16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምረት በኢራን ላይ የተከፈተውን ጦርነት ተከትሎ፣ የእስራኤል የደህንነት አካላት የኢራንን መንግስት ለመገልበጥ አቅደውት የነበረው እጅግ አስገራሚ ሚስጥራዊ ዕቅድ ይፋ መሆኑን ኒው ዮርክ ታይምስ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ፣ ዕቅዱ በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ የኢራኑን የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን እና ሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱን ባለስልጣናት በመግደል፣ በምትካቸው የቀድሞውን አወዛጋቢ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አህመዲነጃድን አዲስ የኢራን መሪ አድርጎ መሾም የሚል ነበር።
የሆሎኮስት (የአይሁዶች እልቂት) እውነታን በመካድ እና "እስራኤል ከካርታ ላይ መጥፋት አለባት" በሚሉ ቀስቃሽ ንግግሮቹ የሚታወቀው እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በፅኑ ሲደግፍ የነበረው አህመዲነጃድ ለዚህ ቦታ መመረጡ፣ ለኢራን የፖለቲካ ተንታኞች እጅግ ያልተጠበቀ እና አስገራሚ ምርጫ ሆኖባቸዋል። ኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጸው፣ አህመዲነጃድ ከዚህ ቀደም ከኢራኑ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጠንከር ያለ የፖለቲካ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ በቁም እስረኝነት ላይ ይገኝ የነበረ ቢሆንም፣ እስራኤል ግን እሱን እንደ አማራጭ መሪ ለመጠቀም ሚስጥራዊ ምክክር አድርጋበት ነበር።
ነገር ግን ዕቅዱ ሳይሳካ የቀረው አህመዲነጃድ ከቁም እስራት ለማምለጥ ሲሞክር በእስራኤል የአየር ድብደባ ሳቢያ ቴህራን ውስጥ በመቁሰሉ እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአደባባይ ባለመታየቱ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል ካዘጋጀቻቸው ዘርፈ ብዙ የጦርነት ምዕራፎች መካከል የመጀመሪያው በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት የኢራን መሪዎችን መምታት እና የኩርድ ታጣቂዎችን በኢራን ላይ ማሰለፍ የነበረ ቢሆንም፣ የኩርዶች ወረራ ግን ሳይሳካ ቀርቷል። ሆኖም እስራኤል በደረሰው የፖለቲካ ጫና እና በዋና ዋና መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ሳቢያ የኢራን ገዥ መደብ ሙሉ በሙሉ ይፈራርሳል፤ ከዚያም ያዘጋጀነው "አማራጭ መንግስት" ስልጣኑን ይረከባል የሚል እምነት ነበራት።
የሆሎኮስት (የአይሁዶች እልቂት) እውነታን በመካድ እና "እስራኤል ከካርታ ላይ መጥፋት አለባት" በሚሉ ቀስቃሽ ንግግሮቹ የሚታወቀው እንዲሁም የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በፅኑ ሲደግፍ የነበረው አህመዲነጃድ ለዚህ ቦታ መመረጡ፣ ለኢራን የፖለቲካ ተንታኞች እጅግ ያልተጠበቀ እና አስገራሚ ምርጫ ሆኖባቸዋል። ኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጸው፣ አህመዲነጃድ ከዚህ ቀደም ከኢራኑ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጠንከር ያለ የፖለቲካ ቅራኔ ውስጥ ገብቶ በቁም እስረኝነት ላይ ይገኝ የነበረ ቢሆንም፣ እስራኤል ግን እሱን እንደ አማራጭ መሪ ለመጠቀም ሚስጥራዊ ምክክር አድርጋበት ነበር።
ነገር ግን ዕቅዱ ሳይሳካ የቀረው አህመዲነጃድ ከቁም እስራት ለማምለጥ ሲሞክር በእስራኤል የአየር ድብደባ ሳቢያ ቴህራን ውስጥ በመቁሰሉ እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በአደባባይ ባለመታየቱ እንደሆነ ተገልጿል። እስራኤል ካዘጋጀቻቸው ዘርፈ ብዙ የጦርነት ምዕራፎች መካከል የመጀመሪያው በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት የኢራን መሪዎችን መምታት እና የኩርድ ታጣቂዎችን በኢራን ላይ ማሰለፍ የነበረ ቢሆንም፣ የኩርዶች ወረራ ግን ሳይሳካ ቀርቷል። ሆኖም እስራኤል በደረሰው የፖለቲካ ጫና እና በዋና ዋና መሰረተ ልማቶች ላይ በደረሰው ውድመት ሳቢያ የኢራን ገዥ መደብ ሙሉ በሙሉ ይፈራርሳል፤ ከዚያም ያዘጋጀነው "አማራጭ መንግስት" ስልጣኑን ይረከባል የሚል እምነት ነበራት።
25 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አዲሱ የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በህይወት እንዳሉ እንደሚያምኑ ገልጸዋል። ይሁን እንጂ መሪው በመጋቢት ወር መጀመሪያ አካባቢ የተገደሉትን አባታቸውን ለመተካት ከተሾሙበት ጊዜ አንስቶ በአደባባይ ታይተውም ሆነ ድምፃቸው ተሰምቶ አያውቅም።
ኔታንያሁ ከሲቢኤስ የቴሌቪዥን ጣቢያ "60 ሚኒትስ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ስለ አዲሱ መሪ (ታናሹ ኻሜኒ) አካላዊ ሁኔታ እና የአመራር ተጽዕኖ ተጠይቀው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲመልሱም፤ "በህይወት እንዳሉ አስባለሁ። ነገር ግን በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ለመናገር ይከብዳል። የሆነ የመሬት ውስጥ መሸሸጊያ (bunker) ወይም ሚስጥራዊ ቦታ ውስጥ ተደብቀዋል" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ሞጅታባ "ስልጣኑን እና ተጽዕኖውን ለማሳረፍ እየሞከረ ነው" ካሉ በኋላ፣ ነገር ግን ይህ የሞጅታባ ስልጣን ከቀድሞው መሪ (ከአባታቸው አሊ ኻሜኒ) ጋር ሲነጻጸር በእጅጉ ያነሰ መሆኑን ገምግመዋል።
ኔታንያሁ ከሲቢኤስ የቴሌቪዥን ጣቢያ "60 ሚኒትስ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ስለ አዲሱ መሪ (ታናሹ ኻሜኒ) አካላዊ ሁኔታ እና የአመራር ተጽዕኖ ተጠይቀው ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲመልሱም፤ "በህይወት እንዳሉ አስባለሁ። ነገር ግን በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ለመናገር ይከብዳል። የሆነ የመሬት ውስጥ መሸሸጊያ (bunker) ወይም ሚስጥራዊ ቦታ ውስጥ ተደብቀዋል" ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ሞጅታባ "ስልጣኑን እና ተጽዕኖውን ለማሳረፍ እየሞከረ ነው" ካሉ በኋላ፣ ነገር ግን ይህ የሞጅታባ ስልጣን ከቀድሞው መሪ (ከአባታቸው አሊ ኻሜኒ) ጋር ሲነጻጸር በእጅጉ ያነሰ መሆኑን ገምግመዋል።
2 months ago
"የተኩስ አቁም ስምምነቱ ሊባኖስን አይጨምርም" ኔታንያሁ
#fastmereja I የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያደረገችውን የሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደግፉም፣ ስምምነቱ እስራኤል በሊባኖስ የምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ እንደማያካትት በይፋ አስታወቁ። ይህ መግለጫ የወጣው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ "ተኩስ አቁሙ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ስፍራ ተግባራዊ ይሆናል" ካሉ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
ኔታንያሁ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መግለጫ፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ለአሜሪካና ለእስራኤል የኒውክሌርና የሚሳይል ስጋት እንዳትሆን የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚደግፉ ገልጸዋል። ሆኖም ግን "የሁለት ሳምንቱ የተኩስ አቁም ሊባኖስን አይጨምርም" በማለት እስራኤል በሰሜን በኩል ከሂዝቦላ ጋር የምታደርገውን ውጊያ እንደማታቆም ግልጽ አድርገዋል።
ሊባኖስ ወደዚህ ጦርነት የገባችው እ.ኤ.አ መጋቢት 2 ቀን የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ሂዝቦላ ጥቃት በመሰንዘሩ ነበር። በእስራኤል ጥቃት እስካሁን ከ1,500 በላይ ሊባኖሳውያን መገደላቸውና 1.2 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ መፈናቀላቸው ይነገራል።
ኔታንያሁ ይህን ይበሉ እንጂ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሰላም የሂዝቦላ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በኢራን የሚመራ በመሆኑ፣ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት በኢራንና በአሜሪካ መካከል የሚደረገው ድርድር ለሊባኖስ እጣ ፈንታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር ዛሬ ረቡዕ ጠዋት በደቡብ ሊባኖስ ስሪፋ እና ሳዲቂን በተባሉ አካባቢዎች የአየር ጥቃት መፈጸሙን የሀገሪቱ ብሔራዊ የዜና ወኪል ዘግቧል።
#fastmereja I የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ አሜሪካ ከኢራን ጋር ያደረገችውን የሁለት ሳምንት የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደግፉም፣ ስምምነቱ እስራኤል በሊባኖስ የምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ እንደማያካትት በይፋ አስታወቁ። ይህ መግለጫ የወጣው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ "ተኩስ አቁሙ ሊባኖስን ጨምሮ በሁሉም ስፍራ ተግባራዊ ይሆናል" ካሉ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው።
ኔታንያሁ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መግለጫ፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ለአሜሪካና ለእስራኤል የኒውክሌርና የሚሳይል ስጋት እንዳትሆን የሚያደርጉትን ጥረት እንደሚደግፉ ገልጸዋል። ሆኖም ግን "የሁለት ሳምንቱ የተኩስ አቁም ሊባኖስን አይጨምርም" በማለት እስራኤል በሰሜን በኩል ከሂዝቦላ ጋር የምታደርገውን ውጊያ እንደማታቆም ግልጽ አድርገዋል።
ሊባኖስ ወደዚህ ጦርነት የገባችው እ.ኤ.አ መጋቢት 2 ቀን የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ሂዝቦላ ጥቃት በመሰንዘሩ ነበር። በእስራኤል ጥቃት እስካሁን ከ1,500 በላይ ሊባኖሳውያን መገደላቸውና 1.2 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ መፈናቀላቸው ይነገራል።
ኔታንያሁ ይህን ይበሉ እንጂ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሰላም የሂዝቦላ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በኢራን የሚመራ በመሆኑ፣ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት በኢራንና በአሜሪካ መካከል የሚደረገው ድርድር ለሊባኖስ እጣ ፈንታ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር ዛሬ ረቡዕ ጠዋት በደቡብ ሊባኖስ ስሪፋ እና ሳዲቂን በተባሉ አካባቢዎች የአየር ጥቃት መፈጸሙን የሀገሪቱ ብሔራዊ የዜና ወኪል ዘግቧል።
3 months ago
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ ልጃቸው ሥልጣኑን የመረከቡ ጉዳይ ያሳስባቸው እንደነበር የአሜሪካ የስለላ መረጃ አሳየ
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው እርሳቸውን ተክቶ ሥልጣን እንዲይዝ የማድረግ ሀሳብ ላይ ጥርጣሬ እንደነበራቸው የአሜሪካ የስለላ መረጃ ማሳየቱን የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ።
ይህንን የሚገልጸው የስለላ መረጃ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዙሪያቸው ላሉ ጥቂት ሰዎች እንደቀረበ ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ያሳያል።
የቀድሞው አያቶላህ ልጃቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ብሩህ ጭንቅላት አለው የሚባል ባለመሆኑ እንዲሁም ለመሪነት ብቁ የሆነ ሰው ተደርጎ ባለመታየቱ ሥልጣኑን እንዳይረከብ ስጋት እንደነበራቸው የአሜሪካ ስለላ ትንተና አመልክቷል ተብሏል።
በተጨማሪም አባት በልጃቸው የግል ሕይወቱ ውስጥ ስላለው ችግር ያውቁ እንደነበር መረጃው እንዳሳየ ምንጮቹ ተናግረዋል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ከሳምንት በፊት ልጃቸው ሥልጣኑን ተረክበዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ በዚህ ሳምንት የሰጡት የመጀመሪያ መግለጫ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ቢነበብም ሥልጣኑን ከተረከቡ ወዲህ እስካሁን አልታዩም።
ሞጅታባ ሳይጎዱ አልቀሩም የሚሉ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አግራቺ ግን ጠቅላይ መሪ “ጥሩ ጤንነት ላይ” እንደሚገኙ እና “ሁኔታውን ሙሉ በሙሉ እየተቆጣጠሩ” መሆኑን በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።
BBC
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው እርሳቸውን ተክቶ ሥልጣን እንዲይዝ የማድረግ ሀሳብ ላይ ጥርጣሬ እንደነበራቸው የአሜሪካ የስለላ መረጃ ማሳየቱን የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ።
ይህንን የሚገልጸው የስለላ መረጃ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዙሪያቸው ላሉ ጥቂት ሰዎች እንደቀረበ ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ያሳያል።
የቀድሞው አያቶላህ ልጃቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ብሩህ ጭንቅላት አለው የሚባል ባለመሆኑ እንዲሁም ለመሪነት ብቁ የሆነ ሰው ተደርጎ ባለመታየቱ ሥልጣኑን እንዳይረከብ ስጋት እንደነበራቸው የአሜሪካ ስለላ ትንተና አመልክቷል ተብሏል።
በተጨማሪም አባት በልጃቸው የግል ሕይወቱ ውስጥ ስላለው ችግር ያውቁ እንደነበር መረጃው እንዳሳየ ምንጮቹ ተናግረዋል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ከሳምንት በፊት ልጃቸው ሥልጣኑን ተረክበዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ በዚህ ሳምንት የሰጡት የመጀመሪያ መግለጫ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ቢነበብም ሥልጣኑን ከተረከቡ ወዲህ እስካሁን አልታዩም።
ሞጅታባ ሳይጎዱ አልቀሩም የሚሉ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አግራቺ ግን ጠቅላይ መሪ “ጥሩ ጤንነት ላይ” እንደሚገኙ እና “ሁኔታውን ሙሉ በሙሉ እየተቆጣጠሩ” መሆኑን በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።
BBC
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ሞተዋል የተባሉት የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ሚስት በሕይወት መኖራቸው ተገለጸ
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ተባባሪ የሆነው ፋርስ ኒውስ ኤጀንሲ፣ የቀድሞው የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ባለቤት ማንሱሬህ ኮጃስቴህ ባገርዛዴህ በሕይወት መኖራቸውን አስታወቀ።
ባለቤታቸው ላይ በደረሰ ጥቃት መገደላቸውን ወይም በኮማ ውስጥ መሆናቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች በስህተት የተሰራጩ መሆናቸውን ኤጀንሲው ገልጿል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ተባባሪ የሆነው ፋርስ ኒውስ ኤጀንሲ፣ የቀድሞው የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ባለቤት ማንሱሬህ ኮጃስቴህ ባገርዛዴህ በሕይወት መኖራቸውን አስታወቀ።
ባለቤታቸው ላይ በደረሰ ጥቃት መገደላቸውን ወይም በኮማ ውስጥ መሆናቸውን የሚገልጹ ዘገባዎች በስህተት የተሰራጩ መሆናቸውን ኤጀንሲው ገልጿል።
3 months ago
የአባታቸውን መንበር ለመረከብ የተቃረቡት ቀጣዩ የኢራን መሪ ማን ናቸው?
