8 days ago
ኢትዮጵያዊያን - ቀይ ባህር፣ መካ፣ አረፋከዶክተር ኢድሪስ መሐመድ ጋር የተደረገ ልዩ የአረፋ በዓል ቆይታ
#አረፋ #ኢድአላደሃ #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #eidaladha #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #فانا_عربي_بودكاست
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#አረፋ #ኢድአላደሃ #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #eidaladha #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #فانا_عربي_بودكاست
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
8 days ago
9 days ago
የኢቢሲ የለውጥ ሥራዎች አገርን የሚጠቅሙና ኢትዮጵያዊነትን የሚያንጸባርቁ ናቸው፦ ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
9 days ago
ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ይልቅ ለሀገርና ለሉዓላዊነት ቅድሚያ በመስጠት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የዐረፋን በዓል ታሪካዊ ዳራ በማስታወስ፣ ወስነብዩ ኢብራሂም ልጃቸውን እስማኤልን ለመስዋዕትነት ለማቅረብ ያሳዩትን ቆራጥነት እንደ ትልቅ ማሳያ ጠቅሰዋል።
"ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ጠንካራና ጽኑ ሀገር መሆን የምትችለው የሚወዱትን ነገር ሳይቀር ለሀገራቸው ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም "የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም 'ሀገርነት እና ሉዓላዊነት' ይሰኛል" በማለት፣ ሉዓላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆምና በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ የበለጸገች ሀገር ሆና እንድትወጣ የሚመኙ ሁሉ ምኞታቸውን በተግባር እንዲገልጹ፣ ድህነትን ለማሸነፍና የሀገርን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
"ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዋዕት ለመሆን አናመንታ" ሲሉም ጠንካራ ሀገራዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#eidaladha #pmabiyahmed #ethiopia #patriotism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ይልቅ ለሀገርና ለሉዓላዊነት ቅድሚያ በመስጠት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የዐረፋን በዓል ታሪካዊ ዳራ በማስታወስ፣ ወስነብዩ ኢብራሂም ልጃቸውን እስማኤልን ለመስዋዕትነት ለማቅረብ ያሳዩትን ቆራጥነት እንደ ትልቅ ማሳያ ጠቅሰዋል።
"ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ጠንካራና ጽኑ ሀገር መሆን የምትችለው የሚወዱትን ነገር ሳይቀር ለሀገራቸው ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም "የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም 'ሀገርነት እና ሉዓላዊነት' ይሰኛል" በማለት፣ ሉዓላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆምና በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ የበለጸገች ሀገር ሆና እንድትወጣ የሚመኙ ሁሉ ምኞታቸውን በተግባር እንዲገልጹ፣ ድህነትን ለማሸነፍና የሀገርን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
"ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዋዕት ለመሆን አናመንታ" ሲሉም ጠንካራ ሀገራዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#eidaladha #pmabiyahmed #ethiopia #patriotism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
9 days ago
ኢትዮጵያዊያን - ቀይ ባሕር፣ መካ፣ አረፋ
ነገ በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#አረፋ #ኢድአላደሃ #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #eidaladha #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #فانا_عربي_بودكاست
9 days ago
