8 hours ago
ኢትዮጵያ እየተጠናቀቀ ባለው 2018 ዓ.ም ከ124 በላይ ዓለም አቀፍ ሜዳሊያዎች መገኘታቸውን ተገለጸ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
#ethiopia | በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ አዲስ እይታን በመፍጠር፣ ህጋዊና መዋቅራዊ ማዕቀፎችን በማጠናከር እንዲሁም በርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ የ2018 በጀት ዓመት አመርቂና ስኬታማ ጊዜ የነበረ መሆኑ ተገለጸ።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚያካሄደው የባህል፣ ጥበባትና ስፖርት ጥናትና ምርምር ጉባኤ እንዲሁም ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ ላይ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ አቶ መክዩ መሀመድ እንደገለጹት፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዓመታዊ የሴክተር ጉባኤ የታቀዱ ግቦችን በጋራ ለመገምገም እና ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
አክለውም ዘንድሮ የስፖርት ልማት ስራዎች በተሻለ መንገድ የተፈጸሙበትና በአጠቃላይ የስፖርት ዘመን ተብሎ ሊወሰድ የሚችልበት የስኬት ዓመት እንደነበር ጠቁመዋል።
የስፖርት ቤተሰቡ በተደጋጋሚ ያነሳቸው የነበሩ ህጋዊና አሰራር ነክ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትር ድኤታው፣ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትና ምሁራንን ያሳተፈ አዲስ የስፖርት ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁንና አዋጁም ወደ ትግበራ መግባቱን አስረድተዋል።
ይህ አዲስ ፖሊሲ የመንግስትን አመራር ሰጪነት፣ ከ139 ሺህ በላይ የሚሆኑ ህዝባዊ አደረጃጀቶችንና ማህበራትን አቅጣጫ፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚያፋጥነው የግል ባለሀብቶች ተሳትፎን በግልጽ የለየ አዲስ እይታ ይዞ መምጣቱንም አብራርተዋል።
ስፖርት ከሜዳ ውድድር ባለፈ የህዝቦች ወንድማማችነትን የሚገነባ፣ ሰላምና አንድነትን የሚያጠናክር ትልቅ የሀገር ልማት መሳሪያ መሆኑን የገለጹት አቶ መክዩ መሀመድ፣ በዚህ ዓመት በተካሄዱ 420 የክልል አቀፍ እና 118 ሀገር አቀፍ ውድድሮች ከአስር ሺዎች በላይ ስፖርተኞች መሳተፋቸውን ገልጸዋል። እነዚህ መድረኮች የወጡ አትሌቶችን ከማፍራት ባሻገር ሰላምን በመገንባትና ህዝቦችን በማቀራረብ ረገድ የጎላ ሚና እንደነበራቸው አብራርተዋል።
ህብረተሰቡን ንቁና ስፖርትን ባህል ያደረገ ለማድረግ በተሰራው ስራ የስፖርት አዘዋታሪው ህዝብ ቁጥር 24 በመቶ ወይም 32 ሚሊዮን ማድረስ መቻሉን ሚኒስትር ድኤታው ጠቁመዋል። ከዚህ በተጨማሪ ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ ከ45 ሺህ በላይ የስፖርት ፋሲሊቲዎች መገንባታቸውንና እነዚህንም በቴክኖሎጂ ዘመናዊ የማድረግ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአለም አቀፍና ቀጠናዊ ውድድሮች የሀገሪቱን ስም የሚያስጠሩ አሸናፊ ብሄራዊ ቡድኖችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት አትሌቶቻችን ከ124 በላይ ሜዳሊያዎችን ማስመዝገባቸውን አቶ መክዩ መሀመድ አበክረው ገልጸዋል።
በተለይም በታዳጊዎች ልማት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ከ45 ሺህ በላይ ታዳጊዎች በማሰልጠኛ ማዕከላት ውስጥ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የስፖርት ቱሪዝምን ለማበራታት በተደረገው ጥረት ከ29 በላይ ዓለም አቀፍ ውድድሮችና ኮንፈረንሶች በኢትዮጵያ መካሄዳቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች ግንባታም ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ስፖርት ለሀገር ጂዲፒ እና ለስራ እድል ፈጠራ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ የተጀመሩ ጥናቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አብራርተዋል።
በመጨረሻም፣ በአዲሱ ፖሊሲ የባህል ስፖርት ልዩ ትኩረት ማግኘቱንና በቀጣይ ዓመት ኢትዮጵያ የአፍሪካ የባህል ስፖርት ፌስቲቫልን በበላይነት እንደምታዘጋጅ አቶ መክዩ መሀመድ ገልጸው፤ ላመጣው ስኬት ለስፖርት ቤተሰቡና ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopiansports #ethiopiasportpolicy #sportsdevelopment #ethiopia#youthinsports #sportinspiration
2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
4 days ago
የአርሰናል ደጋፊዎችን የሚያገናኝ "ገነርስ" የተሰኘ ማህበር ተመሠረተ
#ethiopia | የእግር ኳስ ፍቅርን ከአባላት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር የሚያስተሳስረው አዲሱ ዓለም አቀፍ ተቋም "ገነርስ"የሚል ስያሜ የተሰጠው ማህበር በኢትዮጵያ፣ በጀርመን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መሠረቱን ጥሎ በይፋ ሥራ መጀመሩን አሳወቀ።
ተቋሙ በአለም ዙሪያ የሚገኙ የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎችን በአንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ስር በማሰባሰብ፣ አባላቱ በህይወታቸው እርስ በርስ እንዲደጋገፉ እና አዲስ የዕድል በሮች እንዲከፈቱላቸው የሚያስችል ዘላቂ ስርዓት ዘርግቷል።
ከደጋፊነት ማዕቀፍ ባለፈም ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመስረት ለአባላቱ ተጨባጭ ጥቅሞችን፣ የሥራ ዕድሎችን እና የንግድ አማራጮችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
አባላቱ በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ አገልግሎቶችን የሚዘረጋው ገርነስ ማህበር ፤ ከግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ጀምሮ እስከ ጤና፣ ሆቴል፣ ቱሪዝም እና የጉዞ አገልግሎቶች ድረስ በተመረጡ አጋር ተቋማት ልዩ ቅናሾችንና መስተንግዶዎችን እያቀረበ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ አባላትን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ ሳቢ የዲጂታል ሚዲያ ይዘቶችን በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#gunners #arsenal #arsenalethiopia #gunners #ethiopiangunners
#ethiopia | የእግር ኳስ ፍቅርን ከአባላት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ጋር የሚያስተሳስረው አዲሱ ዓለም አቀፍ ተቋም "ገነርስ"የሚል ስያሜ የተሰጠው ማህበር በኢትዮጵያ፣ በጀርመን እና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መሠረቱን ጥሎ በይፋ ሥራ መጀመሩን አሳወቀ።
ተቋሙ በአለም ዙሪያ የሚገኙ የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎችን በአንድ ጠንካራ ማህበረሰብ ስር በማሰባሰብ፣ አባላቱ በህይወታቸው እርስ በርስ እንዲደጋገፉ እና አዲስ የዕድል በሮች እንዲከፈቱላቸው የሚያስችል ዘላቂ ስርዓት ዘርግቷል።
ከደጋፊነት ማዕቀፍ ባለፈም ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነት በመመስረት ለአባላቱ ተጨባጭ ጥቅሞችን፣ የሥራ ዕድሎችን እና የንግድ አማራጮችን ለማስፋፋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
አባላቱ በዕለት ተዕለት ኑሯቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሰፊ አገልግሎቶችን የሚዘረጋው ገርነስ ማህበር ፤ ከግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች ግብይት ጀምሮ እስከ ጤና፣ ሆቴል፣ ቱሪዝም እና የጉዞ አገልግሎቶች ድረስ በተመረጡ አጋር ተቋማት ልዩ ቅናሾችንና መስተንግዶዎችን እያቀረበ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ አባላትን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ ሳቢ የዲጂታል ሚዲያ ይዘቶችን በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#gunners #arsenal #arsenalethiopia #gunners #ethiopiangunners
5 days ago
በቢሾፍቱ ከተማ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተከሉ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከጤና ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር «ጤናማ ምግብ ለአስተማማኝ ህይወት፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ ትውልድ!» በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ አድራጎት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የኮፕ 32 (COP 32) አየር ንብረት ጉባኤን ከማገዝ ባሻገር አገር በቀል፣ ፍራፍሬ እና ለመድኃኒትነት የሚውሉ ተክሎችን በመትከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዕለቱም ከሰባት ነጥብ አንድ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከምግብነት ባለፈ ለመድኃኒትነት ጭምር የሚጠቅሙ እንደ ማንጎ እና አቮካዶ ያሉ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄራን ገርባ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን አቅም ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን በምታደርገው ጥረት ውስጥ የመድኃኒትነት እጽዋትን መንከባከብ ትልቅ ድርሻ አለው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ለዕድገታቸው ተገቢውን ቋሚ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ይህንን አረንጓዴ ልማት ከምርምርና ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅምን ለማጠናከር እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በበኩላቸው፣ የጤና ሴክተሩ በበጎ ፈቃደኝነት መርሃ ግብሩ አጠቃላይ ከሁለት መቶ ኃምሳ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን አንስተዋል።
ከአዲስ አበባ እስከ ቢሾፍቱ ባለው የፍጥነት መንገድ ዳርቻ የተጀመረው ይህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከአንድ ዓመት በኋላ ከፍተኛ የእጽዋት ሽፋን እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ የተተከሉትን ችግኞች በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ለታለመለት ዓላማ ማብቃት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#greenlegacyethiopia#ethiopia
#bishoftu #climateaction #healthylife
#cop32 #healthsector #treeplanting
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከጤና ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር «ጤናማ ምግብ ለአስተማማኝ ህይወት፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ ትውልድ!» በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ አድራጎት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የኮፕ 32 (COP 32) አየር ንብረት ጉባኤን ከማገዝ ባሻገር አገር በቀል፣ ፍራፍሬ እና ለመድኃኒትነት የሚውሉ ተክሎችን በመትከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዕለቱም ከሰባት ነጥብ አንድ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከምግብነት ባለፈ ለመድኃኒትነት ጭምር የሚጠቅሙ እንደ ማንጎ እና አቮካዶ ያሉ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄራን ገርባ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን አቅም ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን በምታደርገው ጥረት ውስጥ የመድኃኒትነት እጽዋትን መንከባከብ ትልቅ ድርሻ አለው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ለዕድገታቸው ተገቢውን ቋሚ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ይህንን አረንጓዴ ልማት ከምርምርና ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅምን ለማጠናከር እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በበኩላቸው፣ የጤና ሴክተሩ በበጎ ፈቃደኝነት መርሃ ግብሩ አጠቃላይ ከሁለት መቶ ኃምሳ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን አንስተዋል።
ከአዲስ አበባ እስከ ቢሾፍቱ ባለው የፍጥነት መንገድ ዳርቻ የተጀመረው ይህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከአንድ ዓመት በኋላ ከፍተኛ የእጽዋት ሽፋን እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ የተተከሉትን ችግኞች በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ለታለመለት ዓላማ ማብቃት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#greenlegacyethiopia#ethiopia
#bishoftu #climateaction #healthylife
#cop32 #healthsector #treeplanting
6 days ago
የሞተው ሕያው የሆነበት ማሩ ከዋሻ የሚፈስበት አስደናቂው ስፍራ
♦️ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ምስራቅ በለሳ ወረዳ፣ ጎጋ ቀበሌ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ የቀደመ ታሪኩን ፣ የተፈጥሮ ግርማውንና ታአምራት በአንድ ላይ የያዘ ድንቅ መንፈሳዊ ስፍራ ነው።
አባቶች እንደሚያስረዱት የስፍራው የቀደመ መጠሪያ "ዛጅር ማኤል" ይሰኝ ነበር። ይህ ስም "ዛጅር" ማለት ውሃ በደረቅ አለት ላይ ፈንጥቆ የሚወጣበትን አቅጣጫ ሲያመላክት፣ "ማ" ዋሻውን፣ "ኤል" ደግሞ የሰማይ አምላክን በመወከል እግዚአብሔር በድንቅ ሁኔታ በደረቅ አለት ላይ ውሃ የፈነጠቀበት ስፍራ መሆኑን ይናገራሉ።
የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና ጸኃፊ አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚገልጹት፣ የቦታው ተአምራዊ ጉዞ በይፋ ጎልቶ መታየት የጀመረው በ2013 ዓ.ም የጸበል አገልግሎት ሲጀመር ነው።
በተለይም የስፍራውን ስም ከአዲሱ ስያሜ ጋር ያያዘው ታዓምር በዚሁ ዘመን ተከስቷል። ከገዳሙ 12 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በምትገኘው ዙ ሐሙሲት ከተማ አቅራቢያ የምትኖር አንዲት ሴት በጽኑ ታማ ወደ ህክምና ከተወሰደች በኋላ በቃሬዛ ላይ እያለች ህይወቷ ያልፋል።
በወቅቱ የጸበሉ አስተዳዳሪ የነበሩት አባት እና ሌሎች ካህናት አስከሬኑን ይዘው በመንገድ ላይ ሳሉ የእግዚአብሔርን ኃይል በማመን ቅዱስ ጸበሉን አፍሰው ረጩባት። በዚያው ቅጽበት የሞተችው ሴት ትንፋሽ ተመልሶላት ተነሳች፤ ሙሉ ፈውስ አግኝታም ድንቅ ምስክርነቷን ሰጠች።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጸበሉ "ሙት አንሳ" የሚለውን ስያሜ አገኘ። በኋላም ከዋሻው በላይ ከሚንጠበጠበው ማር ጋር ተያይዞ "ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም" ተብሎ መጠራት ጀመረ።
የገዳሙ መነኮሳት እንደሚናገሩት በዋሻው ጣሪያ ላይ ለዘመናት ሳይቆረጥ የቆየ ልዩ ማር ይገኛል። ይህ ማር በተለያዩ ጊዜያት በራዕይ "ተቆርጦ ለምእመናን ፈውስ ይሁን" የሚል መልእክት ይሰጥ የነበረ ቢሆንም፣ የቦታው ገደላማና አስፈሪ አቀማመጥ ማንም እንዲደፍረው አላደረገም።
ቆየት ብሎ መነኮሳቱ በጸሎትና በምህላ ሲገቡ ንቡ ቦታውን ለቆ ይወጣል። ማሩ አሁን ላይ እየተቆረጠ ለበርካታ ድውያናትና ምእመናን ዘላቂ ፈውስን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ዛሬ ለቁጥር በርካታ የሆኑ መነኮሳት የሚኖሩበት ይህ ታላቅ ገዳም የተመሰረተው በአንድ አባት መንፈሳዊ ታዛዥነትና ጽናት ነው። አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚያስረዱት፣ በ2009 ዓመተ ምህረት ግንቦት 21 ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ አባ ብርሃነ ማርያም ከድዊ አንሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ በፊታቸው የተለየ ብርሃን እየመራቸው
ቦታው ይደርሳሉ።
ያን ብርሃን እየተከተሉ የሶስት ሰዓት መንገድ በእግር ተጉዘው አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ስፍራ ሲደርሱ ብርሃኑ ተሰወረባቸው። በወቅቱ ምንም ዓይነት መኖሪያ ቤትና መጠለያ በሌለበት፣ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ በበዛበት ወቅት አባታችን በእርጥብ ዋሻ ውስጥ ማደር ጀመሩ።
እግዚአብሔርም በቸርነቱ የሚያድሩበትን ስፍራ ደረቅ በማድረግ ጠበቃቸው፤ የዕለት ምግባቸውንም የአካባቢው ህዝብና ጸበልተኞች እያመጡ ያቀርቡላቸው ነበር።
የአባታችንን ትምህርትና ተአምራዊ ፈውሱን ያዩ በርካታ መንፈሳውያን ልጆች በየጊዜው ወደ ስፍራው በመምጣታቸው የምናኔ ሀሳብ በብዙዎች ህሊና ውስጥ ሰረፀ። አባ ብርሃነ ሠላም አያይዘው እንደሚገልጹት፣ በ2011 ዓመተ ምህረት በአካባቢው ሰበካ ጉባኤ ድጋፍ የተገዙ በሬዎችን በመጠቀም መሬት ማረስና የጋራ ኑሮ ተጀመረ። በ2013 ዓመተ ምህረት የመነኮሳቱ ቁጥር ከመቶ በላይ በመድረሱ የአካባቢው ህዝብና ካህናት ተመካክረው ቦታ በመስጠታቸው ትንሽ መቃኞ ተሠርቶ ታቦተ ሚካኤል ገባ።
በመጨረሻም በ2014 ዓመተ ምህረት መስከረም 29 ቀን በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቡጽዕ አቡነ ዮሐንስ አባታዊ ቡራኬና ውሳኔ ገዳም የመሆን ሙሉ ክብሩንና ስያሜውን አገኘ።
ይህን መንፈሳዊና ታሪካዊ ገዳም የሚገኘው ከአዲስ አበባ
በሰሜን አቅጣጫ 667 ኪሎ ሜትር፣ ከባህርዳር ከተማ 183 ኪሎ ሜትር፣ ከዞኑ ጎንደር ከተማ በአዲስ ዘመን - እብናት -ጎሃላ 192 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከጎንደር ማክሰኚት- አረባያ -ጎሃላ 119 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ በአባቶችና በእናቶች ጸሎትና በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ እስከ ዛሬ የቆየ፣ ለትውልድ የሚተርፍ ታላቅ መንፈሳዊ አደራ ነው።
ይህ ገዳም ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከሰሞኑን በገዳሙና በአካባቢው በመዘዋወር እየተከናወኑ ያሉትን የልማት ሥራዎች ተመልክተናል፤ የተመለከትነውንም በተከታታይ ክፍሎች እናቀርብላችኋለን።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#mutansa #ethiopianmonastery #gondarethiopia #ethiopianorthodox #spiritualjourney
♦️ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
#ethiopia | በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ምስራቅ በለሳ ወረዳ፣ ጎጋ ቀበሌ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ የቀደመ ታሪኩን ፣ የተፈጥሮ ግርማውንና ታአምራት በአንድ ላይ የያዘ ድንቅ መንፈሳዊ ስፍራ ነው።
አባቶች እንደሚያስረዱት የስፍራው የቀደመ መጠሪያ "ዛጅር ማኤል" ይሰኝ ነበር። ይህ ስም "ዛጅር" ማለት ውሃ በደረቅ አለት ላይ ፈንጥቆ የሚወጣበትን አቅጣጫ ሲያመላክት፣ "ማ" ዋሻውን፣ "ኤል" ደግሞ የሰማይ አምላክን በመወከል እግዚአብሔር በድንቅ ሁኔታ በደረቅ አለት ላይ ውሃ የፈነጠቀበት ስፍራ መሆኑን ይናገራሉ።
የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የስብከተ ወንጌል ኃላፊ እና ጸኃፊ አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚገልጹት፣ የቦታው ተአምራዊ ጉዞ በይፋ ጎልቶ መታየት የጀመረው በ2013 ዓ.ም የጸበል አገልግሎት ሲጀመር ነው።
በተለይም የስፍራውን ስም ከአዲሱ ስያሜ ጋር ያያዘው ታዓምር በዚሁ ዘመን ተከስቷል። ከገዳሙ 12 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ በምትገኘው ዙ ሐሙሲት ከተማ አቅራቢያ የምትኖር አንዲት ሴት በጽኑ ታማ ወደ ህክምና ከተወሰደች በኋላ በቃሬዛ ላይ እያለች ህይወቷ ያልፋል።
በወቅቱ የጸበሉ አስተዳዳሪ የነበሩት አባት እና ሌሎች ካህናት አስከሬኑን ይዘው በመንገድ ላይ ሳሉ የእግዚአብሔርን ኃይል በማመን ቅዱስ ጸበሉን አፍሰው ረጩባት። በዚያው ቅጽበት የሞተችው ሴት ትንፋሽ ተመልሶላት ተነሳች፤ ሙሉ ፈውስ አግኝታም ድንቅ ምስክርነቷን ሰጠች።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ጸበሉ "ሙት አንሳ" የሚለውን ስያሜ አገኘ። በኋላም ከዋሻው በላይ ከሚንጠበጠበው ማር ጋር ተያይዞ "ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም" ተብሎ መጠራት ጀመረ።
የገዳሙ መነኮሳት እንደሚናገሩት በዋሻው ጣሪያ ላይ ለዘመናት ሳይቆረጥ የቆየ ልዩ ማር ይገኛል። ይህ ማር በተለያዩ ጊዜያት በራዕይ "ተቆርጦ ለምእመናን ፈውስ ይሁን" የሚል መልእክት ይሰጥ የነበረ ቢሆንም፣ የቦታው ገደላማና አስፈሪ አቀማመጥ ማንም እንዲደፍረው አላደረገም።
ቆየት ብሎ መነኮሳቱ በጸሎትና በምህላ ሲገቡ ንቡ ቦታውን ለቆ ይወጣል። ማሩ አሁን ላይ እየተቆረጠ ለበርካታ ድውያናትና ምእመናን ዘላቂ ፈውስን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ዛሬ ለቁጥር በርካታ የሆኑ መነኮሳት የሚኖሩበት ይህ ታላቅ ገዳም የተመሰረተው በአንድ አባት መንፈሳዊ ታዛዥነትና ጽናት ነው። አባ ብርሃነ ሠላም እንደሚያስረዱት፣ በ2009 ዓመተ ምህረት ግንቦት 21 ከሌሊቱ 10 ሰዓት ላይ አባ ብርሃነ ማርያም ከድዊ አንሳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ተነስተው ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ በፊታቸው የተለየ ብርሃን እየመራቸው
ቦታው ይደርሳሉ።
ያን ብርሃን እየተከተሉ የሶስት ሰዓት መንገድ በእግር ተጉዘው አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ስፍራ ሲደርሱ ብርሃኑ ተሰወረባቸው። በወቅቱ ምንም ዓይነት መኖሪያ ቤትና መጠለያ በሌለበት፣ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ በበዛበት ወቅት አባታችን በእርጥብ ዋሻ ውስጥ ማደር ጀመሩ።
እግዚአብሔርም በቸርነቱ የሚያድሩበትን ስፍራ ደረቅ በማድረግ ጠበቃቸው፤ የዕለት ምግባቸውንም የአካባቢው ህዝብና ጸበልተኞች እያመጡ ያቀርቡላቸው ነበር።
የአባታችንን ትምህርትና ተአምራዊ ፈውሱን ያዩ በርካታ መንፈሳውያን ልጆች በየጊዜው ወደ ስፍራው በመምጣታቸው የምናኔ ሀሳብ በብዙዎች ህሊና ውስጥ ሰረፀ። አባ ብርሃነ ሠላም አያይዘው እንደሚገልጹት፣ በ2011 ዓመተ ምህረት በአካባቢው ሰበካ ጉባኤ ድጋፍ የተገዙ በሬዎችን በመጠቀም መሬት ማረስና የጋራ ኑሮ ተጀመረ። በ2013 ዓመተ ምህረት የመነኮሳቱ ቁጥር ከመቶ በላይ በመድረሱ የአካባቢው ህዝብና ካህናት ተመካክረው ቦታ በመስጠታቸው ትንሽ መቃኞ ተሠርቶ ታቦተ ሚካኤል ገባ።