#ethiopia | የኢራን መንፈሳዊ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒን ለመተካት በሚደረገው የሥልጣን ሽግግር ሂደት ውስጥ የልጃቸው የሞጅታባ ኻሜኒ ስም በጉልህ እየተነሳ ይገኛል።
በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ መዋቅር ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ሞጅታባ፣ በተለይም አባታቸውን ለመተካት ዋነኛው ዕጩ እንደሆኑ የብዙዎች ግምት ነው።
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በሴፕቴምበር 1969 በሰሜናዊ ምስራቅ ማሽሃድ ከተማ የተወለዱት ሞጅታባ፣ ከአሊ ኻሜኒ ስድስት ልጆች መካከል ሁለተኛው ናቸው።
የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቴህራን በሚገኘው ታዋቂው 'አላቪ' ሃይማኖታዊ ትምህርት ቤት የተከታተሉ ሲሆን፣ ገና በ17 ዓመታቸው በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት በውትድርና ውስጥ ለአጭር ጊዜያት ማገልገላቸው ይነገራል።
ይህ የጦርነት ተሳትፎ ለኢራን አገዛዝ መጠናከርና ለምዕራባውያን ያላቸውን ጠንካራ አቋም ለመቅረጽ ትልቅ ሚና እንደነበረው ይታመናል።
ከጦርነቱ በኋላ በ1999 የሃይማኖት ትምህርታቸውን ለመቀጠል ወደ ሺዓ ሥነ-መለኮት ማዕከል 'ቁም' ያቀኑት ሞጅታባ፣ ምንም እንኳን እስካሁን የሃይማኖት መሪዎች የሚለብሱትን የክብር ልብስ (Turban) ባይለብሱም፣ ከበስተጀርባ በኢራን የደህንነትና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ትልቅ ስልጣን እንዳላቸው ይነገራል። አሁን ላይ የኢራን ቀጣይ መሪ ማን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ የብዙዎች አይን በሞጅታባ ላይ አርፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #bisratfm #ኢራን #ሞጅታባ_ኻሜኒ #አሊ_ኻሜኒ #የፖለቲካ_ዜና #መካከለኛው_ምስራቅ #iran #mojtabakhamenei #news
#ethiopia | የኢራን መንፈሳዊ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒን ለመተካት በሚደረገው የሥልጣን ሽግግር ሂደት ውስጥ የልጃቸው የሞጅታባ ኻሜኒ ስም በጉልህ እየተነሳ ይገኛል።
በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ መዋቅር ውስጥ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳላቸው የሚነገርላቸው ሞጅታባ፣ በተለይም አባታቸውን ለመተካት ዋነኛው ዕጩ እንደሆኑ የብዙዎች ግምት ነው።
እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በሴፕቴምበር 1969 በሰሜናዊ ምስራቅ ማሽሃድ ከተማ የተወለዱት ሞጅታባ፣ ከአሊ ኻሜኒ ስድስት ልጆች መካከል ሁለተኛው ናቸው።
የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቴህራን በሚገኘው ታዋቂው 'አላቪ' ሃይማኖታዊ ትምህርት ቤት የተከታተሉ ሲሆን፣ ገና በ17 ዓመታቸው በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት በውትድርና ውስጥ ለአጭር ጊዜያት ማገልገላቸው ይነገራል።
ይህ የጦርነት ተሳትፎ ለኢራን አገዛዝ መጠናከርና ለምዕራባውያን ያላቸውን ጠንካራ አቋም ለመቅረጽ ትልቅ ሚና እንደነበረው ይታመናል።
ከጦርነቱ በኋላ በ1999 የሃይማኖት ትምህርታቸውን ለመቀጠል ወደ ሺዓ ሥነ-መለኮት ማዕከል 'ቁም' ያቀኑት ሞጅታባ፣ ምንም እንኳን እስካሁን የሃይማኖት መሪዎች የሚለብሱትን የክብር ልብስ (Turban) ባይለብሱም፣ ከበስተጀርባ በኢራን የደህንነትና የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ትልቅ ስልጣን እንዳላቸው ይነገራል። አሁን ላይ የኢራን ቀጣይ መሪ ማን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ የብዙዎች አይን በሞጅታባ ላይ አርፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #bisratfm #ኢራን #ሞጅታባ_ኻሜኒ #አሊ_ኻሜኒ #የፖለቲካ_ዜና #መካከለኛው_ምስራቅ #iran #mojtabakhamenei #news
3 months ago
ኢራን ጠቅላይ መሪዋን ልትሰይም ነው፤ እስራኤል መራጮቹን እና ተመራጩን እያደነች መሆኗን ገለጸች
ቀጣዩን የኢራን ጠቅላይ መሪ ለመሰየም እየመከረ ያለው የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ከፍተኛ የሊቃውንት ጉባዔ ከስምምነት ላይ መድረሱ ተነገረ።
ጉባዔው የመጨረሻውን ውሳኔ ለማሳለፍ የጋራ አቋም ላይ መድረሱ አንድ አባሉ ሲናገሩ፣ እስራኤል ደግሞ መራጮችን እና ተመራጩን ዒላማ ማድረጓን እንደምትቀጥል አስታወቀች።
ሞሐመድ መህዲ ሚርባጌሪ ለኢራን ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት “ጽኑ እና የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል” በማለት አንዳንድ መቋጫ የሚሹ ነገሮች ብቻ መቅረታቸውን አመልክተዋል።
የሊቃውንቱ ጉባዔ ትኩረት ሰጥቶ ያለማቋረጥ የሚጠበቅበትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ነገር ግን "በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንቅፋቶች አሉ። ለዚህም ሥራዎች በጥንቃቄ ተሠርተው በመግባባት ለታሪክ እንዲቀመጡ ይደረጋል” ብለዋል።
አስካሁን ባለው ሂደት "ግልጽ እና አስተማማኝ የጋራ የሃሳብ አንድነት ላይ ተደርሷል” ያሉት የጉባዔው አባል “እንቅፋቶች” ያሏቸው ጉዳዮችም በፍጥነት እንደሚወገዱ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
የኢራን ከፍተኛ ሊቃውንት ቀጣዩን መሪ ለመምረጥ የሚያከናወኑትን ተግባር በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸችው እስራኤል ደግሞ የአያቶላህ አሊ ኻሜኒን የሚተካውን መሪ ማደኗን እንደምትቀጥል አስጠንቅቃለች።
የእስራኤል ጦር በፋርስ ቋንቋ [የኢራን ብሔራዊ ቋንቋ] በኤክስ ላይ ባሰፈረው ጽሑፍ “ለአስርታት ተሰብስቦ የማያውቀው የኢራን የሊቃውንት ጉባዔ፣ በቆም ከተማ ውስጥ በቅርቡ ስብሰባውን ያደርጋል።
"ልንነግራችሁ የምንፈልገው ጠቅላይ መሪውን ለመተካት የሚፈልገውን እና ተተኪውን ለመሰየም የሚጥሩትን ሰዎች በሙሉ እስራኤል ማደኗን ትቀጥላላች።
"ተተኪውን መሪ ለመምረጥ በሚደረገው ስብሰባ የሚሳተፉትን በሙሉ ዒላማ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማንል ልናስጠነቅቃችሁ እንፈልጋለን። ይህ ማስጠንቀቂያ ነው!” በማለት የሚመረጠውን መሪ ብቻ ሳይሆን በምርጫው የሚሳተፉትን ከማጥቃት ወደኋላ እንደማትል እስራኤል አስታውቃለች።
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት በጀመሩ በመጀመሪያው ሰዓት ላይ ነበር የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ኻሜኒ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተገደሉት።
BBC
ቀጣዩን የኢራን ጠቅላይ መሪ ለመሰየም እየመከረ ያለው የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ከፍተኛ የሊቃውንት ጉባዔ ከስምምነት ላይ መድረሱ ተነገረ።
ጉባዔው የመጨረሻውን ውሳኔ ለማሳለፍ የጋራ አቋም ላይ መድረሱ አንድ አባሉ ሲናገሩ፣ እስራኤል ደግሞ መራጮችን እና ተመራጩን ዒላማ ማድረጓን እንደምትቀጥል አስታወቀች።
ሞሐመድ መህዲ ሚርባጌሪ ለኢራን ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት “ጽኑ እና የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል” በማለት አንዳንድ መቋጫ የሚሹ ነገሮች ብቻ መቅረታቸውን አመልክተዋል።
የሊቃውንቱ ጉባዔ ትኩረት ሰጥቶ ያለማቋረጥ የሚጠበቅበትን እያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፤ ነገር ግን "በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንቅፋቶች አሉ። ለዚህም ሥራዎች በጥንቃቄ ተሠርተው በመግባባት ለታሪክ እንዲቀመጡ ይደረጋል” ብለዋል።
አስካሁን ባለው ሂደት "ግልጽ እና አስተማማኝ የጋራ የሃሳብ አንድነት ላይ ተደርሷል” ያሉት የጉባዔው አባል “እንቅፋቶች” ያሏቸው ጉዳዮችም በፍጥነት እንደሚወገዱ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
የኢራን ከፍተኛ ሊቃውንት ቀጣዩን መሪ ለመምረጥ የሚያከናወኑትን ተግባር በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸችው እስራኤል ደግሞ የአያቶላህ አሊ ኻሜኒን የሚተካውን መሪ ማደኗን እንደምትቀጥል አስጠንቅቃለች።
የእስራኤል ጦር በፋርስ ቋንቋ [የኢራን ብሔራዊ ቋንቋ] በኤክስ ላይ ባሰፈረው ጽሑፍ “ለአስርታት ተሰብስቦ የማያውቀው የኢራን የሊቃውንት ጉባዔ፣ በቆም ከተማ ውስጥ በቅርቡ ስብሰባውን ያደርጋል።
"ልንነግራችሁ የምንፈልገው ጠቅላይ መሪውን ለመተካት የሚፈልገውን እና ተተኪውን ለመሰየም የሚጥሩትን ሰዎች በሙሉ እስራኤል ማደኗን ትቀጥላላች።
"ተተኪውን መሪ ለመምረጥ በሚደረገው ስብሰባ የሚሳተፉትን በሙሉ ዒላማ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማንል ልናስጠነቅቃችሁ እንፈልጋለን። ይህ ማስጠንቀቂያ ነው!” በማለት የሚመረጠውን መሪ ብቻ ሳይሆን በምርጫው የሚሳተፉትን ከማጥቃት ወደኋላ እንደማትል እስራኤል አስታውቃለች።
ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት በጀመሩ በመጀመሪያው ሰዓት ላይ ነበር የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ኻሜኒ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት የተገደሉት።
BBC
3 months ago
የኢራን ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን የትራንፕን ''እጅ ስጡ '' ውድቅ አደረጉ
የኢራን ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ሀገራቸው “ያለ አንዳች ቅድመ-ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ” የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የሰጡትን ማሳሰቢያ ውድቅ አደረጉ። ፔዢሽኪያን የዶናልድ ትራምፕን ማሳሰቢያ “ሕልም” ብለውታል።
በቪዲዮ ተቀርጾ በተላለፈ ንግግራቸው “ወደ መቃብራቸው ሊወስዱት ይገባል” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን “ያለ አንዳች ቅድመ-ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ” ያሳሰቡት ትናንት አርብ ነበር።
ለዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሰብአዊነት ማዕቀፍ እና ለመርሆዎቻቸው ኢራን ቁርጠኛ እንደሆነች የገለጹት ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን “ለነዚያ መርሆዎች ቁርጠኛ መሆን አለባቸው። የኢራንን ጨምሮ የማንኛውንም ሀገር መብቶች ችላ ማለት አይችሉም” ሲሉ ተናግረዋል።
እስራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን የገጠሙት ጦርነት ስምንተኛ ቀኑን ሲያስቆጥር ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ሀገራቸው በአጎራባች ሃገራት ላይ ለተፈጸሙ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶች በራሳቸው ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።
የኢራን ወታደራዊ አዛዦች እና የሀገሪቱ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ፕሬዝዳንቱ “አረመኔያዊ” ባሉት ጥቃት በመገደላቸው የሀገሪቱ ጦር “አዛዦቻቸው ባለመኖራቸው ምክንያት በፍላጎታቸው ተኮሱ፤ አስፈላጊ የሆነውን ሁሉ አደረጉ” ሲሉ ተናግረዋል። “በክብር እና በኃይል” ሀገራቸውን እንደተከላከሉም አሞግሰዋል።
ካሁን በኋላ ጎረቤት ሀገራት ጥቃት ካልፈጸሙ በስተቀር የኢራን ጦር ጥቃት እንዳይፈጽም ወይም ሚሳይል እንዳይተኩስ ጊዜያዊ የመሪዎች ምክር ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን ፕሬዝደንቱ ገልጸዋል። “ይህንን በዲፕሎማሲ መፍታት አለብን ብዬ አስባለሁ” ብለዋል። ፕሬዝዳንት ፔዜክሽያን በጥቃቶቹ ሳቢያ እየጨመረ የመጣውን የባሕረ ሰላጤው አረብ ሃገራት ቁጣ ለማርገብ ቢሞክሩም፣ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ግን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃቶች በዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎችን አስተጓጉለዋል።
የኤሜሬትስ አየር መንገድም በረራ መጀመሩን ከገለጸ ከአንድ ቀን በኋላ በድጋሚ በረራዉ መቋረጡን አስታውቋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ ሶሻል በተባለ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ በኩል በጻፉት መልክዕት ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ይቅርታ የጠየቁት በኢራን ላይ “ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በፈጸሙት የማያቋርጥ ጥቃት” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
DW Amharic
የኢራን ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ሀገራቸው “ያለ አንዳች ቅድመ-ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ” የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የሰጡትን ማሳሰቢያ ውድቅ አደረጉ። ፔዢሽኪያን የዶናልድ ትራምፕን ማሳሰቢያ “ሕልም” ብለውታል።
በቪዲዮ ተቀርጾ በተላለፈ ንግግራቸው “ወደ መቃብራቸው ሊወስዱት ይገባል” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን “ያለ አንዳች ቅድመ-ሁኔታ እጅ እንድትሰጥ” ያሳሰቡት ትናንት አርብ ነበር።
ለዓለም አቀፍ ሕግ፣ የሰብአዊነት ማዕቀፍ እና ለመርሆዎቻቸው ኢራን ቁርጠኛ እንደሆነች የገለጹት ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን “ለነዚያ መርሆዎች ቁርጠኛ መሆን አለባቸው። የኢራንን ጨምሮ የማንኛውንም ሀገር መብቶች ችላ ማለት አይችሉም” ሲሉ ተናግረዋል።
እስራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን የገጠሙት ጦርነት ስምንተኛ ቀኑን ሲያስቆጥር ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ሀገራቸው በአጎራባች ሃገራት ላይ ለተፈጸሙ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶች በራሳቸው ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።
የኢራን ወታደራዊ አዛዦች እና የሀገሪቱ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ፕሬዝዳንቱ “አረመኔያዊ” ባሉት ጥቃት በመገደላቸው የሀገሪቱ ጦር “አዛዦቻቸው ባለመኖራቸው ምክንያት በፍላጎታቸው ተኮሱ፤ አስፈላጊ የሆነውን ሁሉ አደረጉ” ሲሉ ተናግረዋል። “በክብር እና በኃይል” ሀገራቸውን እንደተከላከሉም አሞግሰዋል።
ካሁን በኋላ ጎረቤት ሀገራት ጥቃት ካልፈጸሙ በስተቀር የኢራን ጦር ጥቃት እንዳይፈጽም ወይም ሚሳይል እንዳይተኩስ ጊዜያዊ የመሪዎች ምክር ቤት ውሳኔ ማስተላለፉን ፕሬዝደንቱ ገልጸዋል። “ይህንን በዲፕሎማሲ መፍታት አለብን ብዬ አስባለሁ” ብለዋል። ፕሬዝዳንት ፔዜክሽያን በጥቃቶቹ ሳቢያ እየጨመረ የመጣውን የባሕረ ሰላጤው አረብ ሃገራት ቁጣ ለማርገብ ቢሞክሩም፣ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ግን የሚሳኤልና የድሮን ጥቃቶች በዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎችን አስተጓጉለዋል።