የነፍስ ተናፋቂው ጥሪ፤ ሐጅ የሙስሊሞች የሕይወት ዘመን ታላቅ መንፈሳዊ ሕልምና የዒባዳ ማዕዘን
#ethiopia | ሐጅ... የአላህ (ሱ.ወ) ቤት ወደሆነችውና የሙዕሚኖች ልብ ዘወትር ወደምትናፍቃት ቅድስት መካ የሚደረግ፣ በአካል ለቻለና አቅም ላለው ሙስሊም ሁሉ በሕይወት ዘመን አንድ ጊዜ የመፈጸም ግዴታ ያለበት አምስተኛው የእስልምና ማዕዘን ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ የግል መንፈሳዊ ጥንካሬን ማደሻ ብቻ ሳይሆን፣ የታማኝነት እና የዓለም አቀፋዊ የእስልምና አንድነት ከፍተኛ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ምድራዊ ማዕረግና የሀብት ልዩነትን ሁሉ አውልቀው፣ ተመሳሳይ ነጭ ኢሕራም ለብሰው በአንድነት ሲቆሙ ፍጹም የእኩልነት እና የወንድማማችነት ትርጉም በተግባር ይገለጻል።
ይህ ሥርዓት ከዘመናት በፊት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩትን መንገዶች በመከተል የሚከናወን ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተግባር ከነቢዩ ኢብራሂምና (ረ.ወ) ከነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ጋር የተያያዘ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው።
ጉዞው በእስልምና የጨረቃ አቆጣጠር 12ኛው ወር "ዙል-ሒጃ" ላይ የሚፈጸም ሲሆን፣ የጨረቃ አቆጣጠር ከግሪጎሪያን አቆጣጠር ጋር ሲነጻጸር በየዓመቱ ወደ 11 ቀናት ገደማ ወደ ኋላ ስለሚሽከረከር የሐጅ ወቅት በተለያዩ የአየር ንብረቶች (በበጋ፣ በክረምትና በጸደይ) ላይ እንዲያርፍ ያደርገዋል።
የዚህ ታላቅ የሐጅ ሥርዓት ማጠናቀቂያ በመላው ዓለም በታላቅ ድምቀት በሚከበረው ዒድ አል-አድሃ (የአረፋ በዓል) ላይ ይደርሳል።
አማኞች መስዋዕት በማቅረብ፣ ያረዱትን አንድ ሦስተኛ ለቤተሰቦቻቸው፣ አንድ ሦስተኛ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ቀሪውን አንድ ሦስተኛ ለድሆች በማካፈል አጋርነታቸውንና እስላማዊ ፍቅራቸውን ይገልጻሉ።
በአካል ደክሞ በመንፈስ ታድሶ የሚመለስበት ሐጅ የትዕግስት፣ የትሕትናና የአንድነት ትምህርት ቤት ነው። አላህ (ሱ.ወ) ለሁላችንም ይህንን የአላህን ምሕረትና በረከት የምንቀበልበትን ልዩ የሕይወት አጋጣሚ ይወፍቀን።
በኢቲሃድ አብራር(ebc)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #hajj #makkah #eidaladha #islam #muslimummah #faith
#ethiopia | ሐጅ... የአላህ (ሱ.ወ) ቤት ወደሆነችውና የሙዕሚኖች ልብ ዘወትር ወደምትናፍቃት ቅድስት መካ የሚደረግ፣ በአካል ለቻለና አቅም ላለው ሙስሊም ሁሉ በሕይወት ዘመን አንድ ጊዜ የመፈጸም ግዴታ ያለበት አምስተኛው የእስልምና ማዕዘን ነው።
ይህ ታላቅ ጉዞ የግል መንፈሳዊ ጥንካሬን ማደሻ ብቻ ሳይሆን፣ የታማኝነት እና የዓለም አቀፋዊ የእስልምና አንድነት ከፍተኛ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ምድራዊ ማዕረግና የሀብት ልዩነትን ሁሉ አውልቀው፣ ተመሳሳይ ነጭ ኢሕራም ለብሰው በአንድነት ሲቆሙ ፍጹም የእኩልነት እና የወንድማማችነት ትርጉም በተግባር ይገለጻል።
ይህ ሥርዓት ከዘመናት በፊት ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ያስተማሩትን መንገዶች በመከተል የሚከናወን ሲሆን፣ እያንዳንዱ ተግባር ከነቢዩ ኢብራሂምና (ረ.ወ) ከነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ታሪክ ጋር የተያያዘ ጥልቅ መንፈሳዊ ትርጉም አለው።
ጉዞው በእስልምና የጨረቃ አቆጣጠር 12ኛው ወር "ዙል-ሒጃ" ላይ የሚፈጸም ሲሆን፣ የጨረቃ አቆጣጠር ከግሪጎሪያን አቆጣጠር ጋር ሲነጻጸር በየዓመቱ ወደ 11 ቀናት ገደማ ወደ ኋላ ስለሚሽከረከር የሐጅ ወቅት በተለያዩ የአየር ንብረቶች (በበጋ፣ በክረምትና በጸደይ) ላይ እንዲያርፍ ያደርገዋል።
የዚህ ታላቅ የሐጅ ሥርዓት ማጠናቀቂያ በመላው ዓለም በታላቅ ድምቀት በሚከበረው ዒድ አል-አድሃ (የአረፋ በዓል) ላይ ይደርሳል።
አማኞች መስዋዕት በማቅረብ፣ ያረዱትን አንድ ሦስተኛ ለቤተሰቦቻቸው፣ አንድ ሦስተኛ ለጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ቀሪውን አንድ ሦስተኛ ለድሆች በማካፈል አጋርነታቸውንና እስላማዊ ፍቅራቸውን ይገልጻሉ።
በአካል ደክሞ በመንፈስ ታድሶ የሚመለስበት ሐጅ የትዕግስት፣ የትሕትናና የአንድነት ትምህርት ቤት ነው። አላህ (ሱ.ወ) ለሁላችንም ይህንን የአላህን ምሕረትና በረከት የምንቀበልበትን ልዩ የሕይወት አጋጣሚ ይወፍቀን።
በኢቲሃድ አብራር(ebc)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #hajj #makkah #eidaladha #islam #muslimummah #faith