11 days ago
የማዕድን ዘርፍ እና አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
14 days ago
ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
16 days ago
በዘመናት መካከል የጸኑ ደጋፊዎች የደስታ ምሽት...
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) "አርሰናል ዋንጫ ይበላል?" አዎ ሆኗል መልሱ። የለንደን ሰማይ ወደ ቀይነት ተቀይሯል። የመድፈኞቹ ትንሳኤ ከ22 አመት በኋላ በቬታሊቲ ስታዲየም ተበስሯል ።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ (ከፈረንጆቹ 2004 ጀምሮ) የዘለቀው የአርሰናል ደጋፊዎች የዋንጫ ጥማት ሊሽር የአንዲት ነፍስ ወደ ምድር መጥታ ወጣት እስክትባል ተስፋ አስቆራጭ ነበር ።
ደጋፊዎቹ ግን በፅናት ስንት ጉድ መጥቶ በሄደበት ትንፋሻቸውን ውጠው ጠብቀዋል።
ዓለም ቅርጿን ብትቀያይር የአለም ዋንጫ ወደ አፍሪካ ምድር ቢመጣ፣ እነ ቤጂንግ የሉሏ ዘዋሪ ቢሆኑ፣ ኢትዮጵያ ዓባይን ገድባ ድግሷን ብትመርቅም አርሰናል ግን ዋንጫ አልበላም።
ዛሬ ግን ኤሚሬትስ ስታዲየም የናፈቀውን የፕሪሚየር ሊግ ክብር ዳግም አጊንቶ የደጋፊዎቹ ምድር ርዳለች ። ምድር አርግዳለች ።
ዋንጫው አርሰናል ዛሬ ላይ በቆመበት ደረጃ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ባለፉት አራት ዓመታት ሚኬል አርቴታ በትዕግስት የገነባው ሂደትን የማመን ፍሬ ነው።
ታዋቂው የእግር ኳስ ተንታኝ ጂሚ ካራገር በቅርቡ በሰጠው ትንታኔ፣ "የዘንድሮው አርሰናል ካለፉት ሁለት ዓመታት የሚለየው በአእምሮ ጥንካሬው ነው" ብሎ ነበር።
መድፈኞቹ ቀደም ሲል ወሳኝ ጨዋታዎች ላይ የመንሸራተት ባህሪ ነበራቸው፤ ዘንድሮ ግን በሜዳቸውም ሆነ ከሜዳቸው ውጪ እንደ ሻምፒዮን መጫወትን ተላምደዋል።
በመከላከሉ ረገድ የገነቡት የብረት ግንብ ለሊጉ ጥቂት ጎል ተቆጣሪ ቡድን እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።
በመካከለኛው ክፍል ደግሞ እንግሊዛዊው ዴክላን ራይስ የቡድኑ ሞተር በመሆን መከላከሉንና ማጥቃቱን በሚገርም ሁኔታ አስተሳስሮታል።
"እግር ኳስ በሜዳ ላይ ቢጫወትም አሸናፊው ግን በቁጥሮች ውስጥ ቀድሞ ይታያል" እንደሚባለው ሁሉ፣ የመረጃ ትንታኔዎች ለአርሰናል ትልቅ ተስፋ ነበራቸው።
አርሰናል ዘንድሮ በንፁህ ግብ መውጣት የሊጉን ክብረ ወሰን አድሷል ፤ ግብ ጠባቂው የወርቅ ዋንጫን ወስዷል።
እንግሊዛዊው ተንታኝ ጋሪ ኔቭል "አርሰናል ዘንድሮ ያንን የድል ተራራ መውጣት ብቻ ሳይሆን፣ ተራራው ላይ ባንዲራቸውን ለመትከል የሚያስችል ትጥቅ እንዳላቸው አሳይተዋል።"
ተንታኞች እንደሚስማሙት አርሰናል ካለፈው ዓመት ስህተቱ ተምሮ ስብስቡን በማስፋቱ፣ ተጫዋቾች ቢደክሙም የሚተኩት አቅም ተመሳሳይ ሆኗል።
የሊጉ ዋንጫ እጣ ፈንታ በሁለት ስፔናውያን አሰልጣኞች ፍልሚያ ሆኖ ፔፕ ጋርዲዮላን ለስንብት አርቴታን ለአሸናፊነት አብቅቷል።
ከመምህሩ ደቀ መዝሙሩ እንደሚባለው አርቴታ በጭንቅም ቢሆን የናፈቀውን ዋንጫ ለመሳም ታድሏል።
የ "ኖርዝ ለንደን ፎርኤቨር" መዝሙር በኤምሬትስ ሰማይ ስር በድል አድራጊነት እየተዘመረ ነው ።
የሉዊስ ደንፎርድ ግጥሞች "ይህ የደሜ ቀለም ነው፤ ለዘላለም የኔ ነው" እያሉ ሲያስተጋቡ፣ በደጋፊዎች አይን ላይ የሚታየው እንባ የክለቡን ጥልቅ ትስስር ያሳያል።
ይህ መዝሙር ደጋፊውን ከመጫወቻ ሜዳው ጋር በማስተሳሰር፣ ተጫዋቾቹ እስከ መጨረሻው ሰከንድ እንዲዋጉ የሚያደርግ የሞራል ስንቅ ነበር ።
ደጋፊዎቹ ቀይ ጭስ በማዘጋጀት ለንደንን ወደ ቀይ ቀለም ለመቀየር ቆርጠዋል። ይህ ድል ለደጋፊዎቹ ከእግር ኳስ ዋንጫ በላይ ነው፤ የለንደን የበላይነትን ዳግም የሚያረጋግጡበት ታላቅ ክስተት ነው።
አርሰናል ዋንጫ ይበላል? አዎ! የተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተመልካች ዓለም ነዋሪዎች የሚቀበሉት እውነት ሆኗል።
የመድፈኞቹ የቀረረው እንባ በደስታ ፈንጠዝያ ባሉበት የምድር ጫፍ ተተክቷል።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) "አርሰናል ዋንጫ ይበላል?" አዎ ሆኗል መልሱ። የለንደን ሰማይ ወደ ቀይነት ተቀይሯል። የመድፈኞቹ ትንሳኤ ከ22 አመት በኋላ በቬታሊቲ ስታዲየም ተበስሯል ።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ (ከፈረንጆቹ 2004 ጀምሮ) የዘለቀው የአርሰናል ደጋፊዎች የዋንጫ ጥማት ሊሽር የአንዲት ነፍስ ወደ ምድር መጥታ ወጣት እስክትባል ተስፋ አስቆራጭ ነበር ።
ደጋፊዎቹ ግን በፅናት ስንት ጉድ መጥቶ በሄደበት ትንፋሻቸውን ውጠው ጠብቀዋል።
ዓለም ቅርጿን ብትቀያይር የአለም ዋንጫ ወደ አፍሪካ ምድር ቢመጣ፣ እነ ቤጂንግ የሉሏ ዘዋሪ ቢሆኑ፣ ኢትዮጵያ ዓባይን ገድባ ድግሷን ብትመርቅም አርሰናል ግን ዋንጫ አልበላም።
ዛሬ ግን ኤሚሬትስ ስታዲየም የናፈቀውን የፕሪሚየር ሊግ ክብር ዳግም አጊንቶ የደጋፊዎቹ ምድር ርዳለች ። ምድር አርግዳለች ።
ዋንጫው አርሰናል ዛሬ ላይ በቆመበት ደረጃ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ባለፉት አራት ዓመታት ሚኬል አርቴታ በትዕግስት የገነባው ሂደትን የማመን ፍሬ ነው።
ታዋቂው የእግር ኳስ ተንታኝ ጂሚ ካራገር በቅርቡ በሰጠው ትንታኔ፣ "የዘንድሮው አርሰናል ካለፉት ሁለት ዓመታት የሚለየው በአእምሮ ጥንካሬው ነው" ብሎ ነበር።
መድፈኞቹ ቀደም ሲል ወሳኝ ጨዋታዎች ላይ የመንሸራተት ባህሪ ነበራቸው፤ ዘንድሮ ግን በሜዳቸውም ሆነ ከሜዳቸው ውጪ እንደ ሻምፒዮን መጫወትን ተላምደዋል።
በመከላከሉ ረገድ የገነቡት የብረት ግንብ ለሊጉ ጥቂት ጎል ተቆጣሪ ቡድን እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።
በመካከለኛው ክፍል ደግሞ እንግሊዛዊው ዴክላን ራይስ የቡድኑ ሞተር በመሆን መከላከሉንና ማጥቃቱን በሚገርም ሁኔታ አስተሳስሮታል።
"እግር ኳስ በሜዳ ላይ ቢጫወትም አሸናፊው ግን በቁጥሮች ውስጥ ቀድሞ ይታያል" እንደሚባለው ሁሉ፣ የመረጃ ትንታኔዎች ለአርሰናል ትልቅ ተስፋ ነበራቸው።
አርሰናል ዘንድሮ በንፁህ ግብ መውጣት የሊጉን ክብረ ወሰን አድሷል ፤ ግብ ጠባቂው የወርቅ ዋንጫን ወስዷል።
እንግሊዛዊው ተንታኝ ጋሪ ኔቭል "አርሰናል ዘንድሮ ያንን የድል ተራራ መውጣት ብቻ ሳይሆን፣ ተራራው ላይ ባንዲራቸውን ለመትከል የሚያስችል ትጥቅ እንዳላቸው አሳይተዋል።"
ተንታኞች እንደሚስማሙት አርሰናል ካለፈው ዓመት ስህተቱ ተምሮ ስብስቡን በማስፋቱ፣ ተጫዋቾች ቢደክሙም የሚተኩት አቅም ተመሳሳይ ሆኗል።
የሊጉ ዋንጫ እጣ ፈንታ በሁለት ስፔናውያን አሰልጣኞች ፍልሚያ ሆኖ ፔፕ ጋርዲዮላን ለስንብት አርቴታን ለአሸናፊነት አብቅቷል።
ከመምህሩ ደቀ መዝሙሩ እንደሚባለው አርቴታ በጭንቅም ቢሆን የናፈቀውን ዋንጫ ለመሳም ታድሏል።
የ "ኖርዝ ለንደን ፎርኤቨር" መዝሙር በኤምሬትስ ሰማይ ስር በድል አድራጊነት እየተዘመረ ነው ።
የሉዊስ ደንፎርድ ግጥሞች "ይህ የደሜ ቀለም ነው፤ ለዘላለም የኔ ነው" እያሉ ሲያስተጋቡ፣ በደጋፊዎች አይን ላይ የሚታየው እንባ የክለቡን ጥልቅ ትስስር ያሳያል።
ይህ መዝሙር ደጋፊውን ከመጫወቻ ሜዳው ጋር በማስተሳሰር፣ ተጫዋቾቹ እስከ መጨረሻው ሰከንድ እንዲዋጉ የሚያደርግ የሞራል ስንቅ ነበር ።
ደጋፊዎቹ ቀይ ጭስ በማዘጋጀት ለንደንን ወደ ቀይ ቀለም ለመቀየር ቆርጠዋል። ይህ ድል ለደጋፊዎቹ ከእግር ኳስ ዋንጫ በላይ ነው፤ የለንደን የበላይነትን ዳግም የሚያረጋግጡበት ታላቅ ክስተት ነው።
አርሰናል ዋንጫ ይበላል? አዎ! የተወዳጁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተመልካች ዓለም ነዋሪዎች የሚቀበሉት እውነት ሆኗል።
የመድፈኞቹ የቀረረው እንባ በደስታ ፈንጠዝያ ባሉበት የምድር ጫፍ ተተክቷል።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
16 days ago
የትግራይ የሰላም እና ለውጥ ምክር ቤት ተመሠረተ
«የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት» የተባለ ስብስብ አዲስ አበባ ዉስጥ ተቋቋመ። የተለያዩ የሃገር ዉስጥ መገናኛዎች እንደዘገቡት፤ ከስምንት ወራት በፊት የትግራይ ለውጥ ፈላጊ ኃይሎች ንቅናቄ በሚል የተቋቋመው ማህበር ማኒፌስቶውን በማሻሻል «የትግራይ የሰላም ለውጥ ምክር ቤት» በሚል አዲስ አበባ ላይ የመጀመሪያ የምስረታ ጉባዔውን ትናንት ሰኞ አደርጓል።
በምክር ቤቱ ምስረታ ጉባዔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪዎች መካከል የሆኑት ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ጀነራል ጎዕሽ ገብረ ፣ ሰባት ማህበራዊ መሠረታቸውን ትግራይ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የቀድሞ የክልሉ አመራሮች፣ የቀድሞ ወታደራዊ አዛዦችና ታጋዮች እንዲሁም ማህበራት መገኘታቸዉን የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። አቶ ጌታቸዉ ረዳ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በቅርቡ መቀሌ እንደሚገባ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ ምስረታ ዋና አላማ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት እና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ በጉልበት ስልጣን የተቆጣጠረውን የህወሓትን ቡድን በማስወገድ በክልሉ ምርጫ ተደርጎ ህጋዊ መንግስት እንዲመሠረት በተደራጀ መንገድ በመጓዝ ሰላማዊ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር ነው መባሉም ተመልክቷል።
ከዚህ ሌላ ትግራይ ክልልን ከጦርነቱ ወደነበረችበት ሕገ መንግሥታዊ የግዛት ቅርጿ በመመለስ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ በተደራጀ ሁኔታ መስራት ነዉ። ምክር ቤቱ አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ስምረት፣ ባይቶና፣ ዓረና ትግራይ፣ ትንሳኤ 70 እንደርታ እና ቃንቺ ሀቂ እንዲሁም በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱትን የሀራ_መሬት ታጋዮችን ወታደራዊ ክንፍ ማሰባሰቡ ተገልጿል።
DW Amharic
«የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት» የተባለ ስብስብ አዲስ አበባ ዉስጥ ተቋቋመ። የተለያዩ የሃገር ዉስጥ መገናኛዎች እንደዘገቡት፤ ከስምንት ወራት በፊት የትግራይ ለውጥ ፈላጊ ኃይሎች ንቅናቄ በሚል የተቋቋመው ማህበር ማኒፌስቶውን በማሻሻል «የትግራይ የሰላም ለውጥ ምክር ቤት» በሚል አዲስ አበባ ላይ የመጀመሪያ የምስረታ ጉባዔውን ትናንት ሰኞ አደርጓል።
በምክር ቤቱ ምስረታ ጉባዔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪዎች መካከል የሆኑት ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ጀነራል ጎዕሽ ገብረ ፣ ሰባት ማህበራዊ መሠረታቸውን ትግራይ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የቀድሞ የክልሉ አመራሮች፣ የቀድሞ ወታደራዊ አዛዦችና ታጋዮች እንዲሁም ማህበራት መገኘታቸዉን የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። አቶ ጌታቸዉ ረዳ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በቅርቡ መቀሌ እንደሚገባ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ ምስረታ ዋና አላማ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት እና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ በጉልበት ስልጣን የተቆጣጠረውን የህወሓትን ቡድን በማስወገድ በክልሉ ምርጫ ተደርጎ ህጋዊ መንግስት እንዲመሠረት በተደራጀ መንገድ በመጓዝ ሰላማዊ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር ነው መባሉም ተመልክቷል።
ከዚህ ሌላ ትግራይ ክልልን ከጦርነቱ ወደነበረችበት ሕገ መንግሥታዊ የግዛት ቅርጿ በመመለስ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ በተደራጀ ሁኔታ መስራት ነዉ። ምክር ቤቱ አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ስምረት፣ ባይቶና፣ ዓረና ትግራይ፣ ትንሳኤ 70 እንደርታ እና ቃንቺ ሀቂ እንዲሁም በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱትን የሀራ_መሬት ታጋዮችን ወታደራዊ ክንፍ ማሰባሰቡ ተገልጿል።
DW Amharic
28 days ago
ሰውዬው "አትርሱኝ" የሚለውን ቃል እንደ እናቱ ምርቃት ሳይሆን እንደ ታክስ መክፈያ ደረሰኝ ነው የሚያየው። አንዳንዱ "አትርሱኝ" ባይ ደግሞ "አትርሱኝ" የሚለውን ቃል ሲጠቀም፣ ቃልኪዳን እየገባ ሳይሆን "ሪከርድ" እያደረገ ነው የሚመስለው።
ለካስ ሳናውቀው "አትርሱኝ" ማለት ያለ እረፍት እኔን በማሰብ ተሰቃዩ ማለት ሆኗል!