የኤሜሬትስ አየር መንገድም በረራ መጀመሩን ከገለጸ ከአንድ ቀን በኋላ በድጋሚ በረራዉ መቋረጡን አስታውቋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ ሶሻል በተባለ ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ በኩል በጻፉት መልክዕት ፕሬዝዳንት መሱድ ፔዤሺኪያን ይቅርታ የጠየቁት በኢራን ላይ “ዩናይትድ ስቴትስ እና እስራኤል በፈጸሙት የማያቋርጥ ጥቃት” ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
DW Amharic
3 months ago
ዶናልድ ትራምፕ የቀጣዩን የኢራን መሪ ምርጫ ላይ "እጃቸው መግባት እንዳለበት" ገለጹ
#fastmereja I የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀጣዩን የኢራን መሪ በመምረጡ ሂደት ላይ በግል መሳተፍ እንደሚፈልጉ በዛሬው ዕለት ለኤክሲዮስ በሰጡት ቃለ ምልልስ አስታወቁ።
ትራምፕ ከኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ህልፈት በኋላ፣ አዲሱን የሀገሪቱን መሪ በመሰየሙ ሂደት ላይ እሳቸው በግላቸው መሳተፍ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጸዋል።
ትራምፕ የሟቹ መሪ ልጅ የሆኑት ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ተተኪ የመሆን ከፍተኛ ዕድል እንዳላቸው ለኤክሲዮስ አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ቦታ ተረክበው መሪ መሆናቸው "ተቀባይነት የሌለው" ውጤት እንደሆነም ትራምፕ በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው አስገንዝበዋል።
ይህ የትራምፕ አስተያየት አሜሪካ በቀጣይ በኢራን የውስጥ ፖለቲካ እና በመሪዎች ሽግግር ላይ ጠንከር ያለ ተጽዕኖ ለማሳደር ያላትን ፍላጎት የሚያሳይ ነው ተብሏል።
#fastmereja I የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቀጣዩን የኢራን መሪ በመምረጡ ሂደት ላይ በግል መሳተፍ እንደሚፈልጉ በዛሬው ዕለት ለኤክሲዮስ በሰጡት ቃለ ምልልስ አስታወቁ።
ትራምፕ ከኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ህልፈት በኋላ፣ አዲሱን የሀገሪቱን መሪ በመሰየሙ ሂደት ላይ እሳቸው በግላቸው መሳተፍ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጸዋል።
ትራምፕ የሟቹ መሪ ልጅ የሆኑት ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ተተኪ የመሆን ከፍተኛ ዕድል እንዳላቸው ለኤክሲዮስ አረጋግጠዋል። ይሁን እንጂ ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ቦታ ተረክበው መሪ መሆናቸው "ተቀባይነት የሌለው" ውጤት እንደሆነም ትራምፕ በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው አስገንዝበዋል።
ይህ የትራምፕ አስተያየት አሜሪካ በቀጣይ በኢራን የውስጥ ፖለቲካ እና በመሪዎች ሽግግር ላይ ጠንከር ያለ ተጽዕኖ ለማሳደር ያላትን ፍላጎት የሚያሳይ ነው ተብሏል።
3 months ago
ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት የሃዘን መግለጫ ሰጡ
#fastmereja I የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በሰማዕትነት ማረፋቸውን ተከትሎ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሃዘናቸውን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በኤምባሲው በተዘጋጀው የሃዘን መግለጫ ስነ-ስርዓት ላይ በመገኘት በመዝገቡ ላይ መልዕክታቸውን አስፍረዋል።
ሼክ ኢብራሂም ቱፋ ለኢራን ህዝብ እና መንግስት ያላቸውን ጥልቅ አጋርነት የገለጹ ሲሆን፣ ድርጊቱን "በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ የተፈጸመ አሰቃቂ ጥቃት" ሲሉ ጠርተውታል።
ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የአሊ ኻሜኒ ማረፍ "ኪሳራው ለኢራናውያን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ላሉ ሙስሊሞች ሁሉ ነው" በማለት የችግሩን ዓለም አቀፋዊነት ገልጸዋል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በሰማዕትነት ማረፋቸውን ተከትሎ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሃዘናቸውን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ በኤምባሲው በተዘጋጀው የሃዘን መግለጫ ስነ-ስርዓት ላይ በመገኘት በመዝገቡ ላይ መልዕክታቸውን አስፍረዋል።
ሼክ ኢብራሂም ቱፋ ለኢራን ህዝብ እና መንግስት ያላቸውን ጥልቅ አጋርነት የገለጹ ሲሆን፣ ድርጊቱን "በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ የተፈጸመ አሰቃቂ ጥቃት" ሲሉ ጠርተውታል።
ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የአሊ ኻሜኒ ማረፍ "ኪሳራው ለኢራናውያን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ላሉ ሙስሊሞች ሁሉ ነው" በማለት የችግሩን ዓለም አቀፋዊነት ገልጸዋል።
3 months ago
ከኻሜኒ ቀብር በኋላ ተተኪያቸው ይታወቃል፣ እስራኤልም አዲሱ መሪን ዒላማ እንደምታደርግ ዝታለች
የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ መከናወን የሚጀምር ሲሆን፣ የሚተካቸውም አዲስ መሪ ግብአተ መሪታቸውን ተከትሎ ይፋ እንደሚደረግ የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ምርጫውን የሚያከናውነው ምክር ቤት ጽህፈት ቤቶች ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ሲዘገብ፤ እስራኤልም ለደኅንነቷ ስጋት ሆኖ የሚቀጥል መሪ ከተመረጠ እርምጃ እንደምትወስድ አስታውቃለች።
የጠቅላይ መሪው የቀብር ሥነ ሥርዓት ሦስት ቀናትን እንደሚወስድ እና ከቀብሩ በኋላ የእስላማዊ ሪፐብሊኩ መሪ የሚሰይሙት መንፈሳዊ እና ፖለቲካዊ ሥልጣን ያላቸው መሪዎች በአካል ተሰብስበው ምርጫውን እንደሚያከናውኑ ፋርስ የተባለው የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ምርጫውን የሚያካሂደው ምክር ቤት አባላት ለአሜሪካ እና እስራኤል እንዳይጋለጡ "አስፈላጊ የሆነው የደኅንነት ጥበቃ እርምጃዎች በከፍተኛ ደረጃ መወሰዱን” ዘገባዎች እየጠቆሙ ነው።
ነገር ግን 'ቆም' በምትባለው ከተማ የሚገኘው የከፍተኛ ባለሥልጣናቱ ጉባዔ አባላት ጽህፈት ቤት ማክሰኞ እንዲሁም ቴህራን ውስጥ ስብሰባ የሚያደርጉበት ቦታ ዛሬ በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥቃት እንደተፈጸመበት ቢቢሲ ፐርሺያ ዘግቧል።
የአያቶላህ ኻሜኒ ቀብር በትክክል የት እንደሚካሄድ እስካሁን ያልተገለጸ ሲሆን፣ የኢራን መገናኛ ብዙኃን ግን ማሻድ በምትባለው ከተማ ውስጥ በሚገኘው ስምንተኛው የሺዓ ኢማም የእምነት ስፍራ ሊሆን እንደሚችል እየዘገቡ ነው።
የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ሦስተኛው ጠቅላይ መሪ ማን እንደሚሆን እየተጠበቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኒው ዮርክ ታይምስ የኢራን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ የሟቹ መሪ ልጅ ሞጅታባ ኻሜኒ አዲሱ መሪ እንዲሆን ከስምምነት ላይ መደረሱን እና ይፋ እንደሚደረግ ዘግቧል።
ፋርስ ዜና ወኪል ከኻሜኒ ቀብር በኋላ የመሪው ማንነት ይፋ እንደሚደረግ እና የሹመት ሥነ ሥርዓቱም በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚሆን ገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ ለአገራቸው ጠላት የሆነ የትኛውም ተተኪ ቢመጣ ዒላማቸው እንደሚሆን ተናግረዋል።
“እስራኤልን የማጥፋት ዕቅድን የሚቀጥል፣ አሜሪካን ላይ የሚዝት፣ የኢራንን ሕዝብ የሚጨቁን የትኛውም ተተኪ በማያጠራጥር ሁኔታ ለመደምሰስ ዒላማችን ይሆናል” ብለዋል የመከላከያ ሚኒስትሩ።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21/2018 ዓ.ም. በኢራን ላይ በከፈቱት ጥቃት የአገሪቱን ጠቅላይ መሪ ጨምሮ በርካታ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ባለሥልጣናት ተገድለዋል።
BBC
የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ መከናወን የሚጀምር ሲሆን፣ የሚተካቸውም አዲስ መሪ ግብአተ መሪታቸውን ተከትሎ ይፋ እንደሚደረግ የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ምርጫውን የሚያከናውነው ምክር ቤት ጽህፈት ቤቶች ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ሲዘገብ፤ እስራኤልም ለደኅንነቷ ስጋት ሆኖ የሚቀጥል መሪ ከተመረጠ እርምጃ እንደምትወስድ አስታውቃለች።
የጠቅላይ መሪው የቀብር ሥነ ሥርዓት ሦስት ቀናትን እንደሚወስድ እና ከቀብሩ በኋላ የእስላማዊ ሪፐብሊኩ መሪ የሚሰይሙት መንፈሳዊ እና ፖለቲካዊ ሥልጣን ያላቸው መሪዎች በአካል ተሰብስበው ምርጫውን እንደሚያከናውኑ ፋርስ የተባለው የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ምርጫውን የሚያካሂደው ምክር ቤት አባላት ለአሜሪካ እና እስራኤል እንዳይጋለጡ "አስፈላጊ የሆነው የደኅንነት ጥበቃ እርምጃዎች በከፍተኛ ደረጃ መወሰዱን” ዘገባዎች እየጠቆሙ ነው።
ነገር ግን 'ቆም' በምትባለው ከተማ የሚገኘው የከፍተኛ ባለሥልጣናቱ ጉባዔ አባላት ጽህፈት ቤት ማክሰኞ እንዲሁም ቴህራን ውስጥ ስብሰባ የሚያደርጉበት ቦታ ዛሬ በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥቃት እንደተፈጸመበት ቢቢሲ ፐርሺያ ዘግቧል።
የአያቶላህ ኻሜኒ ቀብር በትክክል የት እንደሚካሄድ እስካሁን ያልተገለጸ ሲሆን፣ የኢራን መገናኛ ብዙኃን ግን ማሻድ በምትባለው ከተማ ውስጥ በሚገኘው ስምንተኛው የሺዓ ኢማም የእምነት ስፍራ ሊሆን እንደሚችል እየዘገቡ ነው።
የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ሦስተኛው ጠቅላይ መሪ ማን እንደሚሆን እየተጠበቀ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኒው ዮርክ ታይምስ የኢራን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ የሟቹ መሪ ልጅ ሞጅታባ ኻሜኒ አዲሱ መሪ እንዲሆን ከስምምነት ላይ መደረሱን እና ይፋ እንደሚደረግ ዘግቧል።
ፋርስ ዜና ወኪል ከኻሜኒ ቀብር በኋላ የመሪው ማንነት ይፋ እንደሚደረግ እና የሹመት ሥነ ሥርዓቱም በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚሆን ገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር ኢዝራኤል ካትዝ ለአገራቸው ጠላት የሆነ የትኛውም ተተኪ ቢመጣ ዒላማቸው እንደሚሆን ተናግረዋል።
“እስራኤልን የማጥፋት ዕቅድን የሚቀጥል፣ አሜሪካን ላይ የሚዝት፣ የኢራንን ሕዝብ የሚጨቁን የትኛውም ተተኪ በማያጠራጥር ሁኔታ ለመደምሰስ ዒላማችን ይሆናል” ብለዋል የመከላከያ ሚኒስትሩ።
አሜሪካ እና እስራኤል የካቲት 21/2018 ዓ.ም. በኢራን ላይ በከፈቱት ጥቃት የአገሪቱን ጠቅላይ መሪ ጨምሮ በርካታ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ባለሥልጣናት ተገድለዋል።
BBC
3 months ago
የኢራን የቀድሞው የደኅንነት ኃላፊ በክህደት ወንጀል ተጠረጠሩ
#ethiopia | ለረጅም ዓመታት የኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የስለላ መዋቅርን በበላይነት ሲመሩ የቆዩት ሆሴን ታኢብ፣ ከእስራኤል (ሞሳድ) ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ።
ጥርጣሬውን የቀሰቀሰው "የ20 ደቂቃ" ድራማ
ለባለሥልጣኑ መታሰር እንደ ዋነኛ መነሻ የተጠቀሰው፣ በቅርቡ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸማቸው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ የታየው ያልተለመደ ክስተት ነው። ሆሴን ታኢብ ከሀገሪቱ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒ ጋር በስብሰባ ላይ ሳሉ፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ 20 ደቂቃ በፊት "ታምሜአለሁ" በሚል ምክንያት በድንገት አቋርጠው መውጣታቸው ከፍተኛ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ ድርጊታቸው ስለ ጥቃቱ አስቀድመው መረጃ እንደነበራቸውና ራሳቸውን ለማዳን እንዲሁም ለጠላት መረጃ አሳልፎ በመስጠት ሳይተባበሩ እንዳልቀረ ተገምቷል።
የታኢብ ተፅዕኖ እና የክስተቱ ክብደት
ሆሴን ታኢብ በኢራን የደኅንነት መዋቅር ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ሚስጥር አዋቂ ሰው እንደነበሩ ይነገራል። እንደ አይሪሽ ታይምስ እና ኢራን ኢንተርናሽናል ዘገባ ከሆነ፣ የእሳቸው መታሰር በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለውን ያለመተማመን ስሜት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የሞሳድ ሰርጎ ገብነት እስከ የትኛው የሥልጣን እርከን ድረስ እንደዘለቀ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እስራኤል #ሞሳድ #ሆሴንታኢብ #የስለላ_መረጃ #ሰበር_ዜና #iran #intelligence #mossad
#ethiopia | ለረጅም ዓመታት የኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የስለላ መዋቅርን በበላይነት ሲመሩ የቆዩት ሆሴን ታኢብ፣ ከእስራኤል (ሞሳድ) ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ።
ጥርጣሬውን የቀሰቀሰው "የ20 ደቂቃ" ድራማ
ለባለሥልጣኑ መታሰር እንደ ዋነኛ መነሻ የተጠቀሰው፣ በቅርቡ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸማቸው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ የታየው ያልተለመደ ክስተት ነው። ሆሴን ታኢብ ከሀገሪቱ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒ ጋር በስብሰባ ላይ ሳሉ፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ 20 ደቂቃ በፊት "ታምሜአለሁ" በሚል ምክንያት በድንገት አቋርጠው መውጣታቸው ከፍተኛ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ ድርጊታቸው ስለ ጥቃቱ አስቀድመው መረጃ እንደነበራቸውና ራሳቸውን ለማዳን እንዲሁም ለጠላት መረጃ አሳልፎ በመስጠት ሳይተባበሩ እንዳልቀረ ተገምቷል።
የታኢብ ተፅዕኖ እና የክስተቱ ክብደት
ሆሴን ታኢብ በኢራን የደኅንነት መዋቅር ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ሚስጥር አዋቂ ሰው እንደነበሩ ይነገራል። እንደ አይሪሽ ታይምስ እና ኢራን ኢንተርናሽናል ዘገባ ከሆነ፣ የእሳቸው መታሰር በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለውን ያለመተማመን ስሜት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የሞሳድ ሰርጎ ገብነት እስከ የትኛው የሥልጣን እርከን ድረስ እንደዘለቀ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እስራኤል #ሞሳድ #ሆሴንታኢብ #የስለላ_መረጃ #ሰበር_ዜና #iran #intelligence #mossad
Sponsored by
Surafel
3 months ago
‹‹ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች›› የኔታንያሁ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews
3 months ago
በኢራን አደባባዮች የአስር ሺዎች ቁጣ፦ "አንገዛም፣ አንሸነፍም!"
የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢራውያን በቴህራን እና ቁም ከተሞች ዛሬ ለሊት አደባባይ በመውጣት መጠነ ሰፊ የድጋፍ ሰልፍ እያደረጉ ይገኛሉ።
ሰልፈኞቹ "አንገዛም! አንሸነፍም!" በሚሉ መፈክሮች የታጀቡ ሲሆን፣ ለሟቹ መሪ ያላቸውን ጽኑ ታማኝነት እየገለጹ ነው።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ምስሎች ላይ እንደሚታየው፣ ቁጣ የተሞላባቸው ሰልፈኞች "በቀል! በቀል!" እያሉ ሲጮሁ ተደምጠዋል።
የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢራውያን በቴህራን እና ቁም ከተሞች ዛሬ ለሊት አደባባይ በመውጣት መጠነ ሰፊ የድጋፍ ሰልፍ እያደረጉ ይገኛሉ።
ሰልፈኞቹ "አንገዛም! አንሸነፍም!" በሚሉ መፈክሮች የታጀቡ ሲሆን፣ ለሟቹ መሪ ያላቸውን ጽኑ ታማኝነት እየገለጹ ነው።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ምስሎች ላይ እንደሚታየው፣ ቁጣ የተሞላባቸው ሰልፈኞች "በቀል! በቀል!" እያሉ ሲጮሁ ተደምጠዋል።
3 months ago
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከአዲሶቹ የኢራን መሪዎች ጋር ለንግግር ተስማሙ
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አያቶላህ አሊ ኻሜኒን ጨምሮ ከፍተኛ የኢራን አመራሮች ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ ስልጣን ከያዙት አዲሶቹ የሀገሪቱ መሪዎች ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ።
እንደ "አትላንቲክ መጽሄት" ዘገባ ከሆነ፣ ፕሬዝዳንቱ አዲሱ የኢራን አመራር ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ፍላጎት እንዳሳየና እሳቸውም ጥያቄውን መቀበላቸውን በይፋ ገልጸዋል። ትራምፕ በሰጡት አስተያየት የኢራን ወገን ቀደም ብሎ ይህን መሰል እርምጃ መውሰድ እንደነበረበት በመጠቆም ወቅሰዋል።
ቁልፍ ነጥቦች
* የንግግር ዝግጁነት፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "መነጋገር ይፈልጋሉ፤ እኔም ለመነጋገር ተስማምቻለሁ፤ ስለዚህ አነጋግራቸዋለሁ" በማለት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።
* የዘገየ ውሳኔ፦ ኢራን ከዚህ ቀደም ዲፕሎማሲያዊ አማራጮችን መጠቀም እንደነበረባት የገለጹት ትራምፕ፣ "በጣም ተግባራዊና ቀላል የነበረውን ነገር ለማድረግ በጣም ዘግይተዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
* ያልተወሰነ ቀጠሮ፦ ንግግሩ መቼ እና የት እንደሚካሄድ የተጠየቁት ፕሬዝዳንቱ፣ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ይህ አዲስ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎች ትኩረት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን
#getutemesgen #getu #ጌጡ #trump #iran #diplomacy #breakingnews #middleeast #ትራምፕ #ኢራን #ዜና
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አያቶላህ አሊ ኻሜኒን ጨምሮ ከፍተኛ የኢራን አመራሮች ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ ስልጣን ከያዙት አዲሶቹ የሀገሪቱ መሪዎች ጋር ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ።
እንደ "አትላንቲክ መጽሄት" ዘገባ ከሆነ፣ ፕሬዝዳንቱ አዲሱ የኢራን አመራር ከዋሽንግተን ጋር ለመነጋገር ፍላጎት እንዳሳየና እሳቸውም ጥያቄውን መቀበላቸውን በይፋ ገልጸዋል። ትራምፕ በሰጡት አስተያየት የኢራን ወገን ቀደም ብሎ ይህን መሰል እርምጃ መውሰድ እንደነበረበት በመጠቆም ወቅሰዋል።
ቁልፍ ነጥቦች
* የንግግር ዝግጁነት፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "መነጋገር ይፈልጋሉ፤ እኔም ለመነጋገር ተስማምቻለሁ፤ ስለዚህ አነጋግራቸዋለሁ" በማለት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።
* የዘገየ ውሳኔ፦ ኢራን ከዚህ ቀደም ዲፕሎማሲያዊ አማራጮችን መጠቀም እንደነበረባት የገለጹት ትራምፕ፣ "በጣም ተግባራዊና ቀላል የነበረውን ነገር ለማድረግ በጣም ዘግይተዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
* ያልተወሰነ ቀጠሮ፦ ንግግሩ መቼ እና የት እንደሚካሄድ የተጠየቁት ፕሬዝዳንቱ፣ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ይህ አዲስ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የፖለቲካ ውጥረት ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎች ትኩረት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን
#getutemesgen #getu #ጌጡ #trump #iran #diplomacy #breakingnews #middleeast #ትራምፕ #ኢራን #ዜና
3 months ago
አሊ ሬዛ አራፊ በጊዜያዊነት ኢራንን እንዲመሩ ተመረጡ
የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ መገደላቸውን ተከትሎ አሊ ሬዛ አራፊ ሀገሪቱን በጊዜያዊነት እንዲመሩ መመረጣቸውን ኢራን ኢንተርናሽናልና አል ጀዚራ ዘገቡ።
ክስተቱ የተከናወነው በኢራን መዲና ቴህራን ሲሆን፤ ጠቅላይ መሪው አያቶላህ አሊ ኻሜኒ በእስራኤልና አሜሪካ ጥቃት በቢሯቸው ውስጥ መገደላቸውን ተከትሎ ሀገሪቱ የ40 ቀን ብሔራዊ የሐዘን ቀን አውጃለች።
እንደ ዘገባው ከሆነ አዲሱ ተመራጭ አሊ ሬዛ አራፊ ከፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን እና ከፍትሕ ሚኒስትር ጎላም ሆሴይን ሞህሴኒ ኤጄይ ጋር በመሆን የሽግግር አመራር ምክር ቤት አባል ሆነው ተመርጠዋል።
አሊ ሬዛ አራፊ የተገደሉትን ጠቅላይ መሪ ቦታ ተክተው እንደሚሠሩ አል አረቢያ የዘገበ ሲሆን፤ በ1937 በማሽሀድ ተወልደው በ86 ዓመታቸው የተገደሉት አሊ ኻሜኒ መላውን ኢራን ለ35 ዓመታት በበላይነት መምራታቸው ይታወሳል።
አዲሱ የሽግግር አመራር ምክር ቤት ሀገሪቱ ያለችበትን የጦርነት ውጥረትና ቀጣዩን የጠቅላይ መሪ ምርጫ የማመቻቸት ኃላፊነት እንደሚኖርበት ተመላክቷል።
የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ መገደላቸውን ተከትሎ አሊ ሬዛ አራፊ ሀገሪቱን በጊዜያዊነት እንዲመሩ መመረጣቸውን ኢራን ኢንተርናሽናልና አል ጀዚራ ዘገቡ።
ክስተቱ የተከናወነው በኢራን መዲና ቴህራን ሲሆን፤ ጠቅላይ መሪው አያቶላህ አሊ ኻሜኒ በእስራኤልና አሜሪካ ጥቃት በቢሯቸው ውስጥ መገደላቸውን ተከትሎ ሀገሪቱ የ40 ቀን ብሔራዊ የሐዘን ቀን አውጃለች።
እንደ ዘገባው ከሆነ አዲሱ ተመራጭ አሊ ሬዛ አራፊ ከፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን እና ከፍትሕ ሚኒስትር ጎላም ሆሴይን ሞህሴኒ ኤጄይ ጋር በመሆን የሽግግር አመራር ምክር ቤት አባል ሆነው ተመርጠዋል።
አሊ ሬዛ አራፊ የተገደሉትን ጠቅላይ መሪ ቦታ ተክተው እንደሚሠሩ አል አረቢያ የዘገበ ሲሆን፤ በ1937 በማሽሀድ ተወልደው በ86 ዓመታቸው የተገደሉት አሊ ኻሜኒ መላውን ኢራን ለ35 ዓመታት በበላይነት መምራታቸው ይታወሳል።
አዲሱ የሽግግር አመራር ምክር ቤት ሀገሪቱ ያለችበትን የጦርነት ውጥረትና ቀጣዩን የጠቅላይ መሪ ምርጫ የማመቻቸት ኃላፊነት እንደሚኖርበት ተመላክቷል።
3 months ago
"የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ግድያ በሙስሊሞች ላይ የታወጀ የጦርነት አዋጅ ነው" የኢራን ፕሬዝዳንት
#fastmereja I የአሜሪካ እና የእስራኤል ጥቃት የኢራንን ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን መግደሉን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዘሽኪያን ድርጊቱን "በሙስሊሞች ላይ የታወጀ የጦርነት አዋጅ" ሲሉ ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ ባወጡት መግለጫ "የኢስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ ሥልጣን ባለቤት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቁ የሺዓ መሪ መገደል፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሚገኙ ሙስሊሞች በተለይም በሺዓዎች ላይ በግልጽ የታወጀ የጦርነት አዋጅ ተደርጎ ይወሰዳል" ብለዋል።
ኢራን የዚህ "ታሪካዊ ወንጀል" ፈፃሚዎችን እና አቀናባሪዎችን የመበቀል ሕጋዊ ግዴታ እና መብት እንዳላት ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ይህ ግድያ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያሸጋገረ ሲሆን፣ የኢራን መንግስት ጠንካራ ምላሽ ለመስጠት እየተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
#fastmereja I የአሜሪካ እና የእስራኤል ጥቃት የኢራንን ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒን መግደሉን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዘሽኪያን ድርጊቱን "በሙስሊሞች ላይ የታወጀ የጦርነት አዋጅ" ሲሉ ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ ባወጡት መግለጫ "የኢስላማዊት ሪፐብሊክ ኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ ሥልጣን ባለቤት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የታወቁ የሺዓ መሪ መገደል፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሚገኙ ሙስሊሞች በተለይም በሺዓዎች ላይ በግልጽ የታወጀ የጦርነት አዋጅ ተደርጎ ይወሰዳል" ብለዋል።
ኢራን የዚህ "ታሪካዊ ወንጀል" ፈፃሚዎችን እና አቀናባሪዎችን የመበቀል ሕጋዊ ግዴታ እና መብት እንዳላት ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ይህ ግድያ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ውጥረት ወደ ከፍተኛ ደረጃ ያሸጋገረ ሲሆን፣ የኢራን መንግስት ጠንካራ ምላሽ ለመስጠት እየተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
3 months ago
የኢራንን መንፈሳዊ መሪ አሊ ኻሜኒን ለመግደል የሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ ድብቅ ሴራ እንዴት ተሳካ?
ዓለም በሰላም ተኝታ በነበረችበት በዚያ ቅዳሜ ንጋት፣ የኢራን ሰማይ በፈንጂ ድምፅና በብርሃን ነበልባል ተቀደደ። ይህ ተራ ወታደራዊ ግጭት አልነበረም፤ ይልቁንም ለዓመታት ሲታቀድ የቆየ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እና በከፍተኛ የደህንነት መረጃ ብልጫ የተመራ የታሪክ መለወጫ ኩነት ነበር።
የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ እና የእስራኤሉ ሞሳድ የኢራንን መንፈሳዊ መሪ አሊ ኻሜኒን እና የጦር አዛዦቻቸውን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተጠቀሙበት ስልት የደህንነት ተቋማቱን ጥብቅ ምስጢር ፍንትው አድርጎ አሳይቷል።
ጥቃቱ መጀመሪያ የታቀደው ለዓርብ ምሽት ነበር። ሆኖም ግን፣ በመጨረሻው ሰዓት ጥቃቱ ወደ ቅዳሜ ንጋት እንዲሸጋገር ተደረገ። የዚህ ውሳኔ ምክንያት የቴክኒክ ብልሽት ሳይሆን "የወርቅ ዕድል" ተብሎ የሚጠራው የደህንነት መረጃ ነበር።
ሲ.አይ.ኤ ከኢራን አገዛዝ የውስጥ ክበብ ባገኘው መረጃ መሰረት፣ አሊ ኻሜኒ እና የኢራን ከፍተኛ የደህንነት ምክር ቤት አባላት በቴህራን እምብርት በሚገኝ አንድ ህንፃ ውስጥ ለድንገተኛ ስብሰባ እንደሚቀመጡ አረጋገጠ።
ይህንን መረጃ ተከትሎ 200 የሚጠጉ የእስራኤል F-15 እና F-35 የጦር ጄቶች ወደ ኢራን ሰማይ ተመዘገዘጉ።
የአየር መከላከያ ስርአቶችን በመጣስ በቀጥታ የኻሜኒ ቢሮ የሚገኝበትን ህንፃ ኢላማ አደረጉ።
ለወራት ሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ የኻሜኒን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ሲከታተሉ ቆይተዋል። ወታደራዊ ተንታኞች እንደሚሉት፣ እንዲህ ያለውን ጥብቅ ጥበቃ የሚደረግለት መሪ በትክክል ባለበት ቦታ ማግኘት የሚቻለው በሳተላይት ብቻ ሳይሆን "በመሬት ላይ ባለ ምንጭ" ነው።
ይህ ማለት በአያቶላዎች አገዛዝ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን ያላቸው ግለሰቦች መረጃውን ለምዕራባውያን አሳልፈው ሰጥተዋል ማለት ነው። ይህ የተቀናጀ ስራ እንደ ቬንዙዌላው ኒኮላስ ማዱሮ የግዞት ሙከራ ሁሉ፣ በስርአቱ ውስጥ ከፍተኛ መቃቃር እና የደህንነት መላላት መኖሩን ማሳያ ሆኗል።
በጥቃቱ ሳቢያ አሊ ኻሜኒ ብቻ ሳይሆኑ፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ ጀነራል መሐመድ ፓክፑር እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ጀነራል አዚዝ ናሲርዛዴህ መገደላቸው ተረጋግጧል።
በተለይም አድሚራል አሊ ሻምካኒ መገደላቸው ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል፤ ምክንያቱም እርሳቸው ኢራን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በድርድር እንድትመለስ ሲወተውቱ የነበሩ ቁልፍ ሰው ነበሩ።
የአገዛዙ ደጋፊዎች በቴህራን አደባባዮች ቁርአን እየቀሩና እያለቀሱ "በቀል" ሲሉ እየዛቱ ነው።
ደበአንጻሩ አገዛዙ ያሰቃየናል የሚሉ ወጣቶችና ሴቶች በድብቅ ደስታቸውን እየገለጹ ሲሆን፣ የአያቶላዎች ዘመን ማክተሙን እንደ አዲስ ጅማሮ እያዩት ነው።
ሲ.አይ.ኤ ለዋይት ሃውስ ባቀረበው ማስጠንቀቂያ፣ የኻሜኒ ሞት ያስከተለው የፖለቲካ ክፍተት ጉዳዩን ይበልጥ አደገኛ ሊያደርገው እንደሚችል ገልጿል። በስርአቱ ውስጥ የቀሩት ወታደራዊ አዛዦች ስልጣኑን ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ጥረት ቀጠናው ወደ ከፋ ጦርነት ሊገባ ይችላል የሚል ስጋት አለ።
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጥቃቱን "የሰው ልጅ የሞራል እሴቶችን የጣሰ" ሲሉ ቢኮንኑም፣ እንደ የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ ፕሬዝዳንት ያሉ መሪዎች ደግሞ "የአምባገነኖች ዘመን ማብቂያ" ሲሉ ገልጸውታል።
የካቲት 21/2018 ዓ.ም በታሪክ መዝገብ ላይ የሚሰፍረው የቴክኖሎጂ እና የደህንነት መረጃ ጥምረት የታላቅ ሀገርን እጣ ፈንታ በሰዓታት ውስጥ የለወጠበት ቀን ሆኖ ነው።አሜሪካንም እንደ አሸባሪ እና የጎበዝ አለቃ የቆጠሩ ብዙ አሉ።
ኢራን አሁን የቆመችው በማይታወቅ ማዕበል መካከል ነው፤ ቀጣዩ መሪ ማን ይሆናል? ጦርነቱስ ወዴት ያመራል? የሚለው የዓለም ቀዳሚ ጥያቄ ሆኗል።
ዓለም በሰላም ተኝታ በነበረችበት በዚያ ቅዳሜ ንጋት፣ የኢራን ሰማይ በፈንጂ ድምፅና በብርሃን ነበልባል ተቀደደ። ይህ ተራ ወታደራዊ ግጭት አልነበረም፤ ይልቁንም ለዓመታት ሲታቀድ የቆየ፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ እና በከፍተኛ የደህንነት መረጃ ብልጫ የተመራ የታሪክ መለወጫ ኩነት ነበር።
የአሜሪካው ሲ.አይ.ኤ እና የእስራኤሉ ሞሳድ የኢራንን መንፈሳዊ መሪ አሊ ኻሜኒን እና የጦር አዛዦቻቸውን በቁጥጥር ስር ለማዋል የተጠቀሙበት ስልት የደህንነት ተቋማቱን ጥብቅ ምስጢር ፍንትው አድርጎ አሳይቷል።
ጥቃቱ መጀመሪያ የታቀደው ለዓርብ ምሽት ነበር። ሆኖም ግን፣ በመጨረሻው ሰዓት ጥቃቱ ወደ ቅዳሜ ንጋት እንዲሸጋገር ተደረገ። የዚህ ውሳኔ ምክንያት የቴክኒክ ብልሽት ሳይሆን "የወርቅ ዕድል" ተብሎ የሚጠራው የደህንነት መረጃ ነበር።
ሲ.አይ.ኤ ከኢራን አገዛዝ የውስጥ ክበብ ባገኘው መረጃ መሰረት፣ አሊ ኻሜኒ እና የኢራን ከፍተኛ የደህንነት ምክር ቤት አባላት በቴህራን እምብርት በሚገኝ አንድ ህንፃ ውስጥ ለድንገተኛ ስብሰባ እንደሚቀመጡ አረጋገጠ።
ይህንን መረጃ ተከትሎ 200 የሚጠጉ የእስራኤል F-15 እና F-35 የጦር ጄቶች ወደ ኢራን ሰማይ ተመዘገዘጉ።
የአየር መከላከያ ስርአቶችን በመጣስ በቀጥታ የኻሜኒ ቢሮ የሚገኝበትን ህንፃ ኢላማ አደረጉ።
ለወራት ሲ.አይ.ኤ እና ሞሳድ የኻሜኒን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ሲከታተሉ ቆይተዋል። ወታደራዊ ተንታኞች እንደሚሉት፣ እንዲህ ያለውን ጥብቅ ጥበቃ የሚደረግለት መሪ በትክክል ባለበት ቦታ ማግኘት የሚቻለው በሳተላይት ብቻ ሳይሆን "በመሬት ላይ ባለ ምንጭ" ነው።
