2 hours ago
ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
12 days ago
ድንጋይ አቅልጣ ዶላር የምታድነው ኢትዮጵያ፤ የሴራሚክ ምርት ከውጭ ጥገኝነት ወደ ሉዓላዊ አቅም
#የኢንዱስትሪ_ሽግግር #ኢትዮጵያ_ታምርት #ceramicindustry #madeinethiopia #importsubstitution
13 days ago
የማዕድን ዘርፍ እና አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
17 days ago
አሉታዊ ትርክቶችን የተሻገረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአምስቱ ምሰሶዎች ስኬት
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
27 days ago
ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ ምሉዕ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን በሁሉም መስክ አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ደግሞ የዚህ መርኃችን ዋነኛ ዓምድ ነው።
#ኢትዮጵያታምርት #madeinethiopia #ethiopiatamrit #economicsovereignty #ethiopiandevelopment #manufacturing #industrialrevolution #homegrowneconomy
Sponsored by
Surafel
28 days ago
በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ስምምነት ተፈጽሟል - አቶ መላኩ አለበል
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በ4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ስምምነት ተፈጽሟል አሉ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ለ6 ቀናት ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
አቶ መላኩ አለበል ማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በኤክስፖው ከ350 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈዋል።
162 ሺህ 154 ሰዎች በጎበኙት ኤክስፖ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ 20 ስታርት አፖች የፈጠራ ስራቸውን ለጎብኝዎች አቅርበዋል ብለዋል።
አዳዲስ ፈጠራ የተጨመረባቸው የምርት ልማት ውድድሮች በ22 ኢንዱስትሪዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን፤ በምግብ ቅምሻ 10 ድርጅቶች ከተለያዩ ግብዓቶች ያመረቷቸውን ምርቶች በተሳታፊዎች ማስመረጣቸውን ገልጸዋል።
ከ12 ሺህ በላይ የግብይት ትስስሮች በአምራቾች መካከል መፈጸማቸው የኤክስፖው ስኬት እንደነበረ አመልክተዋል።
በተጨማሪም ከ57 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን፣ በ7 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዓለም አቀፍ ሴሚናሮች መካሄዳቸውን እና የመንግሥትን ፖሊሲ ለግሉ ዘርፍ ትርጉም ባለው መልኩ ማስተዋወቅ መቻሉን አብራርተዋል።
በለይኩን ዓለም
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በ4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ57 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ስምምነት ተፈጽሟል አሉ፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ለ6 ቀናት ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡
አቶ መላኩ አለበል ማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በኤክስፖው ከ350 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተሳትፈዋል።
162 ሺህ 154 ሰዎች በጎበኙት ኤክስፖ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ 20 ስታርት አፖች የፈጠራ ስራቸውን ለጎብኝዎች አቅርበዋል ብለዋል።
አዳዲስ ፈጠራ የተጨመረባቸው የምርት ልማት ውድድሮች በ22 ኢንዱስትሪዎች ለእይታ የቀረቡ ሲሆን፤ በምግብ ቅምሻ 10 ድርጅቶች ከተለያዩ ግብዓቶች ያመረቷቸውን ምርቶች በተሳታፊዎች ማስመረጣቸውን ገልጸዋል።
ከ12 ሺህ በላይ የግብይት ትስስሮች በአምራቾች መካከል መፈጸማቸው የኤክስፖው ስኬት እንደነበረ አመልክተዋል።
በተጨማሪም ከ57 ቢሊየን ብር በላይ የገበያ ስምምነት መፈጸሙን፣ በ7 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዓለም አቀፍ ሴሚናሮች መካሄዳቸውን እና የመንግሥትን ፖሊሲ ለግሉ ዘርፍ ትርጉም ባለው መልኩ ማስተዋወቅ መቻሉን አብራርተዋል።
በለይኩን ዓለም
29 days ago
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ…
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2014 ዓ.ም “ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” ከመጀመሩ በፊት እንደ ሀገር ኢንዱስትሪዎች በዓይነትም ሆነ በቁጥር አነስተኛ ነበሩ አሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ የተከፈተው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በድምቀት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል።
ተኪ ምርቶችን በዓይነት፣ በጥራትና በብዛት ማምረት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ የዘርፉን አቅም መገንባት የዘመኑ አርበኝነት ተደርጎ ይወሰዳልና ሁነቱ በዘንድሮው የአርበኞች በዓል ላይ ማረፉ ታሪካዊ ግጥምጥሞሽ ሆኗል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት÷ ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በፊት እንደ ሀገር የነበሩት ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ ነበሩ።
የነበሩት ኢንዱስትሪዎችም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በምርት ሂደት መስተጓጎላቸው እና በሰሜኑ ጦርነት የጥቃት ኢላማ መሆናቸው ትልቅ ጫና እንደነበር አንስተዋል።
ከዚያ መንገድ ለመውጣት እና አዲስ መንገድ ለመከተል የ“ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” መጀመሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሚያግዝ ሰነድ ቀርቦ ውይይት በመደረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ድጋፍ ማግኘቱን አመልክተዋል።
በዚህም በንቅናቄው "በኢትዮጵያ ዲዛይን ተደርገው፣ በኢትዮጵያ ተመርተው እና ተገጣጥመው ለሥራ የቀረቡ ማሽኖችን ወደምናይበት ምዕራፍ ተሸጋግረናል" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇
https://www.youtube.com/wa...
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2014 ዓ.ም “ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” ከመጀመሩ በፊት እንደ ሀገር ኢንዱስትሪዎች በዓይነትም ሆነ በቁጥር አነስተኛ ነበሩ አሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሚያዚያ 25 "ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ የተከፈተው 4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በድምቀት ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል።
ተኪ ምርቶችን በዓይነት፣ በጥራትና በብዛት ማምረት የውጭ ምንዛሪ ወጪን ከማስቀረት ባለፈ የዘርፉን አቅም መገንባት የዘመኑ አርበኝነት ተደርጎ ይወሰዳልና ሁነቱ በዘንድሮው የአርበኞች በዓል ላይ ማረፉ ታሪካዊ ግጥምጥሞሽ ሆኗል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንዳሉት÷ ከኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በፊት እንደ ሀገር የነበሩት ኢንዱስትሪዎች አነስተኛ ነበሩ።
የነበሩት ኢንዱስትሪዎችም በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት በምርት ሂደት መስተጓጎላቸው እና በሰሜኑ ጦርነት የጥቃት ኢላማ መሆናቸው ትልቅ ጫና እንደነበር አንስተዋል።
ከዚያ መንገድ ለመውጣት እና አዲስ መንገድ ለመከተል የ“ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ” መጀመሩን ያስታወሱት ሚኒስትሩ÷ የኢትዮጵያን አምራች ኢንዱስትሪ ተግዳሮቶች ለመፍታት የሚያግዝ ሰነድ ቀርቦ ውይይት በመደረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ድጋፍ ማግኘቱን አመልክተዋል።
በዚህም በንቅናቄው "በኢትዮጵያ ዲዛይን ተደርገው፣ በኢትዮጵያ ተመርተው እና ተገጣጥመው ለሥራ የቀረቡ ማሽኖችን ወደምናይበት ምዕራፍ ተሸጋግረናል" ብለዋል።
ሚኒስትሩ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ👇
https://www.youtube.com/wa...
29 days ago
ከመሸመት ወደ ማምረት፡ የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ስኬቶች
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢኮኖሚ መዋቅሯን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር ግዙፍና ታሪካዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።
ይህ የሽግግር ጉዞ የሀገራችንን የብልጽግና ራዕይ ከማሳካት ባለፈ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና ራስን ለመቻል እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ተወስዷል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረትና ተግባራዊ የተደረጉት አዳዲስ ፖሊሲዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ከነበረበት የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ ወጥቶ ወደ ተሻለ የማምረት አቅም እንዲሸጋገር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገት ቀደም ሲል ከነበረበት 4.8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 10.7 በመቶ በመመንጠቅ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።
ሙሉ ዘገባውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ebc
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢኮኖሚ መዋቅሯን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር ግዙፍና ታሪካዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።
ይህ የሽግግር ጉዞ የሀገራችንን የብልጽግና ራዕይ ከማሳካት ባለፈ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና ራስን ለመቻል እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ተወስዷል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረትና ተግባራዊ የተደረጉት አዳዲስ ፖሊሲዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ከነበረበት የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ ወጥቶ ወደ ተሻለ የማምረት አቅም እንዲሸጋገር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገት ቀደም ሲል ከነበረበት 4.8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 10.7 በመቶ በመመንጠቅ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።
ሙሉ ዘገባውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ebc
29 days ago
የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እስከ ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።
#ኢትዮጵያ_ታምርት #ለሁለንተናዊ_ሉዓላዊነት #እኛም_እንሸምት
http://linktr.ee/fdremoi
Location: https://maps.app.goo.gl/nb...
30 days ago
u12e8u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d) u12aeu1235u1273u122b u1295u130du130du122d...u12a5u12e8u1208u1218u1291 u1209u12d3u120bu12cau1290u1275 u12e8u1208u121d...u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1273u121du122du1275 |MadeinEthiopia |u12e8u1200u1308u122du1309u12f3u12ed
#pmabiyahemedali #ethiopia #manufacturing #industry #development ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኮስታራ ንግግር...እየለመኑ ሉዓላዊነት የለም...ኢትዮጵያ ታምርት |MadeinEthiopia |የሀገርጉዳይ
#pmabiyahemedali #ethiopia #manufacturing #industry #development
1 month ago
በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ የዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ
በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው መርሃ-ግብር ወቅት የሚቆይ የተሽከርካሪዎች ዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተከፈተውና ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየው ብሔራዊ ኤክስፖ በርካታ አምራቾችንና የኢንዱስትሪ ተቋማትን እያሳተፈ ይገኛል።
በሀገር ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም ዘርፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየውና የሦስት መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ባለቤት የሆነው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው ላይ ከ13 በላይ የተለያዩ የተሽከርካሪ ሞዴሎችን ይዞ መቅረቡን የድርጅቱ ተወካዮች ገልጸዋል።
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በገበያው ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሱትን የውሊንግ (Wuling) ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ለቤተሰብ፣ ለታክሲ አገልግሎት፣ ለድርጅቶች ሰርቪስ እንዲሁም ለጭነትና ለካርጎ አገልግሎት የሚውሉ ፒክአፖችንና ቫኖችን ማቅረቡን አስታውቋል።
የሽያጭ ሂደቱንና የተጠቃሚዎችን አቅም በተመለከተ ከድርጅቱ ተወካዮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች ክፍያውን በጥሬ ገንዘብ (ካሽ) መፈጸም የሚችሉ ሲሆን፣ በተለዋጭ አማራጭ ደግሞ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ30% እስከ 50% የሚሆነውን ቅድመ ክፍያ በመክፈል ተሽከርካሪዎቹን በብድር መውሰድ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል።
በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው መርሃ-ግብር ወቅት የሚቆይ የተሽከርካሪዎች ዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተከፈተውና ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየው ብሔራዊ ኤክስፖ በርካታ አምራቾችንና የኢንዱስትሪ ተቋማትን እያሳተፈ ይገኛል።
በሀገር ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም ዘርፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየውና የሦስት መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ባለቤት የሆነው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው ላይ ከ13 በላይ የተለያዩ የተሽከርካሪ ሞዴሎችን ይዞ መቅረቡን የድርጅቱ ተወካዮች ገልጸዋል።
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በገበያው ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሱትን የውሊንግ (Wuling) ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ለቤተሰብ፣ ለታክሲ አገልግሎት፣ ለድርጅቶች ሰርቪስ እንዲሁም ለጭነትና ለካርጎ አገልግሎት የሚውሉ ፒክአፖችንና ቫኖችን ማቅረቡን አስታውቋል።
የሽያጭ ሂደቱንና የተጠቃሚዎችን አቅም በተመለከተ ከድርጅቱ ተወካዮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች ክፍያውን በጥሬ ገንዘብ (ካሽ) መፈጸም የሚችሉ ሲሆን፣ በተለዋጭ አማራጭ ደግሞ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ30% እስከ 50% የሚሆነውን ቅድመ ክፍያ በመክፈል ተሽከርካሪዎቹን በብድር መውሰድ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል።
1 month ago
ዲኬ ሆልዲንግስ የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬን እያዳነ መሆኑን ገለጸ
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
#fastmereja I በአራተኛው ዙር "የኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ የተሳተፈው ዲኬ ሆልዲንግስ (DK Holdings)፣ ትራክተሮችንና የግብርና መሣሪያዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የውጭ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ መተካት መቻሉን አስታወቀ። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት ምርቶቹን እስከ 70 በመቶ የሚደርስ የሀገር ውስጥ ግብዓት በመጠቀም እያመረተ ይገኛል።
የኩባንያው ተወካይ አቶ ታረቀኝ ይልማ ለፋስት መረጃ እንደገለጹት፣ ድርጅቱ በግብርናው ዘርፍ ያለውን የቴክኖሎጂ ክፍተት ለመሙላት ሚዛን አማን ላይ ግዙፍ የትራክተር ማምረቻ ፋብሪካ እየገነባ ነው። ከትራክተር ባሻገር እንደ ማረሻ፣ መከትከቻ፣ የበቆሎ መፈልፈያ እና መውቂያ ያሉ የግብርና መሣሪያዎችን በሀገር ውስጥ ባለሙያዎችና ማሽነሪዎች እያመረተ ለገበሬው እያቀረበ ይገኛል።
ኩባንያው የኤሌክትሪክ ፍጆታን የሚቆጥቡና የክልሎችን ባህላዊ እሴት የሚያንፀባርቁ "ስማርት ፖሎችን" (ዘመናዊ የጎዳና መብራት ምሶሶዎች) በማምረት በጎንደር፣ በሚዛንና በቢሾፍቱ ከተሞች ተግባራዊ አድርጓል።
ቀደም ሲል 100 ፐርሰንት ከውጭ ይገቡ የነበሩ ትራንስፎርመሮችን የሀገሪቱን የጥራት ደረጃ በጠበቀ መልኩ በሀገር ውስጥ እያመረተ ነው። ለከተማ ውበትና ለጽዳት አገልግሎት የሚውሉ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ጋንዳዎችን በስፋት እያቀረበ ይገኛል።
ዲኬ ሆልዲንግስ እነዚህን ምርቶች በሀገር ውስጥ ማምረቱ በከፍተኛ ዶላር ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንና በቀጣይም የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የመገጣጠም እና የመተከል ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
1 month ago
በተለዋዋጩ የዓለም ሁኔታ ውስጥ የጸናች ሀገር ለመገንባት …
