10 days ago
ያለደመወዝ ኢትዮጵያውያንን በማገልገል ላይ የሚገኙት አሜሪካዊቷ የሕፃናት ሕክምና ስፔሻሊስት
#ethiopia | ሕፃኗ ከመወለጃ ጊዜዋ ቀድማ በመወለዷ፣ ኪሎዋ ከሚጠበቀው በታች ሆኗል። ይህም በሕይወት ለመቆየት አስጊ እንደሆነ ይገለጻል። በዚህ ምክንያት የሕፃኗ ቤተሰቦች በጭንቀት ተውጠዋል።
ከዚህ ቀደም መሰል ሕፃናትን ከሞት የታደጉት እነ ዶ/ር ሚሼል፣ የዚህችንም ሕፃን ሕይወት ለማትረፍ ብዙ ለፍተዋል። ደግነቱ የዶ/ር ሚሼልና ባልደረቦቻቸው ልፋት መና አልቀረም፣ ከሳምንታት የልዩ ክትትል ሕክምና በኋላ የሕፃኗ የመኖር ተስፋ ለምልሟል።
ዶ/ር ሚሼል ዬትስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ወላይታ ዞን፣ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል የሕፃናት ሕክምና ክፍል በበጎ ፈቃደኝነት በማገልገል ላይ ያሉ አሜሪካዊት የሕፃናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው። ላለፉት 12 ዓመታት በሆስፒታሉ ያገለገሉት ባለሙያዋ ተሞክሯቸውን አካፍለውናል።
ዶ/ር ሚሼል እንዳጫወቱን፣ 700 ግራም ብቻ ሆና የተወለደችው ሕፃን በሆስፒታሉ በተደረገላት ከፍተኛ ክትትልና እንክብካቤ በቅርቡ ከጨቅላ ሕፃናት ማቆያ (Incubator) ወደ እናቷ እቅፍ የተሸጋገረች ሲሆን፣ በጥሩ ጤንነት ላይ ትገኛለች።
ይህን መሰል የሕክምና ተዓምር ለእነ ዶ/ር ሚሼል የየዕለት ሥራ አካል ነው። የሚገርመው፣ እርሳቸውን ጨምሮ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል የሚያገለግሉ ሁሉም ዓለም አቀፍ ሠራተኞች ለአገልግሎታቸው ከሆስፒታሉም ሆነ ከሀገር ምንም ዓይነት ክፍያ አይቀበሉም።
የዕለት ተዕለት ኑሯቸው የሚደገፈው በትውልድ ሀገራቸው ከሚገኙ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ከአብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች በሚደረግላቸው የገንዘብ ድጋፍ (donation) ነው።
ከሶስት ልጆቻቸው ሁለቱን በኢትዮጵያ የወለዱት አሜሪካዊቷ በጎ ፈቃደኛ ሐኪም፣ በሙያቸው ኢትዮጵያውያንን እያገለገሉ፣ የሕጻናትና እናቶችን ሕይወት ከሞት እየታደጉ ይገኛሉ።
በዶ/ር ሚሼል እና የሙያ አጋሮቻቸው ነፃ የሕክምና አገልግሎት አማካኝነት፣ የመክፈል አቅም የሌላቸው በርካታ ኢትዮጵያውያን ታክመው ድነዋል። ይህን ማየት ሁሉንም ድካም የሚያስረሳ ትልቅ በረከት መሆኑን ዶ/ር ሚሼል በእርካታ ይገልጻሉ።
ከትውልድ ሀገር ርቆ መኖር፣ የቤተሰብ አባል ሲታመም በቅርብ አለመገኘት እንዲሁም በሠርግና ልቅሶ አለመታደም ከባድ ቢሆንም፣ ፈጣሪ ለዚህ አገልግሎት እንደጠራቸውና ፍላጎታቸውን ሁሉ እርሱ እንደሚያሟላላቸው በጽኑ ያምናሉ።
ይህ ዓይነቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሆስፒታሉ ለኅብረተሰቡ የሚያቀርበውን የሕክምና አገልግሎት በተመጣጣኝ ክፍያ ለማቅረብና አቅመ ደካሞችን ለመርዳት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ያሉን የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤፍሬም ገብረሥላሴ ናቸው።
