርነት የሚደረግበት አውድማ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጣሪያ ስር ተሰባስበው፣ በገዛ ሀገራቸው እጣ ፈንታ ላይ የራሳቸውን የስምምነት ማህተም የሚያኖሩበት የነጻነት መድረክ ነው። ይህ የሰለጠነ ምክክር በራሱ የሉዓላዊነት ትልቅ መገለጫ ነው፤ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በጽኑ የሚዘጋ፣ የጠላትን ሴራ ከሥሩ የሚነቅል የብሔራዊ መግባባት የጋራ ቃል ኪዳን ነው።
ታሪክ እንደመሰከረው፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ልብ ሲመክሩ እና ሲተባበሩ የውጭ ጠላቶች ሐፍረት ይከናነባሉ። ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን፣ "እኔ" ከሚለው ራስ ወዳድነት ወጥተን "እኛ" በሚል ጽኑ መንፈስ በአንድነት ስንቆም፣ የማይደፈረውን የዓባይን ወንዝ ገድበን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን አድርገናል። በተመሳሳይ፣ ከዘመናት የመልክዓ ምድር እስራታችን በጥሰን ለመውጣት፣ ታሪካዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት መብታችንን ለማረጋገጥ በምናደርገው ፍትሐዊ የዲፕሎማሲ እና የጂኦፖለቲካ ጉዞ፣ ዳግም ብሔራዊ አንድነታችንን ለዓለም እያረጋገጥን ነው። በባቢሎን ሕዝብ ላይ እንደሆነው ጠላት ቋንቋችንን ሊያዘበራርቅ ሲጥር፣ እኛ ግን የልማት፣ የሰላም እና የብልጽግናን አንድ ቋንቋ መናገር ጀምረናል።
በመሆኑም፣ ሐምሌ 8 የሚጠነሰሰው ሀገራዊ ምክክር፣ ኢትዮጵያን ከውስጥ አጽንቶ፣ ከውጭ የሚመጣባትን የጥፋት ማዕበል የሚመክት የማይበገር ጋሻችን ነው። በምክክሩ፣ ለዘመናት የተነዛው የጥላቻ እና የመከፋፈል ትርክት ይከሽፋል፤ በምክክሩ፣ ሀገረ-መንግሥቱን ለማፍረስ የተወጠነው የጠላት ሴራ የሸረሪት ድር ሆኖ ይበጣጠሳል! ዛሬ ከስሜት ፖለቲካ ወጥተን በምክንያት እና በስክነት ስንመክር፣ የዘመናት የኢትዮጵያ ጠላቶች አንገታቸውን ይደፋሉ። የኢትዮጵያ ሕዳሴ በልጆቿ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር፣ በጥልቅ መከባበር እና በጽኑ አንድነት በዐለት ላይ ተመስርቶ ወደ ፊት ይገሰግሳል። አዎ! በምክክሩ የጠላት ሴራ ይከሽፋል፤ ታላቂቱ ኢትዮጵያም ለዘለዓለም በክብር ጸንታ ትኖራለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #socialcontract #ebc
***********************
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት በድንበሯ ምሰሶዎች እና በጦር ኃይሏ ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በሕዝቦቿ ልብ ውስጥ በሚታነጸው የጋራ መግባባት እና በማይናወጠው የአንድነት ዐለት ላይ የቆመ ነው። ታላቋ ኢትዮጵያ፣ የዘመናት ፈተናዎችን ተሻግራ፣ በታሪክ አውሎ ንፋስ ውስጥ አልፋ ዛሬ ላይ የደረሰችው፣ በልጆቿ ደም እና አጥንት በተከፈለ መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ ከልዩነት ማዕበል በላይ በገነነ የውስጥ መተባበር እና የሕብረት ጸጋ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገራችን ቀና ብላ እንዳትራመድ፣ የጋራ ቋንቋ እና አንድ የልብ ትርታ እንዳይኖራት የባቢሎንን የመከፋፈል እርግማን ሲያዘንቡባት ኖረዋል። አንድ ሆነን የብልጽግናን ግንብ እንዳንገነባ ቋንቋችንን በማዘበራረቅ፣ አንዱን ወገን በመደለልና ሌላውን በማግለል ከጥንት ጀምሮ የልዩነት እና የጥላቻ መርዝ ሲግቱን ቆይተዋል።
የጠላቶቻችን ሴራ ጊዜና መልኩን ይቀይራል እንጂ ዓላማው አንድ እና ጥርት ያለ ነው፤ እርሱም ኢትዮጵያን የእርስ በርስ ጦርነት አውድማ ማድረግ፤ ከሁለቱ ውሃዎቿ ማራቅ ነው። ወንድም በወንድሙ ላይ ጠመንጃ እንዲያነሳ፣ እልህ አስጨራሽ እና ትውልድ አምካኝ የእርስ በርስ መተላለቅ ውስጥ እንድንዘፈቅ ጠላቶቻችን ያልሸረቡት አሻጥር፣ ያልቆፈሩት የጥፋት ጉድጓድ አልነበረም። አንዱን ወገን በስውር በማስታጠቅ፣ ሌላውን በማዳከም ለዘመናት በወንድማማቾች ደም ሲነግዱ ኖረዋል። ከዚህም አልፎ የኢትዮጵያን ጂኦፖለቲካዊ ጡንቻ በማዛል፣ ተፈጥሯዊ እና ታሪካዊ የባህር በሯን በማሳጣት፣ የውሃ ላይ እትብቷን በመበጠስ፣ በየብስ እንድትታጠር አድርገዋል። በኢኮኖሚ ደቅቃ፣ በፖለቲካ ተከፋፍላ እንደ ምስጥ በውስጧ በምትበላ ሀገር ላይ የራሳቸውን የባንዳ ዙፋን ለመትከል ያልፈነቀሉት ቋጥኝ አልነበረም።
ሆኖም የኢትዮጵያ የእምቢተኝነት፣ የአልደፈር ባይነት መንፈስ በመከራ ውስጥ የሚጠነክር፣ በእሳት የሚፈተን ወርቅ ነው! ጠላቶቻችን "ተበታተኑ፣ ፈረሱ፣ አከተመላቸው" ሲሉን፣ እኛ ግን ከውድቀታችን አፈር ውስጥ ዳግም እንመዘዛለን። እነሆ የፊታችን ሐምሌ 8 የሚጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የፖለቲካ ስብራታችንን የምንጠግንበት፣ የዘመናት ቁስላችንን በይቅርታ የምናክምበት የሕልውና እና የሉዓላዊነታችን ዋነኛ ምሰሶ ነው። ይህ ጉባዔ ተራ የፖለቲካ ልሂቃን የቃላት ጦርነት የሚደረግበት አውድማ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጣሪያ ስር ተሰባስበው፣ በገዛ ሀገራቸው እጣ ፈንታ ላይ የራሳቸውን የስምምነት ማህተም የሚያኖሩበት የነጻነት መድረክ ነው። ይህ የሰለጠነ ምክክር በራሱ የሉዓላዊነት ትልቅ መገለጫ ነው፤ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በጽኑ የሚዘጋ፣ የጠላትን ሴራ ከሥሩ የሚነቅል የብሔራዊ መግባባት የጋራ ቃል ኪዳን ነው።
