2 days ago
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስብሰባዎች ላይ ማንቀላፋታቸውን ተከትሎ አዳዲስ ቅጽል ስሞች እየተሰጧቸው መሆኑ ተገለጸ::
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሃውስ የስብሰባ አዳራሾች እና በተለያዩ ይፋዊ መድረኮች ላይ አይናቸውን ጨፍነው ሲያንቀላፉ የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የፖለቲካ ውይይትና ክርክር አስነስቷል።
በተለይም ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እና የፖለቲካ ታዛቢዎች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።
በቅርቡ በዋይት ሃውስ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ስለ ቀጠናዊ የውጭ ፖሊሲ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ለተወሰኑ ደቂቃዎች አይናቸውን ጨፍነው በመቀመጣቸው፣ ተቺዎቻቸው ቀደም ሲል ለጆ ባይደን ይሰጡት የነበረውን “ Sleepy Joe" (አንቀላፋው ጆ) የሚለውን ስም ወደ *Sleepy Donald" (አንቀላፋው ዶናልድ) እና *Slump Trump"በመቀየር አዳዲስ የፌዝ ቅጽል ስሞችን እየሰጧቸው ይገኛሉ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ በስብሰባዎች ላይ አልተኛሁም፤ ይልቁንም "አይኖቼን እያሳረፍኩ ነበር" በማለት የቀረበውን ክስ አስተባብለዋል።
ጤንነታቸውም ፍጹም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ብርቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በእጃቸው ላይ ስለሚስተዋለው የመቁሰል ወይም የደም መቋጠር ምልክት ሲጠየቁ፣ ደም ለማቅጠኛ የሚወስዱት አስፕሪን ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት በቀላሉ የሚፈጠር ምልክት እንደሆነና ምንም አይነት ከባድ የጤና እክል እንደሌለባቸው አስረድተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምስክርነት "ትራምፕ በስብሰባ ላይ ሲተኙ አይቼ አላውቅም፤ እንዲያውም እኩለ ሌሊትና ማለዳ 11 ሰዓት ላይ ስልክ እየደወሉ ስለሚቀሰቅሱኝ እሱ የማይተኛ መሆኑ ነው ትልቁ ችግር" በማለት በምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን ወቀሳ ተከላክለዋል።
ይህ የፕሬዚዳንቱ ሁኔታ በዋይት ሃውስ ውስጥ ባሉ የውስጥ አዋቂዎችና በፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው ዘንድ የእድሜና የጤና ሁኔታ ክትትል ጥያቄዎችን በድጋሚ እንዲነሱ ምክንያት ሆኗል😁
Seledadotio
Seledadotio
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሃውስ የስብሰባ አዳራሾች እና በተለያዩ ይፋዊ መድረኮች ላይ አይናቸውን ጨፍነው ሲያንቀላፉ የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የፖለቲካ ውይይትና ክርክር አስነስቷል።
በተለይም ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እና የፖለቲካ ታዛቢዎች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።
በቅርቡ በዋይት ሃውስ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ስለ ቀጠናዊ የውጭ ፖሊሲ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ለተወሰኑ ደቂቃዎች አይናቸውን ጨፍነው በመቀመጣቸው፣ ተቺዎቻቸው ቀደም ሲል ለጆ ባይደን ይሰጡት የነበረውን “ Sleepy Joe" (አንቀላፋው ጆ) የሚለውን ስም ወደ *Sleepy Donald" (አንቀላፋው ዶናልድ) እና *Slump Trump"በመቀየር አዳዲስ የፌዝ ቅጽል ስሞችን እየሰጧቸው ይገኛሉ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ በስብሰባዎች ላይ አልተኛሁም፤ ይልቁንም "አይኖቼን እያሳረፍኩ ነበር" በማለት የቀረበውን ክስ አስተባብለዋል።
ጤንነታቸውም ፍጹም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ብርቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በእጃቸው ላይ ስለሚስተዋለው የመቁሰል ወይም የደም መቋጠር ምልክት ሲጠየቁ፣ ደም ለማቅጠኛ የሚወስዱት አስፕሪን ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት በቀላሉ የሚፈጠር ምልክት እንደሆነና ምንም አይነት ከባድ የጤና እክል እንደሌለባቸው አስረድተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምስክርነት "ትራምፕ በስብሰባ ላይ ሲተኙ አይቼ አላውቅም፤ እንዲያውም እኩለ ሌሊትና ማለዳ 11 ሰዓት ላይ ስልክ እየደወሉ ስለሚቀሰቅሱኝ እሱ የማይተኛ መሆኑ ነው ትልቁ ችግር" በማለት በምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን ወቀሳ ተከላክለዋል።
ይህ የፕሬዚዳንቱ ሁኔታ በዋይት ሃውስ ውስጥ ባሉ የውስጥ አዋቂዎችና በፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው ዘንድ የእድሜና የጤና ሁኔታ ክትትል ጥያቄዎችን በድጋሚ እንዲነሱ ምክንያት ሆኗል😁
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
በ"ቪቫ ሶፍት" የንግድ ምልክት መብት ጥሰት የተጠረጠሩት ግለሰብ ላይ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ፤
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
5 days ago
ለኢትዮጵያ አዲስ የፖለቲካ ባህል ያመጣው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ ታሪክ የሰላማዊ ፖለቲካ ውድድር እና የሕዝብ ተሳትፎ መጠናከርን ያሳየ ነው አሉ።
በብልፅግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኤዴዔ እንዳሉት÷ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የምርጫ ታሪክና ሂደት በመቀየር በሀገሪቱ አስተማማኝና ዘመናዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል አዲስ የፖለቲካ ባህል ተመዝግቧል።
ኋላ ቀርና በኃይል የመጠቀም የፖለቲካ ፉክክር ሥርዓት በመቀየር በትብብር እና በፖለቲካዊ ውድድር መርህ ላይ የተመሰረተ አዲስ አሰራር በተግባር መታየቱንም አስረድተዋል።
ሰኞ ምርጫ አከናውነን ማክሰኞ ወደ ሥራ እንገባለን ያልነውን አሳክተናል ያሉት ኃላፊው÷ ምርጫው ኢትዮጵያ አሸናፊ የሆነችበት የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ማለፉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፅ የመስጠት ሂደትና ያሳየው ትዕግስት በዓለም አቀፍና በውጭ ታዛቢዎች ዘንድ አድናቆትና ምስክርነት ተሰጥቶታልም ነው ያሉት።
የኢዜማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ታሪኩ ድንበሩ በበኩላቸው÷ ባለፉት ስድስት ምርጫዎች ይስተዋሉ የነበሩ የፖለቲካ ምልክቶች፣ የሚዲያ አጠቃቀም እና የመንግሥት ተቋማት ምላሽ ሰጪነት ተግዳሮቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አለመታየታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች በመወያየት የተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ ያገኙበት ልዩ ሂደት የነበረበትና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች በቦታው ተገኝተው ፈጣን ምላሽ የሰጡበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል።
በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራትና የምርጫው ውጤት ሲገለጽ ውጤቱን በጸጋ በመቀበል ለሀገር ግንባታ በትብብር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ልምምድ ታሪክ የሰላማዊ ፖለቲካ ውድድር እና የሕዝብ ተሳትፎ መጠናከርን ያሳየ ነው አሉ።
በብልፅግና ፓርቲ ኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሞገስ ኤዴዔ እንዳሉት÷ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የኢትዮጵያን የምርጫ ታሪክና ሂደት በመቀየር በሀገሪቱ አስተማማኝና ዘመናዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል አዲስ የፖለቲካ ባህል ተመዝግቧል።
ኋላ ቀርና በኃይል የመጠቀም የፖለቲካ ፉክክር ሥርዓት በመቀየር በትብብር እና በፖለቲካዊ ውድድር መርህ ላይ የተመሰረተ አዲስ አሰራር በተግባር መታየቱንም አስረድተዋል።
ሰኞ ምርጫ አከናውነን ማክሰኞ ወደ ሥራ እንገባለን ያልነውን አሳክተናል ያሉት ኃላፊው÷ ምርጫው ኢትዮጵያ አሸናፊ የሆነችበት የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ማለፉን አመልክተዋል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ በሰላማዊ መንገድ ድምፅ የመስጠት ሂደትና ያሳየው ትዕግስት በዓለም አቀፍና በውጭ ታዛቢዎች ዘንድ አድናቆትና ምስክርነት ተሰጥቶታልም ነው ያሉት።
የኢዜማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ታሪኩ ድንበሩ በበኩላቸው÷ ባለፉት ስድስት ምርጫዎች ይስተዋሉ የነበሩ የፖለቲካ ምልክቶች፣ የሚዲያ አጠቃቀም እና የመንግሥት ተቋማት ምላሽ ሰጪነት ተግዳሮቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አለመታየታቸውን አመልክተዋል።
እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቶች በመወያየት የተፈጠሩ ችግሮች መፍትሄ ያገኙበት ልዩ ሂደት የነበረበትና የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች በቦታው ተገኝተው ፈጣን ምላሽ የሰጡበት ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል።
በቀጣይም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራትና የምርጫው ውጤት ሲገለጽ ውጤቱን በጸጋ በመቀበል ለሀገር ግንባታ በትብብር መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በሶስና አለማየሁ
21 days ago
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
Sponsored by
Surafel
23 days ago
ከቁጥሮች በስተጀርባ ያለው ሀገራዊ ተስፋ
**********
ሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሂቃን መድረክ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ኅብረተሰብ ድምፅ የሚሰማበት ታሪካዊ ሂደት ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራት ስታቲስቲካዊ መረጃዎች ስንመረምር፣ ተቋሙ በመሬት ላይ ያሉ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ ምን ያህል ሰፊ ርቀት መጓዝ እንደቻለ ቁጥሮቹ በራሳቸው ጉልህ ምስክርነት ይሰጣሉ።
የአንድ ሀገራዊ ምክክር ስኬት በዋናነት የሚለካው ባረጋገጠው የተደራሽነት መጠን እና ሽፋን ነው።
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከሁሉም የማኅበረሰብ ከፍል የተወከሉ 400 ተሳታፊዎችን ያካተተ መድረክ በማዘጋጀት ነው ሥራውን የጀመረው። በአሁኑ ወቅት የሀገራችንን 93 በመቶ መልክዓ ምድራዊ ወሰን መሸፈን ችሏል።
ከ11 ክልሎች እና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ1 ሺህ 234 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመለየት ለአጠቃላይ ምክክሩ የሚሆኑ የአጀንዳ ሐሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል።
ሙሉ መረጃውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopian #nationaldialogue #inclusivedialogue #nationalconsensus #ebc
**********
ሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሂቃን መድረክ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ኅብረተሰብ ድምፅ የሚሰማበት ታሪካዊ ሂደት ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራት ስታቲስቲካዊ መረጃዎች ስንመረምር፣ ተቋሙ በመሬት ላይ ያሉ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ ምን ያህል ሰፊ ርቀት መጓዝ እንደቻለ ቁጥሮቹ በራሳቸው ጉልህ ምስክርነት ይሰጣሉ።
የአንድ ሀገራዊ ምክክር ስኬት በዋናነት የሚለካው ባረጋገጠው የተደራሽነት መጠን እና ሽፋን ነው።
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከሁሉም የማኅበረሰብ ከፍል የተወከሉ 400 ተሳታፊዎችን ያካተተ መድረክ በማዘጋጀት ነው ሥራውን የጀመረው። በአሁኑ ወቅት የሀገራችንን 93 በመቶ መልክዓ ምድራዊ ወሰን መሸፈን ችሏል።
ከ11 ክልሎች እና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ1 ሺህ 234 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመለየት ለአጠቃላይ ምክክሩ የሚሆኑ የአጀንዳ ሐሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል።
ሙሉ መረጃውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopian #nationaldialogue #inclusivedialogue #nationalconsensus #ebc
29 days ago
በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ
#ethiopia | የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት ከዚህ በኋላ በሚያወጧቸው ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን የሕክምና ምስክርነት ማካተት እንዳይችሉ እገዳ ተጣለ።
ይህ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ አዘገጃጀትና ሥርጭት መመሪያ ቁጥር 1134/2018 ተገቢ ያልሆኑ የማስታወቂያ አሠራሮች በኅብረተሰቡ ዘንድ የተሳሳተ ግንዛቤ እየፈጠሩ በመሆኑ የሕዝብን የሥነምግባርና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የወጣ ነው።
መመሪያው በቴሌቪዥን፣ በራዲዮ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በድረገጾች፣ በቢልቦርዶችና በታተሙ ቁሳቁሶች ላይ የሚወጡ ማስታወቂያዎችን በሙሉ ይመለከታል።
አዲሱ ሕግ በጤና ማስታወቂያዎች ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በሙሉ አገልግሎቱን በትክክል ያገኙ መሆን እንዳለባቸውና አስቀድመው በጽሑፍ ስምምነት መስጠት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
ተሳታፊዎቹ ሕፃናት፣ የአእምሮ ጤና እክል ያለባቸው ወይም በራሳቸው መወሰን የማይችሉ ወገኖች ከሆኑ ደግሞ ከወላጅ ወይም ከሕጋዊ አሳዳጊ የጽሑፍ ፈቃድ ማግኘት ግዴታ ሆኗል።
ይህንን ድንጋጌ በመጣስ ያለፍቃድ ወይም አገልግሎቱን ያላገኘን ሰው ምስክር አድርጎ የተጠቀመ ተቋም ከ20 ሺሕ እስከ 50 ሺሕ ብር፣ እንዲሁም ሕፃናትንና ውሳኔ መስጠት የማይችሉ ሰዎችን ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ያሳተፈ ተቋም እስከ 100 ሺሕ ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጠብቀዋል።
የተጣለውን አስተዳደራዊ ቅጣት በሦስት ወር ውስጥ የማይከፍሉ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀታቸው እንዲታገድ ይደረጋል።
በተጨማሪም መመሪያው ለማስታወቂያ አሰራጮች እና ለሚዲያ ተቋማት አዲስ ኃላፊነት ጥሏል።
ማስታወቂያዎችን የሚያስተላልፉ አካላት ይዘቱ መመሪያውን ያሟላ እና ትክክለኛ መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ ያለባቸው ሲሆን፣ ሕጉን የጣሰ ማስታወቂያ ያስተላለፈ የሚዲያ ተቋም ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ከ10 ሺሕ እስከ 30 ሺሕ ብር ሊቀጣ ይችላል።
ይህ ክልከላ በብዙኃን መገናኛዎች፣ በትራንስፖርት ላይ በሚለጠፉ፣ በሹራቦች፣ በራሪ ወረቀቶችና በቢልቦርዶች ላይ የሚወጡ ማስታወቂያዎችንም ይጨምራል።
ማስታወቂያዎች የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲ ያከበሩ፣ ከልክ ያለፈ የሙያ ቃላትን የማያበዙና ለሕዝብ ግልጽ በሆነ ቋንቋ የሚዘጋጁ መሆን አለባቸው።
በተለይም የመጀመሪያው ምርጫ፣ የሁሉም ምርጫ እና የመሳሰሉ አባባሎችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ሲሆን፣ ተቋማት ከሌሎች የተሻሉ እንደሆኑ አድርገው ማቅረብ ወይም የእነሱ ባለሙያዎች ብቻ ልዩ ችሎታ እንዳላቸው አድርገው መናገር አይችሉም።
እንዲሁም ከአንድ ተቋም ሕክምና ካላገኙ አደጋ ሊገጥም እንደሚችል የሚያስፈራሩ ወይም በስሜት ላይ የሚያሴሩ የማስታወቂያ ይዘቶች የተከለከሉ ሲሆን፣ ተቋማት ያገኟቸውን ሽልማቶች በማስታወቂያ ላይ ማካተት የሚችሉት የሽልማቱን ዘመን፣ ምክንያቱንና ሰጪውን አካል በትክክል ሲገልጹ ብቻ መሆኑ ተደንግጓል።