ሆስፒታሉ የላቀ የሕክምና አገልግሎት መስጠት፣ ብቁ የሕክምና ባለሙያዎችን ማፍራት እና ከፍሎ የመታከም አቅም የሌላቸውን ማገዝን ዋነኛ ዓላማዎቹ አድርጎ መነሳቱን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ ዶ/ር ሚሼልን የመሳሰሉ በጎ ሰዎችን በማሰባሰብ እና በየዓመቱ እስከ 40 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ ከመላው ኢትዮጵያ ለሚመጡ የመክፈል አቅም የሌላቸው ታካሚዎች ነጻ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #soddochristianhospital #communityservice #drmichelleyates
#ethiopia | ሕፃኗ ከመወለጃ ጊዜዋ ቀድማ በመወለዷ፣ ኪሎዋ ከሚጠበቀው በታች ሆኗል። ይህም በሕይወት ለመቆየት አስጊ እንደሆነ ይገለጻል። በዚህ ምክንያት የሕፃኗ ቤተሰቦች በጭንቀት ተውጠዋል።
ከዚህ ቀደም መሰል ሕፃናትን ከሞት የታደጉት እነ ዶ/ር ሚሼል፣ የዚህችንም ሕፃን ሕይወት ለማትረፍ ብዙ ለፍተዋል። ደግነቱ የዶ/ር ሚሼልና ባልደረቦቻቸው ልፋት መና አልቀረም፣ ከሳምንታት የልዩ ክትትል ሕክምና በኋላ የሕፃኗ የመኖር ተስፋ ለምልሟል።
ዶ/ር ሚሼል ዬትስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ወላይታ ዞን፣ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል የሕፃናት ሕክምና ክፍል በበጎ ፈቃደኝነት በማገልገል ላይ ያሉ አሜሪካዊት የሕፃናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው። ላለፉት 12 ዓመታት በሆስፒታሉ ያገለገሉት ባለሙያዋ ተሞክሯቸውን አካፍለውናል።
ዶ/ር ሚሼል እንዳጫወቱን፣ 700 ግራም ብቻ ሆና የተወለደችው ሕፃን በሆስፒታሉ በተደረገላት ከፍተኛ ክትትልና እንክብካቤ በቅርቡ ከጨቅላ ሕፃናት ማቆያ (Incubator) ወደ እናቷ እቅፍ የተሸጋገረች ሲሆን፣ በጥሩ ጤንነት ላይ ትገኛለች።
ይህን መሰል የሕክምና ተዓምር ለእነ ዶ/ር ሚሼል የየዕለት ሥራ አካል ነው። የሚገርመው፣ እርሳቸውን ጨምሮ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል የሚያገለግሉ ሁሉም ዓለም አቀፍ ሠራተኞች ለአገልግሎታቸው ከሆስፒታሉም ሆነ ከሀገር ምንም ዓይነት ክፍያ አይቀበሉም።
የዕለት ተዕለት ኑሯቸው የሚደገፈው በትውልድ ሀገራቸው ከሚገኙ ወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ከአብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም ከበጎ አድራጎት ድርጅቶች በሚደረግላቸው የገንዘብ ድጋፍ (donation) ነው።
ከሶስት ልጆቻቸው ሁለቱን በኢትዮጵያ የወለዱት አሜሪካዊቷ በጎ ፈቃደኛ ሐኪም፣ በሙያቸው ኢትዮጵያውያንን እያገለገሉ፣ የሕጻናትና እናቶችን ሕይወት ከሞት እየታደጉ ይገኛሉ።
በዶ/ር ሚሼል እና የሙያ አጋሮቻቸው ነፃ የሕክምና አገልግሎት አማካኝነት፣ የመክፈል አቅም የሌላቸው በርካታ ኢትዮጵያውያን ታክመው ድነዋል። ይህን ማየት ሁሉንም ድካም የሚያስረሳ ትልቅ በረከት መሆኑን ዶ/ር ሚሼል በእርካታ ይገልጻሉ።
ከትውልድ ሀገር ርቆ መኖር፣ የቤተሰብ አባል ሲታመም በቅርብ አለመገኘት እንዲሁም በሠርግና ልቅሶ አለመታደም ከባድ ቢሆንም፣ ፈጣሪ ለዚህ አገልግሎት እንደጠራቸውና ፍላጎታቸውን ሁሉ እርሱ እንደሚያሟላላቸው በጽኑ ያምናሉ።
ይህ ዓይነቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሆስፒታሉ ለኅብረተሰቡ የሚያቀርበውን የሕክምና አገልግሎት በተመጣጣኝ ክፍያ ለማቅረብና አቅመ ደካሞችን ለመርዳት ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ያሉን የሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤፍሬም ገብረሥላሴ ናቸው።