ታሪክ እንደመሰከረው፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ልብ ሲመክሩ እና ሲተባበሩ የውጭ ጠላቶች ሐፍረት ይከናነባሉ። ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን፣ "እኔ" ከሚለው ራስ ወዳድነት ወጥተን "እኛ" በሚል ጽኑ መንፈስ በአንድነት ስንቆም፣ የማይደፈረውን የዓባይን ወንዝ ገድበን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን አድርገናል። በተመሳሳይ፣ ከዘመናት የመልክዓ ምድር እስራታችን በጥሰን ለመውጣት፣ ታሪካዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት መብታችንን ለማረጋገጥ በምናደርገው ፍትሐዊ የዲፕሎማሲ እና የጂኦፖለቲካ ጉዞ፣ ዳግም ብሔራዊ አንድነታችንን ለዓለም እያረጋገጥን ነው። በባቢሎን ሕዝብ ላይ እንደሆነው ጠላት ቋንቋችንን ሊያዘበራርቅ ሲጥር፣ እኛ ግን የልማት፣ የሰላም እና የብልጽግናን አንድ ቋንቋ መናገር ጀምረናል።
በመሆኑም፣ ሐምሌ 8 የሚጠነሰሰው ሀገራዊ ምክክር፣ ኢትዮጵያን ከውስጥ አጽንቶ፣ ከውጭ የሚመጣባትን የጥፋት ማዕበል የሚመክት የማይበገር ጋሻችን ነው። በምክክሩ፣ ለዘመናት የተነዛው የጥላቻ እና የመከፋፈል ትርክት ይከሽፋል፤ በምክክሩ፣ ሀገረ-መንግሥቱን ለማፍረስ የተወጠነው የጠላት ሴራ የሸረሪት ድር ሆኖ ይበጣጠሳል! ዛሬ ከስሜት ፖለቲካ ወጥተን በምክንያት እና በስክነት ስንመክር፣ የዘመናት የኢትዮጵያ ጠላቶች አንገታቸውን ይደፋሉ። የኢትዮጵያ ሕዳሴ በልጆቿ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር፣ በጥልቅ መከባበር እና በጽኑ አንድነት በዐለት ላይ ተመስርቶ ወደ ፊት ይገሰግሳል። አዎ! በምክክሩ የጠላት ሴራ ይከሽፋል፤ ታላቂቱ ኢትዮጵያም ለዘለዓለም በክብር ጸንታ ትኖራለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #socialcontract #ebc
1 month ago
#ለጎፎሬ_ደብረ_መንክራት_በአታ_ለማርያም_ቤ /ክ ህንፃ ማሰሪ
ያ
#10000ሺህ ሰው #100 #100 ብር ብያወጣ #1000000 ይሆናል ይህ ቀላል አይደለምና #100 ብር ብቻ ሰጥተን ምዕመናን ተቀድሶ በ40 በ80 እንዲጠመቁና እንዲቆርቡ ፍትሓት እንዲደረግላቸው ከምሥጢረተ ቤተክርስቲያን እንድሳተፉ ምክንያት እንሁን።
ለሊቀ ካህናት ክርስቶስ ቅድስተ ቅዱሳን ለሆነች ለእመብርሃን ለስሟ መጠሪያ መታሰቢያ መቅደስ እንስራ!!!
🙏እስከሁን የመሠረቱ ሥራ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ስሆን የኮሎን ሙሌት ለመከናወን #ከ100ብር ጀምሮ ድጋፍ እንድታደርግ እጅግ ተመጽነናል።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
🙏 degnet0321
ያ
#10000ሺህ ሰው #100 #100 ብር ብያወጣ #1000000 ይሆናል ይህ ቀላል አይደለምና #100 ብር ብቻ ሰጥተን ምዕመናን ተቀድሶ በ40 በ80 እንዲጠመቁና እንዲቆርቡ ፍትሓት እንዲደረግላቸው ከምሥጢረተ ቤተክርስቲያን እንድሳተፉ ምክንያት እንሁን።
ለሊቀ ካህናት ክርስቶስ ቅድስተ ቅዱሳን ለሆነች ለእመብርሃን ለስሟ መጠሪያ መታሰቢያ መቅደስ እንስራ!!!