ይህ ሰውዬ አገር ሰላም ሆኖ፣ ፀሐይ ወጥቶ ሲገባም ጭምር "አትርሱኝ" ይላል። ቆይ ምን ያህል ቢረሳ ነው? ወይስ ረሺው ብዙ ነው? እኔ የምለው... ሰውዬው "የረሳኝ" ብሎ የሚጠረጥራቸው ሰዎች ብዛት፣ በምርጫ ወቅት "ያልመረጠኝ" ብሎ ከሚቆጥር ፖለቲከኛ ይበልጣል።
ለሠርግ ተጠርቶ "እንኳን ደስ አላችሁ" ከማለት ይልቅ "አትርሱኝ" ይላል። ሙሽሮቹ በጫጉላ ሰዓት እንኳ የእርሱን ፊት እያሰቡ "እንዴት ይረሳል?" እያሉ እንዲጨነቁ ይፈልጋል። ደግሞ እኮ የሚረሳ ነገር ቢኖረው አይቆጭም። ሰውዬው እንደ ድሮ ስልክ "ኮንታክት" በቃሉ የያዘው ቁጥር የለም፤ ግን "አትርሱኝ" ማለቱን አይረሳም።
አንድ ቀን እንዲያውም እንዲህ ሆነ... ሞት መጥቶ በሩን ሲያንኳኳ፣ ሰውዬው መርዶውን ከመቀበሉ በፊት "እሺ መሞቴንስ እሞታለሁ፤ ግን በኋላ ስትመለስ እንዳትረሳኝ" ብሎታል ይባላል። መቃብሩ ላይ "አትርሱኝ" የሚል ፅሁፍ ካልተፃፈማ፣ ትንሳኤ ቀን መጥቶ "አልተፃፈም" ብሎ "ሪፖርት" እንደሚያደርግ አልጠራጠርም።
እሱ "አትርሱኝ" የሚለው ቃል ለእርሱ የህይወት "ሴፍቲ ቤልት" ናት። አየር በነፃ እንደምናገኘው ሁሉ እርሱም ትዝታን በነፃ ማግኘት ይፈልጋል። ግን የሚገርመው ነገር፣ እርሱን ለማስታወስ ስትሞክር የምታስታውሰው ብቸኛ ነገር እርሱ "አትርሱኝ" ማለቱን ብቻ ነው።
ወዳጄ... የዚህን ሰውዬ ስም ከረሳኸው አይከፋም፤ "አትርሱኝ" ማለቱን ከረሳህ ግን እራሱ መጥቶ "ለምን ረሳኸኝ?" ብሎ ትዝታህን "አፕዴት" ያደርገዋል። እንዲያውም እኮ "አትርሱኝ" ማለት የአማርኛ ቋንቋ "ቫይረስ" ሆኗል። አንድን ነገር ለመናገር መግቢያህ "አትርሱኝ" ከሆነ፣ ንግግሩ ሳይጀምር ሰልችቶሃል ማለት ነው።
በእውነት ለመናገር... ሰውዬው ከሞተ በኋላ እንኳ በመንፈስ መጥቶ የቁም ጓደኞቹን "ቅምጥል ትዝታ" እያሳከከ "እንዴ... የዛሬ አምስት ዓመት እንዲህ ብዬህ አልነበር? እንዴት ረሳኸኝ?" ሳይላቸው አይቀርም።
እኔ የምለው... ሐኪም ቤት ሄዶ "ዶክተር... መታመሜን እንዳትረሳው" ቢል ሐኪሙ መድኃኒት ይፅፍለታል ወይስ "የመርሳት በሽታ" ያለበት እራሱ ሐኪሙ እንደሆነ ይቆጥራል?
ለማንኛውም... ይህንን ወግ አንብባችሁ ስትጨርሱ "አትርሱኝ" እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እኔ "ረሱኝ" ብዬ ኮርጃለሁ!
አበጀ በለው የላኩልን
ለካስ ሳናውቀው "አትርሱኝ" ማለት ያለ እረፍት እኔን በማሰብ ተሰቃዩ ማለት ሆኗል!
ይህ ሰውዬ አገር ሰላም ሆኖ፣ ፀሐይ ወጥቶ ሲገባም ጭምር "አትርሱኝ" ይላል። ቆይ ምን ያህል ቢረሳ ነው? ወይስ ረሺው ብዙ ነው? እኔ የምለው... ሰውዬው "የረሳኝ" ብሎ የሚጠረጥራቸው ሰዎች ብዛት፣ በምርጫ ወቅት "ያልመረጠኝ" ብሎ ከሚቆጥር ፖለቲከኛ ይበልጣል።
ለሠርግ ተጠርቶ "እንኳን ደስ አላችሁ" ከማለት ይልቅ "አትርሱኝ" ይላል። ሙሽሮቹ በጫጉላ ሰዓት እንኳ የእርሱን ፊት እያሰቡ "እንዴት ይረሳል?" እያሉ እንዲጨነቁ ይፈልጋል። ደግሞ እኮ የሚረሳ ነገር ቢኖረው አይቆጭም። ሰውዬው እንደ ድሮ ስልክ "ኮንታክት" በቃሉ የያዘው ቁጥር የለም፤ ግን "አትርሱኝ" ማለቱን አይረሳም።
አንድ ቀን እንዲያውም እንዲህ ሆነ... ሞት መጥቶ በሩን ሲያንኳኳ፣ ሰውዬው መርዶውን ከመቀበሉ በፊት "እሺ መሞቴንስ እሞታለሁ፤ ግን በኋላ ስትመለስ እንዳትረሳኝ" ብሎታል ይባላል። መቃብሩ ላይ "አትርሱኝ" የሚል ፅሁፍ ካልተፃፈማ፣ ትንሳኤ ቀን መጥቶ "አልተፃፈም" ብሎ "ሪፖርት" እንደሚያደርግ አልጠራጠርም።
እሱ "አትርሱኝ" የሚለው ቃል ለእርሱ የህይወት "ሴፍቲ ቤልት" ናት። አየር በነፃ እንደምናገኘው ሁሉ እርሱም ትዝታን በነፃ ማግኘት ይፈልጋል። ግን የሚገርመው ነገር፣ እርሱን ለማስታወስ ስትሞክር የምታስታውሰው ብቸኛ ነገር እርሱ "አትርሱኝ" ማለቱን ብቻ ነው።
ወዳጄ... የዚህን ሰውዬ ስም ከረሳኸው አይከፋም፤ "አትርሱኝ" ማለቱን ከረሳህ ግን እራሱ መጥቶ "ለምን ረሳኸኝ?" ብሎ ትዝታህን "አፕዴት" ያደርገዋል። እንዲያውም እኮ "አትርሱኝ" ማለት የአማርኛ ቋንቋ "ቫይረስ" ሆኗል። አንድን ነገር ለመናገር መግቢያህ "አትርሱኝ" ከሆነ፣ ንግግሩ ሳይጀምር ሰልችቶሃል ማለት ነው።
በእውነት ለመናገር... ሰውዬው ከሞተ በኋላ እንኳ በመንፈስ መጥቶ የቁም ጓደኞቹን "ቅምጥል ትዝታ" እያሳከከ "እንዴ... የዛሬ አምስት ዓመት እንዲህ ብዬህ አልነበር? እንዴት ረሳኸኝ?" ሳይላቸው አይቀርም።
እኔ የምለው... ሐኪም ቤት ሄዶ "ዶክተር... መታመሜን እንዳትረሳው" ቢል ሐኪሙ መድኃኒት ይፅፍለታል ወይስ "የመርሳት በሽታ" ያለበት እራሱ ሐኪሙ እንደሆነ ይቆጥራል?
ለማንኛውም... ይህንን ወግ አንብባችሁ ስትጨርሱ "አትርሱኝ" እንዳትሉኝ። ምክንያቱም እኔ "ረሱኝ" ብዬ ኮርጃለሁ!
አበጀ በለው የላኩልን
28 days ago
የማያልቀው የወርቅ ማዕድን ፍለጋ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በመጋቢት እና ሚያዚያ 2018 ዓ.ም ወራት ያከናወኗቸው ተግባራት
በመጋቢት እና ሚያዚያ 2018 ዓ.ም ወራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳይንሳዊ የምርምር ልህቀት፣ በከተማ ልማት፣ በኢኮኖሚ ሪፎርም እና በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
• የፕሮጀክቶች ምረቃ እና የሥራ ጅማሮ
የመጋቢት ወር በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የተመረቁበት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ውስጥ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀዋል። ይህ ማዕከል 40 የላብራቶሪ ክፍሎችን እና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራት የሚያረጋግጥ የባዮ-ኢኩቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን ያካተተ ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍ፣ የሚያዝያ ወር በአገልግሎት እና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ግንባታ ረገድ ጉልህ እመርታ የታየበት ወር ነበር። የአራዳ ፓርክ ፕሮጀክት ከፍተኛ የሆነ የከተማ ገጽታ ለውጥ የታየበት ሲሆን፤ ቀደም ሲል ችላ ተብለውና ለአደጋ ተጋልጠው የነበሩ ቤቶች የሚገኙበትን 40 ሄክታር መሬት ወደ ዘመናዊ ሁለገብ መዳረሻነት ቀይሮታል። ይህ የተቀናጀ የመሠረተ-ልማት እና የመሬት አጠቃቀም ውጤታማነት የታየበት ፕሮጀክት፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ ከ700 በላይ ነባር ቤቶችን የማደስ ስራን አካቷል።
ከዚህም በተጨማሪ በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውና የኦሊምፒክ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት መሠረተ-ልማቶችን፣ የ15 የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊዎችን ሃውልት እና ለተነሺ ነዋሪዎች ተብለው የተገነቡ 105 የንግድ ሱቆችን የያዘው የአዲስ ስፖርት ፓርክ በዚሁ ወር ተመርቋል።
የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት አቅም ለማሳደግ የ100 ሜጋ ዋት የአሰላ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ተመርቋል። በተጨማሪም በሀዋሳ የቶዮ ምዕራፍ 2፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎች ሥራ ጀምረዋል። እነዚህ ፋብሪካዎች ከአዲሱ የኤች.ዜድ (HZ) ጋዝ ፋብሪካ ጋር በመሆን በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹህ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በቱሪዝም ዘርፍ፦ በገበታ ለትውልድ መርሃ-ግብር የተገነባው የሀሮ ደንዲ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። በመጨረሻም፣ እንደ መታወቂያ ምዝገባ እና የሥራ ፈቃድ ያሉ መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የታለመው የመሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ስራ ጀምሯል።
• ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ ኅብረት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና የዲጂታል ጤና መሪ ሆነው የተሾሙት በያዝነው የሚያዝያ ነው።
ይህ ኃላፊነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአካታች ዕድገት ቁልፍ መሣሪያ የሆኑትን የፈጠራ ሥራዎችን እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በማሳደግ ረገድ እያሳዩት ያለውን የአመራር ጥበብ እውቅና የሰጠ ሲሆን ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ንቁ አመራር ሰጪነት በዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ያስመዘገበችውን ጉልህ ስራ የሚያሳይ ነው።
• የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአፈጻጸም ግምገማ፦
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሦስተኛውን የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም እና የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ግምገማ መርተዋል። በዚህም የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት 9.2 በመቶ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ወደ 10.2 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። ሪፖርቱ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ላይ የተመዘገበውን ስኬታማ ሽግግር በዝርዝር ያሳየ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ኪሳራ ያስመዘግቡ የነበሩ ተቋማት በአሁኑ ወቅት 2.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ ወደ ማስገባት ተሸጋግረዋል። ለዚህ ውጤት መገኘት ቁልፍ የሆነው የግሉ ዘርፍ የኢኮኖሚ እድገቱ ዋና መሪ እንዲሆን ቅድሚያ የሚሰጠው የሪፎርም አጀንዳ ነው።
ይህም እንደ ካፒታል ገበያ ባሉ አዳዲስ የፋይናንስ ሥርዓቶች እና እያደገ በመጣው የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነት እየተደገፈ ይገኛል።
• የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማጠናከር አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) እና ሮቦቲክስን በመጠቀም ወደ ቺፕስ እና ዳታ (ኢንዱስትሪ 4.0) መሸጋገር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የውጭ ምርቶችን መተካት የቻለው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የይዞታ መጠን ወደ 88 በመቶ ማድረሱን በስኬትነቱ ጠቅሰዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ሰላማዊ የባሕር በር ማግኘት የሀገር የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት የሰጡ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ መሆኗ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዳትሆን ከፍተኛ የሎጂስቲክስ ወጪ እንደሚጨምርባት አስገንዝበዋል።
• ማህበራዊ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ አመራር፦
“ማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ” በተሰኘው እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የምክክር መድረክ ላይ፣ መንግሥት ባለፉት ስምንት ዓመታት ከ19.8 ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን እና ይበልጥ ተዓማኒነት ያለው ሥርዓተ-ትምህርት ተግባራዊ መደረጉ ተገልጿል።
በጤናው ዘርፍም በቅደመ መከላከል እና አክሞ ማዳን፤ መካከል የተሻለ ሚዛን ለመፍጠር ለ30 ዓመታት ያገለገለው ፖሊሲ እንዲሻሻል ተደርጓል። በአካባቢ ጥበቃ ረገድም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 የሚካሄደውን የኮፕ32 (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ ቅድመ ዝግጅት የጀመረች ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ዝግጅቱ ከሀገራዊው የአረንጓዴ ልማት ግቦች ጋር የተጣጣመ መሆኑን እንዲያረጋግጥ ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴውን ሰብስበው አቅጣጫ ተሰጥተዋል።
• ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር፦
ኢትዮጵያ የብሩንዲ፣ የላይቤሪያ፣ የደቡብ ሱዳን እና የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንቶችን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያስተናገደች ሲሆን፤ ይህም በመከላከያ፣ በጤና፣ በትምህርት እና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ በርካታ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አስችሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር፣ ከአፍሪካ ኤክስፖርትና ኢምፖርት (Afrexim) ባንክ ፕሬዝዳንት፣ እንዲሁም ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ እና የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጅቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትርን በመቀበል በሁለትዮሽ ትብብሮች ዙሪያ የመከሩ ሲሆን፤ ከአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ጋር ደግሞ በአፍሪካ ህብረት ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ዲጂታል ጤና ረገድ የተሰጣቸውን ሚና ጨምሮ ሰፋ ባሉ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በሀገር ውስጥ ጉዳይ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ከሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ጋር በመገናኘት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን የገመገሙ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንቱን የሥራ ዘመን ለተጨማሪ አንድ ዓመት በይፋ አራዝመዋል።
