Logo
FastMereja
ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት የሃዘን መግለጫ ሰጡ
#fastmereja I ​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ በሰማዕትነት ማረፋቸውን ተከትሎ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሃዘናቸውን ገልጸዋል።

​ፕሬዝዳንቱ በኤምባሲው በተዘጋጀው የሃዘን መግለጫ ስነ-ስርዓት ላይ በመገኘት በመዝገቡ ላይ መልዕክታቸውን አስፍረዋል።

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ ለኢራን ህዝብ እና መንግስት ያላቸውን ጥልቅ አጋርነት የገለጹ ሲሆን፣ ድርጊቱን "በእስራኤል እና በዩናይትድ ስቴትስ የተፈጸመ አሰቃቂ ጥቃት" ሲሉ ጠርተውታል።

​ፕሬዝዳንቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የአሊ ኻሜኒ ማረፍ "ኪሳራው ለኢራናውያን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ላሉ ሙስሊሞች ሁሉ ነው" በማለት የችግሩን ዓለም አቀፋዊነት ገልጸዋል።

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.