#health #ministryofhealth #law #media #advertising #directive #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት ከዚህ በኋላ በሚያወጧቸው ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን የሕክምና ምስክርነት ማካተት እንዳይችሉ እገዳ ተጣለ።
ይህ የጤና አገልግሎት ማስታወቂያ አዘገጃጀትና ሥርጭት መመሪያ ቁጥር 1134/2018 ተገቢ ያልሆኑ የማስታወቂያ አሠራሮች በኅብረተሰቡ ዘንድ የተሳሳተ ግንዛቤ እየፈጠሩ በመሆኑ የሕዝብን የሥነምግባርና የባህል እሴቶችን ለመጠበቅ የወጣ ነው።
መመሪያው በቴሌቪዥን፣ በራዲዮ፣ በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በድረገጾች፣ በቢልቦርዶችና በታተሙ ቁሳቁሶች ላይ የሚወጡ ማስታወቂያዎችን በሙሉ ይመለከታል።
አዲሱ ሕግ በጤና ማስታወቂያዎች ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በሙሉ አገልግሎቱን በትክክል ያገኙ መሆን እንዳለባቸውና አስቀድመው በጽሑፍ ስምምነት መስጠት እንዳለባቸው ያስገድዳል።
ተሳታፊዎቹ ሕፃናት፣ የአእምሮ ጤና እክል ያለባቸው ወይም በራሳቸው መወሰን የማይችሉ ወገኖች ከሆኑ ደግሞ ከወላጅ ወይም ከሕጋዊ አሳዳጊ የጽሑፍ ፈቃድ ማግኘት ግዴታ ሆኗል።
ይህንን ድንጋጌ በመጣስ ያለፍቃድ ወይም አገልግሎቱን ያላገኘን ሰው ምስክር አድርጎ የተጠቀመ ተቋም ከ20 ሺሕ እስከ 50 ሺሕ ብር፣ እንዲሁም ሕፃናትንና ውሳኔ መስጠት የማይችሉ ሰዎችን ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ያሳተፈ ተቋም እስከ 100 ሺሕ ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ይጠብቀዋል።
የተጣለውን አስተዳደራዊ ቅጣት በሦስት ወር ውስጥ የማይከፍሉ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀታቸው እንዲታገድ ይደረጋል።
በተጨማሪም መመሪያው ለማስታወቂያ አሰራጮች እና ለሚዲያ ተቋማት አዲስ ኃላፊነት ጥሏል።
ማስታወቂያዎችን የሚያስተላልፉ አካላት ይዘቱ መመሪያውን ያሟላ እና ትክክለኛ መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ ያለባቸው ሲሆን፣ ሕጉን የጣሰ ማስታወቂያ ያስተላለፈ የሚዲያ ተቋም ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ከ10 ሺሕ እስከ 30 ሺሕ ብር ሊቀጣ ይችላል።
ይህ ክልከላ በብዙኃን መገናኛዎች፣ በትራንስፖርት ላይ በሚለጠፉ፣ በሹራቦች፣ በራሪ ወረቀቶችና በቢልቦርዶች ላይ የሚወጡ ማስታወቂያዎችንም ይጨምራል።
ማስታወቂያዎች የሀገሪቱን የጤና ፖሊሲ ያከበሩ፣ ከልክ ያለፈ የሙያ ቃላትን የማያበዙና ለሕዝብ ግልጽ በሆነ ቋንቋ የሚዘጋጁ መሆን አለባቸው።
በተለይም የመጀመሪያው ምርጫ፣ የሁሉም ምርጫ እና የመሳሰሉ አባባሎችን መጠቀም ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ሲሆን፣ ተቋማት ከሌሎች የተሻሉ እንደሆኑ አድርገው ማቅረብ ወይም የእነሱ ባለሙያዎች ብቻ ልዩ ችሎታ እንዳላቸው አድርገው መናገር አይችሉም።
እንዲሁም ከአንድ ተቋም ሕክምና ካላገኙ አደጋ ሊገጥም እንደሚችል የሚያስፈራሩ ወይም በስሜት ላይ የሚያሴሩ የማስታወቂያ ይዘቶች የተከለከሉ ሲሆን፣ ተቋማት ያገኟቸውን ሽልማቶች በማስታወቂያ ላይ ማካተት የሚችሉት የሽልማቱን ዘመን፣ ምክንያቱንና ሰጪውን አካል በትክክል ሲገልጹ ብቻ መሆኑ ተደንግጓል።
#health #ministryofhealth #law #media #advertising #directive #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ የሆኑት የባህር ኃይል አድሚራል ብራድ ኩፐር፣ አሜሪካ በየካቲት ወር መገባደጃ ላይ የጀመረችው "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የተሰኘው ወታደራዊ ዘመቻ የኢራንን ወታደራዊ አቅም እና በቀጠናው ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት ሙሉ በሙሉ ማዳከሙን አስታወቁ። አዛዡ ይህንን የተናገሩት በዋሽንግተን ዲሲ ለሴኔቱ የጦር ኃይሎች ኮሚቴ ስለ 2027 የበጀት ዓመት ጥያቄ እና በቀጠናው ስላለው ወታደራዊ አሰላለፍ ምስክርነት በሰጡበት ወቅት ነው።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
አዛዡ በምስክርነታቸው እንዳብራሩት፣ የአሜሪካ ኃይሎች ከ40 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወታደራዊ ግባቸውን በማሳካት የኢራንን የመከላከል አቅም ክፉኛ መትተዋል። በተለይም ባለፈው ዓመት ሚያዝያ እና ጥቅምት ወራት በእስራኤል ላይ ታይቶ የማያውቅ የጅምላ ሚሳኤል ጥቃት የፈጸመችው ኢራን፣ አሁን ላይ ይህን መሰል ጥቃት የመፈጸም አቅሟ በአሜሪካ ኃይሎች ተወግዷል። አድሚራል ኩፐር አክለውም፣ የኢራን የድሮን፣ የሚሳኤል እና የባህር ኃይል መከላከያ ኢንዱስትሪ በ90 በመቶ መውደሙን እና ቀሪ አቅሟ 10 በመቶ ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኢራን የባህር ኃይል ይህንን ከባድ ውድመት ተቋቁሞ አቅሙን መልሶ ለመገንባት ከ5 እስከ 10 ዓመታት ሊወስድበት እንደሚችልም ወታደራዊ ግምገማቸውን አቅርበዋል።
ይህ ወታደራዊ እርምጃ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይኖራት ያስቀመጡትን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ከዚህም ባሻገር ኢራን በቀጠናው ለሚገኙ አሸባሪ ቡድኖች ስታደርግ የነበረው ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ ክፉኛ ተመቷል። ለዓመታት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እና የጦር መሣሪያ ሲቀርብላቸው የነበሩት እንደ ሐማስ፣ ሕዝቦላህ እና ሁቲ ያሉ የተኪ ተዋጊ (Proxy) ቡድኖች፣ በዘመቻው ምክንያት ከኢራን የሚያገኙት ማንኛውም ዓይነት ትጥቅም ሆነ ሃብት መቋረጡን አዛዡ አብራርተዋል። ይህ ድል በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን፣ ለወራት የተደረገ ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ እና የዓመታት ልምድ ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
"ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊዩሪ" የአሜሪካን ወታደራዊ የበላይነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ በመካከለኛው ምሥራቅ ካሉ አጋር አገራት ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩ ተገልጿል። አድሚራል ኩፐር እንደገለጹት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ኳታር እና ሳዑዲ አረቢያ ከአሜሪካ ጋር ጎን ለጎን በመቆም ራሳቸውንም ሆነ አሜሪካውያንን በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል። በተጨማሪም ይህ ግዙፍ ወታደራዊ ስኬት ያለ ዮርዳኖስ እና እስራኤል የጠበቀ አጋርነት ሊሳካ እንደማይችል በመግለጽ፣ ዘመቻው በቀጠናው ያለውን የጸጥታ ትብብር ምን ያህል እንዳጠናከረው መስክረዋል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኤርትራ የተመድ ሰብአዊ መብት ምክር ቤት ‹‹ስሜን እያጠፋ ነው›› አለች፡፡ ወደ31 የሚሆኑ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ትላንት ባወጡት የጋራ መግለጫ የተመድ ሰብአዊ መብት ምክር ቤት የኤርትራ ራፖርተር ስራ ዘመን እንዲራዘም ጠይቀዋል፡፡ ለምክር ቤቱና ለምክር ቤቱ አባል አገራት ባስገቡት በዚህ ደብዳቤ በመጪው ሀምሌ ወር በሚከናወነው ስብሰባ ላይ ራፖርተሩ የኤርትራን ሰብአዊ መብት አያያዝ የተመለከተ ሪፖርት እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡ ተቋማቱ እንደገለፁት ባለፈው አመት ለምክር ቤቱ በቀረበው ኤርትራን የተመለከተ ሪፖርት ላይ የሰብአዊ መብት አያያዙ መሰረታዊ ለውጥ እንዳላመጣ መገለፁን አውስተዋል፡፡
ጨምረውም የተመድ የኤርትራ ሰብአዊ መብት መርማሪ ኮሚሽን የመጀመሪያ ሪፖርቱን ካወጣበት ከዛሬ 10 አመት ጀምሮ ምንም አይነት መሻሻል አለመታየቱን አስታውቀው የመንግስት ባለስልጣናት የሚፈፅሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት አሁንም እንደቀጠሉበት አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም የኤርትራ ራፖርተሩ የስራ ጊዜያቸው እንዲራዘምና ወደኤርትራ በመሄድ ያለውን ሁኔታ ገምግምው በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በሚከናወነው የምክር ቤቱ ስብሰባ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ለዚህ ጥሪ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ዛሬ መልስ የሰጡ ሲሆን ሲገልፁም ‹‹በኤርትራ ላይ የሚደረገው የስም ማጥፋት ዘመቻ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ዘመቻ ለሁለት አስርት አመት ያህል ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰውም በድርጊቱ ላይ የተወሰኑ አገራት እጃቸው እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም የተመድ ራፖርተር ምስክርነት ‹‹የተለመደ ስም ማጥፋት፣ የጠባብ ቡድኖች ፍላጎትና ተረት ነው›› በማለት በመግለፅ ተቃወሞ አሰምተዋል፡፡
ጨምረውም የተመድ የኤርትራ ሰብአዊ መብት መርማሪ ኮሚሽን የመጀመሪያ ሪፖርቱን ካወጣበት ከዛሬ 10 አመት ጀምሮ ምንም አይነት መሻሻል አለመታየቱን አስታውቀው የመንግስት ባለስልጣናት የሚፈፅሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት አሁንም እንደቀጠሉበት አስረድተዋል፡፡ በመሆኑም የኤርትራ ራፖርተሩ የስራ ጊዜያቸው እንዲራዘምና ወደኤርትራ በመሄድ ያለውን ሁኔታ ገምግምው በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በሚከናወነው የምክር ቤቱ ስብሰባ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ለዚህ ጥሪ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ዛሬ መልስ የሰጡ ሲሆን ሲገልፁም ‹‹በኤርትራ ላይ የሚደረገው የስም ማጥፋት ዘመቻ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ዘመቻ ለሁለት አስርት አመት ያህል ሲከናወን መቆየቱን ጠቅሰውም በድርጊቱ ላይ የተወሰኑ አገራት እጃቸው እንዳለበት አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም የተመድ ራፖርተር ምስክርነት ‹‹የተለመደ ስም ማጥፋት፣ የጠባብ ቡድኖች ፍላጎትና ተረት ነው›› በማለት በመግለፅ ተቃወሞ አሰምተዋል፡፡
1 month ago
በመንገደኞች ላይ በተፈጸመ ጥቃት የበርካታ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ
#fastmereja I በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ ውስጥ ትናንት ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከአሶሳ ወደ ግልገል በለስ በመጓዝ ላይ በነበሩ ሲቪል መንገደኞች ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ጥቃቱ የተፈጸመው መንገደኞቹ በማንኩሽ ከተማ አድረው ጉዟቸውን በጀመሩበት ወቅት መሆኑ ታውቋል።
እንደ ነዋሪዎች ምስክርነት፣ በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ30 እስከ 35 እንደሚደርስ የሚገመት ሲሆን፣ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችም ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ መውደማቸውን የሚያሳዩ ምስሎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ተሰራጭተዋል።
በአካባቢው ቀድሞውንም የታጣቂዎች እንቅስቃሴ እንደሚስተዋል የገለጹት የዓይን እማኞች፣ ድርጊቱን የፈጸመው ራሱን "የጉምዝ ነጻ አውጪ ኃይል" ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን መሆኑን ጠቁመዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት ስፍራ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሚገኝበት ወረዳ ውስጥ መሆኑ የጸጥታ ስጋቱን አሳሳቢ አድርጎታል። በጉዳዩ ላይ ከክልሉ መንግሥትም ሆነ ከመተከል ዞን የኮምዩንኬሽን መምሪያ በኩል ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም ሲል ዶቸ ቬለ ዘግቧል። ሆኖም የክልሉ ፖሊስ ባልደረባ ስለ ሁኔታው መረጃ ደርሷቸው ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን በወቅቱ ለዶቸ ቨለ በሰጡት ቃል አመልክተዋል።
#fastmereja I በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ ውስጥ ትናንት ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከአሶሳ ወደ ግልገል በለስ በመጓዝ ላይ በነበሩ ሲቪል መንገደኞች ላይ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ጥቃቱ የተፈጸመው መንገደኞቹ በማንኩሽ ከተማ አድረው ጉዟቸውን በጀመሩበት ወቅት መሆኑ ታውቋል።
እንደ ነዋሪዎች ምስክርነት፣ በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ30 እስከ 35 እንደሚደርስ የሚገመት ሲሆን፣ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችም ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ መውደማቸውን የሚያሳዩ ምስሎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ተሰራጭተዋል።
በአካባቢው ቀድሞውንም የታጣቂዎች እንቅስቃሴ እንደሚስተዋል የገለጹት የዓይን እማኞች፣ ድርጊቱን የፈጸመው ራሱን "የጉምዝ ነጻ አውጪ ኃይል" ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን መሆኑን ጠቁመዋል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት ስፍራ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በሚገኝበት ወረዳ ውስጥ መሆኑ የጸጥታ ስጋቱን አሳሳቢ አድርጎታል። በጉዳዩ ላይ ከክልሉ መንግሥትም ሆነ ከመተከል ዞን የኮምዩንኬሽን መምሪያ በኩል ዝርዝር ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም ሲል ዶቸ ቬለ ዘግቧል። ሆኖም የክልሉ ፖሊስ ባልደረባ ስለ ሁኔታው መረጃ ደርሷቸው ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን በወቅቱ ለዶቸ ቨለ በሰጡት ቃል አመልክተዋል።
1 month ago
የታሪክ ምስክርነቱ እና የካሜራዬ የሕይወት ጉዞ
* ከምፅዋ እስከ ራያ ግንባር
#ethiopia | ለእኔ ካሜራዬ ተራ የሥራ መሣሪያ ሳይሆን የኢትዮጵያን ፈታኝ ወቅቶች፣ የጀግንነት ታሪኮችንና ወሳኝ ኩነቶችን በከፍተኛ መስዋዕትነት የዘገብኩበት ታማኝ የትግል አጋሬ ነው።
እያንዳንዱ በምስል የቀረጸው ትዕይንት ከጀርባው የእኔን የሕይወት ተጋድሎ ይዟል።
በአሁኑ ወቅት የማኅበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም አጭርና ፍሬ ነገር ላይ ያተኮሩ ታሪኮችን የሚመርጥ በመሆኑ፣ እኔም በታሪካዊ የታሪክ መጋጠሚያዎች ላይ ተገኝቼ በሌንሴ ያስቀረሁትንና ያለፍኩበትን የሕይወት መስዋዕትነት እንደሚከተለው በአጭሩ አጋራችኋለሁ።
የታሪክ ምስክርነት ከምፅዋ እስከ ባድመ
በደርግ ሥርዓት ወቅት ገና በለጋ ዕድሜዬ በምፅዋ በረሃዎች ውስጥ የነበረውን የጦርነት እሳት በካሜራዬ እየቀረጽኩ የሀገርን ዋጋ በተግባር ተረድቻለሁ።
በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ሌንሴን ወደ ጠላት ጥይትና ወደ ወገኖቼ ተጋድሎ ባዞርኩበት ቅጽበት የሀገር ፍቅር ትርጉም በውስጤ ይሰርጽ ነበር። እያንዳንዱን ገድል ለትውልድ እንዲተላለፍ በምስል ስዘግብ እኔም የታሪኩ አካል ነበርኩ።
ይህ በምፅዋ የጀመረው ጉዞ በኢህአዴግ ዘመን በባድመና በፆረና ግንባሮችም ቀጥሏል። የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር የተደረገውን ተጋድሎ ከጥይት ይልቅ የካሜራዬን ድምጽ እያስቀደምኩ በታማኝነት መዝግቤያለሁ።
ድንበር ተሻጋሪው ሌንስ በባይደዋና ሞቃዲሾ
የካሜራዬ ጉዞ ከሀገር ድንበር ተሻግሮ በጎረቤት ሶማሊያ ባይደዋና ሞቃዲሾ ምድረ በዳዎች ድረስ ዘልቋል። ስጋትና አቧራ በነገሰበት በዚያ ቀጠና የኢትዮጵያ ሠራዊት ለሰላም የከፈለውን ዋጋና የህልውና ትግሉን በምስል በመክተብ የታሪክ ድርሻዬን ተወጥቻለሁ። በእያንዳንዱ ምስል ውስጥ ቆራጥነትንና የጀግንነት ታሪክን ለዓለም አሳይቻለሁ።
የቅርቡ ተጋድሎ ከቅራቅር እስከ ራያ
ሀገራችን ወደ አዲስ የለውጥ ምዕራፍ ስትሸጋገር የሕግ ማስከበር ዘመቻውን ለመዘገብ በግንባር ቀደምትነት ተሰማርቼ ነበር። ከቅራቅር እስከ ቆላ ተንቤን፣ ከጋሸና እስከ ራያ ግንባር ድረስ የድል ብስራቶችንና ልዩ ልዩ ሁነቶችን በካሜራዬ ስዘግብ ቆይቻለሁ።
በራያ ግንባር በፈንጂ በደረሰብኝ ጉዳት ካሜራዬ ለጊዜው እንዲያርፍና በአካሌ ላይ ድካም ቢፈጠርም መንፈሴ ግን አልተሰበረም። በዚያ አስከፊ ፍንዳታ ወቅት እንኳ ካሜራዬን አጥብቄ መያዜ የጽናቴ መገለጫ ነበር። ያ አጋጣሚ በደሜና በቁስሌ የጻፍኩት የሀገር ፍቅር አሻራ ሆኖ በታሪክ ውስጥ ይኖራል።
በበረሃ አቧራና በጦርነት እሳት ውስጥ የታጠቡት እነዚህ ምስሎች ለእኔ ምስክርነት ብቻ ሳይሆኑ ለሀገሬ የከፈልኩት መስዋዕትነትና የሕይወቴ ትልቁ ኩራት ናቸው።
