የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም ማሳያ ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግሥት ቀልጣፋ፣ ተዓማኒና ቀጣይነት ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም ማሳያ ነው አሉ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ የወልድያ ከተማ መሶብ ዘመናዊ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በዛሬው ዕለት መርቀን በይፋ ስራ አስጀምረናል ብለዋል።
10 days ago