ሆስፒታሉ የላቀ የሕክምና አገልግሎት መስጠት፣ ብቁ የሕክምና ባለሙያዎችን ማፍራት እና ከፍሎ የመታከም አቅም የሌላቸውን ማገዝን ዋነኛ ዓላማዎቹ አድርጎ መነሳቱን ገልጸዋል።
ሆስፒታሉ ዶ/ር ሚሼልን የመሳሰሉ በጎ ሰዎችን በማሰባሰብ እና በየዓመቱ እስከ 40 ሚሊዮን ብር በጀት በመመደብ ከመላው ኢትዮጵያ ለሚመጡ የመክፈል አቅም የሌላቸው ታካሚዎች ነጻ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #soddochristianhospital #communityservice #drmichelleyates
1 month ago
ደም በመለገስ የእናቶችን ሕይወት እንታደግ! — ከቡና ደጋፊዎችና ከኮሌጃችን የቀረበ ጥሪ
#ethiopia | ታላቅ የሰብዓዊነት መርሐ ግብር! ኮሌጃችን ከ"ኳስ ሜዳ እና አካባቢው የቡና ደጋፊዎች መረዳጃ ዕድር" ጋር በመተባበር ልዩ የደም ልገሣ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።
ይህ ልገሣ በተለይ በወሊድ ወቅት ደም ለሚያስፈልጋቸው እናቶቻችን ሕይወት መትረፍ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። አንድ ጠብታ ደም የአንዲት እናትን ሕይወት፣ የአንድን ቤተሰብ ተስፋ ሊያድን ይችላል።
መቼና የት?
ነገ ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም (እሁድ)
ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ
በኮሌጁ ቅጥር ግቢ — ዋናው ሕንጻ መግቢያ
የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊነት በስታዲየም ጩኸት ብቻ አይገደብም፤ እንዲህ ባሉ ወሳኝ የሕይወት አድን ተግባራት ላይም ግንባር ቀደም መሆንን ይጠይቃል።
ነገ ጠዋት ሁላችንም በኮሌጃችን ቅጥር ግቢ በመገኘት ደም በመለገስ ለወገኖቻችን አለኝታነታችንን የምናሳይበት ዕለት ነው። እናቶችን ማዳን ትውልድን ማዳን ነው!
ደምዎን ይለግሱ፣ ሕይወት ይታደጉ!
#getu #blooddonation #ethiopiabunna #savemothers #communityservice #addisababa #humanitarian #lifesaving #ደምልገሣ #እናቶችንእናድን #ኢትዮጵያቡና #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ታላቅ የሰብዓዊነት መርሐ ግብር! ኮሌጃችን ከ"ኳስ ሜዳ እና አካባቢው የቡና ደጋፊዎች መረዳጃ ዕድር" ጋር በመተባበር ልዩ የደም ልገሣ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።
ይህ ልገሣ በተለይ በወሊድ ወቅት ደም ለሚያስፈልጋቸው እናቶቻችን ሕይወት መትረፍ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። አንድ ጠብታ ደም የአንዲት እናትን ሕይወት፣ የአንድን ቤተሰብ ተስፋ ሊያድን ይችላል።
መቼና የት?
ነገ ሚያዚያ 18/2018 ዓ.ም (እሁድ)
ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ
በኮሌጁ ቅጥር ግቢ — ዋናው ሕንጻ መግቢያ
የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊነት በስታዲየም ጩኸት ብቻ አይገደብም፤ እንዲህ ባሉ ወሳኝ የሕይወት አድን ተግባራት ላይም ግንባር ቀደም መሆንን ይጠይቃል።
ነገ ጠዋት ሁላችንም በኮሌጃችን ቅጥር ግቢ በመገኘት ደም በመለገስ ለወገኖቻችን አለኝታነታችንን የምናሳይበት ዕለት ነው። እናቶችን ማዳን ትውልድን ማዳን ነው!
ደምዎን ይለግሱ፣ ሕይወት ይታደጉ!