ይህ ታሪክ በጽናትና በጀግንነት የተገነባ ሕያው ምስክርነቴ ነው።
ዳኜ አበራ
ፎቶግራፈር
#history #journalism #heroism #documentary #warcorrespondent #ethiopianarmy #resilience #photography #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
አቶ ዘገየ አስፋው አረፉ
#ethiopia | ከሁለት ቀን በፊት በኦቦ ሌንጮ ለታ የመፅሐፍ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ በስካይ ላይት አብረውን ታድመው የነበሩት የ84 አመቱ አቶ ዘገየ አስፋው ትናንት ሌሊት ማረፋቸው ተነገረ።
ዘገየ አስፋው (Zegeye Asfaw) በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው አንጋፋ ምሁር፣ የህግ ባለሙያ እና የቀድሞ ሚኒስትር ነበሩ። በተለይም በደርግ ዘመን የነበረውን ታሪካዊ "መሬት ላራሹ" አዋጅ በማርቀቅና በማስፈጸም ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል።
ዋና ዋና የሥራ መስኮች
የመሬት ስርአት ለውጥ፡ አቶ ዘገየ በ1967 ዓ.ም የወጣውን የመሬት ይዞታ አዋጅ በማርቀቅ ረገድ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን፣ የመሬትና የሕዝብ ማስፈር ሚኒስትር በመሆንም አገልግለዋል።
የመንግሥት የኃላፊነት ደረጃዎች፡ በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ወቅት (1983-1984 ዓ.ም) የግብርና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ፡ ሁንዴ (Hundee) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በመመሥረት በግብርናና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን አከናውነዋል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን በማገልገል ላይ ነበሩ።
የሕይወት ታሪክና የትምህርት ዝግጅት
በ1934 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ የተወለዱት አቶ ዘገየ፣ ትምህርታቸውን በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በሕግ ትምህርት ተከታትለዋል። በተማሪዎች እንቅስቃሴ ወቅትም ንቁ ተሳትፎ ነበራቸው። በፖለቲካዊ አቋማቸው ምክንያት በተለያዩ ሥርዓቶች የእስር እንግልት ደርሶባቸዋል፤ ለምሳሌ በደርግ ዘመን ለ10 ዓመታት ታስረዋል።
የሥነ-ጽሑፍ ሥራ
የአቶ ዘገየን የሕይወት ጉዞና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ታሪክ የሚተርክ Land to the Tiller የተሰኘ መጽሐፍ በኤን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) ተጽፎ ለንባብ በቅቷል።
በ1987 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. 1995) የመሠረቱት ሁንዴ (HUNDEE) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በሚከተሉት ላይ ያተኩራል፦
የሴቶች መብት፡ ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብት እንዲኖራቸውና በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ይሠራል።
የአካባቢ ጥበቃ፡ በገጠር አካባቢዎች የደን መልሶ ልማትና የውሃ ጥበቃ ሥራዎችን ያከናውናል።
የአርሶ አደሮች ማህበራት፡ ገበሬዎች ምርታቸውን በፍትሐዊ ዋጋ እንዲሸጡ የገበያ ትስስር ይፈጥራል።
መሬት ላራሹ" እንደ መጽሐፍ
እ.ኤ.አ. በ2020 የታተመው Land to the Tiller: An Interview with Zegeye Asfaw የተሰኘው መጽሐፍ በአን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአቶ ዘገየን የሕይወት ታሪክና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ትግል በዝርዝር ይተርካል። መጽሐፉ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካትታል፦
የታሪክ ምስክርነት፡ አቶ ዘገየ በሦስት የተለያዩ መንግሥታት (በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በደርግ እና በሽግግር መንግሥቱ) ውስጥ ስለነበራቸው ቆይታ እና በመሬት ማሻሻያ ዙሪያ ስለነበረው ትግል በዝርዝር ይገልጻሉ።
የግል መስዋዕትነት፡ ፖሊሲውን ለማስፈጸም ሲሉ የከፈሉትን ዋጋ፣ በተለይም በደርግ እስር ቤት ያሳለፏቸውን 10 ዓመታት ይተርካል።
የሰሜንና የደቡብ ልዩነት፡ በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል የነበረውን የ"ርስት" ሥርዓት እና በደቡብ የነበረውን የ"ጭሰኝነት" ሥርዓት ታሪካዊ ዳራ ይተነትናል።
"መሬት ላራሹ" እንደ ፖሊሲ (1967 ዓ.ም)
አቶ ዘገየ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም የወጣውን የገጠር መሬት ይዞታ አዋጅ (Proclamation 31/1975) በማርቀቅ ግንባር ቀደም ነበሩ። ይህ አዋጅ፦ [1]
የዘመናት የፊውዳል ጭቆናን በማክተም መሬት ለመንግሥትና ለሕዝብ እንዲሆን አድርጓል።
ጭሰኝነትን እና ማንኛውንም ዓይነት የመሬት ኪራይ ወይም የጉልበት ብዝበዛ አግዷል።
ገበሬው በራሱ መሬት ላይ ባለቤት (ይዞታ ያለው) እንዲሆን በማድረግ የኢትዮጵያን የክፍለ ሀብት ስርጭት ለውጧል።#ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
#ethiopia | ከሁለት ቀን በፊት በኦቦ ሌንጮ ለታ የመፅሐፍ ምረቃ መርሀ ግብር ላይ በስካይ ላይት አብረውን ታድመው የነበሩት የ84 አመቱ አቶ ዘገየ አስፋው ትናንት ሌሊት ማረፋቸው ተነገረ።
ዘገየ አስፋው (Zegeye Asfaw) በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው አንጋፋ ምሁር፣ የህግ ባለሙያ እና የቀድሞ ሚኒስትር ነበሩ። በተለይም በደርግ ዘመን የነበረውን ታሪካዊ "መሬት ላራሹ" አዋጅ በማርቀቅና በማስፈጸም ረገድ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሰው እንደነበሩ ይነገርላቸዋል።
ዋና ዋና የሥራ መስኮች
የመሬት ስርአት ለውጥ፡ አቶ ዘገየ በ1967 ዓ.ም የወጣውን የመሬት ይዞታ አዋጅ በማርቀቅ ረገድ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ሲሆን፣ የመሬትና የሕዝብ ማስፈር ሚኒስትር በመሆንም አገልግለዋል።
የመንግሥት የኃላፊነት ደረጃዎች፡ በኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት ወቅት (1983-1984 ዓ.ም) የግብርና ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ፡ ሁንዴ (Hundee) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በመመሥረት በግብርናና በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ በርካታ ሥራዎችን አከናውነዋል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን በማገልገል ላይ ነበሩ።
የሕይወት ታሪክና የትምህርት ዝግጅት
በ1934 ዓ.ም በምዕራብ ሸዋ የተወለዱት አቶ ዘገየ፣ ትምህርታቸውን በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በሕግ ትምህርት ተከታትለዋል። በተማሪዎች እንቅስቃሴ ወቅትም ንቁ ተሳትፎ ነበራቸው። በፖለቲካዊ አቋማቸው ምክንያት በተለያዩ ሥርዓቶች የእስር እንግልት ደርሶባቸዋል፤ ለምሳሌ በደርግ ዘመን ለ10 ዓመታት ታስረዋል።
የሥነ-ጽሑፍ ሥራ
የአቶ ዘገየን የሕይወት ጉዞና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ታሪክ የሚተርክ Land to the Tiller የተሰኘ መጽሐፍ በኤን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) ተጽፎ ለንባብ በቅቷል።
በ1987 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. 1995) የመሠረቱት ሁንዴ (HUNDEE) የተባለውን መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት በሚከተሉት ላይ ያተኩራል፦
የሴቶች መብት፡ ሴቶች የመሬት ባለቤትነት መብት እንዲኖራቸውና በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ይሠራል።
የአካባቢ ጥበቃ፡ በገጠር አካባቢዎች የደን መልሶ ልማትና የውሃ ጥበቃ ሥራዎችን ያከናውናል።
የአርሶ አደሮች ማህበራት፡ ገበሬዎች ምርታቸውን በፍትሐዊ ዋጋ እንዲሸጡ የገበያ ትስስር ይፈጥራል።
መሬት ላራሹ" እንደ መጽሐፍ
እ.ኤ.አ. በ2020 የታተመው Land to the Tiller: An Interview with Zegeye Asfaw የተሰኘው መጽሐፍ በአን ኦስትሁይዘን (Ann Oosthuizen) የተዘጋጀ ሲሆን፣ የአቶ ዘገየን የሕይወት ታሪክና የኢትዮጵያን የመሬት ፖለቲካ ትግል በዝርዝር ይተርካል። መጽሐፉ የሚከተሉትን ነጥቦች ያካትታል፦
የታሪክ ምስክርነት፡ አቶ ዘገየ በሦስት የተለያዩ መንግሥታት (በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በደርግ እና በሽግግር መንግሥቱ) ውስጥ ስለነበራቸው ቆይታ እና በመሬት ማሻሻያ ዙሪያ ስለነበረው ትግል በዝርዝር ይገልጻሉ።
የግል መስዋዕትነት፡ ፖሊሲውን ለማስፈጸም ሲሉ የከፈሉትን ዋጋ፣ በተለይም በደርግ እስር ቤት ያሳለፏቸውን 10 ዓመታት ይተርካል።
የሰሜንና የደቡብ ልዩነት፡ በኢትዮጵያ ሰሜናዊ ክፍል የነበረውን የ"ርስት" ሥርዓት እና በደቡብ የነበረውን የ"ጭሰኝነት" ሥርዓት ታሪካዊ ዳራ ይተነትናል።
"መሬት ላራሹ" እንደ ፖሊሲ (1967 ዓ.ም)
አቶ ዘገየ የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም የወጣውን የገጠር መሬት ይዞታ አዋጅ (Proclamation 31/1975) በማርቀቅ ግንባር ቀደም ነበሩ። ይህ አዋጅ፦ [1]
የዘመናት የፊውዳል ጭቆናን በማክተም መሬት ለመንግሥትና ለሕዝብ እንዲሆን አድርጓል።
ጭሰኝነትን እና ማንኛውንም ዓይነት የመሬት ኪራይ ወይም የጉልበት ብዝበዛ አግዷል።
ገበሬው በራሱ መሬት ላይ ባለቤት (ይዞታ ያለው) እንዲሆን በማድረግ የኢትዮጵያን የክፍለ ሀብት ስርጭት ለውጧል።#ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
1 month ago
የአንጋፋው ፖለቲከኛ ሌንጮ ለታን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞ የሚዳስስ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
1 month ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
1 month ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንገደኞች ምርጫ (APEX ) የ2026 ተሸላሚ ሆነ !
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንገደኞች እውነተኛ ምስክርነት ላይ ተመስርቶ የሚሰጠውን የ2026 የ-APEX (Passenger Choice Award) "የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ" ሽልማትን በድጋሚ ተቀዳጅቷል።
የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ እውቅናው በቀጥታ ከመንገደኞች የተሰጠ በመሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንገደኞች እውነተኛ ምስክርነት ላይ ተመስርቶ የሚሰጠውን የ2026 የ-APEX (Passenger Choice Award) "የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ" ሽልማትን በድጋሚ ተቀዳጅቷል።
የአየር መንገዱ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ እውቅናው በቀጥታ ከመንገደኞች የተሰጠ በመሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።
2 months ago
በሱዳን የተማረከው የትግራይ ተወላጅ
ቅጥረኛ ተዋጊ የቡርሃንን ሚስጥር አጋለጠ
በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የተማረከው የትግራይ ተወላጅ ቅጥረኛ ተዋጊ፣ የሱዳን ጦር መሪ የሆኑት አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ጦርነቱን ለማራዘም በውጭ ሀገር ተዋጊዎች ላይ ያላቸውን ጥገኝነት የሚያጋልጥ ምስክርነት ሰጥቷል። በህወሃት እንደሰለጠነ የተነገረው ይህ ግለሰብ በሱዳን ጦር ውስጥ የታየ ብቸኛ የውጭ ተዋጊ አይደለም።
የሱዳን ጦር ጦርነቱን ለማስቀጠል የኢራን ኦፕሬቲቭንና ከሙስሊም ወንድማማቾች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታጣቂዎች ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ኃይላትን ይጠቀማል የሚል ክስ በተደጋጋሚ ሲቀርብበት ቆይቷል። ይህ ቅጥረኛ ተዋጊ የተማረከው በበርሊን በተካሄደው የሰላምና የሰብአዊ ድጋፍ ጉባኤ ማግስት ሲሆን፣ በጉባኤው ላይ ዓለም አቀፍ ኃይሎች ለሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ እንደሚሰጡ ቃል በመግባት ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ ማድረጋቸው ይታወሳል።
seledadotio
seledadotio
ቅጥረኛ ተዋጊ የቡርሃንን ሚስጥር አጋለጠ
በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት ውስጥ የተማረከው የትግራይ ተወላጅ ቅጥረኛ ተዋጊ፣ የሱዳን ጦር መሪ የሆኑት አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ጦርነቱን ለማራዘም በውጭ ሀገር ተዋጊዎች ላይ ያላቸውን ጥገኝነት የሚያጋልጥ ምስክርነት ሰጥቷል። በህወሃት እንደሰለጠነ የተነገረው ይህ ግለሰብ በሱዳን ጦር ውስጥ የታየ ብቸኛ የውጭ ተዋጊ አይደለም።
የሱዳን ጦር ጦርነቱን ለማስቀጠል የኢራን ኦፕሬቲቭንና ከሙስሊም ወንድማማቾች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታጣቂዎች ጨምሮ የተለያዩ የውጭ ኃይላትን ይጠቀማል የሚል ክስ በተደጋጋሚ ሲቀርብበት ቆይቷል። ይህ ቅጥረኛ ተዋጊ የተማረከው በበርሊን በተካሄደው የሰላምና የሰብአዊ ድጋፍ ጉባኤ ማግስት ሲሆን፣ በጉባኤው ላይ ዓለም አቀፍ ኃይሎች ለሰብአዊ እርዳታ ድጋፍ እንደሚሰጡ ቃል በመግባት ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ ማድረጋቸው ይታወሳል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
የመክሊት : የስኬት አርበኛ
#ethiopia | የመክሊት 25 ዓመታት ጉዞ ትርጉም የሚኖረው በደጃፋችን ባሉ ስኬታማ ደንበኞች ሕይወት ውስጥ ነው። በዚህ መዝጊያ ምዕራፍ፣ ተቋሙን እንደ መሸጋገሪያ ድልድይ ተጠቅመው ከድህነት ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ ስድስት “የስኬት አርበኞችን” እናስተዋውቃችኋለን።
እነ ታየች፣ መነን፣ ጸዳለ፣ አቤልና ለገሰ የመክሊትን ብድር በመጠቀም የፈጠሩት የሥራ ዕድልና ያፈሩት ሀብት የሚደነቅ ነው።
በተለይም እንደ ወይዘሮ ሙሉወርቅ ያሉ ከሻይ ንግድ ተነስተው ፎቅ ያቆሙ እናቶች ታሪክ፣ መክሊት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እያበረከተ ያለውን ተጨባጭ ድርሻ ያረጋግጣል። ይህ ምዕራፍ የቃል ብቻ ሳይሆን የተግባር ምስክርነት፣ የሕልም እውን መሆንና የመክሊት የሩብ ክፍለ ዘመን ትልቁ ትርፍ ነው፡፡
ከ500 ብር ብድር እስከ ሚሊዮኖች መዋዕለ ንዋይ
የወይዘሮ ታየች ፈለቀ
የሩብ ክፍለ ዘመን የጥንካሬና የድል ጉዞ
ወይዘሮ ታየች ፈለቀ ሕይወትን በፈተና ነው የጀመሩት። በ15 ዓመታቸው እናት የሆኑት ታየች፣ ገና በወጣትነታቸው ባለቤታቸውን በአደጋ አጡ። ሁለት ልጆቻቸውን ይዘው በትምህርትና በንግድ መካከል ሲታገሉ እናታቸውም አረፉባቸው። በዚያ የጨለማ ወቅት ነበር መክሊት “ቤት ለቤት” ግንዛቤ ሲሰጥ የደረሰላቸው።
“እናቴ ሞታብኝ፣ ተስፋ ቆርጬ በነበረበት ወቅት ነው መክሊት የመጣው” ይላሉ። ያኔ በ1993 ዓ.ም የመጀመሪያዋን 500 ብር ሲበደሩ ፍርሃት አልነበረባቸውም። “ብሩን ወስጄ ሠርቼ አተርፍበታለሁ እንጂ አልፈራሁም፤ ባይሆንልኝ እንኳ በልቼው ልሙት በሚል ቆራጥነት ነው የጀመርኩት” ሲሉ ያንን ታሪካዊ ጅማሬ ያስታውሳሉ።
የዕድገት መሰላል፦ ከጠላ ጥመቃ እስከ አይሱዚ መኪና
ያቺ 500 ብር የለውጥ ቁልፍ ነበረች። በጠላና በእንጀራ ንግድ የጀመሩት ታየች፣ ቀስ በቀስ ወደ ከብት እርባታ ተሸጋገሩ። ከአንድ ላም ተነስተው እስከ ሰባት ከብቶች ማርባት ቻሉ። በመካከሉ የእግር መሰበር አደጋና የንግድ መደብዘዝ ቢያጋጥማቸውም፣ መክሊት ዳግም ብድር በመስጠት ከውድቀት
አነሳቸው።
ዛሬ ወይዘሮ ታየች የሦስት ሱቆች ባለቤት ናቸው። ሁለቱን አንድ አድርገው አንዱን ደግሞ መጋዘን አድርገው ይጠቀሙባቸዋል፡ ፡ ከዚህም ባለፈ ለልጃቸው 600 ሺህ ብር ከመክሊት ተበድረው ከራሳቸውም ጨምረው አይሱዚ የጭነት መኪና በመግዛት ከሰው ጥገኝነት አላቀውታል። ጭቃ የነበሩ የቤት ክፍሎቻቸውን አፍርሰው በዘመናዊ መልክ በመገንባት ዛሬ በወር እስከ 50 ሺህ ብር የቤት ኪራይ ገቢ የሚያገኙበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
የገንዘብ አያያዝ ጥበብ፦ “ዋናህን አትብላ”
ለወይዘሮ ታየች ስኬት ትልቁ ምስጢር ጥብቅ የገንዘብ ዲሲፕሊን ነው። “አንድ መቶ ብር ይዘህ የምትገዛበት አስፈላጊ ነገር ካለ፣ ቢርብህ እንኳ በዚያ ገንዘብ መብላት የለብህም፤ ዋናህን መብላት የለብህም” የሚል ፅኑ መርህ አላቸው። ልጆቻቸው እንኳ እናታቸው ገንዘብ እንዳላት በማያውቁበት ሁኔታ፣ በቁጠባና በዕቅድ በመመራት ትልቅ ቤት መገንባትና የሚሊዮን ብር ብድሮችን በአግባቡ መመለስ ችለዋል።
“መክሊት የእናት ጓዳ ነው፤ መክሊት ሕይወቴን የቀየረ፣ መሠረቴና ቤቴ ነው”
መክሊት ለታየች ምንድነው?
