1 day ago
ከሥርዓት ጥበቃ ወደ ዜጎች ደኅንነት፦ የፀጥታ ተቋማቱ ጥልቅ ሪፎርም
************************
የዓለማችን የፀጥታና ደኅንነት ስጋቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ውስብስብ እና ተለዋዋጭ እየሆኑ መጥተዋል። በዚህም ከባህላዊ ጦርነቶች ባሻገር ከሳይበር ጥቃት እስከ ሐሰተኛ መረጃዎች ሥርጭት ድረስ እጅግ ልዩ ባህርይ የተላበሱ ጉዳዮች በመከሰት ላይ ይገኛሉ።
ለዚህም የአሁኑ ትውልድ ጊዜውን የዋጀ፣ ውስብስብ ፈተናዎችን መመከት የሚያስችል ሁለንተናዊ ዕውቀት፣ ብቃትና ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቀ አይበገሬ ተቋም የመገንባት ኃላፊነት ከትከሻው ላይ ወድቋል።
በሀገራችን ነባራዊ ዳራ ደግሞ፣ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት የረጅም ዘመን የፖለቲካ ስብራታችን ዋነኛ ማሳያ ሆነው ቆይተዋል።
ከሪፎርሙ በፊት ተቋማት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ሕዝባዊ ሆነው ከመገንባት ይልቅ፣ ውስን ርዕዮተ ዓለምን ወይም የጥቅም ቡድንን ለማስጠበቅ የቆሙ ነበሩ። በዚህም ምክንያት ሥርዓቱን ለመጠበቅ ሲሉ ለዜጎች ሰብዓዊ መብት ጥሰት መባባስ ዋነኛ መሣሪያ በመሆን አገልግለዋል።
ተቋማቱን ከፖለቲካ ወገንተኝነት በማላቀቅ “ሀገር አስቀጥል” ተቋማት እንዲሆኑ ሙያዊ ነፃነታቸውን በማረጋገጥ በዘመናዊና አስተማማኝ መሠረት ላይ ለመገንባት እንደ ሀገር የተጀመረው ሪፎርም ወቅቱ የሚጠይቀው ቁልፍ ተግባር ሆኖ ተገኝቷል።
የሪፎርሙ ውጣ ውረድ እና ጉዞ
ይህ ጥልቅ የለውጥ ጉዞ ፈፅሞ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ለዘመናት በአምባገነን ሥርዓቶችና በኋላቀር እሳቤ ተተብትበው የኖሩት ተቋማት፣ እንኳን የፖለቲካ ሥርዓቱን መቀየር ቀርቶ ራሳቸው ጥልቅ ስብራት የነበረባቸው በመሆኑ፣ ሪፎርሙን ከውስጥ መጀመር ግዴታ ነበር።
በሌላ በኩል በተለያዩ አካባቢዎች የነበሩ በኢትዮጵያ ጠላቶች የተጠነሰሱ ግጭቶች እና የጽንፈኝነት እንቅስቃሴዎችን እየመከቱ፣ ኢትዮጵያን እያስቀጠሉ፣ ጎን ለጎን ራሳቸው በጥልቅ ሪፎርም ውስጥ የማለፍ ፈተናን ተሻግረዋል።
ይሁንና የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እነዚህን እንቅፋቶችና ፈተናዎች ወደ ዕድል በመቀየር ተቋማቱን ከስብራት አውጥቶ ወደ ዘላቂ የሰላም አስከባሪነት አሸጋግረዋቸዋል።
ከየት ወደየት? እይታ እና ተልዕኮ
በሪፎርሙ ሂደት ተቋሞቻችን ኢትዮጵያን በብቃት ማስቀጠል ችለዋል፦
• ተቋማቱ ከርዕዮተ ዓለም ጠባቂነት ሙሉ በሙሉ ተላቅቀው፣ የኢትዮጵያ እና የዜጎቿ የጋራ ደኅንነትና ክብር ዘብ ወደመሆን ተሸጋግረዋል።
• ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በመሆን፣ ሕገ መንግሥቱን ብቻ መሠረት አድርገው ሕዝብን በገለልተኝነት የሚያገለግሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
• የሪፎርሙ ርዕይ በሕዝብ አመኔታ የተገነባ፣ ለሀገር ውስጥና ለቀጣናዊ ስጋቶች የማይበገር ተወዳዳሪ ተቋም መፍጠር አስችሏል።
• በተልዕኮውም የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣ የሀገርን ድንበር ማስከበርና፣ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ከአፍራሽ እንቅስቃሴዎች አጥብቆ መከላከል ተችሏል።
የሪፎርሙ የትግበራ አግባብነት የሚለካው የሰው ኃይልን በአዲስ የሙያ ሥነ ምግባር በማነፅ እንዲሁም ግልጽነትና ተጠያቂነትን በሚያሰፍን የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት ነው። ሪፎርሙ የፀጥታ መዋቅሩ ሠፊ ሕዝባዊ መሰረት እንዲኖረው ያደረገ አካታች አሠራርንም ዘርግቷል።
ዘመናዊ ጋሻ ለመሆን ቴክኖሎጂ ወሳኝ በመሆኑም ተከታታይ እርምጃዎች ተወስደዋል።
• ሰብዓዊ፣ መዋቅራዊና ቴክኖሎጂያዊ ብቃት ያላቸው የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት ተፈጥረዋል።
• የመከላከያ ቴክኖሎጂዎችን በሀገር ውስጥ በማላመድና በመፍጠር፣ ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ትጥቆችን የማሟላት ስኬት ተመዝግቧል።
• አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን፣ የቢግ ዳታ ጥልቅ ትንታኔንና የሳይበር ደኅንነትን በመጠቀም፣ ወንጀልን ከመፈፀሙ በፊት የመተንበይና የማክሸፍ የላቀ አቅም ተገንብቷል።
በአጠቃላይ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ስኬታማ ሪፎርም የትናንቱን የመዋቅር ክፍተት በመጠገን፣ ኢትዮጵያን ከነባር ጠላቶች በአስተማማኝ ሁኔታ መከላከል የሚችል አቅም መፍጠር ተችሏል።
ዘመኑን የዋጀው ይህ ጋሻ የዜጎችን መብት የሚያስከብርና የሀገር ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ የማዕዘን ድንጋይ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #fdredefenseforce #ethiopianfederalpolice #ethiopianairforce #ebc
************************
የዓለማችን የፀጥታና ደኅንነት ስጋቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ውስብስብ እና ተለዋዋጭ እየሆኑ መጥተዋል። በዚህም ከባህላዊ ጦርነቶች ባሻገር ከሳይበር ጥቃት እስከ ሐሰተኛ መረጃዎች ሥርጭት ድረስ እጅግ ልዩ ባህርይ የተላበሱ ጉዳዮች በመከሰት ላይ ይገኛሉ።
ለዚህም የአሁኑ ትውልድ ጊዜውን የዋጀ፣ ውስብስብ ፈተናዎችን መመከት የሚያስችል ሁለንተናዊ ዕውቀት፣ ብቃትና ዘመናዊ ትጥቅ የታጠቀ አይበገሬ ተቋም የመገንባት ኃላፊነት ከትከሻው ላይ ወድቋል።
በሀገራችን ነባራዊ ዳራ ደግሞ፣ የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት የረጅም ዘመን የፖለቲካ ስብራታችን ዋነኛ ማሳያ ሆነው ቆይተዋል።
ከሪፎርሙ በፊት ተቋማት ነፃ፣ ገለልተኛ እና ሕዝባዊ ሆነው ከመገንባት ይልቅ፣ ውስን ርዕዮተ ዓለምን ወይም የጥቅም ቡድንን ለማስጠበቅ የቆሙ ነበሩ። በዚህም ምክንያት ሥርዓቱን ለመጠበቅ ሲሉ ለዜጎች ሰብዓዊ መብት ጥሰት መባባስ ዋነኛ መሣሪያ በመሆን አገልግለዋል።
ተቋማቱን ከፖለቲካ ወገንተኝነት በማላቀቅ “ሀገር አስቀጥል” ተቋማት እንዲሆኑ ሙያዊ ነፃነታቸውን በማረጋገጥ በዘመናዊና አስተማማኝ መሠረት ላይ ለመገንባት እንደ ሀገር የተጀመረው ሪፎርም ወቅቱ የሚጠይቀው ቁልፍ ተግባር ሆኖ ተገኝቷል።
የሪፎርሙ ውጣ ውረድ እና ጉዞ
ይህ ጥልቅ የለውጥ ጉዞ ፈፅሞ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ለዘመናት በአምባገነን ሥርዓቶችና በኋላቀር እሳቤ ተተብትበው የኖሩት ተቋማት፣ እንኳን የፖለቲካ ሥርዓቱን መቀየር ቀርቶ ራሳቸው ጥልቅ ስብራት የነበረባቸው በመሆኑ፣ ሪፎርሙን ከውስጥ መጀመር ግዴታ ነበር።
በሌላ በኩል በተለያዩ አካባቢዎች የነበሩ በኢትዮጵያ ጠላቶች የተጠነሰሱ ግጭቶች እና የጽንፈኝነት እንቅስቃሴዎችን እየመከቱ፣ ኢትዮጵያን እያስቀጠሉ፣ ጎን ለጎን ራሳቸው በጥልቅ ሪፎርም ውስጥ የማለፍ ፈተናን ተሻግረዋል።
ይሁንና የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች እነዚህን እንቅፋቶችና ፈተናዎች ወደ ዕድል በመቀየር ተቋማቱን ከስብራት አውጥቶ ወደ ዘላቂ የሰላም አስከባሪነት አሸጋግረዋቸዋል።
ከየት ወደየት? እይታ እና ተልዕኮ
በሪፎርሙ ሂደት ተቋሞቻችን ኢትዮጵያን በብቃት ማስቀጠል ችለዋል፦
• ተቋማቱ ከርዕዮተ ዓለም ጠባቂነት ሙሉ በሙሉ ተላቅቀው፣ የኢትዮጵያ እና የዜጎቿ የጋራ ደኅንነትና ክብር ዘብ ወደመሆን ተሸጋግረዋል።
• ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በመሆን፣ ሕገ መንግሥቱን ብቻ መሠረት አድርገው ሕዝብን በገለልተኝነት የሚያገለግሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
• የሪፎርሙ ርዕይ በሕዝብ አመኔታ የተገነባ፣ ለሀገር ውስጥና ለቀጣናዊ ስጋቶች የማይበገር ተወዳዳሪ ተቋም መፍጠር አስችሏል።
• በተልዕኮውም የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ፣ የሀገርን ድንበር ማስከበርና፣ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን ከአፍራሽ እንቅስቃሴዎች አጥብቆ መከላከል ተችሏል።
የሪፎርሙ የትግበራ አግባብነት የሚለካው የሰው ኃይልን በአዲስ የሙያ ሥነ ምግባር በማነፅ እንዲሁም ግልጽነትና ተጠያቂነትን በሚያሰፍን የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ በማስገባት ነው። ሪፎርሙ የፀጥታ መዋቅሩ ሠፊ ሕዝባዊ መሰረት እንዲኖረው ያደረገ አካታች አሠራርንም ዘርግቷል።
ዘመናዊ ጋሻ ለመሆን ቴክኖሎጂ ወሳኝ በመሆኑም ተከታታይ እርምጃዎች ተወስደዋል።
• ሰብዓዊ፣ መዋቅራዊና ቴክኖሎጂያዊ ብቃት ያላቸው የጸጥታና ደኅንነት ተቋማት ተፈጥረዋል።
• የመከላከያ ቴክኖሎጂዎችን በሀገር ውስጥ በማላመድና በመፍጠር፣ ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ትጥቆችን የማሟላት ስኬት ተመዝግቧል።
• አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን፣ የቢግ ዳታ ጥልቅ ትንታኔንና የሳይበር ደኅንነትን በመጠቀም፣ ወንጀልን ከመፈፀሙ በፊት የመተንበይና የማክሸፍ የላቀ አቅም ተገንብቷል።
በአጠቃላይ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ስኬታማ ሪፎርም የትናንቱን የመዋቅር ክፍተት በመጠገን፣ ኢትዮጵያን ከነባር ጠላቶች በአስተማማኝ ሁኔታ መከላከል የሚችል አቅም መፍጠር ተችሏል።
ዘመኑን የዋጀው ይህ ጋሻ የዜጎችን መብት የሚያስከብርና የሀገር ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ የማዕዘን ድንጋይ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #fdredefenseforce #ethiopianfederalpolice #ethiopianairforce #ebc
4 days ago
የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ጋር የሐዋሳን ከተማ ልማት ፕሮጀክት ለማፋጠን ያለመ ስትራቴጂካዊ ውይይት አደረጉ!
በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራው የኩባንያችን ከፍተኛ ማኔጅመንት ቡድን፣ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ከከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በከተማዋ እያስመዘገበችው የሚገኘውን ፈጣን የዲጂታል ዕድገት እንዲሁም የመጻኢ የቴክኖሎጂ ትስስርን ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ኩባንያችን እያከናወናቸው የሚገኙ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን በማድነቅ፤ በተለይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም እያበረከተ ለሚገኘው ቁልፍ ሚና እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ክቡር ከንቲባው ቀደም ሲል በከተማዋ ለተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ኩባንያችን ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ሐዋሳ ከአዲስ አበባ በመቀጠል ዋነኛ የቱሪዝም እና የኮንፈረንስ መዳረሻ እንድትሆን ለማስቻል ያለመ አዲስ የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ውጥን ይፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በመካሄድ ላይ ያለውን የ"ስማርት ሲቲ" ፕሮጀክት እና የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ለማፋጠን የኢትዮ ቴሌኮም ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረው ጠይቀዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ ኩባንያችን መሰል የከተማ ልማት ውጥኖችን ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አረጋግጠዋል። ሐዋሳ በፋይበር መሰረተ ልማት እንዲሁም በ4ጂ እና በ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ የታጠቀች ከተማ መሆኗን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት አስተማማኝ የሆነ የኔትወርክ ሽፋን እና ጥራትን ማሳደግ ታሳቢ ያደረግ መጠነ ሰፊ የማስፋፋት እና የማዘመን ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ በመካሄድ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂና በቴሌብር በማዘመን፣ የሥራ ቅልጥፍናንና የገቢ አሰባሰብን ማሳደግ እንደሚቻል ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ገልጸዋል። በተመሳሳይ፣ በዘመን ገበያ አማካኝነት ለነጋዴዎች የገበያ ትስስርን በማስፋፋት ረገድ ሰፊ የዲጂታላይዜሽን ዕድሎችና የሥራ ፈጠራ አጋጣሚዎች መኖራቸውን አስገንዝበዋል።
ሐዋሳን ንፁህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በዲጂታል የታገዘ የሕዝብ መዳረሻ ለማድረግ እንዲሁም የተቀናጀ የዲጂታል ሥነ-ምህዳርን ለመፍጠር ያለመ ሰፊ ስትራቴጂካዊ ውይይት ተደርጓል። በዚሁ መሠረት የኩባንያችንን አቅም በመጠቀም የሐዋሳ "ስማርት ሲቲ" ልማትን ለማፋጠን፣ የቴሌብር አገልግሎቶችን በሙሉ አቅም ማቀናጀት፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ፣ የትራፊክ እና የሞቢሊቲ መፍትሔዎች፣ የመሠረተ ልማት ጥበቃ እንዲሁም የኔትወርክ ዝርጋታን የሚያቀላጥፉ የኮሪደር ልማት ትብብሮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በመጨረሻም፣ የኩባንያችን ማኔጅመንት ለሐዋሳ ከተማ ዕድገትና ለአዲሱ የሐዋሳ ሐይቅ ልማት ፕሮጀክት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ያረጋገጠ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በቴክኖሎጂ የማብቃትና ዲጂታል መጻኢን የመገንባት ትልቅ ራዕያችን አካል መሆኑ ተመላክቷል።
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ !
#ethiotelecom #telebirr #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia #smartcity #hawassa #digitalethiopia
በዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የተመራው የኩባንያችን ከፍተኛ ማኔጅመንት ቡድን፣ ከሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ እና ከከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በከተማዋ እያስመዘገበችው የሚገኘውን ፈጣን የዲጂታል ዕድገት እንዲሁም የመጻኢ የቴክኖሎጂ ትስስርን ለማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሂዷል።
ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ ኩባንያችን እያከናወናቸው የሚገኙ መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሥራዎችን በማድነቅ፤ በተለይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ረገድ ኢትዮ ቴሌኮም እያበረከተ ለሚገኘው ቁልፍ ሚና እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ክቡር ከንቲባው ቀደም ሲል በከተማዋ ለተከናወኑ የልማት ፕሮጀክቶች ኩባንያችን ላደረገው ሁለገብ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ ሐዋሳ ከአዲስ አበባ በመቀጠል ዋነኛ የቱሪዝም እና የኮንፈረንስ መዳረሻ እንድትሆን ለማስቻል ያለመ አዲስ የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ውጥን ይፋ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። በመሆኑም በመካሄድ ላይ ያለውን የ"ስማርት ሲቲ" ፕሮጀክት እና የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ለማፋጠን የኢትዮ ቴሌኮም ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረው ጠይቀዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ በበኩላቸው፤ ኩባንያችን መሰል የከተማ ልማት ውጥኖችን ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አረጋግጠዋል። ሐዋሳ በፋይበር መሰረተ ልማት እንዲሁም በ4ጂ እና በ5ጂ የሞባይል ቴክኖሎጂ የታጠቀች ከተማ መሆኗን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት አስተማማኝ የሆነ የኔትወርክ ሽፋን እና ጥራትን ማሳደግ ታሳቢ ያደረግ መጠነ ሰፊ የማስፋፋት እና የማዘመን ሥራ በተጠናከረ ሁኔታ በመካሄድ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የከተማ አስተዳደሩን አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂና በቴሌብር በማዘመን፣ የሥራ ቅልጥፍናንና የገቢ አሰባሰብን ማሳደግ እንደሚቻል ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ገልጸዋል። በተመሳሳይ፣ በዘመን ገበያ አማካኝነት ለነጋዴዎች የገበያ ትስስርን በማስፋፋት ረገድ ሰፊ የዲጂታላይዜሽን ዕድሎችና የሥራ ፈጠራ አጋጣሚዎች መኖራቸውን አስገንዝበዋል።
ሐዋሳን ንፁህ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና በዲጂታል የታገዘ የሕዝብ መዳረሻ ለማድረግ እንዲሁም የተቀናጀ የዲጂታል ሥነ-ምህዳርን ለመፍጠር ያለመ ሰፊ ስትራቴጂካዊ ውይይት ተደርጓል። በዚሁ መሠረት የኩባንያችንን አቅም በመጠቀም የሐዋሳ "ስማርት ሲቲ" ልማትን ለማፋጠን፣ የቴሌብር አገልግሎቶችን በሙሉ አቅም ማቀናጀት፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ፣ የትራፊክ እና የሞቢሊቲ መፍትሔዎች፣ የመሠረተ ልማት ጥበቃ እንዲሁም የኔትወርክ ዝርጋታን የሚያቀላጥፉ የኮሪደር ልማት ትብብሮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል።
በመጨረሻም፣ የኩባንያችን ማኔጅመንት ለሐዋሳ ከተማ ዕድገትና ለአዲሱ የሐዋሳ ሐይቅ ልማት ፕሮጀክት አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ያረጋገጠ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በቴክኖሎጂ የማብቃትና ዲጂታል መጻኢን የመገንባት ትልቅ ራዕያችን አካል መሆኑ ተመላክቷል።
#ዲጂታል_ኢትዮጵያን_ዕውን_በማድረግ_ላይ !
#ethiotelecom #telebirr #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia #smartcity #hawassa #digitalethiopia
4 days ago
ሰላም፣ እንደምን አደራችሁ?
ዘመኑን የዋጀ መከላከያ ሠራዊት፤ ለኢትዮጵያ ልዕልና መሰረት
ከመከላከያ ሠራዊት ተልዕኮዎች መካከል የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ፣ የሕዝብን ደህንነት ማረጋገጥና ቀጣናዊ ሰላምን ማስከበር ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
በዓለም ላይ ያሉ የጸጥታ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ ባሉበት በዚህ ዘመን የሀገራት የመከላከያ አቅም በቁጥር እና በወታደራዊ መሳሪያዎች ብቻ የሚለካበት ጊዜ አልፏል።
አሁን ላይ የሚካሄዱ ዘመናዊ ጦርነቶች አሸናፊነት በቴክኖሎጂ፣ በመረጃ፣ በሳይበር ሥርዓት እና በፈጣን ውሳኔ ሰጪነት ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡
ከእነዚህ መሰረታዊ መርሆች አንጻር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመኑን ለመዋጀት በተለያዩ ዘርፎች የለውጥ ጉዞ ላይ ይገኛል። ሠራዊቱ ለሀገር ባንዴራ፣ ክብርና ነጻነት ራሱን የሚሰዋ እንዲሁም ለቀጣናው ሀገራት መከታ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ወረራዎችን በመመከት ነጻነቷን ያስጠበቀች ከመሆኗ ባለፈ የአፍሪካ ጸረ ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴ ቀንዲል ናት፡፡
አሁን ላይ ያለው የጸጥታ ፈተና ደግሞ ከትናንቱ በእጅጉ የተለየ ነው ፤ ከባህላዊ የድንበር ጥቃት ባሻገር የሽብር አደጋዎች፣ የሳይበር ጥቃቶች፣ የሀሰት መረጃ ዘመቻዎችና የተደራጁ ወንጀሎች አዳዲስ ፈተናዎች ሆነው ብቅ ብለዋል።
ስለሆነም ነባራዊ ሁኔታውን የሚመጥን በሁለንታዊ አቅሙ የጎለበተ ዘመናዊ ሠራዊት መገንባት እነዚህን የወቅቱ ፈተናዎች በድል ለመወጣት ያስችላል፡፡
የኢትየጵያ መከላከያ ሠራዊት ከጦር ዝግጅት በላይ በቴክኖሎጂ እና በመረጃ ላይ የተመሰረተ አቅም እንዲገነባ እየተከናወነ የሚገኘው ሥራም የሚደነቅ ነው፡፡
የኢትየጵያ መከላከያ ሠራዊት ታሪክን በደምና በአጥንት ቀለም ከመጻፍ አልፎ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ በእውቀት፣ በሥራ እና በቴክኖሎጂ ምሰሶ ላይ የሚያቆም ግዙፍ ሃይል እየሆነ ነው፡፡
በለውጡ መንግሥት በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎች የኢትዮጵያ መከላከያ በስልጠና፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ ተጨባጭ ለውጦችን አስመዝግቧል።
የድሮን ቴክኖሎጂ፣ የዘመናዊ የመረጃ ሥርዓቶች አጠቃቀም፣ የልዩ ኃይል ስልጠናዎች እና የፈጣን ምላሽ አቅሞች የዚህ ለውጥ አካል ሆነው ይጠቀሳሉ።
ከዚህ ባለፈም መከላከያው በዘመናዊ የጦር ስልቶች እና በዲጂታል ግንኙነት ስርዓቶች ላይ ያደረገው ትኩረት ዘመኑን የመዋጀት ሒደቱ እየተጠናከረ መሆኑን ያሳያል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳሉት÷ ሠራዊቱ እጅግ ዘመናዊ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በመታጠቅ የየብስ፣ የአየርና የሳይበር ምህዳርን በበላይነት የሚቆጣጠር አስፈሪ የብረት ክንድ ሆኗል።
መከላከያ ሠራዊት የጠላትን ትንኮሳና ጥቃት በስነ ልቦና የበላይነት፣ በዘመናዊ ትጥቅ እና በላቀ ወታደራዊ ሳይንስ የማክሸፍ አቅሙ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱንም አውስተዋል፡፡
እያንዳንዱ መኮንን አካላዊ ጀግንነትን ብቻ ሳይሆን፣ አውዳሚ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቶችን በብልሃት እና በፍጥነት የሚያከሽፍ፣ የተረጋጋ አዕምሮ ያለው የዘመኑ የጥበብ ሰው ሆኖ ተቀርጿልም ነው ያሉት፡፡
የሠራዊቱን ሁለንተናዊ የማድረግ አቅም ይበልጥ ለማሳደግም በዘርፉ የሚከናወነው ዘመኑን የመዋጀት ሥራ የዓለምን ብሎም የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡
የሳይበር ደህንነት አቅምን ይበልጥ ማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ የመከላከያ ኢንዱስትሪን ማሳደግ፣ የሰው ኃይል ሙያዊ ብቃትን ማጎልበት እና በምርምርና ፈጠራ ላይ ትኩረት መስጠት ቀጣይ ተግባራት ናቸው።
የዘመናዊ መከላከያ ጥንካሬ የሚለካው በሚገዛው መሳሪያ ብዛት ሳይሆን፣ በራሱ የሚፈጥረው ዕውቀት፣ ቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ብቃት መሆኑንም መረዳት ግድ ይላል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ መከላከያ ዘመኑን ከመዋጀት አንጻር ሲታይ፣ በታሪካዊ የጦር ጀግንነት ላይ ብቻ የማይመረኮዝ፣ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ እና በሙያዊ ብቃት የተደገፈ ዘመናዊ ተቋም ለመሆን የጀመረው ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ ነው፡፡
ዘመኑን የዋጀ መከላከያ ሠራዊት፤ ለኢትዮጵያ ልዕልና መሰረት
ከመከላከያ ሠራዊት ተልዕኮዎች መካከል የሀገርን ሉዓላዊነት መጠበቅ፣ የሕዝብን ደህንነት ማረጋገጥና ቀጣናዊ ሰላምን ማስከበር ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡
በዓለም ላይ ያሉ የጸጥታ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ ባሉበት በዚህ ዘመን የሀገራት የመከላከያ አቅም በቁጥር እና በወታደራዊ መሳሪያዎች ብቻ የሚለካበት ጊዜ አልፏል።
አሁን ላይ የሚካሄዱ ዘመናዊ ጦርነቶች አሸናፊነት በቴክኖሎጂ፣ በመረጃ፣ በሳይበር ሥርዓት እና በፈጣን ውሳኔ ሰጪነት ላይ የተመሰረቱ ናቸው፡፡
ከእነዚህ መሰረታዊ መርሆች አንጻር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመኑን ለመዋጀት በተለያዩ ዘርፎች የለውጥ ጉዞ ላይ ይገኛል። ሠራዊቱ ለሀገር ባንዴራ፣ ክብርና ነጻነት ራሱን የሚሰዋ እንዲሁም ለቀጣናው ሀገራት መከታ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በታሪኳ የውጭ ወረራዎችን በመመከት ነጻነቷን ያስጠበቀች ከመሆኗ ባለፈ የአፍሪካ ጸረ ቅኝ ግዛት እንቅስቃሴ ቀንዲል ናት፡፡
አሁን ላይ ያለው የጸጥታ ፈተና ደግሞ ከትናንቱ በእጅጉ የተለየ ነው ፤ ከባህላዊ የድንበር ጥቃት ባሻገር የሽብር አደጋዎች፣ የሳይበር ጥቃቶች፣ የሀሰት መረጃ ዘመቻዎችና የተደራጁ ወንጀሎች አዳዲስ ፈተናዎች ሆነው ብቅ ብለዋል።
ስለሆነም ነባራዊ ሁኔታውን የሚመጥን በሁለንታዊ አቅሙ የጎለበተ ዘመናዊ ሠራዊት መገንባት እነዚህን የወቅቱ ፈተናዎች በድል ለመወጣት ያስችላል፡፡
የኢትየጵያ መከላከያ ሠራዊት ከጦር ዝግጅት በላይ በቴክኖሎጂ እና በመረጃ ላይ የተመሰረተ አቅም እንዲገነባ እየተከናወነ የሚገኘው ሥራም የሚደነቅ ነው፡፡
የኢትየጵያ መከላከያ ሠራዊት ታሪክን በደምና በአጥንት ቀለም ከመጻፍ አልፎ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ በእውቀት፣ በሥራ እና በቴክኖሎጂ ምሰሶ ላይ የሚያቆም ግዙፍ ሃይል እየሆነ ነው፡፡
በለውጡ መንግሥት በተከናወኑ ዘርፈ ብዙ የሪፎርም ሥራዎች የኢትዮጵያ መከላከያ በስልጠና፣ በአደረጃጀት እና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ ተጨባጭ ለውጦችን አስመዝግቧል።
የድሮን ቴክኖሎጂ፣ የዘመናዊ የመረጃ ሥርዓቶች አጠቃቀም፣ የልዩ ኃይል ስልጠናዎች እና የፈጣን ምላሽ አቅሞች የዚህ ለውጥ አካል ሆነው ይጠቀሳሉ።
ከዚህ ባለፈም መከላከያው በዘመናዊ የጦር ስልቶች እና በዲጂታል ግንኙነት ስርዓቶች ላይ ያደረገው ትኩረት ዘመኑን የመዋጀት ሒደቱ እየተጠናከረ መሆኑን ያሳያል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳሉት÷ ሠራዊቱ እጅግ ዘመናዊ የጦር ቴክኖሎጂዎችን በመታጠቅ የየብስ፣ የአየርና የሳይበር ምህዳርን በበላይነት የሚቆጣጠር አስፈሪ የብረት ክንድ ሆኗል።
መከላከያ ሠራዊት የጠላትን ትንኮሳና ጥቃት በስነ ልቦና የበላይነት፣ በዘመናዊ ትጥቅ እና በላቀ ወታደራዊ ሳይንስ የማክሸፍ አቅሙ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱንም አውስተዋል፡፡
እያንዳንዱ መኮንን አካላዊ ጀግንነትን ብቻ ሳይሆን፣ አውዳሚ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቶችን በብልሃት እና በፍጥነት የሚያከሽፍ፣ የተረጋጋ አዕምሮ ያለው የዘመኑ የጥበብ ሰው ሆኖ ተቀርጿልም ነው ያሉት፡፡
የሠራዊቱን ሁለንተናዊ የማድረግ አቅም ይበልጥ ለማሳደግም በዘርፉ የሚከናወነው ዘመኑን የመዋጀት ሥራ የዓለምን ብሎም የቀጣናውን ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡
የሳይበር ደህንነት አቅምን ይበልጥ ማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ የመከላከያ ኢንዱስትሪን ማሳደግ፣ የሰው ኃይል ሙያዊ ብቃትን ማጎልበት እና በምርምርና ፈጠራ ላይ ትኩረት መስጠት ቀጣይ ተግባራት ናቸው።
የዘመናዊ መከላከያ ጥንካሬ የሚለካው በሚገዛው መሳሪያ ብዛት ሳይሆን፣ በራሱ የሚፈጥረው ዕውቀት፣ ቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ብቃት መሆኑንም መረዳት ግድ ይላል፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ መከላከያ ዘመኑን ከመዋጀት አንጻር ሲታይ፣ በታሪካዊ የጦር ጀግንነት ላይ ብቻ የማይመረኮዝ፣ በእውቀት፣ በቴክኖሎጂ እና በሙያዊ ብቃት የተደገፈ ዘመናዊ ተቋም ለመሆን የጀመረው ጉዞ ይበልጥ ማጠናከር አስፈላጊ ነው፡፡
7 days ago
ሰላም፣ እንደምን አደራችሁ?