የሚያዝ ወር የትንሳኤ በዓል የተከበረበት በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በማዘጋጀትና አነስተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የቁሳቁስ ድጋፍ በማጋራት ተጠናቋል።
#ethiopiadelivers #pmoethiopia
በመጋቢት እና ሚያዚያ 2018 ዓ.ም ወራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሳይንሳዊ የምርምር ልህቀት፣ በከተማ ልማት፣ በኢኮኖሚ ሪፎርም እና በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።
• የፕሮጀክቶች ምረቃ እና የሥራ ጅማሮ
የመጋቢት ወር በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የተመረቁበት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ውስጥ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀዋል። ይህ ማዕከል 40 የላብራቶሪ ክፍሎችን እና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራት የሚያረጋግጥ የባዮ-ኢኩቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን ያካተተ ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍ፣ የሚያዝያ ወር በአገልግሎት እና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ግንባታ ረገድ ጉልህ እመርታ የታየበት ወር ነበር። የአራዳ ፓርክ ፕሮጀክት ከፍተኛ የሆነ የከተማ ገጽታ ለውጥ የታየበት ሲሆን፤ ቀደም ሲል ችላ ተብለውና ለአደጋ ተጋልጠው የነበሩ ቤቶች የሚገኙበትን 40 ሄክታር መሬት ወደ ዘመናዊ ሁለገብ መዳረሻነት ቀይሮታል። ይህ የተቀናጀ የመሠረተ-ልማት እና የመሬት አጠቃቀም ውጤታማነት የታየበት ፕሮጀክት፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ ከ700 በላይ ነባር ቤቶችን የማደስ ስራን አካቷል።
ከዚህም በተጨማሪ በ5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውና የኦሊምፒክ ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት መሠረተ-ልማቶችን፣ የ15 የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊዎችን ሃውልት እና ለተነሺ ነዋሪዎች ተብለው የተገነቡ 105 የንግድ ሱቆችን የያዘው የአዲስ ስፖርት ፓርክ በዚሁ ወር ተመርቋል።
የሀገሪቱን የኃይል አቅርቦት አቅም ለማሳደግ የ100 ሜጋ ዋት የአሰላ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ተመርቋል። በተጨማሪም በሀዋሳ የቶዮ ምዕራፍ 2፣ የኦሪጂን እና የሉሚንቴክ የሶላር ፋብሪካዎች ሥራ ጀምረዋል። እነዚህ ፋብሪካዎች ከአዲሱ የኤች.ዜድ (HZ) ጋዝ ፋብሪካ ጋር በመሆን በዓመት 11.3 ጊጋ ዋት ንጹህ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በቱሪዝም ዘርፍ፦ በገበታ ለትውልድ መርሃ-ግብር የተገነባው የሀሮ ደንዲ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። በመጨረሻም፣ እንደ መታወቂያ ምዝገባ እና የሥራ ፈቃድ ያሉ መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የታለመው የመሶብ ተንቀሳቃሽ የአውቶቡስ አገልግሎት ስራ ጀምሯል።
• ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ ኅብረት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና የዲጂታል ጤና መሪ ሆነው የተሾሙት በያዝነው የሚያዝያ ነው።
ይህ ኃላፊነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአካታች ዕድገት ቁልፍ መሣሪያ የሆኑትን የፈጠራ ሥራዎችን እና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን በማሳደግ ረገድ እያሳዩት ያለውን የአመራር ጥበብ እውቅና የሰጠ ሲሆን ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ንቁ አመራር ሰጪነት በዲጂታላይዜሽን ዘርፍ ያስመዘገበችውን ጉልህ ስራ የሚያሳይ ነው።
• የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአፈጻጸም ግምገማ፦
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሦስተኛውን የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም እና የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ግምገማ መርተዋል። በዚህም የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት 9.2 በመቶ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፣ በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ወደ 10.2 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። ሪፖርቱ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ላይ የተመዘገበውን ስኬታማ ሽግግር በዝርዝር ያሳየ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ኪሳራ ያስመዘግቡ የነበሩ ተቋማት በአሁኑ ወቅት 2.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ ወደ ማስገባት ተሸጋግረዋል። ለዚህ ውጤት መገኘት ቁልፍ የሆነው የግሉ ዘርፍ የኢኮኖሚ እድገቱ ዋና መሪ እንዲሆን ቅድሚያ የሚሰጠው የሪፎርም አጀንዳ ነው።
ይህም እንደ ካፒታል ገበያ ባሉ አዳዲስ የፋይናንስ ሥርዓቶች እና እያደገ በመጣው የመንግሥትና የግል ዘርፍ አጋርነት እየተደገፈ ይገኛል።
• የኢንዱስትሪ ስትራቴጂ ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማጠናከር አርቴፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) እና ሮቦቲክስን በመጠቀም ወደ ቺፕስ እና ዳታ (ኢንዱስትሪ 4.0) መሸጋገር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የውጭ ምርቶችን መተካት የቻለው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የይዞታ መጠን ወደ 88 በመቶ ማድረሱን በስኬትነቱ ጠቅሰዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ፣ ሰላማዊ የባሕር በር ማግኘት የሀገር የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት የሰጡ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ መሆኗ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዳትሆን ከፍተኛ የሎጂስቲክስ ወጪ እንደሚጨምርባት አስገንዝበዋል።
• ማህበራዊ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ አመራር፦
“ማኅበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ” በተሰኘው እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የምክክር መድረክ ላይ፣ መንግሥት ባለፉት ስምንት ዓመታት ከ19.8 ሚሊዮን በላይ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን እና ይበልጥ ተዓማኒነት ያለው ሥርዓተ-ትምህርት ተግባራዊ መደረጉ ተገልጿል።
በጤናው ዘርፍም በቅደመ መከላከል እና አክሞ ማዳን፤ መካከል የተሻለ ሚዛን ለመፍጠር ለ30 ዓመታት ያገለገለው ፖሊሲ እንዲሻሻል ተደርጓል። በአካባቢ ጥበቃ ረገድም ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 የሚካሄደውን የኮፕ32 (COP32) ጉባኤን ለማስተናገድ ቅድመ ዝግጅት የጀመረች ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ዝግጅቱ ከሀገራዊው የአረንጓዴ ልማት ግቦች ጋር የተጣጣመ መሆኑን እንዲያረጋግጥ ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴውን ሰብስበው አቅጣጫ ተሰጥተዋል።
• ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር፦
ኢትዮጵያ የብሩንዲ፣ የላይቤሪያ፣ የደቡብ ሱዳን እና የሞዛምቢክ ፕሬዝዳንቶችን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ያስተናገደች ሲሆን፤ ይህም በመከላከያ፣ በጤና፣ በትምህርት እና በዲጂታል መሠረተ-ልማት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ በርካታ የመግባቢያ ስምምነቶች እንዲፈረሙ አስችሏል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአውሮፓ ህብረት ዓለም አቀፍ አጋርነት ኮሚሽነር፣ ከአፍሪካ ኤክስፖርትና ኢምፖርት (Afrexim) ባንክ ፕሬዝዳንት፣ እንዲሁም ከፖርቹጋል የውጭ ጉዳይ እና የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ጋር ተወያይተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጅቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትርን በመቀበል በሁለትዮሽ ትብብሮች ዙሪያ የመከሩ ሲሆን፤ ከአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ጋር ደግሞ በአፍሪካ ህብረት ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ዲጂታል ጤና ረገድ የተሰጣቸውን ሚና ጨምሮ ሰፋ ባሉ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በሀገር ውስጥ ጉዳይ፦
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ከሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ጋር በመገናኘት ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን የገመገሙ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንቱን የሥራ ዘመን ለተጨማሪ አንድ ዓመት በይፋ አራዝመዋል።
የሚያዝ ወር የትንሳኤ በዓል የተከበረበት በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በማዘጋጀትና አነስተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሠራተኞች የቁሳቁስ ድጋፍ በማጋራት ተጠናቋል።
#ethiopiadelivers #pmoethiopia
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ማህበራዊ ትንሳኤ ከምኞት ወደ እውነታ
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የነበሩባትን ሥር የሰደዱ ማህበራዊ ስብራቶች ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በብልሃትና በጥልቀት ስትጠግን ቆይታለች። ዛሬ ላይ ቆመን ስንመለከት ሀገራዊ ግንባታችን በወረቀት ላይ ከሰፈረው ወጥቶ፣ በዜጎች ጤና፣ በእውቀት ብርሃንና በምግብ ዋስትና ዐውድማ ላይ በተግባር እየተተረጎመ ይገኛል። ይህ ጉዞ ተራ የፖሊሲ ማሻሻያ ሳይሆን የኢትዮጵያን የነገ ማንነት የሚወስን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ለሰላሳ ዓመታት በፖሊሲ ማነቆ ታስሮ የቆየው የጤናው ዘርፍ፣ ዛሬ አዲስ እስትንፋስ ዘርቶበታል። “ቀድሞ መከላከል ለነገው ተስፋ፣ አክሞ ማዳን ለዛሬው ዋስትና” በሚል ፖሊሲያችን መከላከልን ብቻ ሳይሆን ሕይወትን ታድጎ ማቆየትንም ትልቅ ግቡ አድርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑት ተግባራት ዘርፉን ከመሠረቱ የለወጡ ናቸው።
ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ መድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶችን የማምረት አቅሟን ማሳደጓ፣ የውጭ ጥገኝነትን ቀንሶ የሉዓላዊነታችን አንዱ አካል ሆኗል። ይህ ስኬት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን፣ በዓለም አቀፍ የጤና ዲፕሎማሲ መድረክ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ድምፅ እንድትሆን አስችሏታል።
ወረርሽኞችን የመለየትና የመቆጣጠር አቅም ማደግ፣ የዲጂታል ጤና ሥርዓት ትግበራ እና የባለሙያዎች ብቃት መጨመር የሀገራችንን የጤና ዋስትና አስተማማኝ አድርገውታል።
“ሳይደግስ አይጣላም” እንዲሉ በትምህርት ዘርፍ የነበረውን የጥራት ውድቀት ለመቀልበስ የተከፈለው መስዋዕትነት ለነገው ትውልድ ትልቅ መሠረት ጥሏል። የሥርዓተ-ትምህርት ክለሳውና የፈተናዎች አስተዳደር መሻሻል የዕውቀት ሌብነትን አክስሞ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን የመቅረጽ ጉዟችንን አፋጥኖታል።
በተለይም ለጥራት መውደቅ ዋነኛ ምክንያት የነበረውን የቅድመ መደበኛ ትምህርት ክፍተት ለመሙላት የተጀመረው ንቅናቄ የሚደነቅ ነው። “እንጨት በለጋነቱ፣ ልጅ በጨቅላነቱ” እንደሚባለው የነገውን ምሁር ዛሬውኑ በጥራት ለመቅረጽ የተያዘው ስትራቴጂ በተግባር እየታየ ነው።
በቅርቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚገነቡት 1 ሺህ 452 አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ87 ሺህ በላይ ሕጻናትን ወደ ዕውቀት ማዕድ የሚጋብዝ ድንቅ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ነው። ይህ ኢንቨስትመንት ለነገው ትውልድ የሚቆረስ የዕውቀት እንጀራ ነው።
ሀገር የምትገነባውና ማህበራዊ ልማት ትርጉም የሚኖረው በምግብ ዋስትና ነውና “የዘሩትን ያጭዳሉ” የሚለው ብሂል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማታችን ላይ እውን ሆኗል። በላባችንና በውኃ ሀብታችን የፈጠርነው ተዓምር፣ ኢትዮጵያ ከልመና እጅ ወደ ሰጪነት የምታደርገውን ሽግግር እያፋጠነው ይገኛል።
የውኃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እያሸጋገረን ነው። ይህ የታታሪነት ውጤት ለሀገር ግንባታ ሂደት የጸና መሠረት ጥሏል።
ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩት የማህበራዊ ዘርፍ እንቅስቃሴዎች የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን የኑሮ ጥራት የሚቀይሩ ተጨባጭ ተግባራትን ያቀፉ ናቸው። “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንዲሉ፣ እነዚህ የፖሊሲና የተግባር ውጤቶች ተደምረው ነገ የምንረከባት ኢትዮጵያ በጤና የተሻለች፣ በእውቀቷ የዳበረችና በልመና የማታፍር እንድትሆን አድርገዋታል።
