23 days ago
ከቁጥሮች በስተጀርባ ያለው ሀገራዊ ተስፋ
**********
ሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሂቃን መድረክ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ኅብረተሰብ ድምፅ የሚሰማበት ታሪካዊ ሂደት ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራት ስታቲስቲካዊ መረጃዎች ስንመረምር፣ ተቋሙ በመሬት ላይ ያሉ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ ምን ያህል ሰፊ ርቀት መጓዝ እንደቻለ ቁጥሮቹ በራሳቸው ጉልህ ምስክርነት ይሰጣሉ።
የአንድ ሀገራዊ ምክክር ስኬት በዋናነት የሚለካው ባረጋገጠው የተደራሽነት መጠን እና ሽፋን ነው።
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከሁሉም የማኅበረሰብ ከፍል የተወከሉ 400 ተሳታፊዎችን ያካተተ መድረክ በማዘጋጀት ነው ሥራውን የጀመረው። በአሁኑ ወቅት የሀገራችንን 93 በመቶ መልክዓ ምድራዊ ወሰን መሸፈን ችሏል።
ከ11 ክልሎች እና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ1 ሺህ 234 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመለየት ለአጠቃላይ ምክክሩ የሚሆኑ የአጀንዳ ሐሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል።
ሙሉ መረጃውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopian #nationaldialogue #inclusivedialogue #nationalconsensus #ebc
**********
ሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ልሂቃን መድረክ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ኅብረተሰብ ድምፅ የሚሰማበት ታሪካዊ ሂደት ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያከናወናቸውን ተግባራት ስታቲስቲካዊ መረጃዎች ስንመረምር፣ ተቋሙ በመሬት ላይ ያሉ ፈተናዎችን እየተጋፈጠ ምን ያህል ሰፊ ርቀት መጓዝ እንደቻለ ቁጥሮቹ በራሳቸው ጉልህ ምስክርነት ይሰጣሉ።
የአንድ ሀገራዊ ምክክር ስኬት በዋናነት የሚለካው ባረጋገጠው የተደራሽነት መጠን እና ሽፋን ነው።
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከሁሉም የማኅበረሰብ ከፍል የተወከሉ 400 ተሳታፊዎችን ያካተተ መድረክ በማዘጋጀት ነው ሥራውን የጀመረው። በአሁኑ ወቅት የሀገራችንን 93 በመቶ መልክዓ ምድራዊ ወሰን መሸፈን ችሏል።
ከ11 ክልሎች እና ከ2 የከተማ አስተዳደሮች የተውጣጡ ከ1 ሺህ 234 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመለየት ለአጠቃላይ ምክክሩ የሚሆኑ የአጀንዳ ሐሳቦችን ለኮሚሽኑ አስረክበዋል።
ሙሉ መረጃውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopian #nationaldialogue #inclusivedialogue #nationalconsensus #ebc
Comments