ይህ ማለት በአያቶላዎች አገዛዝ ውስጥ ከፍተኛ ስልጣን ያላቸው ግለሰቦች መረጃውን ለምዕራባውያን አሳልፈው ሰጥተዋል ማለት ነው። ይህ የተቀናጀ ስራ እንደ ቬንዙዌላው ኒኮላስ ማዱሮ የግዞት ሙከራ ሁሉ፣ በስርአቱ ውስጥ ከፍተኛ መቃቃር እና የደህንነት መላላት መኖሩን ማሳያ ሆኗል።
በጥቃቱ ሳቢያ አሊ ኻሜኒ ብቻ ሳይሆኑ፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ አዛዥ ጀነራል መሐመድ ፓክፑር እና የመከላከያ ሚኒስትሩ ጀነራል አዚዝ ናሲርዛዴህ መገደላቸው ተረጋግጧል።
በተለይም አድሚራል አሊ ሻምካኒ መገደላቸው ከፍተኛ ድንጋጤ ፈጥሯል፤ ምክንያቱም እርሳቸው ኢራን ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በድርድር እንድትመለስ ሲወተውቱ የነበሩ ቁልፍ ሰው ነበሩ።
የአገዛዙ ደጋፊዎች በቴህራን አደባባዮች ቁርአን እየቀሩና እያለቀሱ "በቀል" ሲሉ እየዛቱ ነው።
ደበአንጻሩ አገዛዙ ያሰቃየናል የሚሉ ወጣቶችና ሴቶች በድብቅ ደስታቸውን እየገለጹ ሲሆን፣ የአያቶላዎች ዘመን ማክተሙን እንደ አዲስ ጅማሮ እያዩት ነው።
ሲ.አይ.ኤ ለዋይት ሃውስ ባቀረበው ማስጠንቀቂያ፣ የኻሜኒ ሞት ያስከተለው የፖለቲካ ክፍተት ጉዳዩን ይበልጥ አደገኛ ሊያደርገው እንደሚችል ገልጿል። በስርአቱ ውስጥ የቀሩት ወታደራዊ አዛዦች ስልጣኑን ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ጥረት ቀጠናው ወደ ከፋ ጦርነት ሊገባ ይችላል የሚል ስጋት አለ።
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጥቃቱን "የሰው ልጅ የሞራል እሴቶችን የጣሰ" ሲሉ ቢኮንኑም፣ እንደ የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ ፕሬዝዳንት ያሉ መሪዎች ደግሞ "የአምባገነኖች ዘመን ማብቂያ" ሲሉ ገልጸውታል።
የካቲት 21/2018 ዓ.ም በታሪክ መዝገብ ላይ የሚሰፍረው የቴክኖሎጂ እና የደህንነት መረጃ ጥምረት የታላቅ ሀገርን እጣ ፈንታ በሰዓታት ውስጥ የለወጠበት ቀን ሆኖ ነው።አሜሪካንም እንደ አሸባሪ እና የጎበዝ አለቃ የቆጠሩ ብዙ አሉ።
ኢራን አሁን የቆመችው በማይታወቅ ማዕበል መካከል ነው፤ ቀጣዩ መሪ ማን ይሆናል? ጦርነቱስ ወዴት ያመራል? የሚለው የዓለም ቀዳሚ ጥያቄ ሆኗል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ሰሜን ኮሪያ በኢራን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት "ሕገ-ወጥ ወረራ" ስትል አወገዘች
ሰሜን ኮሪያ እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ የሰነዘሩት ጥቃት የሀገርን ሉዓላዊነት የጣሰ "ሕገ-ወጥ ወረራ" ነው ስትል መኮነኗን የሀገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን (KCNA) ዘግቧል።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ የሀገሪቱን "ወሮበላ" ባሕርይ የሚያሳይና የሚጠበቅ ነበር ብለዋል።
በእስራኤልና አሜሪካ የተከፈተው "የወረራ ጦርነት" በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት የለውም። የኢራን ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ ጥቃቱ በመካከለኛው ምስራቅ ከፍተኛ አለመረጋጋት ይፈጥራል የሚል ስጋት ነግሷል። የክልሉ ሀገራት በመካከለኛው ምስራቅ ሰላምና መረጋጋትን ለመመለስ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
ሰሜን ኮሪያ እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ የሰነዘሩት ጥቃት የሀገርን ሉዓላዊነት የጣሰ "ሕገ-ወጥ ወረራ" ነው ስትል መኮነኗን የሀገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን (KCNA) ዘግቧል።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ፣ የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ የሀገሪቱን "ወሮበላ" ባሕርይ የሚያሳይና የሚጠበቅ ነበር ብለዋል።
በእስራኤልና አሜሪካ የተከፈተው "የወረራ ጦርነት" በማንኛውም ሁኔታ ተቀባይነት የለውም። የኢራን ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ ጥቃቱ በመካከለኛው ምስራቅ ከፍተኛ አለመረጋጋት ይፈጥራል የሚል ስጋት ነግሷል። የክልሉ ሀገራት በመካከለኛው ምስራቅ ሰላምና መረጋጋትን ለመመለስ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
3 months ago
ሰበር ዜና፡ የኢራን መንፈሳዊ መሪ ህልፈትን ተከትሎ አዲስ ጊዜያዊ መሪ ተሰየሙ
የኢራን የዜና ወኪል (ISNA) እንደዘገበው፤ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ከዚህ ዓለም በሞት መለያየታቸውን ተከትሎ፣
ታዋቂው የህግ ባለሙያና የአስተዳደር ምክር ቤት አባል አያቶላ አሊሬዛ አራፊ የመሪነቱን ተግባራት በጊዜያዊነት እንዲመሩ ተመድበዋል።
የአያቶላ አሊ ኻሜኒን ሞት ተከትሎ በሀገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ የአመራር ክፍተት ለመሙላት የአስተዳደር ምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጓል።
በኢራን ሕገ-መንግሥት መሠረት፣ አዲስ ቋሚ መሪ በኤክስፐርቶች ጉባኤ (Assembly of Experts) እስኪመረጥ ድረስ፣ አያቶላ አራፊ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ተግባራትን በበላይነት የመምራት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
ይህ ድንገተኛ ሹመት በሀገሪቱ የጸጥታና የፖለቲካ መረጋጋት እንዲሰፍንና የመንግሥት ተቋማት ሥራቸውን ያለ መቆራረጥ እንዲቀጥሉ ለማድረግ የታለመ ነው።
ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ፣ ይህ የሽግግር አመራር ለቀጣዩ የኢራን የፖለቲካ አቅጣጫ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተነግሯል።
Via ISNA
seledadotio
seledadotio
የኢራን የዜና ወኪል (ISNA) እንደዘገበው፤ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ከዚህ ዓለም በሞት መለያየታቸውን ተከትሎ፣
ታዋቂው የህግ ባለሙያና የአስተዳደር ምክር ቤት አባል አያቶላ አሊሬዛ አራፊ የመሪነቱን ተግባራት በጊዜያዊነት እንዲመሩ ተመድበዋል።
የአያቶላ አሊ ኻሜኒን ሞት ተከትሎ በሀገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ የአመራር ክፍተት ለመሙላት የአስተዳደር ምክር ቤቱ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጓል።
በኢራን ሕገ-መንግሥት መሠረት፣ አዲስ ቋሚ መሪ በኤክስፐርቶች ጉባኤ (Assembly of Experts) እስኪመረጥ ድረስ፣ አያቶላ አራፊ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ተግባራትን በበላይነት የመምራት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
ይህ ድንገተኛ ሹመት በሀገሪቱ የጸጥታና የፖለቲካ መረጋጋት እንዲሰፍንና የመንግሥት ተቋማት ሥራቸውን ያለ መቆራረጥ እንዲቀጥሉ ለማድረግ የታለመ ነው።
ሀገሪቱ አሁን ባለችበት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ፣ ይህ የሽግግር አመራር ለቀጣዩ የኢራን የፖለቲካ አቅጣጫ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተነግሯል።
Via ISNA
seledadotio
seledadotio
3 months ago
የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ ከአሜሪካ እና እስራኤል በተሰነዘረ ጥቃት ከቤተሰቦቻቸው እና ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር መገደላቸውን ባለሥልጣናት ማረጋገጣቸዉ ይታወቃል
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ ከበላይ መሪዉ በተጨማሪ፣ በዚሁ ጥቃት የአያቶላ አሊኻሜኒ ልጅ፣ አማች፣ የልጅ ልጅ እና ምራታቸውም ተገድለዋል።
በእስራኤል እና አሜሪካ ጥቃት የሞቱት የኢራን ባለስልጣናት ቁጥር ቢያንስ 40 እንደሚደርስም ተገልጿል።
ከተገደሉት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ከፍተኛ አማካሪ እና የኒውክሌር ተደራዳሪ የሆኑት አሊ ሻምካኒ እንዲሁም የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል መሀመድ ፓክፑር እንደሚገኙበት ተዘግቧል።
ከአያቶላህ አሊ ጋር ስብሰባ ላይ የነበሩ 10 ከፍተኛ ባለልጣናት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል ተብሏል።
በጥቃቱ ህይወታቸው ማለፉ የተረጋገጠው አመራሮች የሚከተሉት ናቸው፦
አዚዝ ናሲርዛዴህ፦ የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር።
ሌተናል ጄኔራል አብዱልራሂም ሞሳቪ፦ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ።
ሜጀር ጄኔራል መሀመድ ፓክፑር፦ የኢሊት እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) መሪ።
አሊ ሻምካኒ፦ የመከላከያ ም/ቤት ፀሐፊ።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ምሽት በሰጡት መግለጫ "አብዛኛው የኢራን ከፍተኛ አመራር አልቋል" ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል ዛሬ ያወጣው መረጃ የትራምፕን ንግግር የሚያጠናክር ሆኗል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ ከበላይ መሪዉ በተጨማሪ፣ በዚሁ ጥቃት የአያቶላ አሊኻሜኒ ልጅ፣ አማች፣ የልጅ ልጅ እና ምራታቸውም ተገድለዋል።
በእስራኤል እና አሜሪካ ጥቃት የሞቱት የኢራን ባለስልጣናት ቁጥር ቢያንስ 40 እንደሚደርስም ተገልጿል።
ከተገደሉት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ከፍተኛ አማካሪ እና የኒውክሌር ተደራዳሪ የሆኑት አሊ ሻምካኒ እንዲሁም የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል ምድር ጦር አዛዥ ጄኔራል መሀመድ ፓክፑር እንደሚገኙበት ተዘግቧል።
ከአያቶላህ አሊ ጋር ስብሰባ ላይ የነበሩ 10 ከፍተኛ ባለልጣናት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል ተብሏል።
በጥቃቱ ህይወታቸው ማለፉ የተረጋገጠው አመራሮች የሚከተሉት ናቸው፦
አዚዝ ናሲርዛዴህ፦ የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር።
ሌተናል ጄኔራል አብዱልራሂም ሞሳቪ፦ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ።
ሜጀር ጄኔራል መሀመድ ፓክፑር፦ የኢሊት እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) መሪ።
አሊ ሻምካኒ፦ የመከላከያ ም/ቤት ፀሐፊ።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትላንት ምሽት በሰጡት መግለጫ "አብዛኛው የኢራን ከፍተኛ አመራር አልቋል" ማለታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል ዛሬ ያወጣው መረጃ የትራምፕን ንግግር የሚያጠናክር ሆኗል።
3 months ago
የዙፋን ንቅናቄ፡ የኻሜኒ ሞት እና የኢራን እርግጠኛ ያልሆነ መጻኢ እድል
በአለም አቀፍ ሚዲያ እንዳየነው የካቲት ወር ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የድንጋጤ እና የታሪክ መታጠፊያ ሆኖ ተመዝግቧል።
ለ37 ዓመታት አገሪቱን በብረት እጅ የመሩት የ86 ዓመቱ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ በቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሳሉ በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥምር የአየር ጥቃት መገደላቸው ተሰምቷል።
ይህ ዜና በኢራን አደባባዮች ላይ የለቅሶ እና የደስታ ድምጾችን በአንድ ላይ ያስተጋባ ቢሆንም፣ ከሁሉ በላይ ግን "ቀጥሎ ምን ይፈጠራል?" የሚለው ጥያቄ ዓለምን እያስጨነቀ ይገኛል።
ከ1979 አብዮት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የታየው ይህ ከፍተኛ የሥልጣን ሽግግር፣ በጦርነት ደመና ስር የወደቀችውን ኢራን ወደ አዲስ እና ያልተገመተ ምዕራፍ እየመራት ነው።
እ.ኤ.አ በ1989 የአብዮቱ መሪ አያቶላ ሩሆላ ኾሜኒ ሲሞቱ፣ አሊ ኻሜኒ ተተኪ ይሆናሉ ብሎ የገመተ ብዙም አልነበረም። በወቅቱ የነበረው የኢራን ሕገ-መንግሥት መሪው ከፍተኛ የሃይማኖት ደረጃ (ማርጃ) እንዲኖረው ቢደነግግም፣ ኻሜኒ ያ ደረጃ አልነበራቸውም። ሆኖም ግን፣ ኾሜኒ ከመሞታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ ሕገ-መንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረጋቸው፣ "ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ብቃት" ያለው ሃይማኖታዊ ሊቅ እንዲመረጥ መንገድ ተከፈተ።
ባለፉት 37 ዓመታት ኻሜኒ ስልጣናቸውን አደላደሉ። በጦር ኃይሉ፣ በፍትህ ሥርዓቱ እና በመገናኛ ብዙኃን ላይ ፍጹም ቁጥጥር አደረጉ። ፕሬዝዳንቶች ቢመጡና ቢሄዱም፣ ኻሜኒ ግን የአገሪቱ ስትራቴጂካዊ ኮምፓስ ሆነው ቀጠሉ።
የ"መቋቋም ኢኮኖሚ" ፖሊሲን በመከተል ከምዕራባውያን ጋር የነበራቸውን ጥርጣሬ አጠናክረዋል፤ በተለይም በ2009፣ 2022 እና በቅርቡ በ2025-26 የተቀሰቀሱ ሕዝባዊ አመጾችን በኃይል በመጨፍለቅ ስልጣናቸውን ጠብቀዋል።
በዚህ ሂደት ውስጥም የአብዮታዊ ዘብ ጦር (IRGC) የአገሪቱ ዋነኛ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ አከርካሪ እንዲሆን አድርገዋል።
እንደ ሕገ-መንግሥቱ ከሆነ፣ የ88 የሃይማኖት ሊቃውንት ስብስብ የሆነው "የሊቃውንት ጉባኤ" በአስቸኳይ አዲስ መሪ የመምረጥ ኃላፊነት አለበት። እስከዚያው ድረስ ግን አገሪቱ በሦስት ወገን ኮሚቴ—በፕሬዝዳንቱ፣ በፍትህ ሚኒስትሩ እና በአንድ የጥበቃ ምክር ቤት አባል—ትመራለች።
ነገር ግን ጥያቄው ያለው ተቋማዊ አሠራሩ ላይ ሳይሆን፣ በጦርነት እና በውስጥ ውጥረት ውስጥ ባለች አገር ውስጥ የትኛው ቡድን የበላይነቱን ይይዛል የሚለው ላይ ነው።
መጻኢ እድሎች፡ ሦስቱ የኢራን መንገዶች
ኢራን ከሚከተሉት ሦስት አቅጣጫዎች በአንዱ ልትጓዝ ትችላለች ተብሎ ይገመታል፡-
1. "ኻሜኒዝም ያለ ኻሜኒ" (የሥርዓቱ ቀጣይነት)
ይህ በጣም ቅርብ የሆነው ግምት ነው። የሊቃውንት ጉባኤው ከአብዮታዊ ዘብ ጦር ጋር ስምምነት ያለው፣ የሥርዓቱን መሠረት የማይንድ መሪ ሊሰይም ይችላል። ሆኖም አዲሱ መሪ የኻሜኒን ዓይነት የ37 ዓመት የተገነባ የጥቅም መረብና ተሰሚነት ስለማይኖረው፣ በቡድኖች መካከል ያለው ፍጥጫ ሊባባስ ይችላል።
2. የወታደራዊ አገዛዝ ሽግግር
አገሪቱ በውጭ ኃይሎች ጥቃት ስር መሆኗን ተገን በማድረግ፣ የአብዮታዊ ዘብ ጦር (IRGC) በግልጽም ሆነ በስውር ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ ሊቆጣጠር ይችላል። በዚህ ጊዜ ፖለቲካው ወደ "ደህንነት" ብቻ ያዘነብላል፤ የተቃውሞ ድምጾች በከፋ ሁኔታ ይታፈናሉ፣ እንዲሁም ከዓለም ጋር ያለው ግንኙነት ይበልጥ ይሻክራል።
3. ከፍተኛ መበታተን እና ውዝግብ
በሃይማኖታዊ ሊቃውንት እና በወታደራዊው ክፍል መካከል ስምምነት ካልተደረሰ፣ ወይም የሕዝብ ቁጣ ከኢኮኖሚ ውድቀት ጋር ተዳምሮ ገንፍሎ ከወጣ፣ ሥርዓቱ ሊንገዳገድ ይችላል። ምንም እንኳን እስላማዊ ሪፐብሊኩ ከዚህ ቀደም መሰል ቀውሶችን ቢወጣም፣ የአሁኑ ጥቃት እና የመሪው ድንገተኛ ሞት ግን ሥርዓቱን ወደ ማይመለስበት ገደል ውስጥ ሊከተው ይችላል።
የተበታተነው ተቃውሞ እና ያልተመለሰው ጥያቄ
የኻሜኒን መሞት ተከትሎ በውጭ አገራት ያሉ ኢራናውያን ደስታቸውን በቪዲዮዎች ቢገልጹም፣ ሥርዓቱን ለመተካት የሚያስችል የተቀናጀ ኃይል አለመኖሩ ትልቁ ፈተና ነው።
የንጉሣዊው ሥርዓት ደጋፊዎች፡ በሬዛ ፓህላቪ ዙሪያ ቢሰባሰቡም፣ በኢራን ውስጥ ያላቸው ተቀባይነት አጠራጣሪ ነው።
ዴሞክራሲያዊ ተሟጋቾች፡ ምንም እንኳን በሐሳብ ደረጃ ቢበዙም፣ የተባበረ አመራር የላቸውም።
ብሔርተኛ ቡድኖች (እንደ ኩርዶች)፡ የራሳቸውን የራስ-ገዝ አስተዳደር ከማስጠበቅ ባለፈ ለአገራዊ አመራር ያላቸው ሚና ውስን ነው።
ይህ የአመራር ክፍተት ሥርዓቱ ቢወድቅ እንኳ አገሪቱን ወደ ሰላማዊ ዴሞክራሲ ሳይሆን ወደለየለት የእርስ በርስ ትርምስ ሊመራት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ሞት የአንድ ግለሰብ ማለፍ ብቻ ሳይሆን፣ ኢራን ላለፉት አራት አስርት ዓመታት የገነባችው የፖለቲካ ሕንጻ መናድ ነው። ኢራን አሁን የምትገኘው በማይታወቅ ውቅያኖስ ላይ ነው። አገሪቱ ወደ አዲስ የነጻነት ምዕራፍ ትሻገራለች ወይንስ ይበልጥ ወደ ጠነከረ አምባገነንነትና ወታደራዊ አገዛዝ ትገባለች?