#getu #blooddonation #ethiopiabunna #savemothers #communityservice #addisababa #humanitarian #lifesaving #ደምልገሣ #እናቶችንእናድን #ኢትዮጵያቡና #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት የማዕድ ማጋራት መርሐግብር ድጋፍ አደረገ
#ethiopia | ዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት የ1447 ዓመተ ሂጅራ የረመዷን ጾምን በማስመልከት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ለሚገኙ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሐግብር በዛሬው ዕለት አከናወነ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አቶ ታፈሰ አመንሲሳ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ከተመሠረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም፣ የቆመለትን ዓላማ ለማሳካት ሰፊ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ድርጅቱ ሥራውን ለማከናወን የውጭ ፈንዶችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም፣ የታሰበው ድጋፍ ባልተገኘበት ወቅት "ዮዳሄ እጃችን ለድጋፍ፣ ልባችን ለፍቅር " በሚል መሪ ቃል መንፈስ አባላቱን በማስተባበር በወረዳው ለሚገኙ ወገኖች የረመዳንን ጾም በማስመልከት የማዕድ መርሐግብር ማከናወኑን ገልጸዋል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደህንነት ገብሩ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ያሳየው የተራድኦ ተግባር የሚመሰገን መሆኑን ገልጸው፤ መሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች የሕዝቡን የአንድነትና የመረዳዳት እሴት እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ለዝግጅቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የድርጅቱ አባላት፣ የወረዳው አመራሮችና በጎ ፈቃደኞች ምስጋና ቀርቧል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደህንነት ገብሩ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ያሳየው የተራድኦ ተግባር የሚመሰገን መሆኑን ገልጸው፤ መሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች የሕዝቡን የአንድነትና የመረዳዳት እሴት እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ለዝግጅቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የድርጅቱ አባላት፣ የወረዳው አመራሮችና በጎ ፈቃደኞች ምስጋና ቀርቧል።
በዕለቱ የማዕድ ማጋራት መርሐግብር ላይ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደህንነት ገብሩ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 1113/2011፣ በምዝገባ ቁጥር 7460 ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ሕጋዊ ሰውነት አግኝቶ መንቀሳቀስ መጀመሩ ይታወቃል።
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#yodahecharity #ramadankareem #iftarsharing #ethiopia #socialimpact #communityservice #charityevent #kirkossubcity #selfreliance
#ethiopia | ዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት የ1447 ዓመተ ሂጅራ የረመዷን ጾምን በማስመልከት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ለሚገኙ ወገኖች የማዕድ ማጋራት መርሐግብር በዛሬው ዕለት አከናወነ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አቶ ታፈሰ አመንሲሳ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ከተመሠረተ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም፣ የቆመለትን ዓላማ ለማሳካት ሰፊ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ድርጅቱ ሥራውን ለማከናወን የውጭ ፈንዶችን ለማግኘት ጥረት ቢያደርግም፣ የታሰበው ድጋፍ ባልተገኘበት ወቅት "ዮዳሄ እጃችን ለድጋፍ፣ ልባችን ለፍቅር " በሚል መሪ ቃል መንፈስ አባላቱን በማስተባበር በወረዳው ለሚገኙ ወገኖች የረመዳንን ጾም በማስመልከት የማዕድ መርሐግብር ማከናወኑን ገልጸዋል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደህንነት ገብሩ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ያሳየው የተራድኦ ተግባር የሚመሰገን መሆኑን ገልጸው፤ መሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች የሕዝቡን የአንድነትና የመረዳዳት እሴት እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ለዝግጅቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የድርጅቱ አባላት፣ የወረዳው አመራሮችና በጎ ፈቃደኞች ምስጋና ቀርቧል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደህንነት ገብሩ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ያሳየው የተራድኦ ተግባር የሚመሰገን መሆኑን ገልጸው፤ መሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች የሕዝቡን የአንድነትና የመረዳዳት እሴት እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ለዝግጅቱ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ የድርጅቱ አባላት፣ የወረዳው አመራሮችና በጎ ፈቃደኞች ምስጋና ቀርቧል።
በዕለቱ የማዕድ ማጋራት መርሐግብር ላይ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደህንነት ገብሩ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የዮዳሄ የበጎ አድራጎት ድርጅት በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 1113/2011፣ በምዝገባ ቁጥር 7460 ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ሕጋዊ ሰውነት አግኝቶ መንቀሳቀስ መጀመሩ ይታወቃል።
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#yodahecharity #ramadankareem #iftarsharing #ethiopia #socialimpact #communityservice #charityevent #kirkossubcity #selfreliance
4 months ago
ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ለ200 የኮሪደር ልማት ባለሙያዎች የእራት ግብዣ አደረገ
#ethiopia | ለከተማችን ፅዳት እና ውበት ቀን ከሌት እየሰሩ ለሚገኙ በቦሌ ብራስ አካባቢ ለተመደቡ የኮሪደር ልማት ሠራተኞች፤ ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቅዳሜ ምሽት (ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም) የራት ግብዣ በማድረግ አብሮነቷን እና ምስጋናዋን ገልጻለች።
የቤተክርስቲያኗ ማህበራዊ አሻራ:
ከዚህ ቀደም በቦሌ ድልድይ አካባቢ ማራኪ መናፈሻዎችን ሰርቶ በማስረከብ አካባቢን አረንጓዴ የማድረግ ስራ የሰራችው ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን፤ አሁንም ማህበራዊ ኃላፊነቷን በመወጣት ከ200 በላይ ለሚሆኑ ባለሙያዎች የራት ግብዣ አድርጋለች።
"ይህንን እንድናደርግ ለረዳን ጌታ ክብር ይሁንለት!"
ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን
#yugocitychurch #communityservice #socialresponsibility #addisababa #corridordevelopment #thankyou
#ethiopia | ለከተማችን ፅዳት እና ውበት ቀን ከሌት እየሰሩ ለሚገኙ በቦሌ ብራስ አካባቢ ለተመደቡ የኮሪደር ልማት ሠራተኞች፤ ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን ቅዳሜ ምሽት (ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም) የራት ግብዣ በማድረግ አብሮነቷን እና ምስጋናዋን ገልጻለች።
የቤተክርስቲያኗ ማህበራዊ አሻራ:
ከዚህ ቀደም በቦሌ ድልድይ አካባቢ ማራኪ መናፈሻዎችን ሰርቶ በማስረከብ አካባቢን አረንጓዴ የማድረግ ስራ የሰራችው ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን፤ አሁንም ማህበራዊ ኃላፊነቷን በመወጣት ከ200 በላይ ለሚሆኑ ባለሙያዎች የራት ግብዣ አድርጋለች።
"ይህንን እንድናደርግ ለረዳን ጌታ ክብር ይሁንለት!"
ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን
#yugocitychurch #communityservice #socialresponsibility #addisababa #corridordevelopment #thankyou
5 months ago
🌳 ቴፒን በጋራ እናልማ
የ"ትንሿ ኢትዮጵያ" ዳግም ውልደትና የልማት ጥሪ
#ethiopia | የታሪክ ድርሳናት እንደሚነግሩን ቴፒ ከተማ በ1911 ዓ.ም የተቆረቆረች፣ የኢትዮጵያ የዘመናዊነት አውራ ጎዳና ቀዳሚ ተጠቃሚ የነበረች ታሪካዊ የንግድ ማዕከል ናት። ገና በ1960ዎቹ የአውሮፕላን ትራንስፖርት፣ በ1966 የጤና ጣቢያና የጠጠር መንገድ የነበራት ቴፒ፤ ዛሬም ያንን ገናና ታሪኳን አድሳ ወደ ከፍታ ለመመለስ ቆርጣ ተነስታለች።
🇪🇹 ቴፒ፦ የብዝሃነትና የተፈጥሮ ዕንቁ
አረንጓዴ ካባ የደረበችው ቴፒ፣ "ትንሿ ኢትዮጵያ" ተብላ ትጠራለች። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በፍቅርና በመከባበር የሚኖሩባት፣ የቡናና የቅመማ ቅመም ምርቷን ለዓለም ገበያ የምታቀርብ የኢኮኖሚ ምሰሶ ናት።
🚧 የልማት እንቅፋትና አዲስ ተስፋ
ከተማዋ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ምርት የምታቀርብ ብትሆንም፣ የዘመናዊ መንገድ መሠረተ ልማት እጥረት ትልቅ ፈተና ሆኖባት ቆይቷል። ይህንን ችግር ለመፍታት፦
ከሚዛን፣ ከማሻ-ጎሬ እና ከሽሽንዳ የሚመጡ ዋና ዋና መንገዶች በፍጥነት እየተገነቡ ይገኛሉ።
ነገር ግን፦
የከተማዋ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች የሁላችንንም እገዛ ይሻሉ።
🤝 የ"ህብረት" ጥሪ ለቴፒ ልጆችና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ!