ይህ የለውጥ ጉዞ የፖሊሲ ማሻሻያ ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን ኑሮ በተግባር የመቀየር ታላቅ የትውልድ አደራ መፈጸሚያ ሆኗል። ባለፉት ዓመታት በትምህርት፣ በጤና፣ በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በባህልና ስፖርት የተመዘገቡ ውጤቶች የነገውን ጉዞ ብሩህ የሚያደርግ ነው። ኢትዮጵያ በማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ የምታደርገው ጥረት ለሌሎችም አርአያ የሚሆንና የዜጎችን ተስፋ የሚያለመልም ታላቅ ስኬት ነው።
የኢቢሲዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የነበሩባትን ሥር የሰደዱ ማህበራዊ ስብራቶች ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በብልሃትና በጥልቀት ስትጠግን ቆይታለች። ዛሬ ላይ ቆመን ስንመለከት ሀገራዊ ግንባታችን በወረቀት ላይ ከሰፈረው ወጥቶ፣ በዜጎች ጤና፣ በእውቀት ብርሃንና በምግብ ዋስትና ዐውድማ ላይ በተግባር እየተተረጎመ ይገኛል። ይህ ጉዞ ተራ የፖሊሲ ማሻሻያ ሳይሆን የኢትዮጵያን የነገ ማንነት የሚወስን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
ለሰላሳ ዓመታት በፖሊሲ ማነቆ ታስሮ የቆየው የጤናው ዘርፍ፣ ዛሬ አዲስ እስትንፋስ ዘርቶበታል። “ቀድሞ መከላከል ለነገው ተስፋ፣ አክሞ ማዳን ለዛሬው ዋስትና” በሚል ፖሊሲያችን መከላከልን ብቻ ሳይሆን ሕይወትን ታድጎ ማቆየትንም ትልቅ ግቡ አድርጓል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑት ተግባራት ዘርፉን ከመሠረቱ የለወጡ ናቸው።
ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ መድኃኒትና የሕክምና ግብዓቶችን የማምረት አቅሟን ማሳደጓ፣ የውጭ ጥገኝነትን ቀንሶ የሉዓላዊነታችን አንዱ አካል ሆኗል። ይህ ስኬት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን፣ በዓለም አቀፍ የጤና ዲፕሎማሲ መድረክ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ድምፅ እንድትሆን አስችሏታል።
ወረርሽኞችን የመለየትና የመቆጣጠር አቅም ማደግ፣ የዲጂታል ጤና ሥርዓት ትግበራ እና የባለሙያዎች ብቃት መጨመር የሀገራችንን የጤና ዋስትና አስተማማኝ አድርገውታል።
“ሳይደግስ አይጣላም” እንዲሉ በትምህርት ዘርፍ የነበረውን የጥራት ውድቀት ለመቀልበስ የተከፈለው መስዋዕትነት ለነገው ትውልድ ትልቅ መሠረት ጥሏል። የሥርዓተ-ትምህርት ክለሳውና የፈተናዎች አስተዳደር መሻሻል የዕውቀት ሌብነትን አክስሞ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን የመቅረጽ ጉዟችንን አፋጥኖታል።
በተለይም ለጥራት መውደቅ ዋነኛ ምክንያት የነበረውን የቅድመ መደበኛ ትምህርት ክፍተት ለመሙላት የተጀመረው ንቅናቄ የሚደነቅ ነው። “እንጨት በለጋነቱ፣ ልጅ በጨቅላነቱ” እንደሚባለው የነገውን ምሁር ዛሬውኑ በጥራት ለመቅረጽ የተያዘው ስትራቴጂ በተግባር እየታየ ነው።
በቅርቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚገነቡት 1 ሺህ 452 አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ከ87 ሺህ በላይ ሕጻናትን ወደ ዕውቀት ማዕድ የሚጋብዝ ድንቅ የሀገር ግንባታ ምሰሶ ነው። ይህ ኢንቨስትመንት ለነገው ትውልድ የሚቆረስ የዕውቀት እንጀራ ነው።
ሀገር የምትገነባውና ማህበራዊ ልማት ትርጉም የሚኖረው በምግብ ዋስትና ነውና “የዘሩትን ያጭዳሉ” የሚለው ብሂል በበጋ መስኖ ስንዴ ልማታችን ላይ እውን ሆኗል። በላባችንና በውኃ ሀብታችን የፈጠርነው ተዓምር፣ ኢትዮጵያ ከልመና እጅ ወደ ሰጪነት የምታደርገውን ሽግግር እያፋጠነው ይገኛል።
የውኃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እያሸጋገረን ነው። ይህ የታታሪነት ውጤት ለሀገር ግንባታ ሂደት የጸና መሠረት ጥሏል።
ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩት የማህበራዊ ዘርፍ እንቅስቃሴዎች የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን የኑሮ ጥራት የሚቀይሩ ተጨባጭ ተግባራትን ያቀፉ ናቸው። “ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንዲሉ፣ እነዚህ የፖሊሲና የተግባር ውጤቶች ተደምረው ነገ የምንረከባት ኢትዮጵያ በጤና የተሻለች፣ በእውቀቷ የዳበረችና በልመና የማታፍር እንድትሆን አድርገዋታል።
ይህ የለውጥ ጉዞ የፖሊሲ ማሻሻያ ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን ኑሮ በተግባር የመቀየር ታላቅ የትውልድ አደራ መፈጸሚያ ሆኗል። ባለፉት ዓመታት በትምህርት፣ በጤና፣ በክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በባህልና ስፖርት የተመዘገቡ ውጤቶች የነገውን ጉዞ ብሩህ የሚያደርግ ነው። ኢትዮጵያ በማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ የምታደርገው ጥረት ለሌሎችም አርአያ የሚሆንና የዜጎችን ተስፋ የሚያለመልም ታላቅ ስኬት ነው።
የኢቢሲዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
1 month ago
በሞቱ ህይወትን የሰጠን በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልንን የአባታችንን የመድኃኔዓለምን ቤት ከመፍረስ እንታደግ! 🙏✨
የወደቀውን ለማቅናት፣ የፈረሰውን ለመጠገን ሁላችንም ኦርቶዶክሳውያን እንረባረብ!
ከ60 አመት በላይ ያስቆጠረው በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቀይት ወረዳ የሚገኘው መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ዛሬ በከባድ ችግር ላይ ይገኛል። ከእድሜ ብዛት የተነሳ የቤተ መቅደሱ ቋሚ ምሰሶዎች በምስጥ ተበልተው፣ ጣሪያውም በማፍሰሱ ምክንያት የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ፣ ምንጣፍ እንዲሁም ንዋየቅድሳቱ በመሉ ከጥቅም ውጪ ሆኗል የአባታችን የመድኃኔዓለም ማደሪያ መቅደሱም ሊወድቅ ጥቂት ቀርቶታል።
አባቶችም በተማፅኖ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን እርዱን እያሉ ከፊታችን ቆመዋል!
ስለ እኛ በቀራንዮ አደባባይ ስጋውን የቆረሰው ፣ደሙን ያፈሰሰውና የእሾህ አክሊል የደፋው በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልን መድኃኔዓለም፣ ዛሬ የእኛን እጅ ይፈልጋል። ከ 200 ብር ጀምረን የአቅማችንን በመለገስ ይህንን ታሪካዊ መቅደስ ከመፍረስ እንታደግ።
የባንክ አካውንት (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - CBE)፦
🏦 1000756255626
(መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤ/ክ)
📞 ለበለጠ መረጃ
+251-920-950007
(እባክዎን የክርስትና ስምዎን በቴሌግራም ወይም በዋትሳፕ በዚሁ ስልክ ይላኩላቸው በፀሎት ያስቧችኋል)
እባካችሁ ሼር (Share) በማድረግ ድምፅ ሁኑልኝ! 🙏⛪
#getu #medhanealem #savethechurch #northshewa #ethiopianorthodox #humanitariancall #heritageconservation #ethiopia #የመድኃኔዓለምቤት #ሰሜንሸዋ #ቤተክርስቲያን #ጥሪ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
1 month ago
በሞቱ ህይወትን የሰጠን በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልንን የአባታችንን የመድኃኔዓለምን ቤት ከመፍረስ እንታደግ! 🙏✨
የወደቀውን ለማቅናት፣ የፈረሰውን ለመጠገን ሁላችንም ኦርቶዶክሳውያን እንረባረብ!
ከ60 አመት በላይ ያስቆጠረው በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቀይት ወረዳ የሚገኘው መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ዛሬ በከባድ ችግር ላይ ይገኛል። ከእድሜ ብዛት የተነሳ የቤተ መቅደሱ ቋሚ ምሰሶዎች በምስጥ ተበልተው፣ ጣሪያውም በማፍሰሱ ምክንያት የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ፣ ምንጣፍ እንዲሁም ንዋየቅድሳቱ በመሉ ከጥቅም ውጪ ሆኗል የአባታችን የመድኃኔዓለም ማደሪያ መቅደሱም ሊወድቅ ጥቂት ቀርቶታል።
አባቶችም በተማፅኖ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን እርዱን እያሉ ከፊታችን ቆመዋል!
ስለ እኛ በቀራንዮ አደባባይ ስጋውን የቆረሰው ፣ደሙን ያፈሰሰውና የእሾህ አክሊል የደፋው በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልን መድኃኔዓለም፣ ዛሬ የእኛን እጅ ይፈልጋል። ከ 200 ብር ጀምረን የአቅማችንን በመለገስ ይህንን ታሪካዊ መቅደስ ከመፍረስ እንታደግ።
የባንክ አካውንት (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - CBE)፦
🏦 1000756255626
(መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤ/ክ)
📞 ለበለጠ መረጃ
+251-920-950007
(እባክዎን የክርስትና ስምዎን በቴሌግራም ወይም በዋትሳፕ በዚሁ ስልክ ይላኩላቸው በፀሎት ያስቧችኋል)
እባካችሁ ሼር (Share) በማድረግ ድምፅ ሁኑልኝ! 🙏⛪
#getu #medhanealem #savethechurch #northshewa #ethiopianorthodox #humanitariancall #heritageconservation #ethiopia #የመድኃኔዓለምቤት #ሰሜንሸዋ #ቤተክርስቲያን #ጥሪ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
በሞቱ ህይወትን የሰጠን በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልንን የአባታችንን የመድኃኔዓለምን ቤት ከመፍረስ እንታደግ! 🙏✨
የወደቀውን ለማቅናት፣ የፈረሰውን ለመጠገን ሁላችንም ኦርቶዶክሳውያን እንረባረብ!
ከ60 አመት በላይ ያስቆጠረው በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቀይት ወረዳ የሚገኘው መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ዛሬ በከባድ ችግር ላይ ይገኛል። ከእድሜ ብዛት የተነሳ የቤተ መቅደሱ ቋሚ ምሰሶዎች በምስጥ ተበልተው፣ ጣሪያውም በማፍሰሱ ምክንያት የአባታችን የመድኃኔዓለም ማደሪያ ሊወድቅ ጥቂት ቀርቶታል።
አባቶችም በተማፅኖ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን እርዱን እያሉ ከፊታችን ቆመዋል!
ስለ እኛ በቀራንዮ አደባባይ ስጋውን የቆረሰው ፣ደሙን ያፈሰሰውና የእሾህ አክሊል የደፋው በትንሳኤው ትንሳኤያችንን ያወጀልን መድኃኔዓለም፣ ዛሬ የእኛን እጅ ይፈልጋል። ከ 200 ብር ጀምረን የአቅማችንን በመለገስ ይህንን ታሪካዊ መቅደስ ከመፍረስ እንታደግ።
የባንክ አካውንት (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - CBE)፦
🏦 1000756255626
(መለጥ ደብረ ፀሐይ መድኃኔዓለም ቤ/ክ)
📞 ለበለጠ መረጃ
+251-920-950007
(እባክዎን የክርስትና ስምዎን በቴሌግራም ወይም በዋትሳፕ በዚሁ ስልክ ይላኩላቸው በፀሎት ያስቧችኋል)
እባካችሁ ሼር (Share) በማድረግ ድምፅ ሁኑልኝ! 🙏⛪
#getu #medhanealem #savethechurch #northshewa #ethiopianorthodox #humanitariancall #heritageconservation #ethiopia #የመድኃኔዓለምቤት #ሰሜንሸዋ #ቤተክርስቲያን #ጥሪ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ከፍተኛ የፖሊስ አመራር የነበሩት ኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ በታጠቁ ኃይሎች ተገደሉ
#fastmereja I በከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፍተኛ አመራር የነበሩት ኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ፣ የትንሳኤ በዓል ከቤተሰቦቻቸው ጋር አሳልፈው ወደ ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ በታጠቁ ኃይሎች በተከፈተባቸው ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉ ተሰማ። ኮማንደሯ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በኩል ተመርጠው በሀገር መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዋር ኮሌጅ የስትራቴጂክ አመራር ስልጠና በመከታተል ላይ ነበሩ።
ግድያው የተፈጸመው ሚያዝያ 05 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡35 ላይ ኮማንደሯ ከቤተሰብ ጥየቃ ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ሳሉ መሆኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው የሀዘን መግለጫ አረጋግጧል።
ኮማንደር አልማዝ የሁለት ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ እናት ነበሩ። የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በከፍተኛ አመራሩ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
#fastmereja I በከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፍተኛ አመራር የነበሩት ኮማንደር አልማዝ ዮሐንስ፣ የትንሳኤ በዓል ከቤተሰቦቻቸው ጋር አሳልፈው ወደ ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ በታጠቁ ኃይሎች በተከፈተባቸው ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉ ተሰማ። ኮማንደሯ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በኩል ተመርጠው በሀገር መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ዋር ኮሌጅ የስትራቴጂክ አመራር ስልጠና በመከታተል ላይ ነበሩ።
ግድያው የተፈጸመው ሚያዝያ 05 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡35 ላይ ኮማንደሯ ከቤተሰብ ጥየቃ ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ ሳሉ መሆኑን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው የሀዘን መግለጫ አረጋግጧል።
ኮማንደር አልማዝ የሁለት ሴትና የአንድ ወንድ ልጅ እናት ነበሩ። የከምባታ ዞን ፖሊስ መምሪያ በከፍተኛ አመራሩ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል።
2 months ago
ዛሬ ማዕዶት ነው!
#ethiopia | የትንሳኤ በዓልን በደስታ አክብረን፣ ዛሬ የበዓሉ ማግስት ሰኞ ላይ እንገኛለን። ይህች ቀን በቤተክርስቲያን ስነ-ስርዓት "ማዕዶት" ትባላለች።
ማዕዶት ማለት ምን ማለት ነው?