በመጨረሻም በ2014 ዓመተ ምህረት መስከረም 29 ቀን በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቡጽዕ አቡነ ዮሐንስ አባታዊ ቡራኬና ውሳኔ ገዳም የመሆን ሙሉ ክብሩንና ስያሜውን አገኘ።
ይህን መንፈሳዊና ታሪካዊ ገዳም የሚገኘው ከአዲስ አበባ
በሰሜን አቅጣጫ 667 ኪሎ ሜትር፣ ከባህርዳር ከተማ 183 ኪሎ ሜትር፣ ከዞኑ ጎንደር ከተማ በአዲስ ዘመን - እብናት -ጎሃላ 192 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከጎንደር ማክሰኚት- አረባያ -ጎሃላ 119 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም፤ በአባቶችና በእናቶች ጸሎትና በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ እስከ ዛሬ የቆየ፣ ለትውልድ የሚተርፍ ታላቅ መንፈሳዊ አደራ ነው።
ይህ ገዳም ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከሰሞኑን በገዳሙና በአካባቢው በመዘዋወር እየተከናወኑ ያሉትን የልማት ሥራዎች ተመልክተናል፤ የተመለከትነውንም በተከታታይ ክፍሎች እናቀርብላችኋለን።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#mutansa #ethiopianmonastery #gondarethiopia #ethiopianorthodox #spiritualjourney
Sponsored by
Surafel
7 days ago
በ800 ሚሊየን ችግኞች የሚጻፈው አሻራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ የሀገሪቱን ገጽታ ከመቀየር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት ህያው መድረክ ሆኗል።
በዚህ ዓመትም በይፋ በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በመላው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተከናወነ ሲሆን፤ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላን ለማከናወንም ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት ጥሪ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም ታሪክ ለመጻፍ አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ እንዲደረግ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ክንድና ህብረት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን ተክሎ ሌላ ተአምር ለማስመዝገብ የቀሩት አምስት ቀናት ብቻ መቅረቱንም ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት የገለጹት።
ይህ ታላቅ ጥረት የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ተማሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት ተቋማት፣ ባለሀብቶች፣ ሃይማኖታዊ ተቋማትና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጭምር በመሳተፍ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንዲሆን አድርገውታል።
በመሆኑም በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል ዘመቻ ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ ለአየር ንብረት መቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ በማጉላት ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ወጣቶች፣ አባቶች፣ እናቶችና ህፃናት እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ መስክ በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መግለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም፣ አረንጓዴና የተባረከች ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ እና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት የደን ሀብቷን ለማሳደግ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖዎችን የመቋቋም ጉዞ ዛሬ ላይ የሀገሪቱን ገጽታ ከመቀየር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚጠቀስ አርአያነት ያለው ተግባር ሆኗል።
ይህ በየዓመቱ በከፍተኛ ህዝባዊ ንቅናቄ የሚታወቀው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ የወደፊት ትውልድ ተስፋን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያንጽ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሚሊየኖች ከዳር እስከ ዳር በዝናብና በብርድ ሳይበገሩ በመዝመት ምድርን የሚያለመልሙበት ህያው መድረክ ሆኗል።
በዚህ ዓመትም በይፋ በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በመላው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተከናወነ ሲሆን፤ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላን ለማከናወንም ዝግጅት ተደርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ባስተላለፉት ጥሪ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም ታሪክ ለመጻፍ አስፈላጊው ዝግጅት ሁሉ እንዲደረግ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ክንድና ህብረት በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን ተክሎ ሌላ ተአምር ለማስመዝገብ የቀሩት አምስት ቀናት ብቻ መቅረቱንም ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት የገለጹት።
ይህ ታላቅ ጥረት የደን ሽፋንን በእጥፍ ከማሳደግ ባሻገር፣ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የውሃ አካላትን ለማበልጸግና የግብርና ምርታማነትን በዘላቂነት ለማሳደግ የጎላ ሚና ይጫወታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፣ የሚተከሉት ችግኞች የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ የፍራፍሬ ተክሎች እንዲሁም የኢኮኖሚ ጥቅም የሚሰጡ የዛፍ ዝርያዎችን ያካተቱ በመሆናቸው ለሀገራችን የኢኮኖሚ እድገት አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።
ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የችግኝ ተከላ ዘመቻዎች ተማሪዎች፣ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት ተቋማት፣ ባለሀብቶች፣ ሃይማኖታዊ ተቋማትና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጭምር በመሳተፍ መርሐ ግብሩ ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የሀገራዊ አንድነት መገለጫ እንዲሆን አድርገውታል።
በመሆኑም በቀጣዮቹ ቀናት የሚካሄደው 800 ሚሊየን ችግኞችን በአንድ ጀምበር የመትከል ዘመቻ ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ልማት፣ ለአየር ንብረት መቋቋም፣ ለምግብ ዋስትናና ለትውልድ ተሻጋሪ የተፈጥሮ ሀብት ግንባታ የሚያበረክተውን ድርሻ የበለጠ በማጉላት ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረክታል።
እያንዳንዱ ዜጋ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት የድርሻውን እንዲወጣ የሚጠይቀው ይህ ሀገራዊ ጥሪ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖሩ ወጣቶች፣ አባቶች፣ እናቶችና ህፃናት እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ መስክ በመውጣት የራሳቸውን ታሪካዊ ዐሻራ እንዲያኖሩ በር የከፈተ ሆኗል።
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል እቅድ የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጽናት፣ የህብረትና የልማት ታላቅ መግለጫ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በተፈጥሮ ሃብታቸው ላይ አዲስ ሕይወት የሚዘሩበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ለም፣ አረንጓዴና የተባረከች ሀገር የሚያስረክቡበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ እና የመጠበቅ ባሕልን ማሳደግ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ዋነኛ ምሰሶ በመሆኑ እያንዳንዱ የተተከለ ችግኝ ጸድቆ ለፍሬ እንዲበቃ ሁሉም አካላት የተቀናጀ ጥረትና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በዮናስ ጌትነት
9 days ago
ሀገራዊ ምክክሩ ለዘላቂ ሰላምና አንድነት መሠረት እየጣለ ነው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ባሕላዊ የውይይትና የእርቅ እሴቶች በማጎልበት ሀገራዊ መግባባትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው አሉ የምክክሩ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌዎች።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌ ታደሰ አሸሙ እንዳሉት÷ በመመካከር፣ በመነጋገር እና በመወያየት የማይፈታ ችግር የለም፤ይህም የኢትዮጵያን ባሕላዊ የእርቅ ሥርዓት በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በቀደሙት ዘመናት ኢትዮጵያውያን ልዩነቶችን በዋርካ ስር በመወያየትና በመመካከር የሚፈቱበት ባሕል እንደነበራቸው ጠቁመው፤ ይህንን በማስፋት የተጀመረው የምክክር ሂደት ለሰላም፣ ለአንድነትና ለማህበራዊ ትስስር ትልቅ ጠቃሚ አለው ብለዋል፡፡
ለረጅም ዓመታት ያልተፈቱ ጥያቄዎችን ሁሉንም ወገኖች በማሳተፍ መፍትሔ መፈለግ የምክክሩ ዋና ጥንካሬ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ወጣቶች ጥያቄያቸውን በሕጋዊ እና በሰለጠነ መንገድ እንዲያቀርቡ ማስቻሉ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
ሌላኛው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌ ውማ ጌታቸው በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ የተጣሉ ወገኖችን በእርቅ የማቀራረብ ጠንካራ ባሕል ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል፡፡
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱም ይህንን እሴት በማጠናከር ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና አንድነት አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል።
ምክክሩ ሀገሪቱ በጋራ ራዕይና በጋራ አቅጣጫ እንድትጓዝ የሚያግዝ መድረክ ከመሆኑም በላይ በዜጎች መካከል ያለውን መተማመን ለማጠናከር የሚያስችል ሂደት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ባሕላዊ የግጭት አፈታት እሴቶችን ከዘመናዊ የምክክር ሥርዓቶች ጋር በማጣመር እየተካሄደ ያለው ሂደት ለሀገሪቱ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ያነሱት ደግሞ ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ በለጠ ባሹ ናቸው።
ምክክሩ የኢትዮጵያን ታሪካዊ አንድነት፣ ወንድማማችነት እና መተሳሰብ በድጋሚ ለማጠናከር እንዲሁም የልዩነት ጉዳዮችን በውይይት የመፍታት ባሕል እንዲጎለብት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ በምክክር፣ በመግባባትና በባሕላዊ የእርቅ እሴቶች ላይ የተመሰረተ ሀገራዊ ተሳትፎን በማጠናከር ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ ሰላምና የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት ሁሉም አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው የኢትዮጵያን ባሕላዊ የውይይትና የእርቅ እሴቶች በማጎልበት ሀገራዊ መግባባትን ለማጠናከር ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው አሉ የምክክሩ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌዎች።
የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌ ታደሰ አሸሙ እንዳሉት÷ በመመካከር፣ በመነጋገር እና በመወያየት የማይፈታ ችግር የለም፤ይህም የኢትዮጵያን ባሕላዊ የእርቅ ሥርዓት በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በቀደሙት ዘመናት ኢትዮጵያውያን ልዩነቶችን በዋርካ ስር በመወያየትና በመመካከር የሚፈቱበት ባሕል እንደነበራቸው ጠቁመው፤ ይህንን በማስፋት የተጀመረው የምክክር ሂደት ለሰላም፣ ለአንድነትና ለማህበራዊ ትስስር ትልቅ ጠቃሚ አለው ብለዋል፡፡
ለረጅም ዓመታት ያልተፈቱ ጥያቄዎችን ሁሉንም ወገኖች በማሳተፍ መፍትሔ መፈለግ የምክክሩ ዋና ጥንካሬ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ወጣቶች ጥያቄያቸውን በሕጋዊ እና በሰለጠነ መንገድ እንዲያቀርቡ ማስቻሉ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
ሌላኛው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊ የሀገር ሽማግሌ ውማ ጌታቸው በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ የተጣሉ ወገኖችን በእርቅ የማቀራረብ ጠንካራ ባሕል ያላት ሀገር መሆኗን ገልጸዋል፡፡
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱም ይህንን እሴት በማጠናከር ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና አንድነት አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል።
ምክክሩ ሀገሪቱ በጋራ ራዕይና በጋራ አቅጣጫ እንድትጓዝ የሚያግዝ መድረክ ከመሆኑም በላይ በዜጎች መካከል ያለውን መተማመን ለማጠናከር የሚያስችል ሂደት መሆኑን ጠቁመዋል።
በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ ባሕላዊ የግጭት አፈታት እሴቶችን ከዘመናዊ የምክክር ሥርዓቶች ጋር በማጣመር እየተካሄደ ያለው ሂደት ለሀገሪቱ ትልቅ ለውጥ እንደሚያመጣ ያነሱት ደግሞ ሌላኛው የሀገር ሽማግሌ በለጠ ባሹ ናቸው።
ምክክሩ የኢትዮጵያን ታሪካዊ አንድነት፣ ወንድማማችነት እና መተሳሰብ በድጋሚ ለማጠናከር እንዲሁም የልዩነት ጉዳዮችን በውይይት የመፍታት ባሕል እንዲጎለብት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።
የሀገር ሽማግሌዎቹ በምክክር፣ በመግባባትና በባሕላዊ የእርቅ እሴቶች ላይ የተመሰረተ ሀገራዊ ተሳትፎን በማጠናከር ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ ሰላምና የተረጋጋች ሀገር ለመገንባት ሁሉም አካላት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።
በዮናስ ጌትነት
16 days ago
በመደመር መንግሥት ራዕይ የኢትዮጵያ ከተሞች እመርታ
የሀገራት ኢኮኖሚ፣ የሥልጣኔ ደረጃ እና የወደፊት ተስፋ የሚገለጥባቸው ዋና ማዕከላት የሆኑት ከተሞች በዘመናችን የሚታየው ፈጣን የከተሜነት እድገት ከተሞችን ከመኖሪያ ስፍራነት በላይ የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት፣ የፈጠራ እና የማኅበራዊ ለውጥ ሞተር አድርጓቸዋል።
ኢትዮጵያም በዚህ ዓለም አቀፍ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለማረጋገጥ በመደመር ፍልስፍና የተመራ የከተማ ልማት አቅጣጫን በመከተል የተለያዩ ዘርፎችን ያካተተ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች።
በዚህም ባለፉት ስምንት ዓመታት የከተሞች ልማት የሕንፃ ግንባታና የመንገድ ዝርጋታ ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ እድገት፣ የመዋቅራዊ ሽግግር፣ የማኅበራዊ አካታችነት እና የዜጎች የኑሮ ጥራት ማሻሻያ የተዋሃደበት አቅጣጫ ሆኗል።
በዚህ መነሻም ከተሞች ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለቱሪዝም ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት አስተማማኝ እና ተወዳዳሪ የንግድ ማዕከላት እንዲሆኑ የሚያግዙ ፖሊሲዎችና ሪፎርሞች ተተግብረዋል።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች የከተሞችን ገጽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከለወጡ ታላላቅ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን በአዲስ አበባ የተጀመረው ፕሮጀክት ከ50 በላይ በሚሆኑ የሀገሪቱ ከተሞች መስፋፋት ችሏል።
የተሻለ የትራንስፖርት አውታረ መረብ፣ የእግረኛ መንገዶች፣ አረንጓዴ ስፍራዎች እና ለባህልና ለመዝናኛ የተመቹ የሕዝብ አደባባዮችን የፈጠረው ይህ ለውጥ የከተሞችን ውበት ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎችን ጤና እና የሕይወት ጥራትን ለማሻሻልም አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የከተማ ልማቱ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ዕድሎችንም በማስፋት ረገድ ጉልህ ሚና የተጫወተ ሲሆን፤ የተሻሻሉ መሠረተ ልማቶች አዲስ አበባን የኮንፈረንስና የቱሪዝም መዳረሻ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ገቢን ከማሳደግ ባሻገር ለወጣቶችና ለሴቶች አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ፈጥረዋል።
የከተማ ልማትን በሰው ተኮር እይታ የሚመለከተው የመደመር ፍልስፍና በዚህ መሠረት የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና ሥራ ፕሮግራም ከ11 ከተሞች ተነስቶ ወደ 88 ከተሞች በመስፋፋት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ አድርጓል።
ፕሮግራሙ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በከተሞች የሚከናወኑ የጽዳት፣ የአረንጓዴ ልማትና የተፋሰስ ሥራዎችን በመደገፍ ማኅበራዊ ተጠቃሚነቱን አሳይቷል።
የመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ ከተሞች የታየው ለውጥ የግንባታ ሥራዎች ውጤት ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን፣ ማኅበራዊ አካታችነትን፣ አካባቢያዊ ዘላቂነትን እና የዜጎችን ኑሮ ጥራት በአንድነት የሚያሳድግ መዋቅራዊ ሽግግር ነው።
ይህ ጉዞ በሁሉም የሀገሪቱ ከተሞች በስፋት ተጠናክሮ ሲቀጥል፣ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ፣ ለዜጎቿ ምቹ እና ለቀጣይ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የጣለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ዓምድ ሆኖ ይቀጥላል።
በዮናስ ጌትነት
የሀገራት ኢኮኖሚ፣ የሥልጣኔ ደረጃ እና የወደፊት ተስፋ የሚገለጥባቸው ዋና ማዕከላት የሆኑት ከተሞች በዘመናችን የሚታየው ፈጣን የከተሜነት እድገት ከተሞችን ከመኖሪያ ስፍራነት በላይ የኢኮኖሚ፣ የኢንቨስትመንት፣ የፈጠራ እና የማኅበራዊ ለውጥ ሞተር አድርጓቸዋል።
ኢትዮጵያም በዚህ ዓለም አቀፍ እድገት ውስጥ የራሷን ድርሻ ለማረጋገጥ በመደመር ፍልስፍና የተመራ የከተማ ልማት አቅጣጫን በመከተል የተለያዩ ዘርፎችን ያካተተ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች።
በዚህም ባለፉት ስምንት ዓመታት የከተሞች ልማት የሕንፃ ግንባታና የመንገድ ዝርጋታ ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ እድገት፣ የመዋቅራዊ ሽግግር፣ የማኅበራዊ አካታችነት እና የዜጎች የኑሮ ጥራት ማሻሻያ የተዋሃደበት አቅጣጫ ሆኗል።
በዚህ መነሻም ከተሞች ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለቱሪዝም ሳቢ፣ ለኢንቨስትመንት አስተማማኝ እና ተወዳዳሪ የንግድ ማዕከላት እንዲሆኑ የሚያግዙ ፖሊሲዎችና ሪፎርሞች ተተግብረዋል።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች የከተሞችን ገጽታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከለወጡ ታላላቅ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን በአዲስ አበባ የተጀመረው ፕሮጀክት ከ50 በላይ በሚሆኑ የሀገሪቱ ከተሞች መስፋፋት ችሏል።
የተሻለ የትራንስፖርት አውታረ መረብ፣ የእግረኛ መንገዶች፣ አረንጓዴ ስፍራዎች እና ለባህልና ለመዝናኛ የተመቹ የሕዝብ አደባባዮችን የፈጠረው ይህ ለውጥ የከተሞችን ውበት ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎችን ጤና እና የሕይወት ጥራትን ለማሻሻልም አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የከተማ ልማቱ የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ዕድሎችንም በማስፋት ረገድ ጉልህ ሚና የተጫወተ ሲሆን፤ የተሻሻሉ መሠረተ ልማቶች አዲስ አበባን የኮንፈረንስና የቱሪዝም መዳረሻ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ገቢን ከማሳደግ ባሻገር ለወጣቶችና ለሴቶች አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ፈጥረዋል።
የከተማ ልማትን በሰው ተኮር እይታ የሚመለከተው የመደመር ፍልስፍና በዚህ መሠረት የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና ሥራ ፕሮግራም ከ11 ከተሞች ተነስቶ ወደ 88 ከተሞች በመስፋፋት ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ አድርጓል።
ፕሮግራሙ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በከተሞች የሚከናወኑ የጽዳት፣ የአረንጓዴ ልማትና የተፋሰስ ሥራዎችን በመደገፍ ማኅበራዊ ተጠቃሚነቱን አሳይቷል።
የመደመር እሳቤ በኢትዮጵያ ከተሞች የታየው ለውጥ የግንባታ ሥራዎች ውጤት ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናን፣ ማኅበራዊ አካታችነትን፣ አካባቢያዊ ዘላቂነትን እና የዜጎችን ኑሮ ጥራት በአንድነት የሚያሳድግ መዋቅራዊ ሽግግር ነው።
ይህ ጉዞ በሁሉም የሀገሪቱ ከተሞች በስፋት ተጠናክሮ ሲቀጥል፣ ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ፣ ለዜጎቿ ምቹ እና ለቀጣይ ትውልድ ጠንካራ መሠረት የጣለች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ዓምድ ሆኖ ይቀጥላል።
በዮናስ ጌትነት
16 days ago
የ4 ሺህ ድምፆች ውክልና፡- ሀገራዊ ምክክሩ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል ሲያድስ
*********************
የጥይት ቋንቋን በሰለጠነ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት የጦር ሜዳ ጀግንነትን ደግሞ በሐሳብ ልዕልና ለመተካት የሚያስችለው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 4 ሺህ ተመካካሪዎች ያካተተውን ሰፊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት ሀገራችን ከጦርነት አዙሪት ወጥታ ወደ ዘላቂ ሰላምና የሀገር ግንባታ የምትሸጋገርበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በማኅበረሰቡ ዘንድ እንደ ገዳ እና የሽምግልና ሥርዓቶች ያሉ የዳበረ የውይይትና የችግር አፈታት ባህል ቢኖርም፣ የፖለቲካው ማኅበረሰብ ግን ከዚህ እሴት ባለመቅዳቱ "አሸናፊ ወደ ቤተመንግሥት፣ ተሸናፊ ወደ ግዞት" የሚል አጥፊ የፖለቲካ ባህል ስር ሰዶ ቆይቷል።