መልሱ የሚገኘው በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በቴህራን በሚደረጉት የኃይል ሽኩቻዎች ላይ ይሆናል።
በአለም አቀፍ ሚዲያ እንዳየነው የካቲት ወር ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የድንጋጤ እና የታሪክ መታጠፊያ ሆኖ ተመዝግቧል።
ለ37 ዓመታት አገሪቱን በብረት እጅ የመሩት የ86 ዓመቱ አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ በቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሳሉ በእስራኤል እና በአሜሪካ ጥምር የአየር ጥቃት መገደላቸው ተሰምቷል።
ይህ ዜና በኢራን አደባባዮች ላይ የለቅሶ እና የደስታ ድምጾችን በአንድ ላይ ያስተጋባ ቢሆንም፣ ከሁሉ በላይ ግን "ቀጥሎ ምን ይፈጠራል?" የሚለው ጥያቄ ዓለምን እያስጨነቀ ይገኛል።
ከ1979 አብዮት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ የታየው ይህ ከፍተኛ የሥልጣን ሽግግር፣ በጦርነት ደመና ስር የወደቀችውን ኢራን ወደ አዲስ እና ያልተገመተ ምዕራፍ እየመራት ነው።
እ.ኤ.አ በ1989 የአብዮቱ መሪ አያቶላ ሩሆላ ኾሜኒ ሲሞቱ፣ አሊ ኻሜኒ ተተኪ ይሆናሉ ብሎ የገመተ ብዙም አልነበረም። በወቅቱ የነበረው የኢራን ሕገ-መንግሥት መሪው ከፍተኛ የሃይማኖት ደረጃ (ማርጃ) እንዲኖረው ቢደነግግም፣ ኻሜኒ ያ ደረጃ አልነበራቸውም። ሆኖም ግን፣ ኾሜኒ ከመሞታቸው ጥቂት ቀደም ብሎ ሕገ-መንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረጋቸው፣ "ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ብቃት" ያለው ሃይማኖታዊ ሊቅ እንዲመረጥ መንገድ ተከፈተ።
ባለፉት 37 ዓመታት ኻሜኒ ስልጣናቸውን አደላደሉ። በጦር ኃይሉ፣ በፍትህ ሥርዓቱ እና በመገናኛ ብዙኃን ላይ ፍጹም ቁጥጥር አደረጉ። ፕሬዝዳንቶች ቢመጡና ቢሄዱም፣ ኻሜኒ ግን የአገሪቱ ስትራቴጂካዊ ኮምፓስ ሆነው ቀጠሉ።
የ"መቋቋም ኢኮኖሚ" ፖሊሲን በመከተል ከምዕራባውያን ጋር የነበራቸውን ጥርጣሬ አጠናክረዋል፤ በተለይም በ2009፣ 2022 እና በቅርቡ በ2025-26 የተቀሰቀሱ ሕዝባዊ አመጾችን በኃይል በመጨፍለቅ ስልጣናቸውን ጠብቀዋል።
በዚህ ሂደት ውስጥም የአብዮታዊ ዘብ ጦር (IRGC) የአገሪቱ ዋነኛ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ አከርካሪ እንዲሆን አድርገዋል።
እንደ ሕገ-መንግሥቱ ከሆነ፣ የ88 የሃይማኖት ሊቃውንት ስብስብ የሆነው "የሊቃውንት ጉባኤ" በአስቸኳይ አዲስ መሪ የመምረጥ ኃላፊነት አለበት። እስከዚያው ድረስ ግን አገሪቱ በሦስት ወገን ኮሚቴ—በፕሬዝዳንቱ፣ በፍትህ ሚኒስትሩ እና በአንድ የጥበቃ ምክር ቤት አባል—ትመራለች።
ነገር ግን ጥያቄው ያለው ተቋማዊ አሠራሩ ላይ ሳይሆን፣ በጦርነት እና በውስጥ ውጥረት ውስጥ ባለች አገር ውስጥ የትኛው ቡድን የበላይነቱን ይይዛል የሚለው ላይ ነው።
መጻኢ እድሎች፡ ሦስቱ የኢራን መንገዶች
ኢራን ከሚከተሉት ሦስት አቅጣጫዎች በአንዱ ልትጓዝ ትችላለች ተብሎ ይገመታል፡-
1. "ኻሜኒዝም ያለ ኻሜኒ" (የሥርዓቱ ቀጣይነት)
ይህ በጣም ቅርብ የሆነው ግምት ነው። የሊቃውንት ጉባኤው ከአብዮታዊ ዘብ ጦር ጋር ስምምነት ያለው፣ የሥርዓቱን መሠረት የማይንድ መሪ ሊሰይም ይችላል። ሆኖም አዲሱ መሪ የኻሜኒን ዓይነት የ37 ዓመት የተገነባ የጥቅም መረብና ተሰሚነት ስለማይኖረው፣ በቡድኖች መካከል ያለው ፍጥጫ ሊባባስ ይችላል።
2. የወታደራዊ አገዛዝ ሽግግር
አገሪቱ በውጭ ኃይሎች ጥቃት ስር መሆኗን ተገን በማድረግ፣ የአብዮታዊ ዘብ ጦር (IRGC) በግልጽም ሆነ በስውር ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ ሊቆጣጠር ይችላል። በዚህ ጊዜ ፖለቲካው ወደ "ደህንነት" ብቻ ያዘነብላል፤ የተቃውሞ ድምጾች በከፋ ሁኔታ ይታፈናሉ፣ እንዲሁም ከዓለም ጋር ያለው ግንኙነት ይበልጥ ይሻክራል።
3. ከፍተኛ መበታተን እና ውዝግብ
በሃይማኖታዊ ሊቃውንት እና በወታደራዊው ክፍል መካከል ስምምነት ካልተደረሰ፣ ወይም የሕዝብ ቁጣ ከኢኮኖሚ ውድቀት ጋር ተዳምሮ ገንፍሎ ከወጣ፣ ሥርዓቱ ሊንገዳገድ ይችላል። ምንም እንኳን እስላማዊ ሪፐብሊኩ ከዚህ ቀደም መሰል ቀውሶችን ቢወጣም፣ የአሁኑ ጥቃት እና የመሪው ድንገተኛ ሞት ግን ሥርዓቱን ወደ ማይመለስበት ገደል ውስጥ ሊከተው ይችላል።
የተበታተነው ተቃውሞ እና ያልተመለሰው ጥያቄ
የኻሜኒን መሞት ተከትሎ በውጭ አገራት ያሉ ኢራናውያን ደስታቸውን በቪዲዮዎች ቢገልጹም፣ ሥርዓቱን ለመተካት የሚያስችል የተቀናጀ ኃይል አለመኖሩ ትልቁ ፈተና ነው።
የንጉሣዊው ሥርዓት ደጋፊዎች፡ በሬዛ ፓህላቪ ዙሪያ ቢሰባሰቡም፣ በኢራን ውስጥ ያላቸው ተቀባይነት አጠራጣሪ ነው።
ዴሞክራሲያዊ ተሟጋቾች፡ ምንም እንኳን በሐሳብ ደረጃ ቢበዙም፣ የተባበረ አመራር የላቸውም።
ብሔርተኛ ቡድኖች (እንደ ኩርዶች)፡ የራሳቸውን የራስ-ገዝ አስተዳደር ከማስጠበቅ ባለፈ ለአገራዊ አመራር ያላቸው ሚና ውስን ነው።
ይህ የአመራር ክፍተት ሥርዓቱ ቢወድቅ እንኳ አገሪቱን ወደ ሰላማዊ ዴሞክራሲ ሳይሆን ወደለየለት የእርስ በርስ ትርምስ ሊመራት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ሞት የአንድ ግለሰብ ማለፍ ብቻ ሳይሆን፣ ኢራን ላለፉት አራት አስርት ዓመታት የገነባችው የፖለቲካ ሕንጻ መናድ ነው። ኢራን አሁን የምትገኘው በማይታወቅ ውቅያኖስ ላይ ነው። አገሪቱ ወደ አዲስ የነጻነት ምዕራፍ ትሻገራለች ወይንስ ይበልጥ ወደ ጠነከረ አምባገነንነትና ወታደራዊ አገዛዝ ትገባለች?
መልሱ የሚገኘው በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በቴህራን በሚደረጉት የኃይል ሽኩቻዎች ላይ ይሆናል።
3 months ago
የአያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደል ዜና ያነበበው ባለሙያ እያለቀሰ ዜናውን ሲያነብ ታይቷል
የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን፣ የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ዜና አቅራቢ በዕንባ ታጅቦ ዛሬ ጠዋት ያረጋገጠበት ቅጽበት ይህ ነው።
የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን፣ የኢራን መንግሥት ቴሌቪዥን ጣቢያ ዜና አቅራቢ በዕንባ ታጅቦ ዛሬ ጠዋት ያረጋገጠበት ቅጽበት ይህ ነው።
3 months ago
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ
#ethiopia | የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን የኢራን መንግሥት አረጋግጦ 40 የሐዘን ቀናት አወጀ። መሪው እስራኤል እና አሜሪካ ቅዳሜ ዕለት ቴህራን ውስጥ በፈጸሙት ጥቃት መገደላቸውን የአገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አረጋገጡ።
በኢራን ፖለቲካ እና መንፈሳዊ ህይወት ውስጥ ለ37 ዓመታት የመጨረሻውን ቃል ሲናገሩ የቆዩት አያቶላህ ዓሊ ኻሚኒ፣ ዛሬ በታሪክ መዝገብ ውስጥ የሚቀመጥ ትልቅ አሻራ ጥለው አልፈዋል።
"አያ" ማለት ምልክት ወይም አንቀፅ ማለት ሲሆን "አያቶላህ" ማለት ደግሞ "የአላህ ምልክት" ማለት ነው። ይህ ማዕረግ በሺዓ ሙስሊሞች ዘንድ እጅግ የላቀ እውቀትና ስነ-ምግባር ላላቸው መንፈሳዊ መሪዎች የሚሰጥ የክብር ስም ነው።
በወጣትነታቸው የሻህ መሀመድ ሬዛን አገዛዝ በመቃወማቸው ከ6 ጊዜ በላይ ታስረዋል።
በ1979ኙ አብዮት ወቅት በተደረገባቸው የግድያ ሙከራ ቀኝ እጃቸው ጉዳት ደርሶበት እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ ድረስ በግራ እጃቸው ብቻ እንዲጠቀሙ ሆኗል።
መጀመሪያ ፕሬዝዳንት፣ በኋላም ከ1989 ጀምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ በመሆን ኢራንን በኒውክሊየር እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ አዘምነዋል።
አያቶላህ ኻሚኒ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሶሪያ፣ የመን፣ ፍልስጤም እና ሩሲያ ጎን በመቆም ጠንካራ የክልላዊ ኃይል ቢገነቡም፣ በሀገር ውስጥ ግን በሰብዓዊ መብት ጥሰት እና በሃሳብ ነፃነት መገደብ በተደጋጋሚ ይተቹ ነበር። ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች መሪውን ተችተዋል በሚል ለእስር መዳረጋቸው የአገዛዛቸው ጥቁር ጥላ ተደርጎ ይነሳል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ (Ayatollah Ali Khamenei) የዘመናዊቷ ኢራን ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪና የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ (Supreme Leader) ናቸው።
አሊ ኻሜኒ ሚያዝያ 19 ቀን 1939 (እ.ኤ.አ) በኢራን የተቀደሰች ከተማ በምትባለው ማሽሃድ ተወለዱ። ቤተሰቦቻቸው እጅግ ሃይማኖተኛና ድሆች ነበሩ።
ገና በለጋ ዕድሜያቸው የሃይማኖት ትምህርት የጀመሩ ሲሆን፣ በቁም (Qom) ከተማ ታዋቂ በሆኑ የሺዓ መሪዎች ዘንድ ተምረዋል።
ከአያቶላህ ኾሜኒ ጋር ያላቸው ግንኙነት፦
የኢራን አብዮት መሪ ከነበሩት አያቶላህ ሩሖላህ ኾሜኒ ጋር የቅርብ ግንኙነት ነበራቸው። በወቅቱ የነበረውን የሻህ መንግሥት በመቃወማቸው በተደጋጋሚ ታስረዋል፣ ተሰደዋል እንዲሁም ተደብድበዋል።
የ1979 አብዮት፦ አብዮቱ ሲፈነዳና የሻህ መንግሥት ሲወድቅ፣ ኻሜኒ የአብዮቱ ምክር ቤት አባል በመሆን ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
* ፕሬዝዳንትነት (1981-1989)፦ በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። በዚህ ወቅት በደረሰባቸው የግድያ ሙከራ ቀኝ እጃቸው ላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ከፍተኛ መሪነት (1989 - አሁን)፦
አያቶላህ ኾሜኒ በ1989 ሲሞቱ፣ አሊ ኻሜኒ የኢራን "ከፍተኛ መሪ" (Supreme Leader) ሆነው ተሾሙ። በኢራን ሕገ-መንግሥት መሠረት ከፍተኛው ስልጣን በእሳቸው እጅ ነው።
የኻሜኒ ርዕዮተ-ዓለምና አቋም
ፀረ-ምዕራባውያን አሜሪካን "ታላቁ ሰይጣን" በማለት ይተቻሉ፤ የምዕራባውያን ባህልና ፖለቲካ በኢራን ላይ ተፅዕኖ እንዳይኖረው በጥብቅ ይከላከላሉ።
ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ (ሊባኖስ፣ ሶሪያ፣ የመንና ኢራቅ) ያላትን ተፅዕኖ ለማስፋት ትልቅ ስራ ሰርተዋል። እንደ ሄዝቦላህ ያሉ ቡድኖች ዋነኛ ደጋፊ ናቸው።
የኢራን የኒውክሊየር ፕሮግራም ለሰላማዊ ዓላማ ነው ቢሉም፣ ከምዕራባውያን ጋር ላለው ፍጥጫ ዋነኛ ምክንያት የእሳቸው ጽኑ አቋም ነው።
አሁን ላይ ዕድሜያቸው የገፋ (86 ዓመት ገደማ) በመሆናቸው፣ ስለ ጤንነታቸውና ስለ ተተኪዎቻቸው ብዙ ግምቶች ይነገራሉ። ሆኖም አሁንም ድረስ የኢራን የጦር ኃይሎች፣ የፍትሕ ሥርዓትና የመንግሥት መዋቅር የመጨረሻ ትዕዛዝ የሚቀበለው ከእሳቸው ነው።
የአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ተተኪ ማን ሊሆን ይችላል?
አሊ ኻሜኒ ዕድሜያቸው እየገፋ በመምጣቱ (86 ዓመት)፣ በኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ተተኪን የመሰየም ጉዳይ እጅግ ሚስጥራዊና አሳሳቢ ሆኗል። ተተኪውን የሚመርጠው "Assembly of Experts" የተሰኘው 88 የሃይማኖት ምሁራን ስብስብ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ስሞች በዋነኝነት ይነሳሉ፦
ሞጅታባ ኻሜኒ (Mojtaba Khamenei)፦
የአሊ ኻሜኒ ሁለተኛ ልጅ ናቸው። ምንም እንኳን በይፋ ባይገለጽም፣ ከጀርባ ከፍተኛ ተፅዕኖ እንዳላቸውና የሪቮሉሽነሪ ጋርዱን ድጋፍ እንደሚያገኙ ይታመናል። ይሁን እንጂ ስልጣኑ "ቤተሰባዊ" እንዳይመስል ስጋት አለ።
* አሊሬዛ አራፊ (Alireza Arafi)፦ ታዋቂ የሃይማኖት ምሁርና የ"Assembly of Experts" አባል ናቸው። በሃይማኖታዊ መዋቅሩ ውስጥ ተቀባይነት ያላቸው በመሆኑ እንደ ገለልተኛ ተተኪ ሊታዩ ይችላሉ።
መሀመድ ባገር ቃሊባፍ (Mohammad Bagher Ghalibaf)፦
የፓርላማው አፈ ጉባኤና የቀድሞ የጦር አዛዥ ናቸው። የሪቮሉሽነሪ ጋርድ አመራሮች ይበልጥ "ወታደራዊና ተግባራዊ" መሪ ከፈለጉ የእሳቸው ስም ሊነሳ ይችላል።
የኢራን ሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) ምንድነው?
ይህ ድርጅት በኢራን ውስጥ ከወትሮው ጦር ሰራዊት (Army) ጎን ለጎን የሚንቀሳቀስ ነገር ግን እጅግ ኃያል የሆነ የጦር ኃይል ነው።
ዋነኛ አላማው የኢስላማዊ አብዮቱን መርሆዎች መጠበቅና የመንግስቱን ህልውና ማረጋገጥ ነው።
የቁድስ ኃይል (Quds Force) የሪቮሉሽነሪ ጋርድ ክፍል ከሀገር ውጭ ያሉ ምስጢራዊ ስራዎችንና እንደ ሄዝቦላህ፣ ሀማስ እና ሁቲ ያሉ ቡድኖችን የማሰልጠንና የማስታጠቅ ኃላፊነት አለበት።
ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ፦ ሪቮሉሽነሪ ጋርዱ የጦር ኃይል ብቻ አይደለም፤ በኢራን ውስጥ ግዙፍ የግንባታ፣ የነዳጅ እና የኮሙኒኬሽን ኩባንያዎችን ይቆጣጠራል። ይህም በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ የማይናወጥ አቅም ሰጥቶታል።
አሁን ባለው የኢራንና እስራኤል ጦርነት ውስጥ ሪቮሉሽነሪ ጋርዱ ዋነኛ ተዋናይ ነው። እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ስትሰነዝር ኢላማ የምታደርገው የዚህን ኃይል የጦር ሰፈሮችና የሚሳኤል ማከማቻዎችን ነው።
የእስራኤል ጥቃት ኢላማዎች ምን ነበሩ?