"ማዕዶት" የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "መሻገር" ማለት ነው። ይህም የእስራኤል ልጆች ከግብፅ ባርነት ወደ ከነዓን መሻገራቸውን፣ እንዲሁም እኛ የሰው ልጆች ከሞት ወደ ህይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሲኦል ወደ ገነት የተሻገርንበትን ታላቅ ምስጢር የምናስብበት ነው።
ትናንት የጀመርነው ታላቅ የደስታ በዓል ዛሬም በቤተሰባዊ ጨዋታና በምስጋና ይቀጥላል።
ትናንት በስራ ወይም በተለያዩ ምክንያቶች ያልተገናኙ ዘመድ አዝማድ የሚጠያየቁበት፣ ማዕድ የሚጋሩበትና ፍቅር የሚታደስበት ቀን ነው።
ከረዥሙ የሁዳዴ ጾም በኋላ ሰውነታችንና መንፈሳችን አዲስ ብርታትን የሚያገኝበት፣ ወደ መደበኛ ስራችን ከመመለሳችን በፊት የምናርፍበት ዕለት ነው።
ፈጣሪ ሀገራችንንና ህዝባችንን ከክፉ ነገር ሁሉ አሻግሮ ለሰላምና ለፍቅር ብርሃን ያብቃን!
መልካም የትንሳኤ ማግስት ይሁንላችሁ! 🕊️
Getu Temesgen - (ጌጡ
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የትንሳኤ በዓልን በደስታ አክብረን፣ ዛሬ የበዓሉ ማግስት ሰኞ ላይ እንገኛለን። ይህች ቀን በቤተክርስቲያን ስነ-ስርዓት "ማዕዶት" ትባላለች።
ማዕዶት ማለት ምን ማለት ነው?
"ማዕዶት" የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም "መሻገር" ማለት ነው። ይህም የእስራኤል ልጆች ከግብፅ ባርነት ወደ ከነዓን መሻገራቸውን፣ እንዲሁም እኛ የሰው ልጆች ከሞት ወደ ህይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሲኦል ወደ ገነት የተሻገርንበትን ታላቅ ምስጢር የምናስብበት ነው።
ትናንት የጀመርነው ታላቅ የደስታ በዓል ዛሬም በቤተሰባዊ ጨዋታና በምስጋና ይቀጥላል።
ትናንት በስራ ወይም በተለያዩ ምክንያቶች ያልተገናኙ ዘመድ አዝማድ የሚጠያየቁበት፣ ማዕድ የሚጋሩበትና ፍቅር የሚታደስበት ቀን ነው።
ከረዥሙ የሁዳዴ ጾም በኋላ ሰውነታችንና መንፈሳችን አዲስ ብርታትን የሚያገኝበት፣ ወደ መደበኛ ስራችን ከመመለሳችን በፊት የምናርፍበት ዕለት ነው።
ፈጣሪ ሀገራችንንና ህዝባችንን ከክፉ ነገር ሁሉ አሻግሮ ለሰላምና ለፍቅር ብርሃን ያብቃን!
መልካም የትንሳኤ ማግስት ይሁንላችሁ! 🕊️
Getu Temesgen - (ጌጡ
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በ110 ሺህ ብር በተገዛ ሰንጋ በሬ ውስጥ ከ10 ግራም በላይ የወርቅ ክምችት ተገኘ
የትንሳኤ በዓል በቃሊቲ የመኖሪያ ካምፕ ለሚገኙ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ያልተጠበቀ ነገር አጋጥሟቸዋል።
አባላቱ ለበዓል ቅርጫ ካረዱት ሰንጋ በሬ ሀሞት ውስጥ ከ10 ግራም በላይ የሚመዝን ወርቅ ማግኘታቸውን የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን አስታውቋል።
የፖሊስ አባላቱ እንደሚናገሩት፣ በዘንድሮው በዓል የከብት ዋጋ በመወደዱ ምክንያት ይህንን ሰንጋ በሬ ለመግዛት ብዙ ድካምና እንግልት አሳልፈዋል።በመጨረሻም በ110 ሺህ ብር የገዙት ሰንጋ፣ ለበዓሉ ድግስ ብቻ ሳይሆን ያልተጠበቀ ወርቅ ይዞላቸው እንደሚመጣ አልገመቱም ነበር።
በአሁኑ ሰዓት የፖሊስ አባላቱ የተገኘውን ወርቅ ለመሸጥ ከወርቅ ተረካቢዎች ጋር የዋጋ ድርድር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
Via የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን
seledadotio
seledadotio
የትንሳኤ በዓል በቃሊቲ የመኖሪያ ካምፕ ለሚገኙ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ያልተጠበቀ ነገር አጋጥሟቸዋል።
አባላቱ ለበዓል ቅርጫ ካረዱት ሰንጋ በሬ ሀሞት ውስጥ ከ10 ግራም በላይ የሚመዝን ወርቅ ማግኘታቸውን የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን አስታውቋል።
የፖሊስ አባላቱ እንደሚናገሩት፣ በዘንድሮው በዓል የከብት ዋጋ በመወደዱ ምክንያት ይህንን ሰንጋ በሬ ለመግዛት ብዙ ድካምና እንግልት አሳልፈዋል።በመጨረሻም በ110 ሺህ ብር የገዙት ሰንጋ፣ ለበዓሉ ድግስ ብቻ ሳይሆን ያልተጠበቀ ወርቅ ይዞላቸው እንደሚመጣ አልገመቱም ነበር።
በአሁኑ ሰዓት የፖሊስ አባላቱ የተገኘውን ወርቅ ለመሸጥ ከወርቅ ተረካቢዎች ጋር የዋጋ ድርድር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።
Via የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን
seledadotio
seledadotio
2 months ago
አስቸኳይ የእርዳታ ተማጽኖ
ለጀግናው ብስክሌተኛ ሀይላይ አርአያ ደራሽ እንሁን! 🚴♂️🙏
#ethiopia | ሀገሩን በብስክሌት ስፖርት ለብዙ ዓመታት በክብር ያስጠራው፣ በፅናቱ ለብዙዎች አርአያ የነበረው የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባል ሀይላይ አርአያ፣ በአሁኑ ሰዓት በከባድ የጤና ችግር ምክንያት በሆስፒታል አልጋ ላይ ይገኛል።
ከዚህ በፊት ታክሞ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ህመሙ በአጣዳፊ ሁኔታ በማገርሸቱ ጀግናው የእያንዳንዳችንን ድጋፍ ይፈልጋል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
(CBE)፦ 1000365329854
ሀይላይ አርአያ ገ/ማርያም
(HAILAY ARAYA G/MARIAM)
ለተጨማሪ መረጃ
+251-915-815264
"ጀግና ሲወድቅ አይታይም" የሚለውን አባባል በተግባር ቀይረን፣ ይህን ጀግና በጋራ እናንሳው።
ዛሬ የምናደርገው ትንሽ ድጋፍ ለሀይላይ የነገ ህይወቱ ትንሳኤ ነው።
እባካችሁ ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን።
#getu #helphailayaraya #ethiopianhero #cyclingethiopia #humanitarianaid #sportscommunity #addisababa #ethiopia #supportourheroes #ርዳታ #ለሀይላይአርአያ #ጀግናሲወድቅአይታይም #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ለጀግናው ብስክሌተኛ ሀይላይ አርአያ ደራሽ እንሁን! 🚴♂️🙏
#ethiopia | ሀገሩን በብስክሌት ስፖርት ለብዙ ዓመታት በክብር ያስጠራው፣ በፅናቱ ለብዙዎች አርአያ የነበረው የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባል ሀይላይ አርአያ፣ በአሁኑ ሰዓት በከባድ የጤና ችግር ምክንያት በሆስፒታል አልጋ ላይ ይገኛል።
ከዚህ በፊት ታክሞ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ህመሙ በአጣዳፊ ሁኔታ በማገርሸቱ ጀግናው የእያንዳንዳችንን ድጋፍ ይፈልጋል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
(CBE)፦ 1000365329854
ሀይላይ አርአያ ገ/ማርያም
(HAILAY ARAYA G/MARIAM)
ለተጨማሪ መረጃ
+251-915-815264
"ጀግና ሲወድቅ አይታይም" የሚለውን አባባል በተግባር ቀይረን፣ ይህን ጀግና በጋራ እናንሳው።
ዛሬ የምናደርገው ትንሽ ድጋፍ ለሀይላይ የነገ ህይወቱ ትንሳኤ ነው።
እባካችሁ ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን።
#getu #helphailayaraya #ethiopianhero #cyclingethiopia #humanitarianaid #sportscommunity #addisababa #ethiopia #supportourheroes #ርዳታ #ለሀይላይአርአያ #ጀግናሲወድቅአይታይም #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
በትንሳኤ ሳምንት የጊፍት ኤክስፖን ሳያዩ ቤት እንዳይገዙ!
****
ለአጭር ጊዜ በተዘጋጀው የጊፍት የትንሳኤ ኤክስፖ በአፓርትመንቶችና በንግድ ሱቆች እስከ 15% ቅናሽ ተደርጓል፡፡
በ5% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ዕድሉ ተመቻችቷል!
ኤክስፖው ሚያዝያ 10/2018 ዓ.ም. ይጠናቀቃል!
ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
ለበለጠ መረጃ
+251 984 6565 65
Visit 🌐 https://www.giftrealestate...
****
ለአጭር ጊዜ በተዘጋጀው የጊፍት የትንሳኤ ኤክስፖ በአፓርትመንቶችና በንግድ ሱቆች እስከ 15% ቅናሽ ተደርጓል፡፡
በ5% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ዕድሉ ተመቻችቷል!
ኤክስፖው ሚያዝያ 10/2018 ዓ.ም. ይጠናቀቃል!
ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
ለበለጠ መረጃ
+251 984 6565 65
Visit 🌐 https://www.giftrealestate...
2 months ago
ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ለሩሲያ ምስጋና አቀረቡ
#ethiopia | የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
መሪዎቹ በውይይታቸው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን መልካም ጉርብትና እና ስልታዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ሩሲያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ግጭቶችን ለማርገብ ለምትከተለው መርህ-ተኮር አቋም ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፤ ሞስኮ ለኢራን ሕዝብ ላደረገችው ሰብአዊ እርዳታም አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢራኑ ፕሬዝዳንት ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ለመላው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ይህ የመሪዎቹ የሁለትዮሽ ውይይት በምዕራባውያን ማዕቀብ ውስጥ የሚገኙት ሁለቱ አገራት በኢኮኖሚ፣ በጸጥታና በዲፕሎማሲ መስኮች ያላቸውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በሚጥሩበት ወቅት የተደረገ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #russia #diplomacy #putin #pezeshkian #geopolitics #tehran #moscow #ኢራን #ሩሲያ #ዲፕሎማሲ #ዜና
#ethiopia | የኢራኑ ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን ከሩሲያው አቻቸው ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
መሪዎቹ በውይይታቸው በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን መልካም ጉርብትና እና ስልታዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን የጋራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን ሩሲያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ግጭቶችን ለማርገብ ለምትከተለው መርህ-ተኮር አቋም ምስጋናቸውን ያቀረቡ ሲሆን፤ ሞስኮ ለኢራን ሕዝብ ላደረገችው ሰብአዊ እርዳታም አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢራኑ ፕሬዝዳንት ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና ለመላው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ይህ የመሪዎቹ የሁለትዮሽ ውይይት በምዕራባውያን ማዕቀብ ውስጥ የሚገኙት ሁለቱ አገራት በኢኮኖሚ፣ በጸጥታና በዲፕሎማሲ መስኮች ያላቸውን ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር በሚጥሩበት ወቅት የተደረገ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #russia #diplomacy #putin #pezeshkian #geopolitics #tehran #moscow #ኢራን #ሩሲያ #ዲፕሎማሲ #ዜና
2 months ago
ብርብር ማርያም