ይሁንና አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ይህንን የተዛባ የፖለቲካ ትርክት በማረም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ሂደት ነው።
በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ትንታኔያቸውን የሰጡት የማኅበራዊ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት ተሾመ ኢትዮጵያ ጠንካራ የመንግሥት ምስረታ ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም፣ በውስጣዊ ክፍፍሎች እና የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካ ፍላጎት ምክንያት በሚፈለገው ልክ ማደግ አለመቻሏን ይገልጻሉ።
ይሁንና በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በከተማ ልማት እና በዲፕሎማሲ እያስመዘገበች ያለችውን አበረታች ዕድገት ለማስቀጠል፣ ሀገራዊ ምክክሩ ወቅታዊ እና ወሳኝ መድኃኒት መሆኑን አስምረውበታል።
በየትኛውም የዓለም ክፍል ጦርነት ትርፍ አምጥቶ እንደማያውቅና ይልቁንም አምራች ኃይልን እና ሀገራዊ ኢኮኖሚን እንደሚያወድም ያነሱት ምሁሩ፣ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የሚዲያ አካላት እና የሃይማኖት አባቶች አጀንዳዎቻቸውን ኦዲት በማድረግ ለትውልድ የሚሻገር ሀገር ለመገንባት በጋራ ሊቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡
በየትኛውም ስሌት የምክክር መድረኩን መጀመር በራሱ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላም እና ልማት ለሚሹ ኃይሎች ታላቅ ድል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁማ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆን ያለበት ዘላቂ የሀገር ግንባታ ነው።
ሀገረ-መንግሥት የመመስረቱ ሂደት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅም በእኩልነትና በመተባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ አንድነትን ለመፍጠር መመካከር የግድ ይላል።
ባለፈው ታሪክ ውስጥ የተፈጠሩ ቁርሾዎችንና ህመሞችን በዛሬው ዘመን የሰብአዊ መብት መነጽር ከመመዘን ይልቅ፣ ያለፈውን እንደ መማሪያ በመውሰድ ለጋራ የወደፊት ራዕይ በጋራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡
በዚህ ዘመን እውነተኛ ጀግንነት የሚለካው በጦር ሜዳ ሳይሆን፣ በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ የሰለጠነ ድርድር መሆኑንም ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስና የኅብረተሰቡን አንገብጋቢ አጀንዳዎች በማሰባሰብ የሁሉንም ድምፅ ያካተተ ዴሞክራሲያዊ ሂደት እያስኬደ ይገኛል።
መላው ማኅበረሰብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየተሳተፈበት የሚገኘው ይህ መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ሁለት ዓመት ከመዋጋት፣ 20 ዓመት መወያየት ይሻላል" በማለት ያስቀመጡትን መርህ በተግባር የሚተረጉም ነው።
በመሆኑም፣ ይህ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በአንድ አዳራሽ የተሰባሰቡበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ፣ ዜጎች ልዩነቶቻቸውን በሰለጠነ መንገድ በማንሸራሸር ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ መሰረት የሚጥሉበት ወርቃማ እድል ነው፡፡
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #nationbuilding #ebcdotstream
*********************
የጥይት ቋንቋን በሰለጠነ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት የጦር ሜዳ ጀግንነትን ደግሞ በሐሳብ ልዕልና ለመተካት የሚያስችለው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ በኢትዮጵያ ተከፍቷል።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 4 ሺህ ተመካካሪዎች ያካተተውን ሰፊ የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ ይህ ታሪካዊ ክስተት ሀገራችን ከጦርነት አዙሪት ወጥታ ወደ ዘላቂ ሰላምና የሀገር ግንባታ የምትሸጋገርበት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ በማኅበረሰቡ ዘንድ እንደ ገዳ እና የሽምግልና ሥርዓቶች ያሉ የዳበረ የውይይትና የችግር አፈታት ባህል ቢኖርም፣ የፖለቲካው ማኅበረሰብ ግን ከዚህ እሴት ባለመቅዳቱ "አሸናፊ ወደ ቤተመንግሥት፣ ተሸናፊ ወደ ግዞት" የሚል አጥፊ የፖለቲካ ባህል ስር ሰዶ ቆይቷል።
ይሁንና አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ይህንን የተዛባ የፖለቲካ ትርክት በማረም ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ ተስፋ የተጣለበት ሂደት ነው።
በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ትንታኔያቸውን የሰጡት የማኅበራዊ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪው ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት ተሾመ ኢትዮጵያ ጠንካራ የመንግሥት ምስረታ ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም፣ በውስጣዊ ክፍፍሎች እና የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካ ፍላጎት ምክንያት በሚፈለገው ልክ ማደግ አለመቻሏን ይገልጻሉ።
ይሁንና በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በከተማ ልማት እና በዲፕሎማሲ እያስመዘገበች ያለችውን አበረታች ዕድገት ለማስቀጠል፣ ሀገራዊ ምክክሩ ወቅታዊ እና ወሳኝ መድኃኒት መሆኑን አስምረውበታል።
በየትኛውም የዓለም ክፍል ጦርነት ትርፍ አምጥቶ እንደማያውቅና ይልቁንም አምራች ኃይልን እና ሀገራዊ ኢኮኖሚን እንደሚያወድም ያነሱት ምሁሩ፣ የፖለቲካ ልሂቃን፣ የሚዲያ አካላት እና የሃይማኖት አባቶች አጀንዳዎቻቸውን ኦዲት በማድረግ ለትውልድ የሚሻገር ሀገር ለመገንባት በጋራ ሊቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡
በየትኛውም ስሌት የምክክር መድረኩን መጀመር በራሱ ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሰላም እና ልማት ለሚሹ ኃይሎች ታላቅ ድል ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁማ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራዊ ስኬቶችን ማስመዝገብ የቻለች ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ መሆን ያለበት ዘላቂ የሀገር ግንባታ ነው።
ሀገረ-መንግሥት የመመስረቱ ሂደት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅም በእኩልነትና በመተባበር ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ አንድነትን ለመፍጠር መመካከር የግድ ይላል።
ባለፈው ታሪክ ውስጥ የተፈጠሩ ቁርሾዎችንና ህመሞችን በዛሬው ዘመን የሰብአዊ መብት መነጽር ከመመዘን ይልቅ፣ ያለፈውን እንደ መማሪያ በመውሰድ ለጋራ የወደፊት ራዕይ በጋራ መሥራት ያስፈልጋል፡፡
በዚህ ዘመን እውነተኛ ጀግንነት የሚለካው በጦር ሜዳ ሳይሆን፣ በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ የሰለጠነ ድርድር መሆኑንም ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
ባለፉት አራት ዓመታት ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፣ ከ1 ሺህ 200 በላይ ወረዳዎችን በማዳረስና የኅብረተሰቡን አንገብጋቢ አጀንዳዎች በማሰባሰብ የሁሉንም ድምፅ ያካተተ ዴሞክራሲያዊ ሂደት እያስኬደ ይገኛል።
መላው ማኅበረሰብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እየተሳተፈበት የሚገኘው ይህ መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ሁለት ዓመት ከመዋጋት፣ 20 ዓመት መወያየት ይሻላል" በማለት ያስቀመጡትን መርህ በተግባር የሚተረጉም ነው።
በመሆኑም፣ ይህ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በአንድ አዳራሽ የተሰባሰቡበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ፣ ዜጎች ልዩነቶቻቸውን በሰለጠነ መንገድ በማንሸራሸር ለነገዋ ኢትዮጵያ ጠንካራ መሰረት የሚጥሉበት ወርቃማ እድል ነው፡፡
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogue #nationbuilding #ebcdotstream
17 days ago
ኢትዮጵያ ወደ ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት የምታደርገው ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዘመናዊው ዓለም የሀገራት ፉክክር በወታደራዊ ኃይል ወይም በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፡፡
የቴክኖሎጂ አቅም፣ የዲጂታል መሠረተ ልማትና የመረጃ ሉዓላዊነት የሀገራትን የወደፊት እድገት የሚወስኑ ቁልፍ መለኪያዎች ሆነዋል።
ኢትዮጵያም ባለፉት 5 ዓመታት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ያከናወነቻቸው ሥራዎች የዲጂታል ሽግግር መሠረት ጥለዋል፡፡ በ2ኛው ምዕራፍ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ወደ ቀጣዩ የቴክኖሎጂ ዘመን ለማሸጋገር በትኩረት እየሰራች ነው።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ዋና ግብ የመንግሥት አሰራርን ማዘመን፣ የቢሮክራሲ ጫናን መቀነስ፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን ማፋጠንና የዜጎችን የኑሮ ጥራት ማሻሻል ነበር።
በዚህም የቴሌኮም ዘርፉ ለውድድር ተከፍቶ፣ የ4ኛና 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎቶች ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲስፋፉ በማድረግ የኢንተርኔት ተደራሽነትን እንዲጠናከር አድርጓል፡፡ በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ የሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎችንም አስፍቷል።
የዲጂታል ፋይናንስ ሽግግሩም በሀገሪቱ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ሲሆን÷ የሠራተኞች ደመወዝ፣ የነዳጅ ግብይትና የትራፊክ ቅጣት ክፍያዎች በዲጂታል ስርዓት መፈጸማቸው ግብይቶችን ፈጣን፣ ግልጽና ቀልጣፋ አድርጓል።
በተመሳሳይ ሚሊየኖች በፋይዳ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት ተመዝግበው አገልግሎት እያገኙ ሲሆን÷ የፓስፖርት፣ የንግድ ፈቃድና የታክስ አገልግሎቶችን ወደ ኦንላይን ማሸጋገር ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የሙስና እድሎችንም ለመቀነስ አስችሏል።
የቴክኖሎጂ ሽግግሩ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን ብቻ አልተወሰነም፤ የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማሳደግ ለወደፊቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ጠንካራ የሰው ኃይል ለመገንባት አግዟል፡፡ይህም ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ወደ መፍጠርና ማልማት የሚደረግ ስልታዊ ሽግግር መሆኑን ያሳያል።
የዲጂታል ሉዓላዊነቷን ለማጠናከር ከሶፍትዌር ልማት ባለፈ በሃርድዌር ምርት ላይም ትኩረት የሰጠችው ኢትዮጵያ የላፕቶፕ፣ የታብሌትና ሌሎች ዲጂታል መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት የፋብሪካ ግንባታ እያከናወነች ትገኛለች።
ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ሩቅ ይመስል የነበረው የድሮን ቴክኖሎጂ ዛሬ በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉ በቴክኖሎጂ ራስን የመቻል አቅም እየጠነከረ መምጣቱን ያመለክታል።
ዲጂታላይዜሽን ያለ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሊሳካ እንደማይችል በመገንዘብም ኢትዮጵያ የሕግ፣ የተቋምና የቴክኖሎጂ አቅሟን በማጠናከር የዲጂታል ሥነ ምህዳሯን እየገነባች ትገኛለች።
የተሻሻለው ብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ፣ የግል መረጃ ጥበቃና የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ሕጎች ለዲጂታል ኢኮኖሚው አስተማማኝ ሕጋዊ መሠረት ፈጥረዋል።
በተመሳሳይ የመከላከያ ሳይበር ማዕከል የሰለጠኑ የሳይበር ኃይሎችን በማፍራት የአገሪቱን ዲጂታል ሀብቶችና ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ አቅሙን እያጠናከረ ይገኛል።
በዚህ መሠረት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የ2025 ስትራቴጂ ቀጣይ ምዕራፍ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ወደ ቴክኖሎጂ ፈጠራና ወደ ሉዓላዊ የመረጃ ሥርዓት የሚያሸጋግር ብሔራዊ ራዕይ ነው።
ስትራቴጂው የሰው ሰራሽ አስተውሎትን እና ሌሎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በኢኮኖሚ፣ በመንግሥታዊ አገልግሎትና በማኅበራዊ ዘርፎች ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ያለመ ነው።
በመሆኑም ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታል ጉዞ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከማስፋት ባለፈ የራሷን ቴክኖሎጂ የምትፈጥር፣ የምታመርትና የምትጠብቅ ሀገር ለመሆን የተጀመረ ስልታዊ ጉዞ መሆኑን በግልጽ አሳይቷል።
የዲጂታል 2030 ራዕይ ጥንካሬ ያላት፣ በቴክኖሎጂ ራሷን የቻለች እና ለወደፊቱ ፉክክር ዝግጁ የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሠረት ይጥላል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዘመናዊው ዓለም የሀገራት ፉክክር በወታደራዊ ኃይል ወይም በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፡፡
የቴክኖሎጂ አቅም፣ የዲጂታል መሠረተ ልማትና የመረጃ ሉዓላዊነት የሀገራትን የወደፊት እድገት የሚወስኑ ቁልፍ መለኪያዎች ሆነዋል።
ኢትዮጵያም ባለፉት 5 ዓመታት በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ያከናወነቻቸው ሥራዎች የዲጂታል ሽግግር መሠረት ጥለዋል፡፡ በ2ኛው ምዕራፍ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ወደ ቀጣዩ የቴክኖሎጂ ዘመን ለማሸጋገር በትኩረት እየሰራች ነው።
የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ዋና ግብ የመንግሥት አሰራርን ማዘመን፣ የቢሮክራሲ ጫናን መቀነስ፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን ማፋጠንና የዜጎችን የኑሮ ጥራት ማሻሻል ነበር።
በዚህም የቴሌኮም ዘርፉ ለውድድር ተከፍቶ፣ የ4ኛና 5ኛ ትውልድ ኔትወርክ አገልግሎቶች ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲስፋፉ በማድረግ የኢንተርኔት ተደራሽነትን እንዲጠናከር አድርጓል፡፡ በዲጂታል ኢኮኖሚ ውስጥ የሚፈጠሩ አዳዲስ ዕድሎችንም አስፍቷል።
የዲጂታል ፋይናንስ ሽግግሩም በሀገሪቱ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ሲሆን÷ የሠራተኞች ደመወዝ፣ የነዳጅ ግብይትና የትራፊክ ቅጣት ክፍያዎች በዲጂታል ስርዓት መፈጸማቸው ግብይቶችን ፈጣን፣ ግልጽና ቀልጣፋ አድርጓል።
በተመሳሳይ ሚሊየኖች በፋይዳ ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት ተመዝግበው አገልግሎት እያገኙ ሲሆን÷ የፓስፖርት፣ የንግድ ፈቃድና የታክስ አገልግሎቶችን ወደ ኦንላይን ማሸጋገር ጊዜን ከመቆጠብ ባሻገር የሙስና እድሎችንም ለመቀነስ አስችሏል።
የቴክኖሎጂ ሽግግሩ በአገልግሎት ዲጂታላይዜሽን ብቻ አልተወሰነም፤ የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ የወጣቶችን የቴክኖሎጂ ክህሎት በማሳደግ ለወደፊቱ የዲጂታል ኢኮኖሚ ጠንካራ የሰው ኃይል ለመገንባት አግዟል፡፡ይህም ቴክኖሎጂን ከመጠቀም ወደ መፍጠርና ማልማት የሚደረግ ስልታዊ ሽግግር መሆኑን ያሳያል።
የዲጂታል ሉዓላዊነቷን ለማጠናከር ከሶፍትዌር ልማት ባለፈ በሃርድዌር ምርት ላይም ትኩረት የሰጠችው ኢትዮጵያ የላፕቶፕ፣ የታብሌትና ሌሎች ዲጂታል መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ለማምረት የፋብሪካ ግንባታ እያከናወነች ትገኛለች።
ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ሩቅ ይመስል የነበረው የድሮን ቴክኖሎጂ ዛሬ በሀገር ውስጥ ማምረት መቻሉ በቴክኖሎጂ ራስን የመቻል አቅም እየጠነከረ መምጣቱን ያመለክታል።
ዲጂታላይዜሽን ያለ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሊሳካ እንደማይችል በመገንዘብም ኢትዮጵያ የሕግ፣ የተቋምና የቴክኖሎጂ አቅሟን በማጠናከር የዲጂታል ሥነ ምህዳሯን እየገነባች ትገኛለች።
የተሻሻለው ብሔራዊ የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ፣ የግል መረጃ ጥበቃና የኤሌክትሮኒክስ ግብይት ሕጎች ለዲጂታል ኢኮኖሚው አስተማማኝ ሕጋዊ መሠረት ፈጥረዋል።
በተመሳሳይ የመከላከያ ሳይበር ማዕከል የሰለጠኑ የሳይበር ኃይሎችን በማፍራት የአገሪቱን ዲጂታል ሀብቶችና ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ አቅሙን እያጠናከረ ይገኛል።
በዚህ መሠረት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የ2025 ስትራቴጂ ቀጣይ ምዕራፍ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ፣ ወደ ቴክኖሎጂ ፈጠራና ወደ ሉዓላዊ የመረጃ ሥርዓት የሚያሸጋግር ብሔራዊ ራዕይ ነው።
ስትራቴጂው የሰው ሰራሽ አስተውሎትን እና ሌሎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በኢኮኖሚ፣ በመንግሥታዊ አገልግሎትና በማኅበራዊ ዘርፎች ሥር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ያለመ ነው።
በመሆኑም ኢትዮጵያ የጀመረችው የዲጂታል ጉዞ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ከማስፋት ባለፈ የራሷን ቴክኖሎጂ የምትፈጥር፣ የምታመርትና የምትጠብቅ ሀገር ለመሆን የተጀመረ ስልታዊ ጉዞ መሆኑን በግልጽ አሳይቷል።
የዲጂታል 2030 ራዕይ ጥንካሬ ያላት፣ በቴክኖሎጂ ራሷን የቻለች እና ለወደፊቱ ፉክክር ዝግጁ የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሠረት ይጥላል።
በዮናስ ጌትነት
Sponsored by
Surafel
19 days ago
በትግራይ ሕዝብ ላይ የተጫነ የጥፋት ቡድን
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተደመደመ በኋላ በስምምነቱ መሠረት በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ታይቶ ነበር።
በዚህም የትግራይ ሕዝብ የሰላም አየር እንዲተነፍስና ስለ መልሶ ግንባታና ልማት እንዲያስብ የሚያስችል ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ተከፍቶ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ የመጣው የሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን የጥፋት አባዜ ለሰላምና ለመግባባት በቁርጠኝነት ሲሠሩ የነበሩትን የጊዜያዊ አስተዳደሩን መሪዎች ከአመራርነት በማንሸራተት በክልሉ ላይ አዲስ የውጥረት ነፋስ እንዲነፍስ እያደረገ ይገኛል።
የፌደራል መንግሥት ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት፣ በማቋቋምና ወደ ማኅበረሰቡ በመመለስ የበኩሉን ታሪካዊ ኃላፊነት በስኬት ቢወጣም ህገ ወጡ ቡድን ግን አሁንም በሐሰት አሉባልታዎች ለክልሉ ህልውና ፈታኝ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ እንዳሉት፤ የትግራይ ሕዝብ የጥፋት መረብ በዘረጉ የስልጣን ጥመኛ ጥቂት ወንጀለኞች ታጋች ሆኗል።
ይህ ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ ሲሆን፤ ዛሬም የክልሉን የልማት ተጠቃሚነት መና እያደረገው ይገኛል።
የትግራይ ሕዝብ አሁን ላይ “ያለፈው ይበቃናል” በማለት ለግጭት እምቢተኝነቱን በግልጽ እያሳየ ቢሆንም ሕገወጡ ቡድን ግን ዕድሜያቸው ያልደረሱ አዳጊ ወጣቶች ላይ ጭምር አፈሳና እገታ እየፈጸመ ሲሆን ይህ ተግባር የትግራይ ወጣት ቀዬውን ጥሎ እንዲሰደድ እያስገደደው ሲሆን ድርጊቱም በትግራይ እናቶች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና ቁጣን እያስነሳ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በነበራቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍነው ለሱዳን ኃይሎች እስከመሸጥ መድረሳቸውንና ምንም ለማያውቁት ጦርነት ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሁሉ በላይ አሳሳቢውና አደገኛው ጉዳይ፣ ይህ የጥፋት ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማይሹ ታሪካዊ ጠላቶችን አጀንዳ አንግቦ፣ የሀገሪቱን የውስጥ ጥንካሬ ለማዳከም ሌት ተቀን ከሚሠራው የሻዕቢያ ሥርዓት ጋር ያደረገው ድብቅ ግንኙነት ነው።
በተለይም ኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገቷን ለማረጋገጥ ያነሳችውን የባሕር በር ጥያቄ ለማኮላሸት ከሚሠራው ሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ይህ ግንኙነት ዳግም “የትሮይ ፈረስን” ወደ ክልሉ የማስገባት ያህል የከፋ አደጋ አለው።
ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በትግራይ ሰላም መውረዱ እረፍት የነሳው ሻዕቢያ “ትግራይ ጨርሳ ካልጠፋች” በሚል እሳቤ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን የሻዕቢያ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ያሉ አኩራፊ ኃይሎችን በማደራጀት በሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም እንዳይኖር ማድረግ መሆኑን አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ትንታኔ አብራርተው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት በምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ “የሻዕቢያ ሥርዓት ዳግም ሕዝባችንን እንዲበድል ዕድል አንሰጠውም፤ ከሞከረ የመጨረሻው ሙከራው ይሆናል” ሲሉ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።