ለወይዘሮ ታየች መክሊት ድርጅት ብቻ አይደለም። “መክሊት የእናት ጓዳ ነው፤ መክሊት ሕይወቴን የቀየረ፣ መሠረቴና ቤቴ ነው” ይላሉ። በታመሙበት ወቅት ሠራተኞቹ ቤታቸው ድረስ መጥተው ጉዳያቸውን የሚፈጽሙላቸው መሆኑ ተቋሙ ለደንበኞቹ ያለውን ቅርበት የሚያሳይ እንደሆነ ይመሰክራሉ።
ዛሬ ወይዘሮ ታየች የልጅ ልጆቻቸውን በግል ትምህርት ቤት እያስተማሩ፣ በትርፍ ሰዓታቸው በባልትና ሥራ ተጠምደው በሰላም ይኖራሉ። በ25 ዓመቱ ጉዞ ውስጥ መክሊትና ታየች
አብረው አድገዋል፣ አብረውም ከፍ ብለዋል።
#መክሊት #የስኬትታሪክ #ጥንካሬ #ቁጠባ #ብድርናቁጠባ #ኢኮኖሚ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የመክሊት 25 ዓመታት ጉዞ ትርጉም የሚኖረው በደጃፋችን ባሉ ስኬታማ ደንበኞች ሕይወት ውስጥ ነው። በዚህ መዝጊያ ምዕራፍ፣ ተቋሙን እንደ መሸጋገሪያ ድልድይ ተጠቅመው ከድህነት ወደ ባለሀብትነት የተሸጋገሩ ስድስት “የስኬት አርበኞችን” እናስተዋውቃችኋለን።
እነ ታየች፣ መነን፣ ጸዳለ፣ አቤልና ለገሰ የመክሊትን ብድር በመጠቀም የፈጠሩት የሥራ ዕድልና ያፈሩት ሀብት የሚደነቅ ነው።
በተለይም እንደ ወይዘሮ ሙሉወርቅ ያሉ ከሻይ ንግድ ተነስተው ፎቅ ያቆሙ እናቶች ታሪክ፣ መክሊት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እያበረከተ ያለውን ተጨባጭ ድርሻ ያረጋግጣል። ይህ ምዕራፍ የቃል ብቻ ሳይሆን የተግባር ምስክርነት፣ የሕልም እውን መሆንና የመክሊት የሩብ ክፍለ ዘመን ትልቁ ትርፍ ነው፡፡
ከ500 ብር ብድር እስከ ሚሊዮኖች መዋዕለ ንዋይ
የወይዘሮ ታየች ፈለቀ
የሩብ ክፍለ ዘመን የጥንካሬና የድል ጉዞ
ወይዘሮ ታየች ፈለቀ ሕይወትን በፈተና ነው የጀመሩት። በ15 ዓመታቸው እናት የሆኑት ታየች፣ ገና በወጣትነታቸው ባለቤታቸውን በአደጋ አጡ። ሁለት ልጆቻቸውን ይዘው በትምህርትና በንግድ መካከል ሲታገሉ እናታቸውም አረፉባቸው። በዚያ የጨለማ ወቅት ነበር መክሊት “ቤት ለቤት” ግንዛቤ ሲሰጥ የደረሰላቸው።
“እናቴ ሞታብኝ፣ ተስፋ ቆርጬ በነበረበት ወቅት ነው መክሊት የመጣው” ይላሉ። ያኔ በ1993 ዓ.ም የመጀመሪያዋን 500 ብር ሲበደሩ ፍርሃት አልነበረባቸውም። “ብሩን ወስጄ ሠርቼ አተርፍበታለሁ እንጂ አልፈራሁም፤ ባይሆንልኝ እንኳ በልቼው ልሙት በሚል ቆራጥነት ነው የጀመርኩት” ሲሉ ያንን ታሪካዊ ጅማሬ ያስታውሳሉ።
የዕድገት መሰላል፦ ከጠላ ጥመቃ እስከ አይሱዚ መኪና
ያቺ 500 ብር የለውጥ ቁልፍ ነበረች። በጠላና በእንጀራ ንግድ የጀመሩት ታየች፣ ቀስ በቀስ ወደ ከብት እርባታ ተሸጋገሩ። ከአንድ ላም ተነስተው እስከ ሰባት ከብቶች ማርባት ቻሉ። በመካከሉ የእግር መሰበር አደጋና የንግድ መደብዘዝ ቢያጋጥማቸውም፣ መክሊት ዳግም ብድር በመስጠት ከውድቀት
አነሳቸው።
ዛሬ ወይዘሮ ታየች የሦስት ሱቆች ባለቤት ናቸው። ሁለቱን አንድ አድርገው አንዱን ደግሞ መጋዘን አድርገው ይጠቀሙባቸዋል፡ ፡ ከዚህም ባለፈ ለልጃቸው 600 ሺህ ብር ከመክሊት ተበድረው ከራሳቸውም ጨምረው አይሱዚ የጭነት መኪና በመግዛት ከሰው ጥገኝነት አላቀውታል። ጭቃ የነበሩ የቤት ክፍሎቻቸውን አፍርሰው በዘመናዊ መልክ በመገንባት ዛሬ በወር እስከ 50 ሺህ ብር የቤት ኪራይ ገቢ የሚያገኙበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
የገንዘብ አያያዝ ጥበብ፦ “ዋናህን አትብላ”
ለወይዘሮ ታየች ስኬት ትልቁ ምስጢር ጥብቅ የገንዘብ ዲሲፕሊን ነው። “አንድ መቶ ብር ይዘህ የምትገዛበት አስፈላጊ ነገር ካለ፣ ቢርብህ እንኳ በዚያ ገንዘብ መብላት የለብህም፤ ዋናህን መብላት የለብህም” የሚል ፅኑ መርህ አላቸው። ልጆቻቸው እንኳ እናታቸው ገንዘብ እንዳላት በማያውቁበት ሁኔታ፣ በቁጠባና በዕቅድ በመመራት ትልቅ ቤት መገንባትና የሚሊዮን ብር ብድሮችን በአግባቡ መመለስ ችለዋል።
“መክሊት የእናት ጓዳ ነው፤ መክሊት ሕይወቴን የቀየረ፣ መሠረቴና ቤቴ ነው”
መክሊት ለታየች ምንድነው?
ለወይዘሮ ታየች መክሊት ድርጅት ብቻ አይደለም። “መክሊት የእናት ጓዳ ነው፤ መክሊት ሕይወቴን የቀየረ፣ መሠረቴና ቤቴ ነው” ይላሉ። በታመሙበት ወቅት ሠራተኞቹ ቤታቸው ድረስ መጥተው ጉዳያቸውን የሚፈጽሙላቸው መሆኑ ተቋሙ ለደንበኞቹ ያለውን ቅርበት የሚያሳይ እንደሆነ ይመሰክራሉ።
ዛሬ ወይዘሮ ታየች የልጅ ልጆቻቸውን በግል ትምህርት ቤት እያስተማሩ፣ በትርፍ ሰዓታቸው በባልትና ሥራ ተጠምደው በሰላም ይኖራሉ። በ25 ዓመቱ ጉዞ ውስጥ መክሊትና ታየች
አብረው አድገዋል፣ አብረውም ከፍ ብለዋል።
#መክሊት #የስኬትታሪክ #ጥንካሬ #ቁጠባ #ብድርናቁጠባ #ኢኮኖሚ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የጦር ሚኒስትር ፒት ሄግሴዝ ለ2027 በጀት ዓመት የቀረበውን የ1.5 ትሪሊዮን ዶላር ታሪካዊ የመከላከያ በጀት አስመልክቶ በሰጡት ምስክርነት፣ የአሁኑ ወቅት ዋነኛ ተቃዋሚዎች የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው መሆናቸውን ገለጹ። ሄግሴዝ እንደተናገሩት፣ በአሁኑ ወቅት አሜሪካ እየገጠማት ያለው ትልቁ ፈተና የውጭ ጠላቶች ሳይሆኑ፣ በኮንግረስ ውስጥ ያሉት "ግድየለሽ እና ተስፋ የቆረጡ" የዲሞክራቲክ ፓርቲ አባላት የሚሰነዝሯቸው ንግግሮች ናቸው።
ሚኒስትሩ በዛሬው የኮንግረስ ውሎ ስለ ኢራን ጉዳይ ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "አሜሪካ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ ባለቤት እንድትሆን አትፈቅድም" በማለት የገቡትን ቃል ደግመውታ። በአሁኑ ወቅትም አሜሪካ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚሰሩ ተደራዳሪዎች እንዳሏት ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ2027 በጀት ዓመት የጠየቁት የ1.5 ትሪሊዮን ዶላር መከላከያ በጀት "የወቅቱን አጣዳፊነት" የሚያንፀባርቅ መሆኑን ሄግሴዝ አስረድተዋል። ይህ ከፍተኛ የበጀት ጥያቄ አሜሪካ ያለችበትን የውጥረት ወቅት ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑንም አክለዋል።
የመከላከያ ሚኒስትሩ አክለውም፣ ይህ የበጀት ጭማሪ አስፈላጊ የሆነው የሀገሪቱን የመከላከያ ኢንዱስትሪ መሠረት ዳግም ወደ "ጦርነት ጊዜ ዝግጁነት" (Wartime footing) ለመመለስ ታስቦ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አሜሪካ ለሚገጥሟት ወታደራዊ ስጋቶች ያላትን ምላሽ የማጠናከር ስትራቴጂ አካል መሆኑ ተመልክቷል።
ሚኒስትሩ በዛሬው የኮንግረስ ውሎ ስለ ኢራን ጉዳይ ለመወያየት ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "አሜሪካ ኢራን የኒውክሌር መሣሪያ ባለቤት እንድትሆን አትፈቅድም" በማለት የገቡትን ቃል ደግመውታ። በአሁኑ ወቅትም አሜሪካ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚሰሩ ተደራዳሪዎች እንዳሏት ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ2027 በጀት ዓመት የጠየቁት የ1.5 ትሪሊዮን ዶላር መከላከያ በጀት "የወቅቱን አጣዳፊነት" የሚያንፀባርቅ መሆኑን ሄግሴዝ አስረድተዋል። ይህ ከፍተኛ የበጀት ጥያቄ አሜሪካ ያለችበትን የውጥረት ወቅት ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑንም አክለዋል።
የመከላከያ ሚኒስትሩ አክለውም፣ ይህ የበጀት ጭማሪ አስፈላጊ የሆነው የሀገሪቱን የመከላከያ ኢንዱስትሪ መሠረት ዳግም ወደ "ጦርነት ጊዜ ዝግጁነት" (Wartime footing) ለመመለስ ታስቦ መሆኑን ገልጸዋል። ይህም አሜሪካ ለሚገጥሟት ወታደራዊ ስጋቶች ያላትን ምላሽ የማጠናከር ስትራቴጂ አካል መሆኑ ተመልክቷል።
2 months ago
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የልባችሁን መልካም መሻት ትሙላላችሁ🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
2 months ago
ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
2 months ago
♦️አዲስአበባ ግራንድ ፕሪ አዲስ ለኢትዮጵያ የፈጠረው ሌላኛው ወርቃማ ዕድል
♦️ወጣቱ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ መሀሪ ነጋሽ የአለም አትሌቲክስ ባደረገለት ጥሪ ሀገሩን ወክሎ ወደ ቦትስዋና ዛሬ ተጉዟል
♦️የአለም አትሌቲክስ የውድድር ዋና ዳይሬክተር መሀሪ ባለ ልዩ ተሰጦ እና በጣም አቅም ያለው ወጣት ሲሉ አመካሽተውታል
♦️በቀጣይስ ወጣቱን ባለሙያ በዓለም አትሌቲክስ በቋሚነት እናየው ይሁን ?
#ethiopia | የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በታላቅ ስኬት ያከናወነውን አዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር ከነሀስ ወደ ወርቅ ደረጃ ከመሸጋገሩ በተጨማሪ ሌላ ወርቃማ እድል እንደ ሀገር ይዞ ተከስቷል ።
የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት መሀሪ ነጋሽ በግራንድ ፕሪ እና በተለያዩ የፌዴሬሽኑ ትልልቅ ውድድሮች ባሳየው ብቃት፣አቅም እና ስኬት በአለምአቀፍ ደረጃ ተወዳጅነትንና ተቀባይነትን አግኝቶ ፌዴሬሽኑ ከዚህ በፊት ሲወቀስበት የነበረው በዓለምአቀፍ አደባባይ የተሳትፎ እጥረትን በሰበረ መልኩ በዓለም አትሌቲክስ ጥሪ ተደርጎለት
ዛሬ ጠዋት(ከደቂቃዎች በፊት) ወደ ቦትስዋና ጋቦሮኒ አምርቷል ።
ለወጣቱ ሀላፊ በቀጥታ ከአለም አትሌቲክስ ለዚህ ዕድል ከኢትዮጵያ በብቸኝነት መጋበዙ እዩኝ እዩኝ ሳይል፣ ማንም ሳያየው በጨለማ የተደከመበትን ስራው ፣በዓለም መድረክ ፍሬው መታየት መጀመሩ ለሌሎች ወጣት ባለሙያዎችም በር ከፋች ተደርጎ ተወስዷል።
ከአዲስአበባ እስከ አለም አትሌቲክስ (World Athletics )
በውጤት፣በልፋት እና በነጮች የተሰጠ ታላቅ የተግባር ምስክርነት ማረጋገጫ ሆኖ በተወሠደው በዚህ ዕድል በአቅሙ፣በእውቀቱ እና በስነምግባሩ የተመሰከረለት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት መሀሪ ነጋሽ የአለም አትሌቲክስ (World Athletics )
እውቅና በመስጠት በአለም አቀፍ ደረጃ በቦትስዋና የሚካሄደውን የዓለም አትሌቲክስ የሚዲያ አካዳሚ ፕሮግራም(World Athletics Media Acadamy Program )ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቦለት ዛሬ(ሠኞ) ንጋት ላይ ወደ ስፍራው አቅንቷል ።
በሚሰራው ስራ በሁሉም የተመሰገነው ወጣት መሀሪ ከአገር ባለፈ፣ የአለም አቀፍ አትሌቲክስ የውድድር ዳይሬክተር ፒርስ ኦካላጋን "ልዩ ተሰጥኦ ያላውና በጣም ጎበዝ የሚዲያ ባለሙያ(Talented
Professional PR and Media Director )"በማለትም በተደጋጋሚ አድናቆት ሲያቀርቡለትና ምስክርነት ሲሠጡለትም ተሠምቷል።
ወጣት መሀሪ ያገኘው እድል እንደ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን እንደ አገርም ኢትዮጵያ በታላላቅ የዓለም የአትሌቲክስ መድረኮች ተወካይ ሳይኖራት መቅረቱ የሚያስቆጭ ቢሆንም አሁን ግን ይሄን ቁጭት የሚያስረሳ የሚመስል ፍንጭ በመታየቱ ሁላችንንም የሚያኮራ ሆኖ ተገኝቷል።
ወጣት መሀሪ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዶ በተጠናቀቀው የአዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር "በዓለም አትሌቲክስ" ተመርጦ የውድድሩ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር በመሆን የመራ ሲሆን በተለይም ውድድሩ ዓለምአቀፍ ስታንዳርድ ይዘት ያለው እንዲሆን እና ስኬታማ እንዲሆን ላደረገው አሰተዋጽኦ በዳይሬክተሩ ተደጋጋሚ እውቅና የተሰጠውና ምስጋና የተቸረው ሲሆን በአለምአቀፍ መድረክም እንዲሳተፍ
አስችሎታል ።
ወጣት መሀሪ በእንደዚህ ዓይነት ትልቅ ምስክርነት በአለም መድረክ እንዲወጡ አቅም እና እውቀት የሚጠይቅ ቢሆንም ነገርግን በሁሉም ዘርፍ ማድረግ እንደሚቻል አሳይቷል ።
ወጣት መሀሪ በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ ከሚድያ ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት እና ተሳትፎ ከማረጋገጥ ባለፈ፣ፌዴሬሽኑ በውጭ ግንኙነት እና በስፖርት ዲፕሎማሲ የተሻለ አቅም እንዲኖረው እና በአለም አትሌቲክስ ተቀባይነት እንዲያገኝ የተለያዩ
ተግባራት አከናውኗል ።
ቀጣይ የወጣቱ ጉዞ ወዴት ይሁን? የሚለውን ...አብረን የምናየው ይሆናል ..የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ግን እንደ መሀሪ አይነት ሰው ማበራከት ይጠበቅበታል ።
ፌዴሬሽኑ ጉዞውን የተሳካ እንዲሆንና ለወጣት መሀሪ ያደረገውን ድጋፍም ከፍተኛ ምስጋና ይገበዋል ።
ወጣት መሀሪ ነጋሽ ከተለያዩ የዓለም አገራት ከተወጣጡ በድምሩ ከ12 ባለሙያዎች አንዱ ሆነህ "ኢትዮጵያ"የሚለውን ታላቅ ስም አንግበህ በዚህ መድረክ በመገኘትህ እና የልፋትህ ውጤት በመሆኑ የሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ዝግጅት ክፍል እንኳን ደስ አለህ ለማለት ይወዳል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️ወጣቱ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ መሀሪ ነጋሽ የአለም አትሌቲክስ ባደረገለት ጥሪ ሀገሩን ወክሎ ወደ ቦትስዋና ዛሬ ተጉዟል
♦️የአለም አትሌቲክስ የውድድር ዋና ዳይሬክተር መሀሪ ባለ ልዩ ተሰጦ እና በጣም አቅም ያለው ወጣት ሲሉ አመካሽተውታል
♦️በቀጣይስ ወጣቱን ባለሙያ በዓለም አትሌቲክስ በቋሚነት እናየው ይሁን ?