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በተለዋዋጭና ውስብስብ ዓለም አቀፋዊ አውድ ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ለአንድ ሀገር የምርት ብቻ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከጥሬ እቃ አቅርቦት፣ ከገበያ ሰንሰለት፣ ከደንበኛ የተለጠጠ ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ክስተቶች አንጻር ዓለም ተለዋዋጭነት ይበዛበታል፡፡
ታዲያ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጸንቶ መቆም፣ ችግሮችን ተቋቁሞ መቀጠል እና ሀገር በፈተና እንዳትናወጥ ማድረግ የሚችል አምራች ኢንዱስትሪ መገንባት ለአንድ ሀገር እጅግ አስፈላጊ እና የጥንካሬ መመዘኛም ነው።
ይህንን መሰረት በማድረግ መንግሥት የሀገር ውስጥ ምርታማነትን ለማሳደግ ከሚሰራባቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መካከል አንዱ አምራች ኢንዱስትሪ ነው።
ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግም “የኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ መተግበር ከጀመረ ውሎ አድሯል።
ንቅናቄው የኢንዱስትሪውን እንቅስቃሴ ከማፋጠን ባለፈ ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለምታደርገውን ጉዞ እውን መሆን የጎላ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች ይገጥሟቸው የነበሩ ችግሮችን በመፍታት የማምረት አቅማቸው እንዲጎለብት ከማድረግ በተጨማሪ በርካታ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ አስችሏል።
ንቅናቄው መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመፍታትና የአምራች ዘርፉን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ሀገራዊ ብልጽግናን በተግባር እያረጋገጠ ሲሆን፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተደረገ የተቀናጀ ጥረት፣ በዘርፉ የታየው ዕድገትና የተመዘገቡት ስኬቶች ለዚህ ማሳያ ናቸው።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የ100 ቀናት ግምገማ እና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከለውጡ ወዲህ ቁልፍ ውጤት ተገኝቶበታል።
ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት የዘርፎችን ድርሻ በተመለከተ የኢንዱስትሪው ዘርፍ በ2010 ዓ.ም 27 በመቶ ድርሻ የነበረው ሲሆን በ2017 ዓ.ም ወደ 30 በመቶ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት፣ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ማስገኘት፣ የሥራ እድል መፍጠር እና ሌሎችም ዐበይት ዓላማዎች የሰነቀ ሲሆን ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና ገበያን በማረጋጋት ረገድም ሚናው ከፍተኛ ነው።
በብርሃኑ አበራ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በተለዋዋጭና ውስብስብ ዓለም አቀፋዊ አውድ ውስጥ አምራች ኢንዱስትሪ ለአንድ ሀገር የምርት ብቻ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከጥሬ እቃ አቅርቦት፣ ከገበያ ሰንሰለት፣ ከደንበኛ የተለጠጠ ፍላጎት እንዲሁም ከዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ክስተቶች አንጻር ዓለም ተለዋዋጭነት ይበዛበታል፡፡
ታዲያ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ጸንቶ መቆም፣ ችግሮችን ተቋቁሞ መቀጠል እና ሀገር በፈተና እንዳትናወጥ ማድረግ የሚችል አምራች ኢንዱስትሪ መገንባት ለአንድ ሀገር እጅግ አስፈላጊ እና የጥንካሬ መመዘኛም ነው።
ይህንን መሰረት በማድረግ መንግሥት የሀገር ውስጥ ምርታማነትን ለማሳደግ ከሚሰራባቸው ዘርፈ ብዙ ሥራዎች መካከል አንዱ አምራች ኢንዱስትሪ ነው።
ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግም “የኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ መተግበር ከጀመረ ውሎ አድሯል።
ንቅናቄው የኢንዱስትሪውን እንቅስቃሴ ከማፋጠን ባለፈ ኢትዮጵያ ወደ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ለምታደርገውን ጉዞ እውን መሆን የጎላ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች ይገጥሟቸው የነበሩ ችግሮችን በመፍታት የማምረት አቅማቸው እንዲጎለብት ከማድረግ በተጨማሪ በርካታ አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ አስችሏል።
ንቅናቄው መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመፍታትና የአምራች ዘርፉን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ሀገራዊ ብልጽግናን በተግባር እያረጋገጠ ሲሆን፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተደረገ የተቀናጀ ጥረት፣ በዘርፉ የታየው ዕድገትና የተመዘገቡት ስኬቶች ለዚህ ማሳያ ናቸው።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) የ2018 በጀት ዓመት የ100 ቀናት ግምገማ እና የ9 ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከለውጡ ወዲህ ቁልፍ ውጤት ተገኝቶበታል።
ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት የዘርፎችን ድርሻ በተመለከተ የኢንዱስትሪው ዘርፍ በ2010 ዓ.ም 27 በመቶ ድርሻ የነበረው ሲሆን በ2017 ዓ.ም ወደ 30 በመቶ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት፣ የውጭ ምንዛሪ ገቢ ማስገኘት፣ የሥራ እድል መፍጠር እና ሌሎችም ዐበይት ዓላማዎች የሰነቀ ሲሆን ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና ገበያን በማረጋጋት ረገድም ሚናው ከፍተኛ ነው።
በብርሃኑ አበራ
1 month ago
ኢትዮጵያን ወደ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት የሚቀይረው አዲሱ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር
********************
ኢትዮጵያ ከተፈጥሮ ያገኘችውን የማዕድን ሀብት በጥሬው ወደ ውጭ ከመላክ ባለፈ፣ እሴት ጨምሮ ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት በማዋል ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፈች ትገኛለች።
ከሪፎርሙ በፊት ዘርፉ ለሀገራዊ ምርት ያለው አስተዋጽኦ ከአንድ በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ማዕድንን የኢኮኖሚው ዋነኛ ምሰሶ በማድረግ የኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት እንዲሆን ተደርጓል።
ይህም በየዓመቱ ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያና ለብረት ግብዓቶች ግዢ የሚወጣውን ከ8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አለው።
በተለይም በብረት ማዕድን ዘርፍ ከ1.1 ቢሊዮን ቶን በላይ ክምችት ላይ በመመስረት በዓመት ሦስት ሚሊዮን ቶን ብረት በሀገር ውስጥ ለማምረት ሰፊ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
በወርቅ ምርት ዘርፍም ቢሆን ከ2010 እስከ 2017 ባሉት ዓመታት ውስጥ የ1241.4 በመቶ ከፍተኛ የኤክስፖርት ዕድገት መመዝገቡ የሪፎርሙን ውጤታማነት በተጨባጭ ያሳያል። በተጨማሪም በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አማካኝነት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት ተችሏል።
ይህ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር ኢትዮጵያ ከውጭ ጥገኝነት እንድትላቀቅና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነቷን በጽኑ መሠረት ላይ እንድታቆም እያደረገው ያለውን ዘርፈ ብዙ ለውጥ በዝርዝር ለማንበብ ድረ ገጻችንን ይጎብኙ።
#ethiopia #mining #industry #economicsovereignty #ethiopiatamirt #mineralreform #investment
********************
ኢትዮጵያ ከተፈጥሮ ያገኘችውን የማዕድን ሀብት በጥሬው ወደ ውጭ ከመላክ ባለፈ፣ እሴት ጨምሮ ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት በማዋል ረገድ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፈች ትገኛለች።
ከሪፎርሙ በፊት ዘርፉ ለሀገራዊ ምርት ያለው አስተዋጽኦ ከአንድ በመቶ በታች የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ማዕድንን የኢኮኖሚው ዋነኛ ምሰሶ በማድረግ የኢንዱስትሪ ሽግግር መሠረት እንዲሆን ተደርጓል።
ይህም በየዓመቱ ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያና ለብረት ግብዓቶች ግዢ የሚወጣውን ከ8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አለው።
በተለይም በብረት ማዕድን ዘርፍ ከ1.1 ቢሊዮን ቶን በላይ ክምችት ላይ በመመስረት በዓመት ሦስት ሚሊዮን ቶን ብረት በሀገር ውስጥ ለማምረት ሰፊ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
በወርቅ ምርት ዘርፍም ቢሆን ከ2010 እስከ 2017 ባሉት ዓመታት ውስጥ የ1241.4 በመቶ ከፍተኛ የኤክስፖርት ዕድገት መመዝገቡ የሪፎርሙን ውጤታማነት በተጨባጭ ያሳያል። በተጨማሪም በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አማካኝነት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት ተችሏል።
ይህ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር ኢትዮጵያ ከውጭ ጥገኝነት እንድትላቀቅና ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነቷን በጽኑ መሠረት ላይ እንድታቆም እያደረገው ያለውን ዘርፈ ብዙ ለውጥ በዝርዝር ለማንበብ ድረ ገጻችንን ይጎብኙ።
#ethiopia #mining #industry #economicsovereignty #ethiopiatamirt #mineralreform #investment
1 month ago
ኢትዮ ቴሌኮም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማሳደግና የገበያ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራረመ
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኢትዮ ቴሌኮም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማሳደግና የገበያ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራረመ
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ትላንት ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በተከፈተው አራተኛው "ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ባለፉት አራት ዓመታት የገቢ ምርትን በአገር ውስጥ ለመተካት በተደረገው ጥረት 14.5 ቢሊዮን ዶላር ማዳን መቻሉን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፣ መንግስታቸው በውጭ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ በወሰደው ጠንካራ እርምጃ በአማካይ በዓመት 3.5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ ወጪ መቀነስ ተችሏል። በተጨማሪም ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ ወደ 1,000 የሚጠጉ ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ስራ መመለሳቸውን እንደ ትልቅ ስኬት አንስተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሀገሪቱ የንግድ ሚዛን አሁንም ከፍተኛ ጉድለት ያለበት መሆኑን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የገቢ ምርት ወጪ 17 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት የተመዘገበው ከፍተኛው የኤክስፖርት ገቢ ግን 8.3 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። ይህም ዓመታዊ የንግድ ሚዛን ጉድለቱ ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን ያሳያል።
በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ለኤክስፖርት ገቢ ያለው ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑ ተመልክቷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከጥቂት ወራት በፊት ለፓርላማ እንደገለጹት፣ ዘርፉ ለማሽነሪዎችና ለግብዓቶች ከባንኮች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ቢያገኝም፣ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያስመዘገበው የኤክስፖርት ገቢ 97 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው።
ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ሀገሪቱ በምግብ እና በኢንዱስትሪ ምርቶች ራሷን ለመቻል በምታደርገው ጥረት ላይ ያላትን ተስፋ የሚያሳይ ቢሆንም፣ ዘርፉ ከውጭ ምንዛሬ ተጠቃሚነት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ አስገኝነቱን እንዲያሳድግ ከፍተኛ ስራ እንደሚጠበቅበት የዘርፉ ተንታኞች ይገልጻሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፣ መንግስታቸው በውጭ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ በወሰደው ጠንካራ እርምጃ በአማካይ በዓመት 3.5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ ወጪ መቀነስ ተችሏል። በተጨማሪም ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ ወደ 1,000 የሚጠጉ ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ስራ መመለሳቸውን እንደ ትልቅ ስኬት አንስተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣የሀገሪቱ የንግድ ሚዛን አሁንም ከፍተኛ ጉድለት ያለበት መሆኑን ይፋዊ መረጃዎች ያመለክታሉ። የኢትዮጵያ ዓመታዊ የገቢ ምርት ወጪ 17 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት የተመዘገበው ከፍተኛው የኤክስፖርት ገቢ ግን 8.3 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው። ይህም ዓመታዊ የንግድ ሚዛን ጉድለቱ ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን ያሳያል።
በተለይም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ለኤክስፖርት ገቢ ያለው ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑ ተመልክቷል። የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ መላኩ አለበል ከጥቂት ወራት በፊት ለፓርላማ እንደገለጹት፣ ዘርፉ ለማሽነሪዎችና ለግብዓቶች ከባንኮች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ቢያገኝም፣ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያስመዘገበው የኤክስፖርት ገቢ 97 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው።
ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ሀገሪቱ በምግብ እና በኢንዱስትሪ ምርቶች ራሷን ለመቻል በምታደርገው ጥረት ላይ ያላትን ተስፋ የሚያሳይ ቢሆንም፣ ዘርፉ ከውጭ ምንዛሬ ተጠቃሚነት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ አስገኝነቱን እንዲያሳድግ ከፍተኛ ስራ እንደሚጠበቅበት የዘርፉ ተንታኞች ይገልጻሉ።
1 month ago
የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻን 46 በመቶ ከፍ ማድረግ የቻለው "ኢትዮጵያ ታምርት" ስኬቶች
*****************
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ይፋ የሆነው ዲጂታል መጽሔት እንደጠቆመው፤ "ኢትዮጵያ ታምርት" ብሔራዊ ንቅናቄ መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመፍታት የአምራች ዘርፉን የኢኮኖሚ ምህዳር በአዲስ መልክ እየቀረጸው ይገኛል።
ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት 29 ሚሊዮን ቶን የነበረው የኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት በአሁኑ ወቅት ወደ 76 ሚሊዮን ቶን ከፍ ብሏል።
በመሠረተ ልማት ረገድም ባለፉት አራት ዓመታት 3.4 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የቀረበ ሲሆን፤ በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለባለሀብቶች ተላልፏል።
የፋይናንስ አቅርቦትን በተመለከተ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርበው ብድር ከ8.1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብር ሲያድግ፤ ለከፍተኛ አምራቾች የሚቀርበው ደግሞ ከ52 ቢሊዮን ወደ 262 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ ለከፍተኛ አምራቾች የቀረበው 2.28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አሳድጓል። የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገትም በ2017 ዓ.ም 10.7 በመቶ በመድረስ የምርት መጠኑን 195.4 ቢሊዮን ብር አድርሶታል።
ኢትዮጵያ በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ ስልታዊ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 4.85 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን የቻለች ሲሆን፤ የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻም ከ30 ወደ 46 በመቶ አድጓል።
በዲፕሎማሲው ረገድ የብሪክስ አባል መሆኗና የተደረጉ ማሻሻያዎች ከ2 ሺህ 800 በላይ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ አስችለዋል።
በተጨማሪም ተዘግተው የነበሩ 993 ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ የተመለሱ ሲሆን፤ ዘንድሮ የሚካሄደው "ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018" በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በስብጥሩ የላቀ ታሪካዊ ሁነት እንደሚሆን ተመላክቷል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiatamirt #pmoethiopia #manufacturingethiopia #madeinethiopia
*****************
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ይፋ የሆነው ዲጂታል መጽሔት እንደጠቆመው፤ "ኢትዮጵያ ታምርት" ብሔራዊ ንቅናቄ መዋቅራዊ ማነቆዎችን በመፍታት የአምራች ዘርፉን የኢኮኖሚ ምህዳር በአዲስ መልክ እየቀረጸው ይገኛል።
ንቅናቄው ከመጀመሩ በፊት 29 ሚሊዮን ቶን የነበረው የኢንዱስትሪ ግብዓት አቅርቦት በአሁኑ ወቅት ወደ 76 ሚሊዮን ቶን ከፍ ብሏል።
በመሠረተ ልማት ረገድም ባለፉት አራት ዓመታት 3.4 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የቀረበ ሲሆን፤ በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ለባለሀብቶች ተላልፏል።
የፋይናንስ አቅርቦትን በተመለከተ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርበው ብድር ከ8.1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብር ሲያድግ፤ ለከፍተኛ አምራቾች የሚቀርበው ደግሞ ከ52 ቢሊዮን ወደ 262 ቢሊዮን ብር ከፍ ብሏል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ ለከፍተኛ አምራቾች የቀረበው 2.28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አሳድጓል። የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገትም በ2017 ዓ.ም 10.7 በመቶ በመድረስ የምርት መጠኑን 195.4 ቢሊዮን ብር አድርሶታል።
ኢትዮጵያ በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ ስልታዊ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 4.85 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን የቻለች ሲሆን፤ የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻም ከ30 ወደ 46 በመቶ አድጓል።