ሻዕቢያ በኢትዮጵያ የውስጥ ኃይሎች ላይ መረብ በመዘርጋት ሉዓላዊነታችንን ለመፈታተን መሞከሩ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንም ፈለገም አልፈለገም ትልቅ ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ተዘግታ እንደማትኖርና በሰላማዊና በሰከነ ውይይት የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረው ነበር።
አሁንም የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል ምንም ዓይነት የጦርነት ዓላማ እንደሌለው ያረጋገጠ ሲሆን ይልቁንም ለሰላማዊ ውይይት እና ምክክር ጥሪ እያቀረበ ይገኛል።
ሀገራዊ ውይይትን የሽግግር ፍትሕንና ይቅርታን የመረጠው የመደመር መንግሥት ለሰላም ያለው በር ምንጊዜም ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል።
ሆኖም የሀገርን ሉዓላዊነት የሚፈታተን ማናቸውም ዓይነት የውጭ ትንኮሳና የውስጥ ተላላኪዎች የጥፋት እጅ ከመጣ መንግሥት ሀገሪቱን ለማስጠበቅ ከየትኛውም ጊዜ በላይ የተሟላ ዝግጁነት አለ።
የትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚያገኘው ከጥፋት አጋሮች ጋር በመሻረክ ሳይሆን የሰላምን አማራጭ በመቀበል ለልማትና ለትውልድ ግንባታ ሲሰለፍ ብቻ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ከተደመደመ በኋላ በስምምነቱ መሠረት በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ከተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል ከፍተኛ ቁርጠኝነት ታይቶ ነበር።
በዚህም የትግራይ ሕዝብ የሰላም አየር እንዲተነፍስና ስለ መልሶ ግንባታና ልማት እንዲያስብ የሚያስችል ተስፋ ሰጪ ምዕራፍ ተከፍቶ እንደነበር ይታወሳል።
ነገር ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ የመጣው የሕገ ወጡ የህወሓት ቡድን የጥፋት አባዜ ለሰላምና ለመግባባት በቁርጠኝነት ሲሠሩ የነበሩትን የጊዜያዊ አስተዳደሩን መሪዎች ከአመራርነት በማንሸራተት በክልሉ ላይ አዲስ የውጥረት ነፋስ እንዲነፍስ እያደረገ ይገኛል።
የፌደራል መንግሥት ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን ትጥቅ በማስፈታት፣ በማቋቋምና ወደ ማኅበረሰቡ በመመለስ የበኩሉን ታሪካዊ ኃላፊነት በስኬት ቢወጣም ህገ ወጡ ቡድን ግን አሁንም በሐሰት አሉባልታዎች ለክልሉ ህልውና ፈታኝ እንቅፋት እየሆነ ይገኛል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዚዳንት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ እንዳሉት፤ የትግራይ ሕዝብ የጥፋት መረብ በዘረጉ የስልጣን ጥመኛ ጥቂት ወንጀለኞች ታጋች ሆኗል።
ይህ ቡድን ሥልጣን ላይ በቆየበት ወቅት ሀገር ከማልማት ይልቅ የግል ጥቅምን ያስቀደመ ሲሆን፤ ዛሬም የክልሉን የልማት ተጠቃሚነት መና እያደረገው ይገኛል።
የትግራይ ሕዝብ አሁን ላይ “ያለፈው ይበቃናል” በማለት ለግጭት እምቢተኝነቱን በግልጽ እያሳየ ቢሆንም ሕገወጡ ቡድን ግን ዕድሜያቸው ያልደረሱ አዳጊ ወጣቶች ላይ ጭምር አፈሳና እገታ እየፈጸመ ሲሆን ይህ ተግባር የትግራይ ወጣት ቀዬውን ጥሎ እንዲሰደድ እያስገደደው ሲሆን ድርጊቱም በትግራይ እናቶች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና ቁጣን እያስነሳ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በነበራቸው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሎ የትግራይ ወጣቶች በጉልበት ታፍነው ለሱዳን ኃይሎች እስከመሸጥ መድረሳቸውንና ምንም ለማያውቁት ጦርነት ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሁሉ በላይ አሳሳቢውና አደገኛው ጉዳይ፣ ይህ የጥፋት ቡድን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የማይሹ ታሪካዊ ጠላቶችን አጀንዳ አንግቦ፣ የሀገሪቱን የውስጥ ጥንካሬ ለማዳከም ሌት ተቀን ከሚሠራው የሻዕቢያ ሥርዓት ጋር ያደረገው ድብቅ ግንኙነት ነው።
በተለይም ኢትዮጵያ ዘላቂ ዕድገቷን ለማረጋገጥ ያነሳችውን የባሕር በር ጥያቄ ለማኮላሸት ከሚሠራው ሻዕቢያ ጋር የሚደረግ ይህ ግንኙነት ዳግም “የትሮይ ፈረስን” ወደ ክልሉ የማስገባት ያህል የከፋ አደጋ አለው።
ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላ በትግራይ ሰላም መውረዱ እረፍት የነሳው ሻዕቢያ “ትግራይ ጨርሳ ካልጠፋች” በሚል እሳቤ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን የሻዕቢያ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ያሉ አኩራፊ ኃይሎችን በማደራጀት በሀገሪቱ የተረጋጋ ሰላም እንዳይኖር ማድረግ መሆኑን አቶ ጌታቸው ረዳ በሰጡት ትንታኔ አብራርተው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት በምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ “የሻዕቢያ ሥርዓት ዳግም ሕዝባችንን እንዲበድል ዕድል አንሰጠውም፤ ከሞከረ የመጨረሻው ሙከራው ይሆናል” ሲሉ በጥብቅ አስጠንቅቀዋል።
ሻዕቢያ በኢትዮጵያ የውስጥ ኃይሎች ላይ መረብ በመዘርጋት ሉዓላዊነታችንን ለመፈታተን መሞከሩ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የባሕር በር ማጣቷ ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማንም ፈለገም አልፈለገም ትልቅ ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያ ተዘግታ እንደማትኖርና በሰላማዊና በሰከነ ውይይት የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረው ነበር።
አሁንም የፌደራል መንግሥት በትግራይ ክልል ምንም ዓይነት የጦርነት ዓላማ እንደሌለው ያረጋገጠ ሲሆን ይልቁንም ለሰላማዊ ውይይት እና ምክክር ጥሪ እያቀረበ ይገኛል።
ሀገራዊ ውይይትን የሽግግር ፍትሕንና ይቅርታን የመረጠው የመደመር መንግሥት ለሰላም ያለው በር ምንጊዜም ክፍት መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል።
ሆኖም የሀገርን ሉዓላዊነት የሚፈታተን ማናቸውም ዓይነት የውጭ ትንኮሳና የውስጥ ተላላኪዎች የጥፋት እጅ ከመጣ መንግሥት ሀገሪቱን ለማስጠበቅ ከየትኛውም ጊዜ በላይ የተሟላ ዝግጁነት አለ።
የትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚያገኘው ከጥፋት አጋሮች ጋር በመሻረክ ሳይሆን የሰላምን አማራጭ በመቀበል ለልማትና ለትውልድ ግንባታ ሲሰለፍ ብቻ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
20 days ago
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት 100ኛ ዓመቱን አከበረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
#ethiopia | የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) "የአንድ ክፍለ ዘመን ጥረት ለተሻለ የሕብረተሰብ ጤና" በሚል መሪ ቃል ታሪካዊ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ዛሬ በከፍተኛ ድምቀት አክብሯል።
ይህ መቶ ዓመታትን የተሻገረው ክብረ በዓል ተቋሙ ላለፉት አሥርት ዓመታት የሀገሪቱን የጤና ደህንነት ለመጠበቅ ያደረገውን ዘርፈ ብዙ ጉዞ የዘከረ ሲሆን፣ በቀጣይም የጤና ሥርዓቱን ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር አዲስ ቃል ኪዳን የተገባበት መድረክ ሆኗል።
በበዓሉ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ ጠንካራ የሕብረተሰብ ጤና ተቋማት የሀገር ደህንነትና ልማት መሠረቶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ መንግሥት ተቋሙን ይበልጥ ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም ተቋሙ ከጊዜው ጋር እንዲራመድ የዲጂታል ቴክኖሎጂንና የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀምን ማሳደግ እንደሚገባው አሳስበዋል።
በተመሳሳይ መልኩ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ ተቋሙ ላለፉት 100 ዓመታት በበሽታ ቅኝት፣ በላቦራቶሪ አገልግሎትና በምርምር ዘርፍ ያበረከተውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያወሱ ሲሆን፣ አዳዲስ ወረርሽኞችንና የአየር ንብረት ለውጥ ያመጣቸውን የጤና ተግዳሮቶች ለመመከት ጠንካራ ተቋማዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልጸዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በኢትዮጵያ ተወካይ ፕሮፌሰር ፍራንሲስ ካስሎ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በአፍሪካ እጅግ ጠንካራ ከሆኑ የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ ተቋሙን የዓለም ጤና ድርጅት የትብብር ማዕከል ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን ይፋ አድርገዋል።
የአፍሪካ የበሽታ መከላከያና መቆጣጠሪያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጄን ካሴያም በበኩላቸው የወደፊቱ የሕብረተሰብ ጤና ያለ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የማይታሰብ መሆኑን ጠቁመው፣ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ እያደረገች ያለችው ጥረት ለጤናው ዘርፍ ስኬት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሳይ ኃይሉ ተቋሙ ያለፉትን ስኬቶች መሠረት በማድረግ በቀጣዩ መቶ ዓመታት የሀገሪቱን የሳይንስና የጤና ሉዓላዊነት በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ ቃል ገብተዋል።
በበዓሉ ማጠቃለያ ላይም ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በምርምርና በአመራርነት ያገለገሉ ባለውለታዎች ከፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ እጅ የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthsovereignty #publichealthethiopia
#aiinhealthcare #ethiopia
#ephi #ministryofhealthethiopia
20 days ago
ቀጣሪና ተቀጣሪን ያገናኘ የአንድ ቀን የሥራ አውደ ርዕይ ተካሄደ
#ethiopia | በቅርቡ የመቶኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ያከበረውና የ ISO 21001 ዓለም አቀፍ የጥራት ሰርትፍኬት ባለቤት የሆነው ታሪካዊው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፤ በ2018 ዓ.ም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከሥራ ገበያው ጋር የሚያስተሳስር የሥራ አውደ ርዕይ ተካሄደ
በኮሌጁ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀውና ከአንድ ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ መድረክ፣ በዋናነት ቀጣሪና ተቀጣሪን በአንድ ጣሪያ ስር በማገናኘት ሰልጣኞች ሥራ ፍለጋ የሚንከራተቱበትን እንዲሁም አሠሪዎች ለቅጥር ማስታወቂያ የሚያወጡትን ጊዜና ወጪ ለመቀነስ ያለመ ነው።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ መርሃ ግብሩን ለተቋሙና ለሰልጣኞች "ወሰኝ መርሐግብር " ሲሉ ገልጸውታል። ዲኑ እንዳብራሩት፣ ኮሌጁ ስልጠና የመስጠት ብቻ ሳይሆን ተማሪዎቹን ከኢንዱስትሪ ጋር የማስተሳሰር ኃላፊነት ስላለበት ይህንን ተነሳሽነት ወስዷል።
አውደ ርዕዩ የራሱን 967 ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባ ለሚገኙ 14 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተመራቂዎችና በማኅበራዊ ሚዲያ ጥሪውን ሰምተው ለመጡ የሥራ ፈላጊዎች ሁሉ ክፍት የተደረገ ነበር። ከዚህ ባሻገር፣ ተመራቂዎቹ ለሥራው ዓለም ብቁ እንዲሆኑ ለማድረግ ከ "ሟስ ኮንሰልት" ጋር በመተባበር አስቀድሞ የሲቪ አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ አቀራረብ ክህሎቶች ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።
በዕለቱ የተገኙት የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት የውጤት ተኮር ልማት ዘርፍ በቢሮ ደረጃ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ በበኩላቸው፣ የሰለጠነ የሰው ኃይልን ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር ማገናኘት የመንግሥት ዋነኛ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቅሰው መድረኩ ያለውን የጎላ ፋይዳ አድንቀዋል።
ለዚህ ሁነት መሳካት የ "EASE" ፕሮጀክት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉም ተገልጿል።
በአውደ ርዕዩ ላይ ከ30 በላይ ታዋቂ ሆቴሎች፣ የቅጥር መተግበሪያዎች፣ የጋርመንት ኢንዱስትሪዎች፣ የቁጠባና ብድር ማኅበራትና የመገልገያ ዕቃዎች አምራቾች የተሳተፉ ሲሆን፣ በተለይም በኮሌጁ የሥራ ማበልጸጊያ ማዕከል የታቀፉና የ Generative AI ቴክኖሎጂን በመጠቀም ድር ጣቢያዎችን የሚያለሙ የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶች ሥራ ትልቅ ትኩረትን ስቧል።
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ይህንን ውጤታማ የሥራ ትስስር መድረክ በየዓመቱ ይበልጥ በማሻሻል እንደ ዓመታዊ ቋሚ መርሃ ግብር ለማስቀጠል ማቀዱን አስታውቋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#jobfair #teferimekonnen #addisababa #ethiopiajobs #tvet #careeropportunity #employment #easeproject
#ethiopia | በቅርቡ የመቶኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ያከበረውና የ ISO 21001 ዓለም አቀፍ የጥራት ሰርትፍኬት ባለቤት የሆነው ታሪካዊው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፤ በ2018 ዓ.ም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከሥራ ገበያው ጋር የሚያስተሳስር የሥራ አውደ ርዕይ ተካሄደ
በኮሌጁ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀውና ከአንድ ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ መድረክ፣ በዋናነት ቀጣሪና ተቀጣሪን በአንድ ጣሪያ ስር በማገናኘት ሰልጣኞች ሥራ ፍለጋ የሚንከራተቱበትን እንዲሁም አሠሪዎች ለቅጥር ማስታወቂያ የሚያወጡትን ጊዜና ወጪ ለመቀነስ ያለመ ነው።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ መርሃ ግብሩን ለተቋሙና ለሰልጣኞች "ወሰኝ መርሐግብር " ሲሉ ገልጸውታል። ዲኑ እንዳብራሩት፣ ኮሌጁ ስልጠና የመስጠት ብቻ ሳይሆን ተማሪዎቹን ከኢንዱስትሪ ጋር የማስተሳሰር ኃላፊነት ስላለበት ይህንን ተነሳሽነት ወስዷል።
አውደ ርዕዩ የራሱን 967 ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባ ለሚገኙ 14 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተመራቂዎችና በማኅበራዊ ሚዲያ ጥሪውን ሰምተው ለመጡ የሥራ ፈላጊዎች ሁሉ ክፍት የተደረገ ነበር። ከዚህ ባሻገር፣ ተመራቂዎቹ ለሥራው ዓለም ብቁ እንዲሆኑ ለማድረግ ከ "ሟስ ኮንሰልት" ጋር በመተባበር አስቀድሞ የሲቪ አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ አቀራረብ ክህሎቶች ስልጠና ተሰጥቷቸዋል።
በዕለቱ የተገኙት የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት የውጤት ተኮር ልማት ዘርፍ በቢሮ ደረጃ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ በበኩላቸው፣ የሰለጠነ የሰው ኃይልን ከኢንዱስትሪው ፍላጎት ጋር ማገናኘት የመንግሥት ዋነኛ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቅሰው መድረኩ ያለውን የጎላ ፋይዳ አድንቀዋል።
ለዚህ ሁነት መሳካት የ "EASE" ፕሮጀክት ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉም ተገልጿል።
በአውደ ርዕዩ ላይ ከ30 በላይ ታዋቂ ሆቴሎች፣ የቅጥር መተግበሪያዎች፣ የጋርመንት ኢንዱስትሪዎች፣ የቁጠባና ብድር ማኅበራትና የመገልገያ ዕቃዎች አምራቾች የተሳተፉ ሲሆን፣ በተለይም በኮሌጁ የሥራ ማበልጸጊያ ማዕከል የታቀፉና የ Generative AI ቴክኖሎጂን በመጠቀም ድር ጣቢያዎችን የሚያለሙ የፈጠራ ባለቤት የሆኑ ወጣቶች ሥራ ትልቅ ትኩረትን ስቧል።
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ይህንን ውጤታማ የሥራ ትስስር መድረክ በየዓመቱ ይበልጥ በማሻሻል እንደ ዓመታዊ ቋሚ መርሃ ግብር ለማስቀጠል ማቀዱን አስታውቋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#jobfair #teferimekonnen #addisababa #ethiopiajobs #tvet #careeropportunity #employment #easeproject
20 days ago
አሐዱ ባንክ 4ኛ ዓመቱን በእንጦጦ የችግኝ ተከላ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች እያከበረ ይገኛል
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
21 days ago
“ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ ” ቢሾፍቱ ከተማ ሊገነባ ነው
#ethiopia | ለዓመታት በልብ ህክምና በጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማራው “ኸርት አታክ ኢትዮጵያ”፣ የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን ይበልጥ ዘላቂና ተደራሽ ለማድረግ “ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ” የተሰኘ የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታወቀ።
ቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርፖርት አቅራቢያ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክት፣ ትርፍንና በጎ አድራጎትን ባጣመረ ማህበራዊ የንግድ ስራ መርህ የሚመራ ነው።
የፕሮጀክቱ መጀመር ይፋ የሆነው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ ስምምነት በተፈራረመበት ወቅት ሲሆን፣ በፊርማ ስነ-ስርዓቱም ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ፣ እና የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የድርጅቱ ተባባሪ መስራችና የልብ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ እንደገለጹት፣ ሃርት አታክ ኢትዮጵያ እስካሁን የ660 ታካሚዎችን ህይወት መታደግ ቢችልም፣ ካለው ሰፊ የልብ ህመም ችግር አንጻር የበጎ አድራጎት ስራ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ወደዚህ አዲስ አሠራር መሸጋገር አስፈልጓልብለዋል።
ይህ አዲስ መዋቅር አቅም ያላቸው ታካሚዎች እየከፈሉ እንዲታከሙ፣ አቅም የሌላቸው ደግሞ በነጻ የህክምና እድል እንዲያገኙ በማድረግ ዘላቂነት ያለው ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረገው ስምምነት የኢትዮጵያውያንን የውጭ ሀገር የህክምና ፍሰት ከመቀነስ ባለፈ፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ታካሚዎችን ወደ ሀገሪቱ ለመሳብ የሚያስችል “ፍላይት ቱ ሂል” (Flight to Heal) የተሰኘ ፕሮግራም ለማስጀመር ትልቅ በር ይከፍታል። የልብ ህክምናን ጨምሮ የእናቶችና ህጻናት ጤናን፣ ካንሰርን፣ የነርቭ እና የድንገተኛ አደጋ ህክምናዎችን ያካተቱ ዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረቻን ለማስፋፋትና ባለሙያዎችን በህንድ ሀገር በልዩ ሁኔታ ለማሰልጠን አቅዷል።
በተጨማሪም በህክምና ከተማው ውስጥ የሚመሰረተው የህክምና ትምህርት ቤት ቀጣዩን የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ትውልድ በራሱ አቅም ለማስተማርና ለማብቃት ታላቅ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #intimahealthcity #heartattackethiopia #ethiopianairlines #medicaltourism #healthcareafrica #flighttoheal #africahealthcare
#ethiopia | ለዓመታት በልብ ህክምና በጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማራው “ኸርት አታክ ኢትዮጵያ”፣ የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን ይበልጥ ዘላቂና ተደራሽ ለማድረግ “ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ” የተሰኘ የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታወቀ።
ቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርፖርት አቅራቢያ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክት፣ ትርፍንና በጎ አድራጎትን ባጣመረ ማህበራዊ የንግድ ስራ መርህ የሚመራ ነው።
የፕሮጀክቱ መጀመር ይፋ የሆነው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ ስምምነት በተፈራረመበት ወቅት ሲሆን፣ በፊርማ ስነ-ስርዓቱም ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ፣ እና የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የድርጅቱ ተባባሪ መስራችና የልብ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ እንደገለጹት፣ ሃርት አታክ ኢትዮጵያ እስካሁን የ660 ታካሚዎችን ህይወት መታደግ ቢችልም፣ ካለው ሰፊ የልብ ህመም ችግር አንጻር የበጎ አድራጎት ስራ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ወደዚህ አዲስ አሠራር መሸጋገር አስፈልጓልብለዋል።
ይህ አዲስ መዋቅር አቅም ያላቸው ታካሚዎች እየከፈሉ እንዲታከሙ፣ አቅም የሌላቸው ደግሞ በነጻ የህክምና እድል እንዲያገኙ በማድረግ ዘላቂነት ያለው ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረገው ስምምነት የኢትዮጵያውያንን የውጭ ሀገር የህክምና ፍሰት ከመቀነስ ባለፈ፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ታካሚዎችን ወደ ሀገሪቱ ለመሳብ የሚያስችል “ፍላይት ቱ ሂል” (Flight to Heal) የተሰኘ ፕሮግራም ለማስጀመር ትልቅ በር ይከፍታል። የልብ ህክምናን ጨምሮ የእናቶችና ህጻናት ጤናን፣ ካንሰርን፣ የነርቭ እና የድንገተኛ አደጋ ህክምናዎችን ያካተቱ ዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረቻን ለማስፋፋትና ባለሙያዎችን በህንድ ሀገር በልዩ ሁኔታ ለማሰልጠን አቅዷል።
በተጨማሪም በህክምና ከተማው ውስጥ የሚመሰረተው የህክምና ትምህርት ቤት ቀጣዩን የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ትውልድ በራሱ አቅም ለማስተማርና ለማብቃት ታላቅ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #intimahealthcity #heartattackethiopia #ethiopianairlines #medicaltourism #healthcareafrica #flighttoheal #africahealthcare
Sponsored by