የእስራኤል አየር ኃይል በኢራን ላይ የሰነዘረው ጥቃት በሦስት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነበር፡-
* የአየር መከላከያ ሥርዓቶች (S-300)፦
ኢራን ከሩሲያ ያገኘቻቸውን እና ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመጠበቅ የተተከሉ የአየር መከላከያ ራዳሮችን እና የሚሳኤል ባትሪዎችን እስራኤል መጀመሪያ ኢላማ አድርጋለች። ይህን ያደረገችው የኢራንን ሰማይ ለቀጣይ ጥቃቶች ክፍት ለማድረግ ነው።
* የሚሳኤል ማምረቻ ተቋማት፦
በቴህራን አቅራቢያ የሚገኙ እና ለባሊስቲክ ሚሳኤሎች ጠንካራ ነዳጅ (Solid Fuel) የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ተመተዋል። ይህም ኢራን ሚሳኤሎችን በፍጥነት የመተካት አቅሟን ለወራት ወይም ለዓመታት እንደሚያዳክምባት ይገመታል።
* የሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) የጦር ሰፈሮች፦
በኢራቅ እና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኙ የሎጅስቲክስ ማዕከላት ጥቃት ደርሶባቸዋል።
የኢራን ሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) የሰጠው ምላሽ
ጥቃቱን ተከትሎ ከኢራን ከፍተኛ አመራሮች የተሰጡት ምላሾች መጀመሪያ ላይ የጥቃቱን መጠን "ዝቅ አድርጎ የመመልከት" (Downplaying) ዝንባሌ ቢታይባቸውም፣ በኋላ ግን ማስጠንቀቂያዎች እየጠነከሩ መጥተዋል፦
* አያቶላህ አሊ ኻሜኒ፦
"ጥቃቱ ሊጋነንም ሆነ ዝቅ ተደርጎ ሊታይ አይገባም" በማለት፣ ኢራን ብሄራዊ ክብሯን ለመጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ እንደምትወስድ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ገልጸዋል።
ጄነራል ሆሴን ሳላሚ (የIRGC ዋና አዛዥ)፦
እስራኤል ለፈጸመችው "ስህተት" አስደንጋጭ እና የማይታሰብ ዋጋ እንደምትከፍል ዝተዋል። የሪቮሉሽነሪ ጋርድ አመራሮች "True Promise III" (እውነተኛ ቃል ኪዳን 3) በሚል መጠሪያ ሦስተኛ ዙር የሚሳኤል ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የኃይል ሚዛን (The Red Line)
ይህ ጥቃት በመካከለኛው ምስራቅ ለብዙ ዓመታት የነበረውን "በተኪ መዋጋት" (Proxy War) ደንብ ሰብሮታል። አሁን ሁለቱ ሀገራት በቀጥታ አንዱ በሌላው ምድር ላይ ጥቃት መፈጸም የጀመሩበት አዲስ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን።
የእስራኤል መልዕክት፦ "ኢራን ውስጥ የትኛውንም ቦታ መድረስ እንችላለን፤ የኒውክሊየር እና የነዳጅ ማዕከላትን ደግሞ ለቀጣይ ጥቃት አስቀምጠናል" የሚል ነው።
የኢራን ስጋት፦ ተጨማሪ ጥቃት መሰንዘር እስራኤልን ወደ ኒውክሊየር ተቋማት ጥቃት እንድትሸጋገር ሊገፋፋት ይችላል የሚል ስጋት በቴህራን አለ።
#አያቶላህኻሚኒ #ኢራን #መካከለኛውምስራቅ #ታሪክ #መንፈሳዊመሪ #አብዮት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #alikhamenei #iran #middleeasthistory
#ethiopia | የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን የኢራን መንግሥት አረጋግጦ 40 የሐዘን ቀናት አወጀ። መሪው እስራኤል እና አሜሪካ ቅዳሜ ዕለት ቴህራን ውስጥ በፈጸሙት ጥቃት መገደላቸውን የአገሪቱ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን አረጋገጡ።
በኢራን ፖለቲካ እና መንፈሳዊ ህይወት ውስጥ ለ37 ዓመታት የመጨረሻውን ቃል ሲናገሩ የቆዩት አያቶላህ ዓሊ ኻሚኒ፣ ዛሬ በታሪክ መዝገብ ውስጥ የሚቀመጥ ትልቅ አሻራ ጥለው አልፈዋል።
"አያ" ማለት ምልክት ወይም አንቀፅ ማለት ሲሆን "አያቶላህ" ማለት ደግሞ "የአላህ ምልክት" ማለት ነው። ይህ ማዕረግ በሺዓ ሙስሊሞች ዘንድ እጅግ የላቀ እውቀትና ስነ-ምግባር ላላቸው መንፈሳዊ መሪዎች የሚሰጥ የክብር ስም ነው።
በወጣትነታቸው የሻህ መሀመድ ሬዛን አገዛዝ በመቃወማቸው ከ6 ጊዜ በላይ ታስረዋል።
በ1979ኙ አብዮት ወቅት በተደረገባቸው የግድያ ሙከራ ቀኝ እጃቸው ጉዳት ደርሶበት እስከ ህይወታቸው ፍፃሜ ድረስ በግራ እጃቸው ብቻ እንዲጠቀሙ ሆኗል።
መጀመሪያ ፕሬዝዳንት፣ በኋላም ከ1989 ጀምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ በመሆን ኢራንን በኒውክሊየር እና በኢንዱስትሪ ዘርፍ አዘምነዋል።
አያቶላህ ኻሚኒ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሶሪያ፣ የመን፣ ፍልስጤም እና ሩሲያ ጎን በመቆም ጠንካራ የክልላዊ ኃይል ቢገነቡም፣ በሀገር ውስጥ ግን በሰብዓዊ መብት ጥሰት እና በሃሳብ ነፃነት መገደብ በተደጋጋሚ ይተቹ ነበር። ጋዜጠኞችና ፀሐፊዎች መሪውን ተችተዋል በሚል ለእስር መዳረጋቸው የአገዛዛቸው ጥቁር ጥላ ተደርጎ ይነሳል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ (Ayatollah Ali Khamenei) የዘመናዊቷ ኢራን ተፅዕኖ ፈጣሪ መሪና የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ (Supreme Leader) ናቸው።
አሊ ኻሜኒ ሚያዝያ 19 ቀን 1939 (እ.ኤ.አ) በኢራን የተቀደሰች ከተማ በምትባለው ማሽሃድ ተወለዱ። ቤተሰቦቻቸው እጅግ ሃይማኖተኛና ድሆች ነበሩ።
ገና በለጋ ዕድሜያቸው የሃይማኖት ትምህርት የጀመሩ ሲሆን፣ በቁም (Qom) ከተማ ታዋቂ በሆኑ የሺዓ መሪዎች ዘንድ ተምረዋል።
ከአያቶላህ ኾሜኒ ጋር ያላቸው ግንኙነት፦
የኢራን አብዮት መሪ ከነበሩት አያቶላህ ሩሖላህ ኾሜኒ ጋር የቅርብ ግንኙነት ነበራቸው። በወቅቱ የነበረውን የሻህ መንግሥት በመቃወማቸው በተደጋጋሚ ታስረዋል፣ ተሰደዋል እንዲሁም ተደብድበዋል።
የ1979 አብዮት፦ አብዮቱ ሲፈነዳና የሻህ መንግሥት ሲወድቅ፣ ኻሜኒ የአብዮቱ ምክር ቤት አባል በመሆን ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
* ፕሬዝዳንትነት (1981-1989)፦ በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል። በዚህ ወቅት በደረሰባቸው የግድያ ሙከራ ቀኝ እጃቸው ላይ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ከፍተኛ መሪነት (1989 - አሁን)፦
አያቶላህ ኾሜኒ በ1989 ሲሞቱ፣ አሊ ኻሜኒ የኢራን "ከፍተኛ መሪ" (Supreme Leader) ሆነው ተሾሙ። በኢራን ሕገ-መንግሥት መሠረት ከፍተኛው ስልጣን በእሳቸው እጅ ነው።
የኻሜኒ ርዕዮተ-ዓለምና አቋም
ፀረ-ምዕራባውያን አሜሪካን "ታላቁ ሰይጣን" በማለት ይተቻሉ፤ የምዕራባውያን ባህልና ፖለቲካ በኢራን ላይ ተፅዕኖ እንዳይኖረው በጥብቅ ይከላከላሉ።
ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ (ሊባኖስ፣ ሶሪያ፣ የመንና ኢራቅ) ያላትን ተፅዕኖ ለማስፋት ትልቅ ስራ ሰርተዋል። እንደ ሄዝቦላህ ያሉ ቡድኖች ዋነኛ ደጋፊ ናቸው።
የኢራን የኒውክሊየር ፕሮግራም ለሰላማዊ ዓላማ ነው ቢሉም፣ ከምዕራባውያን ጋር ላለው ፍጥጫ ዋነኛ ምክንያት የእሳቸው ጽኑ አቋም ነው።
አሁን ላይ ዕድሜያቸው የገፋ (86 ዓመት ገደማ) በመሆናቸው፣ ስለ ጤንነታቸውና ስለ ተተኪዎቻቸው ብዙ ግምቶች ይነገራሉ። ሆኖም አሁንም ድረስ የኢራን የጦር ኃይሎች፣ የፍትሕ ሥርዓትና የመንግሥት መዋቅር የመጨረሻ ትዕዛዝ የሚቀበለው ከእሳቸው ነው።
የአያቶላህ አሊ ኻሜኒ ተተኪ ማን ሊሆን ይችላል?
አሊ ኻሜኒ ዕድሜያቸው እየገፋ በመምጣቱ (86 ዓመት)፣ በኢራን ከፍተኛ የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ተተኪን የመሰየም ጉዳይ እጅግ ሚስጥራዊና አሳሳቢ ሆኗል። ተተኪውን የሚመርጠው "Assembly of Experts" የተሰኘው 88 የሃይማኖት ምሁራን ስብስብ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ስሞች በዋነኝነት ይነሳሉ፦
ሞጅታባ ኻሜኒ (Mojtaba Khamenei)፦
የአሊ ኻሜኒ ሁለተኛ ልጅ ናቸው። ምንም እንኳን በይፋ ባይገለጽም፣ ከጀርባ ከፍተኛ ተፅዕኖ እንዳላቸውና የሪቮሉሽነሪ ጋርዱን ድጋፍ እንደሚያገኙ ይታመናል። ይሁን እንጂ ስልጣኑ "ቤተሰባዊ" እንዳይመስል ስጋት አለ።
* አሊሬዛ አራፊ (Alireza Arafi)፦ ታዋቂ የሃይማኖት ምሁርና የ"Assembly of Experts" አባል ናቸው። በሃይማኖታዊ መዋቅሩ ውስጥ ተቀባይነት ያላቸው በመሆኑ እንደ ገለልተኛ ተተኪ ሊታዩ ይችላሉ።
መሀመድ ባገር ቃሊባፍ (Mohammad Bagher Ghalibaf)፦
የፓርላማው አፈ ጉባኤና የቀድሞ የጦር አዛዥ ናቸው። የሪቮሉሽነሪ ጋርድ አመራሮች ይበልጥ "ወታደራዊና ተግባራዊ" መሪ ከፈለጉ የእሳቸው ስም ሊነሳ ይችላል።
የኢራን ሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) ምንድነው?
ይህ ድርጅት በኢራን ውስጥ ከወትሮው ጦር ሰራዊት (Army) ጎን ለጎን የሚንቀሳቀስ ነገር ግን እጅግ ኃያል የሆነ የጦር ኃይል ነው።
ዋነኛ አላማው የኢስላማዊ አብዮቱን መርሆዎች መጠበቅና የመንግስቱን ህልውና ማረጋገጥ ነው።
የቁድስ ኃይል (Quds Force) የሪቮሉሽነሪ ጋርድ ክፍል ከሀገር ውጭ ያሉ ምስጢራዊ ስራዎችንና እንደ ሄዝቦላህ፣ ሀማስ እና ሁቲ ያሉ ቡድኖችን የማሰልጠንና የማስታጠቅ ኃላፊነት አለበት።
ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ፦ ሪቮሉሽነሪ ጋርዱ የጦር ኃይል ብቻ አይደለም፤ በኢራን ውስጥ ግዙፍ የግንባታ፣ የነዳጅ እና የኮሙኒኬሽን ኩባንያዎችን ይቆጣጠራል። ይህም በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ የማይናወጥ አቅም ሰጥቶታል።
አሁን ባለው የኢራንና እስራኤል ጦርነት ውስጥ ሪቮሉሽነሪ ጋርዱ ዋነኛ ተዋናይ ነው። እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ስትሰነዝር ኢላማ የምታደርገው የዚህን ኃይል የጦር ሰፈሮችና የሚሳኤል ማከማቻዎችን ነው።
የእስራኤል ጥቃት ኢላማዎች ምን ነበሩ?
የእስራኤል አየር ኃይል በኢራን ላይ የሰነዘረው ጥቃት በሦስት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነበር፡-
* የአየር መከላከያ ሥርዓቶች (S-300)፦
ኢራን ከሩሲያ ያገኘቻቸውን እና ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ለመጠበቅ የተተከሉ የአየር መከላከያ ራዳሮችን እና የሚሳኤል ባትሪዎችን እስራኤል መጀመሪያ ኢላማ አድርጋለች። ይህን ያደረገችው የኢራንን ሰማይ ለቀጣይ ጥቃቶች ክፍት ለማድረግ ነው።
* የሚሳኤል ማምረቻ ተቋማት፦
በቴህራን አቅራቢያ የሚገኙ እና ለባሊስቲክ ሚሳኤሎች ጠንካራ ነዳጅ (Solid Fuel) የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ተመተዋል። ይህም ኢራን ሚሳኤሎችን በፍጥነት የመተካት አቅሟን ለወራት ወይም ለዓመታት እንደሚያዳክምባት ይገመታል።
* የሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) የጦር ሰፈሮች፦
በኢራቅ እና በሶሪያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኙ የሎጅስቲክስ ማዕከላት ጥቃት ደርሶባቸዋል።
የኢራን ሪቮሉሽነሪ ጋርድ (IRGC) የሰጠው ምላሽ
ጥቃቱን ተከትሎ ከኢራን ከፍተኛ አመራሮች የተሰጡት ምላሾች መጀመሪያ ላይ የጥቃቱን መጠን "ዝቅ አድርጎ የመመልከት" (Downplaying) ዝንባሌ ቢታይባቸውም፣ በኋላ ግን ማስጠንቀቂያዎች እየጠነከሩ መጥተዋል፦
* አያቶላህ አሊ ኻሜኒ፦
"ጥቃቱ ሊጋነንም ሆነ ዝቅ ተደርጎ ሊታይ አይገባም" በማለት፣ ኢራን ብሄራዊ ክብሯን ለመጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ እንደምትወስድ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ገልጸዋል።
ጄነራል ሆሴን ሳላሚ (የIRGC ዋና አዛዥ)፦
እስራኤል ለፈጸመችው "ስህተት" አስደንጋጭ እና የማይታሰብ ዋጋ እንደምትከፍል ዝተዋል። የሪቮሉሽነሪ ጋርድ አመራሮች "True Promise III" (እውነተኛ ቃል ኪዳን 3) በሚል መጠሪያ ሦስተኛ ዙር የሚሳኤል ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
አዲሱ የኃይል ሚዛን (The Red Line)
ይህ ጥቃት በመካከለኛው ምስራቅ ለብዙ ዓመታት የነበረውን "በተኪ መዋጋት" (Proxy War) ደንብ ሰብሮታል። አሁን ሁለቱ ሀገራት በቀጥታ አንዱ በሌላው ምድር ላይ ጥቃት መፈጸም የጀመሩበት አዲስ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን።
የእስራኤል መልዕክት፦ "ኢራን ውስጥ የትኛውንም ቦታ መድረስ እንችላለን፤ የኒውክሊየር እና የነዳጅ ማዕከላትን ደግሞ ለቀጣይ ጥቃት አስቀምጠናል" የሚል ነው።
የኢራን ስጋት፦ ተጨማሪ ጥቃት መሰንዘር እስራኤልን ወደ ኒውክሊየር ተቋማት ጥቃት እንድትሸጋገር ሊገፋፋት ይችላል የሚል ስጋት በቴህራን አለ።
#አያቶላህኻሚኒ #ኢራን #መካከለኛውምስራቅ #ታሪክ #መንፈሳዊመሪ #አብዮት #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #alikhamenei #iran #middleeasthistory
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢራን የመሪዋን አያቶላ አሊ ኻሜኒን ሞት አረጋገጠች
የኔታ ሚዲያ
የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ የሀገሪቱ ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል ጥምር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አስታወቀ።
ዜናውን ያበሰረው ጋዜጠኛ ጥልቅ በሆነ ሐዘን እና በእንባ ታጅቦ በፋርሲ ቋንቋ ያነበበው ይፋዊ መግለጫ የሚከተለውን ይላል፦
"ያለ እረፍት እና ድካም ለዘለቀው የሁሴኒ ተጋድሎ ሕይወት በኋላ እንደ እስላማዊ ጥበቃ ጽኑ ተራራ በሆነው ታላቅ እና ሰማያዊ መንፈስ፤ የርኅራኄ እና የቁርጠኝነት አባት፣ የሙስሊሞች መሪ እና ኢማም፣ ክቡር አያቶላ ሰይድ አሊ ሁሴኒ ኻሜኒ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክን ቅዱስ መቅደስ ክብር የማስጠበቅ ጉዞ ላይ ሳሉ ጣፋጩን የሰማዕትነት ጽዋ በመጎንጨት ወደ ልዑል ሰማያዊው መንግሥት ተቀላቅለዋል።"
እንደ ዘገባው ከሆነ መሪው ለህልፈት የተዳረጉት በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል የተሰነዘሩ ጥቃቶችን ተከትሎ ነው።
በቴህራን እና በሌሎች ዋና ዋና ከተሞች ከፍተኛ የሐዘን ድባብ እየታየ ነው
የኔታ ሚዲያ
የኢራን መንግሥታዊ ሚዲያ የሀገሪቱ ከፍተኛ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል ጥምር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አስታወቀ።
ዜናውን ያበሰረው ጋዜጠኛ ጥልቅ በሆነ ሐዘን እና በእንባ ታጅቦ በፋርሲ ቋንቋ ያነበበው ይፋዊ መግለጫ የሚከተለውን ይላል፦
"ያለ እረፍት እና ድካም ለዘለቀው የሁሴኒ ተጋድሎ ሕይወት በኋላ እንደ እስላማዊ ጥበቃ ጽኑ ተራራ በሆነው ታላቅ እና ሰማያዊ መንፈስ፤ የርኅራኄ እና የቁርጠኝነት አባት፣ የሙስሊሞች መሪ እና ኢማም፣ ክቡር አያቶላ ሰይድ አሊ ሁሴኒ ኻሜኒ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክን ቅዱስ መቅደስ ክብር የማስጠበቅ ጉዞ ላይ ሳሉ ጣፋጩን የሰማዕትነት ጽዋ በመጎንጨት ወደ ልዑል ሰማያዊው መንግሥት ተቀላቅለዋል።"
እንደ ዘገባው ከሆነ መሪው ለህልፈት የተዳረጉት በዩናይትድ ስቴትስ እና በእስራኤል የተሰነዘሩ ጥቃቶችን ተከትሎ ነው።
በቴህራን እና በሌሎች ዋና ዋና ከተሞች ከፍተኛ የሐዘን ድባብ እየታየ ነው
3 months ago
❗️ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአያቶላ አሊ ኻሜኒን መገደል አስታወቁ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን በይፋ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያ ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ "በታሪክ ውስጥ እጅግ ክፉ ከሆኑ ሰዎች አንዱ የነበረው ኻሜኒ ሞቷል" ሲሉ ገልጸዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሜሪካ እና እስራኤል በጋራ ባደረጉት የተቀናጀ ጥቃት መሆኑን የገለጹት ትራምፕ፣ የቴክኖሎጂ የበላይነታቸውን በመጠቀም መሪውን መከታተል እንደቻሉ አብራርተዋል።