📌 እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ
#ethiopia | በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን በጨንቻ ወረዳ ከከተማው 30 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኘው ብርብር ማርያም፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ ታሪኳን የምታስታውስበት ታላቅ ገዳም ናት።
በዚህ ገዳም ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የመሥዋዕተ ኦሪት ማዕከል እንደነበረች የሚነገርላት ሲሆን፣ መሥዋዕቱ ይቀርብበት የነበረው "ዳታን" የተባለው ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ ለታሪክ ምስክር ሆኖ ይገኛል።
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሐ ዘመነ መንግሥት የክርስትና እምነት በኢትዮጵያ ሲስፋፋ፣ በብርብር ማርያም ይከናወን የነበረው የኦሪት ሥርዓት በሐዲስ ኪዳን መሥዋዕት እንዲተካ ተደርጓል።
ከጌታችን ልደት በፊት 400 ዓመት አካባቢ ጀምሮ የብሉይ ኪዳን ትምህርት ሲሰጥባትና መሥዋዕት ሲሰዋባት የኖረችው ይህች ስፍራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ የሃይማኖት ማዕከል በመሆን አገልግላለች።
በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ዐፄ ገብረ መስቀል፣ ቅዱስ ያሬድንና አቡነ አረጋዊን በማስከተል ወደ ደቡብ ሲጓዙ የታቦተ ማርያምን ጽላት ይዘው ወደዚሁ ስፍራ አቅንተዋል።
ግንቦት 20 ቀን ገዳሟ ደርሰው ሌሊቱን በጸሎትና በማኅሌት ካደሩ በኋላ፣ በማግሥቱ ግንቦት 21 ቀን አቡነ አረጋዊ ቤተ መቅደሱን በሜሮን ባርከው ታቦተ ማርያምን በክብር አግብተዋል። በዚሁ ዕለት ዐፄ ገብረ መስቀል ለገዳሟ መተዳደሪያ የሚሆን ሰፊ ርስት መስጠታቸው በታሪክ ድርሳናት ተመዝግቦ ይገኛል።
በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቡዳ ኬንና የተባለ ፀረ-ሃይማኖት ኃይል ገዳሟን ለማጥፋትና ለማቃጠል ቢሞክርም፣ በተአምር ሳይሳካለት መቅረቱ የገዳሟን ቅዱስነት የሚያሳይ ሌላኛው ታሪክ ነው። ከብዙ ዘመናት መረሳት በኋላ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዐፄ እስክንድር ዘመን በድጋሚ የተተከለች ሲሆን፣ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብና በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥታትም የታደሰችና የተገደመች መሆኗ ይነገራል።
የገዳሟ የመጀመሪያው መምህር አባ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ፣ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩት ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ምሁርና ደራሲ አባ ባሕርይም በዚህች ደብር ለረጅም ጊዜ ኖረዋል።
በዐፄ ምኒልክ ዘመን የኢትዮጵያ ግዛት ሲቀናጅ ገዳሟ በወርቅና በብር የተሠሩ ንዋያተ ቅድሳት፣ የነገሥታት ዘውዶችና ልዩ ልዩ ቅርሶች መገኛ ነበረች። ምንም እንኳ አሁን ላይ አብዛኞቹ ቅርሶች ባይገኙም፣ ገዳሟ አሁንም ድረስ ጥንታዊ አሻራዋን ጠብቃ ትገኛለች።
በ1928 ዓ.ም. ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ይህችን ታሪካዊ ቤተክርስቲያን በአውሮፕላን ቦምብ ለማጋየት ቢሞክርም፣ ተወርውሮ የወረደው ቦምብ ሳይፈነዳ እንደ ድንጋይ ተንከባሎ መውረዱ የእግዚአብሔር ጥበቃ ያልተለያት መሆኑን ያረጋግጣል።
ይህ ዛሬም ድረስ በግቢው ውስጥ የሚገኘው ቦምብና ሌሎች ታሪካዊ ምልክቶች፣ ብርብር ማርያም ለኢትዮጵያ ካላት መንፈሳዊና ታሪካዊ ፋይዳ በተጨማሪ ለጎብኚዎችና ለተመራማሪዎች ትልቅ መስህብ መሆኗን ያሳያሉ።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
📌 እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ
#ethiopia | በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን በጨንቻ ወረዳ ከከተማው 30 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኘው ብርብር ማርያም፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ረጅም ዘመናት ያስቆጠረ ታሪኳን የምታስታውስበት ታላቅ ገዳም ናት።
በዚህ ገዳም ከክርስቶስ ልደት በፊት ጀምሮ የመሥዋዕተ ኦሪት ማዕከል እንደነበረች የሚነገርላት ሲሆን፣ መሥዋዕቱ ይቀርብበት የነበረው "ዳታን" የተባለው ስፍራ እስከ ዛሬ ድረስ ለታሪክ ምስክር ሆኖ ይገኛል።
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሐ ዘመነ መንግሥት የክርስትና እምነት በኢትዮጵያ ሲስፋፋ፣ በብርብር ማርያም ይከናወን የነበረው የኦሪት ሥርዓት በሐዲስ ኪዳን መሥዋዕት እንዲተካ ተደርጓል።
ከጌታችን ልደት በፊት 400 ዓመት አካባቢ ጀምሮ የብሉይ ኪዳን ትምህርት ሲሰጥባትና መሥዋዕት ሲሰዋባት የኖረችው ይህች ስፍራ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ቀዳሚዋ የሃይማኖት ማዕከል በመሆን አገልግላለች።
በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ዐፄ ገብረ መስቀል፣ ቅዱስ ያሬድንና አቡነ አረጋዊን በማስከተል ወደ ደቡብ ሲጓዙ የታቦተ ማርያምን ጽላት ይዘው ወደዚሁ ስፍራ አቅንተዋል።
ግንቦት 20 ቀን ገዳሟ ደርሰው ሌሊቱን በጸሎትና በማኅሌት ካደሩ በኋላ፣ በማግሥቱ ግንቦት 21 ቀን አቡነ አረጋዊ ቤተ መቅደሱን በሜሮን ባርከው ታቦተ ማርያምን በክብር አግብተዋል። በዚሁ ዕለት ዐፄ ገብረ መስቀል ለገዳሟ መተዳደሪያ የሚሆን ሰፊ ርስት መስጠታቸው በታሪክ ድርሳናት ተመዝግቦ ይገኛል።
በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቡዳ ኬንና የተባለ ፀረ-ሃይማኖት ኃይል ገዳሟን ለማጥፋትና ለማቃጠል ቢሞክርም፣ በተአምር ሳይሳካለት መቅረቱ የገዳሟን ቅዱስነት የሚያሳይ ሌላኛው ታሪክ ነው። ከብዙ ዘመናት መረሳት በኋላ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዐፄ እስክንድር ዘመን በድጋሚ የተተከለች ሲሆን፣ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብና በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥታትም የታደሰችና የተገደመች መሆኗ ይነገራል።
የገዳሟ የመጀመሪያው መምህር አባ ሠርጸ ድንግል ሲሆኑ፣ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩት ታዋቂው ኢትዮጵያዊ ምሁርና ደራሲ አባ ባሕርይም በዚህች ደብር ለረጅም ጊዜ ኖረዋል።
በዐፄ ምኒልክ ዘመን የኢትዮጵያ ግዛት ሲቀናጅ ገዳሟ በወርቅና በብር የተሠሩ ንዋያተ ቅድሳት፣ የነገሥታት ዘውዶችና ልዩ ልዩ ቅርሶች መገኛ ነበረች። ምንም እንኳ አሁን ላይ አብዛኞቹ ቅርሶች ባይገኙም፣ ገዳሟ አሁንም ድረስ ጥንታዊ አሻራዋን ጠብቃ ትገኛለች።
በ1928 ዓ.ም. ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ይህችን ታሪካዊ ቤተክርስቲያን በአውሮፕላን ቦምብ ለማጋየት ቢሞክርም፣ ተወርውሮ የወረደው ቦምብ ሳይፈነዳ እንደ ድንጋይ ተንከባሎ መውረዱ የእግዚአብሔር ጥበቃ ያልተለያት መሆኑን ያረጋግጣል።
ይህ ዛሬም ድረስ በግቢው ውስጥ የሚገኘው ቦምብና ሌሎች ታሪካዊ ምልክቶች፣ ብርብር ማርያም ለኢትዮጵያ ካላት መንፈሳዊና ታሪካዊ ፋይዳ በተጨማሪ ለጎብኚዎችና ለተመራማሪዎች ትልቅ መስህብ መሆኗን ያሳያሉ።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
📜 18-8-8-8፡ የታሪክና የጥበብ ዘላለማዊነት ቀመር
የኢትዮጵያ ሰው "ንብን የነካ ማር አይቀምስም"ይላል።
እኛም ሳናውቅ በቀናነት እና በፍቅር የሰጠነው ሃሳብ የንቦቹን ንጉሥ ነክተን የአድናቂዎቹ ሲገስፁን ነው ነገሩ የገባን!
አልበሙን ለማጀብ በየቀለሙና በየመስመሩ ላይ የተደረገው የግራፊክስ ጥንቃቄም ሆነ የዜማው ብስለት፣ስራው "ጊዜ የማይሽረው" እንዲሆን ታስቦ መሆኑን ከቅርብ ሰው ተደውሎ ተረድተናል።
ታላቁ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ አዲሱን አልበም "ኢዮሪካ" (ETORIKA) ለማቅረብ ጊዜ የወሰደው እንዲሁ በቸልታ ሳይሆን፣ በየዘመኑ የማይጠወልግ እና በትውልድ ዘንድ የሚኖር ጥበብን ለመቅረጽ ነው።
ይህ በልዩ ጥንቃቄ የተቀመረ ምስላዊ ጥበብ (Graphics) በውስጡ የያዛቸው ምልክቶች ራሳቸው ትልቅ የታሪክ ምስጢር አላቸው
የ"ቶ" ፊደልና የአክሱም ሐውልት (ጽዮን)
ጥንታዊ ስልጣኔያችንን እና የሕይወት ትንሳኤን የሚወክሉ ሆነው አልበሙ እንደ ሐውልቱ ጸንቶ የሚኖር መሆኑን ያበስራሉ።
የአፍሪካ ሰዓት ⏱️
የአፍሪካ ምስል ያለበት የእጅ ሰዓት ማሰሪያው የአክሱም ሐውልት ሆኖ መሰራቱ ጊዜና ታሪክ ተሳስረው "የአፍሪካ ሰዓት" መድረሱን ያሳያል።
ባንዲራና ጥለቱ 🟢🟡🔴
አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ጥለቱ የማንነታችንና የነጻነታችን ዘላለማዊ አርማ ሆኖ ሎጎውን አሽቆጥቁጦታል።
ይህ በልዩ ጥንቃቄ የተሰራ ጥበብ ደግሞ ከ1888 ዓ.ም የዓድዋ ድል ታሪክ ጋር በሚገርም የቁጥሮች ቀመር ተሳስሯል፦
* 18 ዘፈኖች (Tracks)
* ሚያዝያ 8 ቀን
* 2018 ዓመተ ምህረት
* ከቀኑ 8 ሰዓት
ይህ በስምንት ቁጥር የታጀበ የቁጥሮች ሰልፍ ዝም ብሎ አጋጣሚ አይደለም። ስምንት ቁጥርን በጋድም ስናስቀምጠው የዘላለማዊነት (♾️)ምልክት ነው።
ይህም ቴዲ ስለ ዓድዋ ጀግኖች "ጥቁር ሰው" ብሎ ሲዘፍን ታሪክን ዘላለማዊ እንዳደረገው ሁሉ ይህ አዲስ አልበምም ከታየው ረቂቅ ግራፊክስ ጀምሮ እስከ 18ቱ ዜማዎች ጊዜ የማይሽረውና እንደ ምልክቱ ለዘላለም በልባችን የሚኖር ጥበብ መሆኑን ያበስራል።
ሚያዝያ 8 ጥበብ ከታሪክ ጋር ተጋብታ ዘላለማዊነቷን ለዓለም የምታውጅበት ዕለት ይሆናል!
ላስቀየምናችሁ አፉ በሉን🙏
Case closed
የኢትዮጵያ ሰው "ንብን የነካ ማር አይቀምስም"ይላል።
እኛም ሳናውቅ በቀናነት እና በፍቅር የሰጠነው ሃሳብ የንቦቹን ንጉሥ ነክተን የአድናቂዎቹ ሲገስፁን ነው ነገሩ የገባን!
አልበሙን ለማጀብ በየቀለሙና በየመስመሩ ላይ የተደረገው የግራፊክስ ጥንቃቄም ሆነ የዜማው ብስለት፣ስራው "ጊዜ የማይሽረው" እንዲሆን ታስቦ መሆኑን ከቅርብ ሰው ተደውሎ ተረድተናል።
ታላቁ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ አዲሱን አልበም "ኢዮሪካ" (ETORIKA) ለማቅረብ ጊዜ የወሰደው እንዲሁ በቸልታ ሳይሆን፣ በየዘመኑ የማይጠወልግ እና በትውልድ ዘንድ የሚኖር ጥበብን ለመቅረጽ ነው።
ይህ በልዩ ጥንቃቄ የተቀመረ ምስላዊ ጥበብ (Graphics) በውስጡ የያዛቸው ምልክቶች ራሳቸው ትልቅ የታሪክ ምስጢር አላቸው
የ"ቶ" ፊደልና የአክሱም ሐውልት (ጽዮን)
ጥንታዊ ስልጣኔያችንን እና የሕይወት ትንሳኤን የሚወክሉ ሆነው አልበሙ እንደ ሐውልቱ ጸንቶ የሚኖር መሆኑን ያበስራሉ።
የአፍሪካ ሰዓት ⏱️
የአፍሪካ ምስል ያለበት የእጅ ሰዓት ማሰሪያው የአክሱም ሐውልት ሆኖ መሰራቱ ጊዜና ታሪክ ተሳስረው "የአፍሪካ ሰዓት" መድረሱን ያሳያል።
ባንዲራና ጥለቱ 🟢🟡🔴
አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ጥለቱ የማንነታችንና የነጻነታችን ዘላለማዊ አርማ ሆኖ ሎጎውን አሽቆጥቁጦታል።
ይህ በልዩ ጥንቃቄ የተሰራ ጥበብ ደግሞ ከ1888 ዓ.ም የዓድዋ ድል ታሪክ ጋር በሚገርም የቁጥሮች ቀመር ተሳስሯል፦
* 18 ዘፈኖች (Tracks)
* ሚያዝያ 8 ቀን
* 2018 ዓመተ ምህረት
* ከቀኑ 8 ሰዓት
ይህ በስምንት ቁጥር የታጀበ የቁጥሮች ሰልፍ ዝም ብሎ አጋጣሚ አይደለም። ስምንት ቁጥርን በጋድም ስናስቀምጠው የዘላለማዊነት (♾️)ምልክት ነው።
ይህም ቴዲ ስለ ዓድዋ ጀግኖች "ጥቁር ሰው" ብሎ ሲዘፍን ታሪክን ዘላለማዊ እንዳደረገው ሁሉ ይህ አዲስ አልበምም ከታየው ረቂቅ ግራፊክስ ጀምሮ እስከ 18ቱ ዜማዎች ጊዜ የማይሽረውና እንደ ምልክቱ ለዘላለም በልባችን የሚኖር ጥበብ መሆኑን ያበስራል።
ሚያዝያ 8 ጥበብ ከታሪክ ጋር ተጋብታ ዘላለማዊነቷን ለዓለም የምታውጅበት ዕለት ይሆናል!