Surafel
23 days ago
የሀገር በቀል ዕውቀት ለሀገራዊ ምክክር ስኬት…
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዙሪያ ሀገራት የፖለቲካ ቀውስ፣ የማኅበራዊ ክፍፍል እና የግጭት ሁኔታዎችን ለመሻገር አንዳንዶቹ በሕግና በፖለቲካ ማሻሻያዎች ላይ ሲያተኩሩ ሌሎች ደግሞ በብሔራዊ ምክክር አማካኝነት የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ ሞክረዋል።
ሀገራት ዘላቂ ሰላም ለማጽናት በሚያደርጉት በዚህ ሒደት ፖለቲካዊ ውሳኔዎች ብቻ ሙሉ በሙሉ መፍትሔ ማምጣት አይችሉም፡፡
በተለይም ሕዝቦች ለዘመናት ያዳበሩትን የሀገር በቀል ዕውቀትና ዕሴት በመጠቀም የሰዎችን ልቦና መፈወስና ማህበራዊ ትስስርን እንደገና መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡
በማኅበረሰቦች ውስጥ ለብዙ ትውልዶች በተግባር የተፈተነ፣ በልምድ የተገነባና በባሕል የተወረሰ የአኗኗር ጥበብ የሆኑት እነዚህ የሀገር በቀል ዕውቀቶች ግጭትን በንግግር ለመፍታት፣ እርቅን ለማምጣት፣ ማኅበረሰብን ለማስታረቅና ከተፈጠረ ጉዳት በኋላ የጋራ ኑሮን እንደገና ለመገንባትን ያስችላሉ።
ሀገር በቀል ዕውቀትን በመጠቀም ችግሮችን በመፍታት ረገድ ልምድ ካላቸው ሀገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ አንዷ ናት፡፡ይህም ከአፓርታይድ ሥርዓት መውደቅ በኋላ ሀገሪቱ በበቀል ወይም በኃይል ሳይሆን በውይይትና በመግባባት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንድትሻገር አስችሏታል።
ይህ “እኔ ስላለሁ አንተ አለህ፣ አንተ ስላለህ እኔ አለሁ” የሚለው የደቡብ አፍሪካ ጥንታዊ ዕሴት መደበኛ ብሔራዊ የውይይት መድረክ ባይሆንም፣ የዕርቁን፣ የጋራ መደማመጡን፣ የይቅርታን እና አብሮ የመኖርን መንፈስ የቀረጸ ባሕላዊና ሥነ ምግባራዊ ማዕቀፍ ሆኖ አገልግሏል።
በዚህም የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተቋቋመበት ወቅት የፍርድ ሒደቱ ሰዎችን በማግለልና በመቅጣት ላይ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን የተበላሹ ግንኙነቶችን በመጠገንና ማህበራዊ ፈውስን በማምጣት ላይ እንዲያተኩር ያስቻለ ሀገር በቀል የሞራል ዕሴት ነው።
የሀገር በቀል ዕውቀት ዘመናዊ የመንግሥት ተቋማትን በእምነት፣ በመተማመንና በማኅበራዊ ቅቡልነት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ የደቡብ አፍሪካ ተሞክሮ አንድ ጠቃሚ ትምህርት ያስተምራል።
ኢትዮጵያም ያሏትን ለዘመናት የቆዩ በርካታ የሀገር በቀል የግጭት አፈታት ልምዶችን ከዘመናዊ የሕግና የፖለቲካ ተቋማት ጋር በማጣጣም ለሕዝብ ውይይት የሚያስፈልገውን እምነትና መተማመን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
እነዚህ ጥንታዊ ዕሴቶች ዘመናዊውን የመንግሥት አወቃቀርና የሕግ የበላይነት የሚያግዙ፣ ለሕዝብ ውይይቶች ጥልቀትንና መንፈሳዊ ጥንካሬን የሚሰጡ ተጨማሪ ሃብቶች ተደርገው ሊወሰዱ ይገባል።
በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅራኔዎቿን በዘላቂነት ለመፍታት ባለፉት ዓመታት ስታከናውን የቆየችውን የአጀንዳ ልየታ በስኬት በማጠናቀቅ፣ አሁን ላይ ታሪካዊና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዮች የሚሳተፉበት የሀገራዊ ምክክር ጉባዔም የዚህ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማሳያ ነው፡፡ ሒደቱ ሙሉ በሙሉ አካታችና ፍትሃዊ እንዲሆን የተለያዩ አመለካከት ያላቸውና ከተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዮች እየተሳተፉበት ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ የምክክር እንቅስቃሴ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ በማሳደግ፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ትልቅ ዕድል የያዘ ሲሆን÷ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን ከዘመናዊ የመንግሥት አወቃቀር ጋር በማጣመር የተባበረች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ለመስጠት ያስችላል።
ስለሆነም ለዚህ ታላቅ ሀገራዊ ግብ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲና ባለድርሻ አካል የበኩሉን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ሊያበረክት ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዙሪያ ሀገራት የፖለቲካ ቀውስ፣ የማኅበራዊ ክፍፍል እና የግጭት ሁኔታዎችን ለመሻገር አንዳንዶቹ በሕግና በፖለቲካ ማሻሻያዎች ላይ ሲያተኩሩ ሌሎች ደግሞ በብሔራዊ ምክክር አማካኝነት የጋራ መፍትሔ ለመፈለግ ሞክረዋል።
ሀገራት ዘላቂ ሰላም ለማጽናት በሚያደርጉት በዚህ ሒደት ፖለቲካዊ ውሳኔዎች ብቻ ሙሉ በሙሉ መፍትሔ ማምጣት አይችሉም፡፡
በተለይም ሕዝቦች ለዘመናት ያዳበሩትን የሀገር በቀል ዕውቀትና ዕሴት በመጠቀም የሰዎችን ልቦና መፈወስና ማህበራዊ ትስስርን እንደገና መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡
በማኅበረሰቦች ውስጥ ለብዙ ትውልዶች በተግባር የተፈተነ፣ በልምድ የተገነባና በባሕል የተወረሰ የአኗኗር ጥበብ የሆኑት እነዚህ የሀገር በቀል ዕውቀቶች ግጭትን በንግግር ለመፍታት፣ እርቅን ለማምጣት፣ ማኅበረሰብን ለማስታረቅና ከተፈጠረ ጉዳት በኋላ የጋራ ኑሮን እንደገና ለመገንባትን ያስችላሉ።
ሀገር በቀል ዕውቀትን በመጠቀም ችግሮችን በመፍታት ረገድ ልምድ ካላቸው ሀገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ አንዷ ናት፡፡ይህም ከአፓርታይድ ሥርዓት መውደቅ በኋላ ሀገሪቱ በበቀል ወይም በኃይል ሳይሆን በውይይትና በመግባባት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንድትሻገር አስችሏታል።
ይህ “እኔ ስላለሁ አንተ አለህ፣ አንተ ስላለህ እኔ አለሁ” የሚለው የደቡብ አፍሪካ ጥንታዊ ዕሴት መደበኛ ብሔራዊ የውይይት መድረክ ባይሆንም፣ የዕርቁን፣ የጋራ መደማመጡን፣ የይቅርታን እና አብሮ የመኖርን መንፈስ የቀረጸ ባሕላዊና ሥነ ምግባራዊ ማዕቀፍ ሆኖ አገልግሏል።
በዚህም የእውነትና የዕርቅ ኮሚሽን በተቋቋመበት ወቅት የፍርድ ሒደቱ ሰዎችን በማግለልና በመቅጣት ላይ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን የተበላሹ ግንኙነቶችን በመጠገንና ማህበራዊ ፈውስን በማምጣት ላይ እንዲያተኩር ያስቻለ ሀገር በቀል የሞራል ዕሴት ነው።
የሀገር በቀል ዕውቀት ዘመናዊ የመንግሥት ተቋማትን በእምነት፣ በመተማመንና በማኅበራዊ ቅቡልነት ለማጠናከር ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ የደቡብ አፍሪካ ተሞክሮ አንድ ጠቃሚ ትምህርት ያስተምራል።
ኢትዮጵያም ያሏትን ለዘመናት የቆዩ በርካታ የሀገር በቀል የግጭት አፈታት ልምዶችን ከዘመናዊ የሕግና የፖለቲካ ተቋማት ጋር በማጣጣም ለሕዝብ ውይይት የሚያስፈልገውን እምነትና መተማመን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
እነዚህ ጥንታዊ ዕሴቶች ዘመናዊውን የመንግሥት አወቃቀርና የሕግ የበላይነት የሚያግዙ፣ ለሕዝብ ውይይቶች ጥልቀትንና መንፈሳዊ ጥንካሬን የሚሰጡ ተጨማሪ ሃብቶች ተደርገው ሊወሰዱ ይገባል።
በዚሁ መሠረት ኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅራኔዎቿን በዘላቂነት ለመፍታት ባለፉት ዓመታት ስታከናውን የቆየችውን የአጀንዳ ልየታ በስኬት በማጠናቀቅ፣ አሁን ላይ ታሪካዊና ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ከተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዮች የሚሳተፉበት የሀገራዊ ምክክር ጉባዔም የዚህ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማሳያ ነው፡፡ ሒደቱ ሙሉ በሙሉ አካታችና ፍትሃዊ እንዲሆን የተለያዩ አመለካከት ያላቸውና ከተለያዩ የማሕበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ ተወካዮች እየተሳተፉበት ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ የምክክር እንቅስቃሴ የዜጎችን እምነትና ተሳትፎ በማሳደግ፣ ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ትልቅ ዕድል የያዘ ሲሆን÷ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን ከዘመናዊ የመንግሥት አወቃቀር ጋር በማጣመር የተባበረች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ለመስጠት ያስችላል።
ስለሆነም ለዚህ ታላቅ ሀገራዊ ግብ ስኬት እያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲና ባለድርሻ አካል የበኩሉን አዎንታዊ አስተዋጽኦ ሊያበረክት ይገባል።
በዮናስ ጌትነት
24 days ago
“የንባብ ከተማ” የተሰኘ የህጻናት ቲያትር በድምቀት ተመረቀ
#ethiopia | የህፃናትን የንባብ ባህል ለማዳበር ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀው “የንባብ ከተማ” የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር ዛሬ ረፋድ ላይ ለእይታ በቃ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቲያትር ቤቶች አስተዳደር፣ የህጻናትን እና የወጣቶችን ጥበባዊ ተሰጥኦ ለማሳደግና ታሪክን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ዘመናዊ የቲያትር መድረኮችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋገኘው ለገሠ እንደገለጹት፣ ከተማዋ ዘመናዊ የንባብና የመዝናኛ ቦታዎችን በመገንባት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራች ነው።
በዚህም መሰረት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው እና ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የህጻናት እና ወጣቶች ቲያትር ቤት ለህጻናት የተዘጋጀ አዲስ ቲያትር በይፋ መመረቁን ጠቅሰው፣ ይህንን መድረክ ለታለመለት አላማ ሙሉ ለሙሉ ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በቋሚነት ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል።
ለህፃናትና ለወላጆች ምቹ በሆነው በዚህ አዳራሽ፣ ከቴአትር በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮች እንደሚኖሩት ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#addisababa #theaterlife #culturalheritage #ethiopianarts #kidstheater #citydevelopment #performingarts #communityengagement
#ethiopia | የህፃናትን የንባብ ባህል ለማዳበር ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀው “የንባብ ከተማ” የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር ዛሬ ረፋድ ላይ ለእይታ በቃ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቲያትር ቤቶች አስተዳደር፣ የህጻናትን እና የወጣቶችን ጥበባዊ ተሰጥኦ ለማሳደግና ታሪክን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ዘመናዊ የቲያትር መድረኮችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋገኘው ለገሠ እንደገለጹት፣ ከተማዋ ዘመናዊ የንባብና የመዝናኛ ቦታዎችን በመገንባት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራች ነው።
በዚህም መሰረት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው እና ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የህጻናት እና ወጣቶች ቲያትር ቤት ለህጻናት የተዘጋጀ አዲስ ቲያትር በይፋ መመረቁን ጠቅሰው፣ ይህንን መድረክ ለታለመለት አላማ ሙሉ ለሙሉ ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በቋሚነት ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል።
ለህፃናትና ለወላጆች ምቹ በሆነው በዚህ አዳራሽ፣ ከቴአትር በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮች እንደሚኖሩት ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#addisababa #theaterlife #culturalheritage #ethiopianarts #kidstheater #citydevelopment #performingarts #communityengagement
25 days ago
በዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ የተጻፉ ሁለት አዳዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መጽሐፍት ተመረቁ
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
25 days ago
ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ግድያ ለመበቀል ቃል ገቡ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ አያቶላ ሞጅታባ ኻሜኒ የተገደሉትን አባታቸውን አሊ ኻሜኒን ደም መበቀል የመላው የኢራን ሕዝብ ፍላጎት በመሆኑ የአጸፋው ርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ።
ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ሥርዓተ ቀብር መፈጸሙን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ካለአግባብ የንጹሃንን ህይወት የቀጠፉ ወንጀለኛና ክብር የለሽ ነፍሰ ገዳዮችን ለመበቀል ቃል እንገባለን ብለዋል።
ለሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የሽኝት ሥነ ስርዓት ተጠናቅቆ የኢራን የቀድሞው መሪ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።
አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ኢራን ተከታታይ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰዷ ይታወሳል።
በሌላ በኩል ኢራን የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለመግደል አዲስ እቅድ ማውጣቷን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሶኛል ስትል እስራኤል በቅርቡ ለአሜሪካ የደህንነት መረጃ ማጋራቷን ዘገባዎች አመላክተዋል።
ይህንን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ትሰስር ገጻቸው በኩል ኢራን በእሳቸው ላይ የግድያ ሙከራ ካደረገች በሺዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችን በኢራን ላይ እንደሚተኩሱ ማስጠንቀቃቸውን የዘገበው አናዶሉ ነው።
ቴህራን እና ዋሽንግተን በሁሉም ግንባሮች ላይ የሚደረጉ ውጊያዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው የባህር ኃይል እገዳ እንዲነሳ እና የሆርሙዝ ሰርጥ በድጋሚ እንዲከፈት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመው ነበር።
ይሁን እንጂ በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት በመሰንዘሩ ምክንያት በሁለቱ ወገኖች መካከል ተቀዛቅዞ የነበረው ውጊያ በድጋሜ እየተባባሰ መምጣቱ ይታወቃል።
በቱርክ በተካሄደው የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን (ኔቶ) ስብሰባ ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ማብቃቱን መግለጻቸው ይታወሳል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ አያቶላ ሞጅታባ ኻሜኒ የተገደሉትን አባታቸውን አሊ ኻሜኒን ደም መበቀል የመላው የኢራን ሕዝብ ፍላጎት በመሆኑ የአጸፋው ርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ።
ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ሥርዓተ ቀብር መፈጸሙን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ካለአግባብ የንጹሃንን ህይወት የቀጠፉ ወንጀለኛና ክብር የለሽ ነፍሰ ገዳዮችን ለመበቀል ቃል እንገባለን ብለዋል።
ለሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የሽኝት ሥነ ስርዓት ተጠናቅቆ የኢራን የቀድሞው መሪ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።
አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ኢራን ተከታታይ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰዷ ይታወሳል።
በሌላ በኩል ኢራን የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለመግደል አዲስ እቅድ ማውጣቷን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሶኛል ስትል እስራኤል በቅርቡ ለአሜሪካ የደህንነት መረጃ ማጋራቷን ዘገባዎች አመላክተዋል።
ይህንን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ትሰስር ገጻቸው በኩል ኢራን በእሳቸው ላይ የግድያ ሙከራ ካደረገች በሺዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችን በኢራን ላይ እንደሚተኩሱ ማስጠንቀቃቸውን የዘገበው አናዶሉ ነው።
ቴህራን እና ዋሽንግተን በሁሉም ግንባሮች ላይ የሚደረጉ ውጊያዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችው የባህር ኃይል እገዳ እንዲነሳ እና የሆርሙዝ ሰርጥ በድጋሚ እንዲከፈት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመው ነበር።
ይሁን እንጂ በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል በሚያልፉ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት በመሰንዘሩ ምክንያት በሁለቱ ወገኖች መካከል ተቀዛቅዞ የነበረው ውጊያ በድጋሜ እየተባባሰ መምጣቱ ይታወቃል።
በቱርክ በተካሄደው የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን (ኔቶ) ስብሰባ ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ማብቃቱን መግለጻቸው ይታወሳል።
በዮናስ ጌትነት
Sponsored by
Surafel
26 days ago
የዲጂታል ፋይናንስ ሥርዓት ለሁለንተናዊ ብልጽግና…
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ገንዘብ ዝውውርን የሁለንተናዊ ብልጽግናዋ ወሳኝ ምሰሶ አድርጋ እየተከተለች ትገኛለች።
አስደናቂ የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በጥሬ ገንዘብ ላይ ከተመሰረተ አሰራር ወጥታ በዲጂታል ምህዳር በየዓመቱ በትሪሊየን የሚቆጠር የገንዘብ ዝውውር ወደሚከናወንባት ሀገር ተቀይራለች።
የመሰረተ ልማት መስፋፋትና የቴሌኮም ዘርፉ ማደግ ደግሞ ለተመዘገበው አስደናቂ ለውጥ ግንባር ቀደም ኃይል ነው፡፡
የሀገሪቱ የቴሌኮም ተጠቃሚዎች ቁጥር ወደ 87 ነጥብ 9 ሚሊየን በማደጉ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱ 99 ነጥብ 8 በመቶ የሕዝብ ተደራሽነትን እንዲያገኝ አስችሎታል።
ከዚህም በላይ የ4ጂ እና የ5ጂ መስፋፋት ለዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱ መፋጠን አስተማማኝ መሰረት ጥሏል።
በዚህ የዲጂታል ምህዳር ውስጥ የላቀ ስኬት ያስመዘገበው የኢትዮ ቴሌኮም ‘ቴሌብር’ መተግበሪያ በሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር 58 ሚሊየን አድርሷል፡፡
ቴሌብር ብቻውን ከ58 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን በማፍራት አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፤ እስካሁን ድረስ ከ6 ነጥብ 88 ትሪሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር አስተናግዷል፡፡
ይህ መተግበሪያ ከገንዘብ ማስተላለፍ ባለፈ ለዜጎች የብድር አገልግሎት በመስጠት ለፋይናንስ አካታችነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፡፡
በሞባይል የሚደረገው የገንዘብ ዝውውር በጥሬ ገንዘብ ከሚደረገው መብለጡ የሽግግሩን ጥልቀት ያሳያል።
ይህ የፋይናንስ ዘርፍ ዘመናዊነት የግብይት ወጪን በመቀነስና ለዜጎች ምቾትን በመፍጠር ብቻ የሚገደብ ሳይሆን የፋይናንስ ደህንነትንና ግልጽነትን በማረጋገጥ ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
የፋይናንስ ተቋማትን አሰራር በማዘመንና ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት፤ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና በማጭበርበር ወንጀል ሊመዘበር የነበረ በቢሊየን የሚቆጠር ሃብት ማዳን ተችሏል።
እንዲሁም የወንጀል ተጠርጣሪዎች የሚንቀሳቀሱባቸው የባንክ ሂሳቦች እንዲታገዱ በማድረግ ደኅንነቱ የተጠበቀ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ አቅም ሆኗል።
አጠቃላይ የዲጂታል ሽግግሩ አሁን ላይ ከመሰረተ ልማት ዝርጋታ ባለፈ ወደ ተጨባጭ ድርጊትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወደሚመራ አስተዳደር እየተሸጋገረ ነው፡፡
የፋይዳ መታወቂያ ደግሞ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን በማበርከት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
መንግሥት እየተገበረ የሚገኘው የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የተጀመረውን ስኬት ይበልጥ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ይህ የዲጂታል ክፍያና የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ዘመናዊነት ሀገሪቱ በግብርና፣ በኮንስትራክሽን፣ በቱሪዝም እና በሌሎችም ቁልፍ የልማት መስኮች ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የማይናወጥና አስተማማኝ የፋይናንስ የጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ገንዘብ ዝውውርን የሁለንተናዊ ብልጽግናዋ ወሳኝ ምሰሶ አድርጋ እየተከተለች ትገኛለች።
አስደናቂ የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምዕራፍ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በጥሬ ገንዘብ ላይ ከተመሰረተ አሰራር ወጥታ በዲጂታል ምህዳር በየዓመቱ በትሪሊየን የሚቆጠር የገንዘብ ዝውውር ወደሚከናወንባት ሀገር ተቀይራለች።
የመሰረተ ልማት መስፋፋትና የቴሌኮም ዘርፉ ማደግ ደግሞ ለተመዘገበው አስደናቂ ለውጥ ግንባር ቀደም ኃይል ነው፡፡
የሀገሪቱ የቴሌኮም ተጠቃሚዎች ቁጥር ወደ 87 ነጥብ 9 ሚሊየን በማደጉ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱ 99 ነጥብ 8 በመቶ የሕዝብ ተደራሽነትን እንዲያገኝ አስችሎታል።
ከዚህም በላይ የ4ጂ እና የ5ጂ መስፋፋት ለዲጂታል ክፍያ ሥርዓቱ መፋጠን አስተማማኝ መሰረት ጥሏል።
በዚህ የዲጂታል ምህዳር ውስጥ የላቀ ስኬት ያስመዘገበው የኢትዮ ቴሌኮም ‘ቴሌብር’ መተግበሪያ በሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ የሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር 58 ሚሊየን አድርሷል፡፡
ቴሌብር ብቻውን ከ58 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን በማፍራት አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፤ እስካሁን ድረስ ከ6 ነጥብ 88 ትሪሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር አስተናግዷል፡፡
ይህ መተግበሪያ ከገንዘብ ማስተላለፍ ባለፈ ለዜጎች የብድር አገልግሎት በመስጠት ለፋይናንስ አካታችነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፡፡
በሞባይል የሚደረገው የገንዘብ ዝውውር በጥሬ ገንዘብ ከሚደረገው መብለጡ የሽግግሩን ጥልቀት ያሳያል።
ይህ የፋይናንስ ዘርፍ ዘመናዊነት የግብይት ወጪን በመቀነስና ለዜጎች ምቾትን በመፍጠር ብቻ የሚገደብ ሳይሆን የፋይናንስ ደህንነትንና ግልጽነትን በማረጋገጥ ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
የፋይናንስ ተቋማትን አሰራር በማዘመንና ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት፤ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና በማጭበርበር ወንጀል ሊመዘበር የነበረ በቢሊየን የሚቆጠር ሃብት ማዳን ተችሏል።
እንዲሁም የወንጀል ተጠርጣሪዎች የሚንቀሳቀሱባቸው የባንክ ሂሳቦች እንዲታገዱ በማድረግ ደኅንነቱ የተጠበቀ የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ አቅም ሆኗል።
አጠቃላይ የዲጂታል ሽግግሩ አሁን ላይ ከመሰረተ ልማት ዝርጋታ ባለፈ ወደ ተጨባጭ ድርጊትና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወደሚመራ አስተዳደር እየተሸጋገረ ነው፡፡
የፋይዳ መታወቂያ ደግሞ ለዜጎች ቀልጣፋ አሰራርን በማበርከት ረገድ ትልቅ አስተዋጽዖ እያበረከተ ይገኛል።
መንግሥት እየተገበረ የሚገኘው የዲጂታል 2030 ስትራቴጂ የተጀመረውን ስኬት ይበልጥ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ ለማድረግ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ይህ የዲጂታል ክፍያና የገንዘብ ዝውውር ሥርዓት ዘመናዊነት ሀገሪቱ በግብርና፣ በኮንስትራክሽን፣ በቱሪዝም እና በሌሎችም ቁልፍ የልማት መስኮች ለጀመረችው የብልጽግና ጉዞ የማይናወጥና አስተማማኝ የፋይናንስ የጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
በዮናስ ጌትነት
27 days ago
ኢትዮጵያ በህክምና መሳሪያዎች ቁጥጥር ከአፍሪካ የመጀመሪያዋ ለመሆን እየተጋች ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱና ከውጭ የሚገቡ የህክምና መሳሪያዎችን ጥራትና ደህንነት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ።
በባለስልጣኑ የህክምና መሳሪያ ጥራት ምርመራ ላብራቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ቃልአብ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፣ ላብራቶሪው በአዲስ መዋቅር ከተደራጀ በኋላ በህክምና መሳሪያዎች ጥራት ምርመራ፣ በምዝገባ፣ ከገበያ በኋላ በሚደረግ የጥራት ክትትልና ጥርጣሬ የወደቀባቸውን ምርቶች በመመርመር ረገድ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ላብራቶሪው በአሁኑ ወቅት ኮንዶም፣ (ሄፐታይተስ) ቢ እና ሲ እንዲሁም የወባ መመርመሪያዎችን ጨምሮ በርካታ የህክምና መሳሪያዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባገኘበት አግባብ እየመረመረ መሆኑን አቶ ቃልአብ አብራርተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የወንድና የሴት ኮንዶሞች፣ የቀዶ ህክምናና የላብራቶሪ ጓንቶች፣ መርፌ፣ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያዎችና ማስኮችን ጥራት በተደራጀ መልኩ የመመርመር አቅም መገንባቱን ገልጸዋል። ይህ የጥራት ምርመራ አሰራር በዘፈቀደ የሚከናወን ሳይሆን፣ በመንግስት ላይ የሚባክን ወጪን ለመቀነስና የህብረተሰቡን ጤና ይበልጥ ለመጠበቅ ሲባል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና የችግር ዳሰሳ ጥናትን መሰረት ያደረገ "በስጋት ላይ የተመሰረተ አቀራረብ" የተከተለ መሆኑን አስረድተዋል።
የናሙና አወሳሰድ ሂደቱን በተመለከተ አቶ ቃልአብ እንደገለጹት፣ የህክምና መሳሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡባቸው የድንበር ኬላዎችና ወደቦች ላይ ዓለም አቀፍ የአይሶ (ISO 2859-1) ስታንዳርድን የተከተለ ጥብቅ የናሙና አሰባሰብ ይከናወናል።
ከዚህም በተጨማሪ ምርቶች አንዴ ወደ ሀገር ውስጥ ከገቡ በኋላ በትራንስፖርትና በክምችት ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ መበላሸቶችን ለመቆጣጠር ሲባል፣ በዓመት ሁለት ጊዜ ከገበያ ላይ ራንደምሊ ናሙናዎች ይሰበሰባሉ።
ይህ የገበያ ቅኝት ጥናትም እጅግ ሞቃታማ የሆኑትን እንደ አፋርና ጋምቤላ ያሉ አካባቢዎችን እንዲሁም ቀዝቃዛ የሚባሉትን እንደ ደብረብርሃን ያሉ አካባቢዎችን በማካተት ምርቶቹ በተለያዩ የአየር ንብረቶች ውስጥ ያላቸውን ጥንካሬ ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ጠቁመዋል።
በባለስልጣኑ አቅም የማይሰሩ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ዩሪን ስትሪፕ ያሉ ምርቶች ላይ የጥራት ጉድለት ጥርጣሬ ሲፈጠርም በአስቸኳይ ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ምርመራ ተደርጎ ፈጣን የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ አብራርተዋል።
የመንግስትን የዜጎች ቻርተር መሰረት በማድረግ የደንበኞችን የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜ ለማሳጠር ሰፊ ማሻሻያ መደረጉን መሪ ስራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል። ቀደም ሲል ለአንድ የኮንዶም ባች ምርመራ 15 ቀናት ይፈጅ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ሰራተኞች ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በትርፍ ሰዓትና በምሽት ጭምር እንዲሰሩ በማድረግ የምርመራ ጊዜውን እስከ 50 በመቶ በመቀነስ ወደ 7 እና 8 ቀናት ዝቅ ማድረግ ተችሏል።
በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአቅርቦት እጥረት የሚያጋጥምባቸው አጋጣሚዎች ሲኖሩ ሂደቱን ይበልጥ በማፋጠን በ3 ቀናት ውስጥ ብቻ ምርመራውን አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ አሰራር መዘርጋቱን አቶ ቃልአብ ጠቁመዋል።
ኮንዶሞች ወደ ገበያ ከመውጣታቸው በፊት እንደ አየር መያዝ አቅም (ከ18 ሊትር በላይ መቻል ያለበት)፣ የግፊት መቋቋም (ከ1 ኪሎ ፓስካል በላይ) እና የቀዳዳ መኖርና አለመኖር (ሆል ቴስት) ምርመራዎች መቶ በመቶ እንደሚሰሩባቸው በማረጋገጥ፣ በግንኙነት ወቅት የሚፈጠሩ መቅረትና መበላሸቶች በአብዛኛው ከአጠቃቀምና ከተጨማሪ ሉብሪካንት አጠቃቀም ችግሮች ጋር የተያያዙ መሆናቸውንና ህብረተሰቡ በጥቅሉ ላይ ያለውን መመሪያ መከተል እንዳለበት አሳስበዋል።
በመጨረሻም፣ ባለስልጣኑ የላብራቶሪውን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የደረጃ ሶስት (Maturity Level 3) እውቅናን ለማግኘት በትጋት እየሰራ መሆኑን አቶ ቃልአብ አብስረዋል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ደረጃ በህክምና መሳሪያዎች ዘርፍ ይህንን የደረጃ ሶስት እውቅና ያገኘ ሀገር የሌለ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ይህንን ማሳካት ከቻለች የመጀመሪያዋ ሀገር ትሆናለች።
በቅርቡ በባለስልጣኑ በተደረገ ምርመራ የዓለም ጤና ድርጅት እውቅና (ፕሪኳሊፋይድ) በሰጠው የውጭ ፋብሪካ የተመረተ የማላሪያ መድኃኒት የጥራት ጉድለት ተገኝቶበት ውድቅ መደረጉንና ይህም የባለስልጣኑን የአስፈጻሚነት አቅም ያስመሰከረ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ተግባር የዓለም ጤና ድርጅትን ትኩረት የሳበ ሲሆን፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ የህክምና መሳሪያ ጥራት ምርመራ ላብራቶሪ የዓለም ጤና ድርጅት እውቅና ያገኘ እና ለምስራቅ አፍሪካ (ኢጋድ) ሀገራት እንዲሁም ለአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ ዋነኛ የማመሳከሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ ሰፊ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አቶ ቃልአብ ተስፋዬ አረጋግጠዋል።
በጌትነት ተመስገን
#getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#efda #ethiopia #healthinnovation #qualityassurance #medicalstandards #africanpublichealth
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱና ከውጭ የሚገቡ የህክምና መሳሪያዎችን ጥራትና ደህንነት ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ዘመናዊ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ።
በባለስልጣኑ የህክምና መሳሪያ ጥራት ምርመራ ላብራቶሪ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ቃልአብ ተስፋዬ ወርቁ እንደገለጹት፣ ላብራቶሪው በአዲስ መዋቅር ከተደራጀ በኋላ በህክምና መሳሪያዎች ጥራት ምርመራ፣ በምዝገባ፣ ከገበያ በኋላ በሚደረግ የጥራት ክትትልና ጥርጣሬ የወደቀባቸውን ምርቶች በመመርመር ረገድ ሰፊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ላብራቶሪው በአሁኑ ወቅት ኮንዶም፣ (ሄፐታይተስ) ቢ እና ሲ እንዲሁም የወባ መመርመሪያዎችን ጨምሮ በርካታ የህክምና መሳሪያዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባገኘበት አግባብ እየመረመረ መሆኑን አቶ ቃልአብ አብራርተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የወንድና የሴት ኮንዶሞች፣ የቀዶ ህክምናና የላብራቶሪ ጓንቶች፣ መርፌ፣ የሴቶች የንጽህና መጠበቂያዎችና ማስኮችን ጥራት በተደራጀ መልኩ የመመርመር አቅም መገንባቱን ገልጸዋል። ይህ የጥራት ምርመራ አሰራር በዘፈቀደ የሚከናወን ሳይሆን፣ በመንግስት ላይ የሚባክን ወጪን ለመቀነስና የህብረተሰቡን ጤና ይበልጥ ለመጠበቅ ሲባል በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጠና የችግር ዳሰሳ ጥናትን መሰረት ያደረገ "በስጋት ላይ የተመሰረተ አቀራረብ" የተከተለ መሆኑን አስረድተዋል።
የናሙና አወሳሰድ ሂደቱን በተመለከተ አቶ ቃልአብ እንደገለጹት፣ የህክምና መሳሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡባቸው የድንበር ኬላዎችና ወደቦች ላይ ዓለም አቀፍ የአይሶ (ISO 2859-1) ስታንዳርድን የተከተለ ጥብቅ የናሙና አሰባሰብ ይከናወናል።
ከዚህም በተጨማሪ ምርቶች አንዴ ወደ ሀገር ውስጥ ከገቡ በኋላ በትራንስፖርትና በክምችት ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ መበላሸቶችን ለመቆጣጠር ሲባል፣ በዓመት ሁለት ጊዜ ከገበያ ላይ ራንደምሊ ናሙናዎች ይሰበሰባሉ።
ይህ የገበያ ቅኝት ጥናትም እጅግ ሞቃታማ የሆኑትን እንደ አፋርና ጋምቤላ ያሉ አካባቢዎችን እንዲሁም ቀዝቃዛ የሚባሉትን እንደ ደብረብርሃን ያሉ አካባቢዎችን በማካተት ምርቶቹ በተለያዩ የአየር ንብረቶች ውስጥ ያላቸውን ጥንካሬ ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ጠቁመዋል።
በባለስልጣኑ አቅም የማይሰሩ እንደ እርግዝና መመርመሪያ ዩሪን ስትሪፕ ያሉ ምርቶች ላይ የጥራት ጉድለት ጥርጣሬ ሲፈጠርም በአስቸኳይ ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ምርመራ ተደርጎ ፈጣን የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ አብራርተዋል።
የመንግስትን የዜጎች ቻርተር መሰረት በማድረግ የደንበኞችን የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜ ለማሳጠር ሰፊ ማሻሻያ መደረጉን መሪ ስራ አስፈጻሚው ጠቅሰዋል። ቀደም ሲል ለአንድ የኮንዶም ባች ምርመራ 15 ቀናት ይፈጅ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ሰራተኞች ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በትርፍ ሰዓትና በምሽት ጭምር እንዲሰሩ በማድረግ የምርመራ ጊዜውን እስከ 50 በመቶ በመቀነስ ወደ 7 እና 8 ቀናት ዝቅ ማድረግ ተችሏል።
በተለይም በሀገር አቀፍ ደረጃ የአቅርቦት እጥረት የሚያጋጥምባቸው አጋጣሚዎች ሲኖሩ ሂደቱን ይበልጥ በማፋጠን በ3 ቀናት ውስጥ ብቻ ምርመራውን አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ የማድረግ አሰራር መዘርጋቱን አቶ ቃልአብ ጠቁመዋል።
ኮንዶሞች ወደ ገበያ ከመውጣታቸው በፊት እንደ አየር መያዝ አቅም (ከ18 ሊትር በላይ መቻል ያለበት)፣ የግፊት መቋቋም (ከ1 ኪሎ ፓስካል በላይ) እና የቀዳዳ መኖርና አለመኖር (ሆል ቴስት) ምርመራዎች መቶ በመቶ እንደሚሰሩባቸው በማረጋገጥ፣ በግንኙነት ወቅት የሚፈጠሩ መቅረትና መበላሸቶች በአብዛኛው ከአጠቃቀምና ከተጨማሪ ሉብሪካንት አጠቃቀም ችግሮች ጋር የተያያዙ መሆናቸውንና ህብረተሰቡ በጥቅሉ ላይ ያለውን መመሪያ መከተል እንዳለበት አሳስበዋል።
በመጨረሻም፣ ባለስልጣኑ የላብራቶሪውን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) የደረጃ ሶስት (Maturity Level 3) እውቅናን ለማግኘት በትጋት እየሰራ መሆኑን አቶ ቃልአብ አብስረዋል።
በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ደረጃ በህክምና መሳሪያዎች ዘርፍ ይህንን የደረጃ ሶስት እውቅና ያገኘ ሀገር የሌለ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ ይህንን ማሳካት ከቻለች የመጀመሪያዋ ሀገር ትሆናለች።
በቅርቡ በባለስልጣኑ በተደረገ ምርመራ የዓለም ጤና ድርጅት እውቅና (ፕሪኳሊፋይድ) በሰጠው የውጭ ፋብሪካ የተመረተ የማላሪያ መድኃኒት የጥራት ጉድለት ተገኝቶበት ውድቅ መደረጉንና ይህም የባለስልጣኑን የአስፈጻሚነት አቅም ያስመሰከረ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ተግባር የዓለም ጤና ድርጅትን ትኩረት የሳበ ሲሆን፣ በቀጣይ የኢትዮጵያ የህክምና መሳሪያ ጥራት ምርመራ ላብራቶሪ የዓለም ጤና ድርጅት እውቅና ያገኘ እና ለምስራቅ አፍሪካ (ኢጋድ) ሀገራት እንዲሁም ለአፍሪካ መድኃኒት ኤጀንሲ ዋነኛ የማመሳከሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ ሰፊ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አቶ ቃልአብ ተስፋዬ አረጋግጠዋል።
በጌትነት ተመስገን
#getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#efda #ethiopia #healthinnovation #qualityassurance #medicalstandards #africanpublichealth
29 days ago
* የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅም ወደ 45 ፐርሰንት ማሳደግ ተችሏል
* የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ማቹሪቲ ሌቭል ሦስት ብሏታል
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፣ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት በሕክምና መሣሪያዎችና በመድኃኒት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ መሻሻል መመዝገቡን ገልጸዋል።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ መንግሥት በበጀት ዓመቱ ለመድኃኒት ግዢ ብቻ 70 ቢሊየን ብር ወጪ ያደረገ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም 4 ፐርሰንት ብቻ የነበረውን የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅም ወደ 44 እና 45 ፐርሰንት ማሳደግ ተችሏል።
ይህም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ጥቅም ላይ ከሚውሉት መድኃኒቶች መካከል ግማሽ ያህሉ እዚሁ በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ በማድረግ ረገድ ትልቅ እመርታ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ሰፋፊ ሥራዎችን ለማጠናከርም የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን ጨምሮ የተለያዩ የፋርማሲውቲካል ተቋማት የክትባት ምርትን ለመቆጣጠርና የመደገፍ አቅምን ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ።
ከመድኃኒት አቅርቦት ባሻገር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ከ60 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በርካታ ዘመናዊ መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ካላት ሰፊ የሕዝብ ቁጥር አንጻር የሁለትና የሦስት ሆስፒታሎችን አቅም በማሳደግ ብቻ ፍላጎትን ማሟላት እንደማይቻል ገልጸው፣ በአዲስ አበባ ባለፉት ጥቂት ወራት በርካታ የሕክምና ተቋማት መመረቃቸውንና በሚቀጥሉት ጥቂት ወራትም ሌሎች ተጫማሪ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል።
ለአብነትም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን በመጥቀስ፣ ተቋሙ ተጨማሪ የ1,000 አልጋዎች የመያዝ አቅም እንዲኖረው ተደርጎ በከፍተኛ ደረጃ መገንባቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ያለው ፍላጎትና የተከማቸው የሕክምና ዕዳ ሰፊ በመሆኑ፣ በቀጣይነት ጠንካራና ተከታታይነት ያላቸው ሥራዎች እንደሚጠብቁ አስገንዝበዋል።
በፋርማሲውቲካል ዘርፍና በሆስፒታሎች ግንባታ እንዲሁም በቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ በተከናወኑት ስኬታማ ሥራዎች ምክንያት፣ የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን የብቃት ደረጃ ሦስት (Maturation Level 3) በሚል ዕውቅና መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ይህ ደረጃ ጥቂት የአፍሪካ ሀገራት ብቻ የደረሱበት ሲሆን፣ ቀጣዩና ትልቁ ግብ ደረጃ አራትን ማሳካት ነው። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ የምታመርታቸው መድኃኒቶች ለዓለም አቀፍ የኤክስፖርት ገበያ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ትልቅ በር የሚከፍት ነው።
በዘርፉ የታዩ ለውጦችና ዕድገቶች ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም፣ ገና ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች እንዳሉ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊወዳደሩ የሚችሉና እጅግ የጸዱ የሕክምና መስጫ ተቋማትን ለመገንባት በዕቅድ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በመጨረሻም የዜጎችን ጤና ከወረርሽኝ ለመጠበቅ የተከናወኑ የጤና ጥበቃ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የወባ በሽታን ለመከላከል 14 ሚሊየን የሚጠጉ አጎበሮች በነጻ መሰራጨታቸውንና ወደ 3 ሚሊየን በሚጠጉ ቤቶች ላይ የፀረ-ወባ መርጨት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ58 ወረዳዎች የወባ መከላከያ ክትባት የመስጠት ሙከራ መጀመሩን ጠቁመዋል።
በጤና፣ በትምህርትና በአጠቃላይ በማኅበራዊ ዘርፍ የተጀመሩት ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠበቀውን ፍሬ እንዲያፈሩና ዘላቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መንግሥት አበክሮ መስራቱን እንደሚቀጥልበት አስገንዝበዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
* የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን ማቹሪቲ ሌቭል ሦስት ብሏታል
ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia | የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፣ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት በሕክምና መሣሪያዎችና በመድኃኒት አቅርቦት ላይ ከፍተኛ መሻሻል መመዝገቡን ገልጸዋል።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጻ፣ መንግሥት በበጀት ዓመቱ ለመድኃኒት ግዢ ብቻ 70 ቢሊየን ብር ወጪ ያደረገ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም 4 ፐርሰንት ብቻ የነበረውን የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅም ወደ 44 እና 45 ፐርሰንት ማሳደግ ተችሏል።
ይህም በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ጥቅም ላይ ከሚውሉት መድኃኒቶች መካከል ግማሽ ያህሉ እዚሁ በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ በማድረግ ረገድ ትልቅ እመርታ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘርፉ የተጀመሩ ሰፋፊ ሥራዎችን ለማጠናከርም የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩትን ጨምሮ የተለያዩ የፋርማሲውቲካል ተቋማት የክትባት ምርትን ለመቆጣጠርና የመደገፍ አቅምን ለመፍጠር የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ።
ከመድኃኒት አቅርቦት ባሻገር፣ ለሕክምና መሣሪያዎች ግዢ ከ60 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በርካታ ዘመናዊ መሣሪያዎች ወደ ሀገር ውስጥ እየገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያ ካላት ሰፊ የሕዝብ ቁጥር አንጻር የሁለትና የሦስት ሆስፒታሎችን አቅም በማሳደግ ብቻ ፍላጎትን ማሟላት እንደማይቻል ገልጸው፣ በአዲስ አበባ ባለፉት ጥቂት ወራት በርካታ የሕክምና ተቋማት መመረቃቸውንና በሚቀጥሉት ጥቂት ወራትም ሌሎች ተጫማሪ ተቋማት ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል።
ለአብነትም የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን በመጥቀስ፣ ተቋሙ ተጨማሪ የ1,000 አልጋዎች የመያዝ አቅም እንዲኖረው ተደርጎ በከፍተኛ ደረጃ መገንባቱን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ አሁንም ያለው ፍላጎትና የተከማቸው የሕክምና ዕዳ ሰፊ በመሆኑ፣ በቀጣይነት ጠንካራና ተከታታይነት ያላቸው ሥራዎች እንደሚጠብቁ አስገንዝበዋል።
በፋርማሲውቲካል ዘርፍና በሆስፒታሎች ግንባታ እንዲሁም በቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ በተከናወኑት ስኬታማ ሥራዎች ምክንያት፣ የዓለም የመድኃኒት ቁጥጥር ኤጀንሲ ኢትዮጵያን የብቃት ደረጃ ሦስት (Maturation Level 3) በሚል ዕውቅና መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ይህ ደረጃ ጥቂት የአፍሪካ ሀገራት ብቻ የደረሱበት ሲሆን፣ ቀጣዩና ትልቁ ግብ ደረጃ አራትን ማሳካት ነው። ይህ ዕውቅና ኢትዮጵያ የምታመርታቸው መድኃኒቶች ለዓለም አቀፍ የኤክስፖርት ገበያ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ትልቅ በር የሚከፍት ነው።
