Logo
SeledaPost
በ110 ሺህ ብር በተገዛ ሰንጋ በሬ ውስጥ ከ10 ግራም በላይ የወርቅ ክምችት ተገኘ

የትንሳኤ በዓል በቃሊቲ የመኖሪያ ካምፕ ለሚገኙ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ያልተጠበቀ ነገር አጋጥሟቸዋል።

አባላቱ ለበዓል ቅርጫ ካረዱት ሰንጋ በሬ ሀሞት ውስጥ ከ10 ግራም በላይ የሚመዝን ወርቅ ማግኘታቸውን የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን አስታውቋል።

የፖሊስ አባላቱ እንደሚናገሩት፣ በዘንድሮው በዓል የከብት ዋጋ በመወደዱ ምክንያት ይህንን ሰንጋ በሬ ለመግዛት ብዙ ድካምና እንግልት አሳልፈዋል።በመጨረሻም በ110 ሺህ ብር የገዙት ሰንጋ፣ ለበዓሉ ድግስ ብቻ ሳይሆን ያልተጠበቀ ወርቅ ይዞላቸው እንደሚመጣ አልገመቱም ነበር።

በአሁኑ ሰዓት የፖሊስ አባላቱ የተገኘውን ወርቅ ለመሸጥ ከወርቅ ተረካቢዎች ጋር የዋጋ ድርድር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል።

Via የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን

seledadotio
seledadotio
2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.