🙏እስከሁን የመሠረቱ ሥራ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ስሆን የኮሎን ሙሌት ለመከናወን #ከ100ብር ጀምሮ ድጋፍ እንድታደርግ እጅግ ተመጽነናል።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
🙏 degnet0321
1 month ago
❤በእንተ ስማ ለማርያም❤ሼር እናድርግ🙏
👉ለኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በሙሉ ደቡብ ላይ ላለችው ቤተክርስቲያን እንድረስላት ።
❤በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በከምባታ ጠምባሮና አላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጎፎሬ ደብረ መንክራት በዓታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን በጋራ እንሰራ። እነዚህ ጥቂት ምዕመናን ለሀገራቸውና ለነፍሳቸው የሚጸልዩበትን፣ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚያገኙትን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበትን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ለመሥራት ለበርካታ ዓመታት ያሰቡ ቢሆንም በእነርሱ አቅም የሚሆን አይደለምና ተስፋ ቆርጠው ይገኛሉ።
በጎን ደግሞ የሌሎች የእምነት ድርጀቶች በዚህ ደሳሳ ጎጆ የሚትጸልዩ አቅም የሌላችሁ ነችሁና ወደ እኛ ኑ በማለት ታላቅ የሆነ የስነልቦና ጫና እያደረሱባቸው ይገኛሉ እነርሱ ግን ይህንንና ሌሎችንም ጫናዎችን ችላው በሃይማኖታቸው ጸንተው ዛሬም አሉ ።
ስለዚህ ውድ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ለበጎ ነገር የሚትተጉ የተዘጉና የተዘነጉ የገጣሪቷን ቤተክርስቲያን ለማገዝና በረከት ለማግኘት ሁሌ የምትጥሩ በሀገር ውስጥና በውጪ የሚትኖሩ በዚህ ሥራ እንድትሰተፋ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን ።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
🙏 degnet0321
👉ለኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን በሙሉ ደቡብ ላይ ላለችው ቤተክርስቲያን እንድረስላት ።
❤በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በከምባታ ጠምባሮና አላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የጎፎሬ ደብረ መንክራት በዓታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን በጋራ እንሰራ። እነዚህ ጥቂት ምዕመናን ለሀገራቸውና ለነፍሳቸው የሚጸልዩበትን፣ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚያገኙትን፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበትን የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ለመሥራት ለበርካታ ዓመታት ያሰቡ ቢሆንም በእነርሱ አቅም የሚሆን አይደለምና ተስፋ ቆርጠው ይገኛሉ።
በጎን ደግሞ የሌሎች የእምነት ድርጀቶች በዚህ ደሳሳ ጎጆ የሚትጸልዩ አቅም የሌላችሁ ነችሁና ወደ እኛ ኑ በማለት ታላቅ የሆነ የስነልቦና ጫና እያደረሱባቸው ይገኛሉ እነርሱ ግን ይህንንና ሌሎችንም ጫናዎችን ችላው በሃይማኖታቸው ጸንተው ዛሬም አሉ ።
ስለዚህ ውድ ኦርቶዶክሳውያን ምዕመናን ለበጎ ነገር የሚትተጉ የተዘጉና የተዘነጉ የገጣሪቷን ቤተክርስቲያን ለማገዝና በረከት ለማግኘት ሁሌ የምትጥሩ በሀገር ውስጥና በውጪ የሚትኖሩ በዚህ ሥራ እንድትሰተፋ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን ።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
🙏 degnet0321
Sponsored by
Surafel
1 month ago
“ኢትዮጵያ አንድ ቪዛ ብቻ ወስደው መላውን ዓለም የሚያዩባት ድንቅ ሀገር ናት” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
የአረንጓዴ ዐሻራ እና የሕዳሴ ግድብ ስትራቴጂያዊ ቁርኝት
***********************
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ሂደት ቀጥተኛና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
በመርሐ ግብሩ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ማልማት ተችሏል።
በተለይ በዓባይ ተፋሰስ የሚከናወኑ የደን ልማት ሥራዎች መሬቱ ዝናብን አምቆ እንዲይዝ በማድረጋቸው ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውሃ መጠን ወጥ እና አስተማማኝ እንዲሆን አስችሏል።
ይህ የተፈጥሮ ሚዛንን የመጠበቅ ሂደት ግድቡ ያለ ምንም የውኃ እጥረት በታቀደለት ጊዜ በሙሉ አቅሙ ውኃ እንዲይዝ ትልቅ አቅም ሆኗል።
ከውኃ ሙሌቱ ባለፈ የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራ ግድቡ ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት እንዲሰጥ እና የኃይል ማመንጨት ሂደቱ እንዳይስተጓጎል በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል።
በዓባይ ተፋሰስ የተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን በከፍተኛ ደረጃ ስለሚከላከሉ ወደ ግድቡ የሚገባው የደለል መጠን በእጅጉ ቀንሷል።