የቴፒ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ነባራዊ እድገትና ቀደምት ስልጣኔ ባገናዘበ መልኩ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በራስ አቅም ለመገንባት ፕሮጀክት ነድፎ ወደ ተግባር ገብቷል።
በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ የቴፒ ተወላጆች፣ ወዳጆችና የልማት አጋሮች በሙሉ፦ "ዘንድሮ የምትሞሸረውን ቴፒን በጋራ እናስውብ!" ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
💰 የልማት ተሳትፎዎን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያድርጉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000731791558
የአካውንቱ ስም፦ ቴፒ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ አስፓልት ግንባታ
💡 መፈክራችን፦ "በኅብረት ሁሉን እንችላለን!!"
የከተማችን መልማት የሀገራችን ብልፅግና መሠረት ነው። ዛሬ ለቴፒ የምናደርገው ድጋፍ ለነገው ትውልድ የምናስቀምጠው ትልቅ አሻራ ነው።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር፤
በመምህር ኃይማኖት ተስፋዬ እና
በናትናኤል ዳኜ በኩል የተላለፈ መልዕክት
#tepi #ethiopia #development #communityservice #infrastructure #coffeeland #unityindiversity #ethiopiaprogress #tepicity
የ"ትንሿ ኢትዮጵያ" ዳግም ውልደትና የልማት ጥሪ
#ethiopia | የታሪክ ድርሳናት እንደሚነግሩን ቴፒ ከተማ በ1911 ዓ.ም የተቆረቆረች፣ የኢትዮጵያ የዘመናዊነት አውራ ጎዳና ቀዳሚ ተጠቃሚ የነበረች ታሪካዊ የንግድ ማዕከል ናት። ገና በ1960ዎቹ የአውሮፕላን ትራንስፖርት፣ በ1966 የጤና ጣቢያና የጠጠር መንገድ የነበራት ቴፒ፤ ዛሬም ያንን ገናና ታሪኳን አድሳ ወደ ከፍታ ለመመለስ ቆርጣ ተነስታለች።
🇪🇹 ቴፒ፦ የብዝሃነትና የተፈጥሮ ዕንቁ
አረንጓዴ ካባ የደረበችው ቴፒ፣ "ትንሿ ኢትዮጵያ" ተብላ ትጠራለች። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በፍቅርና በመከባበር የሚኖሩባት፣ የቡናና የቅመማ ቅመም ምርቷን ለዓለም ገበያ የምታቀርብ የኢኮኖሚ ምሰሶ ናት።
🚧 የልማት እንቅፋትና አዲስ ተስፋ
ከተማዋ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ምርት የምታቀርብ ብትሆንም፣ የዘመናዊ መንገድ መሠረተ ልማት እጥረት ትልቅ ፈተና ሆኖባት ቆይቷል። ይህንን ችግር ለመፍታት፦
ከሚዛን፣ ከማሻ-ጎሬ እና ከሽሽንዳ የሚመጡ ዋና ዋና መንገዶች በፍጥነት እየተገነቡ ይገኛሉ።
ነገር ግን፦
የከተማዋ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች የሁላችንንም እገዛ ይሻሉ።
🤝 የ"ህብረት" ጥሪ ለቴፒ ልጆችና ለኢትዮጵያውያን በሙሉ!
የቴፒ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ነባራዊ እድገትና ቀደምት ስልጣኔ ባገናዘበ መልኩ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችን በራስ አቅም ለመገንባት ፕሮጀክት ነድፎ ወደ ተግባር ገብቷል።
በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ የቴፒ ተወላጆች፣ ወዳጆችና የልማት አጋሮች በሙሉ፦ "ዘንድሮ የምትሞሸረውን ቴፒን በጋራ እናስውብ!" ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
💰 የልማት ተሳትፎዎን በሚከተለው የባንክ አካውንት ያድርጉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000731791558
የአካውንቱ ስም፦ ቴፒ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎ አስፓልት ግንባታ
💡 መፈክራችን፦ "በኅብረት ሁሉን እንችላለን!!"
የከተማችን መልማት የሀገራችን ብልፅግና መሠረት ነው። ዛሬ ለቴፒ የምናደርገው ድጋፍ ለነገው ትውልድ የምናስቀምጠው ትልቅ አሻራ ነው።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር፤
በመምህር ኃይማኖት ተስፋዬ እና
በናትናኤል ዳኜ በኩል የተላለፈ መልዕክት
#tepi #ethiopia #development #communityservice #infrastructure #coffeeland #unityindiversity #ethiopiaprogress #tepicity
Sponsored by
Surafel