አብሮነት ለሀገር ግንባታና ለዘላቂ ልማት ከፍተኛ ሚና አለው፡፡
የሀገር ግንባታ የአንድን ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ መዋቅር፣ የሕግ የበላይነትን፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬንና የማህበራዊ ትስስርን በአንድ የጋራ ርዕይ ስር የመቅረጽ ዘላቂና ስልታዊ ሒደት ነው።
በታሪካዊና ባህላዊ እሴቶቿ የበለጸገችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውጤታማ የሪፎርም ሒደትና በአስደናቂ የልማት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በዚህ ረገድ ሀገራዊ አንድነትና አብሮነት ለኢኮኖሚ እድገት ብሎም ለፖለቲካዊ መረጋጋት መሰረት ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ንግግሮች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነቶች ሊኖሩ እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ እንዳሉት ፥ የልመናን ታሪክ በመቀየር ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለመገንባት በሀገር ጉዳይ በአንድነት መቆም የግድ ይላል።
ለዚህም በፖለቲካና ሌሎች ጉዳዮች የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ለድርድር የሚቀርብ አለመሆኑን መገንዘብ እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት አብሮነት በማሕበረሰቡ መካከል እምነትንና ትብብርን በመገንባት ጠንካራ ማህበራዊ ካፒታል እንደሚፈጥር የሚያስገነዝብ ነው።
በዚህም በመንግሥት፣ በግል ባለሃብቱና በሕዝብ መካከል የተቀናጀ የልማት አጋርነት እንዲኖር በማስቻል ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ለማሳካት እንደሚያስችል ምስክር የሚሆኑ ሀገራዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
የሀገር ግንባታ የተሟላ የሚሆነው አካታች በመሆን በሚከናወኑ ሀገራዊ ልማቶች የጥቂቶችን ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ዜጋ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ሲችል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ በጋራ ትገነባለች ምሁራንና ባለሙያዎች እውቀታቸውን ለሀገር ተቋማት ግንባታ ማዋል ይጠበቅባቸዋል።
ባለሃብቶች በልማት ስራዎች ላይ በስፋት ሲሰማሩ እንዲሁም አምራች ኃይል የሆነው ወጣት በፈጠራና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በንቃት ሲሳተፍ፤ ሁሉም ዜጋ በተሰማራበት መስክ በጋራ ለሀገር ጥቅም ሲተጋ ሀገር በጋራ ትገነባለች።
ኢትዮጵያን ወደ ላቀ የብልጽግና ምዕራፍ ማሸጋገር የሚቻለው ልዩነቶችን ወደ አዎንታዊ አቅም በመቀየርና የአብሮነት እሴቶችን በማጎልበት ብቻ ነው።
ስለዚህ ዛሬ የምናስቀምጠው የእውቀት፣ የጉልበትና የሀሳብ ጡብ ነገ ጠንካራና የማይናወጥ መንግሥታዊና ሀገራዊ መዋቅር ለመገንባት ያስችላል።
የጋራ ርዕይ፣ የጋራ ሥራና አብሮነት የኢትዮጵያ የወደፊት ጉዞ ስኬት ቁልፎች ናቸው።
ኑ ሀገር እንስራ!
አብሮነት ለሀገር ግንባታና ለዘላቂ ልማት ከፍተኛ ሚና አለው፡፡
የሀገር ግንባታ የአንድን ማሕበረሰብ ሁለንተናዊ መዋቅር፣ የሕግ የበላይነትን፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬንና የማህበራዊ ትስስርን በአንድ የጋራ ርዕይ ስር የመቅረጽ ዘላቂና ስልታዊ ሒደት ነው።
በታሪካዊና ባህላዊ እሴቶቿ የበለጸገችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውጤታማ የሪፎርም ሒደትና በአስደናቂ የልማት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
በዚህ ረገድ ሀገራዊ አንድነትና አብሮነት ለኢኮኖሚ እድገት ብሎም ለፖለቲካዊ መረጋጋት መሰረት ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ንግግሮች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ልዩነቶች ሊኖሩ እንደማይገባ ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ እንዳሉት ፥ የልመናን ታሪክ በመቀየር ለመጪው ትውልድ የተሻለች ሀገር ለመገንባት በሀገር ጉዳይ በአንድነት መቆም የግድ ይላል።
ለዚህም በፖለቲካና ሌሎች ጉዳዮች የሀሳብ ልዩነቶች ቢኖሩም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ለድርድር የሚቀርብ አለመሆኑን መገንዘብ እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት አብሮነት በማሕበረሰቡ መካከል እምነትንና ትብብርን በመገንባት ጠንካራ ማህበራዊ ካፒታል እንደሚፈጥር የሚያስገነዝብ ነው።
በዚህም በመንግሥት፣ በግል ባለሃብቱና በሕዝብ መካከል የተቀናጀ የልማት አጋርነት እንዲኖር በማስቻል ግዙፍ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ለማሳካት እንደሚያስችል ምስክር የሚሆኑ ሀገራዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
የሀገር ግንባታ የተሟላ የሚሆነው አካታች በመሆን በሚከናወኑ ሀገራዊ ልማቶች የጥቂቶችን ብቻ ሳይሆን የሁሉንም ዜጋ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ሲችል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ በጋራ ትገነባለች ምሁራንና ባለሙያዎች እውቀታቸውን ለሀገር ተቋማት ግንባታ ማዋል ይጠበቅባቸዋል።
ባለሃብቶች በልማት ስራዎች ላይ በስፋት ሲሰማሩ እንዲሁም አምራች ኃይል የሆነው ወጣት በፈጠራና በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ በንቃት ሲሳተፍ፤ ሁሉም ዜጋ በተሰማራበት መስክ በጋራ ለሀገር ጥቅም ሲተጋ ሀገር በጋራ ትገነባለች።
ኢትዮጵያን ወደ ላቀ የብልጽግና ምዕራፍ ማሸጋገር የሚቻለው ልዩነቶችን ወደ አዎንታዊ አቅም በመቀየርና የአብሮነት እሴቶችን በማጎልበት ብቻ ነው።
ስለዚህ ዛሬ የምናስቀምጠው የእውቀት፣ የጉልበትና የሀሳብ ጡብ ነገ ጠንካራና የማይናወጥ መንግሥታዊና ሀገራዊ መዋቅር ለመገንባት ያስችላል።
የጋራ ርዕይ፣ የጋራ ሥራና አብሮነት የኢትዮጵያ የወደፊት ጉዞ ስኬት ቁልፎች ናቸው።
ኑ ሀገር እንስራ!
9 days ago
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በሚያስችሉ ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ።
በክልሉ "የዘመነ ፈተና አስተዳደር ስርዓት፤ ለላቀ የትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የ2018 ዓ.ም ሀገራዊና ክልላዊ ፈተና አስተዳደር ምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በዚህ ወቅት÷ ባለፉት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ጥራት ያለው ትምህርት ለማቅረብ ጥራት ያለው የምዘና ስርዓት ውስጥ ማለፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ለዚህም የፈተና ምዘና እና የፈተና አስተዳደር ሥርዓት ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል።
በዘንድሮው ክልላዊ ፈተና የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል 89 ሺህ 538 ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።
የሀገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ ደረጃ የሚሰጡ ፈተናዎችን ከኩረጃ የጸዳ እንዲሆኑ እና ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን መቻሉም ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾን (ዶ/ር) ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ።
በክልሉ "የዘመነ ፈተና አስተዳደር ስርዓት፤ ለላቀ የትምህርት ጥራት" በሚል መሪ ሐሳብ የተዘጋጀ የ2018 ዓ.ም ሀገራዊና ክልላዊ ፈተና አስተዳደር ምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ በዚህ ወቅት÷ ባለፉት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚያስችሉ የሪፎርም ስራዎች ላይ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
የትምህርት ስርዓቱን ለማሻሻል በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ጥራት ያለው ትምህርት ለማቅረብ ጥራት ያለው የምዘና ስርዓት ውስጥ ማለፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
ለዚህም የፈተና ምዘና እና የፈተና አስተዳደር ሥርዓት ማዘመን አስፈላጊ መሆኑን አጽንዖት ሰጥተዋል።
በዘንድሮው ክልላዊ ፈተና የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል 89 ሺህ 538 ተማሪዎችን ለማስፈተን ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።
የሀገር አቀፍ እና ክልል አቀፍ ደረጃ የሚሰጡ ፈተናዎችን ከኩረጃ የጸዳ እንዲሆኑ እና ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን መቻሉም ተገልጿል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾን (ዶ/ር) ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻዎች መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል ገልጿል።
10 days ago
ዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የጉዞ ማዕረጉን በሽልማት እና በበጎ አድራጎት ተግባራት ደመደመ
#ethiopia | ለግማሽ ዓመት ያህል በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር የሰነበተው የዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሸራተን አዲስ ሆቴል በተከናወነ ታላቅ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ የክብር እንግዳ በመሆን የተገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ባንኩ ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እና የኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ላበረከተው ጉልህ ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ገዥው አክለውም ባንኩ የተጀመረውን ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም በመደገፍ በመጪው የለውጥ ምዕራፍ ተወዳዳሪነቱን ይበልጥ እንዲያጠናክር አሳስበዋል።
የዳሸን ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በበኩላቸው የባንኩ የ30 ዓመታት የስኬት ጉዞ የደንበኞች፣ የባለድርሻ አካላትና የሠራተኞች የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ ወደፊትም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ለሀገር እድገት የሚጠበቅበትን ሚና መወጣቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ባንኩ ከጥር 2018 ዓ.ም ጀምሮ የ30ኛ ዓመት ኤክስፖ፣ የኢኖቬሽን ወር እና የሴቶች አቅም ማጎልበቻ መርኃ ግብሮችን ጨምሮ በርካታ ዝግጅቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተጠቅሷል።
በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ባንኩ ለአሁኑ የስኬት ደረጃው እንዲበቃ ስያሜ ከመስጠት ጀምሮ ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉት ለክቡር ሸኽ መሐመድ ሁሴን ዓሊ አላሙዲን ልዩ የዕውቅና ሽልማት ተበርክቷል።
ከተገቢው ክብር ጋር ለ11 የባንኩ መስራቾች፣ ለቀድሞ የቦርድ አመራሮች፣ ለቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ለአጋር ተቋማት፣ ለረጅም ዘመን ደንበኞች እና የረጅም ጊዜ አገልግሎት ላላቸው ሠራተኞችም ዕውቅና ተሰጥቷል።
የማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት ተግባሩ አካል አድርጎም ባንኩ በአዕምሮ እድገት ውስንነት ላላቸው ወገኖች ድጋፍ ለሚያደርገው ለዲቦራ ፋውንዴሽን የ30 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ስጦታ አበርክቷል።
በሌላ በኩል በዳሸን ሱፐር አፕ መተግበሪያ በተካሄደው የዕድል ጨዋታ አሸናፊ ለሆነው ደንበኛ የዘመናዊ ቢዋይዲ ሴጉል የኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት ተላልፏል።
በዚህ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ኢዮብ ተካልኝን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የፋይናንስ ተቋማት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#dashenbank #banking #ethiopianeconomy #finance #deborahfoundation #byd #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ለግማሽ ዓመት ያህል በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር የሰነበተው የዳሸን ባንክ 30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በሸራተን አዲስ ሆቴል በተከናወነ ታላቅ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ የክብር እንግዳ በመሆን የተገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ባንኩ ላለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እና የኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ላበረከተው ጉልህ ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ገዥው አክለውም ባንኩ የተጀመረውን ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም በመደገፍ በመጪው የለውጥ ምዕራፍ ተወዳዳሪነቱን ይበልጥ እንዲያጠናክር አሳስበዋል።
የዳሸን ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አስፋው ዓለሙ በበኩላቸው የባንኩ የ30 ዓመታት የስኬት ጉዞ የደንበኞች፣ የባለድርሻ አካላትና የሠራተኞች የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑን ገልጸው፣ ወደፊትም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ አገልግሎቶችን በማስፋፋት ለሀገር እድገት የሚጠበቅበትን ሚና መወጣቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ባንኩ ከጥር 2018 ዓ.ም ጀምሮ የ30ኛ ዓመት ኤክስፖ፣ የኢኖቬሽን ወር እና የሴቶች አቅም ማጎልበቻ መርኃ ግብሮችን ጨምሮ በርካታ ዝግጅቶችን ሲያካሂድ መቆየቱ ተጠቅሷል።
በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ባንኩ ለአሁኑ የስኬት ደረጃው እንዲበቃ ስያሜ ከመስጠት ጀምሮ ከፍተኛ ድጋፍ ላደረጉት ለክቡር ሸኽ መሐመድ ሁሴን ዓሊ አላሙዲን ልዩ የዕውቅና ሽልማት ተበርክቷል።
ከተገቢው ክብር ጋር ለ11 የባንኩ መስራቾች፣ ለቀድሞ የቦርድ አመራሮች፣ ለቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ለአጋር ተቋማት፣ ለረጅም ዘመን ደንበኞች እና የረጅም ጊዜ አገልግሎት ላላቸው ሠራተኞችም ዕውቅና ተሰጥቷል።
የማህበራዊ ኃላፊነቱን የመወጣት ተግባሩ አካል አድርጎም ባንኩ በአዕምሮ እድገት ውስንነት ላላቸው ወገኖች ድጋፍ ለሚያደርገው ለዲቦራ ፋውንዴሽን የ30 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ስጦታ አበርክቷል።
በሌላ በኩል በዳሸን ሱፐር አፕ መተግበሪያ በተካሄደው የዕድል ጨዋታ አሸናፊ ለሆነው ደንበኛ የዘመናዊ ቢዋይዲ ሴጉል የኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት ተላልፏል።
በዚህ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ የብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ኢዮብ ተካልኝን (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የፋይናንስ ተቋማት መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#dashenbank #banking #ethiopianeconomy #finance #deborahfoundation #byd #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
10 days ago
የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም ማሳያ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት ቀልጣፋ፣ ተዓማኒና ቀጣይነት ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም ማሳያ ነው አሉ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ የወልድያ ከተማ መሶብ ዘመናዊ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በዛሬው ዕለት መርቀን በይፋ ስራ አስጀምረናል ብለዋል።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን በሀገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ኩባንያ የኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ መስጠቱን አስታውቋል። ይህ ታሪካዊ ፈቃድ የተሰጠው መሠረቱን ናይጄሪያ ላደረገው "ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ" የተባለ የፋይናንስ ተቋም ነው።
ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢነት ፈቃዱ የተሰጠው በኢትዮጵያ ለተመዘገበው "ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር" ለተሰኘው የኩባንያው ቅርንጫፍ ነው። ይህ ፈቃድ ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ በኢትዮጵያ ውስጥ የኢንቨስትመንት ባንክ አገልግሎት በይፋ እንዲጀምር የሚያስችለው ሲሆን፣ ተቋሙ እስካሁን በተመሳሳይ ዘርፍ ፈቃድ ካገኙት ሌሎች ስድስት የሀገር ውስጥ የኢንቨስትመንት ባንኮች ጋር ተቀላቅሎ በገበያው ውስጥ ይሳተፋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመጡ ጊዜ ጀምሮ፣ ለረጅም ዓመታት ዝግ እና በመንግስት ቁጥጥር ስር የቆየውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለውጭ እና ለግል ባለሀብቶች ክፍት የማድረግ ሰፊ የማሻሻያ ስራዎችን እያከናወኑ ይገኛሉ። በዚህ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደት ውስጥም፣ በተለይ የባንክ እና የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፎች የውጭ ባለሀብቶችን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ላይ ከሚገኙ መስኮች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢነት ፈቃዱ የተሰጠው በኢትዮጵያ ለተመዘገበው "ዩናይትድ ካፒታል ፋይናንሻል ሰርቪስስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር" ለተሰኘው የኩባንያው ቅርንጫፍ ነው። ይህ ፈቃድ ዩናይትድ ካፒታል ግሩፕ በኢትዮጵያ ውስጥ የኢንቨስትመንት ባንክ አገልግሎት በይፋ እንዲጀምር የሚያስችለው ሲሆን፣ ተቋሙ እስካሁን በተመሳሳይ ዘርፍ ፈቃድ ካገኙት ሌሎች ስድስት የሀገር ውስጥ የኢንቨስትመንት ባንኮች ጋር ተቀላቅሎ በገበያው ውስጥ ይሳተፋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እ.ኤ.አ. በ2018 ወደ ስልጣን ከመጡ ጊዜ ጀምሮ፣ ለረጅም ዓመታት ዝግ እና በመንግስት ቁጥጥር ስር የቆየውን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ለውጭ እና ለግል ባለሀብቶች ክፍት የማድረግ ሰፊ የማሻሻያ ስራዎችን እያከናወኑ ይገኛሉ። በዚህ የኢኮኖሚ ሪፎርም ሂደት ውስጥም፣ በተለይ የባንክ እና የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፎች የውጭ ባለሀብቶችን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ላይ ከሚገኙ መስኮች መካከል በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ።