ላስቀየምናችሁ አፉ በሉን🙏
Case closed
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በአዲስ አበባ ስታዲየም በዝማሬ አገለገሉ
#fastmereja I የኢፌዴሪ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ታላቅ የወንጌላውያን አማኞች የትንሳኤ በዓል የጸሎትና የዝማሬ ፕሮግራም ላይ በመገኘት በመድረክ ላይ በዝማሬ አገልግሏል።
#fastmereja I የኢፌዴሪ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ታላቅ የወንጌላውያን አማኞች የትንሳኤ በዓል የጸሎትና የዝማሬ ፕሮግራም ላይ በመገኘት በመድረክ ላይ በዝማሬ አገልግሏል።
2 months ago
የትንሳኤ ስጦታ
ዳሽን ቢራ ለ5 አንጋፋ አርቲስቶች ቤት ገንብቶ አስረከበ
#ethiopia | ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት ጥበብን ሲያገለግሉ ለቆዩ 5 አንጋፋ አርቲስቶች አዲስ የገነባላቸውን መኖሪያ ቤቶች በዛሬው ዕለት አስረክቧል።
የአርቲስቶቹ የነበሩ የጭቃ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ፈርሰው በዘመናዊ መልክ የተገነቡ ሲሆን፣ ሙሉ የቤት ቁሳቁስም ተሟልቶላቸዋል።
ተ/ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ማትያስ ጌታቸው እንደገለጹት፣ ፋብሪካው ላለፉት 25 ዓመታት ለማህበራዊ ኃላፊነት ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጓል።
የኮከብ መልቲ ሚዲያና ማስታወቂያ ስራ አስኪያጅ አቶ ልዑል፣ ዳሽን ቢራ ላደረገው ፈጣን ምላሽ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ፋብሪካው "የኢትዮጵያ ኪነጥበብ ባለሙያዎች በጎ አድራጎት ማህበር የክብር አምባሳደር" ሆኖ እንዲሾም መወሰኑን ገልጸዋል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ አንጋፋና ወጣት አርቲስቶች እንዲሁም የዳሽን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ቤቶቹ ለባለቤቶቻቸው ተረክበዋል።
"ጥበብን ማክበር - ታሪክን ማክበር ነው!" 🙏
#getu #dashinbeer #ethiopianartists #philanthropyethiopia #eastergift #addisababa #ethiopia #artcommunity #buildinglives #ዳሽንቢራ #ኪነጥበብ #ትንሳኤ #በጎአድራጎት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ዳሽን ቢራ ለ5 አንጋፋ አርቲስቶች ቤት ገንብቶ አስረከበ
#ethiopia | ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ.ማ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት ጥበብን ሲያገለግሉ ለቆዩ 5 አንጋፋ አርቲስቶች አዲስ የገነባላቸውን መኖሪያ ቤቶች በዛሬው ዕለት አስረክቧል።
የአርቲስቶቹ የነበሩ የጭቃ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ፈርሰው በዘመናዊ መልክ የተገነቡ ሲሆን፣ ሙሉ የቤት ቁሳቁስም ተሟልቶላቸዋል።
ተ/ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ማትያስ ጌታቸው እንደገለጹት፣ ፋብሪካው ላለፉት 25 ዓመታት ለማህበራዊ ኃላፊነት ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጓል።
የኮከብ መልቲ ሚዲያና ማስታወቂያ ስራ አስኪያጅ አቶ ልዑል፣ ዳሽን ቢራ ላደረገው ፈጣን ምላሽ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ፋብሪካው "የኢትዮጵያ ኪነጥበብ ባለሙያዎች በጎ አድራጎት ማህበር የክብር አምባሳደር" ሆኖ እንዲሾም መወሰኑን ገልጸዋል።
በስነ-ስርዓቱ ላይ አንጋፋና ወጣት አርቲስቶች እንዲሁም የዳሽን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ቤቶቹ ለባለቤቶቻቸው ተረክበዋል።
"ጥበብን ማክበር - ታሪክን ማክበር ነው!" 🙏
#getu #dashinbeer #ethiopianartists #philanthropyethiopia #eastergift #addisababa #ethiopia #artcommunity #buildinglives #ዳሽንቢራ #ኪነጥበብ #ትንሳኤ #በጎአድራጎት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ለታዳጊ በእምነት እሱባለው ደራሽ እንሁን! 🙏
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሥር በሚገኘው የአዲስ ሕይወት ትምህርት ቤት የ5ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው በእምነት እሱባለው፣ ባጋጠማት ድንገተኛ የአንጎል ደም ስር መበጠስና የደም መርጋት ምክንያት በከባድ ሕመም ላይ ትገኛለች።
ወላጅ እናቷ ወይዘሮ የዝና አያሌው ሕክምናውን በግላቸው ለመሸፈን ከአቅማቸው በላይ ስለሆነባቸው፣ ለልጃቸው ሕይወት መዳን የእናንተን እርዳታና ጸሎት ይሻሉ።
💰 እርዳታ ለማድረግ፦
የባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000635435325 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
የአካውንቱ ስም፦ የዝና አያሌው (Yezina Ayalew)
ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920515114 (በለካዱ ኤርጋቡስ ለሜሳ)
"ዛሬ ለታዳጊ በእምነት የምናደርገው ጥቂት እርዳታ፣ ነገ ለእሷ ትልቅ ተስፋና ትንሳኤ ይሆናል።"
እባካችሁ ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን። በዓሉ የደስታና የፈውስ ይሁንልን!
#getu #humanitarianaid #helpbeemnet #addisababa #ethiopia #healthappeal #unityforlife #charityethiopia #እርዳታ #ለበእምነትእሱባለው #ኢትዮጵያ #ሰብዓዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ሥር በሚገኘው የአዲስ ሕይወት ትምህርት ቤት የ5ኛ ክፍል ተማሪ የሆነችው በእምነት እሱባለው፣ ባጋጠማት ድንገተኛ የአንጎል ደም ስር መበጠስና የደም መርጋት ምክንያት በከባድ ሕመም ላይ ትገኛለች።
ወላጅ እናቷ ወይዘሮ የዝና አያሌው ሕክምናውን በግላቸው ለመሸፈን ከአቅማቸው በላይ ስለሆነባቸው፣ ለልጃቸው ሕይወት መዳን የእናንተን እርዳታና ጸሎት ይሻሉ።
💰 እርዳታ ለማድረግ፦
የባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000635435325 (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
የአካውንቱ ስም፦ የዝና አያሌው (Yezina Ayalew)
ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920515114 (በለካዱ ኤርጋቡስ ለሜሳ)
"ዛሬ ለታዳጊ በእምነት የምናደርገው ጥቂት እርዳታ፣ ነገ ለእሷ ትልቅ ተስፋና ትንሳኤ ይሆናል።"
እባካችሁ ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን። በዓሉ የደስታና የፈውስ ይሁንልን!
#getu #humanitarianaid #helpbeemnet #addisababa #ethiopia #healthappeal #unityforlife #charityethiopia #እርዳታ #ለበእምነትእሱባለው #ኢትዮጵያ #ሰብዓዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ቤተክርስቲያኗ ለ1600 ወገኖች ማዕድ አጋራች
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ 33 ሰንጋዎችን በመግዛት፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ለአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች፣የቀድሞ ወታደሮች አባላት፣የጎዳና ተዳዳሪዎች፣የቀን ጉርሳቸውን በዕለት ሰርተው የሚያገኙ የቀን ሰራተኞች በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሆኑ የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን መሪ የሆኑት
መጋቢ አመሉ ጌታ ገልጸዋል።
እያንዳንዳችን በበጎ ፈቃዳችን ለድሀዎች በመድረስ እና በማገዝ የድሆች አምባሳደር እንሁን ያሉት ፓስተር አመሉ፣
ቤተክርስቲያኗ በጎፈቃደኛ ግለሰቦችን፣ተቋማትንና አብያተ ክርስቲያን በማስተባበር የማዕድ ማጋራት ስታዘጋጅ 14 ዓመታትን አስቆጥራለች ብለዋል።
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በየወሩ 127 አረጋዊያንን እና 209 ህፃናትን በቋሚነት እየረዳች ነው ያሉት፣መጋቢ አመሉ በየበዓላትም የአልባሳት ስጦታ እንደምትሰጥም ገልጸዋል።
ማዕድ ህብረብሔራዊነታችን ማሳያ ነው ያሉት፣የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ምስክር ነጋሽ በበኩላቸው፣ይህ በጎ ተግባር ዜጎችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ተጠቃሚ ያደረገ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ወገኖች በዓሉን በደስታ ማሳለፍ እንዲችሉ እንዲህ አይነት በጎ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ዋና ስራ አሰፈፃማው ተናግረዋል።
የተማሪዎች ምገባን ጨምሮ ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የገለፁት ዶ/ር ምስክር፣በእህማማችነት እና በወንድማማችነት መኖር አለብንም ብለዋል።
የካናዳ አብያተ ክርስቲያናትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ፓስተር መልኬ፣ይህ በጎ ዓላማ የስጋዊም የመንፈሳዊ ግዴታ ነው።
ያለንን ማካፈልም መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮም እንደሆነ ገልጸዋል።
በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ላይ፣የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የሐይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ 33 ሰንጋዎችን በመግዛት፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ለአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች፣የቀድሞ ወታደሮች አባላት፣የጎዳና ተዳዳሪዎች፣የቀን ጉርሳቸውን በዕለት ሰርተው የሚያገኙ የቀን ሰራተኞች በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሆኑ የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን መሪ የሆኑት
መጋቢ አመሉ ጌታ ገልጸዋል።
እያንዳንዳችን በበጎ ፈቃዳችን ለድሀዎች በመድረስ እና በማገዝ የድሆች አምባሳደር እንሁን ያሉት ፓስተር አመሉ፣
ቤተክርስቲያኗ በጎፈቃደኛ ግለሰቦችን፣ተቋማትንና አብያተ ክርስቲያን በማስተባበር የማዕድ ማጋራት ስታዘጋጅ 14 ዓመታትን አስቆጥራለች ብለዋል።
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በየወሩ 127 አረጋዊያንን እና 209 ህፃናትን በቋሚነት እየረዳች ነው ያሉት፣መጋቢ አመሉ በየበዓላትም የአልባሳት ስጦታ እንደምትሰጥም ገልጸዋል።
ማዕድ ህብረብሔራዊነታችን ማሳያ ነው ያሉት፣የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ምስክር ነጋሽ በበኩላቸው፣ይህ በጎ ተግባር ዜጎችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ተጠቃሚ ያደረገ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ወገኖች በዓሉን በደስታ ማሳለፍ እንዲችሉ እንዲህ አይነት በጎ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ዋና ስራ አሰፈፃማው ተናግረዋል።
የተማሪዎች ምገባን ጨምሮ ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የገለፁት ዶ/ር ምስክር፣በእህማማችነት እና በወንድማማችነት መኖር አለብንም ብለዋል።
የካናዳ አብያተ ክርስቲያናትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ፓስተር መልኬ፣ይህ በጎ ዓላማ የስጋዊም የመንፈሳዊ ግዴታ ነው።
ያለንን ማካፈልም መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮም እንደሆነ ገልጸዋል።
በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ላይ፣የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የሐይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ቤተክርስቲያኗ ለ1600 ወገኖች ማዕድ አጋራች
#ethiopia | የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ 33 ሰንጋዎችን በመግዛት፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ለአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች፣የቀድሞ ወታደሮች አባላት፣የጎዳና ተዳዳሪዎች፣የቀን ጉርሳቸውን በዕለት ሰርተው የሚያገኙ የቀን ሰራተኞች በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሆኑ የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን መሪ የሆኑት መጋቢ አመሉ ጌታ ገልጸዋል።
እያንዳንዳችን በበጎ ፈቃዳችን ለድሀዎች በመድረስ እና በማገዝ የድሆች አምባሳደር እንሁን ያሉት ፓስተር አመሉ፣ ቤተክርስቲያኗ በጎፈቃደኛ ግለሰቦችን ፣ ተቋማትንና አብያተ ክርስቲያን በማስተባበር የማዕድ ማጋራት ስታዘጋጅ 14 ዓመታትን አስቆጥራለች ብለዋል።
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በየወሩ 127 አረጋዊያንን እና 209 ህፃናትን በቋሚነት እየረዳች ነው ያሉት፣መጋቢ አመሉ በየበዓላትም የአልባሳት ስጦታ እንደምትሰጥም ገልጸዋል።
ማዕድ ህብረብሔራዊነታችን ማሳያ ነው ያሉት፣ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ምስክር ነጋሽ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ይህ በጎ ተግባር ዜጎችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ተጠቃሚ ያደረገ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ወገኖች በዓሉን በደስታ ማሳለፍ እንዲችሉ እንዲህ አይነት በጎ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ዋና ስራ አሰፈፃማው ተናግረዋል።
የተማሪዎች ምገባን ጨምሮ ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የገለፁት ዶ/ር ምስክር፣በእህማማችነት እና በወንድማማችነት መኖር አለብንም ብለዋል።
የካናዳ አብያተ ክርስቲያናትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ፓስተር መልኬ፣ይህ በጎ ዓላማ የስጋዊም የመንፈሳዊ ግዴታ ነው።
ያለንን ማካፈልም መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮም እንደሆነ ገልጸዋል። በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ላይ፣የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የሐይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ 33 ሰንጋዎችን በመግዛት፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች፣ለአረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች፣የቀድሞ ወታደሮች አባላት፣የጎዳና ተዳዳሪዎች፣የቀን ጉርሳቸውን በዕለት ሰርተው የሚያገኙ የቀን ሰራተኞች በማዕድ ማጋራት ፕሮግራሙ ተጠቃሚ እንደሆኑ የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን መሪ የሆኑት መጋቢ አመሉ ጌታ ገልጸዋል።
እያንዳንዳችን በበጎ ፈቃዳችን ለድሀዎች በመድረስ እና በማገዝ የድሆች አምባሳደር እንሁን ያሉት ፓስተር አመሉ፣ ቤተክርስቲያኗ በጎፈቃደኛ ግለሰቦችን ፣ ተቋማትንና አብያተ ክርስቲያን በማስተባበር የማዕድ ማጋራት ስታዘጋጅ 14 ዓመታትን አስቆጥራለች ብለዋል።
የቦሌ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን በየወሩ 127 አረጋዊያንን እና 209 ህፃናትን በቋሚነት እየረዳች ነው ያሉት፣መጋቢ አመሉ በየበዓላትም የአልባሳት ስጦታ እንደምትሰጥም ገልጸዋል።
ማዕድ ህብረብሔራዊነታችን ማሳያ ነው ያሉት፣ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ምስክር ነጋሽ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ይህ በጎ ተግባር ዜጎችን በኢኮኖሚና በማህበራዊ ተጠቃሚ ያደረገ ስለመሆኑ አስረድተዋል።
ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ወገኖች በዓሉን በደስታ ማሳለፍ እንዲችሉ እንዲህ አይነት በጎ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም ዋና ስራ አሰፈፃማው ተናግረዋል።
የተማሪዎች ምገባን ጨምሮ ሰው ተኮር ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የገለፁት ዶ/ር ምስክር፣በእህማማችነት እና በወንድማማችነት መኖር አለብንም ብለዋል።
የካናዳ አብያተ ክርስቲያናትን ወክለው ንግግር ያደረጉት ፓስተር መልኬ፣ይህ በጎ ዓላማ የስጋዊም የመንፈሳዊ ግዴታ ነው።
ያለንን ማካፈልም መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮም እንደሆነ ገልጸዋል። በማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩ ላይ፣የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣የሐይማኖት አባቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
ድምጻዊ ያሬድ ነጉ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ
#fastmereja I ታዋቂው ድምጻዊ ያሬድ ነጉ መለሰ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አጋርቷል።
ድምጻዊው ባስተላለፈው መልዕክት በዓሉ የሰላም እንዲሆን ከመመኘት ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስስ ሃሳብ አንስቷል። "በሀገራችን የእናቶች እንባ በዛ" ያለው ያሬድ፣ በግፍ እየሞቱ ላሉ ወገኖች "በቃ" የሚባልበት እና ለቅሶ የሚያበቃበት ትንሳኤ እንዲሆን ያለውን መልካም ምኞት ገልጿል።