በዲፕሎማሲው ረገድ የብሪክስ አባል መሆኗና የተደረጉ ማሻሻያዎች ከ2 ሺህ 800 በላይ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ አስችለዋል።
በተጨማሪም ተዘግተው የነበሩ 993 ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ የተመለሱ ሲሆን፤ ዘንድሮ የሚካሄደው "ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018" በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በስብጥሩ የላቀ ታሪካዊ ሁነት እንደሚሆን ተመላክቷል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopiatamirt #pmoethiopia #manufacturingethiopia #madeinethiopia
1 month ago
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው - የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል
*****************
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ላይ የቀረቡት ምርቶች ብዝሃነት እና ጥራት፣ ኢትዮጵያ በጥረቷ እና በልጆቿ የፈጠራ አቅም ብልጽግናዋን ማረጋገጥ እንደምትችል የሚመሰክር ነው ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ፈጠራዎች የደረሱበትን ትልቅ ደረጃም የሚያመላክት ነው ብለዋል ሚኒስትሩ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር።
በመደመር እሳቤ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማካሄድ እና የቢዝነስ ምህዳሩን ምቹ በማድረግ፣ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ምክንያት የማምረት አቅምን በማሳደግ፣ ገቢ ምርትን በመተካት እና ኤክስፖርትን በማሻሻል እንዲሁም የሥራ ዕድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ይበልጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድም ባለፉት 9 ወራት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 222 ኤግዚቢሽኖች ተዘጋጅተው 17 ሺህ 461 አምራቾች ምርቶቻቸውን ማስተዋወቃቸውን አንስተዋል።
በኤግዚቢሽኖቹ ለህብረተሰቡ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ 3.6 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የግብይት ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፣ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ሁኔታ መቀየሩን ገልጸዋል።
በነስሩ ጀማል
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc
*****************
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ላይ የቀረቡት ምርቶች ብዝሃነት እና ጥራት፣ ኢትዮጵያ በጥረቷ እና በልጆቿ የፈጠራ አቅም ብልጽግናዋን ማረጋገጥ እንደምትችል የሚመሰክር ነው ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ፈጠራዎች የደረሱበትን ትልቅ ደረጃም የሚያመላክት ነው ብለዋል ሚኒስትሩ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር።
በመደመር እሳቤ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማካሄድ እና የቢዝነስ ምህዳሩን ምቹ በማድረግ፣ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ምክንያት የማምረት አቅምን በማሳደግ፣ ገቢ ምርትን በመተካት እና ኤክስፖርትን በማሻሻል እንዲሁም የሥራ ዕድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ይበልጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድም ባለፉት 9 ወራት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 222 ኤግዚቢሽኖች ተዘጋጅተው 17 ሺህ 461 አምራቾች ምርቶቻቸውን ማስተዋወቃቸውን አንስተዋል።
በኤግዚቢሽኖቹ ለህብረተሰቡ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ 3.6 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የግብይት ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፣ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ሁኔታ መቀየሩን ገልጸዋል።
በነስሩ ጀማል
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፈረሙት ለምንድን ነው?
*“ኢትዮጵያን የአፍሪካ የፋሽን ተምሳሌት እናደርጋታለን” — አቶ ዘላለም መራዊ
የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት
#ethiopia | በ“ኢትዮጵያ ታምርት” የንግድ ትርኢት ላይ የተሳተፉት የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች አቶ ዘላለም መራዊ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድርጅታቸውን የፈጠራ ስራዎች መጎብኘታቸውንና ከፍተኛ አድናቆት መቸራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በየዓመቱ በሚያደርጉት ጉብኝት በምርቶቹ ላይ የሚታየው መሻሻልና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንዳስደመሟቸው በድርጅቱ የክብር መዝገብ ላይ በፊርማቸው ጭምር አረጋግጠዋል።
በዓለም ላይ ያለው የፋሽን ኢንዱስትሪ እስከ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያንቀሳቅስ የገለጹት አቶ ዘላለም፣ ኢትዮጵያ እንደ ጣልያንና ፈረንሳይ የራሷን የፋሽን “ብራንድ” በመገንባት ከዚህ ገበያ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል።
ኬሬዠ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከውጭ ይገቡ የነበሩ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የቆዳ ውጤቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ለተለያዩ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰጡ የክብር ስጦታዎችን እያቀረበ ይገኛል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን በፋሽንና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ ላይ የማድረስ ጉጉት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አቶ ዘላለም የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች ከመሆናቸው ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን መላው ዘርፍ በቴክኖሎጂ፣ በስልጠናና በጥሬ እቃ አቅርቦት እንዲሻሻል በንቃት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት (ቆዳ) እና የሰው ኃይል በመጠቀም ኢትዮጵያን በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በመላው አፍሪካ ገበያዎች ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ ታላቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን የስራ መሪው በኩራት ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #amn
#የኢትዮጵያታምርት #ቆዳናየቆዳውጤቶች #ዘላለምመራዊ #ኢትዮጵያ #ፋሽን #የሀገርውስጥምርት #ethiopiatamrit #ethiopianfashion #leatherindustry
*“ኢትዮጵያን የአፍሪካ የፋሽን ተምሳሌት እናደርጋታለን” — አቶ ዘላለም መራዊ
የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት
#ethiopia | በ“ኢትዮጵያ ታምርት” የንግድ ትርኢት ላይ የተሳተፉት የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች አቶ ዘላለም መራዊ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድርጅታቸውን የፈጠራ ስራዎች መጎብኘታቸውንና ከፍተኛ አድናቆት መቸራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በየዓመቱ በሚያደርጉት ጉብኝት በምርቶቹ ላይ የሚታየው መሻሻልና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንዳስደመሟቸው በድርጅቱ የክብር መዝገብ ላይ በፊርማቸው ጭምር አረጋግጠዋል።
በዓለም ላይ ያለው የፋሽን ኢንዱስትሪ እስከ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያንቀሳቅስ የገለጹት አቶ ዘላለም፣ ኢትዮጵያ እንደ ጣልያንና ፈረንሳይ የራሷን የፋሽን “ብራንድ” በመገንባት ከዚህ ገበያ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል።
ኬሬዠ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከውጭ ይገቡ የነበሩ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የቆዳ ውጤቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ለተለያዩ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰጡ የክብር ስጦታዎችን እያቀረበ ይገኛል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን በፋሽንና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ ላይ የማድረስ ጉጉት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አቶ ዘላለም የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች ከመሆናቸው ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን መላው ዘርፍ በቴክኖሎጂ፣ በስልጠናና በጥሬ እቃ አቅርቦት እንዲሻሻል በንቃት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት (ቆዳ) እና የሰው ኃይል በመጠቀም ኢትዮጵያን በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በመላው አፍሪካ ገበያዎች ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ ታላቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን የስራ መሪው በኩራት ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #amn
#የኢትዮጵያታምርት #ቆዳናየቆዳውጤቶች #ዘላለምመራዊ #ኢትዮጵያ #ፋሽን #የሀገርውስጥምርት #ethiopiatamrit #ethiopianfashion #leatherindustry