ይህም የግድቡን ውኃ የመያዝ አቅም ከመጠበቁም በላይ ኃይል የሚያመነጩ ተርባይኖችን ከብልሽት በመታደግ የኤሌክትሪክ ምርቱ በስኬት እንዲቀጥል እያደረገ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የአየር ንብረት መጠበቂያ ብቻ ሳይሆን፣ የሕዳሴ ግድብን ኢንቨስትመንት እና የልማት ጉዞ የሚያስቀጥል ታላቅ ብሔራዊ ጋሻ ነው።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው ከግድቡ አሠራር ጋር መቀናጀቱ ዘላቂና አስተማማኝ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምን በተግባር ያሳየ ስኬታማ ሞዴል ሆኖ ይጠቀሳል።
የአረንጓዴ ዐሻራ እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቁርኝት ሀገራችን የልማት አጀንዳዋን በተፈጥሮ ጥበቃ የተደገፈ ለማድረግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #gerd #environmentalprotection #watersecurity #ebc
***********************
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ሂደት ቀጥተኛና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
በመርሐ ግብሩ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ማልማት ተችሏል።
በተለይ በዓባይ ተፋሰስ የሚከናወኑ የደን ልማት ሥራዎች መሬቱ ዝናብን አምቆ እንዲይዝ በማድረጋቸው ወደ ግድቡ የሚፈሰው የውሃ መጠን ወጥ እና አስተማማኝ እንዲሆን አስችሏል።
ይህ የተፈጥሮ ሚዛንን የመጠበቅ ሂደት ግድቡ ያለ ምንም የውኃ እጥረት በታቀደለት ጊዜ በሙሉ አቅሙ ውኃ እንዲይዝ ትልቅ አቅም ሆኗል።
ከውኃ ሙሌቱ ባለፈ የአረንጓዴ ዐሻራ ሥራ ግድቡ ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት እንዲሰጥ እና የኃይል ማመንጨት ሂደቱ እንዳይስተጓጎል በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና ይጫወታል።
በዓባይ ተፋሰስ የተተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን በከፍተኛ ደረጃ ስለሚከላከሉ ወደ ግድቡ የሚገባው የደለል መጠን በእጅጉ ቀንሷል።
ይህም የግድቡን ውኃ የመያዝ አቅም ከመጠበቁም በላይ ኃይል የሚያመነጩ ተርባይኖችን ከብልሽት በመታደግ የኤሌክትሪክ ምርቱ በስኬት እንዲቀጥል እያደረገ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ የአየር ንብረት መጠበቂያ ብቻ ሳይሆን፣ የሕዳሴ ግድብን ኢንቨስትመንት እና የልማት ጉዞ የሚያስቀጥል ታላቅ ብሔራዊ ጋሻ ነው።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው ከግድቡ አሠራር ጋር መቀናጀቱ ዘላቂና አስተማማኝ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምን በተግባር ያሳየ ስኬታማ ሞዴል ሆኖ ይጠቀሳል።
የአረንጓዴ ዐሻራ እና ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ቁርኝት ሀገራችን የልማት አጀንዳዋን በተፈጥሮ ጥበቃ የተደገፈ ለማድረግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #gerd #environmentalprotection #watersecurity #ebc
1 month ago
#ከ100ብር ጀምሮ በመለገስ የበአታ ለማርያምን ቤተመቅደስ ኮሎን እንሙላ🙏
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን የሁል ጊዜ ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራና የመቅደሱ አራቱ ኮሎን ተሞልቷል።
ለዚህም ድጋፋችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንዲሁም በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እያመሰገንን ለቀጣዩ የኮሎን ሙሌትና ለሌሎችም ሥራዎች የተለመደውን #ከ100ብር ጀምሮ ድጋፍ በማድረግ የልዑል እግዚአብሔርን ቤት እንዲሁም የበአታ ለማርያም መታሰቢያ ሠርተን በረከተ ሥጋ ወነፍስ እንድናገኝና ለገጠሩ ምዕመናን አለኝታ እንድንሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
👉 degnet0321
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን የሁል ጊዜ ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራና የመቅደሱ አራቱ ኮሎን ተሞልቷል።
ለዚህም ድጋፋችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም እንዲሁም በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እያመሰገንን ለቀጣዩ የኮሎን ሙሌትና ለሌሎችም ሥራዎች የተለመደውን #ከ100ብር ጀምሮ ድጋፍ በማድረግ የልዑል እግዚአብሔርን ቤት እንዲሁም የበአታ ለማርያም መታሰቢያ ሠርተን በረከተ ሥጋ ወነፍስ እንድናገኝና ለገጠሩ ምዕመናን አለኝታ እንድንሆን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281 #አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815 #ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610 #አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701 #አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101 #ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
አባቶች በጸሎት እንዲያስቡ የክርስትና ስማችሁን
👉 degnet0321
2 months ago
🙏ድንግል ማርያምን የምትወዷት #100ብር ብቻ
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራ ተጠናቋል።
ቀጠይ ሥራዎቹ የኮሎንና ሌሎችም ሥራዎች ይገኛሉ ለዚህ የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች
ፌሮ ብረት ባለ 14 ባለ 10 ባለ 8 አሸዋ ጠጠር ሲሚንቶ ስሆን ውድ የተዋህዶ ልጆች የተለመደውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ የእመቤታችንን የቅድስት በአታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን ለፍጻሜ እንድናደርስ #100ብር #100 ,000 ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍ እንድያደርጉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
#አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
#ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
#አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
#አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
#ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን #ሼር #ሼር
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራ ተጠናቋል።
ቀጠይ ሥራዎቹ የኮሎንና ሌሎችም ሥራዎች ይገኛሉ ለዚህ የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች
ፌሮ ብረት ባለ 14 ባለ 10 ባለ 8 አሸዋ ጠጠር ሲሚንቶ ስሆን ውድ የተዋህዶ ልጆች የተለመደውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ የእመቤታችንን የቅድስት በአታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን ለፍጻሜ እንድናደርስ #100ብር #100 ,000 ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍ እንድያደርጉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
#አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
#ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
#አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
#አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
#ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን #ሼር #ሼር
2 months ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
2 months ago
✍️#100ብር #ለ10000 የበአታ ለማርያም ወዳጆች🙏
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራ ተጠናቋል።
ቀጠይ ሥራዎቹ የኮሎንና ሌሎችም ሥራዎች ይገኛሉ ለዚህ የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች
ፌሮ ብረት ባለ 14 ባለ 10 ባለ 8 አሸዋ ጠጠር ሲሚንቶ ስሆን ውድ የተዋህዶ ልጆች የተለመደውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ የእመቤታችንን የቅድስት በአታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን ለፍጻሜ እንድናደርስ #100ብር #100 ,000 ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍ እንድያደርጉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
#አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
#ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
#አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
#አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
#ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን
በከምባታ ጠምባሮና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በእናንተ በውድ ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍና ትብብር የመሠረቱ ሥራ ተጠናቋል።
ቀጠይ ሥራዎቹ የኮሎንና ሌሎችም ሥራዎች ይገኛሉ ለዚህ የሚያስፈልጉ ማቴሪያሎች
ፌሮ ብረት ባለ 14 ባለ 10 ባለ 8 አሸዋ ጠጠር ሲሚንቶ ስሆን ውድ የተዋህዶ ልጆች የተለመደውን ድጋፍና ትብብር በማድረግ የእመቤታችንን የቅድስት በአታ ለማርያም ህንፃ ቤተክርስቲያን ለፍጻሜ እንድናደርስ #100ብር #100 ,000 ኦርቶዶክሳውያን ድጋፍ እንድያደርጉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም እንጠይቃለን።
❤ድጋፍ ለማድረግ ጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ አሳሪ
#የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
#አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
#ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
#አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
#አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
#ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
📞 ለበለጠ መረጃ፦ 0933055802 ወይም 0911414852
(ድጋፍ ሲያደርጉ የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ - በጸሎት እንድናስብዎት)
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የኢትዮጵያ ስም የጣማቸው ትራምፕ አሁንም ስለግድቡ እየለፈፉ ናቸው!
በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ "ድርድር ለማስጀመር" ሁሉ ማቀዳቸውን እየተናገሩ ናቸው።
በፈረንሳይ የቡድን 7 ጉባዔ ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ ጋር የተገናኙት ትራምፕ፤ የዓባይ ግድብ "ውዝግብንም በድጋሚ ይጀመራል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከሁለትዮሽ ውይይት በኋላ “ከግብጹ ፕሬዝዳንት፣ ከጓደኛዬ ጋር በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። እሳቸው በመላው ዓለም የተከበሩ ናቸው... ግንኙነታችንም በግል ደረጃ ለረጅም ጊዜ በጣም ጠንካራ ሆኖ ቆይቷል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከአልሲሲ ጋር ጥሩ ወዳጅነት እንዳላቸው የገለፁት ትራምፕ፣ "ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ነው የተገነባው" በማለት ገልጸዋል።
"ግዙፍ ግድብ" ሲሉ በጠሩት የህዳሴ ግድብ ላይ "መፍትሔ የሚያመጣ ውይይት እናስጀምራለን" ያሉት ፕሬዝዳንቱ “የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉም ገልጸዋል።
"በኢትዮጵያ የተገነባው ግድብ በግብፅ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ ነው" በማለትም የተለመደ ግጭት ቀስቃሽ ንግግር አድርገዋል።
ትራምፕ ለአል-ሲሲ ሲናገሩ "እውነቱን ማወቅ ከፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጣም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ነው የተያዛችሁት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አነሳስተዋቸዋል። #aljazeera
Seledadotio
Seledadotio
በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ አወዛጋቢ ንግግር የሚያደርጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በድጋሚ "የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ "ድርድር ለማስጀመር" ሁሉ ማቀዳቸውን እየተናገሩ ናቸው።
በፈረንሳይ የቡድን 7 ጉባዔ ላይ ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል-ሲሲ ጋር የተገናኙት ትራምፕ፤ የዓባይ ግድብ "ውዝግብንም በድጋሚ ይጀመራል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከሁለትዮሽ ውይይት በኋላ “ከግብጹ ፕሬዝዳንት፣ ከጓደኛዬ ጋር በመሆኔ ታላቅ ደስታ ይሰማኛል። እሳቸው በመላው ዓለም የተከበሩ ናቸው... ግንኙነታችንም በግል ደረጃ ለረጅም ጊዜ በጣም ጠንካራ ሆኖ ቆይቷል" ሲሉ ተደምጠዋል።
ከአልሲሲ ጋር ጥሩ ወዳጅነት እንዳላቸው የገለፁት ትራምፕ፣ "ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ነው የተገነባው" በማለት ገልጸዋል።
"ግዙፍ ግድብ" ሲሉ በጠሩት የህዳሴ ግድብ ላይ "መፍትሔ የሚያመጣ ውይይት እናስጀምራለን" ያሉት ፕሬዝዳንቱ “የግድቡን ጉዳይ አሁንም እናየዋለን፣ ለመፍታትም ጥረት እናደርጋለን" ሲሉም ገልጸዋል።
"በኢትዮጵያ የተገነባው ግድብ በግብፅ ላይ ከፍተኛ ችግር እያስከተለ ነው" በማለትም የተለመደ ግጭት ቀስቃሽ ንግግር አድርገዋል።
ትራምፕ ለአል-ሲሲ ሲናገሩ "እውነቱን ማወቅ ከፈለጉ፣ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በጣም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ነው የተያዛችሁት ብዬ አስባለሁ" ሲሉ አነሳስተዋቸዋል። #aljazeera
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በምርምር እና በስትራቴጂያዊ ትንተና የተደገፈ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