በዘርፉ የታዩ ለውጦችና ዕድገቶች ተስፋ ሰጪ ቢሆኑም፣ ገና ብዙ የሚቀሩ ሥራዎች እንዳሉ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊወዳደሩ የሚችሉና እጅግ የጸዱ የሕክምና መስጫ ተቋማትን ለመገንባት በዕቅድ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በመጨረሻም የዜጎችን ጤና ከወረርሽኝ ለመጠበቅ የተከናወኑ የጤና ጥበቃ ሥራዎችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የወባ በሽታን ለመከላከል 14 ሚሊየን የሚጠጉ አጎበሮች በነጻ መሰራጨታቸውንና ወደ 3 ሚሊየን በሚጠጉ ቤቶች ላይ የፀረ-ወባ መርጨት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ58 ወረዳዎች የወባ መከላከያ ክትባት የመስጠት ሙከራ መጀመሩን ጠቁመዋል።
በጤና፣ በትምህርትና በአጠቃላይ በማኅበራዊ ዘርፍ የተጀመሩት ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠበቀውን ፍሬ እንዲያፈሩና ዘላቂ ውጤት እንዲያስመዘግቡ መንግሥት አበክሮ መስራቱን እንደሚቀጥልበት አስገንዝበዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
1 month ago
የአበጋር ሥርዓት ለሰላም …
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት በሚደረገው ወሳኝ የሀገራዊ ምክክር ሒደት ውስጥ፣ የሀገር በቀል ዕውቀቶችና የባሕላዊ ዕርቅ ሥርዓቶች ሚና በቀላሉ የሚታይ አይደለም።
ለዚህ ደግሞ በአማራ ክልል በወሎ አካባቢ ለዘመናት የዘለቀው እና ማሕበረሰባዊ መስተጋብርን በማጠናከር ረገድ ትልቅ አቅም ያለው የ“አበጋር” የባሕላዊ ዳኝነትና የሽምግልና ሥርዓት በምሳሌነት የሚጠቀስ ታላቅ የሀገር ሃብት ነው።
ይህ ሥርዓት ከግለሰቦች አለመግባባት ጀምሮ እስከ ደም መቃባት የደረሱ ከባድ ማሕበረሰባዊ ቀውሶችን ያለ ምንም የመንግሥት የኃይል መዋቅር፣ በእውነትና በፈሪሃ ፈጣሪ ላይ ብቻ ተመስርቶ የመፍታት ጥበብ ያለው ሥርዓት ነው።
አንዱ ወገን አሸናፊ ሌላኛው ደግሞ ተሸናፊ ሆኖ ስለሚወጣ ቁርሾውና ቂሙ ለትውልድ የመሸጋገር ዕድል ካለው የመደበኛው የፍርድ ቤት ክርክር የሚለየው የአበጋር ሥርዓት ዋነኛ ፍልስፍናው ‘ሁለቱም አሸናፊ’ የሚያደርገውን እና ሁለቱንም ወገኖች የሚያስማማ የፍትሕ መርህን ይከተላል።
በአበጋር ሥርዓት በዳይ ጥፋቱን አምኖ ይቅርታ የሚጠይቅበት፣ ለተበደለው አካልም ተገቢው ካሳ የሚሰጥበት እና ሁለቱም ወገኖች ቂማቸውን አጥፍተው ወደ ቀድሞው የማሕበራዊ ትስስር ሕይወታቸው የሚመለሱበት በመሆኑ የነገን ቁርሾ ከሥሩ ነቅሎ መጣል የሚያስችል ሥርዓት አለው።
ይህ ዓይነቱ ዘላቂ ሰላምን የማምጣት አቅም አሁን ሀገሪቱ ለምትገኝበትና ዘላቂ አንድነትን ለምትሻበት የሀገራዊ ምክክር ሒደት እጅግ ተፈላጊና መሠረታዊ ግብዓት የመሆን ከፍተኛ አቅም ይዟል።
ሌላው የአበጋር ሥርዓት መገለጫ ለፍትሕ መረጋገጥ የሚሰጠው ፍጹም ታማኝነትና ከማንኛውም ዓይነት ሙስና የጸዳ መሆኑ ሲሆን÷ በሥርዓቱ ውስጥ የሚሳተፉ ሽማግሌዎች የሰውን እጅ የማያዩ የእውነትና የሕሊና ሰዎች በመሆናቸው በማኅበረሰቡ ዘንድ ያላቸው ቅቡልነት እጅግ ከፍተኛ ነው።
ማኅበረሰቡ ለአበጋሮች ቃል የሚገዛበትና የሚታመንበት የሕግ ልቦና ያለው ይህ ሥርዓት የራሱ የሆነ ‘ቁና ሰፊ’ በመባል የሚታወቅ የሕግ አውጪ እና ‘ቁና ሰፋሪ’ በመባል የሚታወቅ ሕግ ተርጓሚ መዋቅር ያቅፋል።
ከዚህ በተጨማሪ በዓመት አንድ ጊዜ በመሰብሰብ ሕጉን የመከለስና ከዘመኑ ጋር በማስማማት ራሱን በራሱ እያደሰ የመጣ ሕያው የሕግ ተቋም መሆን ችሏል።
ይህ የባሕል ዕሴት ከማንነት፣ ከብሔርና ከሃይማኖት ልዩነት የጸዳ መሆኑ ለሀገራዊ ምክክሩ ያለውን ፋይዳ የጎላ ያደርገዋል።
ከየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የመጣ ማንኛውም ሰው ችግር ሲገጥመው ያለ ምንም የባዕድነት ስጋት እኩል ፍትሕና አቀባበል እንዲያገኝ የሚያደርገው ሥርዓቱ ኢትዮጵያውያን የጋራ የሰላም እሴቶችና ታሪካዊ መስተጋብሮች እንዳሏቸው ትልቅ ማሳያ ነው።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እያከናወነች በምትገኘው የሀገራዊ ምክክር ሒደት ውስጥ ስኬትን ለማስመዝገብ፣ እንደ አበጋር ያሉ የሀገር በቀል የግጭት አፈታትና የዕርቅ ሥርዓቶችን ማዕከል ማድረግ ይገባል።
እነዚህን እሴቶች በደንብ አጥንቶ፣ መዝግቦና አደራጅቶ መጠቀም የሕዝቦችን ዘላቂ ሰላምና አብሮነት ለማረጋገጥ ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት እና ለእነዚህ የሀገር ሀብት ልዩ ትኩረትና ድጋፍ በመስጠት፣ ከማኅበረሰቡ ተሰሚነት ካላቸው የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በቅንጅት መሥራት ያስፈልጋል።
የሀገር ሰላም እና አንድነት በዘላቂነት ሊረጋገጥ የሚችለው ከውጭ በሚመጡ ፍልስፍናዎች ሳይሆን፣ እንደ አበጋር ካሉ ከኢትዮጵያውያን ሥነ ልቦና፣ እምነትና ነባራዊ አስተሳሰብ ውስጥ ተጨምቀው ከወጡ የውስጥ የሰላም መሣሪያዎች ጋር ማስተሳሰር ሲቻል ነው።
በዮናስ ጌትነት
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ብሔራዊ አንድነትን ለመገንባት በሚደረገው ወሳኝ የሀገራዊ ምክክር ሒደት ውስጥ፣ የሀገር በቀል ዕውቀቶችና የባሕላዊ ዕርቅ ሥርዓቶች ሚና በቀላሉ የሚታይ አይደለም።
ለዚህ ደግሞ በአማራ ክልል በወሎ አካባቢ ለዘመናት የዘለቀው እና ማሕበረሰባዊ መስተጋብርን በማጠናከር ረገድ ትልቅ አቅም ያለው የ“አበጋር” የባሕላዊ ዳኝነትና የሽምግልና ሥርዓት በምሳሌነት የሚጠቀስ ታላቅ የሀገር ሃብት ነው።
ይህ ሥርዓት ከግለሰቦች አለመግባባት ጀምሮ እስከ ደም መቃባት የደረሱ ከባድ ማሕበረሰባዊ ቀውሶችን ያለ ምንም የመንግሥት የኃይል መዋቅር፣ በእውነትና በፈሪሃ ፈጣሪ ላይ ብቻ ተመስርቶ የመፍታት ጥበብ ያለው ሥርዓት ነው።
አንዱ ወገን አሸናፊ ሌላኛው ደግሞ ተሸናፊ ሆኖ ስለሚወጣ ቁርሾውና ቂሙ ለትውልድ የመሸጋገር ዕድል ካለው የመደበኛው የፍርድ ቤት ክርክር የሚለየው የአበጋር ሥርዓት ዋነኛ ፍልስፍናው ‘ሁለቱም አሸናፊ’ የሚያደርገውን እና ሁለቱንም ወገኖች የሚያስማማ የፍትሕ መርህን ይከተላል።
በአበጋር ሥርዓት በዳይ ጥፋቱን አምኖ ይቅርታ የሚጠይቅበት፣ ለተበደለው አካልም ተገቢው ካሳ የሚሰጥበት እና ሁለቱም ወገኖች ቂማቸውን አጥፍተው ወደ ቀድሞው የማሕበራዊ ትስስር ሕይወታቸው የሚመለሱበት በመሆኑ የነገን ቁርሾ ከሥሩ ነቅሎ መጣል የሚያስችል ሥርዓት አለው።
ይህ ዓይነቱ ዘላቂ ሰላምን የማምጣት አቅም አሁን ሀገሪቱ ለምትገኝበትና ዘላቂ አንድነትን ለምትሻበት የሀገራዊ ምክክር ሒደት እጅግ ተፈላጊና መሠረታዊ ግብዓት የመሆን ከፍተኛ አቅም ይዟል።
ሌላው የአበጋር ሥርዓት መገለጫ ለፍትሕ መረጋገጥ የሚሰጠው ፍጹም ታማኝነትና ከማንኛውም ዓይነት ሙስና የጸዳ መሆኑ ሲሆን÷ በሥርዓቱ ውስጥ የሚሳተፉ ሽማግሌዎች የሰውን እጅ የማያዩ የእውነትና የሕሊና ሰዎች በመሆናቸው በማኅበረሰቡ ዘንድ ያላቸው ቅቡልነት እጅግ ከፍተኛ ነው።
ማኅበረሰቡ ለአበጋሮች ቃል የሚገዛበትና የሚታመንበት የሕግ ልቦና ያለው ይህ ሥርዓት የራሱ የሆነ ‘ቁና ሰፊ’ በመባል የሚታወቅ የሕግ አውጪ እና ‘ቁና ሰፋሪ’ በመባል የሚታወቅ ሕግ ተርጓሚ መዋቅር ያቅፋል።
ከዚህ በተጨማሪ በዓመት አንድ ጊዜ በመሰብሰብ ሕጉን የመከለስና ከዘመኑ ጋር በማስማማት ራሱን በራሱ እያደሰ የመጣ ሕያው የሕግ ተቋም መሆን ችሏል።
ይህ የባሕል ዕሴት ከማንነት፣ ከብሔርና ከሃይማኖት ልዩነት የጸዳ መሆኑ ለሀገራዊ ምክክሩ ያለውን ፋይዳ የጎላ ያደርገዋል።
ከየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል የመጣ ማንኛውም ሰው ችግር ሲገጥመው ያለ ምንም የባዕድነት ስጋት እኩል ፍትሕና አቀባበል እንዲያገኝ የሚያደርገው ሥርዓቱ ኢትዮጵያውያን የጋራ የሰላም እሴቶችና ታሪካዊ መስተጋብሮች እንዳሏቸው ትልቅ ማሳያ ነው።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ እያከናወነች በምትገኘው የሀገራዊ ምክክር ሒደት ውስጥ ስኬትን ለማስመዝገብ፣ እንደ አበጋር ያሉ የሀገር በቀል የግጭት አፈታትና የዕርቅ ሥርዓቶችን ማዕከል ማድረግ ይገባል።
እነዚህን እሴቶች በደንብ አጥንቶ፣ መዝግቦና አደራጅቶ መጠቀም የሕዝቦችን ዘላቂ ሰላምና አብሮነት ለማረጋገጥ ያለውን ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት እና ለእነዚህ የሀገር ሀብት ልዩ ትኩረትና ድጋፍ በመስጠት፣ ከማኅበረሰቡ ተሰሚነት ካላቸው የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በቅንጅት መሥራት ያስፈልጋል።
የሀገር ሰላም እና አንድነት በዘላቂነት ሊረጋገጥ የሚችለው ከውጭ በሚመጡ ፍልስፍናዎች ሳይሆን፣ እንደ አበጋር ካሉ ከኢትዮጵያውያን ሥነ ልቦና፣ እምነትና ነባራዊ አስተሳሰብ ውስጥ ተጨምቀው ከወጡ የውስጥ የሰላም መሣሪያዎች ጋር ማስተሳሰር ሲቻል ነው።
በዮናስ ጌትነት
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ያልተመዘገቡ ዲጂታል ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ መስመር የሚያመጣ የአዋጅ ማሻሻያ ሊደረግ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አሁን ላይ በበይነ መረብ (ዲጂታል) ሚዲያው ዘርፍ የሚታየውን የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ለመግታት፣ ያልተመዘገቡ ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ የምዝገባ ሥርዓት የሚያስገባ የአዋጅ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኃይማኖት ዘለቀ ይህንን የገለጹት፣ “ብቃት ያለው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ የሚዲያ ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዳይሬክተሯ በዚሁ ጊዜ እንዳብራሩት፣ ከአመታት በኋላ በሚዲያው ዘርፍ የተደረገውን ሰፊ ሪፎርም ተከትሎ ድረ-ገጾችን የማፈንና የመዝጋት አሰራር በመቅረቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ጠንካራና ሚዛናዊ የዲጂታል ሚዲያዎች ሊፈጠሩ ችለዋል።
ይሁን እንጂ ይህንን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የሕዝብን አመኔታ ካገኙት ባሻገር፣ የተወሰኑት የዲጅታል ሚዲያዎች የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትና የጋራ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት መበራከታቸውን ዳይሬክተሯ በንግግራቸው አብራርተዋል።
ይህንን አሳሳቢ ተግዳሮት ለመቅረፍም ባለሥልጣኑ በርካታ ተከታዮች እያሏቸው ነገር ግን ሳይመዘገቡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ሚዲያዎችን ሕጋዊ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲሱ አሰራር በፓርላማ ጸድቆ ሲተገበርም፣ ማንኛውም ዲጂታል ሚዲያ በሕጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ ገብቶ ለሀገር ሰላምና ለብሔራዊ ጥቅም በኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚኖርበት አሳስበዋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዓላማ ተቋማትን መቅጣት፣ መዝጋት ወይም መቆጣጠር ብቻ አለመሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ኃይማኖት፣ ተቋሙ ከቁጥጥር ይልቅ በአቅም ግንባታ፣ በምክክር እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል።
በመሆኑም ሕጋዊ ሆነው ለሚመዘገቡ የዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች የጋዜጠኝነት መታወቂያ ከመስጠት ጀምሮ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚያካትቱ የማበረታቻ ሥርዓቶች እንደሚዘረጉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የዘርፉ ባለሙያዎች እርስ በርስ የሚተራረሙበት፣ ለሙያዊ ሥነ-ምግባር መከበር የሚቆምና በሌሎች ሀገራት እንደሚታየው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል ጠንካራ የጋዜጠኞች ማኅበር በማቋቋም በጋራ እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ኢመብባ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #ethiopianmedia #digitalmedia #journalism #mediaregulation #ethiopianews
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አሁን ላይ በበይነ መረብ (ዲጂታል) ሚዲያው ዘርፍ የሚታየውን የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር ስርጭት ለመግታት፣ ያልተመዘገቡ ሚዲያዎችን ወደ ሕጋዊ የምዝገባ ሥርዓት የሚያስገባ የአዋጅ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኃይማኖት ዘለቀ ይህንን የገለጹት፣ “ብቃት ያለው የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ የሚዲያ ኮንፈረንስ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ዳይሬክተሯ በዚሁ ጊዜ እንዳብራሩት፣ ከአመታት በኋላ በሚዲያው ዘርፍ የተደረገውን ሰፊ ሪፎርም ተከትሎ ድረ-ገጾችን የማፈንና የመዝጋት አሰራር በመቅረቱ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ጠንካራና ሚዛናዊ የዲጂታል ሚዲያዎች ሊፈጠሩ ችለዋል።
ይሁን እንጂ ይህንን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው የሕዝብን አመኔታ ካገኙት ባሻገር፣ የተወሰኑት የዲጅታል ሚዲያዎች የሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግር የሚያሰራጩ እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትና የጋራ ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ አካላት መበራከታቸውን ዳይሬክተሯ በንግግራቸው አብራርተዋል።
ይህንን አሳሳቢ ተግዳሮት ለመቅረፍም ባለሥልጣኑ በርካታ ተከታዮች እያሏቸው ነገር ግን ሳይመዘገቡ በዘፈቀደ የሚንቀሳቀሱ ሚዲያዎችን ሕጋዊ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጅ ማሻሻያ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
አዲሱ አሰራር በፓርላማ ጸድቆ ሲተገበርም፣ ማንኛውም ዲጂታል ሚዲያ በሕጋዊ ማዕቀፍ ውስጥ ገብቶ ለሀገር ሰላምና ለብሔራዊ ጥቅም በኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚኖርበት አሳስበዋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዓላማ ተቋማትን መቅጣት፣ መዝጋት ወይም መቆጣጠር ብቻ አለመሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ኃይማኖት፣ ተቋሙ ከቁጥጥር ይልቅ በአቅም ግንባታ፣ በምክክር እና ልዩ ልዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ እንደሚያተኩር ገልጸዋል።
በመሆኑም ሕጋዊ ሆነው ለሚመዘገቡ የዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች የጋዜጠኝነት መታወቂያ ከመስጠት ጀምሮ የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፎችን የሚያካትቱ የማበረታቻ ሥርዓቶች እንደሚዘረጉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የዘርፉ ባለሙያዎች እርስ በርስ የሚተራረሙበት፣ ለሙያዊ ሥነ-ምግባር መከበር የሚቆምና በሌሎች ሀገራት እንደሚታየው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል ጠንካራ የጋዜጠኞች ማኅበር በማቋቋም በጋራ እንዲሰሩ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ኢመብባ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #ethiopianmedia #digitalmedia #journalism #mediaregulation #ethiopianews
1 month ago
ኢትዮጵያን ያላትን የቱሪዝም ጸጋ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማስተዋወቅ የጋዜጠኞች ድርሻ የጎላ መሆኑ ተጠቆመ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ማስተዋወቅ እና የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪዝም ዘርፉን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሞተር ማድረግ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን ግብ ከዳር ለማድረስም መገናኛ ብዙኃን በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ፈጠራ በታከለበትና ማራኪ በሆነ አቀራረብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት፣ አገሪቱ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በተሳለጠ መንገድ ለማስተዋወቅ የሚዲያው ሚና ወደር የለውም ብለዋል።
በቅርቡ የተመሰረተው የቱሪዝም ዘርፍ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ፎረም ዋነኛ ዓላማም ይኸው ገጽታን የመገንባት፣ የማስተዋወቅ እና የሽያጭ ሥራን በተናበበ መልኩ ለመምራት ነው። ሚዲያው የሰዎችን ቀልብ በሚስብ አግባብ መረጃዎችን ሲያቀርብ፣ ሰዎች እንዲጓጉ፣ እንዲመኙ እና የጉዞ ዕቅድ አውጥተው በጀት እንዲመድቡ ከፍተኛ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ እንደገለጹት፣ ማስተዋወቅ የቱሪዝም ስኬት ቁልፍ መሣሪያ ነው። ጎብኚዎች ወደ ስፍራዎቹ መጥተው ማኅበረሰቡ በጥሩ ሁኔታ ሲያስተናግዳቸውና የተደሰቱበትን የጉዞ ልምዳቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያጋሩ የቱሪስቶች ፍሰት በሶስት እና አራት እጥፍ ይጨምራል ብለዋል።
በመላ አገሪቱ ከስምንት መቶ በላይ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች ተለይተው እያንዳንዱ ወረዳ እና ዞን የየራሱን መዳረሻዎች እንዲያለማ አቅጣጫ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን እነዚህን መረጃዎች ከሚኒስቴሩ "ላንድ ኦፍ ኦሪጂን" (Land of Origins)፣ ከ"ማይስ" (MICE)፣ እንዲሁም ከክልል የቱሪዝም ፕላትፎርሞች በተለያዩ ቋንቋዎች በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይሁንና ጋዜጠኞች ጥሬ መረጃዎችን ከማሰራጨት ባለፈ መዳረሻዎቹን በአካል በመጎብኘትና በማጣጣም ስሜትን የሚስቡና ሕያው የሆኑ ዘገባዎችን ለተመልካች ማድረስ እንደሚገባቸው አቶ አለማየሁ በማሳሰብ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
#ethiopia #ethiopiantourism #landoforigins
#miceethiopia
#ethiopia | የኢትዮጵያ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎችን ማስተዋወቅ እና የጎብኚዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪዝም ዘርፉን ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሞተር ማድረግ ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑ ተገለጸ።
ይህንን ግብ ከዳር ለማድረስም መገናኛ ብዙኃን በየአካባቢው የሚገኙ ጸጋዎችን ፈጠራ በታከለበትና ማራኪ በሆነ አቀራረብ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማቅረብ ኃላፊነት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አለማየሁ ጌታቸው እንደገለጹት፣ አገሪቱ ያሏትን እምቅ የቱሪዝም ሀብቶች በተሳለጠ መንገድ ለማስተዋወቅ የሚዲያው ሚና ወደር የለውም ብለዋል።
በቅርቡ የተመሰረተው የቱሪዝም ዘርፍ የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ፎረም ዋነኛ ዓላማም ይኸው ገጽታን የመገንባት፣ የማስተዋወቅ እና የሽያጭ ሥራን በተናበበ መልኩ ለመምራት ነው። ሚዲያው የሰዎችን ቀልብ በሚስብ አግባብ መረጃዎችን ሲያቀርብ፣ ሰዎች እንዲጓጉ፣ እንዲመኙ እና የጉዞ ዕቅድ አውጥተው በጀት እንዲመድቡ ከፍተኛ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል።
አቶ አለማየሁ እንደገለጹት፣ ማስተዋወቅ የቱሪዝም ስኬት ቁልፍ መሣሪያ ነው። ጎብኚዎች ወደ ስፍራዎቹ መጥተው ማኅበረሰቡ በጥሩ ሁኔታ ሲያስተናግዳቸውና የተደሰቱበትን የጉዞ ልምዳቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ሲያጋሩ የቱሪስቶች ፍሰት በሶስት እና አራት እጥፍ ይጨምራል ብለዋል።
በመላ አገሪቱ ከስምንት መቶ በላይ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎች ተለይተው እያንዳንዱ ወረዳ እና ዞን የየራሱን መዳረሻዎች እንዲያለማ አቅጣጫ ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል።
መገናኛ ብዙኃን እነዚህን መረጃዎች ከሚኒስቴሩ "ላንድ ኦፍ ኦሪጂን" (Land of Origins)፣ ከ"ማይስ" (MICE)፣ እንዲሁም ከክልል የቱሪዝም ፕላትፎርሞች በተለያዩ ቋንቋዎች በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይሁንና ጋዜጠኞች ጥሬ መረጃዎችን ከማሰራጨት ባለፈ መዳረሻዎቹን በአካል በመጎብኘትና በማጣጣም ስሜትን የሚስቡና ሕያው የሆኑ ዘገባዎችን ለተመልካች ማድረስ እንደሚገባቸው አቶ አለማየሁ በማሳሰብ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen
#ethiopia #ethiopiantourism #landoforigins
#miceethiopia
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት፤ ከልቀት ማዕከልነት እስከ ዘመናዊ ግብርና እና ዲጂታላይዜሽን
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት እርባታ ጣቢያ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ነው
📌 በአመት እስከ 10 ሚሊዮን ብር ገቢ እያስገኘ ነው
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ የመማር ማስተማር እና የምርምር ስራዎችን ከማህበረሰብ አገልግሎት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩንና የአካባቢውን ነዋሪ እያገዘ እንደሚገኝ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አቸነፍ መላኩ ገለጹ።
ኮሌጁ በስድስት የትምህርት ክፍሎችና በተለያዩ የደረጃ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ከማስተማር ባለፈ፣ በስሩ በሚገኘው ክሊኒክ አማካኝነት ለአካባቢው አርቢዎች የእንስሳት ህክምና፣ የክትባትና የበሽታ መከላከል አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ በዘመናዊ መልክ በተደራጀው የወተት እርባታ ጣቢያው አማካኝነት በቀን ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ ሊትር ወተት በማምረት ጥራቱን የጠበቀ ምርት በቅናሽ ዋጋ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለአካባቢው ነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ በየቀኑ ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ ደንበኞችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የእንስሳት እርባታ ጣቢያ፣ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና በሀኪም የታዘዘላቸው የሆስፒታል ታካሚዎችም በየቀኑ የወተት አቅርቦት እያቀረበ ይገኛል።
የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ አያልሰው ተከስተ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በአካባቢው ገበያ የወተት ዋጋ እስከ ሰማንያ ብር በሚሸጥበት ወቅት ጣቢያው በሀምሳ ብር ዝቅተኛ ዋጋ ለነዋሪው ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ዋጋው ተሻሽሎ በ75 ብር እየቀረበ ይገኛል።