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ጋዜጠኛዋ ቅኝት በአራተኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 #ኢትዮጵያ_ታምርት #expo2026 #expo2018 #ebc #etv #ebcdotstream #news
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
1 month ago
የኢንዱስትሪ ዘርፉን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት የሚያግዝ ህግ እየተዘጋጀ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢንዱስትሪ ዘርፉ ላይ የሚስተዋለውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የሚያግዝ ህግ እየተዘጋጀ ነው አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት 4ኛውን ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው በከፈቱበት ወቅት እንዳሉት፥ የፋይናንስ ተቋማት ለኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚያቀርቡት ብድርና ድጋፍ አነስተኛ መሆኑ ተገምግሟል፡፡
ይህንን ችግር ለመፍታት ከሀገሪቱ ሀብት ምንያህሉ ወደ ኢንዱስትሪ መፍሰስ እንዳለበት የሚወስን ህግ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፥ ይህም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡
ይህ ህግ የግልም የመንግስትም ባንኮችን የሚመለከት ሲሆን፥ የኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚገባውን ድርሻ እንዲያጣ ያደረጉ ሰው ሰራሽ ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችላል ነው ያሉት፡፡
ነገር ግን ብዙ ሀብት ካልፈጠርን አሁን ያለው ሀብት በቂ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሀብት ለሁሉም ዘርፎች ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ለመፍጠር ሁሉም ነገር ንግድና ኮንትሮባንድ ብቻ እንዳይሆን በህግ እንደሚቀየር አስረድተዋል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢንዱስትሪ ዘርፉ ላይ የሚስተዋለውን የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት የሚያግዝ ህግ እየተዘጋጀ ነው አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት 4ኛውን ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ መርቀው በከፈቱበት ወቅት እንዳሉት፥ የፋይናንስ ተቋማት ለኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚያቀርቡት ብድርና ድጋፍ አነስተኛ መሆኑ ተገምግሟል፡፡
ይህንን ችግር ለመፍታት ከሀገሪቱ ሀብት ምንያህሉ ወደ ኢንዱስትሪ መፍሰስ እንዳለበት የሚወስን ህግ እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፥ ይህም በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ ጠቁመዋል፡፡
ይህ ህግ የግልም የመንግስትም ባንኮችን የሚመለከት ሲሆን፥ የኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚገባውን ድርሻ እንዲያጣ ያደረጉ ሰው ሰራሽ ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችላል ነው ያሉት፡፡
ነገር ግን ብዙ ሀብት ካልፈጠርን አሁን ያለው ሀብት በቂ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ሀብት ለሁሉም ዘርፎች ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል ለመፍጠር ሁሉም ነገር ንግድና ኮንትሮባንድ ብቻ እንዳይሆን በህግ እንደሚቀየር አስረድተዋል፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
1 month ago
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ እና ነጻ ነኝ ማለት አይችልም አሉ፡፡
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ያጎናጽፋል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ማምረት ካልቻለች የግብርና ምርትና ሂደቱ በሰዎች በጎ ፈቃድ ላይ መውደቁ አይቀርም ነው ያሉት፡፡
ለምግብ ግብዓት የሚሆኑ የማምረቻ መሳሪያዎች፣ ምርጥ ዘሮች እና ማዳበሪያዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት የተሟላ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡
ነዳጅ እና ጋዝ ማምረት ባለመቻላችን ብዙ ፈተና ገጥሞናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ብዙ የነዳጅ እና ጋዝ ሀብት እንዳላቸው ሀገራት ከፍተኛ አቅም ቢኖራትም እስካሁን ድረስ ማምረት ባለመቻላችን ተቸግረናል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
21 ትሊየን ሜትሪክ ኪዩብ ጋዝ ያላት ሀገር ያንን ሳታመርት በመቆየቷ ትራንስፖርት እና ኢንዱስትሪው ሊታወክ ችሏል ብለዋል፡፡
በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ መሆኑን በማመን ማቀድ፣ መስራት እና መስፋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ነጻ እና ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያዊያን ልመና በቃን እስካላልን ድረስ ጥገኞች ነን ብለዋል፡፡
FBC
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ እና ነጻ ነኝ ማለት አይችልም አሉ፡፡
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ያጎናጽፋል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ማምረት ካልቻለች የግብርና ምርትና ሂደቱ በሰዎች በጎ ፈቃድ ላይ መውደቁ አይቀርም ነው ያሉት፡፡
ለምግብ ግብዓት የሚሆኑ የማምረቻ መሳሪያዎች፣ ምርጥ ዘሮች እና ማዳበሪያዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት የተሟላ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡
ነዳጅ እና ጋዝ ማምረት ባለመቻላችን ብዙ ፈተና ገጥሞናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ብዙ የነዳጅ እና ጋዝ ሀብት እንዳላቸው ሀገራት ከፍተኛ አቅም ቢኖራትም እስካሁን ድረስ ማምረት ባለመቻላችን ተቸግረናል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
21 ትሊየን ሜትሪክ ኪዩብ ጋዝ ያላት ሀገር ያንን ሳታመርት በመቆየቷ ትራንስፖርት እና ኢንዱስትሪው ሊታወክ ችሏል ብለዋል፡፡
በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ መሆኑን በማመን ማቀድ፣ መስራት እና መስፋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ነጻ እና ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያዊያን ልመና በቃን እስካላልን ድረስ ጥገኞች ነን ብለዋል፡፡
FBC
1 month ago
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ እና ነጻ ነኝ ማለት አይችልም አሉ፡፡
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ያጎናጽፋል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ማምረት ካልቻለች የግብርና ምርትና ሂደቱ በሰዎች በጎ ፈቃድ ላይ መውደቁ አይቀርም ነው ያሉት፡፡
ለምግብ ግብዓት የሚሆኑ የማምረቻ መሳሪያዎች፣ ምርጥ ዘሮች እና ማዳበሪያዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት የተሟላ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡
ነዳጅ እና ጋዝ ማምረት ባለመቻላችን ብዙ ፈተና ገጥሞናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ብዙ የነዳጅ እና ጋዝ ሀብት እንዳላቸው ሀገራት ከፍተኛ አቅም ቢኖራትም እስካሁን ድረስ ማምረት ባለመቻላችን ተቸግረናል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
21 ትሊየን ሜትሪክ ኪዩብ ጋዝ ያላት ሀገር ያንን ሳታመርት በመቆየቷ ትራንስፖርት እና ኢንዱስትሪው ሊታወክ ችሏል ብለዋል፡፡
በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ መሆኑን በማመን ማቀድ፣ መስራት እና መስፋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ነጻ እና ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያዊያን ልመና በቃን እስካላልን ድረስ ጥገኞች ነን ብለዋል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እርዳታ የሚቀበል ሀገር ሉዓላዊ እና ነጻ ነኝ ማለት አይችልም አሉ፡፡
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተከፍቷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ያጎናጽፋል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ ማዳበሪያ ማምረት ካልቻለች የግብርና ምርትና ሂደቱ በሰዎች በጎ ፈቃድ ላይ መውደቁ አይቀርም ነው ያሉት፡፡
ለምግብ ግብዓት የሚሆኑ የማምረቻ መሳሪያዎች፣ ምርጥ ዘሮች እና ማዳበሪያዎችን በሀገር ውስጥ ማምረት የተሟላ የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡
ነዳጅ እና ጋዝ ማምረት ባለመቻላችን ብዙ ፈተና ገጥሞናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ኢትዮጵያ ብዙ የነዳጅ እና ጋዝ ሀብት እንዳላቸው ሀገራት ከፍተኛ አቅም ቢኖራትም እስካሁን ድረስ ማምረት ባለመቻላችን ተቸግረናል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
21 ትሊየን ሜትሪክ ኪዩብ ጋዝ ያላት ሀገር ያንን ሳታመርት በመቆየቷ ትራንስፖርት እና ኢንዱስትሪው ሊታወክ ችሏል ብለዋል፡፡
በሁሉም መስክ ማምረት ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ መሆኑን በማመን ማቀድ፣ መስራት እና መስፋት ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡
እርዳታ የሚቀበል ሀገር ነጻ እና ሉዓላዊ ነኝ ማለት አይችልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያዊያን ልመና በቃን እስካላልን ድረስ ጥገኞች ነን ብለዋል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 በይፋ መርቀው ከፈቱ