#ethiopia | የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በታላቅ ስኬት ያከናወነውን አዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር ከነሀስ ወደ ወርቅ ደረጃ ከመሸጋገሩ በተጨማሪ ሌላ ወርቃማ እድል እንደ ሀገር ይዞ ተከስቷል ።
የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት መሀሪ ነጋሽ በግራንድ ፕሪ እና በተለያዩ የፌዴሬሽኑ ትልልቅ ውድድሮች ባሳየው ብቃት፣አቅም እና ስኬት በአለምአቀፍ ደረጃ ተወዳጅነትንና ተቀባይነትን አግኝቶ ፌዴሬሽኑ ከዚህ በፊት ሲወቀስበት የነበረው በዓለምአቀፍ አደባባይ የተሳትፎ እጥረትን በሰበረ መልኩ በዓለም አትሌቲክስ ጥሪ ተደርጎለት
ዛሬ ጠዋት(ከደቂቃዎች በፊት) ወደ ቦትስዋና ጋቦሮኒ አምርቷል ።
ለወጣቱ ሀላፊ በቀጥታ ከአለም አትሌቲክስ ለዚህ ዕድል ከኢትዮጵያ በብቸኝነት መጋበዙ እዩኝ እዩኝ ሳይል፣ ማንም ሳያየው በጨለማ የተደከመበትን ስራው ፣በዓለም መድረክ ፍሬው መታየት መጀመሩ ለሌሎች ወጣት ባለሙያዎችም በር ከፋች ተደርጎ ተወስዷል።
ከአዲስአበባ እስከ አለም አትሌቲክስ (World Athletics )
በውጤት፣በልፋት እና በነጮች የተሰጠ ታላቅ የተግባር ምስክርነት ማረጋገጫ ሆኖ በተወሠደው በዚህ ዕድል በአቅሙ፣በእውቀቱ እና በስነምግባሩ የተመሰከረለት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት መሀሪ ነጋሽ የአለም አትሌቲክስ (World Athletics )
እውቅና በመስጠት በአለም አቀፍ ደረጃ በቦትስዋና የሚካሄደውን የዓለም አትሌቲክስ የሚዲያ አካዳሚ ፕሮግራም(World Athletics Media Acadamy Program )ላይ እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቦለት ዛሬ(ሠኞ) ንጋት ላይ ወደ ስፍራው አቅንቷል ።
በሚሰራው ስራ በሁሉም የተመሰገነው ወጣት መሀሪ ከአገር ባለፈ፣ የአለም አቀፍ አትሌቲክስ የውድድር ዳይሬክተር ፒርስ ኦካላጋን "ልዩ ተሰጥኦ ያላውና በጣም ጎበዝ የሚዲያ ባለሙያ(Talented
Professional PR and Media Director )"በማለትም በተደጋጋሚ አድናቆት ሲያቀርቡለትና ምስክርነት ሲሠጡለትም ተሠምቷል።
ወጣት መሀሪ ያገኘው እድል እንደ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን እንደ አገርም ኢትዮጵያ በታላላቅ የዓለም የአትሌቲክስ መድረኮች ተወካይ ሳይኖራት መቅረቱ የሚያስቆጭ ቢሆንም አሁን ግን ይሄን ቁጭት የሚያስረሳ የሚመስል ፍንጭ በመታየቱ ሁላችንንም የሚያኮራ ሆኖ ተገኝቷል።
ወጣት መሀሪ ባሳለፍነው ሳምንት ተካሂዶ በተጠናቀቀው የአዲስአበባ ግራንድ ፕሪ ውድድር "በዓለም አትሌቲክስ" ተመርጦ የውድድሩ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር በመሆን የመራ ሲሆን በተለይም ውድድሩ ዓለምአቀፍ ስታንዳርድ ይዘት ያለው እንዲሆን እና ስኬታማ እንዲሆን ላደረገው አሰተዋጽኦ በዳይሬክተሩ ተደጋጋሚ እውቅና የተሰጠውና ምስጋና የተቸረው ሲሆን በአለምአቀፍ መድረክም እንዲሳተፍ
አስችሎታል ።
ወጣት መሀሪ በእንደዚህ ዓይነት ትልቅ ምስክርነት በአለም መድረክ እንዲወጡ አቅም እና እውቀት የሚጠይቅ ቢሆንም ነገርግን በሁሉም ዘርፍ ማድረግ እንደሚቻል አሳይቷል ።
ወጣት መሀሪ በተጨማሪም ፌዴሬሽኑ ከሚድያ ጋር ያለውን መልካም ግንኙነት እና ተሳትፎ ከማረጋገጥ ባለፈ፣ፌዴሬሽኑ በውጭ ግንኙነት እና በስፖርት ዲፕሎማሲ የተሻለ አቅም እንዲኖረው እና በአለም አትሌቲክስ ተቀባይነት እንዲያገኝ የተለያዩ
ተግባራት አከናውኗል ።
ቀጣይ የወጣቱ ጉዞ ወዴት ይሁን? የሚለውን ...አብረን የምናየው ይሆናል ..የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ግን እንደ መሀሪ አይነት ሰው ማበራከት ይጠበቅበታል ።
ፌዴሬሽኑ ጉዞውን የተሳካ እንዲሆንና ለወጣት መሀሪ ያደረገውን ድጋፍም ከፍተኛ ምስጋና ይገበዋል ።
ወጣት መሀሪ ነጋሽ ከተለያዩ የዓለም አገራት ከተወጣጡ በድምሩ ከ12 ባለሙያዎች አንዱ ሆነህ "ኢትዮጵያ"የሚለውን ታላቅ ስም አንግበህ በዚህ መድረክ በመገኘትህ እና የልፋትህ ውጤት በመሆኑ የሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል ዝግጅት ክፍል እንኳን ደስ አለህ ለማለት ይወዳል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
2 months ago
ከመቃብር በላይ የሚውል መልካም ስም
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
2 months ago
እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ? እነሆ እደተናገረ ተነስቷል
“እነሆም የጌታ መልአክ ከሰማይ ወረደ፣ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፣ እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና። እንደ ተናገረው ተነስቷልና በዚህ የለም ኑና እዩ አላቸው።” ይለናል ማቴዎስ 28÷5። ስለ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድመው ነቢያት ተናግረዋል። ስለ ጌታችን ትንሣኤ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ጌታችን ራሱ በትምህርቱ ግልጽ አድርጎ ቢናገርም ሰዱቃውያንና ሌሎች ብዙ ሰዎች ለማመን ያዳግታቸው ነበር። አራቱ ወንጌላውያን፣ በማቴ 28፣ በማር 16፣ በሉቃ 24 እና በዮሐ 20 እንዲሁም ቅዱሳን ሐዋርያት በስብከታቸውና በመጽሐፋቸው ስለ ትንሣኤው ምስክርነት በመስጠት አረጋግጠው አስፍተውና አምልተው አስተምረዋል፤ ጽፈዋል።
ከሐዋርያትም መካከል የሆነው ቅዱስ ቶማስ እንኳ ጌታችን በዝግ ቤት ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ የተወጋውን ጎኑን አሳይቶ በክብር መነሣቱን እስከሚያረጋግጥለት ድረስ የጌታችንን ትንሣኤ ለማመን እንደተቸገረ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። በተጨማሪም የጌታን ትንሣኤና ትንሣኤ ሙታንን በአጠቃላይ ለመቀበል የተቸገሩ ብዙዎች እንደነበሩ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን። ክርስቶስ ስለትንሣኤው በዮሐንስ 2÷19 በምሳሌ ሲናገር “ይህንንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ” ብሎ የተናገረውን ሐዋርያቱ የተረዱትና ያመኑት ከትንሣኤው በኋላ ነበር። በ2ኛ ጢሞ 3÷14 ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ለጢሞቴዎስ “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርከው ታውቃለህና።” ሲል እንደጻፈለት እኛም ከማን እንደተማርነው እናውቃለንና የጌታን ትንሣኤ በፍጹም ልብ አምነን ለራሳችን ትንሣኤ እንዘጋጃለን።
ጌታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ለሰው ልጅ ድህነት ሲል ጽኑ መከራና ስቃይን ተቀብሏል። አይሁድ ከያዙት በኋላም ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የሆነ ስቃይ፣ መከራ፣ እንግልትና ግርፋትን ተቀብሎ፤ በቀራንዮ አደባባይ በዕለተ አርብ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ፤ ነፍሱን በፈቃዱ ሰጠ፡፡ አዳምንና ዘሩንም ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መለሳቸው፡፡ በ3ኛው ቀን መቃብር ክፈቱልኝ፣ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ስልጣን በክብር ተነስቷል። መላዕክቱም ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ እነሆ እደተናገረ ተነስቷል ብለው መስክረዋል፡፡ ገዳማውያን በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ለተነሳው ጌታ ፍቅር ዓለምን ትተዋታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ? እነሆ እደተናገረ ተነስቷል
“እነሆም የጌታ መልአክ ከሰማይ ወረደ፣ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፣ እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና። እንደ ተናገረው ተነስቷልና በዚህ የለም ኑና እዩ አላቸው።” ይለናል ማቴዎስ 28÷5። ስለ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አስቀድመው ነቢያት ተናግረዋል። ስለ ጌታችን ትንሣኤ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ጌታችን ራሱ በትምህርቱ ግልጽ አድርጎ ቢናገርም ሰዱቃውያንና ሌሎች ብዙ ሰዎች ለማመን ያዳግታቸው ነበር። አራቱ ወንጌላውያን፣ በማቴ 28፣ በማር 16፣ በሉቃ 24 እና በዮሐ 20 እንዲሁም ቅዱሳን ሐዋርያት በስብከታቸውና በመጽሐፋቸው ስለ ትንሣኤው ምስክርነት በመስጠት አረጋግጠው አስፍተውና አምልተው አስተምረዋል፤ ጽፈዋል።
ከሐዋርያትም መካከል የሆነው ቅዱስ ቶማስ እንኳ ጌታችን በዝግ ቤት ሰላም ለእናንተ ይሁን ብሎ የተወጋውን ጎኑን አሳይቶ በክብር መነሣቱን እስከሚያረጋግጥለት ድረስ የጌታችንን ትንሣኤ ለማመን እንደተቸገረ ቅዱስ መጽሐፍ ይነግረናል። በተጨማሪም የጌታን ትንሣኤና ትንሣኤ ሙታንን በአጠቃላይ ለመቀበል የተቸገሩ ብዙዎች እንደነበሩ ከቅዱሳት መጻሕፍት እንረዳለን። ክርስቶስ ስለትንሣኤው በዮሐንስ 2÷19 በምሳሌ ሲናገር “ይህንንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አስነሣዋለሁ” ብሎ የተናገረውን ሐዋርያቱ የተረዱትና ያመኑት ከትንሣኤው በኋላ ነበር። በ2ኛ ጢሞ 3÷14 ቅዱስ ጳውሎስ ለመንፈስ ልጁ ለጢሞቴዎስ “አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር፣ ከማን እንደ ተማርከው ታውቃለህና።” ሲል እንደጻፈለት እኛም ከማን እንደተማርነው እናውቃለንና የጌታን ትንሣኤ በፍጹም ልብ አምነን ለራሳችን ትንሣኤ እንዘጋጃለን።
ጌታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ለሰው ልጅ ድህነት ሲል ጽኑ መከራና ስቃይን ተቀብሏል። አይሁድ ከያዙት በኋላም ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ የሆነ ስቃይ፣ መከራ፣ እንግልትና ግርፋትን ተቀብሎ፤ በቀራንዮ አደባባይ በዕለተ አርብ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ፤ ነፍሱን በፈቃዱ ሰጠ፡፡ አዳምንና ዘሩንም ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን መለሳቸው፡፡ በ3ኛው ቀን መቃብር ክፈቱልኝ፣ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ስልጣን በክብር ተነስቷል። መላዕክቱም ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትሻላችሁ እነሆ እደተናገረ ተነስቷል ብለው መስክረዋል፡፡ ገዳማውያን በታላቅ ኃይልና ሥልጣን ለተነሳው ጌታ ፍቅር ዓለምን ትተዋታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 months ago
የትንሳኤ በዓል መልዕክትና የድጋፍ ጥሪ
እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
በታላቅነቱና በአሠራሩ ድንቅ የሆነው የአያት ፀበል መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ግንባታ በአባቶቻችን ጸሎትና በደጋግ ምዕመናን ርብርብ አሁን ካለበት ደረጃ ደርሷል።
ይህ በሙቅ ጸበሉና በፈዋሽነቱ የሚታወቀው ደብር፣ በርካቶች ከደዌ ተፈውሰው ምስክርነት የሰጡበት ቅዱስ ስፍራ ነው።
የዚህን ገናና ደብር የቤተ መቅደስ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ፣ በዓለም ዙሪያ የምትገኙ ምዕመናን ሁሉ በችሎታችሁ እንድትሳተፉ የአደራ ጥሪ ቀርቧል።
የድጋፍ ማበርከቻ መንገዶች
(የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)
የሂሳብ ቁጥር 1000589534337
አጭር የክፍያ ቁጥር፦2627
ለተጨማሪ መረጃ
📞 0911431337
📞 0979417409
አያት ፀበል መድኃኔዓለምና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የበረከት እንዲሆንልዎ እመኛለሁ!