"ከእስራኤል ጋር በቅርበት በመስራት፣ እሱም ሆነ አብረውት የነበሩ ሌሎች መሪዎች ምንም ሊያደርጉ አልቻሉም" ሲሉ አክለዋል።
ይህ እርምጃ በኢራን እና በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣይ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢራን እስካሁን በመሪዋ ሞት ዙሪያ የሰጠችው ይፋዊ ምላሽ የለም።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን በይፋ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ በትሩዝ ሶሻል ሚዲያ ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ "በታሪክ ውስጥ እጅግ ክፉ ከሆኑ ሰዎች አንዱ የነበረው ኻሜኒ ሞቷል" ሲሉ ገልጸዋል።
ግድያው የተፈጸመው አሜሪካ እና እስራኤል በጋራ ባደረጉት የተቀናጀ ጥቃት መሆኑን የገለጹት ትራምፕ፣ የቴክኖሎጂ የበላይነታቸውን በመጠቀም መሪውን መከታተል እንደቻሉ አብራርተዋል።
"ከእስራኤል ጋር በቅርበት በመስራት፣ እሱም ሆነ አብረውት የነበሩ ሌሎች መሪዎች ምንም ሊያደርጉ አልቻሉም" ሲሉ አክለዋል።
ይህ እርምጃ በኢራን እና በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣይ ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ኢራን እስካሁን በመሪዋ ሞት ዙሪያ የሰጠችው ይፋዊ ምላሽ የለም።
3 months ago
እስራኤል የመከላከያ ሚኒስትሩን ጨምሮ 7 ከፍተኛ የኢራን የደህንነት እና የወታደራዊ መሪዎች መገደላቸውን ይፋ አደረገች
ጥቃቱ የተፈጸመው፦ ከፍተኛ አመራሮቹ ስብሰባ ላይ በነበሩባቸው ሁለት የቴህራን ቦታዎች ላይ ነው።
የታለሙት ግለሰቦች፦ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በኑክሌር ፕሮግራም እና በድሮን ጥቃቶች ላይ ቁልፍ ሚና ያላቸው ናቸው።
📌 የተገደሉ የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣናት ዝርዝር፦
አዚዝ ናሲርዛዴህ፦ የኢራን መከላከያ ሚኒስትር። የሚሳኤል ልማት እና የጦር መሳሪያ አቅርቦት መሪ።
አሊ ሻምካኒ፦ የመንፈሳዊ መሪው አሊ ኻሜኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የቀድሞ የባህር ሃይል አዛዥ።
መሀመድ ፓክፑር፦ በእስራኤል ላይ የሚሰነዘሩ የሮኬት እና የድሮን ጥቃቶችን የሚመሩ የአብዮታዊ ዘብ አዛዥ።
መሐመድ ሽራዚ፦ የአሊ ኻሜኒ ወታደራዊ ቢሮ ሃላፊ (በመንፈሳዊ መሪው እና በአዛዦች መካከል ያለው ቁልፍ ድልድይ)።
ሳላህ አሳዲ፦ የወታደራዊ አስቸኳይ ጊዜ ዋና መስሪያ ቤት የደህንነት ሃላፊ።
ሁሴን ጃባል-አሜሊያን፦ የላቁ የጦር መሳሪያዎች ምርምር ድርጅት (SPND) ፕሬዝዳንት።
ሬዛ ሞዛፋሪ-ኒያ፦ የቀድሞው የSPND ሃላፊ እና የኑክሌር ፕሮግራም ቁልፍ ሰው።
ቀደም ብሎ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አይቶላ አሊ ኻሜኒ ስለመገደላቸው በሮይተርስ እና ፎክስ ኒውስ ዘገባዎች ቢወጡም፣ እስራኤል እስካሁን በይፋ ያረጋገጠችው የእነዚህን 7 ባለስልጣናት መገደል ብቻ ነው።
ጥቃቱ የተፈጸመው፦ ከፍተኛ አመራሮቹ ስብሰባ ላይ በነበሩባቸው ሁለት የቴህራን ቦታዎች ላይ ነው።
የታለሙት ግለሰቦች፦ በስትራቴጂክ እቅድ፣ በኑክሌር ፕሮግራም እና በድሮን ጥቃቶች ላይ ቁልፍ ሚና ያላቸው ናቸው።
📌 የተገደሉ የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣናት ዝርዝር፦
አዚዝ ናሲርዛዴህ፦ የኢራን መከላከያ ሚኒስትር። የሚሳኤል ልማት እና የጦር መሳሪያ አቅርቦት መሪ።
አሊ ሻምካኒ፦ የመንፈሳዊ መሪው አሊ ኻሜኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የቀድሞ የባህር ሃይል አዛዥ።
መሀመድ ፓክፑር፦ በእስራኤል ላይ የሚሰነዘሩ የሮኬት እና የድሮን ጥቃቶችን የሚመሩ የአብዮታዊ ዘብ አዛዥ።
መሐመድ ሽራዚ፦ የአሊ ኻሜኒ ወታደራዊ ቢሮ ሃላፊ (በመንፈሳዊ መሪው እና በአዛዦች መካከል ያለው ቁልፍ ድልድይ)።
ሳላህ አሳዲ፦ የወታደራዊ አስቸኳይ ጊዜ ዋና መስሪያ ቤት የደህንነት ሃላፊ።
ሁሴን ጃባል-አሜሊያን፦ የላቁ የጦር መሳሪያዎች ምርምር ድርጅት (SPND) ፕሬዝዳንት።
ሬዛ ሞዛፋሪ-ኒያ፦ የቀድሞው የSPND ሃላፊ እና የኑክሌር ፕሮግራም ቁልፍ ሰው።
ቀደም ብሎ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አይቶላ አሊ ኻሜኒ ስለመገደላቸው በሮይተርስ እና ፎክስ ኒውስ ዘገባዎች ቢወጡም፣ እስራኤል እስካሁን በይፋ ያረጋገጠችው የእነዚህን 7 ባለስልጣናት መገደል ብቻ ነው።
3 months ago
በመካከለኛው ምስራቅ የቀሰቀሰው ጦርነት፤ የዱባይ የቅንጦት ሆቴል በኢራን ሚሳኤል ጋየ
በዱባይ የሚገኘው ታዋቂው 'ፌርሞንት ዘ ፓልም' የቅንጦት ሆቴል በደረሰበት የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ።
አደጋው የተከሰተው ኢራን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላይ በሰነዘረችው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት የተተኮሱ ሚሳኤሎች ተመተው ሲወድቁ ባረፉ ፍንጣሪዎች መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ "ኤፒክ ራዝ" እና "ላየንስ ሮር" የተሰኙ ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን ተከትሎ፣ ኢራን በአጸፋው በዱባይ፣ ባህሬን እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር አዳዲስ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት በዱባይ አየር ማረፊያዎች ተዘግተው ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የት እንዳሉ አለመታወቁ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።
seledadotio
seledadotio
በዱባይ የሚገኘው ታዋቂው 'ፌርሞንት ዘ ፓልም' የቅንጦት ሆቴል በደረሰበት የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ።
አደጋው የተከሰተው ኢራን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላይ በሰነዘረችው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት የተተኮሱ ሚሳኤሎች ተመተው ሲወድቁ ባረፉ ፍንጣሪዎች መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ "ኤፒክ ራዝ" እና "ላየንስ ሮር" የተሰኙ ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን ተከትሎ፣ ኢራን በአጸፋው በዱባይ፣ ባህሬን እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር አዳዲስ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት በዱባይ አየር ማረፊያዎች ተዘግተው ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የት እንዳሉ አለመታወቁ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
በመካከለኛው ምስራቅ የቀሰቀሰው ጦርነት፤ የዱባይ የቅንጦት ሆቴል በኢራን ሚሳኤል ጋየ
በዱባይ የሚገኘው ታዋቂው 'ፌርሞንት ዘ ፓልም' የቅንጦት ሆቴል በደረሰበት የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ።
አደጋው የተከሰተው ኢራን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላይ በሰነዘረችው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት የተተኮሱ ሚሳኤሎች ተመተው ሲወድቁ ባረፉ ፍንጣሪዎች መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ "ኤፒክ ራዝ" እና "ላየንስ ሮር" የተሰኙ ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን ተከትሎ፣ ኢራን በአጸፋው በዱባይ፣ ባህሬን እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር አዳዲስ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት በዱባይ አየር ማረፊያዎች ተዘግተው ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የት እንዳሉ አለመታወቁ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።
በዱባይ የሚገኘው ታዋቂው 'ፌርሞንት ዘ ፓልም' የቅንጦት ሆቴል በደረሰበት የእሳት አደጋ ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ።
አደጋው የተከሰተው ኢራን በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ላይ በሰነዘረችው የሚሳኤል ጥቃት ወቅት የተተኮሱ ሚሳኤሎች ተመተው ሲወድቁ ባረፉ ፍንጣሪዎች መሆኑ ተገልጿል።
አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ "ኤፒክ ራዝ" እና "ላየንስ ሮር" የተሰኙ ጥቃቶችን መሰንዘራቸውን ተከትሎ፣ ኢራን በአጸፋው በዱባይ፣ ባህሬን እና ኳታር በሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የመከላከያ ሚኒስቴር አዳዲስ የሚሳኤል እና የድሮን ጥቃቶችን ማክሸፉን አስታውቋል።
በአሁኑ ወቅት በዱባይ አየር ማረፊያዎች ተዘግተው ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የት እንዳሉ አለመታወቁ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሶታል።
3 months ago
እስላማዊው ምሁር አያቶላ አሊ ኻሜኒ
#fastmereja I ዕድሜያቸው 86 ዓመት የሆኑት እስላማዊው ምሁር አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ እ.ኤ.አ. ከ1989 ጀምሮ የኢራን የበላይ መሪ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ። ኻሜኒ ወደዚህ ሥልጣን የመጡት፣ የአሜሪካ ወዳጅ የነበሩትን ሻህ መሐመድ ሬዛ ፓህላቪን ከሥልጣን ያወረደውን የ1979ኙን የኢራን አብዮት የመሩትንና የሪፐብሊኩን መሥራች አያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን በመተካት ነው።
አያቶላ ኻሜኒ በሀገሪቱ የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ከፍተኛውንና የመጨረሻውን የሥልጣን እርከን የጨበጡ ግለሰብ ናቸው።
በሁሉም የመንግሥት የሥልጣን ዘርፎች (ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈጻሚ) ላይ የበላይነት፣ በጦር ኃይሉና በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለው ሙሉ ትዕዛዝ፣ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪነት።
ኻሜኒ በሥልጣን ዘመናቸው ከምዕራባውያን አገራት ጋር በከረረ የጠላትነት ግንኙነት ውስጥ ቆይተዋል። በዚህም ሳቢያ ጠንካራ ማዕቀቦችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ በኢኮኖሚና በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ የሚነሱ ተቃውሞዎችን አስተናግደዋል። መሪው አሜሪካን የኢራን "ቁጥር አንድ ጠላት" ሲሉ የሚጠሯት ሲሆን፣ እስራኤልም በተከታታይ የዚሁ ጠላትነት አካል መሆኗን ይገልጻሉ።
አያቶላ ኻሜኒ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ የመሥራት ፍላጎት እንደሌላትና መርሃ-ግብሩ ለሲቪል አገልግሎት ብቻ የተገደበ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። ምንም እንኳን እስራኤልና አንዳንድ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ኢራን የአቶሚክ ቦምብ ለመሥራት እየጣረች መሆኑን ቢገልጹም፣ የአሜሪካ የደህንነት ተቋማትም ሆኑ የተባበሩት መንግሥታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ለዚህ በቂ ማስረጃ አላገኙም።
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም የወጡ ዓለም አቀፍ የዜና ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ወቅታዊ ሁኔታና ያሉበት ቦታ በውል አይታወቅም።
ሮይተርስ የዜና ወኪል የኢራን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ እየተካሄደ ያለውን የሚሳይልና የአየር ጥቃት ተከትሎ፣ መሪው ከከተማዋ ወጥተው ወደ "ደህንነቱ የተጠበቀ ስፍራ" ተዛውረዋል።
ምንም እንኳን ወደ ሚስጥራዊ ስፍራ መወሰዳቸው ቢረጋገጥም፣ ያ ስፍራ የት እንደሆነ ግን ለደህንነት ሲባል ይፋ አልተደረገም። አንዳንድ ምንጮች ቀደም ብለው መሪው ወደ ተመሸገ የምድር ውስጥ ባንከር ሳይዛወሩ እንዳልቀረ ግምታቸውን እየገለጹ ነው።
#fastmereja I ዕድሜያቸው 86 ዓመት የሆኑት እስላማዊው ምሁር አያቶላ አሊ ኻሜኒ፣ እ.ኤ.አ. ከ1989 ጀምሮ የኢራን የበላይ መሪ በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ። ኻሜኒ ወደዚህ ሥልጣን የመጡት፣ የአሜሪካ ወዳጅ የነበሩትን ሻህ መሐመድ ሬዛ ፓህላቪን ከሥልጣን ያወረደውን የ1979ኙን የኢራን አብዮት የመሩትንና የሪፐብሊኩን መሥራች አያቶላ ሩሆላ ኾሜኒን በመተካት ነው።
አያቶላ ኻሜኒ በሀገሪቱ የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ ከፍተኛውንና የመጨረሻውን የሥልጣን እርከን የጨበጡ ግለሰብ ናቸው።
በሁሉም የመንግሥት የሥልጣን ዘርፎች (ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈጻሚ) ላይ የበላይነት፣ በጦር ኃይሉና በፍትሕ ሥርዓቱ ላይ ያለው ሙሉ ትዕዛዝ፣ የሀገሪቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪነት።
ኻሜኒ በሥልጣን ዘመናቸው ከምዕራባውያን አገራት ጋር በከረረ የጠላትነት ግንኙነት ውስጥ ቆይተዋል። በዚህም ሳቢያ ጠንካራ ማዕቀቦችን እንዲሁም በሀገር ውስጥ በኢኮኖሚና በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ የሚነሱ ተቃውሞዎችን አስተናግደዋል። መሪው አሜሪካን የኢራን "ቁጥር አንድ ጠላት" ሲሉ የሚጠሯት ሲሆን፣ እስራኤልም በተከታታይ የዚሁ ጠላትነት አካል መሆኗን ይገልጻሉ።
አያቶላ ኻሜኒ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ የመሥራት ፍላጎት እንደሌላትና መርሃ-ግብሩ ለሲቪል አገልግሎት ብቻ የተገደበ መሆኑን በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። ምንም እንኳን እስራኤልና አንዳንድ የአሜሪካ ባለሥልጣናት ኢራን የአቶሚክ ቦምብ ለመሥራት እየጣረች መሆኑን ቢገልጹም፣ የአሜሪካ የደህንነት ተቋማትም ሆኑ የተባበሩት መንግሥታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ለዚህ በቂ ማስረጃ አላገኙም።
የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም የወጡ ዓለም አቀፍ የዜና ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የአያቶላ አሊ ኻሜኒ ወቅታዊ ሁኔታና ያሉበት ቦታ በውል አይታወቅም።
ሮይተርስ የዜና ወኪል የኢራን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሆነ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ እየተካሄደ ያለውን የሚሳይልና የአየር ጥቃት ተከትሎ፣ መሪው ከከተማዋ ወጥተው ወደ "ደህንነቱ የተጠበቀ ስፍራ" ተዛውረዋል።
ምንም እንኳን ወደ ሚስጥራዊ ስፍራ መወሰዳቸው ቢረጋገጥም፣ ያ ስፍራ የት እንደሆነ ግን ለደህንነት ሲባል ይፋ አልተደረገም። አንዳንድ ምንጮች ቀደም ብለው መሪው ወደ ተመሸገ የምድር ውስጥ ባንከር ሳይዛወሩ እንዳልቀረ ግምታቸውን እየገለጹ ነው።
Sponsored by
Surafel