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የአምራች ዘርፍ ለማስፋፋት የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክረውን አራተኛውን 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 ዛሬ በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
ኤክስፖው እስካሁን ያሳያቸው እና የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች፦
- የአምራች ዘርፉ ግብዓት አቅርቦት በዓመት ከ9 ሚሊዮን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል፤
- ለአዳዲስ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች ከ3.4 ጊጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል፤
- ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው የፋይናንስ አቅርቦት ከ8.1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ከ262 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍ ብሏል፤
- ለዘርፉ ከ2.28 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተመድቧል፤
- የፋብሪካዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አድጓል፤
- የማምረት አቅም እና ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ዕድገት ይጠበቃል፤
- ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት እስከ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን የተቻለ ሲሆን የወጪ ንግድም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል፤
- ከ2 ሺህ 800 በላይ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የተቻለ ሲሆን፣ ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
ኤክስፖው ኢንዱስትሪዎችን የሚያስተሳስር፣ ኢንቨስትመንትን የሚስብ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ አምራቾችን እና በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎችን የሚያገናኝ ቁልፍ ሀገራዊ መድረክ ሆኗል።
በአጠቃላይ የኤክስፖው መከፈት የአምራች ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያለውን ፋይዳ በማጉላት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ሽግግር እያፋጠነ መሆኑን ያሳያል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
#ebc #ethiopia #industry #madeinethiopia
****************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የአምራች ዘርፍ ለማስፋፋት የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክረውን አራተኛውን 'ኢትዮጵያ ታምርት' ኤክስፖ 2018 ዛሬ በይፋ መርቀው ከፍተዋል።
ኤክስፖው እስካሁን ያሳያቸው እና የተመዘገቡ ዋና ዋና ስኬቶች፦
- የአምራች ዘርፉ ግብዓት አቅርቦት በዓመት ከ9 ሚሊዮን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል፤
- ለአዳዲስ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች ከ3.4 ጊጋ ዋት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ቀርቧል፤
- ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው የፋይናንስ አቅርቦት ከ8.1 ቢሊዮን ወደ 50 ቢሊዮን ብር ያደገ ሲሆን፣ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ከ262 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍ ብሏል፤
- ለዘርፉ ከ2.28 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ተመድቧል፤
- የፋብሪካዎች የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ አድጓል፤
- የማምረት አቅም እና ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ በቀጣይም ተጨማሪ ዕድገት ይጠበቃል፤
- ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት እስከ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን የተቻለ ሲሆን የወጪ ንግድም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል፤
- ከ2 ሺህ 800 በላይ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የተቻለ ሲሆን፣ ለ1.4 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
ኤክስፖው ኢንዱስትሪዎችን የሚያስተሳስር፣ ኢንቨስትመንትን የሚስብ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ አምራቾችን እና በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ጎብኚዎችን የሚያገናኝ ቁልፍ ሀገራዊ መድረክ ሆኗል።
በአጠቃላይ የኤክስፖው መከፈት የአምራች ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ያለውን ፋይዳ በማጉላት የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ሽግግር እያፋጠነ መሆኑን ያሳያል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
#ebc #ethiopia #industry #madeinethiopia
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ከምኞት ወደ እውነት፦ የኢትዮጵያ አዲሱ የሉዓላዊነት ጉዞ በ21ኛው ክፍለ ዘመን
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
1 month ago
1 month ago
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ የሥራ ባህል እየገነባ ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።
አገልግሎቱ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው ብሏል።
ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው ሲልም ገልጿል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ‘በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርትን ከማሳደግና የውጭ ምንዛሬን ከመታደግ ባሻገር ዕውቀትንና ክህሎትን ለዓለም የምናበረክትበት አዲስ የኢንዱስትሪ ምዕራፍ ተጀምሯል!’ በሚል ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፤ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ስራ በማስገባት፣ 4.85 ቢሊየን ዶላር ገቢ ምርትን በመተካት እና 433 ሚሊየን ዶላር ከኤክስፖርት በማስገኘት አስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ውጤት አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መንግሥት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሀገራዊ ንቅናቄ ሲጀምር፣ ግቡ ምርትን ማሳደግና የውጭ ምንዛሬን መታደግ ብቻ አልነበረም።
ከእነዚህ ኢኮኖሚያዊ ስሌቶች ባሻገር፣ ትልቁና ስትራቴጂካዊው ስኬታችን የተመዘገበው ኢትዮጵያን የዕውቀትና የክህሎት ምንጭ በሚያደርገው የሰው ሀብት ልማት ላይ ነው። ዛሬ ላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የፋብሪካዎች ስብስብ መሆኑ ቀርቶ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚገነቡ ብቁ ባለሙያዎችና መሪዎች የሚፈሩበት ታላቅ የተግባር ትምህርት ቤት መሆን ችሏል። ይህ ሽግግር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ቴክኖሎጂ ላኪነትና ክህሎት አቅራቢነት ከፍ የሚያደርግ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ መሠረት የሚጥል የታሪካችን እጥፋት ነው።
በታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በግዙፍ ፋብሪካዎች ውስጥ የታየው ተጨባጭ ለውጥ የመንግሥትን የፖሊሲ ጥንካሬ በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። ከዚህ ቀደም በከፍተኛ ክፍያ በሚመጡ የውጭ ሀገር ዜጎች ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ውስብስብ የቴክኖሎጂ ሲስተሞች፣ ዘመናዊ የምርት መስመሮችና የሶፍትዌር መሠረተ-ልማቶች ዛሬ ላይ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ወጣት መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች እየተመሩ ይገኛሉ። ይህ ስኬታማ የዕውቀት ሽግግር፣ መንግሥት ጥራት ያለው ፖሊሲ የመቅረጽ ብቻ ሳይሆን ፖሊሲን በተጨባጭ ወደ ተግባር የመለወጥና የማስፈጸም አቅም እንዳለው ትልቅ ማሳያ ነው።
በዘረፉ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የተፈጠረላቸውን ምቹ ዐውድ ተጠቀመው ቴክኖሎጂን የመቀበል ብቻ ሳይሆን፣ የመግራትና የማላመድ ብቃታቸውን በተግባር በማሳየት፣ ሀገራችን ለዘመናት የነበረባትን የቴክኖሎጂ ጥገኝነት በፈጠራ አቅማቸው እያስቀሩና አዳዲስ የሥራ ባሕልና የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ ይገኛሉ።
የ "ኢትዮጵያ ታምርት"ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር፣ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው ። በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው። ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶቻች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው።
መንግሥት የኢንዱስትሪ ሽግግሩን ትክክለኛ ፍሬ የሚለካው በወጪ ንግድ ስሌቶች ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂ የደረጀና በዕውቀት የበለጸገ አምራች ዜጋ መፈጠሩ ነው። በመሆኑም ይህን የክህሎት አብዮት ይበልጥ በማፋጠንና ዘርፉን የቴክኖሎጂ ምንጭ በማድረግ፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በቁርጠኝነት ይቀጥላሉ።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።
