2 months ago
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ከመተካት ባለፈ የወጪ ንግድ ገቢን እያሳደገ ያለው የኢትዮጵያ የግብርና ኢንቨስትመንት
*************
ኢትዮጵያ በአስር ዓመቱ የግብርና መሪ ዕቅድ ውስጥ በትኩረት እንዲሰራባቸው ካስቀመጠቻቸው ስትራቴጂካዊ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው የግብርና ኢንቨስትመንት የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት እና የውጪ ምንዛሪን የማሳደግ ሀገራዊ ግቦችን በላቀ ስኬት እያሳካ ይገኛል።
የሀገራችንን ሰፊ የግብርና አቅም በመጠቀም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በስፋት ተሰማርተው ወደ ልማት ገብተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በእርሻ ኢንቨስትመንት ብቻ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በ8 ሺህ 904 ባለሀብቶች እጅ ላይ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
መንግሥት ይህንን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ በመሬት አቅርቦት፣ የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ፣ በውል እርሻ እና በመሰረተ-ልማት ማመቻቸት ረገድ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ከዚህ በተጨማሪም የግብርናውን ዘርፍ ሽግግር የሚያፋጥኑ የሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ሲሆን ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተተገበሩ ዘመናዊ አሰራሮች፣ በኮንትራት እርሻ፣ በምርጥ ዘር ብዜት እንዲሁም በአካታች የሕግ ማዕቀፎች ምክንያት አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።
በአሁኑ ወቅት አበባ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሰብል እና እንስሳት በኢንቨስትመንት ደረጃ በስፋት እየለሙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታና ለወጪ ንግድ በከፍተኛ ደረጃ እየቀረቡ ይገኛሉ።
ለአብነትም የአበባ፣ የአትክልት እና የፍራፍሬ የወጪ ንግድ አፈፃፀምን ስንመለከት በ2013 ዓ.ም ከ309 ሺህ 866 ነጥብ 8 ቶን ምርት 531 ሺህ 480 ዶላር ተገኝቷል።
ይህ ቁጥር በ2017 ዓ.ም እጅግ ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት ከተላከው 395 ሺህ 911 ነጥብ 9 ቶን ምርት 670 ሺህ 627 ነጥብ 4 ዶላር ገቢ ለማግኘት ተችሏል።
የዘንድሮውን የ10 ወራት አፈፃፀም ስንመለከት ደግሞ ከ236 ሺህ 415 ነጥብ 3 ቶን ምርት 408 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል ለሀገራዊ ኢኮኖሚ፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለእውቀት ሽግግር ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያለው የእንስሳት ኢንቨስትመንትም ሌላው ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ ነው።
ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ በእንስሳት ኢንቨስትመንት ለተሰማሩ ባለሀብቶች 112 ሺህ ሄክታር መሬት፣ በእርሻና ሆርቲከልቸር ኢንቨስትምንት ደግሞ 643 ሺህ ሄክታር መሬት በድምሩ ከ750 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተላልፎ ለልማት እንዲውል ተደርጓል።
#agricultureinvestment #ethiopianeconomy #importsubstitution #exportgrowth #ethiopianbroadcastingcorporation
*************
ኢትዮጵያ በአስር ዓመቱ የግብርና መሪ ዕቅድ ውስጥ በትኩረት እንዲሰራባቸው ካስቀመጠቻቸው ስትራቴጂካዊ ዘርፎች መካከል አንዱ የሆነው የግብርና ኢንቨስትመንት የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት እና የውጪ ምንዛሪን የማሳደግ ሀገራዊ ግቦችን በላቀ ስኬት እያሳካ ይገኛል።
የሀገራችንን ሰፊ የግብርና አቅም በመጠቀም በርካታ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶች በስፋት ተሰማርተው ወደ ልማት ገብተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ በእርሻ ኢንቨስትመንት ብቻ ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በ8 ሺህ 904 ባለሀብቶች እጅ ላይ እንደሚገኝ የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
መንግሥት ይህንን ዘርፍ ይበልጥ ለማሳደግ በመሬት አቅርቦት፣ የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽ በማድረግ፣ በውል እርሻ እና በመሰረተ-ልማት ማመቻቸት ረገድ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ከዚህ በተጨማሪም የግብርናውን ዘርፍ ሽግግር የሚያፋጥኑ የሀገር በቀል ቴክኖሎጂዎችን ለባለሀብቶች የማስተዋወቅ ስራ በትኩረት እየተከናወነ ሲሆን ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በተተገበሩ ዘመናዊ አሰራሮች፣ በኮንትራት እርሻ፣ በምርጥ ዘር ብዜት እንዲሁም በአካታች የሕግ ማዕቀፎች ምክንያት አመርቂ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።
በአሁኑ ወቅት አበባ፣ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ሰብል እና እንስሳት በኢንቨስትመንት ደረጃ በስፋት እየለሙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታና ለወጪ ንግድ በከፍተኛ ደረጃ እየቀረቡ ይገኛሉ።
ለአብነትም የአበባ፣ የአትክልት እና የፍራፍሬ የወጪ ንግድ አፈፃፀምን ስንመለከት በ2013 ዓ.ም ከ309 ሺህ 866 ነጥብ 8 ቶን ምርት 531 ሺህ 480 ዶላር ተገኝቷል።
ይህ ቁጥር በ2017 ዓ.ም እጅግ ከፍተኛ ዕድገት በማሳየት ከተላከው 395 ሺህ 911 ነጥብ 9 ቶን ምርት 670 ሺህ 627 ነጥብ 4 ዶላር ገቢ ለማግኘት ተችሏል።
የዘንድሮውን የ10 ወራት አፈፃፀም ስንመለከት ደግሞ ከ236 ሺህ 415 ነጥብ 3 ቶን ምርት 408 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የሚኒስቴሩ መረጃ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል ለሀገራዊ ኢኮኖሚ፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለእውቀት ሽግግር ከፍተኛ አስተዋፅዖ ያለው የእንስሳት ኢንቨስትመንትም ሌላው ትኩረት የተሰጠው ዘርፍ ነው።
ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ በእንስሳት ኢንቨስትመንት ለተሰማሩ ባለሀብቶች 112 ሺህ ሄክታር መሬት፣ በእርሻና ሆርቲከልቸር ኢንቨስትምንት ደግሞ 643 ሺህ ሄክታር መሬት በድምሩ ከ750 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ተላልፎ ለልማት እንዲውል ተደርጓል።
#agricultureinvestment #ethiopianeconomy #importsubstitution #exportgrowth #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
በኢንዱስትሪ ሽግግር ጉዟችን ተጨባጭ ለውጥ እያመጣንባቸው ያሉት ተኪ ምርቶቻችን
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
3 months ago
ድንጋይ አቅልጣ ዶላር የምታድነው ኢትዮጵያ፤ የሴራሚክ ምርት ከውጭ ጥገኝነት ወደ ሉዓላዊ አቅም
#የኢንዱስትሪ_ሽግግር #ኢትዮጵያ_ታምርት #ceramicindustry #madeinethiopia #importsubstitution
3 months ago
ድንጋይ አቅልጣ ዶላር የምታድነው ኢትዮጵያ፤ የሴራሚክ ምርት ከውጭ ጥገኝነት ወደ ሉዓላዊ አቅም እየተቀየረ ነው። እንዴት ካሉ መልሱን በተከታዩ ሊንክ ያገኙታል ➡️ https://youtu.be/K_Lb1Mknq...
#ceramicindustry #madeinethiopia #importsubstitution #economicsovereignty #taborceramics #ebcworld
3 months ago
የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ያስገኘው ትሩፋት
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢትዮጵያ ታምርት ፡ በራስ ላብ፣ የራስ ምርት
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት በገቢ ምርቶች ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የኖረ ኢኮኖሚ የራስን ሉዓላዊነት ሙሉ አያደርገውም። የሀገር ብልጽግና መሠረቱ ደግሞ በባዕድ እጅ የሚሰፈር ሳይሆን በራስ ላብና ጥረት የሚመረት መሆኑ አያጠያይቅም።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን የተጋረጡብንን የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ፈተናዎችን በመሻገር የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከአንቀላፋበት ቀስቅሶ ሕይወት ዘርቶበታል። ይህ ንቅናቄ ዝም ብሎ የቃላት ጋጋታ ሳይሆን “ላብ ካልፈሰሰ፣ አዝመራ የለም” የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳየ፣ የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነታችንን ያበሰረ ብርቱ የለውጥ ማዕበል ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ የለውጡ ጉዞ ውጤታማነት በቁጥር ብቻ ሳይሆን በገበያ ድርሻም ተረጋግጧል። ከሦስት ዓመት በፊት 30 በመቶ ብቻ የነበረው የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻ ዛሬ 41 በመቶ ደርሷል። ይህ መሻሻል ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን፣ ሥራ አቁመው የነበሩ 830 ኢንዱስትሪዎችን ዳግም ወደ ማምረት በመመለስና 325 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችን በአዲስ መንፈስ ወደ ሥራ በማስገባት የተገኘ ድል ነው።
በተለይም ከለውጡ በፊት 8 ሺህ ገደማ የነበሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ዛሬ 26 ሺህ መድረሳቸው፣ ኢኮኖሚው ከመንግሥት መርነት ወደ ግሉ ዘርፍ መዘዋወሩንና የዜጎች የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነት መጎልበቱን ያሳያል። “ታጥቦ ጭቃ” መሆንን አቁመን፣ በገዛ ደጃችን ተኪ ምርቶችን እያመረትን መገኘታችን የኢኮኖሚ ነፃነታችን ማሳያ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ትስስርም ሌላኛው የንቅናቄው ስኬት ነው። ቡና፣ ሻይና ሩዝ በገበሬው እጅ ብቻ ተመርተው ሳይሆን በፋብሪካዎች እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍ አድርጎታል።
“ሳይቀደሙ መቅደም” እንዲሉ መከላከያና ፖሊስ ከውጭ በውድ ምንዛሬ የሚገዛ የደንብ ልብስን ትተው ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካታቸው፣ እንዲሁም የብቅል ገብስ ዘርን እዚሁ ማምረት መቻላችን 3 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን አስችሏል። በተጨማሪም የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳና የምግብ ኢንዱስትሪዎች እምቅ አቅማቸውን እያወጡ ይገኛሉ።
የጥራት መንደር አበርክቶ ደግሞ ለዚህ ሁሉ ስኬት ሞተር ነው። በዓመት 5.2 ሚሊዮን ቶን ምርትን የመመርመር አቅም ያለው ይህ ተቋም፣ የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የጥራት ደረጃቸው እንዲጠበቅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት ይህ ተቋም በዓለም የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ያለንን ተሳትፎ የሚያጎለብት የብልጽግናችን መተማመኛ ነው።
በአጠቃላይ "ኢትዮጵያ ታምርት" ከሸቀጥ ግብይት ባለፈ "የኢትዮጵያ ይሸጥ" የሚል ኩሩ እሳቤን ይዟል። 235 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የወጣቶችን ሕይወት የቀየረው ይህ ንቅናቄ፣ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢኮኖሚ ነፃነታችንን የሚያጸና ነው። በጋራ ካመረትንና የራሳችንን ምርት ከተጠቀምን፣ የብልጽግና ጉዟችን የማይቀለበስ ይሆናል።
ኢትዮጵያ ታምርት፣ ኢትዮጵያ ትበልጽግ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #industry #manufacturing #importsubstitution #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc #ebcdotstream
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት በገቢ ምርቶች ላይ ብቻ ተንጠልጥሎ የኖረ ኢኮኖሚ የራስን ሉዓላዊነት ሙሉ አያደርገውም። የሀገር ብልጽግና መሠረቱ ደግሞ በባዕድ እጅ የሚሰፈር ሳይሆን በራስ ላብና ጥረት የሚመረት መሆኑ አያጠያይቅም።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን የተጋረጡብንን የጥሬ ዕቃ አቅርቦትና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ፈተናዎችን በመሻገር የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ከአንቀላፋበት ቀስቅሶ ሕይወት ዘርቶበታል። ይህ ንቅናቄ ዝም ብሎ የቃላት ጋጋታ ሳይሆን “ላብ ካልፈሰሰ፣ አዝመራ የለም” የሚለውን እውነታ በተግባር ያሳየ፣ የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነታችንን ያበሰረ ብርቱ የለውጥ ማዕበል ነው።
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፣ የለውጡ ጉዞ ውጤታማነት በቁጥር ብቻ ሳይሆን በገበያ ድርሻም ተረጋግጧል። ከሦስት ዓመት በፊት 30 በመቶ ብቻ የነበረው የሀገር ውስጥ ምርቶች የገበያ ድርሻ ዛሬ 41 በመቶ ደርሷል። ይህ መሻሻል ዝም ብሎ የመጣ ሳይሆን፣ ሥራ አቁመው የነበሩ 830 ኢንዱስትሪዎችን ዳግም ወደ ማምረት በመመለስና 325 ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎችን በአዲስ መንፈስ ወደ ሥራ በማስገባት የተገኘ ድል ነው።
በተለይም ከለውጡ በፊት 8 ሺህ ገደማ የነበሩ አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ዛሬ 26 ሺህ መድረሳቸው፣ ኢኮኖሚው ከመንግሥት መርነት ወደ ግሉ ዘርፍ መዘዋወሩንና የዜጎች የሥራ ፈጠራ ተነሳሽነት መጎልበቱን ያሳያል። “ታጥቦ ጭቃ” መሆንን አቁመን፣ በገዛ ደጃችን ተኪ ምርቶችን እያመረትን መገኘታችን የኢኮኖሚ ነፃነታችን ማሳያ ነው።
የግብርናና የኢንዱስትሪ ትስስርም ሌላኛው የንቅናቄው ስኬት ነው። ቡና፣ ሻይና ሩዝ በገበሬው እጅ ብቻ ተመርተው ሳይሆን በፋብሪካዎች እሴት ተጨምሮባቸው ለዓለም ገበያ መቅረባቸው የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍ አድርጎታል።
“ሳይቀደሙ መቅደም” እንዲሉ መከላከያና ፖሊስ ከውጭ በውድ ምንዛሬ የሚገዛ የደንብ ልብስን ትተው ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካታቸው፣ እንዲሁም የብቅል ገብስ ዘርን እዚሁ ማምረት መቻላችን 3 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬን ለማዳን አስችሏል። በተጨማሪም የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳና የምግብ ኢንዱስትሪዎች እምቅ አቅማቸውን እያወጡ ይገኛሉ።
የጥራት መንደር አበርክቶ ደግሞ ለዚህ ሁሉ ስኬት ሞተር ነው። በዓመት 5.2 ሚሊዮን ቶን ምርትን የመመርመር አቅም ያለው ይህ ተቋም፣ የኢትዮጵያ ምርቶች በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና የጥራት ደረጃቸው እንዲጠበቅ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት ይህ ተቋም በዓለም የእሴት ሰንሰለት ውስጥ ያለንን ተሳትፎ የሚያጎለብት የብልጽግናችን መተማመኛ ነው።
በአጠቃላይ "ኢትዮጵያ ታምርት" ከሸቀጥ ግብይት ባለፈ "የኢትዮጵያ ይሸጥ" የሚል ኩሩ እሳቤን ይዟል። 235 ሺህ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር የወጣቶችን ሕይወት የቀየረው ይህ ንቅናቄ፣ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የኢኮኖሚ ነፃነታችንን የሚያጸና ነው። በጋራ ካመረትንና የራሳችንን ምርት ከተጠቀምን፣ የብልጽግና ጉዟችን የማይቀለበስ ይሆናል።
ኢትዮጵያ ታምርት፣ ኢትዮጵያ ትበልጽግ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #industry #manufacturing #importsubstitution #madeinethiopia #ethiopiadelivers #ebc #ebcdotstream
3 months ago
ኢትዮጵያ ለኢንዱስትሪ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጭ ምንዛሬን ከመታደግ ባለፈ የዜጎችን የምርት አቅም በማሳደግ ላይ ትገኛለች።
የቢራ ገብስ ብቅልን፣ ወታደራዊ ዩኒፎርሞችንና ስንዴን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ በማምረት በየዓመቱ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ማስቀረት መቻሉን የሚያሳየውን ዝርዝር መረጃ በኢንፎግራፊክሱ ይመልከቱ።
#ethiopia #industry #madeinethiopia #importsubstitution #productivity #ebc
የቢራ ገብስ ብቅልን፣ ወታደራዊ ዩኒፎርሞችንና ስንዴን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ በማምረት በየዓመቱ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ማስቀረት መቻሉን የሚያሳየውን ዝርዝር መረጃ በኢንፎግራፊክሱ ይመልከቱ።
#ethiopia #industry #madeinethiopia #importsubstitution #productivity #ebc
Comments