11 days ago
ዘመኑን የዋጀው ፌዴራል ፖሊስ፤ ከሀገራዊ ሪፎርም እስከ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች መከላከል ስኬት
***************
የሀገራችንን ታሪክና ልዕልና የሚመጥን ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ሪፎርም፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ቁመና ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
የፌዴራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደገለጹት፤ ተቋሙ የሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባካሄደው ጥልቅ የሪፎርም ትግበራ አሁን ላይ ዘመኑን የዋጀና ውጤታማ ተግባራትን የሚያከናውን ጠንካራ አቅም መገንባት ችሏል።
ይህ አዲስ ተቋማዊ ቁመናም ፖሊስ ከተለዋዋጭ ሁነቶች እና ከዲጂታሉ ዓለም ፈጣን ዕድገት ጋር እኩል እንዲጓዝ ትልቅ አቅም የፈጠረለት ሲሆን፣ በተለይም በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ እንዳስቻለው ተናግረዋል።
ተቋሙ በስኬት ከተወጣቸው ተልዕኮዎች መካከል በየአቅጣጫው መረባቸውን ዘርግተው በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተው የነበሩ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪዎቻቸው እጅ ከፍንጅ በመያዝ ለሕግ ማቅረቡ ዋነኛው መሆኑን ኮሚሽነሩ አንስተዋል።
መሰል የደህንነት ስጋቶች በስፋት የሚከሰቱባቸውን ቀጣናዎች በመለየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው በዚህ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ፖሊስ በቁርጠኝነት ያከናወነው ተግባር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትና ዕውቅና የተቸረው መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም የተነሳ ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ዙሪያ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው ያመላከቱት።
የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁና በቴክኖሎጂ የታገዙ እየሆኑ ቢመጡም፣ ፌዴራል ፖሊስ በዛው ልክ ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ስልታዊ አደረጃጀትን በመጠቀም አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ እያጠናከረ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የፌዴራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።
በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅትና በጋራ መሥራት መቻሉ የተቋሙን ተጽዕኖ፣ ተአማኒነትና ተደራሽነት ይበልጥ ከፍ እንዳደረገው የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ወደፊትም ዘመኑን በዋጀ መንገድ የሕግ የበላይነትን የማስከበር፣ የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥና የሀገርን ሰላም ዘላቂ የማድረግ ስልታዊ ተልዕኮው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
#federalpolice #ethiopia #institutionalreform #bordersecurity #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
የሀገራችንን ታሪክና ልዕልና የሚመጥን ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ሪፎርም፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ቁመና ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
የፌዴራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደገለጹት፤ ተቋሙ የሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባካሄደው ጥልቅ የሪፎርም ትግበራ አሁን ላይ ዘመኑን የዋጀና ውጤታማ ተግባራትን የሚያከናውን ጠንካራ አቅም መገንባት ችሏል።
ይህ አዲስ ተቋማዊ ቁመናም ፖሊስ ከተለዋዋጭ ሁነቶች እና ከዲጂታሉ ዓለም ፈጣን ዕድገት ጋር እኩል እንዲጓዝ ትልቅ አቅም የፈጠረለት ሲሆን፣ በተለይም በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ እንዳስቻለው ተናግረዋል።
ተቋሙ በስኬት ከተወጣቸው ተልዕኮዎች መካከል በየአቅጣጫው መረባቸውን ዘርግተው በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተው የነበሩ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪዎቻቸው እጅ ከፍንጅ በመያዝ ለሕግ ማቅረቡ ዋነኛው መሆኑን ኮሚሽነሩ አንስተዋል።
መሰል የደህንነት ስጋቶች በስፋት የሚከሰቱባቸውን ቀጣናዎች በመለየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው በዚህ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ፖሊስ በቁርጠኝነት ያከናወነው ተግባር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትና ዕውቅና የተቸረው መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም የተነሳ ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ዙሪያ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው ያመላከቱት።
የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁና በቴክኖሎጂ የታገዙ እየሆኑ ቢመጡም፣ ፌዴራል ፖሊስ በዛው ልክ ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ስልታዊ አደረጃጀትን በመጠቀም አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ እያጠናከረ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የፌዴራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።
በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅትና በጋራ መሥራት መቻሉ የተቋሙን ተጽዕኖ፣ ተአማኒነትና ተደራሽነት ይበልጥ ከፍ እንዳደረገው የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ወደፊትም ዘመኑን በዋጀ መንገድ የሕግ የበላይነትን የማስከበር፣ የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥና የሀገርን ሰላም ዘላቂ የማድረግ ስልታዊ ተልዕኮው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
#federalpolice #ethiopia #institutionalreform #bordersecurity #ethiopianbroadcastingcorporation
11 days ago
የናይጀሪያ ባንክ ኢትዮጵያ ገባ‼
ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ፈቃድ አገኘ
በአፍሪካ ግዙፍ የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ የሆነው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል (United Capital Plc) በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ አግኝቷል።
ይህ ስኬት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የፋይናንስ ሊበራላይዜሽን (Financial liberalization) ትግበራ ውጤት ሲሆን፣ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ገበያ ክፍት በማድረግ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየተሰሩ ካሉ ሰፋፊ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ፈቃድ አገኘ
በአፍሪካ ግዙፍ የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ የሆነው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል (United Capital Plc) በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ አግኝቷል።
ይህ ስኬት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የፋይናንስ ሊበራላይዜሽን (Financial liberalization) ትግበራ ውጤት ሲሆን፣ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ገበያ ክፍት በማድረግ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየተሰሩ ካሉ ሰፋፊ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
12 days ago
መንግሥት የሚሊሻውን ኃይል አደረጃጀት ዘመናዊ ለማድረግ፣ በዕውቀትና በሥልጠና ለማበልጸግ እንዲሁም ትጥቅና አቅርቦቱን ለማሻሻል የጀመረውን ተቋማዊ የሪፎርም ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
Sponsored by
Surafel
12 days ago
የኢትዮጵያ ስልታዊ ዲፕሎማሲ፦ ከውስጥ ጽናት እስከ ዓለም አቀፍ ከፍታ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
12 days ago
ፓስፖርት ማውጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ ቀላል እንዲሆን ይደረጋል - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
************************
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የዜጎችን እንግልት ለመቀነስና አሠራሩን ለማዘመን በጀመረው የሪፎርም ሥራ፤ ወደፊት ማንኛውም ሰው ከቤቱ ሳይወጣ የፓስፖርት አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚያገኝበትን አሰራር ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከኢቢሲ "ስለ ሀገር" ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ተቋሙ ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአካሄደው ሪፎርም ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ የያዘውን የዲጂታል አገልግሎት ግብ ለማሳካት ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ሲስተሙን በማቀናጀት ላይ ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ ይህም ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት በአካል መገኘት ሳያስፈልጋቸው፣ በፋይዳ ሲስተም ላይ ያለውን መረጃ በቀጥታ በመጠቀም አገልግሎቱን በኦንላይን ብቻ እንዲያጠናቅቁ ያስችላቸዋል ብለዋል።
በተቋሙ ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከልም ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቁመው፤ ተገልጋዮች ቅሬታ ካላቸው በአካል በተዘጋጁ የአስተያየት መስጫ ዴስኮች ብቻ ሳይሆን፣ በኦንላይን አማራጭ ምስልና ቪዲዮ በማያያዝ ጭምር ማቅረብ የሚችሉበት አሠራር መመቻቸቱን አመልክተዋል።
እያንዳንዱ የተቋሙ ሠራተኛ የኮምፒውተር አጠቃቀም ከአሻራ ጋር የተገናኘ በመሆኑ፣ ማን ምን ዓይነት ሥራ እንደሠራና ምን ዓይነት ጥፋት እንደፈጸመ በኦዲት መለየት ተችሏል። በዚህም መሠረት በዲሲፕሊን ኮሚቴ አማካኝነት በማስረጃ የተደገፈ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።
በኦንላይን አፕሊኬሽን ስም ተገልጋዮችን የሚያታልሉ ደላሎችን ለመከላከልም፣ አንድ ሰው ከአንድ ቦታ ሆኖ ከአሥር በላይ ሰዎችን መመዝገብ የማይችልበት ሲስተም ተዘርግቷል። ይህም ደላሎች የቴክኖሎጂ ክፍተትን በመጠቀም ሕዝቡን እንዲበዘብዙ ያለውን ዕድል እንደቀነሰው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ በየጊዜው ራሱን እያዘመነ የሚሄደውን የማጭበርበር ተግባር ለመመከት፣ ቴክኖሎጂውንና የሕግ ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ይህ የሪፎርም ሥራ ተጠናክሮ ሲቀጥል፣ ተገልጋዩ ያለምንም እንግልትና ያለ ተጨማሪ ክፍያ ፓስፖርቱን እቤቱ ሆኖ የሚያገኝበትን አሠራር ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሠራ ተገልጿል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopian #passport
************************
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የዜጎችን እንግልት ለመቀነስና አሠራሩን ለማዘመን በጀመረው የሪፎርም ሥራ፤ ወደፊት ማንኛውም ሰው ከቤቱ ሳይወጣ የፓስፖርት አገልግሎት በዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚያገኝበትን አሰራር ለመፍጠር እየሠራ መሆኑን አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት ከኢቢሲ "ስለ ሀገር" ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ተቋሙ ሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአካሄደው ሪፎርም ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ የያዘውን የዲጂታል አገልግሎት ግብ ለማሳካት ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር ሲስተሙን በማቀናጀት ላይ ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ፤ ይህም ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት በአካል መገኘት ሳያስፈልጋቸው፣ በፋይዳ ሲስተም ላይ ያለውን መረጃ በቀጥታ በመጠቀም አገልግሎቱን በኦንላይን ብቻ እንዲያጠናቅቁ ያስችላቸዋል ብለዋል።
በተቋሙ ውስጥ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከልም ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቁመው፤ ተገልጋዮች ቅሬታ ካላቸው በአካል በተዘጋጁ የአስተያየት መስጫ ዴስኮች ብቻ ሳይሆን፣ በኦንላይን አማራጭ ምስልና ቪዲዮ በማያያዝ ጭምር ማቅረብ የሚችሉበት አሠራር መመቻቸቱን አመልክተዋል።
እያንዳንዱ የተቋሙ ሠራተኛ የኮምፒውተር አጠቃቀም ከአሻራ ጋር የተገናኘ በመሆኑ፣ ማን ምን ዓይነት ሥራ እንደሠራና ምን ዓይነት ጥፋት እንደፈጸመ በኦዲት መለየት ተችሏል። በዚህም መሠረት በዲሲፕሊን ኮሚቴ አማካኝነት በማስረጃ የተደገፈ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ገልጸዋል።
በኦንላይን አፕሊኬሽን ስም ተገልጋዮችን የሚያታልሉ ደላሎችን ለመከላከልም፣ አንድ ሰው ከአንድ ቦታ ሆኖ ከአሥር በላይ ሰዎችን መመዝገብ የማይችልበት ሲስተም ተዘርግቷል። ይህም ደላሎች የቴክኖሎጂ ክፍተትን በመጠቀም ሕዝቡን እንዲበዘብዙ ያለውን ዕድል እንደቀነሰው ተናግረዋል።
አገልግሎቱ በየጊዜው ራሱን እያዘመነ የሚሄደውን የማጭበርበር ተግባር ለመመከት፣ ቴክኖሎጂውንና የሕግ ማስከበር ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። ይህ የሪፎርም ሥራ ተጠናክሮ ሲቀጥል፣ ተገልጋዩ ያለምንም እንግልትና ያለ ተጨማሪ ክፍያ ፓስፖርቱን እቤቱ ሆኖ የሚያገኝበትን አሠራር ለመፍጠር በትኩረት እንደሚሠራ ተገልጿል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopian #passport
14 days ago
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች ተለይተዋል - የቱሪዝም ሚኒስትር
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
23 days ago
ከ15 ሚሊየን በላይ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ያደረገው ሪፎርም…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ በተገበረቻቸው በርካታ ሪፎርሞች በአራት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ15 ሚሊየን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
መንግስት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ባለሁለት አሃዝ ዕድገት ለማስመዝገብ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ የነበረችበትን የቆየ ተደራራቢ የሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ከፍተኛ ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ በለውጡ ዓመታት በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም የመንግሥትንና የግሉን ዘርፍ ሚና በመለየት አዳዲስ የሥራ ገበያዎችንና ዕድሎችን መፍጠር የተቻለ ሲሆን፥ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ኢኮኖሚውን ወደ ፊት እንዲያስፈነጥሩ ልዩ የትብብር ማዕቀፍ ተፈጥሯል።
የግል ዘርፉ የኢኮኖሚው ዋና ሞተር እንዲሆን ለማስቻል ከተወሰዱ ርምጃዎች መካከል አስፈላጊውን የብድር አቅርቦት ጨምሮ የፋይናንስ ማነቆዎችን መፍታት ይጠቀሳል።
ከ2014 እስከ 2017 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ለ15 ሚሊየን ዜጎች ወይም በአማካይ በየዓመቱ 4 ሚሊየን ለሚጠጉ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ለዚህ ውጤት የሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት ምጣኔ ማደግና የውጭ ሀገር የሥራ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ ድርሻ አበርክተዋል።
ለአብነትም ባለፈው በጀት ዓመት በሀገር ውስጥ ለ4 ነጥብ 4 ሚሊየን ዜጎች፣ በውጭ ሀገራት ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው የውጭ ሀገር የርቀት ሥራ ለ57 ሺህ ዜጎች ሥራ መፍጠር ተችሏል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ባለሁለት አሃዝ ዕድገት ለማስመዝገብ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡
በቀጣይም የዜጎችን ክህሎትና ብቃት በማሳደግ፣ የፋይናንስ አቅርቦትን በማመቻቸት እንዲሁም የዲጂታል ምህዳርን በማስፋት ዜጎች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር (በርቀት ጭምር) ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ በተገበረቻቸው በርካታ ሪፎርሞች በአራት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ15 ሚሊየን በላይ ዜጎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
መንግስት የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ባለሁለት አሃዝ ዕድገት ለማስመዝገብ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ የነበረችበትን የቆየ ተደራራቢ የሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ከፍተኛ ርብርብ የሚጠይቅ በመሆኑ በለውጡ ዓመታት በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም የመንግሥትንና የግሉን ዘርፍ ሚና በመለየት አዳዲስ የሥራ ገበያዎችንና ዕድሎችን መፍጠር የተቻለ ሲሆን፥ የግሉ ዘርፍ ተዋንያን ኢኮኖሚውን ወደ ፊት እንዲያስፈነጥሩ ልዩ የትብብር ማዕቀፍ ተፈጥሯል።
የግል ዘርፉ የኢኮኖሚው ዋና ሞተር እንዲሆን ለማስቻል ከተወሰዱ ርምጃዎች መካከል አስፈላጊውን የብድር አቅርቦት ጨምሮ የፋይናንስ ማነቆዎችን መፍታት ይጠቀሳል።
ከ2014 እስከ 2017 በጀት ዓመት በአጠቃላይ ለ15 ሚሊየን ዜጎች ወይም በአማካይ በየዓመቱ 4 ሚሊየን ለሚጠጉ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
ለዚህ ውጤት የሀገር ውስጥ የሥራ ስምሪት ምጣኔ ማደግና የውጭ ሀገር የሥራ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ ድርሻ አበርክተዋል።
ለአብነትም ባለፈው በጀት ዓመት በሀገር ውስጥ ለ4 ነጥብ 4 ሚሊየን ዜጎች፣ በውጭ ሀገራት ከ500 ሺህ በላይ ዜጎች እንዲሁም ለመጀመሪያ ጊዜ በተተገበረው የውጭ ሀገር የርቀት ሥራ ለ57 ሺህ ዜጎች ሥራ መፍጠር ተችሏል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ፍትሐዊነት የሚያረጋግጥ ባለሁለት አሃዝ ዕድገት ለማስመዝገብ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡
በቀጣይም የዜጎችን ክህሎትና ብቃት በማሳደግ፣ የፋይናንስ አቅርቦትን በማመቻቸት እንዲሁም የዲጂታል ምህዳርን በማስፋት ዜጎች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር (በርቀት ጭምር) ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡
24 days ago
የሴቶች እኩልነት በተግባር…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የመደመር ዕሳቤ ለሴቶች እኩልነትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት፣ ለሕፃናት መብት፣ ለደህንነትና ብሩህ ዓለም የሚታገል የጠራ አስተሳሰብ እና ጽኑ አቋም አለው።
ባለፉት ዓመታት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሴቶች የፖለቲካ ተዋናይ እንዲሁም የሀብት ባለቤት እንዲሆኑ በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
ቀደም ሲል ከፖለቲካውና ከኢኮኖሚው ማዕከል ተገልለው የነበሩ ሴቶች በሀገር ግንባታ ሂደት እንደ አጋር እና ተረጂ ሳይሆን እንደ ዋና ባለቤትና አንቀሳቃሽ ኃይል እንዲሆኑ ተደርጓል።
መንግሥት የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ባከናወናቸው ሥራዎች ሕፃናት የምገባና ምቹ የመማሪያ አካባቢዎች ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ለማድረግ ሥራዎችን ጀምሯል።
የእናቶችና የሕፃናት ሆስፒታል፣ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል እንዲሁም የእንጀራ መጋገሪያ ፋብሪካዎችን በመገንባት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል።
“ሴቶች ሲበለጽጉ ሀገር ትበለፅጋለች” የሚለውን መርሕ በተግባር ለማዋል በተደረገው ጥረት ይበል የሚያሰኝ ውጤት የተገኘ ሲሆን፥ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነትን ከተራ ተሳትፎነት ወደ ማዕከላዊ ተዋናይነት ማሳደግ ተችሏል።
የሴቶች ተሳትፎ በፌዴራል ደረጃ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ውክልና 42 በመቶ፤ በክልል ምክር ቤቶች ደግሞ 45 በመቶ ደርሷል።
በአስፈጻሚ ደረጃ ከሚመደቡ የፌዴራል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውስጥ 51 በመቶው ሴቶች ሲሆኑ፥ 30 በመቶው ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተቋማት ኃላፊዎችና አምባሳደሮች ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በአጠቃላይ በዴሞክራሲ ተቋማት፣ በፍርድ ቤቶች፣ በከንቲባነትና በአስተዳዳሪነት ደረጃ በኃላፊነት ተመድበው እንዲሠሩ ተደርጓል።
አሁን ላይ ሴቶች በቤተሰብና በአካባቢ ማሕበረሰብ ውስጥ የመደመጥ እና የመወሰን አቅማቸው 60 በመቶ ደርሷል።
ይህ ተጨባጭ ተሳትፎ በሀገራዊ የፖሊሲ ቀረጻና በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንዲኖራቸው ዕድል ፈጥሯል።
በኢኮኖሚ ዘርፍ በተወሰደው የሪፎርም እርምጃ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ተረጋግጧል።
የሴቶች የባንክ ሒሳብ የመክፈት መጠን ከ20 በመቶ ወደ 43 በመቶ አድጓል።
13 ሚሊየን የሚሆኑት ሴቶች በብድርና ቁጠባ ማሕበራት ተደራጅተው 30 ቢሊየን የሚደርስ ብር ለመቆጠብ የቻሉ ሲሆን፥ 7 ሚሊየን የሚሆኑ ሴቶች ደግሞ የመሬት ባለቤትነታቸው ተረጋግጧል።
የሴቶችን ደህንነት በማረጋገጥ ዙሪያ በተሰራው ሥራ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ ሽልማት እና እውቅና ለማግኘት በቅታለች።
በጤናው ዘርፍ የሴቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ላይ መሠረታዊ ዕድገት የተመዘገበ ሲሆን፤ በትምህርት ዘርፍም የሴቶች ተሳትፎ በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ከወንዶች እኩል ሆኗል።
በዲጂታል ዘርፍ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ድርሻ 49 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 36 በመቶ የሚሆኑት ለፋይናንስ ግብይት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የመደመር ዕሳቤ ለሴቶች እኩልነትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት፣ ለሕፃናት መብት፣ ለደህንነትና ብሩህ ዓለም የሚታገል የጠራ አስተሳሰብ እና ጽኑ አቋም አለው።
ባለፉት ዓመታት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሴቶች የፖለቲካ ተዋናይ እንዲሁም የሀብት ባለቤት እንዲሆኑ በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
ቀደም ሲል ከፖለቲካውና ከኢኮኖሚው ማዕከል ተገልለው የነበሩ ሴቶች በሀገር ግንባታ ሂደት እንደ አጋር እና ተረጂ ሳይሆን እንደ ዋና ባለቤትና አንቀሳቃሽ ኃይል እንዲሆኑ ተደርጓል።
መንግሥት የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ባከናወናቸው ሥራዎች ሕፃናት የምገባና ምቹ የመማሪያ አካባቢዎች ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ለማድረግ ሥራዎችን ጀምሯል።
የእናቶችና የሕፃናት ሆስፒታል፣ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል እንዲሁም የእንጀራ መጋገሪያ ፋብሪካዎችን በመገንባት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል።
“ሴቶች ሲበለጽጉ ሀገር ትበለፅጋለች” የሚለውን መርሕ በተግባር ለማዋል በተደረገው ጥረት ይበል የሚያሰኝ ውጤት የተገኘ ሲሆን፥ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነትን ከተራ ተሳትፎነት ወደ ማዕከላዊ ተዋናይነት ማሳደግ ተችሏል።
የሴቶች ተሳትፎ በፌዴራል ደረጃ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ውክልና 42 በመቶ፤ በክልል ምክር ቤቶች ደግሞ 45 በመቶ ደርሷል።
በአስፈጻሚ ደረጃ ከሚመደቡ የፌዴራል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውስጥ 51 በመቶው ሴቶች ሲሆኑ፥ 30 በመቶው ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተቋማት ኃላፊዎችና አምባሳደሮች ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በአጠቃላይ በዴሞክራሲ ተቋማት፣ በፍርድ ቤቶች፣ በከንቲባነትና በአስተዳዳሪነት ደረጃ በኃላፊነት ተመድበው እንዲሠሩ ተደርጓል።
አሁን ላይ ሴቶች በቤተሰብና በአካባቢ ማሕበረሰብ ውስጥ የመደመጥ እና የመወሰን አቅማቸው 60 በመቶ ደርሷል።
ይህ ተጨባጭ ተሳትፎ በሀገራዊ የፖሊሲ ቀረጻና በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንዲኖራቸው ዕድል ፈጥሯል።
በኢኮኖሚ ዘርፍ በተወሰደው የሪፎርም እርምጃ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ተረጋግጧል።
የሴቶች የባንክ ሒሳብ የመክፈት መጠን ከ20 በመቶ ወደ 43 በመቶ አድጓል።
13 ሚሊየን የሚሆኑት ሴቶች በብድርና ቁጠባ ማሕበራት ተደራጅተው 30 ቢሊየን የሚደርስ ብር ለመቆጠብ የቻሉ ሲሆን፥ 7 ሚሊየን የሚሆኑ ሴቶች ደግሞ የመሬት ባለቤትነታቸው ተረጋግጧል።
የሴቶችን ደህንነት በማረጋገጥ ዙሪያ በተሰራው ሥራ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ ሽልማት እና እውቅና ለማግኘት በቅታለች።
በጤናው ዘርፍ የሴቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ላይ መሠረታዊ ዕድገት የተመዘገበ ሲሆን፤ በትምህርት ዘርፍም የሴቶች ተሳትፎ በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ከወንዶች እኩል ሆኗል።
በዲጂታል ዘርፍ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ድርሻ 49 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 36 በመቶ የሚሆኑት ለፋይናንስ ግብይት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ።
24 days ago
የኢቢሲ የለውጥ ሥራዎች አገርን የሚጠቅሙና ኢትዮጵያዊነትን የሚያንጸባርቁ ናቸው፦ ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
24 days ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኤልሲ አገልግሎት ክፍያዎችን ከዓለም አቀፍ አሠራር ጋር ሊያጣጥም ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ላይ የሚታየውን የወጪ ጫና ለመቀነስ እና የንግድ ፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር፣ የብድር ሰነድ ወይም የኤልሲ አገልግሎት ክፍያዎችን ከዓለም አቀፍ የዋጋ ተመን አሠራር ጋር የሚያጣጥም አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል።
ማዕከላዊ ባንኩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ የንግድ ባንኮች ከኤልሲ ጋር የተያያዙ የአገልግሎት ክፍያዎችን እና ታሪፎችን ቀደም ሲል ከተቀመጠው ከፍተኛ ጣሪያ ሳይሻገሩ፣ በዓመታዊ እና በተመጣጣኝ ስሌት ላይ በመመስረት አንድ ወጥ እንዲያደርጉ ታዟል።
ይህ የጋራ ስሌት አሠራር የባንኮችን የክፍያ ታሪፎች ግልጽና ተወዳዳሪ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የአገልግሎት ክፍያ ማስተካከያ በሀገሪቱ የወጪና ገቢ ንግድ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎችን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ተገልጿል። የክፍያ ተመኖቹ ከዓለም አቀፍ አሠራር ጋር መጣጣማቸው የኢትዮጵያን የንግድ ፋይናንስ ተዓማኒነት ከመጨመሩም በላይ፣ ሀገሪቱ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እያደረገችው ያለውን በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ሪፎርም ስኬታማ ለማድረግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሏል።
Capital
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴ ላይ የሚታየውን የወጪ ጫና ለመቀነስ እና የንግድ ፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር፣ የብድር ሰነድ ወይም የኤልሲ አገልግሎት ክፍያዎችን ከዓለም አቀፍ የዋጋ ተመን አሠራር ጋር የሚያጣጥም አዲስ መመሪያ ይፋ አድርጓል።
ማዕከላዊ ባንኩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ የንግድ ባንኮች ከኤልሲ ጋር የተያያዙ የአገልግሎት ክፍያዎችን እና ታሪፎችን ቀደም ሲል ከተቀመጠው ከፍተኛ ጣሪያ ሳይሻገሩ፣ በዓመታዊ እና በተመጣጣኝ ስሌት ላይ በመመስረት አንድ ወጥ እንዲያደርጉ ታዟል።
ይህ የጋራ ስሌት አሠራር የባንኮችን የክፍያ ታሪፎች ግልጽና ተወዳዳሪ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ የአገልግሎት ክፍያ ማስተካከያ በሀገሪቱ የወጪና ገቢ ንግድ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎችን ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ተገልጿል። የክፍያ ተመኖቹ ከዓለም አቀፍ አሠራር ጋር መጣጣማቸው የኢትዮጵያን የንግድ ፋይናንስ ተዓማኒነት ከመጨመሩም በላይ፣ ሀገሪቱ ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እያደረገችው ያለውን በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ሪፎርም ስኬታማ ለማድረግ ትልቅ እገዛ ይኖረዋል ተብሏል።
Capital
1 month ago
የልማት አስተዳደር ሪፎርሙ ፖሊሲዎች በተናበበ መንገድ እንዲዘጋጁ አስችሏል - የፕላንና ልማት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የተቀናጀ የልማት አስተዳደር ሪፎርም የተለያዩ ፖሊሲዎች በተናበበ መንገድ እንዲዘጋጁ አስችሏል አለ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፡፡
“የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ሐሳብ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ባስመዘገበችው ስኬት ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ጉባኤ ተካሂዷል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃጽዮን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በሀገር ደረጃ የሚታቀዱ እቅዶች እስከታችኛው የአስተዳደር እርከን ድረስ የሚወርዱበት አሰራርና ማዕቀፍ ሊኖር ይገባል፡፡
ባለፉት ጊዜያት ለእቅድ፣ ክትትልና ግምገማ የሚሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ እንደነበር አስታውሰው፥ በዚህም የሀብትና የሰው ኃይል አመዳደብ ችግር እንደነበረበት ጠቅሰዋል፡፡
የአካባቢ አስተዳደሮች ሚናቸው በግልጽ ያልተለየ በመሆኑ በየደረጃው ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ አሰራር አልነበረም ነው ያሉት፡፡
ከይፋዊ ስታቲስቲክስ ባለፈ የእቅድና ግምገማ ሂደቱ እንዲሁም መረጃዎች በአግባቡ የሚያልፉ ባለመሆናቸው ሀሰተኛና የተጋነኑ ሪፖርቶች ለመንግስት ሲቀርቡ ነበር ብለዋል፡፡
እቅድ እና ፋይናንስ ያልተሳሰረበት አሰራርና በዘፈቀደ የሚከናወን የፕሮጀክት አተገባበር ሀገሪቱን ለማክሮ ኢኮኖሚ መናጋት ዳርገው እንደነበር አንስተዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ አመታት በፖሊሲ ሪፎርም እንዲሁም በእቅድና ክትትል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፥ በዚህም ችግሮቹን በተቀናጀ የልማት አስተዳደር መፍታት መቻሉን አስረድተዋል፡፡
የመንግስትን የውሳኔ አሰጣጥ በተጨባጭ መረጃ መደገፍና ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር በቀጣይ በትኩረት የሚሰራባቸው መስኮች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በአቤል ነዋይ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የተቀናጀ የልማት አስተዳደር ሪፎርም የተለያዩ ፖሊሲዎች በተናበበ መንገድ እንዲዘጋጁ አስችሏል አለ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር፡፡
“የመረጃ ሉዓላዊነት ለፖሊሲ ነጻነት'' በሚል መሪ ሐሳብ ኢትዮጵያ በመረጃና በስታቲስቲክስ የሉዓላዊነት ጉዞ ባስመዘገበችው ስኬት ላይ ያተኮረ ሀገራዊ ጉባኤ ተካሂዷል።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃጽዮን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በሀገር ደረጃ የሚታቀዱ እቅዶች እስከታችኛው የአስተዳደር እርከን ድረስ የሚወርዱበት አሰራርና ማዕቀፍ ሊኖር ይገባል፡፡
ባለፉት ጊዜያት ለእቅድ፣ ክትትልና ግምገማ የሚሰጠው ትኩረት ዝቅተኛ እንደነበር አስታውሰው፥ በዚህም የሀብትና የሰው ኃይል አመዳደብ ችግር እንደነበረበት ጠቅሰዋል፡፡
የአካባቢ አስተዳደሮች ሚናቸው በግልጽ ያልተለየ በመሆኑ በየደረጃው ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ አሰራር አልነበረም ነው ያሉት፡፡
ከይፋዊ ስታቲስቲክስ ባለፈ የእቅድና ግምገማ ሂደቱ እንዲሁም መረጃዎች በአግባቡ የሚያልፉ ባለመሆናቸው ሀሰተኛና የተጋነኑ ሪፖርቶች ለመንግስት ሲቀርቡ ነበር ብለዋል፡፡
እቅድ እና ፋይናንስ ያልተሳሰረበት አሰራርና በዘፈቀደ የሚከናወን የፕሮጀክት አተገባበር ሀገሪቱን ለማክሮ ኢኮኖሚ መናጋት ዳርገው እንደነበር አንስተዋል፡፡
ባለፉት የለውጥ አመታት በፖሊሲ ሪፎርም እንዲሁም በእቅድና ክትትል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፥ በዚህም ችግሮቹን በተቀናጀ የልማት አስተዳደር መፍታት መቻሉን አስረድተዋል፡፡
የመንግስትን የውሳኔ አሰጣጥ በተጨባጭ መረጃ መደገፍና ዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር በቀጣይ በትኩረት የሚሰራባቸው መስኮች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በአቤል ነዋይ
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በረከት ፍስሃጽዮን በሰጡት ማብራሪያ ፤ የኢትዮጵያ የልማት አስተዳደር ሪፎርም ሀገሪቱ የምታቅድበትን፣ ክትትል የምታደርግበትንና ውጤት የምታስመዘግብበትን አካሄድ መሠረታዊ በሆነ መልኩ እየቀየረው ይገኛል።
#ethiopia #digitalethiopia #digitaltransformation #governance #techethiopia
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲገነባና ባህል እንዲሆን ምርጫን ብቻ የመንግሥት ማቋቋሚያ አማራጭ አድርጎ መጠቀም የግድ ይላል። ኢትዮጵያ ምርጫን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ የቅርብ ጊዜ ልምምድ ብቻ ነው ያላት። ያውም የዘንድሮው ምርጫ ገና 7ኛዋ ልምምድ ነው። ልምምዱን ከወትሮዎቹ የተሻለ ባህል ለማድረግ ደግሞ ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ በሕዝቦች የነቃ ተሳትፎ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በመንግሥት ትብብር የሚከናወን ሂደት ነው። ይህ ባህልም በሰዎች የአመለካከት እና የአስተሳሰብ ለውጥን በማምጣት ሀገርን ለመገንባት ያግዛል፡፡ ባህሉን መገንባት የሚያስፈልገው ሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ የአስተሳሰብና የተግባር ለውጥ እንዲመጣ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ባህል እንዲገነባ ምርጫ ያስፈልጋል። ይህንን እውን ለማድረግ የመንግሥት መዋቅር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የማህበራት እና የሚዲያዎች ሚናም ወሳኝ ናቸው፡፡
የመንግሥት መዋቅር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እንደ ማዕከል ለማስተባበር ያግዛል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሳትፏቸው ለሀገር የሚጠቅሙ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን በማመንጨት ወሳኝ ናቸው፡፡ ማህበራት ደግሞ በየአደረጃጀቶቻቸው የለውጥ ተሳትፎ በማድረግ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያግዛሉ፡፡
የሚዲያ ተቋማት በሙያዊ ሥነምግባር እና በሕግ በመመራት እውነተኛ መረጃን ለህዝብ በማቅረብ የዴሞክራሲ ባህልን ግንባታን ያሳልጣሉ፡፡ በድምሩ እነዚህ ተቋማት በትብብር እና በቅንጅት በመስራት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ያግዛሉ።
ህዝብም ለሀገር ግንባታ የሚጠቅሙ አስተሣሰቦችን በማራመድ አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በፖለቲካ ሂደት ላይም የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲን ይገነባል፡፡
ባህሉን ለመገንባት ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ ጠንካራ፣ ውጤታማ እና ዘላቂነት ያላቸውን ድርጅቶች ወይም መዋቅሮችን መፍጠር ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ሀገር ወሳኝ ነው፡፡
የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ስለሚረዱ፡፡ ተቋማት ግንባታ በአጠቃላይ በግልጽ ራዕይ እና ተልዕኮ፣ ህጋዊ መዋቅር፣የሰው ኃይል ልማት፣ በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር፣ ግልጽነትንና ተጠያቂነት ፣ቀጣይነትን፣ የተሻሻለ አገልግሎት፣ እምነት የተገነባበት እና ኢንቨስትመንት የሚሳብበት እንዲሆን ያስችላል፡፡
ከተቋማትም የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ደግሞ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ሰብአዊ መብቶችን ለማስከበር እና የዜጎችን እኩል ተሳትፎ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። እነዚህ ተቋማት ገለልተኛ ናቸው፡፡ ይህ አሰራርም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ያደርጋል፡፡
በዚህ ረገድ ምን ምን ሥራዎች ተሠሩ?
1. በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ የምርጫ ቦርድ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና እውነተኛ ምርጫን ለማካሄድ ያስችላል፡፡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም በዚሁ መሠረት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል፡፡ የምርጫ ቦርድ ተግባር የስልጣን ምንጭ የህዝብ ድምጽ ይሁንታ እንጂ ጠብ መንጃ ያለመሆኑን ያረጋግጣል።
2. ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት ተገንብተው ፍርድ ቤቶች እና የሕግ አስከባሪ አካላት በነጻነት እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡ በምርጫ ወቅትም በነጻነት ክትትል በማድረግ ያለ አድልዎ በማገልገል የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነት ያረጋግጣሉ።
3. የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ነጻ ሆኖ የመብት ጥሰቶችን በመከታተል እየተከላከለ፤ ለፍትሕና ርትዕ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህንንም ማረጋገጥ ተችሏል።
4. የዕንባ ጠባቂ ተቋም የመልካም አስተዳደር እጥረቶች እና የሙስና ጉዳዮችን በመመርመር በገለልተኛነት ለሀቅ ይሰራል፡፡
5. መገናኛ ብዙኃን ነፃ ሆነው ለሕዝብ ትክክለኛ መረጃ እንዲያደርሱ በተሰራው የተቋማት ግንባታ ሪፎርም እውን ሆኗል፡፡ በህዝብ እና በመንግሥት መካከል ሚዛናዊ የመረጃ ድልድይ በመሆንም የመንግሥትን አሰራር ፈትሸው የሚታረመው እንዲስተካከል፤ የሚበረታታው ሞዴል እንዲሆን በማሳየት ያቀርባሉ፡፡
6. የፀጥታ ተቋማት ገለልተኛ ሆነው እንዲገነቡ፣ ሁሉንም እኩል እንዲያገለግሉ፣ ከግለሰብ እና ከፓርቲ በላይ ለሀገር ህልውና እንዲቆሙ ተደርገዋል።
እንደነዚህ አይነት ተቋማትን መገንባት የስልጣን ሚዛንን ለመጠበቅ፣ ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ ግልጽነትን ለመፍጠር፣ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ ለማሳደግ ይረዳሉ፡፡
በሕግ አውጪ፣ ተርጓሚ እና አስፈጻሚ መካከል የስልጣን ሚዛንን በመጠበቅ ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ለሚሰጡት ውሳኔ ተጠያቂ መሆናቸውን በማረጋገጥ የመንግሥት አሰራር ለሕዝብ ክፍት እና ግልጽ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ ሕዝቡም በሕግ እና በአስተዳደር ሥርዓቱ ላይ እምነት እንዲኖረው ያስችላሉ፡፡
በመሆኑም መንግሥት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ተቋማትን መገንባት የግድ ነው ብሎ ስላመነ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ የመጀመሪያው የወሰደው የፖለቲካ ቁርጠኝነት ነው፡፡ ቁርጠኛ በመሆንም የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ ይህም ሥራቸውን ያለጣልቃገብነት እንዲከውኑ አግዟቸዋል፡፡ የፋይናንስ፣ የሎጂስቲክስ እና የሰው ኃይል ነጻነት ኖሯቸው በገለልተኛ ሰራተኞች እንዲሰሩም እያደረገ ይገኛል፡፡
እስከ አሁን እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በርካታ ስራዎችን በጋራ ሰርተናል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ ሂደት በመሆኑ ቀጣይ ነው። ስለዚህ የባህሉ መገለጫ በሆነው የዘንድሮ ምርጫ ላይ ካርዳችንን በመጠቀም ይበጀናል የምንለውን ለመምረጥና ሀገር ለማሻገር ተዘጋጅተናል?
እንዘጋጅ! እንምረጥ! በጋራ ሀገር እናሻግር!
በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲገነባና ባህል እንዲሆን ምርጫን ብቻ የመንግሥት ማቋቋሚያ አማራጭ አድርጎ መጠቀም የግድ ይላል። ኢትዮጵያ ምርጫን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ የቅርብ ጊዜ ልምምድ ብቻ ነው ያላት። ያውም የዘንድሮው ምርጫ ገና 7ኛዋ ልምምድ ነው። ልምምዱን ከወትሮዎቹ የተሻለ ባህል ለማድረግ ደግሞ ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ በሕዝቦች የነቃ ተሳትፎ፣ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በመንግሥት ትብብር የሚከናወን ሂደት ነው። ይህ ባህልም በሰዎች የአመለካከት እና የአስተሳሰብ ለውጥን በማምጣት ሀገርን ለመገንባት ያግዛል፡፡ ባህሉን መገንባት የሚያስፈልገው ሁሉም ዜጎች እኩል ተሳትፎ እንዲኖራቸው፣ በጋራ ጉዳዮች ላይ የአስተሳሰብና የተግባር ለውጥ እንዲመጣ ነው፡፡
የዴሞክራሲ ባህል እንዲገነባ ምርጫ ያስፈልጋል። ይህንን እውን ለማድረግ የመንግሥት መዋቅር፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የማህበራት እና የሚዲያዎች ሚናም ወሳኝ ናቸው፡፡
የመንግሥት መዋቅር የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን እንደ ማዕከል ለማስተባበር ያግዛል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተሳትፏቸው ለሀገር የሚጠቅሙ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮችን በማመንጨት ወሳኝ ናቸው፡፡ ማህበራት ደግሞ በየአደረጃጀቶቻቸው የለውጥ ተሳትፎ በማድረግ በዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ያግዛሉ፡፡
የሚዲያ ተቋማት በሙያዊ ሥነምግባር እና በሕግ በመመራት እውነተኛ መረጃን ለህዝብ በማቅረብ የዴሞክራሲ ባህልን ግንባታን ያሳልጣሉ፡፡ በድምሩ እነዚህ ተቋማት በትብብር እና በቅንጅት በመስራት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ያግዛሉ።
ህዝብም ለሀገር ግንባታ የሚጠቅሙ አስተሣሰቦችን በማራመድ አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በፖለቲካ ሂደት ላይም የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ዴሞክራሲን ይገነባል፡፡
ባህሉን ለመገንባት ተቋማትን መፍጠር የግድ ይላል፡፡ ጠንካራ፣ ውጤታማ እና ዘላቂነት ያላቸውን ድርጅቶች ወይም መዋቅሮችን መፍጠር ለአንድ ማህበረሰብ ወይም ሀገር ወሳኝ ነው፡፡
የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ እድገትን ለማረጋገጥ ስለሚረዱ፡፡ ተቋማት ግንባታ በአጠቃላይ በግልጽ ራዕይ እና ተልዕኮ፣ ህጋዊ መዋቅር፣የሰው ኃይል ልማት፣ በቴክኖሎጂ የዘመነ አሰራር፣ ግልጽነትንና ተጠያቂነት ፣ቀጣይነትን፣ የተሻሻለ አገልግሎት፣ እምነት የተገነባበት እና ኢንቨስትመንት የሚሳብበት እንዲሆን ያስችላል፡፡
ከተቋማትም የዴሞክራሲ ተቋማትን መገንባት ደግሞ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ ሰብአዊ መብቶችን ለማስከበር እና የዜጎችን እኩል ተሳትፎ ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው። እነዚህ ተቋማት ገለልተኛ ናቸው፡፡ ይህ አሰራርም ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ግንባር ቀደም ሚና እንዲጫወቱ ያደርጋል፡፡
በዚህ ረገድ ምን ምን ሥራዎች ተሠሩ?
1. በዴሞክራሲ ተቋማት ግንባታ የምርጫ ቦርድ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ዴሞክራሲያዊ እና እውነተኛ ምርጫን ለማካሄድ ያስችላል፡፡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም በዚሁ መሠረት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል፡፡ የምርጫ ቦርድ ተግባር የስልጣን ምንጭ የህዝብ ድምጽ ይሁንታ እንጂ ጠብ መንጃ ያለመሆኑን ያረጋግጣል።
2. ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት ተገንብተው ፍርድ ቤቶች እና የሕግ አስከባሪ አካላት በነጻነት እንዲሰሩ ተደርጓል፡፡ በምርጫ ወቅትም በነጻነት ክትትል በማድረግ ያለ አድልዎ በማገልገል የሂደቱን ዴሞክራሲያዊነት ያረጋግጣሉ።
3. የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ነጻ ሆኖ የመብት ጥሰቶችን በመከታተል እየተከላከለ፤ ለፍትሕና ርትዕ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህንንም ማረጋገጥ ተችሏል።
4. የዕንባ ጠባቂ ተቋም የመልካም አስተዳደር እጥረቶች እና የሙስና ጉዳዮችን በመመርመር በገለልተኛነት ለሀቅ ይሰራል፡፡
5. መገናኛ ብዙኃን ነፃ ሆነው ለሕዝብ ትክክለኛ መረጃ እንዲያደርሱ በተሰራው የተቋማት ግንባታ ሪፎርም እውን ሆኗል፡፡ በህዝብ እና በመንግሥት መካከል ሚዛናዊ የመረጃ ድልድይ በመሆንም የመንግሥትን አሰራር ፈትሸው የሚታረመው እንዲስተካከል፤ የሚበረታታው ሞዴል እንዲሆን በማሳየት ያቀርባሉ፡፡
6. የፀጥታ ተቋማት ገለልተኛ ሆነው እንዲገነቡ፣ ሁሉንም እኩል እንዲያገለግሉ፣ ከግለሰብ እና ከፓርቲ በላይ ለሀገር ህልውና እንዲቆሙ ተደርገዋል።
እንደነዚህ አይነት ተቋማትን መገንባት የስልጣን ሚዛንን ለመጠበቅ፣ ተጠያቂነትን ለማስፈን፣ ግልጽነትን ለመፍጠር፣ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ ለማሳደግ ይረዳሉ፡፡
በሕግ አውጪ፣ ተርጓሚ እና አስፈጻሚ መካከል የስልጣን ሚዛንን በመጠበቅ ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ለሚሰጡት ውሳኔ ተጠያቂ መሆናቸውን በማረጋገጥ የመንግሥት አሰራር ለሕዝብ ክፍት እና ግልጽ እንዲሆን ያደርጋሉ፡፡ ሕዝቡም በሕግ እና በአስተዳደር ሥርዓቱ ላይ እምነት እንዲኖረው ያስችላሉ፡፡
በመሆኑም መንግሥት የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ተቋማትን መገንባት የግድ ነው ብሎ ስላመነ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ የመጀመሪያው የወሰደው የፖለቲካ ቁርጠኝነት ነው፡፡ ቁርጠኛ በመሆንም የሕግ ማሻሻያዎችን በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማት እንዲፈጠሩ አድርጓል፡፡ ይህም ሥራቸውን ያለጣልቃገብነት እንዲከውኑ አግዟቸዋል፡፡ የፋይናንስ፣ የሎጂስቲክስ እና የሰው ኃይል ነጻነት ኖሯቸው በገለልተኛ ሰራተኞች እንዲሰሩም እያደረገ ይገኛል፡፡
እስከ አሁን እንደ ሀገር ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ በርካታ ስራዎችን በጋራ ሰርተናል። የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ደግሞ ሂደት በመሆኑ ቀጣይ ነው። ስለዚህ የባህሉ መገለጫ በሆነው የዘንድሮ ምርጫ ላይ ካርዳችንን በመጠቀም ይበጀናል የምንለውን ለመምረጥና ሀገር ለማሻገር ተዘጋጅተናል?
እንዘጋጅ! እንምረጥ! በጋራ ሀገር እናሻግር!