አገልግሎቱ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው ብሏል።
ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው ሲልም ገልጿል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ‘በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርትን ከማሳደግና የውጭ ምንዛሬን ከመታደግ ባሻገር ዕውቀትንና ክህሎትን ለዓለም የምናበረክትበት አዲስ የኢንዱስትሪ ምዕራፍ ተጀምሯል!’ በሚል ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፤ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ስራ በማስገባት፣ 4.85 ቢሊየን ዶላር ገቢ ምርትን በመተካት እና 433 ሚሊየን ዶላር ከኤክስፖርት በማስገኘት አስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ውጤት አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መንግሥት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሀገራዊ ንቅናቄ ሲጀምር፣ ግቡ ምርትን ማሳደግና የውጭ ምንዛሬን መታደግ ብቻ አልነበረም።
ከእነዚህ ኢኮኖሚያዊ ስሌቶች ባሻገር፣ ትልቁና ስትራቴጂካዊው ስኬታችን የተመዘገበው ኢትዮጵያን የዕውቀትና የክህሎት ምንጭ በሚያደርገው የሰው ሀብት ልማት ላይ ነው። ዛሬ ላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የፋብሪካዎች ስብስብ መሆኑ ቀርቶ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚገነቡ ብቁ ባለሙያዎችና መሪዎች የሚፈሩበት ታላቅ የተግባር ትምህርት ቤት መሆን ችሏል። ይህ ሽግግር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ቴክኖሎጂ ላኪነትና ክህሎት አቅራቢነት ከፍ የሚያደርግ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ መሠረት የሚጥል የታሪካችን እጥፋት ነው።
በታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በግዙፍ ፋብሪካዎች ውስጥ የታየው ተጨባጭ ለውጥ የመንግሥትን የፖሊሲ ጥንካሬ በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። ከዚህ ቀደም በከፍተኛ ክፍያ በሚመጡ የውጭ ሀገር ዜጎች ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ውስብስብ የቴክኖሎጂ ሲስተሞች፣ ዘመናዊ የምርት መስመሮችና የሶፍትዌር መሠረተ-ልማቶች ዛሬ ላይ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ወጣት መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች እየተመሩ ይገኛሉ። ይህ ስኬታማ የዕውቀት ሽግግር፣ መንግሥት ጥራት ያለው ፖሊሲ የመቅረጽ ብቻ ሳይሆን ፖሊሲን በተጨባጭ ወደ ተግባር የመለወጥና የማስፈጸም አቅም እንዳለው ትልቅ ማሳያ ነው።
በዘረፉ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የተፈጠረላቸውን ምቹ ዐውድ ተጠቀመው ቴክኖሎጂን የመቀበል ብቻ ሳይሆን፣ የመግራትና የማላመድ ብቃታቸውን በተግባር በማሳየት፣ ሀገራችን ለዘመናት የነበረባትን የቴክኖሎጂ ጥገኝነት በፈጠራ አቅማቸው እያስቀሩና አዳዲስ የሥራ ባሕልና የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ ይገኛሉ።
የ "ኢትዮጵያ ታምርት"ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር፣ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው ። በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው። ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶቻች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው።
መንግሥት የኢንዱስትሪ ሽግግሩን ትክክለኛ ፍሬ የሚለካው በወጪ ንግድ ስሌቶች ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂ የደረጀና በዕውቀት የበለጸገ አምራች ዜጋ መፈጠሩ ነው። በመሆኑም ይህን የክህሎት አብዮት ይበልጥ በማፋጠንና ዘርፉን የቴክኖሎጂ ምንጭ በማድረግ፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በቁርጠኝነት ይቀጥላሉ።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
1 month ago
የኢንዱስትሪ ዘርፍ አቅምን የገለጠው ኢትዮጵያ ታምርት …
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲን በመከተል ሀገራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ በአስደናቂ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
ከዚህ ቀደም በግብርና ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የነበረውን የኢኮኖሚ ትኩረት በማስፋት በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በአይቲ ዘርፎች ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በተሰራው ስራ ውጤት ተመዝግቧል።
በዚህ ረገድ በተለይም ከውጭ የሚገባውን ምርት በመቀነስ እና ወደ ውጭ የሚላክ ምርትን በማሳደግ የተጀመረው የአምራች ኢንዱስትሪው ንቅናቄ በአብነት ይጠቀሳል።
በዚህም ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገቡ የኢንዱስትሪ ምርቶች ጥገኝነት ተላቅቃ ራስን በመቻል ብቻ ሳትገደብ ለውጭ ገበያ በማቅረብ በአስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ለዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ረገድ ገና ከጅምሩ ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገቡበት ሆኗል፡፡
በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተዘጉ ፋብሪካዎችን ዳግም ሥራ በማስጀመር፣ ምርታማነትን በማሳደግና በስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም ገቢ ምርቶችን በመተካት በቢሊየን ዶላር የሚገመት የውጭ ምንዛሪ ማዳን ተችሏል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው በተለይም በተኪ ምርቶች ረገድ ባለፉት 9 ወራት ብቻ 4 ነጥብ 85 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ ምርት በሀገር ውስጥ ተመርተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች መተካት ብቻ ሳይሆን ምርታማነትን በማሳደግ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ርዕይን ያነገበ ነው፡፡
ባለፉት 9 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የኢንዱስትሪ ምርቶች 433 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱ የኢንዱስትሪ ዘርፉ በፈጣን የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝ አመላካች ነው፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ስራ ለማስጀመርና የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የማምረት አቅም እንዲያድግ ንቅናቄው ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡
በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን በማላቅ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲወጣ ለማድረግ በተለይም የፋይናንስ እና የኃይል አቅርቦት ልዩ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲን በመከተል ሀገራዊ ብልጽግናን እውን ለማድረግ በአስደናቂ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
ከዚህ ቀደም በግብርና ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የነበረውን የኢኮኖሚ ትኩረት በማስፋት በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝም እና በአይቲ ዘርፎች ያለውን ዕምቅ አቅም በመጠቀም የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በተሰራው ስራ ውጤት ተመዝግቧል።
በዚህ ረገድ በተለይም ከውጭ የሚገባውን ምርት በመቀነስ እና ወደ ውጭ የሚላክ ምርትን በማሳደግ የተጀመረው የአምራች ኢንዱስትሪው ንቅናቄ በአብነት ይጠቀሳል።
በዚህም ኢትዮጵያ ከውጭ ከሚገቡ የኢንዱስትሪ ምርቶች ጥገኝነት ተላቅቃ ራስን በመቻል ብቻ ሳትገደብ ለውጭ ገበያ በማቅረብ በአስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ለዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ረገድ ገና ከጅምሩ ተጨባጭ ውጤቶች የተመዘገቡበት ሆኗል፡፡
በንቅናቄው አማካኝነት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተዘጉ ፋብሪካዎችን ዳግም ሥራ በማስጀመር፣ ምርታማነትን በማሳደግና በስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም ገቢ ምርቶችን በመተካት በቢሊየን ዶላር የሚገመት የውጭ ምንዛሪ ማዳን ተችሏል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያሳየው በተለይም በተኪ ምርቶች ረገድ ባለፉት 9 ወራት ብቻ 4 ነጥብ 85 ቢሊየን ዶላር የሚያወጣ ምርት በሀገር ውስጥ ተመርተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርቶች መተካት ብቻ ሳይሆን ምርታማነትን በማሳደግ ለውጭ ገበያ የማቅረብ ርዕይን ያነገበ ነው፡፡
ባለፉት 9 ወራት ለውጭ ገበያ ከቀረቡ የኢንዱስትሪ ምርቶች 433 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱ የኢንዱስትሪ ዘርፉ በፈጣን የሽግግር ሂደት ላይ እንደሚገኝ አመላካች ነው፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ስራ ለማስጀመርና የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የማምረት አቅም እንዲያድግ ንቅናቄው ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡
በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችን በማላቅ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲወጣ ለማድረግ በተለይም የፋይናንስ እና የኃይል አቅርቦት ልዩ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡
በኃይለማርያም ተገኝ
Comments