ጣቢያው ከዚህ የወተት ሽያጭ ብቻ በወር እስከ 450 ሺህ ብር ገቢ የሚያገኝ ሲሆን፣ በዚህ አመት ብቻ ከእንስሳት ሽያጭ ካገኘው ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ጋር ተዳምሮ፣ በአጠቃላይ በአመት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል።
የተቋሙ የምርምር ስራዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመኑ መምጣታቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አቸነፍ፣ በተለይም አርሶ አደሩን የወንድ ኮርማዎችን የመጠበቅ ወጪ የሚያድንና የሴት ጥጃዎችን ብቻ የመውለድ እድልን የሚያሰፋ የሰው ሰራሽ ማዳቀል ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ በማህበረሰቡ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ፖሊሲና የምርምር ሰነድ ለዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት የቀረበ ሲሆን፣ ሂደቱን ጨርሶ ለፖሊሲ አውጪዎች እንደሚተላለፍ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት ጣቢያው እስከ መቶ ሀያ የሚደርሱ ላሞችና ለምርምር ስራ የሚውሉ በጎችን የያዘ ሲሆን፣ በቀጣይም በደኑ ውስጥ ያለውን የንብ እርባታ ከማስፋፋት ባለፈ በአሳ እርባታ ዘርፍም ለመሰማራት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #gondaruniversity #communityservice #agriculturalresearch
📌 በአመት እስከ 10 ሚሊዮን ብር ገቢ እያስገኘ ነው
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ የመማር ማስተማር እና የምርምር ስራዎችን ከማህበረሰብ አገልግሎት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩንና የአካባቢውን ነዋሪ እያገዘ እንደሚገኝ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አቸነፍ መላኩ ገለጹ።
ኮሌጁ በስድስት የትምህርት ክፍሎችና በተለያዩ የደረጃ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ከማስተማር ባለፈ፣ በስሩ በሚገኘው ክሊኒክ አማካኝነት ለአካባቢው አርቢዎች የእንስሳት ህክምና፣ የክትባትና የበሽታ መከላከል አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ በዘመናዊ መልክ በተደራጀው የወተት እርባታ ጣቢያው አማካኝነት በቀን ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ ሊትር ወተት በማምረት ጥራቱን የጠበቀ ምርት በቅናሽ ዋጋ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለአካባቢው ነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ በየቀኑ ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ ደንበኞችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የእንስሳት እርባታ ጣቢያ፣ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና በሀኪም የታዘዘላቸው የሆስፒታል ታካሚዎችም በየቀኑ የወተት አቅርቦት እያቀረበ ይገኛል።
የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ አያልሰው ተከስተ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በአካባቢው ገበያ የወተት ዋጋ እስከ ሰማንያ ብር በሚሸጥበት ወቅት ጣቢያው በሀምሳ ብር ዝቅተኛ ዋጋ ለነዋሪው ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ዋጋው ተሻሽሎ በ75 ብር እየቀረበ ይገኛል።
ጣቢያው ከዚህ የወተት ሽያጭ ብቻ በወር እስከ 450 ሺህ ብር ገቢ የሚያገኝ ሲሆን፣ በዚህ አመት ብቻ ከእንስሳት ሽያጭ ካገኘው ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ጋር ተዳምሮ፣ በአጠቃላይ በአመት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል።
የተቋሙ የምርምር ስራዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመኑ መምጣታቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አቸነፍ፣ በተለይም አርሶ አደሩን የወንድ ኮርማዎችን የመጠበቅ ወጪ የሚያድንና የሴት ጥጃዎችን ብቻ የመውለድ እድልን የሚያሰፋ የሰው ሰራሽ ማዳቀል ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ በማህበረሰቡ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ፖሊሲና የምርምር ሰነድ ለዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት የቀረበ ሲሆን፣ ሂደቱን ጨርሶ ለፖሊሲ አውጪዎች እንደሚተላለፍ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት ጣቢያው እስከ መቶ ሀያ የሚደርሱ ላሞችና ለምርምር ስራ የሚውሉ በጎችን የያዘ ሲሆን፣ በቀጣይም በደኑ ውስጥ ያለውን የንብ እርባታ ከማስፋፋት ባለፈ በአሳ እርባታ ዘርፍም ለመሰማራት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #gondaruniversity #communityservice #agriculturalresearch
1 month ago
42ኛው የሻምበል አበበ በቂላ ማራቶን በሐዋሳ ከተማ ተካሄደ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግበት የቆየውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው 42ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ የማራቶን ውድድር በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በዚሁ ታላቅ የስፖርት መድረክ ላይ ከ300 በላይ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 74ቱ ሴቶች እንዲሁም 249ኙ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል።
ውድድሩን ይበልጥ ሳቢ ካደረጉት ሁኔታዎች መካከል 12 ታዋቂ ክለቦች እና 4 ክልሎች በንቃት በመሳተፍ ያሳዩት ብርቱ ፉክክር ዋናው መገለጫ ነበር።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሲዳማ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የቴክኒክና የልኬት ሥራዎችን በጥራት አጠናቆ ለውድድሩ ስኬት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጉን የፌድሬሽኑ ከፍተኛ የውድድር ባለሙያ ገልጸዋል እንደነበር ይታወሳል።
ፌዴሬሽን ለአጠቃላይ ውድድሩ ማከናወኛ የሚሆን 6 ሚሊዮን ብር በጀት የመደበ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 458 ሺህ ብሩ በቀጥታ ለአሸናፊዎች ሽልማት እንዲውል ተደርጓል።
ውድድሩ በወንዶች በሴቶች እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ በሆኑ አንጋፋ አትሌቶች መካከል የተካሄደ ሲሆን በዕለቱ የተመዘገቡት የውድድሩ የመጨረሻ በወንዶች እና ሴቶች መደብ የተመዘገበው ውጤት፦
በወንዶች ማራቶን ፉክክር፦
1ኛ፦ ገመቹ ያደሳ (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)
2ኛ፦ ባንቱ መኮንን (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)
3ኛ፦ አቡ ገለቱ (መቻል ስፖርት ክለብ)
በሴቶች ማራቶን ፉክክር፦
1,አትሌት ጠጅቱ ስዩም (ከመቻል)
2,አትሌት ከረኒ ጀሊሳ (ከኦሮሚያ ፖሊስ)
3,አትሌት ትዕግስት ጌትነት (ከኢትዮ ኤሌክትሪክ)
በዚህም መሠረት በሁለቱም ጾታዎች ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች እንደየደረጃቸው ከ10 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር የሚደርስ ማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በአንጋፋ (ቬትራን - ከ50 ዓመት በላይ) አትሌቶች ዘርፍ፦
1ኛ፦ በቀሉ ረታ
2ኛ፦ ቦጋለ ሰይፉ
3ኛ፦ አሰፋ መገርሳ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ
ያፌት ገ/ህይወት
ከሲዳማ ፤ ሐዋሳ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግበት የቆየውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው 42ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ የማራቶን ውድድር በሲዳማ ክልል ርዕሰ መዲና ሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በዚሁ ታላቅ የስፖርት መድረክ ላይ ከ300 በላይ አትሌቶች የተሳተፉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ 74ቱ ሴቶች እንዲሁም 249ኙ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል።
ውድድሩን ይበልጥ ሳቢ ካደረጉት ሁኔታዎች መካከል 12 ታዋቂ ክለቦች እና 4 ክልሎች በንቃት በመሳተፍ ያሳዩት ብርቱ ፉክክር ዋናው መገለጫ ነበር።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከሲዳማ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር የቴክኒክና የልኬት ሥራዎችን በጥራት አጠናቆ ለውድድሩ ስኬት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጉን የፌድሬሽኑ ከፍተኛ የውድድር ባለሙያ ገልጸዋል እንደነበር ይታወሳል።
ፌዴሬሽን ለአጠቃላይ ውድድሩ ማከናወኛ የሚሆን 6 ሚሊዮን ብር በጀት የመደበ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 458 ሺህ ብሩ በቀጥታ ለአሸናፊዎች ሽልማት እንዲውል ተደርጓል።
ውድድሩ በወንዶች በሴቶች እንዲሁም ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ በሆኑ አንጋፋ አትሌቶች መካከል የተካሄደ ሲሆን በዕለቱ የተመዘገቡት የውድድሩ የመጨረሻ በወንዶች እና ሴቶች መደብ የተመዘገበው ውጤት፦
በወንዶች ማራቶን ፉክክር፦
1ኛ፦ ገመቹ ያደሳ (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)
2ኛ፦ ባንቱ መኮንን (ኢትዮ ኤሌክትሪክ)
3ኛ፦ አቡ ገለቱ (መቻል ስፖርት ክለብ)
በሴቶች ማራቶን ፉክክር፦
1,አትሌት ጠጅቱ ስዩም (ከመቻል)
2,አትሌት ከረኒ ጀሊሳ (ከኦሮሚያ ፖሊስ)
3,አትሌት ትዕግስት ጌትነት (ከኢትዮ ኤሌክትሪክ)
በዚህም መሠረት በሁለቱም ጾታዎች ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ደረጃን ይዘው ላጠናቀቁ አትሌቶች እንደየደረጃቸው ከ10 ሺህ እስከ 50 ሺህ ብር የሚደርስ ማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በአንጋፋ (ቬትራን - ከ50 ዓመት በላይ) አትሌቶች ዘርፍ፦
1ኛ፦ በቀሉ ረታ
2ኛ፦ ቦጋለ ሰይፉ
3ኛ፦ አሰፋ መገርሳ ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።
ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽንስ
ያፌት ገ/ህይወት
ከሲዳማ ፤ ሐዋሳ
1 month ago
ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እውነተኛ የፖለቲካ ድርድር እንዲካሔድ ጠየቀ
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአራት የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመሰረተው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሀገርን አፅንቶ ለማስቀጠል እውነተኛ የፖለቲካ ድርድር እንዲካሄድ ጠይቋል።
የፓርቲዎቹ ስብስብ መንግሥት ወደ እውነተኛ ድርድር እስከሚመጣ ድረስ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።
በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የማይደራደር አቋም እንዳለውም ይፋ አድርጓል።
የትብብሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌትነት ወርቁ ከአሐዱ መድረክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ መንግሥት ምርጫ አሸንፌያለሁ በሚል ባለፉት ዓመታት ይከተለው በነበረው መንገድ የሚቀጥል ከሆነ ሀገርን አደጋ ላይ ይጥላል ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።
ትብብሩ ምርጫው ይደገም የሚል አቋም እንደሌለውም ኃላፊው አብራርተዋል።
"ለተፈጠሩ ችግሮች እልባት ለመስጠት የድርድር ሂደቱን መጀመር ለነገ የማይባል ተግባር ነው" ያሉት አቶ ጌትነት የዲሞክራሲ ሥርዓት ባልዳበረባት ኢትዮጵያ የተፈጠሩ ችግሮች በአንድ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ይፈታሉ የሚል እምነት እንደሌላቸው ጠቁመዋል።
ትብብሩ ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ምላሽ እስከሚያገኙ ድረስ ከሥርዓቱ ጋር የሚያደርገውን ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቋሙን በድጋሚ አስታውቋል።
#አሐዱ
ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአራት የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመሰረተው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ሀገርን አፅንቶ ለማስቀጠል እውነተኛ የፖለቲካ ድርድር እንዲካሄድ ጠይቋል።
የፓርቲዎቹ ስብስብ መንግሥት ወደ እውነተኛ ድርድር እስከሚመጣ ድረስ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።
በሀገር ብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ የማይደራደር አቋም እንዳለውም ይፋ አድርጓል።
የትብብሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌትነት ወርቁ ከአሐዱ መድረክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ መንግሥት ምርጫ አሸንፌያለሁ በሚል ባለፉት ዓመታት ይከተለው በነበረው መንገድ የሚቀጥል ከሆነ ሀገርን አደጋ ላይ ይጥላል ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።
ትብብሩ ምርጫው ይደገም የሚል አቋም እንደሌለውም ኃላፊው አብራርተዋል።
"ለተፈጠሩ ችግሮች እልባት ለመስጠት የድርድር ሂደቱን መጀመር ለነገ የማይባል ተግባር ነው" ያሉት አቶ ጌትነት የዲሞክራሲ ሥርዓት ባልዳበረባት ኢትዮጵያ የተፈጠሩ ችግሮች በአንድ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ይፈታሉ የሚል እምነት እንደሌላቸው ጠቁመዋል።
ትብብሩ ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ምላሽ እስከሚያገኙ ድረስ ከሥርዓቱ ጋር የሚያደርገውን ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቋሙን በድጋሚ አስታውቋል።
#አሐዱ
1 month ago
ኢትዮጵያን የሜዲካል ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የፖሊሲና የፋይናንስ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
#ethiopia | ኢትዮጵያ ያላትን የኤቪዬሽን፣ የከተማ መሠረተ-ልማት እና የኢንቨስትመንት ዕድሎች በመጠቀም በሜዲካል ቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ እምቅ አቅም እንዳላት ቢጠቆምም፤ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግና ሀገሪቱን ቀጣዩ የሕክምና ማዕከል ለማድረግ የመንግስት የፖሊሲ ድጋፍ እንዲሁም የፋይናንስ ተቋማት እገዛ እጅግ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
በኢትዮጵያ ያለውን የህክምና ዘርፍ ክፍተት ለመሙላት እና የውጭ ሀገር ህክምናዎችን በተቀላጠፈ መልኩ ለማመቻቸት ላለፉት 12 ዓመታት ሲሰራ የቆየው ጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል፣ በሀገሪቱ የሜዲካል ቱሪዝምን ለማስፋፋት አዳዲስ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ዶክተር በጋሻው ባይለየኝ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በቴክኖሎጂ፣ በባለሙያ ልምድ እንዲሁም በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማነስ ምክንያት ዜጎች የሚፈልጉትን ሙሉ የህክምና አገልግሎት ማግኘት ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ስቃይና ለህይወት ማለፍ እየተዳረጉ ነው።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ድርጅታቸው እንደ ህንድ፣ ታይላንድ እና ቱርክ ካሉ ሀገራት በተጨማሪ፣ በቅርቡ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አጅማን ከሚገኘው ታዋቂው ቱምቤይ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ጋር አዲስ የትብብር ትስስር ፈጥሯል።
ይህ በተባበሩት አረብ ኢምሬት የሚገኘው ትልቅ የህክምና ተቋም በተለይ በኒውሮ ሳይንስ፣ በአጥንት ህክምና እና በሪሃቢሊቴሽን ዘርፎች ላይ የላቀ ስም ያለው ሲሆን፣ ከጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል ጋር በመተባበር ሁለት ታዋቂ ስፔሻሊስት ዶክተሮቹን ወደ ኢትዮጵያ ልኳል።
እነዚህ የውጭ ሀገር ሃኪሞች በአያት አካባቢ በሚገኘው ኑቢራ የህክምና ማዕከል በመገኘት በህብለሰረሰር እና በአጥንት ህክምና ዙሪያ ለታካሚዎች ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እዚህ ካሉ የሀገር ውስጥ ኒውሮ ሰርጀኖች እና ኦርቶፔዲክ ሰርጀኖች ጋር የልምድ ልውውጥና የስልጠና መርሃ ግብር እያካሄዱ ይገኛሉ።
ጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል ከዚህ ቀደምም ከ50 በላይ ኢትዮጵያውያን ሃኪሞችን ወደ ውጭ ሀገር ልኮ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ማመቻቸቱ ይታወሳል።
ዶክተር በጋሻው እንደሚያምኑት፣ የጤና ሚኒስቴር በሀገሪቱ የሜዲካል ቱሪዝምን ለመገንባት የሚያደርገው ጥረት እጅግ የሚበረታታ ከመሆኑም በላይ እንዲያውም "ዘግይተናል" የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፍ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሰለ የኤቪዬሽን መታደሏ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም በዘርፉ ላይ እየታዩ ያሉ የኢንቨስትመንት ለውጦች ሀገሪቱ በሜዲካል ቱሪዝም እንድታድግ ትልቅ መሰረቶች ናቸው።
ይሁን እንጂ ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የመንግስት የፖሊሲና የስትራቴጂ ድጋፍ እንዲሁም የባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት እገዛ እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ጠቁመው፣ ይህ ከተሳካ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የውጭ ዜጎች ጭምር መጥተው የሚታከሙባትና ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝባት የህክምና ማዕከል መሆን እንደምትችል በልበ ሙሉነት ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ኢትዮጵያ ያላትን የኤቪዬሽን፣ የከተማ መሠረተ-ልማት እና የኢንቨስትመንት ዕድሎች በመጠቀም በሜዲካል ቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ እምቅ አቅም እንዳላት ቢጠቆምም፤ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግና ሀገሪቱን ቀጣዩ የሕክምና ማዕከል ለማድረግ የመንግስት የፖሊሲ ድጋፍ እንዲሁም የፋይናንስ ተቋማት እገዛ እጅግ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
በኢትዮጵያ ያለውን የህክምና ዘርፍ ክፍተት ለመሙላት እና የውጭ ሀገር ህክምናዎችን በተቀላጠፈ መልኩ ለማመቻቸት ላለፉት 12 ዓመታት ሲሰራ የቆየው ጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል፣ በሀገሪቱ የሜዲካል ቱሪዝምን ለማስፋፋት አዳዲስ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል።
የድርጅቱ መስራችና ስራ አስኪያጅ ዶክተር በጋሻው ባይለየኝ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ ውስጥ በቴክኖሎጂ፣ በባለሙያ ልምድ እንዲሁም በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማነስ ምክንያት ዜጎች የሚፈልጉትን ሙሉ የህክምና አገልግሎት ማግኘት ባለመቻላቸው ለከፍተኛ ስቃይና ለህይወት ማለፍ እየተዳረጉ ነው።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ድርጅታቸው እንደ ህንድ፣ ታይላንድ እና ቱርክ ካሉ ሀገራት በተጨማሪ፣ በቅርቡ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አጅማን ከሚገኘው ታዋቂው ቱምቤይ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ጋር አዲስ የትብብር ትስስር ፈጥሯል።
ይህ በተባበሩት አረብ ኢምሬት የሚገኘው ትልቅ የህክምና ተቋም በተለይ በኒውሮ ሳይንስ፣ በአጥንት ህክምና እና በሪሃቢሊቴሽን ዘርፎች ላይ የላቀ ስም ያለው ሲሆን፣ ከጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል ጋር በመተባበር ሁለት ታዋቂ ስፔሻሊስት ዶክተሮቹን ወደ ኢትዮጵያ ልኳል።
እነዚህ የውጭ ሀገር ሃኪሞች በአያት አካባቢ በሚገኘው ኑቢራ የህክምና ማዕከል በመገኘት በህብለሰረሰር እና በአጥንት ህክምና ዙሪያ ለታካሚዎች ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እዚህ ካሉ የሀገር ውስጥ ኒውሮ ሰርጀኖች እና ኦርቶፔዲክ ሰርጀኖች ጋር የልምድ ልውውጥና የስልጠና መርሃ ግብር እያካሄዱ ይገኛሉ።
ጌትዌይ ሜዲካል ትራቭል ከዚህ ቀደምም ከ50 በላይ ኢትዮጵያውያን ሃኪሞችን ወደ ውጭ ሀገር ልኮ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ ማመቻቸቱ ይታወሳል።
ዶክተር በጋሻው እንደሚያምኑት፣ የጤና ሚኒስቴር በሀገሪቱ የሜዲካል ቱሪዝምን ለመገንባት የሚያደርገው ጥረት እጅግ የሚበረታታ ከመሆኑም በላይ እንዲያውም "ዘግይተናል" የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፍ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሰለ የኤቪዬሽን መታደሏ፣ የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም በዘርፉ ላይ እየታዩ ያሉ የኢንቨስትመንት ለውጦች ሀገሪቱ በሜዲካል ቱሪዝም እንድታድግ ትልቅ መሰረቶች ናቸው።
ይሁን እንጂ ዘርፉ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የመንግስት የፖሊሲና የስትራቴጂ ድጋፍ እንዲሁም የባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት እገዛ እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ጠቁመው፣ ይህ ከተሳካ ኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ የውጭ ዜጎች ጭምር መጥተው የሚታከሙባትና ተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝባት የህክምና ማዕከል መሆን እንደምትችል በልበ ሙሉነት ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
Sponsored by
Surafel
Comments