2 months ago
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን
የገጠር አድባራትን እና ደብራትን ለመደገፍ የቀረበ ጥሪ
#ethiopia | በከምባታ ጠምባሮ እና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በምዕመናን ሁለንተናዊ እገዛ የመሠረት ግንባታዋ ተጠናቋል።
ለቀጣዩ የዕድገት ምዕራፍ የዓምዶች እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎችን ለማከናወን እንደ ፌሮ ብረት (ባለ 14፣ 10 እና 8)፣ አሸዋ፣ ጠጠር እና ሲሚንቶ ያሉ የግንባታ ቁሳቁሶች በአስቸኳይ ያስፈልጋሉ።
የተዋሕዶ ልጆች ልማዱን የበረከት ተሳትፎ በማድረግ የቅድስት በአታ ለማርያምን የሕንጻ ግንባታ ከፍጻሜ ለማድረስ የበኩላችሁን እንድትወጡ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ጥሪ ቀርቧል።
የሕንጻ አሳሪ ኮሚቴው የባንክ አካውንቶች፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0933055802 ወይም 0911414852 መገናኘት ይችላሉ።
ድጋፍ ሲያደርጉ በጸሎት እንድናስብዎት የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ።
እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና። (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #በአታ_ለማርያም #የበጎ_አድራጎት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን
የገጠር አድባራትን እና ደብራትን ለመደገፍ የቀረበ ጥሪ
#ethiopia | በከምባታ ጠምባሮ እና ሀላባ ሀገረ ስብከት በጠምባሮ ልዩ ወረዳ የምትገኘው የጎፎሬ ደብረ መንክራት በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን በምዕመናን ሁለንተናዊ እገዛ የመሠረት ግንባታዋ ተጠናቋል።
ለቀጣዩ የዕድገት ምዕራፍ የዓምዶች እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎችን ለማከናወን እንደ ፌሮ ብረት (ባለ 14፣ 10 እና 8)፣ አሸዋ፣ ጠጠር እና ሲሚንቶ ያሉ የግንባታ ቁሳቁሶች በአስቸኳይ ያስፈልጋሉ።
የተዋሕዶ ልጆች ልማዱን የበረከት ተሳትፎ በማድረግ የቅድስት በአታ ለማርያምን የሕንጻ ግንባታ ከፍጻሜ ለማድረስ የበኩላችሁን እንድትወጡ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ጥሪ ቀርቧል።
የሕንጻ አሳሪ ኮሚቴው የባንክ አካውንቶች፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000624326281
አቢሲኒያ ባንክ፦ 240587815
ዓባይ ባንክ፦ 362111107991610
አሐዱ ባንክ፦ 0081292811701
አዋሽ ባንክ፦ 013201006748101
ዳሽን ባንክ፦ 5640919295011
ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ በስልክ ቁጥሮች 0933055802 ወይም 0911414852 መገናኘት ይችላሉ።
ድጋፍ ሲያደርጉ በጸሎት እንድናስብዎት የክርስትና ስምዎን መላክዎን አይርሱ።
እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና። (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #በአታ_ለማርያም #የበጎ_አድራጎት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
🌐 የፌስቡክ ገጽ፦ https://www.facebook.com/d...
"እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (2ኛ ቆሮ. 9:7)
#ትኩረት_ለገጠር_ቤተክርስቲያን
2 months ago
ኢትዮጵያ የዓባይ ምንጭ.. የቀይ ባሕር ቁልፍ
https://youtu.be/TOizhJxRp... #ethiopia #redsea #tesfayebeljige #ethiopianhistory #redsea #redseacoast
Sponsored by
Surafel
Comments