ያሬድ ነጉ በመልዕክቱ ማጠቃለያ ላይ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝቷል።
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
#fastmereja I ታዋቂው ድምጻዊ ያሬድ ነጉ መለሰ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አጋርቷል።
ድምጻዊው ባስተላለፈው መልዕክት በዓሉ የሰላም እንዲሆን ከመመኘት ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ የሚዳስስ ሃሳብ አንስቷል። "በሀገራችን የእናቶች እንባ በዛ" ያለው ያሬድ፣ በግፍ እየሞቱ ላሉ ወገኖች "በቃ" የሚባልበት እና ለቅሶ የሚያበቃበት ትንሳኤ እንዲሆን ያለውን መልካም ምኞት ገልጿል።
ያሬድ ነጉ በመልዕክቱ ማጠቃለያ ላይ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝቷል።
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
2 months ago
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች የትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
#fastmereja I የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል በማስመልክት ለሀገሪቱ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችና በዓሉን ለሚያከብሩ ሩሲያውያን በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው፣ የትንሳኤ በዓል በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሰዎች ልብ ውስጥ የእውነተኛ ደስታ፣ የህይወት ድል፣ የፍቅር፣ የደግነት እና የፍትህ ተስፋን የሚሞላ ታላቅ በዓል መሆኑን ገልጸዋል። የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና ሌሎች የክርስትና እምነት ተከታዮች የሀገሪቱን ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች በመጠበቅ፣ የቤተሰብ ተቋምን በማጠናከር እና ወጣቱን ትውልድ በማነጽ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አክለዋል።
በተጨማሪም የሃይማኖት ድርጅቶች ከመንግስት ጋር የሚያደርጉት ገንቢ ትብብር፣ የሃይማኖቶች እና የብሄረሰቦች ውይይት እንዲጠናከር የሚያደርጉት ጥረት እንዲሁም "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ለሚሳተፉ ወታደሮችና ለቤተሰቦቻቸው የሚያደርጉት ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን ፕሬዝዳንት ፑቲን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ በመጨረሻም ለህዝባቸው ጤና እና ብልጽግናን ተመኝተዋል።
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
#fastmereja I የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል በማስመልክት ለሀገሪቱ የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችና በዓሉን ለሚያከብሩ ሩሲያውያን በሙሉ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው፣ የትንሳኤ በዓል በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሰዎች ልብ ውስጥ የእውነተኛ ደስታ፣ የህይወት ድል፣ የፍቅር፣ የደግነት እና የፍትህ ተስፋን የሚሞላ ታላቅ በዓል መሆኑን ገልጸዋል። የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እና ሌሎች የክርስትና እምነት ተከታዮች የሀገሪቱን ታሪካዊ እና ባህላዊ ቅርሶች በመጠበቅ፣ የቤተሰብ ተቋምን በማጠናከር እና ወጣቱን ትውልድ በማነጽ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አክለዋል።
በተጨማሪም የሃይማኖት ድርጅቶች ከመንግስት ጋር የሚያደርጉት ገንቢ ትብብር፣ የሃይማኖቶች እና የብሄረሰቦች ውይይት እንዲጠናከር የሚያደርጉት ጥረት እንዲሁም "ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ለሚሳተፉ ወታደሮችና ለቤተሰቦቻቸው የሚያደርጉት ድጋፍ የሚደነቅ መሆኑን ፕሬዝዳንት ፑቲን በመልዕክታቸው ጠቁመዋል። ፕሬዝዳንቱ በመጨረሻም ለህዝባቸው ጤና እና ብልጽግናን ተመኝተዋል።
ሚያዝያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
2 months ago
እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ? እነሆ እደተናገረ ተነስቷል
“እነሆም የጌታ መልአክ ከሰማይ ወረደ፣ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፣ እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና። እንደ ተናገረው ተነስቷልና በዚህ የለም ኑና እዩ አላቸው።” ይለናል ማቴዎስ 28÷5። ስለ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድመው ነቢያት ተናግረዋል። ስለ ጌታችን ትንሣኤ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ጌታችን ራሱ በትምህርቱ ግልጽ አድርጎ ቢናገርም ሰዱቃውያንና ሌሎች ብዙ ሰዎች ለማመን ያዳግታቸው ነበር። አራቱ ወንጌላውያን፣ በማቴ 28፣ በማር 16፣ በሉቃ 24 እና በዮሐ 20 እንዲሁም ቅዱሳን ሐዋርያት በስብከታቸውና በመጽሐፋቸው ስለ ትንሣኤው ምስክርነት በመስጠት አረጋግጠው አስፍተውና አምልተው አስተምረዋል፤ ጽፈዋል።
ከሐዋርያትም መካከል የሆነው ቅዱስ ቶማስ እንኳ ጌታችን በዝግ ቤት ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ የተወጋውን ጎኑን አሳይቶ በክብር መነሣቱን እስከሚያረጋግጥለት ድረስ የጌታችንን ትንሣኤ ለማመን እንደተቸገረ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። በተጨማሪም የጌታን ትንሣኤና ትንሣኤ ሙታንን በአጠቃላይ ለመቀበል የተቸገሩ ብዙዎች እንደነበሩ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን። ክርስቶስ ስለትንሣኤው በዮሐንስ 2÷19 በምሳሌ ሲናገር “ይህንንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ” ብሎ የተናገረውን ሐዋርያቱ የተረዱትና ያመኑት ከትንሣኤው በኋላ ነበር። በ2ኛ ጢሞ 3÷14 ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ለጢሞቴዎስ “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርከው ታውቃለህና።” ሲል እንደጻፈለት እኛም ከማን እንደተማርነው እናውቃለንና የጌታን ትንሣኤ በፍጹም ልብ አምነን ለራሳችን ትንሣኤ እንዘጋጃለን።
ጌታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ለሰው ልጅ ድህነት ሲል ጽኑ መከራና ስቃይን ተቀብሏል። አይሁድ ከያዙት በኋላም ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የሆነ ስቃይ፣ መከራ፣ እንግልትና ግርፋትን ተቀብሎ፤ በቀራንዮ አደባባይ በዕለተ አርብ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ፤ ነፍሱን በፈቃዱ ሰጠ፡፡ አዳምንና ዘሩንም ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መለሳቸው፡፡ በ3ኛው ቀን መቃብር ክፈቱልኝ፣ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ስልጣን በክብር ተነስቷል። መላዕክቱም ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ እነሆ እደተናገረ ተነስቷል ብለው መስክረዋል፡፡ ገዳማውያን በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ለተነሳው ጌታ ፍቅር ዓለምን ትተዋታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ? እነሆ እደተናገረ ተነስቷል
“እነሆም የጌታ መልአክ ከሰማይ ወረደ፣ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፣ እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና። እንደ ተናገረው ተነስቷልና በዚህ የለም ኑና እዩ አላቸው።” ይለናል ማቴዎስ 28÷5። ስለ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድመው ነቢያት ተናግረዋል። ስለ ጌታችን ትንሣኤ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ጌታችን ራሱ በትምህርቱ ግልጽ አድርጎ ቢናገርም ሰዱቃውያንና ሌሎች ብዙ ሰዎች ለማመን ያዳግታቸው ነበር። አራቱ ወንጌላውያን፣ በማቴ 28፣ በማር 16፣ በሉቃ 24 እና በዮሐ 20 እንዲሁም ቅዱሳን ሐዋርያት በስብከታቸውና በመጽሐፋቸው ስለ ትንሣኤው ምስክርነት በመስጠት አረጋግጠው አስፍተውና አምልተው አስተምረዋል፤ ጽፈዋል።
ከሐዋርያትም መካከል የሆነው ቅዱስ ቶማስ እንኳ ጌታችን በዝግ ቤት ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ የተወጋውን ጎኑን አሳይቶ በክብር መነሣቱን እስከሚያረጋግጥለት ድረስ የጌታችንን ትንሣኤ ለማመን እንደተቸገረ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። በተጨማሪም የጌታን ትንሣኤና ትንሣኤ ሙታንን በአጠቃላይ ለመቀበል የተቸገሩ ብዙዎች እንደነበሩ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን። ክርስቶስ ስለትንሣኤው በዮሐንስ 2÷19 በምሳሌ ሲናገር “ይህንንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ” ብሎ የተናገረውን ሐዋርያቱ የተረዱትና ያመኑት ከትንሣኤው በኋላ ነበር። በ2ኛ ጢሞ 3÷14 ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ለጢሞቴዎስ “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርከው ታውቃለህና።” ሲል እንደጻፈለት እኛም ከማን እንደተማርነው እናውቃለንና የጌታን ትንሣኤ በፍጹም ልብ አምነን ለራሳችን ትንሣኤ እንዘጋጃለን።
ጌታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ለሰው ልጅ ድህነት ሲል ጽኑ መከራና ስቃይን ተቀብሏል። አይሁድ ከያዙት በኋላም ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የሆነ ስቃይ፣ መከራ፣ እንግልትና ግርፋትን ተቀብሎ፤ በቀራንዮ አደባባይ በዕለተ አርብ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ፤ ነፍሱን በፈቃዱ ሰጠ፡፡ አዳምንና ዘሩንም ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መለሳቸው፡፡ በ3ኛው ቀን መቃብር ክፈቱልኝ፣ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ስልጣን በክብር ተነስቷል። መላዕክቱም ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ እነሆ እደተናገረ ተነስቷል ብለው መስክረዋል፡፡ ገዳማውያን በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ለተነሳው ጌታ ፍቅር ዓለምን ትተዋታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 months ago
ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ...
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ የትንሣኤን በዓል ስናከብር ለችግር የተዳረጉ ወገኖችን በማገዝ ቀኑ ለሁላችንም ፍፁም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን አይደለም ብለዋል፡፡
የሞቱና የትንሣኤውን ምስጢር በንጹህ ህሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው ነገር አይኖርም ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ሁላችንም በፈጣሪ መልካም መንገድ ልንጓዝ ይገባል ሲሉም አባታዊ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ ካለው በማካፈል የተራቡትን በማብላት፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ የትንሣኤን በዓል ስናከብር ለችግር የተዳረጉ ወገኖችን በማገዝ ቀኑ ለሁላችንም ፍፁም ብርሃን ሆኖ ይውል ዘንድ ክርስቲያናዊ ግዴታችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ሲያበስረን የትንሣኤ ሰዎች ሆነን በመንፈስና በሞራል በማደግ ብርሃናተ ዓለም ልንሆን እንጂ እንደገና የጨለማው ኃይል መሳሪያዎች ልንሆን አይደለም ብለዋል፡፡
የሞቱና የትንሣኤውን ምስጢር በንጹህ ህሊናችን ካስተዋልነው ውስጣችን እሱን ለመቀበል የሚያዳግተው ነገር አይኖርም ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ሁላችንም በፈጣሪ መልካም መንገድ ልንጓዝ ይገባል ሲሉም አባታዊ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ ካለው በማካፈል የተራቡትን በማብላት፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስና የዕለቱ ደስታ ተካፋይ እንዲሆኑ በማድረግ ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በአዲስ አበባ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የዘጠኝ ዙር መድፍ ተኩስ እንደሚከናወን ተገለጸ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ከለሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ ዘጠኝ ጊዜ የመድፍ ተኩስ እንደሚከናወን አስታውቋል።
በመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ስራዎች ማዕከል በኩል የወጣው ይሄው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የተኩስ ስነ-ስርዓቱ የተለመደውን የበዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ተከትሎ የሚከናወን ነው።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በበኩሉ ህብረተሰቡ ስለ መድፍ ተኩሱ አስቀድሞ ተገቢው መረጃ እንዲኖረው ያሳሰበ ሲሆን፣ ነዋሪዎች ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ የሚሰማውን ድምፅ በበዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ምክንያት የሚከናወን መሆኑን አውቆ ያለምንም ስጋትና መደናገጥ በዓሉን እንዲያከብር ጥሪውን አቅርቧል።
ፖሊስ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችም መልካም የበዓል ምኞቱን ገልጿል።
seledadotio
seledadotio
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ከለሊቱ 9፡00 ሰዓት ላይ ዘጠኝ ጊዜ የመድፍ ተኩስ እንደሚከናወን አስታውቋል።
በመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ስራዎች ማዕከል በኩል የወጣው ይሄው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የተኩስ ስነ-ስርዓቱ የተለመደውን የበዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ተከትሎ የሚከናወን ነው።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በበኩሉ ህብረተሰቡ ስለ መድፍ ተኩሱ አስቀድሞ ተገቢው መረጃ እንዲኖረው ያሳሰበ ሲሆን፣ ነዋሪዎች ከለሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ የሚሰማውን ድምፅ በበዓል አከባበር ስነ-ስርዓት ምክንያት የሚከናወን መሆኑን አውቆ ያለምንም ስጋትና መደናገጥ በዓሉን እንዲያከብር ጥሪውን አቅርቧል።
ፖሊስ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችም መልካም የበዓል ምኞቱን ገልጿል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
የልማት አርበኛዋ ወ/ሮ አልማዝ ሻንቆ ለ40 አባወራዎች የትንሳኤ ማዕድ አጋሩ
#fastmereja I ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም
የልማት አርበኛዋ ወ/ሮ አልማዝ ሻንቆ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ለሚገኙ አቅመ ደካሞችና አረጋውያን የ116 ሺህ ብር የሰንጋ በሬ እና የዱቄት ድጋፍ አደረጉ።
በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ኤልጎ ሉዳ ቀበሌ ዛሬ በተከናወነው በዚህ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ላይ 40 አባወራዎች የቅርጫ ስጋ ተጠቃሚ ሆነዋል። ወ/ሮ አልማዝ ከቅርጫ ስጋው በተጨማሪ ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 10 ኪሎ ግራም የፉርኖ ዱቄት አበርክተዋል።
ተጠቃሚዎቹ በሰጡት አስተያየት ድጋፉ በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ ትልቅ አቅም እንደሆናቸው ገልጸው፣ ለወ/ሮ አልማዝ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።
#fastmereja I ሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም
የልማት አርበኛዋ ወ/ሮ አልማዝ ሻንቆ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ለሚገኙ አቅመ ደካሞችና አረጋውያን የ116 ሺህ ብር የሰንጋ በሬ እና የዱቄት ድጋፍ አደረጉ።
በአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ኤልጎ ሉዳ ቀበሌ ዛሬ በተከናወነው በዚህ የማዕድ ማጋራት መርሃ ግብር ላይ 40 አባወራዎች የቅርጫ ስጋ ተጠቃሚ ሆነዋል። ወ/ሮ አልማዝ ከቅርጫ ስጋው በተጨማሪ ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 10 ኪሎ ግራም የፉርኖ ዱቄት አበርክተዋል።
ተጠቃሚዎቹ በሰጡት አስተያየት ድጋፉ በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ ትልቅ አቅም እንደሆናቸው ገልጸው፣ ለወ/ሮ አልማዝ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል።