2 months ago
ቤተ ጉራጌ
እዣ : የኢንቨስትመንት ፀሐይ እየወጣላት ነው
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው አዲስ የብረት ማምረቻ ፋብሪካ በይፋ ተመረቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የብረት ማምረቻ ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ባለሀብቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል።
የሀሮት ሪልስቴት እህት ኩባንያ የሆነው ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር መሥራችና ባለቤት አቶ ሰኢድ ኑሩ እንደተናገሩት "ቪታ ሳሉቲ የጣልያንኛ ቃል ሲሆን ሰላማዊ ሕይወት የሚል ትርጉም ይዟል። ሰላማዊ ሕይወት በቤተ ጉራጌ - ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ኢትዮጵያ መልካም ምኞት ለመግለጥ ነው። የቤተ ጉራጌ አኗኗርም ለማመላከት ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘውንና የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ የሆነውን ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ፋብሪካን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
አያይዘውም "ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የግል ባለሀብቱ ሚና የላቀ ነው!" ሲሉ አወድሰዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ፋብሪካ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የካፒታል ወጪ የተገነባ ሲሆን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተለያዩ መጠንና ቅርጽ ያላቸው የትቦላሬና የላሜራ ብረት 22 ምርቶችን በከፍተኛ ጥራት የማምረት አቅም አለው።
አቶ ሰኢድ ኑሩ ንግግር "ይህ ፕሮጀክት ከህልም ወደ እውነት፣ ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ነው። ሀገራት የሚበለጽጉት በተፈጥሮ ሀብታቸው ብቻ ሳይሆን ራዕይን ወደ ተግባር በሚቀይሩ ባለሀብቶችና በሥራ ፈጣሪ ዜጎች ነው!" ብለዋል።
አቶ ሰኢድ አያይዘውም የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ከህልም ወደ እውነት ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚኖረው ድርሻ የላቀ ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ያድናል ሲሉ አብስረዋል።
ኢንጂነር ናሆም መገርሣ በ5,000 ካሬ ላይ የሚገኘው ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት ለ123 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተዘዋዋሪ የስራ ዕድሎችን በማመቻቸት ለቀጣናው የኢኮኖሚ እድገት የጎላ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኒፋክቸሪንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፋብሪካው በዞኑ የመጀመሪያው የብረት ፋብሪካ መሆኑን አስረድተዋል።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ጥራታቸውን የጠበቁ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በመገንባትና በማስረከብ ከሚታወቀው የሀሮት ሪል እስቴት ጋር እህት ኩባንያ ነው።
ሀሮት ሪል እስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለህብረተሰቡ በማቅረቡ የኢትዮ ህይ 2025 የሪል እስቴት አዋርድ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
የፋብሪካው አመራሮች ለዚህ ስኬት መገኘት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱት የክልልና የዞን የስራ ኃላፊዎች፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለቲናው አበባ ልማት አክሲዮን ማህበር፣ ለባለሙያዎች እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
የሀሮት ሪል ስቴት የማርኬቲንግ ኃላፊ ፋንትሽ ሸዋ እንደገለጹት፤ ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ ነው። ተቋሙ ከተመሰረተ 4ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ ድርጅቱ ለደንበኞቹ በገባው ቃል መሠረት በቦሌ ቡልቡላ ያስገነባቸውን የመኖሪያ ቤቶች በይፋ አስረክቧል።
በተጨማሪም ከሁለት ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በመስቀል ፍላወር፣ በሀያት ፈረስ ቤት እና በቦሌ ቡልቡላ አካባቢዎች የሚገነቡ ተጨማሪ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች እንደሚያስረክብ አስታውቀዋል።
ሀሮት ሪል ስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለገበያ በማቅረቡ በፈረንጆቹ 2025 በተካሄደው የኢትዮ ሪል ስቴት ሽልማት መርሃ ግብር ላይ በጥራትና በዋጋ አቅርቦት የአሸናፊነት ክብርን ያገኘ ድርጅት መሆኑ አብራርታለች።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር በኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴልና በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ኢንቨስትመንቱን ይበልጥ በማስፋፋት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
ባለሃብቱ አቶ ሰኢድ ይህ ስኬት የአንድ ሰው ጥረትና ውጤት ብቻ አይደለም። ከጀርባው ብዙ እጆች፣ ብዙ ዱአዎች እና ጸሎቶች፣ ብዙ ምክሮች ያሉበት ነው። በዚህ መሠረት ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ ለኢንቨስትመንት ቢሮ፣ ለጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቲናው አበባ ልማት አ/ማሀበር ለሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ለባለሙያዎች እና ለሠራተኞቻችን ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
አቶ ሰኢድ የትምህርት ሕይወታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጥታ የተቀላቀሉት የንግዱን ዓለም ሲሆን፣ መጀመሪያ ላይ በመኪና መለዋወጫ ንግድ በመሰማራትና በመቀጠልም ወደ አስመጪና ላኪነት ዘርፍ በመሸጋገር ረጅም ዓመታትን አሳልፈዋል። በሂደትም የንግድ ሥራቸውን በማስፋት የጀመሩት የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ገና በጅማሮው ከፍተኛ የምስጋና ሽልማትና ዕውቅናን ሊያጎናጽፋቸው ችሏል። ባለሀብቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ማኑፋክቸሪንግና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት በመግባት ላይ ይገኛሉ።
በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ያጋጠማቸው የአስተዳደር ፈተና ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሰይድ ሲመልሱ፣ ምንም ዓይነት ችግር እንዳልገጠማቸው በአጽንኦት ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ ከላይ እስከ ታች ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአስተዳደር አካላት አንድ ባለሀብት እውነተኛ አልሚ መሆኑን ከተረዱ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ የገለጹት አቶ ሰይድ፣ ለእሳቸውም የተደረገላቸውን ተገቢውን ድጋፍና ትብብር በሙሉ አመስግነዋል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ
"በዞናችን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶች ሁሉ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ዝግጁ ነን፣ በቁርጠኝነትም እንሠራለን! ... ዛሬ ኑ" ሲሉ ተደምጠዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ፦ "የጉራጌ ማህበረሰብ በሀገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች ከተሞችን በማልማትና ጠንካራ የንግድ ሥርዓት በመዘርጋት የሚታወቅ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ባለሀብቶች ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው በልማት እየሳተፉ መሆኑ እጅግ ያስደስታል። ይህ ፋብሪካ የሀገር ሀብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል። ሌሎች ባለሀብቶችም በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።"ለአገርና ለሕዝብ መልዕክታቸውን አሰምተዋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት ዶክተር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እና የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አባስ መሀመድን ጨምሮ በርካታ የአመራር አካላት ተገኝተዋል።
"Vita, saluti, peace, life" blends Italian and English expressions of well-being, translating roughly to "life, greetings, peace, and life." This combination evokes a deep desire for a harmonious, healthy existence filled with good energy and wellness.
#manufacturing #factoryinauguration #centralethiopia #guragezone #investment #harotrealestate #vitasaluti #economicgrowth #realestate #housing #bolebulbula #homeownership #ethiopianbusiness #ኢንቨስትመንት #ሪልስቴት #ኢንዱስትሪ #ልማት #የሥራዕድል #ቢዝነስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
እዣ : የኢንቨስትመንት ፀሐይ እየወጣላት ነው
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው አዲስ የብረት ማምረቻ ፋብሪካ በይፋ ተመረቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የብረት ማምረቻ ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ባለሀብቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል።
የሀሮት ሪልስቴት እህት ኩባንያ የሆነው ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር መሥራችና ባለቤት አቶ ሰኢድ ኑሩ እንደተናገሩት "ቪታ ሳሉቲ የጣልያንኛ ቃል ሲሆን ሰላማዊ ሕይወት የሚል ትርጉም ይዟል። ሰላማዊ ሕይወት በቤተ ጉራጌ - ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ኢትዮጵያ መልካም ምኞት ለመግለጥ ነው። የቤተ ጉራጌ አኗኗርም ለማመላከት ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘውንና የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ የሆነውን ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ፋብሪካን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
አያይዘውም "ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የግል ባለሀብቱ ሚና የላቀ ነው!" ሲሉ አወድሰዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ፋብሪካ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የካፒታል ወጪ የተገነባ ሲሆን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተለያዩ መጠንና ቅርጽ ያላቸው የትቦላሬና የላሜራ ብረት 22 ምርቶችን በከፍተኛ ጥራት የማምረት አቅም አለው።
አቶ ሰኢድ ኑሩ ንግግር "ይህ ፕሮጀክት ከህልም ወደ እውነት፣ ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ነው። ሀገራት የሚበለጽጉት በተፈጥሮ ሀብታቸው ብቻ ሳይሆን ራዕይን ወደ ተግባር በሚቀይሩ ባለሀብቶችና በሥራ ፈጣሪ ዜጎች ነው!" ብለዋል።
አቶ ሰኢድ አያይዘውም የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ከህልም ወደ እውነት ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚኖረው ድርሻ የላቀ ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ያድናል ሲሉ አብስረዋል።
ኢንጂነር ናሆም መገርሣ በ5,000 ካሬ ላይ የሚገኘው ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት ለ123 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተዘዋዋሪ የስራ ዕድሎችን በማመቻቸት ለቀጣናው የኢኮኖሚ እድገት የጎላ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኒፋክቸሪንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፋብሪካው በዞኑ የመጀመሪያው የብረት ፋብሪካ መሆኑን አስረድተዋል።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ጥራታቸውን የጠበቁ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በመገንባትና በማስረከብ ከሚታወቀው የሀሮት ሪል እስቴት ጋር እህት ኩባንያ ነው።
ሀሮት ሪል እስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለህብረተሰቡ በማቅረቡ የኢትዮ ህይ 2025 የሪል እስቴት አዋርድ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
የፋብሪካው አመራሮች ለዚህ ስኬት መገኘት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱት የክልልና የዞን የስራ ኃላፊዎች፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለቲናው አበባ ልማት አክሲዮን ማህበር፣ ለባለሙያዎች እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
የሀሮት ሪል ስቴት የማርኬቲንግ ኃላፊ ፋንትሽ ሸዋ እንደገለጹት፤ ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ ነው። ተቋሙ ከተመሰረተ 4ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ ድርጅቱ ለደንበኞቹ በገባው ቃል መሠረት በቦሌ ቡልቡላ ያስገነባቸውን የመኖሪያ ቤቶች በይፋ አስረክቧል።
በተጨማሪም ከሁለት ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በመስቀል ፍላወር፣ በሀያት ፈረስ ቤት እና በቦሌ ቡልቡላ አካባቢዎች የሚገነቡ ተጨማሪ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች እንደሚያስረክብ አስታውቀዋል።
ሀሮት ሪል ስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለገበያ በማቅረቡ በፈረንጆቹ 2025 በተካሄደው የኢትዮ ሪል ስቴት ሽልማት መርሃ ግብር ላይ በጥራትና በዋጋ አቅርቦት የአሸናፊነት ክብርን ያገኘ ድርጅት መሆኑ አብራርታለች።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር በኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴልና በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ኢንቨስትመንቱን ይበልጥ በማስፋፋት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
ባለሃብቱ አቶ ሰኢድ ይህ ስኬት የአንድ ሰው ጥረትና ውጤት ብቻ አይደለም። ከጀርባው ብዙ እጆች፣ ብዙ ዱአዎች እና ጸሎቶች፣ ብዙ ምክሮች ያሉበት ነው። በዚህ መሠረት ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ ለኢንቨስትመንት ቢሮ፣ ለጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቲናው አበባ ልማት አ/ማሀበር ለሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ለባለሙያዎች እና ለሠራተኞቻችን ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
አቶ ሰኢድ የትምህርት ሕይወታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጥታ የተቀላቀሉት የንግዱን ዓለም ሲሆን፣ መጀመሪያ ላይ በመኪና መለዋወጫ ንግድ በመሰማራትና በመቀጠልም ወደ አስመጪና ላኪነት ዘርፍ በመሸጋገር ረጅም ዓመታትን አሳልፈዋል። በሂደትም የንግድ ሥራቸውን በማስፋት የጀመሩት የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ገና በጅማሮው ከፍተኛ የምስጋና ሽልማትና ዕውቅናን ሊያጎናጽፋቸው ችሏል። ባለሀብቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ማኑፋክቸሪንግና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት በመግባት ላይ ይገኛሉ።
በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ያጋጠማቸው የአስተዳደር ፈተና ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሰይድ ሲመልሱ፣ ምንም ዓይነት ችግር እንዳልገጠማቸው በአጽንኦት ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ ከላይ እስከ ታች ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአስተዳደር አካላት አንድ ባለሀብት እውነተኛ አልሚ መሆኑን ከተረዱ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ የገለጹት አቶ ሰይድ፣ ለእሳቸውም የተደረገላቸውን ተገቢውን ድጋፍና ትብብር በሙሉ አመስግነዋል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ
"በዞናችን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶች ሁሉ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ዝግጁ ነን፣ በቁርጠኝነትም እንሠራለን! ... ዛሬ ኑ" ሲሉ ተደምጠዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ፦ "የጉራጌ ማህበረሰብ በሀገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች ከተሞችን በማልማትና ጠንካራ የንግድ ሥርዓት በመዘርጋት የሚታወቅ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ባለሀብቶች ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው በልማት እየሳተፉ መሆኑ እጅግ ያስደስታል። ይህ ፋብሪካ የሀገር ሀብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል። ሌሎች ባለሀብቶችም በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።"ለአገርና ለሕዝብ መልዕክታቸውን አሰምተዋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት ዶክተር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እና የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አባስ መሀመድን ጨምሮ በርካታ የአመራር አካላት ተገኝተዋል።
"Vita, saluti, peace, life" blends Italian and English expressions of well-being, translating roughly to "life, greetings, peace, and life." This combination evokes a deep desire for a harmonious, healthy existence filled with good energy and wellness.
#manufacturing #factoryinauguration #centralethiopia #guragezone #investment #harotrealestate #vitasaluti #economicgrowth #realestate #housing #bolebulbula #homeownership #ethiopianbusiness #ኢንቨስትመንት #ሪልስቴት #ኢንዱስትሪ #ልማት #የሥራዕድል #ቢዝነስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የቴክኖሎጂ እና የማኑፋክቸሪንግ ጥምረት - የሀገራዊ ብልጽግና አዲስ ሞተር
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የኢኮኖሚ መዋቅር ውስጥ እየታየ ላለው የተቀናጀ የለውጥ ጉዞ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ ማሳያ ነው።
ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና የግንባታ ዘርፎች ትልቅ የለውጥ ማዕበል ፈጥረዋል።
ቀደም ሲል በባሕላዊ አሠራር የተተበተበው የግንባታ ኢንዱስትሪ እና በጥሬ ዕቃ ላኪነት የተወሰነው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ፣ ዛሬ በቴክኖሎጂ ታግዘው እና እጅ እና ጓንት ሆነው የሀገር የጀርባ አጥንት ወደ መሆን ተሸጋግረዋል።
የመንግሥት ከፍተኛ የካፒታል በጀት ምደባ፣ የግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች መፈፀም፣ የከተሞች በፍጥነት መስፋፋት እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ዘርፎቹን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግረዋቸዋል።
በተለይም ባለፉት ዓመታት የተገነቡት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ማኑፋክቸሪንግ ለሚደረገው ታሪካዊ መዋቅራዊ ሽግግር ተወዳዳሪ የሌለው ሚና በመጫወት ለግሉ ዘርፍ አዲስ የብርሃን በር ከፍተዋል።
አሁን በደረስንበት ደረጃ ላይ ሆነን ስንመዝነው፣ ይህ የዘመናት የልማት ሕልም ከወረቀት አልፎ በተግባር መሬት እየረገጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት የጎበኙት እና በ3ዲ ሕትመት፣ በቅድመ-ዝግጅት ቀላል ዓረብ ብረት እና በኮንቴይነር መኖሪያ ቤቶች ጥምረት በጥቂት ቀናት ውስጥ የተገነባው ዘመናዊ መንደር፣ ፍጥነት እና ጥራት እርስ በርስ የማይጋጩ መሆናቸውን ያረጋገጠ ሕያው ምስክር ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማሳደግ እና ማበረታቻዎችን በአፈጻጸም ላይ የመሠረቱ ፖሊሲዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ እየሳቡ ይገኛሉ።
በግንባር ቀደምትነት የሚመራው የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄም የገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ አስደናቂ ድሎችን እያስመዘገበ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ 4 ነጥብ 85 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የገቢ ምርትን በጥራት መተካት መቻሉ እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የ10.1% ዕድገት ማስመዝገቡ ትልቅ ስኬት ነው።
ቀደም ሲል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣባቸው የነበሩ እንደ መከላከያ እና ፖሊስ አልባሳት፣ ዘመናዊ የውኃ ቆጣሪዎች፣ የምግብ እና መጠጥ ውጤቶች አሁን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ እየተመረቱ ይገኛሉ።
ከዚህ ባለፈም በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣት ሴቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩ እና የኤኮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን በተግባር ማሳየታቸው አሁን ያለንበትን የላቀ ቁመና ያሳያል።
ሆኖም “ሳይቸግር ጤፍ ብድር” እንዲሉ የተመዘገቡት ስኬቶች በፈተናዎች እና በተግዳሮቶች የተከበቡ መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም። የዓለም አቀፍ ሎጂስቲክስ መጓተት፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች ፍላጎት እና አቅርቦት አለመመጣጠን አሁንም እየታገሉን ያሉ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች ናቸው። ስለዚህ ይህ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ዘላቂ እና ቀጣይ እንዲሆን ከተፈለገ ወደፊት በትኩረት ሊሠሩ የሚገባቸው ወሳኝ የቤት ሥራዎች አሉ።
በመጀመሪያ የውጭ ጥገኝነትን ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የብረት እና ሌሎች ዋና ዋና የማጠናቀቂያ ቁሳቁሶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ይገባል።
በሁለተኛ ደረጃ በግንባታው ዘርፍ የሕንፃ መረጃ ሞዴሊንግ (BIM) እና ዘመናዊ የዲጂታል መከታተያ መተግበሪያዎችን በስፋት በመጠቀም ብክነትን እና ጊዜን የመቀነስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
በሦስተኛ ደረጃ የሕግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎችን በማጠናከር፣ የኮንትራት አስተዳደርን ማዘመን እና የግል እና የመንግሥት አጋርነትን (PPP) ማበረታታት የግድ ይላል።
“ካለፈው ስህተት የተማረ፣ ለወደፊቱ ብልህ ነው” እንደሚባለው፣ የተገኙትን መልካም አጋጣሚዎች በማስፋት እና ድክመቶችን በማረም፣ የጀመርነውን የኢንዱስትሪ ብልጽግና ጉዞ ብሩህ እና ተስፋ ሰጪ ማድረግ የምንችለው በዚሁ በቆራጥነት እና በጋራ የመሥራት ቀጣይነት ባለው መርሕ ላይ ስንጓዝ ብቻ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #manufacturing #technology
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የኢኮኖሚ መዋቅር ውስጥ እየታየ ላለው የተቀናጀ የለውጥ ጉዞ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ዋነኛ ማሳያ ነው።
ባለፉት አምስት ዓመታት የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና የግንባታ ዘርፎች ትልቅ የለውጥ ማዕበል ፈጥረዋል።
ቀደም ሲል በባሕላዊ አሠራር የተተበተበው የግንባታ ኢንዱስትሪ እና በጥሬ ዕቃ ላኪነት የተወሰነው የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ፣ ዛሬ በቴክኖሎጂ ታግዘው እና እጅ እና ጓንት ሆነው የሀገር የጀርባ አጥንት ወደ መሆን ተሸጋግረዋል።
የመንግሥት ከፍተኛ የካፒታል በጀት ምደባ፣ የግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች መፈፀም፣ የከተሞች በፍጥነት መስፋፋት እንዲሁም የአረንጓዴ ዐሻራ እና የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ዘርፎቹን ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግረዋቸዋል።
በተለይም ባለፉት ዓመታት የተገነቡት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ማኑፋክቸሪንግ ለሚደረገው ታሪካዊ መዋቅራዊ ሽግግር ተወዳዳሪ የሌለው ሚና በመጫወት ለግሉ ዘርፍ አዲስ የብርሃን በር ከፍተዋል።
አሁን በደረስንበት ደረጃ ላይ ሆነን ስንመዝነው፣ ይህ የዘመናት የልማት ሕልም ከወረቀት አልፎ በተግባር መሬት እየረገጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት የጎበኙት እና በ3ዲ ሕትመት፣ በቅድመ-ዝግጅት ቀላል ዓረብ ብረት እና በኮንቴይነር መኖሪያ ቤቶች ጥምረት በጥቂት ቀናት ውስጥ የተገነባው ዘመናዊ መንደር፣ ፍጥነት እና ጥራት እርስ በርስ የማይጋጩ መሆናቸውን ያረጋገጠ ሕያው ምስክር ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ወደ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የማሳደግ እና ማበረታቻዎችን በአፈጻጸም ላይ የመሠረቱ ፖሊሲዎች የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ እየሳቡ ይገኛሉ።
በግንባር ቀደምትነት የሚመራው የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄም የገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ረገድ አስደናቂ ድሎችን እያስመዘገበ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ 4 ነጥብ 85 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የገቢ ምርትን በጥራት መተካት መቻሉ እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የ10.1% ዕድገት ማስመዝገቡ ትልቅ ስኬት ነው።
ቀደም ሲል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣባቸው የነበሩ እንደ መከላከያ እና ፖሊስ አልባሳት፣ ዘመናዊ የውኃ ቆጣሪዎች፣ የምግብ እና መጠጥ ውጤቶች አሁን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ እየተመረቱ ይገኛሉ።
ከዚህ ባለፈም በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣት ሴቶች የሥራ ዕድል መፈጠሩ እና የኤኮ-ኢንዱስትሪ ፓርኮች የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን በተግባር ማሳየታቸው አሁን ያለንበትን የላቀ ቁመና ያሳያል።
ሆኖም “ሳይቸግር ጤፍ ብድር” እንዲሉ የተመዘገቡት ስኬቶች በፈተናዎች እና በተግዳሮቶች የተከበቡ መሆናቸውን መዘንጋት የለብንም። የዓለም አቀፍ ሎጂስቲክስ መጓተት፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች ፍላጎት እና አቅርቦት አለመመጣጠን አሁንም እየታገሉን ያሉ መዋቅራዊ ተግዳሮቶች ናቸው። ስለዚህ ይህ የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ዘላቂ እና ቀጣይ እንዲሆን ከተፈለገ ወደፊት በትኩረት ሊሠሩ የሚገባቸው ወሳኝ የቤት ሥራዎች አሉ።
በመጀመሪያ የውጭ ጥገኝነትን ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የብረት እና ሌሎች ዋና ዋና የማጠናቀቂያ ቁሳቁሶችን በሀገር ውስጥ የማምረት አቅምን በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ይገባል።
በሁለተኛ ደረጃ በግንባታው ዘርፍ የሕንፃ መረጃ ሞዴሊንግ (BIM) እና ዘመናዊ የዲጂታል መከታተያ መተግበሪያዎችን በስፋት በመጠቀም ብክነትን እና ጊዜን የመቀነስ የቴክኖሎጂ ሽግግር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
በሦስተኛ ደረጃ የሕግ እና የቁጥጥር ማዕቀፎችን በማጠናከር፣ የኮንትራት አስተዳደርን ማዘመን እና የግል እና የመንግሥት አጋርነትን (PPP) ማበረታታት የግድ ይላል።
“ካለፈው ስህተት የተማረ፣ ለወደፊቱ ብልህ ነው” እንደሚባለው፣ የተገኙትን መልካም አጋጣሚዎች በማስፋት እና ድክመቶችን በማረም፣ የጀመርነውን የኢንዱስትሪ ብልጽግና ጉዞ ብሩህ እና ተስፋ ሰጪ ማድረግ የምንችለው በዚሁ በቆራጥነት እና በጋራ የመሥራት ቀጣይነት ባለው መርሕ ላይ ስንጓዝ ብቻ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #manufacturing #technology
2 months ago
በኢንዱስትሪ ሽግግር ጉዟችን ተጨባጭ ለውጥ እያመጣንባቸው ያሉት ተኪ ምርቶቻችን
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
2 months ago
የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ያስገኘው ትሩፋት
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የአምራች ዘርፉን አቅም ለማሳደግ ትልቅ መሠረት እየጣሉ ያሉት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን
************
እያደገ በመጣው የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ሚና በዋናነት ተጠቃሽ ነው።
ሀገራችን በአሁኑ ወቅት ሁሉንም ዓይነት ኢንቨስትመንት ተቀብለው ማስተናገድ የሚችሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ባለሃብቶችን ተቀብላ በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።
እነዚህ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በተለይም ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።
አሁን ባለው ሁኔታ የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ምርቶቻቸውን በዋናነት ለዓለም ገበያ እንዲያቀርቡ ይበረታታሉ።
በዚሁ መሠረት እንደ ጨርቃ ጨርቅ፣ አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ያሉ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት ላይ ይገኛሉ።
እነዚህ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከኢኮኖሚ ምንጭነታቸው ባሻገር ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችና ባለሙያዎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በፓርኮቹ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የሀገር ውስጥ የሰው ኃይልን በስፋት የሚጠቀሙ በመሆናቸው፣ ወጣቱ ትውልድ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የላቀ የኢንዱስትሪ አመራር ክህሎትን በቀጥታ እንዲቀስም ምቹ መድረክ ፈጥረውለታል።
ይህም የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የአምራች ዘርፉን ሀገራዊ አቅም ለማሳደግ ትልቅ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
ትናንት በይፋ የተመረቀው የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክም የኢትዮጵያን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለዓለም ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርግ ነው።
ከተመሠረተ 11 ዓመታትን ብቻ ያስቆጠረው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ እንደ ቻይና ያሉ ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር በመላው ሀገራችን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ 14 ልዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ገንብቶ በማስተዳደር ላይ ይገኛል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #industrialparks #specialeconomiczones #ebc
************
እያደገ በመጣው የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የኢንዱስትሪ ፓርኮችና የልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ሚና በዋናነት ተጠቃሽ ነው።
ሀገራችን በአሁኑ ወቅት ሁሉንም ዓይነት ኢንቨስትመንት ተቀብለው ማስተናገድ የሚችሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ባለሃብቶችን ተቀብላ በማስተናገድ ላይ ትገኛለች።
እነዚህ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በተለይም ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለሚደረገው ሽግግር ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ።
አሁን ባለው ሁኔታ የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ምርቶቻቸውን በዋናነት ለዓለም ገበያ እንዲያቀርቡ ይበረታታሉ።
በዚሁ መሠረት እንደ ጨርቃ ጨርቅ፣ አልባሳት፣ ቆዳና የቆዳ ውጤቶች ያሉ ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት ላይ ይገኛሉ።
እነዚህ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ከኢኮኖሚ ምንጭነታቸው ባሻገር ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችና ባለሙያዎች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በፓርኮቹ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች የሀገር ውስጥ የሰው ኃይልን በስፋት የሚጠቀሙ በመሆናቸው፣ ወጣቱ ትውልድ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምንና የላቀ የኢንዱስትሪ አመራር ክህሎትን በቀጥታ እንዲቀስም ምቹ መድረክ ፈጥረውለታል።
ይህም የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማፋጠን የአምራች ዘርፉን ሀገራዊ አቅም ለማሳደግ ትልቅ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
ትናንት በይፋ የተመረቀው የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክም የኢትዮጵያን ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጭ ለዓለም ይበልጥ ተደራሽ የሚያደርግ ነው።
ከተመሠረተ 11 ዓመታትን ብቻ ያስቆጠረው የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ እንደ ቻይና ያሉ ሀገራትን ተሞክሮ በመቀመር በመላው ሀገራችን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ 14 ልዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ገንብቶ በማስተዳደር ላይ ይገኛል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #industrialparks #specialeconomiczones #ebc
3 months ago
ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ ምሉዕ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን በሁሉም መስክ አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ደግሞ የዚህ መርኃችን ዋነኛ ዓምድ ነው።
#ኢትዮጵያታምርት #madeinethiopia #ethiopiatamrit #economicsovereignty #ethiopiandevelopment #manufacturing #industrialrevolution #homegrowneconomy
3 months ago
ከመሸመት ወደ ማምረት፡ የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ስኬቶች
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢኮኖሚ መዋቅሯን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር ግዙፍና ታሪካዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።
ይህ የሽግግር ጉዞ የሀገራችንን የብልጽግና ራዕይ ከማሳካት ባለፈ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና ራስን ለመቻል እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ተወስዷል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረትና ተግባራዊ የተደረጉት አዳዲስ ፖሊሲዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ከነበረበት የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ ወጥቶ ወደ ተሻለ የማምረት አቅም እንዲሸጋገር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገት ቀደም ሲል ከነበረበት 4.8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 10.7 በመቶ በመመንጠቅ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።
ሙሉ ዘገባውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ebc
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢኮኖሚ መዋቅሯን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር ግዙፍና ታሪካዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።
ይህ የሽግግር ጉዞ የሀገራችንን የብልጽግና ራዕይ ከማሳካት ባለፈ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና ራስን ለመቻል እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ተወስዷል።
መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረትና ተግባራዊ የተደረጉት አዳዲስ ፖሊሲዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ከነበረበት የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ ወጥቶ ወደ ተሻለ የማምረት አቅም እንዲሸጋገር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገት ቀደም ሲል ከነበረበት 4.8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 10.7 በመቶ በመመንጠቅ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።
ሙሉ ዘገባውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ebc
3 months ago
የኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነት፡ ከውጭ ጥገኝነት ራስን ወደ መቻል የሚደረግ ሽግግር
*******************
ኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያደረገችው ያለው ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሀገራችን መድኃኒትን ማምረት እንደ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ብቻ ሳይሆን እንደ ብሔራዊ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ በመቁጠር ስትራቴጂካዊ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም በቅርቡ የተመረቀው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) በላቁ ላቦራቶሪዎቹ እና በባዮኢኩቫለንስ ማዕከሉ ለዘርፉ የቴክኒክ ጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተገኘው ትምህርት የኢንዱስትሪ ፖሊሲያችንን የቀየረ ሲሆን፣ ከ90 በመቶ በላይ የነበረውን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ብሔራዊ ፍላጎቱን 44 በመቶ መሸፈን ችሏል።
ይህ አቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ 55 በመቶ ለማድረስ በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም የ"ShieldVax Enterprise" ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የክትባት ምርት ማዕከል ለማድረግና ከጥሬ ዕቃ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የማምረት (End-to-End manufacturing) ግብ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገበው የ58 በመቶ የተኪ ምርት አፈጻጸም ለጤናው ዘርፍ ትልቅ ተስፋን የሰጠ ነው።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ራስን ለመቻል የተቀመጠው ግብም በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስኬቱ እውን መሆኑ አይቀሬ ነው።
የኢትዮጵያ ዕድገት በዜጎች ጤና እና በምርታማነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ስለ ትንታኔው ዝርዝር መረጃ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pharmaceuticalsovereignty #healthcareindependence #ahri #shieldvax #selfsufficiency
*******************
ኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያደረገችው ያለው ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሀገራችን መድኃኒትን ማምረት እንደ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ብቻ ሳይሆን እንደ ብሔራዊ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ በመቁጠር ስትራቴጂካዊ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም በቅርቡ የተመረቀው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) በላቁ ላቦራቶሪዎቹ እና በባዮኢኩቫለንስ ማዕከሉ ለዘርፉ የቴክኒክ ጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተገኘው ትምህርት የኢንዱስትሪ ፖሊሲያችንን የቀየረ ሲሆን፣ ከ90 በመቶ በላይ የነበረውን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ብሔራዊ ፍላጎቱን 44 በመቶ መሸፈን ችሏል።
ይህ አቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ 55 በመቶ ለማድረስ በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም የ"ShieldVax Enterprise" ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የክትባት ምርት ማዕከል ለማድረግና ከጥሬ ዕቃ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የማምረት (End-to-End manufacturing) ግብ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገበው የ58 በመቶ የተኪ ምርት አፈጻጸም ለጤናው ዘርፍ ትልቅ ተስፋን የሰጠ ነው።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ራስን ለመቻል የተቀመጠው ግብም በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስኬቱ እውን መሆኑ አይቀሬ ነው።
የኢትዮጵያ ዕድገት በዜጎች ጤና እና በምርታማነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ስለ ትንታኔው ዝርዝር መረጃ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pharmaceuticalsovereignty #healthcareindependence #ahri #shieldvax #selfsufficiency
3 months ago
u12e8u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d) u12aeu1235u1273u122b u1295u130du130du122d...u12a5u12e8u1208u1218u1291 u1209u12d3u120bu12cau1290u1275 u12e8u1208u121d...u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1273u121du122du1275 |MadeinEthiopia |u12e8u1200u1308u122du1309u12f3u12ed
#pmabiyahemedali #ethiopia #manufacturing #industry #development ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኮስታራ ንግግር...እየለመኑ ሉዓላዊነት የለም...ኢትዮጵያ ታምርት |MadeinEthiopia |የሀገርጉዳይ
#pmabiyahemedali #ethiopia #manufacturing #industry #development
3 months ago
የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው - የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል
*****************
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ላይ የቀረቡት ምርቶች ብዝሃነት እና ጥራት፣ ኢትዮጵያ በጥረቷ እና በልጆቿ የፈጠራ አቅም ብልጽግናዋን ማረጋገጥ እንደምትችል የሚመሰክር ነው ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ፈጠራዎች የደረሱበትን ትልቅ ደረጃም የሚያመላክት ነው ብለዋል ሚኒስትሩ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር።
በመደመር እሳቤ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማካሄድ እና የቢዝነስ ምህዳሩን ምቹ በማድረግ፣ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ምክንያት የማምረት አቅምን በማሳደግ፣ ገቢ ምርትን በመተካት እና ኤክስፖርትን በማሻሻል እንዲሁም የሥራ ዕድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ይበልጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድም ባለፉት 9 ወራት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 222 ኤግዚቢሽኖች ተዘጋጅተው 17 ሺህ 461 አምራቾች ምርቶቻቸውን ማስተዋወቃቸውን አንስተዋል።
በኤግዚቢሽኖቹ ለህብረተሰቡ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ 3.6 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የግብይት ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፣ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ሁኔታ መቀየሩን ገልጸዋል።
በነስሩ ጀማል
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc
*****************
4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2018 ላይ የቀረቡት ምርቶች ብዝሃነት እና ጥራት፣ ኢትዮጵያ በጥረቷ እና በልጆቿ የፈጠራ አቅም ብልጽግናዋን ማረጋገጥ እንደምትችል የሚመሰክር ነው ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገለጹ።
ኤክስፖው ሀገር በቀል ፈጠራዎች የደረሱበትን ትልቅ ደረጃም የሚያመላክት ነው ብለዋል ሚኒስትሩ በኤግዚቢሽኑ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር።
በመደመር እሳቤ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ የብሔራዊ ሉዓላዊነታችን ማዕከል ነው ያሉት ሚኒስትሩ፣ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ለዘርፉ በተሰጠው ልዩ ትኩረት የፖሊሲ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት፣ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማካሄድ እና የቢዝነስ ምህዳሩን ምቹ በማድረግ፣ ሰፋፊ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ምክንያት የማምረት አቅምን በማሳደግ፣ ገቢ ምርትን በመተካት እና ኤክስፖርትን በማሻሻል እንዲሁም የሥራ ዕድልን በመፍጠር ተጨባጭ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን ይበልጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ በማድረግ ረገድም ባለፉት 9 ወራት ብቻ በመላ ሀገሪቱ 222 ኤግዚቢሽኖች ተዘጋጅተው 17 ሺህ 461 አምራቾች ምርቶቻቸውን ማስተዋወቃቸውን አንስተዋል።
በኤግዚቢሽኖቹ ለህብረተሰቡ ምርትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ 3.6 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የግብይት ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፣ ይህም የዜጎችን የሀገር ውስጥ ምርት የመጠቀም ባህል በከፍተኛ ሁኔታ መቀየሩን ገልጸዋል።
በነስሩ ጀማል
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc
3 months ago
ኢትዮጵያ ታምርት ፡ በራስ ላብ፣ የራስ ምርት
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት በገቢ ምርቶች ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የኖረ ኢኮኖሚ የራስን ሉዓላዊነት ሙሉ አያደርገውም። የሀገር ብልጽግና መሠረቱ ደግሞ በባዕድ እጅ የሚሰፈር ሳይሆን በራስ ላብና ጥረት የሚመረት መሆኑ አያጠያይቅም።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን የተጋረጡብንን የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ፈተናዎችን በመሻገር የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከአንቀላፋበት ቀስቅሶ ሕይወት ዘርቶበታል። ይህ ንቅናቄ ዝም ብሎ የቃላት ጋጋታ ሳይሆን “ላብ ካልፈሰሰ፣ አዝመራ የለም” የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳየ፣ የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነታችንን ያበሰረ ብርቱ የለውጥ ማዕበል ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ የለውጡ ጉዞ ውጤታማነት በቁጥር ብቻ ሳይሆን በገበያ ድርሻም ተረጋግጧል። ከሦስት ዓመት በፊት 30 በመቶ ብቻ የነበረው የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻ ዛሬ 41 በመቶ ደርሷል። ይህ መሻሻል ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን፣ ሥራ አቁመው የነበሩ 830 ኢንዱስትሪዎችን ዳግም ወደ ማምረት በመመለስና 325 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችን በአዲስ መንፈስ ወደ ሥራ በማስገባት የተገኘ ድል ነው።
በተለይም ከለውጡ በፊት 8 ሺህ ገደማ የነበሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ዛሬ 26 ሺህ መድረሳቸው፣ ኢኮኖሚው ከመንግሥት መርነት ወደ ግሉ ዘርፍ መዘዋወሩንና የዜጎች የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነት መጎልበቱን ያሳያል። “ታጥቦ ጭቃ” መሆንን አቁመን፣ በገዛ ደጃችን ተኪ ምርቶችን እያመረትን መገኘታችን የኢኮኖሚ ነፃነታችን ማሳያ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ትስስርም ሌላኛው የንቅናቄው ስኬት ነው። ቡና፣ ሻይና ሩዝ በገበሬው እጅ ብቻ ተመርተው ሳይሆን በፋብሪካዎች እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍ አድርጎታል።
“ሳይቀደሙ መቅደም” እንዲሉ መከላከያና ፖሊስ ከውጭ በውድ ምንዛሬ የሚገዛ የደንብ ልብስን ትተው ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካታቸው፣ እንዲሁም የብቅል ገብስ ዘርን እዚሁ ማምረት መቻላችን 3 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን አስችሏል። በተጨማሪም የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳና የምግብ ኢንዱስትሪዎች እምቅ አቅማቸውን እያወጡ ይገኛሉ።
የጥራት መንደር አበርክቶ ደግሞ ለዚህ ሁሉ ስኬት ሞተር ነው። በዓመት 5.2 ሚሊዮን ቶን ምርትን የመመርመር አቅም ያለው ይህ ተቋም፣ የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የጥራት ደረጃቸው እንዲጠበቅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት ይህ ተቋም በዓለም የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ያለንን ተሳትፎ የሚያጎለብት የብልጽግናችን መተማመኛ ነው።
በአጠቃላይ "ኢትዮጵያ ታምርት" ከሸቀጥ ግብይት ባለፈ "የኢትዮጵያ ይሸጥ" የሚል ኩሩ እሳቤን ይዟል። 235 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የወጣቶችን ሕይወት የቀየረው ይህ ንቅናቄ፣ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢኮኖሚ ነፃነታችንን የሚያጸና ነው። በጋራ ካመረትንና የራሳችንን ምርት ከተጠቀምን፣ የብልጽግና ጉዟችን የማይቀለበስ ይሆናል።
ኢትዮጵያ ታምርት፣ ኢትዮጵያ ትበልጽግ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #industry #manufacturing #importsubstitution #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc #ebcdotstream
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት በገቢ ምርቶች ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የኖረ ኢኮኖሚ የራስን ሉዓላዊነት ሙሉ አያደርገውም። የሀገር ብልጽግና መሠረቱ ደግሞ በባዕድ እጅ የሚሰፈር ሳይሆን በራስ ላብና ጥረት የሚመረት መሆኑ አያጠያይቅም።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን የተጋረጡብንን የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ፈተናዎችን በመሻገር የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከአንቀላፋበት ቀስቅሶ ሕይወት ዘርቶበታል። ይህ ንቅናቄ ዝም ብሎ የቃላት ጋጋታ ሳይሆን “ላብ ካልፈሰሰ፣ አዝመራ የለም” የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳየ፣ የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነታችንን ያበሰረ ብርቱ የለውጥ ማዕበል ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ የለውጡ ጉዞ ውጤታማነት በቁጥር ብቻ ሳይሆን በገበያ ድርሻም ተረጋግጧል። ከሦስት ዓመት በፊት 30 በመቶ ብቻ የነበረው የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻ ዛሬ 41 በመቶ ደርሷል። ይህ መሻሻል ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን፣ ሥራ አቁመው የነበሩ 830 ኢንዱስትሪዎችን ዳግም ወደ ማምረት በመመለስና 325 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችን በአዲስ መንፈስ ወደ ሥራ በማስገባት የተገኘ ድል ነው።
በተለይም ከለውጡ በፊት 8 ሺህ ገደማ የነበሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ዛሬ 26 ሺህ መድረሳቸው፣ ኢኮኖሚው ከመንግሥት መርነት ወደ ግሉ ዘርፍ መዘዋወሩንና የዜጎች የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነት መጎልበቱን ያሳያል። “ታጥቦ ጭቃ” መሆንን አቁመን፣ በገዛ ደጃችን ተኪ ምርቶችን እያመረትን መገኘታችን የኢኮኖሚ ነፃነታችን ማሳያ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ትስስርም ሌላኛው የንቅናቄው ስኬት ነው። ቡና፣ ሻይና ሩዝ በገበሬው እጅ ብቻ ተመርተው ሳይሆን በፋብሪካዎች እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍ አድርጎታል።
“ሳይቀደሙ መቅደም” እንዲሉ መከላከያና ፖሊስ ከውጭ በውድ ምንዛሬ የሚገዛ የደንብ ልብስን ትተው ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካታቸው፣ እንዲሁም የብቅል ገብስ ዘርን እዚሁ ማምረት መቻላችን 3 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን አስችሏል። በተጨማሪም የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳና የምግብ ኢንዱስትሪዎች እምቅ አቅማቸውን እያወጡ ይገኛሉ።
የጥራት መንደር አበርክቶ ደግሞ ለዚህ ሁሉ ስኬት ሞተር ነው። በዓመት 5.2 ሚሊዮን ቶን ምርትን የመመርመር አቅም ያለው ይህ ተቋም፣ የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የጥራት ደረጃቸው እንዲጠበቅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት ይህ ተቋም በዓለም የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ያለንን ተሳትፎ የሚያጎለብት የብልጽግናችን መተማመኛ ነው።
በአጠቃላይ "ኢትዮጵያ ታምርት" ከሸቀጥ ግብይት ባለፈ "የኢትዮጵያ ይሸጥ" የሚል ኩሩ እሳቤን ይዟል። 235 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የወጣቶችን ሕይወት የቀየረው ይህ ንቅናቄ፣ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢኮኖሚ ነፃነታችንን የሚያጸና ነው። በጋራ ካመረትንና የራሳችንን ምርት ከተጠቀምን፣ የብልጽግና ጉዟችን የማይቀለበስ ይሆናል።
ኢትዮጵያ ታምርት፣ ኢትዮጵያ ትበልጽግ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #industry #manufacturing #importsubstitution #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc #ebcdotstream
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የሀገራችንን 80 በመቶ የቆርኪ ምርት ፍላጎት የሚሸፍን ቆርኪ ፋብሪካ ተመረቀ
***************
በቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና አዲስ የተመረቀው ፋብሪካ የመጠጥ ማሸጊያ ቆርኪ ምርት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ እንዲተካ እንደሀገር እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዝ እንደሆነ ተገልጿል።
በዘርፉ ከተሰማሩ ተቋማት መካከል የዛሬ 14 ዓመት የተመሠረተው "ፔንኤል ኢንደስትሪ" የማስፋፊያ ፋብሪካውን በቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ በዛሬው እለት አስመርቋል።
የፋብሪካው መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ብርቱካን አበበ እንደገለጹት ፋብሪካው ለውጭ ምንዛሬ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከማስቀረት ባለፈ ምርት ለማስመጣት ይፈጅ የነበረውን ከ3 እስከ 4 ወራት ጊዜ ወደ 10 ቀናት ዝቅ ማድረግ ችሏል።
ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረውና የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር እያመጣ የሚገኘው ይህ ፋብሪካ፤ በዓመት ከ4 ሚሊዮን በላይ ቆርኪዎችን የማምረት አቅም እንዳለውም ተመላክቷል።
ቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንደስትሪ መር ለማሸጋገር ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።
በዞኑ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ 250 አልሚዎችና ኢንቨስተሮች መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል።
ይህም ቀደም ሲል ለውጭ ኢንቨስተሮች ብቻ ተገድቦ የነበረውን አሠራር የቀየረ ሲሆን፤ አልሚዎቹ ምርቶቻቸውን ለውጭ ገበያ ብቻ ሳይሆን ከ50 እስከ 100 በመቶ ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡም ይፈቀድላቸዋል።
በሳራ ሳህለሥላሴ
#ethiopia #ebc #specialeconomiczone #industry #localinvestors #ipdc #manufacturing
***************
በቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘው እና አዲስ የተመረቀው ፋብሪካ የመጠጥ ማሸጊያ ቆርኪ ምርት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ እንዲተካ እንደሀገር እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዝ እንደሆነ ተገልጿል።
በዘርፉ ከተሰማሩ ተቋማት መካከል የዛሬ 14 ዓመት የተመሠረተው "ፔንኤል ኢንደስትሪ" የማስፋፊያ ፋብሪካውን በቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ በዛሬው እለት አስመርቋል።
የፋብሪካው መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ ብርቱካን አበበ እንደገለጹት ፋብሪካው ለውጭ ምንዛሬ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ከማስቀረት ባለፈ ምርት ለማስመጣት ይፈጅ የነበረውን ከ3 እስከ 4 ወራት ጊዜ ወደ 10 ቀናት ዝቅ ማድረግ ችሏል።
ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል የፈጠረውና የቴክኖሎጂ ዕውቀት ሽግግር እያመጣ የሚገኘው ይህ ፋብሪካ፤ በዓመት ከ4 ሚሊዮን በላይ ቆርኪዎችን የማምረት አቅም እንዳለውም ተመላክቷል።
ቦሌ ለሚ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ከግብርና ወደ ኢንደስትሪ መር ለማሸጋገር ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።
በዞኑ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ 250 አልሚዎችና ኢንቨስተሮች መካከል 60 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን የኢንደስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታውቋል።
ይህም ቀደም ሲል ለውጭ ኢንቨስተሮች ብቻ ተገድቦ የነበረውን አሠራር የቀየረ ሲሆን፤ አልሚዎቹ ምርቶቻቸውን ለውጭ ገበያ ብቻ ሳይሆን ከ50 እስከ 100 በመቶ ለሀገር ውስጥ ገበያ እንዲያቀርቡም ይፈቀድላቸዋል።
በሳራ ሳህለሥላሴ
#ethiopia #ebc #specialeconomiczone #industry #localinvestors #ipdc #manufacturing
3 months ago
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የላቀ የምርት አፈፃፀም እና የፋብሪካዎች ትርፋማነት ሪፖርት
#ethiopia | የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የ2017 በጀት ዓመት ሙሉ ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀምን ይፋ አድርጓል፡፡
ግሩፑ ባወጣው መረጃ መሠረት በኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት እና ቁጥር ሦስት ስኳር ፋብሪካዎች አማካኝነት በ2017 የምርት ዘመን 32,806.25 ቶን ስኳር እና 46,204.86 ቶን ሞላሰስ ማምረት ተችሏል፡፡
ይህ አፈፃፀም ከቀደመው የ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በስኳር ምርት የ33 በመቶ እንዲሁም በሞላሰስ ምርት የ46 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
በፋይናንስ ረገድ ሁለቱም ፋብሪካዎች በ2017 በጀት ዓመት ከወጪ ቀሪ የ1.5 ቢሊዮን ብር ጥሬ ገንዘብ ትርፍ ያስመዘገቡ ሲሆን በወቅቱ ያልተሸጡ ምርቶችን ጨምሮ አጠቃላይ ትርፋቸው 3.159 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
ፋብሪካዎቹ ባሳዩት ውጤታማነት ምክንያት ለሠራተኞቻቸው የሦስት እርከን የደመወዝ ጭማሪ አድርገዋል፡፡
በተጨማሪም ለመንግስት የሚከፈል የታክስ መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ በመጨመር 970.4 ሚሊዮን ብር ለሀገር ገቢ ሆኗል፡፡
ለስኳር ኢንዱስትሪ ልማት ፈንድ (SIDF) ደግሞ 686.1 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋፅኦ ተደርጓል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀምን በተመለከተ በሁለቱ ፋብሪካዎች 28,741 ቶን ስኳር እና 24,694 ቶን ሞላሰስ ተመርቷል፡፡
ምንም እንኳን በአካባቢው በነበረው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የምርት ሂደቱ ለጊዜው ቢቆምም በደረቅ ወራት በሚከናወነው ሁለተኛ ዙር ምርት የዓመቱ አፈፃፀም ከ2017 የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ 374.7 ሚሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ የተመዘገበ ሲሆን ለመንግስት 838.7 ሚሊዮን ብር ታክስ ተከፍሏል፡፡
ከስኳር ምርት ባሻገር ፋብሪካዎቹ በግብርና እና በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ተሰማርተው የገቢ ምንጫቸውን በማስፋፋት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኦሞ እና በአርጆ ዴዴሳ ፋብሪካዎች የዶሮ፣ የዓሳ፣ የከብት ማድለብ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በመከናወኑ ተጨማሪ 30.69 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል፡፡
በአጠቃላይ ከለውጡ በፊት በከፍተኛ ዕዳ እና የአሠራር ችግር ውስጥ የነበሩት እነዚህ ፋብሪካዎች በአሁኑ ወቅት ውጤታማ ወደመሆን ተሸጋግረዋል፡፡
ተከማችቶ የነበረውን የቆየ ዕዳ በመክፈል ረገድም በ2017 ዓ.ም 378 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ 458.8 ሚሊዮን ብር በላይ መክፈል መቻሉን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በላከልን ሪፖርት አስታውቋል፡፡
#sugarindustry #ethiopianeconomy #omokuraz #development #manufacturing #agriculture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የ2017 በጀት ዓመት ሙሉ ሪፖርት እና የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀምን ይፋ አድርጓል፡፡
ግሩፑ ባወጣው መረጃ መሠረት በኦሞ ኩራዝ ቁጥር ሁለት እና ቁጥር ሦስት ስኳር ፋብሪካዎች አማካኝነት በ2017 የምርት ዘመን 32,806.25 ቶን ስኳር እና 46,204.86 ቶን ሞላሰስ ማምረት ተችሏል፡፡
ይህ አፈፃፀም ከቀደመው የ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በስኳር ምርት የ33 በመቶ እንዲሁም በሞላሰስ ምርት የ46 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
በፋይናንስ ረገድ ሁለቱም ፋብሪካዎች በ2017 በጀት ዓመት ከወጪ ቀሪ የ1.5 ቢሊዮን ብር ጥሬ ገንዘብ ትርፍ ያስመዘገቡ ሲሆን በወቅቱ ያልተሸጡ ምርቶችን ጨምሮ አጠቃላይ ትርፋቸው 3.159 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተገልጿል፡፡
ፋብሪካዎቹ ባሳዩት ውጤታማነት ምክንያት ለሠራተኞቻቸው የሦስት እርከን የደመወዝ ጭማሪ አድርገዋል፡፡
በተጨማሪም ለመንግስት የሚከፈል የታክስ መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ በመጨመር 970.4 ሚሊዮን ብር ለሀገር ገቢ ሆኗል፡፡
ለስኳር ኢንዱስትሪ ልማት ፈንድ (SIDF) ደግሞ 686.1 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዋፅኦ ተደርጓል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈፃፀምን በተመለከተ በሁለቱ ፋብሪካዎች 28,741 ቶን ስኳር እና 24,694 ቶን ሞላሰስ ተመርቷል፡፡
ምንም እንኳን በአካባቢው በነበረው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የምርት ሂደቱ ለጊዜው ቢቆምም በደረቅ ወራት በሚከናወነው ሁለተኛ ዙር ምርት የዓመቱ አፈፃፀም ከ2017 የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ 374.7 ሚሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ የተመዘገበ ሲሆን ለመንግስት 838.7 ሚሊዮን ብር ታክስ ተከፍሏል፡፡
ከስኳር ምርት ባሻገር ፋብሪካዎቹ በግብርና እና በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ተሰማርተው የገቢ ምንጫቸውን በማስፋፋት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኦሞ እና በአርጆ ዴዴሳ ፋብሪካዎች የዶሮ፣ የዓሳ፣ የከብት ማድለብ እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በመከናወኑ ተጨማሪ 30.69 ሚሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል፡፡
በአጠቃላይ ከለውጡ በፊት በከፍተኛ ዕዳ እና የአሠራር ችግር ውስጥ የነበሩት እነዚህ ፋብሪካዎች በአሁኑ ወቅት ውጤታማ ወደመሆን ተሸጋግረዋል፡፡
ተከማችቶ የነበረውን የቆየ ዕዳ በመክፈል ረገድም በ2017 ዓ.ም 378 ሚሊዮን ብር እንዲሁም በ2018 ዘጠኝ ወራት ውስጥ 458.8 ሚሊዮን ብር በላይ መክፈል መቻሉን የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በላከልን ሪፖርት አስታውቋል፡፡
#sugarindustry #ethiopianeconomy #omokuraz #development #manufacturing #agriculture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
6 months ago
የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የ"ኢትዮጵያ ታምርት" 2018 ንቅናቄን በይፋ አስጀምሩ
📌"ኢትዮጵያ ታምርት" ከግንዛቤ ወደ ተግባር ምዕራፍ ተሸጋገረ፤የሀገሪቱ የማምረት አቅም ወደ 66 በመቶ አድጓል
#ethiopia | የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማነቃቃት የተጀመረው ሀገር አቀፍ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ፣ የመጀመራውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ምዕራፍ አጠናቆ ወደ "ድርጊት ምዕራፍ" መሸጋገሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል አስታወቁ።
ሚኒስትሩ ይህን የገለጹት የ2018 በጀት ዓመት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ሲሆን፣ ንቅናቄው በሶስት ዋና ዋና የትግበራ ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፉት ሦስት ዓመታት ከከፍተኛ አመራር እስከ ሰፊው ህዝብ ድረስ የነበረውን የአመለካከት ክፍተት ለመሙላት ሲሰራ መቆየቱን እና ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የተመዘገቡ ውጤቶች
መንግስት የወሰዳቸው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች የግል ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ ታይቶ የማይታወቅ ለውጥ ማምጣታቸውን አቶ መላኩ አብራርተዋል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት ዘርፉን ከነበረበት ዝቅተኛ አፈጻጸም እያወጣው ይገኛል ተብሏል።
በተለይም ከፖሊሲ፣ ከህግ ማዕቀፍ እና ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው የነበሩ ስር የሰደዱ ማነቆዎችን ለመፍታት በተወሰደው እርምጃ ተጨባጭ ለውጦች ተመዝግበዋል።
በዚህም መሰረት፡-
* በ2014 ዓ.ም፡ ከ50 በመቶ በታች (46%) ወርዶ የነበረው የማምረት አቅም፤
* በ2018 ዓ.ም (የመጀመሪያ 6 ወራት)፡ ወደ 66.3 በመቶ ማደግ ችሏል።
የመገናኛ ብዙሃን ሚና
የንቅናቄውን ዓላማና የተገኙ ለውጦችን ለህዝብ በማድረስ ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል። በተለይም "ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖን ጨምሮ ሌሎች ኹነቶችን ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ ስኬታማ ስራ በመሰራቱ ምስጋና አቅርበዋል።
ቀጣዩ የ"ድርጊት ምዕራፍ" የአምራች ኢንዱስትሪውን ችግሮች በተግባር በመፍታትና ምርታማነትን በላቀ ደረጃ በማሳደግ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopiatamirt #industryminister #melakualebel #manufacturing #ethiopianeconomy #actionphase #ኢትዮጵያታምርት #ኢንዱስትሪ #ኢትዮጵያ
📌"ኢትዮጵያ ታምርት" ከግንዛቤ ወደ ተግባር ምዕራፍ ተሸጋገረ፤የሀገሪቱ የማምረት አቅም ወደ 66 በመቶ አድጓል
#ethiopia | የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማነቃቃት የተጀመረው ሀገር አቀፍ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ፣ የመጀመራውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ምዕራፍ አጠናቆ ወደ "ድርጊት ምዕራፍ" መሸጋገሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል አስታወቁ።
ሚኒስትሩ ይህን የገለጹት የ2018 በጀት ዓመት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ሲሆን፣ ንቅናቄው በሶስት ዋና ዋና የትግበራ ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ባለፉት ሦስት ዓመታት ከከፍተኛ አመራር እስከ ሰፊው ህዝብ ድረስ የነበረውን የአመለካከት ክፍተት ለመሙላት ሲሰራ መቆየቱን እና ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የተመዘገቡ ውጤቶች
መንግስት የወሰዳቸው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃዎች የግል ዘርፉን በማነቃቃት ረገድ ታይቶ የማይታወቅ ለውጥ ማምጣታቸውን አቶ መላኩ አብራርተዋል።
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም እና በ10 ዓመቱ የልማት ዕቅድ ውስጥ ለአምራች ኢንዱስትሪው የተሰጠው ትኩረት ዘርፉን ከነበረበት ዝቅተኛ አፈጻጸም እያወጣው ይገኛል ተብሏል።
በተለይም ከፖሊሲ፣ ከህግ ማዕቀፍ እና ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው የነበሩ ስር የሰደዱ ማነቆዎችን ለመፍታት በተወሰደው እርምጃ ተጨባጭ ለውጦች ተመዝግበዋል።
በዚህም መሰረት፡-
* በ2014 ዓ.ም፡ ከ50 በመቶ በታች (46%) ወርዶ የነበረው የማምረት አቅም፤
* በ2018 ዓ.ም (የመጀመሪያ 6 ወራት)፡ ወደ 66.3 በመቶ ማደግ ችሏል።
የመገናኛ ብዙሃን ሚና
የንቅናቄውን ዓላማና የተገኙ ለውጦችን ለህዝብ በማድረስ ረገድ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል። በተለይም "ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖን ጨምሮ ሌሎች ኹነቶችን ለህብረተሰቡ በማስተዋወቅ ስኬታማ ስራ በመሰራቱ ምስጋና አቅርበዋል።
ቀጣዩ የ"ድርጊት ምዕራፍ" የአምራች ኢንዱስትሪውን ችግሮች በተግባር በመፍታትና ምርታማነትን በላቀ ደረጃ በማሳደግ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopiatamirt #industryminister #melakualebel #manufacturing #ethiopianeconomy #actionphase #ኢትዮጵያታምርት #ኢንዱስትሪ #ኢትዮጵያ
6 months ago
15th Ethio-Chamber International Trade Fair
February 4–8, 2026
Meskel Square, Addis Ababa
Don’t Miss Africa’s Growing Business Gateway!
The 15th Ethio-Chamber International Trade Fair brings together business leaders, investors, innovators, manufacturers, traders, and entrepreneurs from Ethiopia and around the world under one roof.
This landmark event is your best platform for trade promotion, investment opportunities, market expansion, and high-level business networking.
Buy Ethiopian! Invest in Ethiopia!
________
Sectors
• Manufacturing
• Agro-Processing
• Import & Export
• Wholesale & Retail
• Mining
• Telecommunications & ICT
• Transportation & Logistics
• Automotive
• Coffee & Agribusiness
• Services
• Small & Medium Enterprises (SMEs)
• And many more
________
Why Participate?
✔ Connect with local and international investors
✔ Discover new markets and partnerships
✔ Showcase products, innovations, and services
✔ Explore trade and investment opportunities
✔ Strengthen your brand visibility
Register Now & Secure Your Place!
Email: ethiochambereventgmail.com
Website: event.ethiopianchamber.com
Call: 0993 512 930 | 0912 495 739
Organized by:
Ethiopian Chamber of Commerce and Sectoral Associations (ECCSA)
in collaboration with Ministry of Trade and Regional Integration (MoTRI)
February 4–8, 2026
Meskel Square, Addis Ababa
Don’t Miss Africa’s Growing Business Gateway!
The 15th Ethio-Chamber International Trade Fair brings together business leaders, investors, innovators, manufacturers, traders, and entrepreneurs from Ethiopia and around the world under one roof.
This landmark event is your best platform for trade promotion, investment opportunities, market expansion, and high-level business networking.
Buy Ethiopian! Invest in Ethiopia!
________
Sectors
• Manufacturing
• Agro-Processing
• Import & Export
• Wholesale & Retail
• Mining
• Telecommunications & ICT
• Transportation & Logistics
• Automotive
• Coffee & Agribusiness
• Services
• Small & Medium Enterprises (SMEs)
• And many more
________
Why Participate?
✔ Connect with local and international investors
✔ Discover new markets and partnerships
✔ Showcase products, innovations, and services
✔ Explore trade and investment opportunities
✔ Strengthen your brand visibility
Register Now & Secure Your Place!
Email: ethiochambereventgmail.com
Website: event.ethiopianchamber.com
Call: 0993 512 930 | 0912 495 739
Organized by:
Ethiopian Chamber of Commerce and Sectoral Associations (ECCSA)
in collaboration with Ministry of Trade and Regional Integration (MoTRI)
Comments