1 month ago
ሀገራዊ ምክክሩ ለምንሻው ለውጥና ሪፎርም ጠንካራ መሠረት የሚጥል ነው ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ፍላጎት መመለስ የሚችልና ለታለመው ሁለንተናዊ ሪፎርም ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለአለፉት ዓመታት የደከመባቸውን ሥራዎች በግልጽ ሪፖርት ማቅረቡን አድንቀዋል።
ኮሚሽነሮቹ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆነው ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ልክ እንደ ወታደር የገቡትን ቃል በመጠበቃቸውም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢትዮጵያ የውይይትና የመደማመጥ ባህል በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን የጠቀሱት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የምክክር ሒደቱ ከሚያስገኘው ተጨባጭ ውጤት ባሻገር፣ በኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ባህል እንዲዳብርና ዜጎች በውይይት ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትን መንገድ እንደሚያጎለብት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም ለውይይት እንዲህ ያለ ሰፊ ዕድል ተገኝቶ እንደማያውቅ አስታውሰው፤ የምክክር ሒደቱን ለማደናቀፍ ጥረት ማድረግም ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ምክክሩ ከታች ወደ ላይ በሚል መርህ ማኅበረሰቡን በአሳተፈ መልኩ መካሄዱን አድንቀው፤ አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ እንዲሁም ሰፊው ማኅበረሰብ በምክክር ሒደቱ የሚሰጠው ሀሳብ ለተሻለ መፍትሄ እጅግ ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የምክክር ሒደቱ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን ያሳተፈ በመሆኑ፣ ለታለመው ለውጥና ሪፎርም ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት የሕገ-መንግስት ማሻሻያ የሚደረገው የመሪዎችን የስልጣን ዘመን ለማራዘም እንደሆነ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በኢትዮጵያም አሁን ባለው ሕገ-መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርቲው እስከመረጠው ድረስ የስልጣን ጊዜ ገደቡ አልተቀመጠም፤ እኛ ግን ይህ አደገኛ ነው፣ ይገደብ ብለን እየተወያየን ነው ብለዋል።
መንግሥት ስልጣኑን በሕግ ለመገደብ ፈቃደኛ በሆነበት ሁኔታ ላይ በምክክሩ አንሳተፍም የሚሉ ወገኖችም ራሳቸውን ሊጠይቁ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መንግስት የምክክሩን ውጤቶችና ምክረ-ሀሳቦች ተቀብሎ ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆኑን ገልጸው፤ ሒደቱ በተሳለጠ መንገድ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል ገብተዋል፡፡
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ebcdotstream #drabiy #pmethiopia #dialogue
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን ፍላጎት መመለስ የሚችልና ለታለመው ሁለንተናዊ ሪፎርም ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለአለፉት ዓመታት የደከመባቸውን ሥራዎች በግልጽ ሪፖርት ማቅረቡን አድንቀዋል።
ኮሚሽነሮቹ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆነው ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ልክ እንደ ወታደር የገቡትን ቃል በመጠበቃቸውም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በኢትዮጵያ የውይይትና የመደማመጥ ባህል በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን የጠቀሱት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ የምክክር ሒደቱ ከሚያስገኘው ተጨባጭ ውጤት ባሻገር፣ በኢትዮጵያ አዲስ የምክክር ባህል እንዲዳብርና ዜጎች በውይይት ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትን መንገድ እንደሚያጎለብት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ከዚህ ቀደም ለውይይት እንዲህ ያለ ሰፊ ዕድል ተገኝቶ እንደማያውቅ አስታውሰው፤ የምክክር ሒደቱን ለማደናቀፍ ጥረት ማድረግም ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ምክክሩ ከታች ወደ ላይ በሚል መርህ ማኅበረሰቡን በአሳተፈ መልኩ መካሄዱን አድንቀው፤ አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ እንዲሁም ሰፊው ማኅበረሰብ በምክክር ሒደቱ የሚሰጠው ሀሳብ ለተሻለ መፍትሄ እጅግ ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
የምክክር ሒደቱ ከ90 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያንን ያሳተፈ በመሆኑ፣ ለታለመው ለውጥና ሪፎርም ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት የሕገ-መንግስት ማሻሻያ የሚደረገው የመሪዎችን የስልጣን ዘመን ለማራዘም እንደሆነ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በኢትዮጵያም አሁን ባለው ሕገ-መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርቲው እስከመረጠው ድረስ የስልጣን ጊዜ ገደቡ አልተቀመጠም፤ እኛ ግን ይህ አደገኛ ነው፣ ይገደብ ብለን እየተወያየን ነው ብለዋል።
መንግሥት ስልጣኑን በሕግ ለመገደብ ፈቃደኛ በሆነበት ሁኔታ ላይ በምክክሩ አንሳተፍም የሚሉ ወገኖችም ራሳቸውን ሊጠይቁ እንደሚገባ አመልክተዋል።
መንግስት የምክክሩን ውጤቶችና ምክረ-ሀሳቦች ተቀብሎ ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጁ መሆኑን ገልጸው፤ ሒደቱ በተሳለጠ መንገድ እንዲቀጥል አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል ገብተዋል፡፡
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ebcdotstream #drabiy #pmethiopia #dialogue
1 month ago
"አገራዊ ምክክሩ የስልጣን ዘመንን ለመገደብ ጭምር ያለመ ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው አገራዊ ምክክር አንዱ ዋና ዓላማ በሕገ መንግሥቱ ላይ ገደብ ያልተቀመጠለትን የመሪዎች የሥልጣን ዘመን በሕግ ለመገደብ መሆኑን አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
መንግሥት የራሱን ሥልጣን በሕግ ለመገደብ እና ሕዝባዊ ጥያቄዎችን መሠረት ያደረገ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ሥልጣኔ በሕግ ይገደብ እያለ ባለበት ሁኔታ ለዚህ የሚታገሉ አካላት 'አንወያይም' ማለታቸው አግባብ አይደለም" ሲሉ በምክክሩ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ኃይሎችን ተችተዋል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ባከናወነው ተግባር መኩራታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምክክሩ ሂደት ከ90% በላይ ኢትዮጵያውያንን ያሳተፈ በመሆኑ ለታለመው ሪፎርም ጠንካራ መሠረት እንደሚጥል እምነታቸውን ገልጸዋል።
(93 በመቶ የሚሆነውን የአገሪቱን አካባቢዎች) የአጀንዳ ልየታና ማሰባሰብ ሥራውን አጠናቋል።
በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በክልሉ ውስጥ ቀጥታ እንቅስቃሴ ማድረግ ባይቻልም በአዲስ አበባና በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችንና ባለድርሻ አካላትን ማሳተፍ መቻሉ ተገልጿል።
በቀጣይም አገራዊ ምክክሩን በማካሄድ የተደረሰባቸውን ስምምነቶችና ምክረ ሃሳቦች ወደ ትግበራ ለማስገባት እንደሚሠራ ኮሚሽኑ አስታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው አገራዊ ምክክር አንዱ ዋና ዓላማ በሕገ መንግሥቱ ላይ ገደብ ያልተቀመጠለትን የመሪዎች የሥልጣን ዘመን በሕግ ለመገደብ መሆኑን አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት የአገራዊ ምክክር ኮሚሽን የግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት ነው።
መንግሥት የራሱን ሥልጣን በሕግ ለመገደብ እና ሕዝባዊ ጥያቄዎችን መሠረት ያደረገ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ሥልጣኔ በሕግ ይገደብ እያለ ባለበት ሁኔታ ለዚህ የሚታገሉ አካላት 'አንወያይም' ማለታቸው አግባብ አይደለም" ሲሉ በምክክሩ ላይ ያልተሳተፉ የፖለቲካ ኃይሎችን ተችተዋል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ባከናወነው ተግባር መኩራታቸውን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የምክክሩ ሂደት ከ90% በላይ ኢትዮጵያውያንን ያሳተፈ በመሆኑ ለታለመው ሪፎርም ጠንካራ መሠረት እንደሚጥል እምነታቸውን ገልጸዋል።
(93 በመቶ የሚሆነውን የአገሪቱን አካባቢዎች) የአጀንዳ ልየታና ማሰባሰብ ሥራውን አጠናቋል።
በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ በክልሉ ውስጥ ቀጥታ እንቅስቃሴ ማድረግ ባይቻልም በአዲስ አበባና በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችንና ባለድርሻ አካላትን ማሳተፍ መቻሉ ተገልጿል።
በቀጣይም አገራዊ ምክክሩን በማካሄድ የተደረሰባቸውን ስምምነቶችና ምክረ ሃሳቦች ወደ ትግበራ ለማስገባት እንደሚሠራ ኮሚሽኑ አስታውቋል።
1 month ago
የተቋማት ግንባታ ለሀገር ልዕልና…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አንድ ሀገር ጠንካራ እና ተከታታይነት ያለውን ዕድገት ማስመዝገብ የሚችለው ጠንካራ ተቋማት ሲኖሩ እንደሆነ እሙን ነው።
በዚህም ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ምሰሶ በመሆን የዜጎች እኩልና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።
በተለይም የፀጥታ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ለዚህ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚሁም ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የሚያስችል መሰረት መጣል ተችሏል።
ተቋማቱ በአመራርና በሰው ኃይል የተጠናከሩ፣ አቅማቸው በቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ በደኅንነት መሰረታዊና አንኳር ክህሎቶች የፈረጠሙ እና በዴሞክራሲያዊ መሰረት ላይ የታነፁ ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
በውጤቱም ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የቆሙ፣ ወገንተኝነታቸው ለህግ ብቻ የሆኑ፣ ጠላቶች ኢትዮጵያ ላይ ፈፅሞ ክፉ እንዳያስቡ የሚያደርጉ፣ ለሀገር ጋሻ እና ጥላ የሆኑ ተቋማት ተገንብተዋል።
በተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች በዘርፉ የሚስተዋሉ ስጋቶችን ከመቀልበስ ባሻገር ቀድሞ ችግሮችን በመለየትና አዝማሚያዎችን በመተንተን ድንገተኛ የሚባሉ የደኅንነትና የፀጥታ ክፍተቶችን ማስቀረት እየተቻለም ይገኛል።
በተጨማሪም ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደረገው ሪፎርም ውትድርና ጀግኖች የሚመርጡት ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት ዋጋ የሚከፈልበት የተከበረ ሙያ መሆን ችሏል።
በዚህም ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመናዊ ትጥቅን በማሟላት የሀገርን ተጋላጭነት ማስቀረት የሚችል አስተማማኝ ኃይል ማድረግ ተችሏል።
ለዚህም የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ እና የድሮን ቴክኖሎጂዎችን የሚያመርተው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በመገንባት ስራ መጀመራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
እንዲሁም ኢትዮጵያ ከዘመኑ ጋር መጓዝ እንድትችል መንግሥት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በማቋቋም ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል።
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ዘርፍ ሲሆን÷ የሰዎችን ህይወት ቀላል በማድረግ በተለያዩ ዘርፎች ለተለያዩ ዓለማ በመዋል ላይ ይገኛል።
ኢትዮጵያም የዘርፉን ሚና በመገንዘብ ተቋም በመገንባት "ኤአይ ለሁሉም" በሚል መሪ ሐሳብ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ከጫፍ ደርሳለች።
በተጨማሪም መንግሥት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም ማድረጉ የሚታወስ ነው።
በአድማሱ አራጋው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አንድ ሀገር ጠንካራ እና ተከታታይነት ያለውን ዕድገት ማስመዝገብ የሚችለው ጠንካራ ተቋማት ሲኖሩ እንደሆነ እሙን ነው።
በዚህም ተቋማት ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ምሰሶ በመሆን የዜጎች እኩልና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።
በተለይም የፀጥታ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ሪፎርም ለዚህ ትልቅ ሚና ያላቸው ሲሆን÷ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚሁም ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር የሚያስችል መሰረት መጣል ተችሏል።
ተቋማቱ በአመራርና በሰው ኃይል የተጠናከሩ፣ አቅማቸው በቴክኖሎጂ የበለፀገ፣ በደኅንነት መሰረታዊና አንኳር ክህሎቶች የፈረጠሙ እና በዴሞክራሲያዊ መሰረት ላይ የታነፁ ነፃ፣ ገለልተኛ እና ብቃት ያላቸው እንዲሆኑ ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።
በውጤቱም ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም የቆሙ፣ ወገንተኝነታቸው ለህግ ብቻ የሆኑ፣ ጠላቶች ኢትዮጵያ ላይ ፈፅሞ ክፉ እንዳያስቡ የሚያደርጉ፣ ለሀገር ጋሻ እና ጥላ የሆኑ ተቋማት ተገንብተዋል።
በተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች በዘርፉ የሚስተዋሉ ስጋቶችን ከመቀልበስ ባሻገር ቀድሞ ችግሮችን በመለየትና አዝማሚያዎችን በመተንተን ድንገተኛ የሚባሉ የደኅንነትና የፀጥታ ክፍተቶችን ማስቀረት እየተቻለም ይገኛል።
በተጨማሪም ከሀገራዊ ለውጡ ማግስት መከላከያ ሠራዊትን ጨምሮ በፀጥታና ደኅንነት ተቋማት በተደረገው ሪፎርም ውትድርና ጀግኖች የሚመርጡት ለሀገር ሉዓላዊ አንድነት ዋጋ የሚከፈልበት የተከበረ ሙያ መሆን ችሏል።
በዚህም ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዘመናዊ ትጥቅን በማሟላት የሀገርን ተጋላጭነት ማስቀረት የሚችል አስተማማኝ ኃይል ማድረግ ተችሏል።
ለዚህም የሆሚቾ ጥይት ፋብሪካ እና የድሮን ቴክኖሎጂዎችን የሚያመርተው ስካይዊን ኤሮኖቲክስ ኢንዱስትሪ በመገንባት ስራ መጀመራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
እንዲሁም ኢትዮጵያ ከዘመኑ ጋር መጓዝ እንድትችል መንግሥት የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በማቋቋም ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል።
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በፍጥነት እያደገ የሚገኝ ዘርፍ ሲሆን÷ የሰዎችን ህይወት ቀላል በማድረግ በተለያዩ ዘርፎች ለተለያዩ ዓለማ በመዋል ላይ ይገኛል።
ኢትዮጵያም የዘርፉን ሚና በመገንዘብ ተቋም በመገንባት "ኤአይ ለሁሉም" በሚል መሪ ሐሳብ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም ከጫፍ ደርሳለች።
በተጨማሪም መንግሥት በጸጥታ አካላት፣ በሰብዓዊ መብት ተቋማት፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ አካላትና በሌሎች የዴሞክራሲ ተቋማት ላይ ሪፎርም ማድረጉ የሚታወስ ነው።
በአድማሱ አራጋው
1 month ago
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ10 ወራት ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ
*****************
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 10 ወራት ውስጥ ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) የ10 ወራት የእቅድ አፈጻጸምን አስመልክተው ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ተቋሙ የሪፎርም እና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርን በመከተሉ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ በሪፎርም ስራዎች እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረጉ፣ በማጭበርበር ምክንያት ሊጠፋ የነበረና ሀገር ልታጣው የነበረ 256.7 ቢሊዮን ብር በጥቅሉ ወደ ገቢ መቀየር መቻሉን ገልጿል።
በበጀት ዓመቱ 725 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ፣ በ10 ወራት ውስጥ ብቻ ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ258 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተመላክቷል።
ለዚህ ስኬታማ አፈጻጸም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እና የተቋሙ አዲስ አደረጃጀት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ ከገቢ እና ወጪ ኮንትሮባንድ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ 23.1 ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች (አልባሳት፣ ማዕድናት፣ መድኃኒቶች፣ ኮስሞቲክስና ኤሌክትሮኒክስ) ተይዘው ገቢ ተደርገዋል። በድንገተኛ ፍተሻና ቁጥጥር ብቻ 2.8 ቢሊዮን ብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
የሕግ ማስከበር ስራውን በተመለከተም፣ በሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማሩ 1,295 ኮንትሮባንዲስቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለሕግ ማቅረብ መቻሉ ተረጋግጧል።
ኮሚሽኑ የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለማበረታታትና ኢንቨስትመንትን ለመደገፍ በሚያደርገው ጥረት፣ ለዘርፉ የሚውል 328.5 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉንም ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
በቀሪዎቹ የበጀት ዓመቱ ወራትም ሕገ-ወጥ ዝውውርን በመከላከል እና የመንግስትን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ረገድ የተጀመረው ውጤታማ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮሚሽኑ አስታውቋል።
በሂሩት እምቢአለ
#ebcdotream #customscommission #revenue
*****************
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 10 ወራት ውስጥ ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) የ10 ወራት የእቅድ አፈጻጸምን አስመልክተው ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ተቋሙ የሪፎርም እና በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርን በመከተሉ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ በሪፎርም ስራዎች እና በቴክኖሎጂ የታገዘ ጥብቅ ቁጥጥር በማድረጉ፣ በማጭበርበር ምክንያት ሊጠፋ የነበረና ሀገር ልታጣው የነበረ 256.7 ቢሊዮን ብር በጥቅሉ ወደ ገቢ መቀየር መቻሉን ገልጿል።
በበጀት ዓመቱ 725 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ፣ በ10 ወራት ውስጥ ብቻ ከ600 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ258 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ተመላክቷል።
ለዚህ ስኬታማ አፈጻጸም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እና የተቋሙ አዲስ አደረጃጀት ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ ከገቢ እና ወጪ ኮንትሮባንድ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ 23.1 ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች (አልባሳት፣ ማዕድናት፣ መድኃኒቶች፣ ኮስሞቲክስና ኤሌክትሮኒክስ) ተይዘው ገቢ ተደርገዋል። በድንገተኛ ፍተሻና ቁጥጥር ብቻ 2.8 ቢሊዮን ብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
የሕግ ማስከበር ስራውን በተመለከተም፣ በሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማሩ 1,295 ኮንትሮባንዲስቶችን በቁጥጥር ስር በማዋል ለሕግ ማቅረብ መቻሉ ተረጋግጧል።
ኮሚሽኑ የሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን ለማበረታታትና ኢንቨስትመንትን ለመደገፍ በሚያደርገው ጥረት፣ ለዘርፉ የሚውል 328.5 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉንም ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
በቀሪዎቹ የበጀት ዓመቱ ወራትም ሕገ-ወጥ ዝውውርን በመከላከል እና የመንግስትን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ ረገድ የተጀመረው ውጤታማ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮሚሽኑ አስታውቋል።
በሂሩት እምቢአለ
#ebcdotream #customscommission #revenue
1 month ago
የኢትዮጵያ የህትመት ዘርፍ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት ሰፊ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነውበታል ተባለ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መሳፍንት ተፈራ እንደገለጹት የሀገሪቱ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸውና ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደተጠቆመው የሪፎርሙ ቀዳሚ ተግባር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የነበሩ ተቋማዊ ችግሮችን በመለየት ተገቢውን መፍትሄ መስጠት ነበር፡፡
በተለይም የይዘት ጥራትን ማሻሻልና ብዝሀነትን ማረጋገጥ፣ ተቋሙን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ የህትመት ውጤቶችን ተደራሽነትና ስርጭት ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትና መዋቅር መፍጠር የሪፎርሙ ዋና ዋና ግቦች ነበሩ፡፡
እነዚህ በመንግስት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት ከዘርፉ እድገት ባለፈ የሀገሪቱን የጋራ ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ተመላክቷል፡፡
#የኢትዮጵያፕሬስድርጅት #ሚዲያ #ህትመት #ሪፎርም #የሚዲያእመርታ #መረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መሳፍንት ተፈራ እንደገለጹት የሀገሪቱ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸውና ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደተጠቆመው የሪፎርሙ ቀዳሚ ተግባር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የነበሩ ተቋማዊ ችግሮችን በመለየት ተገቢውን መፍትሄ መስጠት ነበር፡፡
በተለይም የይዘት ጥራትን ማሻሻልና ብዝሀነትን ማረጋገጥ፣ ተቋሙን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ የህትመት ውጤቶችን ተደራሽነትና ስርጭት ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትና መዋቅር መፍጠር የሪፎርሙ ዋና ዋና ግቦች ነበሩ፡፡
እነዚህ በመንግስት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት ከዘርፉ እድገት ባለፈ የሀገሪቱን የጋራ ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ተመላክቷል፡፡
#የኢትዮጵያፕሬስድርጅት #ሚዲያ #ህትመት #ሪፎርም #የሚዲያእመርታ #መረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
በለውጡ ዋዜማ የሚዲያ ተቋማት በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ነበሩ - ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ
#ethiopia | ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ የነበሩ የሚዲያ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ነበሩባቸው ሲሉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።
እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ማብራሪያ ከሆነ በመገናኛ ብዙኃን ዘርፉ ላይ የታዩት ስብራቶች በፖሊሲና በሕግ ማዕቀፎች፣ በመዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንዲሁም በተቋማዊና በሙያዊ ሥነ ምግባር የታዩ ጉድለቶች የሚጠቀሱ ናቸው።
መንግሥት እነዚህን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ጥልቀት ያላቸው የሚዲያ ማሻሻያዎችን ተግባራዊ አድርጓል።
ከነዚህም ስኬቶች መካከል የባለሥልጣኑ ተጠሪነት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሆን መደረጉ፣ የጋራ ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱ እና ዘርፉ ራሱን በራሱ እንዲመራ የሚያስችሉ የሙያ ማኅበራት ቁጥር እንዲጨምር መደረጉ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
የተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የሚያሳዩ አሃዛዊ መረጃዎች አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ከለውጡ በፊት ከነበረበት 122 ወደ 310 አድጓል።
የሬድዮ ጣቢያዎች ቁጥር ከ52 ወደ 126 ከፍ ሲል፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ደግሞ ከ25 ወደ 128 ደርሰዋል።
በተጨማሪም የሚዲያ የቋንቋ ተደራሽነት ከ39 ወደ 60 ማደጉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ የሚዲያ ምህዳር ሁሉንም አካታች መሆኑን የሚያሳዩት 35 የውጭ መገናኛ ብዙኃን እና 50 የማኅበረሰብ ሚዲያዎች ፈቃድ አግኝተው ወደ ሥራ መግባታቸው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ አጽንኦት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#መገናኛብዙኃን #ሚዲያ #ሪፎርም #ኢትዮጵያ #ዜና #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ የነበሩ የሚዲያ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ነበሩባቸው ሲሉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ ገለጹ።
እንደ ዋና ዳይሬክተሯ ማብራሪያ ከሆነ በመገናኛ ብዙኃን ዘርፉ ላይ የታዩት ስብራቶች በፖሊሲና በሕግ ማዕቀፎች፣ በመዋቅራዊ አደረጃጀቶች እንዲሁም በተቋማዊና በሙያዊ ሥነ ምግባር የታዩ ጉድለቶች የሚጠቀሱ ናቸው።
መንግሥት እነዚህን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ጥልቀት ያላቸው የሚዲያ ማሻሻያዎችን ተግባራዊ አድርጓል።
ከነዚህም ስኬቶች መካከል የባለሥልጣኑ ተጠሪነት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሆን መደረጉ፣ የጋራ ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋቱ እና ዘርፉ ራሱን በራሱ እንዲመራ የሚያስችሉ የሙያ ማኅበራት ቁጥር እንዲጨምር መደረጉ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
የተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የሚያሳዩ አሃዛዊ መረጃዎች አቅርበዋል። አጠቃላይ የመገናኛ ብዙኃን ቁጥር ከለውጡ በፊት ከነበረበት 122 ወደ 310 አድጓል።
የሬድዮ ጣቢያዎች ቁጥር ከ52 ወደ 126 ከፍ ሲል፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ደግሞ ከ25 ወደ 128 ደርሰዋል።
በተጨማሪም የሚዲያ የቋንቋ ተደራሽነት ከ39 ወደ 60 ማደጉ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ የሚዲያ ምህዳር ሁሉንም አካታች መሆኑን የሚያሳዩት 35 የውጭ መገናኛ ብዙኃን እና 50 የማኅበረሰብ ሚዲያዎች ፈቃድ አግኝተው ወደ ሥራ መግባታቸው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ኃይማኖት ዘለቀ አጽንኦት ሰጥተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#መገናኛብዙኃን #ሚዲያ #ሪፎርም #ኢትዮጵያ #ዜና #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
መገናኛ ብዙኃን የጋራ ማንነትን የሚገነቡና ለሀገራዊ ግቦች በቁርጠኝነት መስራት አለባቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የጋራ ማንነትን የሚገነቡና ለሀገራዊ ግቦች በቁርጠኝነት የሚሰሩ መሆን አለባቸው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በለውጡ ዓመታት በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ በተደረገው ሪፎርም የሚታይ ለውጥ ተመዝግቧል።
የለውጡ መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ አቅምን ለማሳደግና ነፃና ገለልተኛ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትን ለመፍጠር በሙያቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችን መፍታት የመጀመሪያው ርምጃ እንደነበር አስታውሰዋል።
በሙያቸው ምክንያት ተዘግተው የቆዩና ወደ ሀገር ቤት ገብተው እንዳይሠሩ የተከለከሉ መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች ወደ ሀገራቸው መጥተው እንዲሠሩ ተፈቅዶላቸዋል ብለዋል።
ከዚህም ባለፈ በመገናኛ ብዙኃን ሪፎርሙ ከውጭ ሆነው የሚዘግቡ መገናኛ ብዙሃን ይጠለፉ (ጃም ይደረጉ) የነበረበትን አሠራር ማስቀረት እንደተቻለ ጠቁመው÷ በለውጡ መንግሥት የፀረ-ሽብር አዋጁን ጨምሮ ሌሎች አሳሪ ሕጎች ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት ሲከፈት ወደ ሙያው ለመግባት የተቸገሩና ነፃነታቸውን ማስተዳደር ያልቻሉ ባለሙያዎች በመፈጠራቸው ለዘርፉ ፈተና እንደሆኑ ገልጸዋል።
በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ባይፈቱም መልካም ሥራዎች ተከናውነዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ያዩትንና የሰሙትን እውነት የሚዘግቡ መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል።
የጋራ ማንነትን የሚገነቡ መሆን እንዳለባቸው ገልጸው÷ መገናኛ ብዙሃን በቅንጅት ለማወያየት የበለጠ ክፍት መሆን እንዳለባቸው ነው የገለጹት።
የሃይማኖት፣ የፖለቲካና የሌሎችም ዘርፎች ዋልታ ረገጥነት ቀርቶ ሚዛናዊነት መንገስ እንዳለበትም አሳስበዋል።
ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ በቂ ጥላቻ፣ መናናቅና መከፋፈል ተዘርቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ አሁን መገናኛ ብዙሃን በአንድነትና የተሳሳቱ ትርክቶችን ማቅናት ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ገልጸዋል።
መገናኛ ብዙኃን የዘገባ ዓላማን፣ አተያይን፣ ሙያዊ ብቃትን እንዲሁም ቅርበትን መሠረት አድርገው መሥራት ይገባቸዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የጋራ ማንነትን የሚገነቡና ለሀገራዊ ግቦች በቁርጠኝነት የሚሰሩ መሆን አለባቸው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎች የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በለውጡ ዓመታት በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ በተደረገው ሪፎርም የሚታይ ለውጥ ተመዝግቧል።
የለውጡ መንግሥት የመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ አቅምን ለማሳደግና ነፃና ገለልተኛ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትን ለመፍጠር በሙያቸው ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችን መፍታት የመጀመሪያው ርምጃ እንደነበር አስታውሰዋል።
በሙያቸው ምክንያት ተዘግተው የቆዩና ወደ ሀገር ቤት ገብተው እንዳይሠሩ የተከለከሉ መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች ወደ ሀገራቸው መጥተው እንዲሠሩ ተፈቅዶላቸዋል ብለዋል።
ከዚህም ባለፈ በመገናኛ ብዙኃን ሪፎርሙ ከውጭ ሆነው የሚዘግቡ መገናኛ ብዙሃን ይጠለፉ (ጃም ይደረጉ) የነበረበትን አሠራር ማስቀረት እንደተቻለ ጠቁመው÷ በለውጡ መንግሥት የፀረ-ሽብር አዋጁን ጨምሮ ሌሎች አሳሪ ሕጎች ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል ብለዋል።
ይሁን እንጂ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት ሲከፈት ወደ ሙያው ለመግባት የተቸገሩና ነፃነታቸውን ማስተዳደር ያልቻሉ ባለሙያዎች በመፈጠራቸው ለዘርፉ ፈተና እንደሆኑ ገልጸዋል።
በመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ባይፈቱም መልካም ሥራዎች ተከናውነዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ያዩትንና የሰሙትን እውነት የሚዘግቡ መሆን እንዳለባቸው ተናግረዋል።
የጋራ ማንነትን የሚገነቡ መሆን እንዳለባቸው ገልጸው÷ መገናኛ ብዙሃን በቅንጅት ለማወያየት የበለጠ ክፍት መሆን እንዳለባቸው ነው የገለጹት።
የሃይማኖት፣ የፖለቲካና የሌሎችም ዘርፎች ዋልታ ረገጥነት ቀርቶ ሚዛናዊነት መንገስ እንዳለበትም አሳስበዋል።
ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ በቂ ጥላቻ፣ መናናቅና መከፋፈል ተዘርቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ አሁን መገናኛ ብዙሃን በአንድነትና የተሳሳቱ ትርክቶችን ማቅናት ላይ ማተኮር እንዳለባቸው ገልጸዋል።
መገናኛ ብዙኃን የዘገባ ዓላማን፣ አተያይን፣ ሙያዊ ብቃትን እንዲሁም ቅርበትን መሠረት አድርገው መሥራት ይገባቸዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሪፎርሙ ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል፡- አቶ ሰይፈ ደርቤ
************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰይፈ ደርቤ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፣ ተቋሙ ከምስረታው ባልተናነሰ ሁኔታ በለውጡ መንግሥት በተከናወነው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት እንደሚቻል ገልጸዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስኪያጁ ገለጻ፤ የተከናወነው የእሳቤ፣ የሕግ፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ተቋሙ በአፍሪካ ደረጃ አስተማማኝና ተፅዕኖ ፈጣሪ የዜና ምንጭ እንዲሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ይህ የሪፎርም እርምጃ ድርጅቱ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ አቅም እንዲላበስ ማድረጉንም አቶ ሰይፈ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ ተደራሽነቱን በማስፋትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ራሱን በማደራጀት፣ ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ ድምፅ በመሆን የወል ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ena #ethiopia #mediareform #nationalnarrative #mediaexcellence
************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት "የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰይፈ ደርቤ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፣ ተቋሙ ከምስረታው ባልተናነሰ ሁኔታ በለውጡ መንግሥት በተከናወነው ዘርፈ ብዙ ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት እንደሚቻል ገልጸዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስኪያጁ ገለጻ፤ የተከናወነው የእሳቤ፣ የሕግ፣ የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ተቋሙ በአፍሪካ ደረጃ አስተማማኝና ተፅዕኖ ፈጣሪ የዜና ምንጭ እንዲሆን ማስቻሉን ጠቁመዋል።
ይህ የሪፎርም እርምጃ ድርጅቱ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅና ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚያስችል ጠንካራ አቅም እንዲላበስ ማድረጉንም አቶ ሰይፈ አብራርተዋል።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ ተደራሽነቱን በማስፋትና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ራሱን በማደራጀት፣ ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ ድምፅ በመሆን የወል ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #ena #ethiopia #mediareform #nationalnarrative #mediaexcellence
1 month ago
ኢዜአ መንግሥት ባደረገው ሪፎርም ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል - አቶ ሰይፈ ደርቤ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከምስረታው ባልተናነሰ የለውጡ መንግሥት በዘርፉና በተቋሙ ባደረገው ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል አሉ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰይፈ ደርቤ።
አቶ ሰይፈ ደርቤ ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በተሰኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደገለጹት÷ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከምስረታው ባልተናነሰ የለውጡ መንግሥት በዘርፉና በተቋሙ ባደረገው ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል።
የተከናወነው የእሳቤ፣ የህግና አደረጃጀት እንዲሁም የአሰራር ሪፎርም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን በአፍሪካ አስተማማኝና ተጽዕኖ ፈጣሪ የዜና ምንጭ በመሆን ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል አቅም እንዲላበስ አስችሎታልም ነው ያሉት።
ተቋሙ ተደራሽነቱን በማስፋት፣ በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ፣ ከኢትዮጵያ ተሻግሮ የአፍሪካ ድምጽ በመሆን የወል ትርክትን እየገነባ ይገኛል ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከምስረታው ባልተናነሰ የለውጡ መንግሥት በዘርፉና በተቋሙ ባደረገው ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል አሉ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰይፈ ደርቤ።
አቶ ሰይፈ ደርቤ ''የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ'' በተሰኘው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደገለጹት÷ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ከምስረታው ባልተናነሰ የለውጡ መንግሥት በዘርፉና በተቋሙ ባደረገው ሪፎርም ምክንያት ዳግም ተወልዷል ማለት ይቻላል።
የተከናወነው የእሳቤ፣ የህግና አደረጃጀት እንዲሁም የአሰራር ሪፎርም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን በአፍሪካ አስተማማኝና ተጽዕኖ ፈጣሪ የዜና ምንጭ በመሆን ብሔራዊ ጥቅምን ማስጠበቅና ብሄራዊ መግባባት መፍጠር የሚያስችል አቅም እንዲላበስ አስችሎታልም ነው ያሉት።
ተቋሙ ተደራሽነቱን በማስፋት፣ በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ፣ ከኢትዮጵያ ተሻግሮ የአፍሪካ ድምጽ በመሆን የወል ትርክትን እየገነባ ይገኛል ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል።
Comments