2 months ago
የተናገሩትን መኖር
***
ለሰው ልጅ በተለይ ደግሞ ለህዝብ መሪ ከባዱ ፈተና ቃል የገቡትን መፈፀም አለመቻል ነው። ቃል ተስፋን ይፈጥራል፣ ተስፋ ደግሞ መጠበቅን። የተገባው ቃል ወደ ተግባር ካልተቀየረ የማይፈፀም ተስፋ ይሆንና ልብን ያሳዝናል። ስለዚህ ቃል እዳ ነው፤ ያውም የእምነት እዳ። በመሆኑም መፈፀም አለበት። ካልተፈፀመ ቅሬታን ያመጣል፣ መተማመንን ይሸረሽራል፣ በመጨረሻም ተቀባይነትን ያሳጣል። የተገባ ቃል ሲፈፀም ደግሞ ደስ ያሰኛል፣ መተማመንን ያመጣል፣ በውጤቱም ቃሉን ለጠበቀው አካል ተቀባይነትና ክብርን ያስገኛል።
የህዝብ አመራር የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት በእቅድ ወይም ከማህበረሰቡ በሚቀርብለት ጥያቄ መነሻ በተለያዩ ጊዜያት ቃል ይገባል። ማህበረሰቡም ቃል ተገብቶለታልና ተግባር ይጠብቃል።
በታሪካችንም ሆነ በእድሜያችን እንዳየነው ቃሉን ከሚጠብቅ ይልቅ ቃሉን ላለመጠበቁ ምክንያት የሚቆጥር መሪ ይበዛል። ቃላቸውን ለመጠበቅ የሚተጉና በእለት ተእለት የሥራ ትጋታቸው ውጤት የሚያሳዩ ጥቂት መሪዎች ደግሞ አሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአመራር ሚናቸው የተናገሩትን በመኖር የሚታወቁ መሪ ናቸው። ለህዝብ ቃል ከገቡ ይተገብሩታል። ለዚህ ደግሞ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እየተቀየረች ያለችው የአዲስ አበባ ከተማ ለጠየቃት ሁሉ መናገር ትችላለች።
የሀገሪቱ ጠ/ሚ/ር አንድ መድረክ ላይ "የሴት ምሳሌ፣ ብርቱ፣ ማርሽ ቀያሪ" በማለት ስለ ወ/ሮ አዳነች መስክረዋል። ከእረፍት አልባ የለውጥ መሪ አንደበት እንደዚህ ዓይነት ምስክርነት መስማት መቻል የከንቲባዋን ብርቱ ጥረትና ውጤታማነት ያሳያል።
እኔም እላለሁ ከንቲባዋ ለመናገር ብለው የሚናገሩ ሳይሆን የተናገሩትን የሚኖሩ ናቸው። ይህም ለብዙ አመራሮች አርዓያና ትምህርት የሚሆን ነው እላለሁ።
ይመጣል ባህሩ
***
ለሰው ልጅ በተለይ ደግሞ ለህዝብ መሪ ከባዱ ፈተና ቃል የገቡትን መፈፀም አለመቻል ነው። ቃል ተስፋን ይፈጥራል፣ ተስፋ ደግሞ መጠበቅን። የተገባው ቃል ወደ ተግባር ካልተቀየረ የማይፈፀም ተስፋ ይሆንና ልብን ያሳዝናል። ስለዚህ ቃል እዳ ነው፤ ያውም የእምነት እዳ። በመሆኑም መፈፀም አለበት። ካልተፈፀመ ቅሬታን ያመጣል፣ መተማመንን ይሸረሽራል፣ በመጨረሻም ተቀባይነትን ያሳጣል። የተገባ ቃል ሲፈፀም ደግሞ ደስ ያሰኛል፣ መተማመንን ያመጣል፣ በውጤቱም ቃሉን ለጠበቀው አካል ተቀባይነትና ክብርን ያስገኛል።
የህዝብ አመራር የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት በእቅድ ወይም ከማህበረሰቡ በሚቀርብለት ጥያቄ መነሻ በተለያዩ ጊዜያት ቃል ይገባል። ማህበረሰቡም ቃል ተገብቶለታልና ተግባር ይጠብቃል።
በታሪካችንም ሆነ በእድሜያችን እንዳየነው ቃሉን ከሚጠብቅ ይልቅ ቃሉን ላለመጠበቁ ምክንያት የሚቆጥር መሪ ይበዛል። ቃላቸውን ለመጠበቅ የሚተጉና በእለት ተእለት የሥራ ትጋታቸው ውጤት የሚያሳዩ ጥቂት መሪዎች ደግሞ አሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአመራር ሚናቸው የተናገሩትን በመኖር የሚታወቁ መሪ ናቸው። ለህዝብ ቃል ከገቡ ይተገብሩታል። ለዚህ ደግሞ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እየተቀየረች ያለችው የአዲስ አበባ ከተማ ለጠየቃት ሁሉ መናገር ትችላለች።
የሀገሪቱ ጠ/ሚ/ር አንድ መድረክ ላይ "የሴት ምሳሌ፣ ብርቱ፣ ማርሽ ቀያሪ" በማለት ስለ ወ/ሮ አዳነች መስክረዋል። ከእረፍት አልባ የለውጥ መሪ አንደበት እንደዚህ ዓይነት ምስክርነት መስማት መቻል የከንቲባዋን ብርቱ ጥረትና ውጤታማነት ያሳያል።
እኔም እላለሁ ከንቲባዋ ለመናገር ብለው የሚናገሩ ሳይሆን የተናገሩትን የሚኖሩ ናቸው። ይህም ለብዙ አመራሮች አርዓያና ትምህርት የሚሆን ነው እላለሁ።
ይመጣል ባህሩ
2 months ago
ዓለም አቀፍ የሰዎች አዘዋዋሪ ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም) በቁጥጥር ስር ዋለ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከ3 ሺህ በላይ ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ያዘዋወረውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲፈለግ የነበረው አደገኛ ወንጀለኛ ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም) ከ9 ግብረ-አበሮቹ ጋር መያዙን አስታወቀ። ተጠርጣሪው በትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ ውስጥ በድብቅ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ስር የዋለው፣ ፖሊስ ከዓለም አቀፉ የ"ROCK" ተቋም ጋር ባደረገው የጋራ ክትትልና የመረጃ ልውውጥ ነው።
ተጠርጣሪው ይትባረክ ዳዊት በተለያዩ አገራት አድሀኖም፣ አህመድ፣ ሙኒር እና ክብሮም የሚሉ ስድስት የሀሰት ስሞችንና ፓስፖርቶችን በመጠቀም ለዓመታት ሲያመልጥ ቆይቷል። በምርመራው እንደተረጋገጠው፣ ግለሰቡና ቡድኑ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳንና ሶማሊያ ወጣቶችን በመመልመል ሊቢያ ውስጥ በሚገኙ አምስት መጋዘኖች አግተው ኢ-ሰብአዊ ስቃይ ሲያደርሱባቸው ነበር።
በዚህ የወንጀል ድርጊት ሳቢያ፦
ከ100 በላይ ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል።
ከ50 በላይ ሴቶች ተደፍረዋል።
ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ተንቀሳቅሷል።
ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በ9 አገራት የሚገኙ 16 ተጎጂዎችን ጨምሮ የ100 ሰዎችን ምስክርነት ተቀብሏል። ተጠርጣሪዎቹ በወንጀል ያፈሩት ሀብትና የባንክ ሂሳብ እንዲታገድ የተደረገ ሲሆን፣ የፖሊስ ምርመራ ተጠናቆ መዝገቡ ለዓቃቤ ሕግ መላኩ ተረጋግጧል።
መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከ3 ሺህ በላይ ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ያዘዋወረውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲፈለግ የነበረው አደገኛ ወንጀለኛ ይትባረክ ዳዊት (ክብሮም) ከ9 ግብረ-አበሮቹ ጋር መያዙን አስታወቀ። ተጠርጣሪው በትግራይ ክልል ሽሬ ከተማ ውስጥ በድብቅ ሲንቀሳቀስ በቁጥጥር ስር የዋለው፣ ፖሊስ ከዓለም አቀፉ የ"ROCK" ተቋም ጋር ባደረገው የጋራ ክትትልና የመረጃ ልውውጥ ነው።
ተጠርጣሪው ይትባረክ ዳዊት በተለያዩ አገራት አድሀኖም፣ አህመድ፣ ሙኒር እና ክብሮም የሚሉ ስድስት የሀሰት ስሞችንና ፓስፖርቶችን በመጠቀም ለዓመታት ሲያመልጥ ቆይቷል። በምርመራው እንደተረጋገጠው፣ ግለሰቡና ቡድኑ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳንና ሶማሊያ ወጣቶችን በመመልመል ሊቢያ ውስጥ በሚገኙ አምስት መጋዘኖች አግተው ኢ-ሰብአዊ ስቃይ ሲያደርሱባቸው ነበር።
በዚህ የወንጀል ድርጊት ሳቢያ፦
ከ100 በላይ ሰዎች ለሞት ተዳርገዋል።
ከ50 በላይ ሴቶች ተደፍረዋል።
ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ ተንቀሳቅሷል።
ፌደራል ፖሊስ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በ9 አገራት የሚገኙ 16 ተጎጂዎችን ጨምሮ የ100 ሰዎችን ምስክርነት ተቀብሏል። ተጠርጣሪዎቹ በወንጀል ያፈሩት ሀብትና የባንክ ሂሳብ እንዲታገድ የተደረገ ሲሆን፣ የፖሊስ ምርመራ ተጠናቆ መዝገቡ ለዓቃቤ ሕግ መላኩ ተረጋግጧል።
መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
2 months ago
የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች የሕግ ጥበቃ
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
0929101037,0983337690
መግቢያ #ethiopia | በኢትዮጵያ ወንጀልን እና ሙስናን ለሚያጋልጡ ጠቋሚዎች ማንነትን መደበቅ፣ ምስጢራዊነትን መጠበቅ እና ከበቀል እርምጃ የመከላከል ህጋዊ ጥበቃ ይደረጋል። ይህ ጥበቃ በተለይም ሙስናን የሚዘግቡ ወገኖች ላይ የሚደርስን ተጽዕኖ ለመቀነስ እና ጠቋሚዎች ያለስጋት መረጃ እንዲሰጡ ለማበረታታት ያለመ ነው።
የተለያዩ የአለማችን ሀገራት ለወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ የሚያደርጉ ሲሆን ይህን የሚያደርጉትም ከባድ እና የተደራጁ ወንጀሎችን በሚመለከት ለሚቀርቡ ጠቋሚዎችና ምስክሮች ነው፡፡ ሀገራችንም ይህንኑ በመረዳት የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 አውጥታ በህግ በተመለከቱ ወንጀሎች ላይ ምስክሮችና ጠቋሚዎች ለሆኑ ሰዎች ጥበቃ ለማድረግ ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ፅሁፍ የምስክር እና ጠቋሚዎችን ጥበቃ ምንነትና የጥበቃ ስምምነት፣ የጥበቃ እርምጃ ዓይነቶችን እና ጥበቃ የሚደረግባቸውን ወንጀሎች በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡
1. የጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ ምንነት እና የጥበቃ ስምምነት
የጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ ማለት አንድን ወንጀል በተመለከተ የሚያውቀውን ለፍርድ ቤት ወይም ለፖሊስ ለመግለፅ የተስማማ ጠቋሚ ወይም ምስክር ቃሉን ወይም መረጃውን በመስጠቱ ምክንያት በራሱ ወይም በቤተሰቡ ላይ ከሚቃጣበት ጉዳት የሚጠበቅበት በህግ የተዘረጋ ሥርአት ነው፡፡ ይህም በጥበቃ ስምምነት መሰረት የሚፈፀም ሲሆን ስምምነቱ በጥበቃ ተጠቃሚው እና በፍትህ ሚኒስቴር መካከል የሚደረግ ነው፡፡ በአዋጁ አንቀፅ 2(2) መሰረት የጥበቃ ተጠቃሚ ከሚኒስቴሩ ጋር የጥበቃ ስምምነት የተፈራረመ ጠቋሚ ወይም የምስክር ወይም የጠቋሚ ወይም የምስክር ቤተሰብ አባል ነው፡፡ የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ያላደረሰ ወይም በፍርድ የተከለከለ ሰው ከሆነ የጥበቃ ስምምነቱ ከወላጆቹ ወይም ከአሳዳሪው ጋር የሚፈረም ሲሆን ነገር ግን የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ከደረሰ ወይም የህግ ችሎታውን መልሶ ካገኘ በኋላ ጥበቃው የሚቀጥል ከሆነ ስምምነቱን የጥበቃ ተጠቃሚው ራሱ መፈረም እንዳለበት በአዋጁ አንቀፅ 8(3) ተደንግጎ ይገኛል፡፡
2. የጥበቃ ተጠቃሚው የሆነው አካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ ሲሆን
መረጃ ወይም ምስክርነት የሚሰጠው በወላጁ ወይም በአሳዳሪው ላይ ሲሆን፣ ወላጅ ወይም አሳዳሪ የሌለው ሲሆን፣ አስፈላጊው ጥረት ተደርጎ ወላጁን ወይም አሳዳሪውን ማግኘት ያልተቻለ እንደሆነ፣ ወላጁ ወይም አሳዳሪው በቂ ባልሆነ ምክንያት ፈቃዱን ሳይሰጥ ሲቀር ወይም በማናቸውም ምክንያት ፈቃዱን መስጠት ሳይችል ሲቀር ሚኒስቴሩ ከልጁ ጋር ልዩ የጥበቃ ስምምነት ሊፈራረም እንደሚችል ከአዋጁ አንቀፅ 9(1) መረዳት ይቻላል፡፡ ሆኖም አካለ መጠን ካላደረሰ ልጅ ጋር የተደረገ ልዩ የጥበቃ ስምምነት ከተፈረመበት ዕለት ጀምሮ ባሉት አስር ቀናት ውስጥ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ መጽደቅ አለበት፡፡ ፍርድ ቤቱም አካለ መጠን ያላደረሰው ልጅ ጥቅምና ደህንነት ይበልጥ ሊረጋገጥ የሚችልበትን ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጥበቃ ስምምነቱን መሻር፣ ማጽደቅ ወይም ማሻሻል እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 9(4) ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡
3. ዋና ዋና የጥበቃ አይነቶች
3.1 ማንነትን መደበቅ፦ የጠቋሚው ማንነት በምርመራ እና ክስ ሂደት ውስጥ በምስጢር እንዲያዝ ይደረጋል።
3.2 ከበቀል ጥበቃ፦ ጠቋሚዎች በስራ ቦታቸው ወይም በሌላ ቦታ ላይ ለጠቆሙት ጥቆማ በቀል እንዳይደርስባቸው ህጉ ይከለክላል።
3.3 የደህንነት ከለላ፦ የወንጀል ድርጊቶችን በመጠቆማቸው ህይወታቸው ወይም ንብረታቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ በሚችልበት ጊዜ ጥበቃ ይደረግላቸዋል።
3.4 ህጋዊ ጥበቃ (Immunities): ጠቋሚዎች ከሰጡት መረጃ ጋር በተያያዘ ከፍትሐብሔር ወይም የወንጀል ተጠያቂነት ጥበቃ ሊደረግላቸው ይችላል። እነዚህ ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ በዝርዝር ሌሎቹንም ጨምሮ ከዚህ በታች ባለው ክፍል የጥበቃ አይነት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው አካላት የሚወሰድላቸው የህግ ጥበቃ አፈጻጸም እንመለከታለን።
4. የጥበቃ ዓይነቶች እና አፈጻጸም
ለወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የሚደረጉ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች በአዋጁ አንቀጽ 4 ስር ተዘርዝረው ይገኛሉ፡፡ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደ ሁኔታው በተናጠል ወይም በጣምራ ለጥበቃ ተጠቃሚ ተፈጻሚ የሚደረጉ ሲሆን ይህም ፡-
የአካልና ንብረት ደህንነት ጥበቃ
የመኖሪያ ስፍራ መቀየርን ጨምሮ ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ ቦታ መስጠት
ማንነትንና ባለንብረትነትን መደበቅ
ማንነትን መቀየር
ለራስ መጠበቂያ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መስጠት
መረጃ በተሰጠበት የወንጀል ድርጊት ያለመከሰስ
መረጃ በሚሰጥበት የወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊትም ሆነ በኋላ ተከሳሽ በጥበቃ ተጠቃሚው መኖሪያ ወይም የሥራ ቦታ ወይም ትምህርት ቤት አካባቢ እንዳይደርስ ማገድ
የፍርድ ሂደት ተጀምሮ ምስክርነት እስከሚሰጥ ድረስ የምስክር ማንነት እንዳይገለጽ ማድረግ
ምስክርነት በዝግ ችሎት እንዲሰጥ ማድረግ
ምስክርነት በአካል ሳይታይ ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆኖ ወይም ማንነትን በመሸፈን እንዲሰጥ ማድረግ
ማስረጃ በኤሌክትሮኒክስ ወይም በሌላ የተለየ ዘዴ እንዲቀርብ ማድረግ
በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት
እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት
የጥበቃ እርምጃው የመኖሪያ ስፍራን ለውጥ ካስከተለ የጓዝ ማንሻ ወጪን መሸፈን
በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ
በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነጻ መስጠት
በጥበቃ እርምጃው ምክንያት ለደረሰ የገቢ ማጣት ወይም በበቀል እርምጃ ለደረሰ የመሥራት ችሎታ ማጣት የመሠረታዊ ፍላጎት ማሟያ ወጪን መሸፈን
በጥበቃ ሥር እያለ ለደረሰ ሞት የቀብር ማስፈጸሚያ ወጪ መሸፈንና ለቤተሰብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ
የጥበቃ ተጠቃሚው የሥራና የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ መርዳት
ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን የሚያካትት ነው፡፡
5. ለምስክር ወይም ጠቋሚዎች ጥበቃ የሚደረግባቸው ወንጀሎች የትኞቹ ናቸው?
ለምስክሮች ወይም ለጠቋሚዎች ጥበቃ የሚደረገው በህጉ ለተመለከቱት ወንጀሎች ሲሆን በወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 አንቀጽ 3 መሰረት የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ማግኘት የሚቻለው የፅኑ እስራት መነሻው ምንም ይሁን ምን ጣራው ግን 10 (አስር አመት) እና ከዚያ በላይ በሆነ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ በሚችል ወንጀል ምስክርነት ወይም ጥቆማን የተመለከተ ሆኖ
የወንጀል ድርጊቱ ያለምስክሩ ወይም ያለጠቋሚው ምስክርነት ወይም ጥቆማ በሌላ ማናቸውም መንገድ ሊረጋገጥ ወይም ሊደረስበት የማይችል ሲሆን እና
በምስክሩ፣ በጠቋሚው ወይም በቤተሰቡ ህይወት፣ አካላዊ ደህንነ፣ ነፃነት ወይም ንብረት ላይ ከባድ አደጋ ያደርሳል ተብሎ ሲታመን እንደሆነ ከአዋጁ አንቀፅ 3(1) መረዳት ይቻላል፡፡
ለአብነትም በኢትዮጵያ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀፅ 16 እና በሰው የመነገድ እና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀፅ 25 የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች በአዋጅ ቁጥር 699/2003 መሰረት ለወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ስለሚደረግ ጥበቃ ደንግገው ይገኛሉ፡፡
ነገር ግን አዋጁ ይህንን መስፈርት ቢያስቀምጥም የፍትህ ሚኒስቴሩ የጥበቃ ተጠቃሚ ላልሆኑ ለማንኛቸውም ምስክሮችና ጠቋሚዎችም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 4 ስር ከተቀመጡ አንዳንድ ጥበቃዎችን እንደአስፈላጊነቱ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ይህም
በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት
እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት
በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ
በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነጻ መስጠት
ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን የሚያካትት ነው፡፡
6. የጹሁፉ ቁልፍ የህግ ማጠቃለያ
የዚህ ጽሁፍ መነሻ የአዋጅ ቁጥር 699/2003 ስለ ወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የሚደረግ የህግ ጥበቃ ሲሆን ከላይ በቀረበው አግባብ የህግ ግንዛቤ መስጠት በተለይም ረቂቅና ከበድ ወንጀሎችን በህዝብና በሀገር ላይ ከባድ ጉዳትን የሚያስከትሉትን ወንጀሎች እንዲጋለጡ ምስክሮችም የህግ ጥበቃ ኖሮዋቸው የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ በዚህ አዋጅ መሠረት ማድረጉ ለህበረተሰቡና ለሀገር ሰላም የሚበጅ ሲሆን በተቃራኒው እንደዚህ አይነት ሰወች በመጠቆማቸው ወይም በመመስከራቸው ምክንያት የአደጋ ወይም የወንጀል ሰለባ ቢሆኑ ለሌላውም ዜጋ በዚህ ልክ ትብብር ለመስጠት የሚፈራ በመሆኑ ፍትህ ተደብቃ የምትቀርበት ሁኔታ ይፈጠራል።ስለሆነም ለከባድ ወንጀል ጠቋሚዎች እና ለምስክሮች መንግስት አስፈላጊውን የህግ ጥበቃ ሊያደርግና ከዚህ አንጻር ለማህበረሰቡ አስፈላጊውን የህግ ግንዛቤ ሊሰጥ ያስፈልጋል።
https://t.me/Fantahunlawye...
https://www.facebook.com/s...
ማጣቀሻዎች/References/
1. የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003
2. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ 1996
3. የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ስነስረአት
4. የኢፊድሪ ወንጀል ስነስረአት እና የማስረጃ ህግ
5. የፍትህ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር የፌስቡክ ገጽ
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
0929101037,0983337690
መግቢያ #ethiopia | በኢትዮጵያ ወንጀልን እና ሙስናን ለሚያጋልጡ ጠቋሚዎች ማንነትን መደበቅ፣ ምስጢራዊነትን መጠበቅ እና ከበቀል እርምጃ የመከላከል ህጋዊ ጥበቃ ይደረጋል። ይህ ጥበቃ በተለይም ሙስናን የሚዘግቡ ወገኖች ላይ የሚደርስን ተጽዕኖ ለመቀነስ እና ጠቋሚዎች ያለስጋት መረጃ እንዲሰጡ ለማበረታታት ያለመ ነው።
የተለያዩ የአለማችን ሀገራት ለወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ የሚያደርጉ ሲሆን ይህን የሚያደርጉትም ከባድ እና የተደራጁ ወንጀሎችን በሚመለከት ለሚቀርቡ ጠቋሚዎችና ምስክሮች ነው፡፡ ሀገራችንም ይህንኑ በመረዳት የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 አውጥታ በህግ በተመለከቱ ወንጀሎች ላይ ምስክሮችና ጠቋሚዎች ለሆኑ ሰዎች ጥበቃ ለማድረግ ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ በዚህ ፅሁፍ የምስክር እና ጠቋሚዎችን ጥበቃ ምንነትና የጥበቃ ስምምነት፣ የጥበቃ እርምጃ ዓይነቶችን እና ጥበቃ የሚደረግባቸውን ወንጀሎች በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡
1. የጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ ምንነት እና የጥበቃ ስምምነት
የጠቋሚዎችና ምስክሮች ጥበቃ ማለት አንድን ወንጀል በተመለከተ የሚያውቀውን ለፍርድ ቤት ወይም ለፖሊስ ለመግለፅ የተስማማ ጠቋሚ ወይም ምስክር ቃሉን ወይም መረጃውን በመስጠቱ ምክንያት በራሱ ወይም በቤተሰቡ ላይ ከሚቃጣበት ጉዳት የሚጠበቅበት በህግ የተዘረጋ ሥርአት ነው፡፡ ይህም በጥበቃ ስምምነት መሰረት የሚፈፀም ሲሆን ስምምነቱ በጥበቃ ተጠቃሚው እና በፍትህ ሚኒስቴር መካከል የሚደረግ ነው፡፡ በአዋጁ አንቀፅ 2(2) መሰረት የጥበቃ ተጠቃሚ ከሚኒስቴሩ ጋር የጥበቃ ስምምነት የተፈራረመ ጠቋሚ ወይም የምስክር ወይም የጠቋሚ ወይም የምስክር ቤተሰብ አባል ነው፡፡ የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ያላደረሰ ወይም በፍርድ የተከለከለ ሰው ከሆነ የጥበቃ ስምምነቱ ከወላጆቹ ወይም ከአሳዳሪው ጋር የሚፈረም ሲሆን ነገር ግን የጥበቃ ተጠቃሚው አካለ መጠን ከደረሰ ወይም የህግ ችሎታውን መልሶ ካገኘ በኋላ ጥበቃው የሚቀጥል ከሆነ ስምምነቱን የጥበቃ ተጠቃሚው ራሱ መፈረም እንዳለበት በአዋጁ አንቀፅ 8(3) ተደንግጎ ይገኛል፡፡
2. የጥበቃ ተጠቃሚው የሆነው አካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ ሲሆን
መረጃ ወይም ምስክርነት የሚሰጠው በወላጁ ወይም በአሳዳሪው ላይ ሲሆን፣ ወላጅ ወይም አሳዳሪ የሌለው ሲሆን፣ አስፈላጊው ጥረት ተደርጎ ወላጁን ወይም አሳዳሪውን ማግኘት ያልተቻለ እንደሆነ፣ ወላጁ ወይም አሳዳሪው በቂ ባልሆነ ምክንያት ፈቃዱን ሳይሰጥ ሲቀር ወይም በማናቸውም ምክንያት ፈቃዱን መስጠት ሳይችል ሲቀር ሚኒስቴሩ ከልጁ ጋር ልዩ የጥበቃ ስምምነት ሊፈራረም እንደሚችል ከአዋጁ አንቀፅ 9(1) መረዳት ይቻላል፡፡ ሆኖም አካለ መጠን ካላደረሰ ልጅ ጋር የተደረገ ልዩ የጥበቃ ስምምነት ከተፈረመበት ዕለት ጀምሮ ባሉት አስር ቀናት ውስጥ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርቦ መጽደቅ አለበት፡፡ ፍርድ ቤቱም አካለ መጠን ያላደረሰው ልጅ ጥቅምና ደህንነት ይበልጥ ሊረጋገጥ የሚችልበትን ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጥበቃ ስምምነቱን መሻር፣ ማጽደቅ ወይም ማሻሻል እንደሚችል በአዋጁ አንቀጽ 9(4) ስር ተደንግጎ ይገኛል፡፡
3. ዋና ዋና የጥበቃ አይነቶች
3.1 ማንነትን መደበቅ፦ የጠቋሚው ማንነት በምርመራ እና ክስ ሂደት ውስጥ በምስጢር እንዲያዝ ይደረጋል።
3.2 ከበቀል ጥበቃ፦ ጠቋሚዎች በስራ ቦታቸው ወይም በሌላ ቦታ ላይ ለጠቆሙት ጥቆማ በቀል እንዳይደርስባቸው ህጉ ይከለክላል።
3.3 የደህንነት ከለላ፦ የወንጀል ድርጊቶችን በመጠቆማቸው ህይወታቸው ወይም ንብረታቸው አደጋ ላይ ሊወድቅ በሚችልበት ጊዜ ጥበቃ ይደረግላቸዋል።
3.4 ህጋዊ ጥበቃ (Immunities): ጠቋሚዎች ከሰጡት መረጃ ጋር በተያያዘ ከፍትሐብሔር ወይም የወንጀል ተጠያቂነት ጥበቃ ሊደረግላቸው ይችላል። እነዚህ ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ በዝርዝር ሌሎቹንም ጨምሮ ከዚህ በታች ባለው ክፍል የጥበቃ አይነት እና ጥበቃ ለሚያስፈልጋቸው አካላት የሚወሰድላቸው የህግ ጥበቃ አፈጻጸም እንመለከታለን።
4. የጥበቃ ዓይነቶች እና አፈጻጸም
ለወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የሚደረጉ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች በአዋጁ አንቀጽ 4 ስር ተዘርዝረው ይገኛሉ፡፡ የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች እንደ ሁኔታው በተናጠል ወይም በጣምራ ለጥበቃ ተጠቃሚ ተፈጻሚ የሚደረጉ ሲሆን ይህም ፡-
የአካልና ንብረት ደህንነት ጥበቃ
የመኖሪያ ስፍራ መቀየርን ጨምሮ ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ ቦታ መስጠት
ማንነትንና ባለንብረትነትን መደበቅ
ማንነትን መቀየር
ለራስ መጠበቂያ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መስጠት
መረጃ በተሰጠበት የወንጀል ድርጊት ያለመከሰስ
መረጃ በሚሰጥበት የወንጀል ጉዳይ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊትም ሆነ በኋላ ተከሳሽ በጥበቃ ተጠቃሚው መኖሪያ ወይም የሥራ ቦታ ወይም ትምህርት ቤት አካባቢ እንዳይደርስ ማገድ
የፍርድ ሂደት ተጀምሮ ምስክርነት እስከሚሰጥ ድረስ የምስክር ማንነት እንዳይገለጽ ማድረግ
ምስክርነት በዝግ ችሎት እንዲሰጥ ማድረግ
ምስክርነት በአካል ሳይታይ ከመጋረጃ በስተጀርባ ሆኖ ወይም ማንነትን በመሸፈን እንዲሰጥ ማድረግ
ማስረጃ በኤሌክትሮኒክስ ወይም በሌላ የተለየ ዘዴ እንዲቀርብ ማድረግ
በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት
እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት
የጥበቃ እርምጃው የመኖሪያ ስፍራን ለውጥ ካስከተለ የጓዝ ማንሻ ወጪን መሸፈን
በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ
በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነጻ መስጠት
በጥበቃ እርምጃው ምክንያት ለደረሰ የገቢ ማጣት ወይም በበቀል እርምጃ ለደረሰ የመሥራት ችሎታ ማጣት የመሠረታዊ ፍላጎት ማሟያ ወጪን መሸፈን
በጥበቃ ሥር እያለ ለደረሰ ሞት የቀብር ማስፈጸሚያ ወጪ መሸፈንና ለቤተሰብ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ
የጥበቃ ተጠቃሚው የሥራና የትምህርት ዕድል እንዲያገኝ መርዳት
ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን የሚያካትት ነው፡፡
5. ለምስክር ወይም ጠቋሚዎች ጥበቃ የሚደረግባቸው ወንጀሎች የትኞቹ ናቸው?
ለምስክሮች ወይም ለጠቋሚዎች ጥበቃ የሚደረገው በህጉ ለተመለከቱት ወንጀሎች ሲሆን በወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003 አንቀጽ 3 መሰረት የጥበቃ እና የጥንቃቄ እርምጃዎች ማግኘት የሚቻለው የፅኑ እስራት መነሻው ምንም ይሁን ምን ጣራው ግን 10 (አስር አመት) እና ከዚያ በላይ በሆነ ፅኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ በሚችል ወንጀል ምስክርነት ወይም ጥቆማን የተመለከተ ሆኖ
የወንጀል ድርጊቱ ያለምስክሩ ወይም ያለጠቋሚው ምስክርነት ወይም ጥቆማ በሌላ ማናቸውም መንገድ ሊረጋገጥ ወይም ሊደረስበት የማይችል ሲሆን እና
በምስክሩ፣ በጠቋሚው ወይም በቤተሰቡ ህይወት፣ አካላዊ ደህንነ፣ ነፃነት ወይም ንብረት ላይ ከባድ አደጋ ያደርሳል ተብሎ ሲታመን እንደሆነ ከአዋጁ አንቀፅ 3(1) መረዳት ይቻላል፡፡
ለአብነትም በኢትዮጵያ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀፅ 16 እና በሰው የመነገድ እና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀፅ 25 የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች በአዋጅ ቁጥር 699/2003 መሰረት ለወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ስለሚደረግ ጥበቃ ደንግገው ይገኛሉ፡፡
ነገር ግን አዋጁ ይህንን መስፈርት ቢያስቀምጥም የፍትህ ሚኒስቴሩ የጥበቃ ተጠቃሚ ላልሆኑ ለማንኛቸውም ምስክሮችና ጠቋሚዎችም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 4 ስር ከተቀመጡ አንዳንድ ጥበቃዎችን እንደአስፈላጊነቱ ሊያደርግ ይችላል፡፡
ይህም
በሚስጥር መያዝ ያለበት ካልሆነ በስተቀር ለጠቋሚ ጥቆማ ባቀረበበት ጉዳይ ላይ ወቅታዊ መረጃና ምክር መስጠት
እንዲመሰክር ለተጠራ ምስክር የጉዞና የውሎ አበል መስጠት
በበቀል የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲታገድ ወይም እንዲሻር ማድረግ ወይም ተመጣጣኝ የሆነ የማካካሻ እርምጃ መውሰድ
በበቀል እርምጃ ለደረሰ ጉዳት የህክምና አገልግሎት በመንግሥት ሆስፒታል በነጻ መስጠት
ለምስክሩ ወይም ለጠቋሚው የምክር አገልግሎት መስጠት ወይም እንዲያገኝ ማድረግን የሚያካትት ነው፡፡
6. የጹሁፉ ቁልፍ የህግ ማጠቃለያ
የዚህ ጽሁፍ መነሻ የአዋጅ ቁጥር 699/2003 ስለ ወንጀል ጠቋሚዎችና ምስክሮች የሚደረግ የህግ ጥበቃ ሲሆን ከላይ በቀረበው አግባብ የህግ ግንዛቤ መስጠት በተለይም ረቂቅና ከበድ ወንጀሎችን በህዝብና በሀገር ላይ ከባድ ጉዳትን የሚያስከትሉትን ወንጀሎች እንዲጋለጡ ምስክሮችም የህግ ጥበቃ ኖሮዋቸው የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ በዚህ አዋጅ መሠረት ማድረጉ ለህበረተሰቡና ለሀገር ሰላም የሚበጅ ሲሆን በተቃራኒው እንደዚህ አይነት ሰወች በመጠቆማቸው ወይም በመመስከራቸው ምክንያት የአደጋ ወይም የወንጀል ሰለባ ቢሆኑ ለሌላውም ዜጋ በዚህ ልክ ትብብር ለመስጠት የሚፈራ በመሆኑ ፍትህ ተደብቃ የምትቀርበት ሁኔታ ይፈጠራል።ስለሆነም ለከባድ ወንጀል ጠቋሚዎች እና ለምስክሮች መንግስት አስፈላጊውን የህግ ጥበቃ ሊያደርግና ከዚህ አንጻር ለማህበረሰቡ አስፈላጊውን የህግ ግንዛቤ ሊሰጥ ያስፈልጋል።
https://t.me/Fantahunlawye...
https://www.facebook.com/s...
ማጣቀሻዎች/References/
1. የወንጀል ምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 699/2003
2. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ 1996
3. የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ስነስረአት
4. የኢፊድሪ ወንጀል ስነስረአት እና የማስረጃ ህግ
5. የፍትህ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር የፌስቡክ ገጽ
2 months ago
የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረቷን ተነጥቃ መውጣቷን አስታወቀች
በሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ የምትመራው የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን፣ በአከራዮች በኩል የቀረበ "የሀሰት ምስክርነት" የፍትህ ሂደቱን አጥምሞታል ስትል በመውቀስ፣ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረቷን አስረክባ ከአገልግሎት ቦታዋ እንድትወጣ መደረጉን ገለጸች። ቤተክርስቲያኗ ላለፉት አራት ዓመታት በሕግ ስትከራከር የቆየች ቢሆንም፣ የካቲት 3 ቀን 2018 ዓ.ም የግቢውን ንብረት አስረክባ እንድትወጣ መደረጉ ታውቋል።
የክርክሩ መነሻ እና የቤተክርስቲያኗ አቋም፦
በ2013 ዓ.ም በ4.5 ሚሊዮን ብር ወጪ አዲስ አዳራሽና ስድስት ክፍሎችን የገነባችው ቤተክርስቲያኗ፣ ግንባታው እንደተጠናቀቀ አከራዮች የቤት ኪራዩን ከ60 ሺህ ወደ 150 ሺህ ብር (ከ100% በላይ) ከፍ በማድረጋቸው አለመግባባቱ ተፈጥሯል።
ቤተክርስቲያኒቱ በግቢው ውስጥ የገነባችውና ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት "ተቀምቻለሁ" ስትል ቅሬታዋን አቅርባለች።
አከራዮች ላለፉት አራት ዓመታት በማህበራዊ ሚዲያ "ተዘረፍን" በማለት የሀሰት ዘመቻ ሲያካሂዱብን ቆይተዋል ስትል ቤተክርስቲያኗ ወቅሳለች።
ማኅበራዊ አስተዋጽኦ እና የበጎ አድራጎት ስራዎች፦
ቤተክርስቲያኗ ላለፉት 16 ዓመታት በአገር አቀፍ እና በአካባቢ ልማት ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረጓን በመግለጽ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ጠቅሳለች፦
ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ላበረከተችው ድጋፍ የ2014 ዓ.ም የዕውቅና ሰርተፍኬት ማግኘቷ። በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ለሚገኙ 85 ህጻናት እና 15 አረጋውያን የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጓ። የተማሪዎች ምገባ አዳራሽ ግንባታ፣ የደም ልገሳ እና የአረጋውያን ቤት እድሳት ላይ መሳተፏ።
ቤተክርስቲያኗ የፍትህ አካላት የሕዝብ ንብረት መነጠቁን ተገንዝበው ፍትህ እንዲሰጧት የጠየቀች ሲሆን፣ ሙሉ መረጃውን ምዕመናን በጎስፕል ቲቪ (Gospel TV) እና በሀሌታ ቲቪ (Haleta TV) መከታተል እንደሚችሉ ገልጻለች።
በሬቨ. ዶ/ር ተዘራ ያሬድ የምትመራው የክብር ሕይወት ቤተክርስቲያን፣ በአከራዮች በኩል የቀረበ "የሀሰት ምስክርነት" የፍትህ ሂደቱን አጥምሞታል ስትል በመውቀስ፣ ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረቷን አስረክባ ከአገልግሎት ቦታዋ እንድትወጣ መደረጉን ገለጸች። ቤተክርስቲያኗ ላለፉት አራት ዓመታት በሕግ ስትከራከር የቆየች ቢሆንም፣ የካቲት 3 ቀን 2018 ዓ.ም የግቢውን ንብረት አስረክባ እንድትወጣ መደረጉ ታውቋል።
የክርክሩ መነሻ እና የቤተክርስቲያኗ አቋም፦
በ2013 ዓ.ም በ4.5 ሚሊዮን ብር ወጪ አዲስ አዳራሽና ስድስት ክፍሎችን የገነባችው ቤተክርስቲያኗ፣ ግንባታው እንደተጠናቀቀ አከራዮች የቤት ኪራዩን ከ60 ሺህ ወደ 150 ሺህ ብር (ከ100% በላይ) ከፍ በማድረጋቸው አለመግባባቱ ተፈጥሯል።
ቤተክርስቲያኒቱ በግቢው ውስጥ የገነባችውና ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት "ተቀምቻለሁ" ስትል ቅሬታዋን አቅርባለች።
አከራዮች ላለፉት አራት ዓመታት በማህበራዊ ሚዲያ "ተዘረፍን" በማለት የሀሰት ዘመቻ ሲያካሂዱብን ቆይተዋል ስትል ቤተክርስቲያኗ ወቅሳለች።
ማኅበራዊ አስተዋጽኦ እና የበጎ አድራጎት ስራዎች፦
ቤተክርስቲያኗ ላለፉት 16 ዓመታት በአገር አቀፍ እና በአካባቢ ልማት ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረጓን በመግለጽ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች ጠቅሳለች፦
ለህዳሴ ግድብ ግንባታ ላበረከተችው ድጋፍ የ2014 ዓ.ም የዕውቅና ሰርተፍኬት ማግኘቷ። በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ለሚገኙ 85 ህጻናት እና 15 አረጋውያን የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጓ። የተማሪዎች ምገባ አዳራሽ ግንባታ፣ የደም ልገሳ እና የአረጋውያን ቤት እድሳት ላይ መሳተፏ።
ቤተክርስቲያኗ የፍትህ አካላት የሕዝብ ንብረት መነጠቁን ተገንዝበው ፍትህ እንዲሰጧት የጠየቀች ሲሆን፣ ሙሉ መረጃውን ምዕመናን በጎስፕል ቲቪ (Gospel TV) እና በሀሌታ ቲቪ (Haleta TV) መከታተል እንደሚችሉ ገልጻለች።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
‹‹ያለ እውቀት በሚነገር ቃል፤ በጎውን ሥራ/ምክር የሚያጨልም ይህ ማነው?!››
ስለመቄዶንያው ብንያም በለጠ፡- ያየነውን እንመስክራለን፤ የሰማነውን እንናገራለን!!
ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር መድረክ የመቄዶንያው መስራች ብንያም በለጠን በተመለከተ ምክርና ወቀሳ አዘል የሆኑ ጽሑፎች ሲዘዋወሩ ነበር፡፡ የጽሑፎቹ ሐሳብ ከታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ፤ ከመጽሐፈ ኢዮብ አንድ ኃይለ-ቃልን አስታወሰኝ፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላል፤
‹‹ያለ እውቀት በሚነገር ቃል፤ በጎውን ሥራ የሚያጨልም ይህ ማነው?!››
ከዚሁ የሐሳብ ሰበዝ ሳልወጣ በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን ማእከል በነበረኝ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቆይታዬ የታዘብኩትን የግሌን ምስክርነት በጥቂቱ ላንሳ፡፡
ብንያምን የማውቀው ከዓመታት በፊት ኮተቤ በወላጆቹ ቤት 100 የሚሆኑ አረጋውያንና አእምሮ ሕሙማንን ሰብስቦ ሲረዳ ነው፡፡ በወቅቱ ማእከሉ ሙሉ በሙሉ ሥራውን ሲያካሂድ የነበረው በበጎ ፈቃደኛ አገልጋዮች ነበር፡፡ እናም አንድ ወቅት ላይ ከአንድ መነኩሴ አባት ጋር በመሆን በበጎ ፈቃደኝነት መቄዶንያን ለማገልግል አብረን ሄድን፡፡
ብንያም በትሕትና ከተቀበለን በኋላ የመጣንበትን ምክንያታችንን ገለጽንለት፡፡ ትሑት በሆነ መንፈስ ምስጋናውን ከገለጸልን በኋላ ፈቃዳችን ቢሆን ለተወሰኑ ጊዜያት እዛው ማእከሉ ውስጥ ከአረጋውያንና ከአእምሮ ሕሙማን ወገኖቻችን ጋር እየኖረን እንድናገለግል ጠየቀን፡፡ እኔም በዕድሜ አረጋዊ የሆኑትም መነኩሴ አባት በሐሳቡ ተስማማን፡፡
ብንያም ፈቃደኝነታችንን በአክብሮትና በምስጋና ከተቀበለ በኋላ በወላጆቹ ቪላ ቤት ውስጥ የአባቱና የእናቱን መኝታ ቤት ለጊዜው ማረፊያ ይሆነን ዘንድ ለእኔና ለመነኩሴው አባት እንዲሰጠን አደረገ፡፡ ልብ በሉ ብንያም ይህን ያማረውን የወላጆቹን መኝታ ቤት እኛ እንዳናርፍበት ሲሰጠን የእርሱ ማረፊያ ክፍል ግን በግቢው ውስጥ በጭቃ በተሠራ ሰርቪስ ቤት ውስጥ ነበር፡፡
ይህ ብቻ አይደለም በቆይታዬ እንደታዘብኩት፤ ብንያም አረጋውያኑ የበሉትን ይበላል፤ የለበሱትን ይለብሳል፤ አብሮአቸው ይውላል፤ አብሮአቸው ያድራል፡፡ እንደውም በማእከሉ ውስጥ ከእርሱ ይልቅ ልዩ እንክብካቤ የሚደረግላቸው አረጋውያን አባቶችና እናቶች ነበሩ፡፡
ይህን ገና ከጅምሩ የመቄዶንያ ቀኝ እጅ የሆነውና ሠርጉን ጭምር በመቄዶንያ ያደረገው ሰይፉ ፋንታሁን፤ አብረውት ይሠሩ የነበሩት ታዬ ወርቁ፣ ጋዜጠኛ ዕፀገነት/የኢቢኤሷ፣ የስፖርት ጋዜጠኛው ታደለ፤ ሀብታሙ አረጋ፤ ከተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድ/ት ከጡረታ ከተገለሉ በኋላ የማእከሉ በጎ ፈቃደኛ የነበሩት ዶ/ር ጌታቸው ተድላ… በወቅቱ በማእከሉ አብረውን የነበሩ ሌሎች በጎ ፈቃደኞችና ማእከሉን ለመጎብኘት የሚመጡ ወገኖች ሁሉ የሚያውቁት፤ የሚመሰክሩት እውነታ ነው፡፡
በመጨረሻም፤
መቄዶንያ የሰዎች እንጂ የመላእክት ስብስብ ያለበት ቦታ አይለደም፡፡ እግር ጥሎት ለሄደም ሆነ በማእከሉ በቅርበት ለሚከታተል ሰው ሊታዘባቸው የሚችላቸው ጥቃቅንም ሆነ ጉልህ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ የማእከሉ ዋና ግብ ግን የቀኑ ጸሐይ፣ የሌሊቱ ቁር የሚፈራረቅባቸውን አረጋውያን አባቶችና እናቶች ከጎዳና ላይ በማንሳት በቀሪ ጥቂት ዘመናቸውን እፎይ ብለው የሚያርፉበት መጠለያ፣ ምግብ፣ አልባሳትና ቤተሰባዊ እንክብካቤ ማሟላት ነው፡፡ ይህን ደግሞ መቄዶንያ ደጋግ ልብ ካላቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖች ጋር በመሆን በስፋት እየሠራ ነው፡፡
ተቺዎቹ፤ ‹‹ብንያም አለባበሱን እንዲቀይር ከመምከርም ባሻገር ምስኪን መስሎ መታየት ምንድ ነው? ነቃ ነቃ በል እንጂ…›› በሚል ላነሱት አስተያየት ይህን ብዬ ጽሑፌን ልቋጭ፡፡
ህንዳውያን ‹‹ታላቁ ነፍስ›› በማለት የሚጠሯቸው የህንድ የነጻት አባት ማሕተመ ጋንዲ በሕይወት ዘመናቸው ልብሳቸው አንድና ተመሳሳይ ነበር፡፡ እኚህ ሰው ከህንዳውያኑ ተራ ዜጎች የተለየ አለባበስና አመጋገብ አልነበራቸውም፡፡ እርሳቸውን ለማግኘት/ለመጎብኘት ለሚመጡት ለታላላቅ የዓለማችን መሪዎች ሆነ ለምድራችን ምስኪኖችንና ጎስቋሎች የነበራቸው አቀባባል፤ የሚያሳዩት ክብር፣ የሚሰጡት ፍቅርና ትሕትና ተመሳሳይ ነበር፡፡
ጋንዲ በአለባበሳቸውም ሆነ በአኗኗራቸው ይህን ተራ መንገድ የተከተሉት ወደውና ፈቅደው እንጂ ገንዘብ ስለቸገራቸው አይደለም፡፡ እኚያ ታላቅ ሰው ባላቸው ተቀባይነት፣ ክብርና ዝና የተነሳ ወርቅ መልበስ፣ በወርቅ ሰሀን መብላት የሚያስችል ዕድል የነበራቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ግን እርሳቸው ያን መንገድ አልፈለጉትም፡፡ ተራ መስለው ግን ደግሞ ታላቅ ሥራን ሠርተው ያለፉ የምድራችን ታላቅ ሰው ናቸው፡፡
እንደ መውጫ፤
መቄዶንያን/ብንያምን በተመለከተ ችግር አለ ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ የሚሏቸውን ችግሮች ለመቅረፍ ተባብሮ መስራት እንጂ ከውጪ ሆነ መተቸት ለውጥ ያመጣል ብዬ አላስብም፡
ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ፤ ‹‹ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ሁሉ ምስጋናና ክብር፤ ሰላምም ይሆንላቸዋል፤›› እንዲል፤ ወንድማችን ብንያም ስላደረገኸውና እያደረግኽ ስላለው የበጎነት ሥራ ከፈጣሪ ዘንድ ምስጋናና ክብር፤ የበዛ ሰላም ይሁንልህ!!
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
ስለመቄዶንያው ብንያም በለጠ፡- ያየነውን እንመስክራለን፤ የሰማነውን እንናገራለን!!
ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር መድረክ የመቄዶንያው መስራች ብንያም በለጠን በተመለከተ ምክርና ወቀሳ አዘል የሆኑ ጽሑፎች ሲዘዋወሩ ነበር፡፡ የጽሑፎቹ ሐሳብ ከታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ፤ ከመጽሐፈ ኢዮብ አንድ ኃይለ-ቃልን አስታወሰኝ፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላል፤
‹‹ያለ እውቀት በሚነገር ቃል፤ በጎውን ሥራ የሚያጨልም ይህ ማነው?!››
ከዚሁ የሐሳብ ሰበዝ ሳልወጣ በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን ማእከል በነበረኝ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ቆይታዬ የታዘብኩትን የግሌን ምስክርነት በጥቂቱ ላንሳ፡፡
ብንያምን የማውቀው ከዓመታት በፊት ኮተቤ በወላጆቹ ቤት 100 የሚሆኑ አረጋውያንና አእምሮ ሕሙማንን ሰብስቦ ሲረዳ ነው፡፡ በወቅቱ ማእከሉ ሙሉ በሙሉ ሥራውን ሲያካሂድ የነበረው በበጎ ፈቃደኛ አገልጋዮች ነበር፡፡ እናም አንድ ወቅት ላይ ከአንድ መነኩሴ አባት ጋር በመሆን በበጎ ፈቃደኝነት መቄዶንያን ለማገልግል አብረን ሄድን፡፡
ብንያም በትሕትና ከተቀበለን በኋላ የመጣንበትን ምክንያታችንን ገለጽንለት፡፡ ትሑት በሆነ መንፈስ ምስጋናውን ከገለጸልን በኋላ ፈቃዳችን ቢሆን ለተወሰኑ ጊዜያት እዛው ማእከሉ ውስጥ ከአረጋውያንና ከአእምሮ ሕሙማን ወገኖቻችን ጋር እየኖረን እንድናገለግል ጠየቀን፡፡ እኔም በዕድሜ አረጋዊ የሆኑትም መነኩሴ አባት በሐሳቡ ተስማማን፡፡
ብንያም ፈቃደኝነታችንን በአክብሮትና በምስጋና ከተቀበለ በኋላ በወላጆቹ ቪላ ቤት ውስጥ የአባቱና የእናቱን መኝታ ቤት ለጊዜው ማረፊያ ይሆነን ዘንድ ለእኔና ለመነኩሴው አባት እንዲሰጠን አደረገ፡፡ ልብ በሉ ብንያም ይህን ያማረውን የወላጆቹን መኝታ ቤት እኛ እንዳናርፍበት ሲሰጠን የእርሱ ማረፊያ ክፍል ግን በግቢው ውስጥ በጭቃ በተሠራ ሰርቪስ ቤት ውስጥ ነበር፡፡
ይህ ብቻ አይደለም በቆይታዬ እንደታዘብኩት፤ ብንያም አረጋውያኑ የበሉትን ይበላል፤ የለበሱትን ይለብሳል፤ አብሮአቸው ይውላል፤ አብሮአቸው ያድራል፡፡ እንደውም በማእከሉ ውስጥ ከእርሱ ይልቅ ልዩ እንክብካቤ የሚደረግላቸው አረጋውያን አባቶችና እናቶች ነበሩ፡፡
ይህን ገና ከጅምሩ የመቄዶንያ ቀኝ እጅ የሆነውና ሠርጉን ጭምር በመቄዶንያ ያደረገው ሰይፉ ፋንታሁን፤ አብረውት ይሠሩ የነበሩት ታዬ ወርቁ፣ ጋዜጠኛ ዕፀገነት/የኢቢኤሷ፣ የስፖርት ጋዜጠኛው ታደለ፤ ሀብታሙ አረጋ፤ ከተባበሩት መንግሥታት የምግብ ድ/ት ከጡረታ ከተገለሉ በኋላ የማእከሉ በጎ ፈቃደኛ የነበሩት ዶ/ር ጌታቸው ተድላ… በወቅቱ በማእከሉ አብረውን የነበሩ ሌሎች በጎ ፈቃደኞችና ማእከሉን ለመጎብኘት የሚመጡ ወገኖች ሁሉ የሚያውቁት፤ የሚመሰክሩት እውነታ ነው፡፡
በመጨረሻም፤
መቄዶንያ የሰዎች እንጂ የመላእክት ስብስብ ያለበት ቦታ አይለደም፡፡ እግር ጥሎት ለሄደም ሆነ በማእከሉ በቅርበት ለሚከታተል ሰው ሊታዘባቸው የሚችላቸው ጥቃቅንም ሆነ ጉልህ ችግሮች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ የማእከሉ ዋና ግብ ግን የቀኑ ጸሐይ፣ የሌሊቱ ቁር የሚፈራረቅባቸውን አረጋውያን አባቶችና እናቶች ከጎዳና ላይ በማንሳት በቀሪ ጥቂት ዘመናቸውን እፎይ ብለው የሚያርፉበት መጠለያ፣ ምግብ፣ አልባሳትና ቤተሰባዊ እንክብካቤ ማሟላት ነው፡፡ ይህን ደግሞ መቄዶንያ ደጋግ ልብ ካላቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖች ጋር በመሆን በስፋት እየሠራ ነው፡፡
ተቺዎቹ፤ ‹‹ብንያም አለባበሱን እንዲቀይር ከመምከርም ባሻገር ምስኪን መስሎ መታየት ምንድ ነው? ነቃ ነቃ በል እንጂ…›› በሚል ላነሱት አስተያየት ይህን ብዬ ጽሑፌን ልቋጭ፡፡
ህንዳውያን ‹‹ታላቁ ነፍስ›› በማለት የሚጠሯቸው የህንድ የነጻት አባት ማሕተመ ጋንዲ በሕይወት ዘመናቸው ልብሳቸው አንድና ተመሳሳይ ነበር፡፡ እኚህ ሰው ከህንዳውያኑ ተራ ዜጎች የተለየ አለባበስና አመጋገብ አልነበራቸውም፡፡ እርሳቸውን ለማግኘት/ለመጎብኘት ለሚመጡት ለታላላቅ የዓለማችን መሪዎች ሆነ ለምድራችን ምስኪኖችንና ጎስቋሎች የነበራቸው አቀባባል፤ የሚያሳዩት ክብር፣ የሚሰጡት ፍቅርና ትሕትና ተመሳሳይ ነበር፡፡
ጋንዲ በአለባበሳቸውም ሆነ በአኗኗራቸው ይህን ተራ መንገድ የተከተሉት ወደውና ፈቅደው እንጂ ገንዘብ ስለቸገራቸው አይደለም፡፡ እኚያ ታላቅ ሰው ባላቸው ተቀባይነት፣ ክብርና ዝና የተነሳ ወርቅ መልበስ፣ በወርቅ ሰሀን መብላት የሚያስችል ዕድል የነበራቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ግን እርሳቸው ያን መንገድ አልፈለጉትም፡፡ ተራ መስለው ግን ደግሞ ታላቅ ሥራን ሠርተው ያለፉ የምድራችን ታላቅ ሰው ናቸው፡፡
እንደ መውጫ፤
መቄዶንያን/ብንያምን በተመለከተ ችግር አለ ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ የሚሏቸውን ችግሮች ለመቅረፍ ተባብሮ መስራት እንጂ ከውጪ ሆነ መተቸት ለውጥ ያመጣል ብዬ አላስብም፡
ታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ፤ ‹‹ነገር ግን በጎ ሥራ ለሚያደርጉ ሁሉ ምስጋናና ክብር፤ ሰላምም ይሆንላቸዋል፤›› እንዲል፤ ወንድማችን ብንያም ስላደረገኸውና እያደረግኽ ስላለው የበጎነት ሥራ ከፈጣሪ ዘንድ ምስጋናና ክብር፤ የበዛ ሰላም ይሁንልህ!!
ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
3 months ago
በዚህ ታሪካዊ የድህነት ስፍራ ተጠርታችኋል!!!
ከ103 ዓመት በላይ ባስቆጠረው ብዙ ገቢረ ተአምራት ወደሚደረግበት ወደ ሰሚ በዕለቱ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
የጉዞ ዋጋ 300 ብር (ደርሶ መልስ )
ለመመዝገብ በ0950008283
የጉዞ ቀን ቅዳሜ በ12 እና እሁድ በ13 ውሎ ገብ
ብዙ ሰዎች በቦታው እየደረሱ በዚህ ቅዱስ ስፍራ ቋጠሯቸው እየተፈታ እየተመለሱ ነው በእለት ስለታችሁን ሰምቶ ለምስክርነት ያብቃችሁ።
Comments