በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ የዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ
በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው መርሃ-ግብር ወቅት የሚቆይ የተሽከርካሪዎች ዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተከፈተውና ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየው ብሔራዊ ኤክስፖ በርካታ አምራቾችንና የኢንዱስትሪ ተቋማትን እያሳተፈ ይገኛል።
በሀገር ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም ዘርፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየውና የሦስት መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ባለቤት የሆነው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው ላይ ከ13 በላይ የተለያዩ የተሽከርካሪ ሞዴሎችን ይዞ መቅረቡን የድርጅቱ ተወካዮች ገልጸዋል።
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በገበያው ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሱትን የውሊንግ (Wuling) ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ለቤተሰብ፣ ለታክሲ አገልግሎት፣ ለድርጅቶች ሰርቪስ እንዲሁም ለጭነትና ለካርጎ አገልግሎት የሚውሉ ፒክአፖችንና ቫኖችን ማቅረቡን አስታውቋል።
የሽያጭ ሂደቱንና የተጠቃሚዎችን አቅም በተመለከተ ከድርጅቱ ተወካዮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች ክፍያውን በጥሬ ገንዘብ (ካሽ) መፈጸም የሚችሉ ሲሆን፣ በተለዋጭ አማራጭ ደግሞ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ30% እስከ 50% የሚሆነውን ቅድመ ክፍያ በመክፈል ተሽከርካሪዎቹን በብድር መውሰድ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል።
በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ በሚገኘው የ«ኢትዮጵያ ታምርት» ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው መርሃ-ግብር ወቅት የሚቆይ የተሽከርካሪዎች ዋጋ ቅናሽ ማድረጉን አስታወቀ።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተከፈተውና ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየው ብሔራዊ ኤክስፖ በርካታ አምራቾችንና የኢንዱስትሪ ተቋማትን እያሳተፈ ይገኛል።
በሀገር ውስጥ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም ዘርፍ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየውና የሦስት መገጣጠሚያ ፋብሪካዎች ባለቤት የሆነው ኦክሎክ ሞተርስ፣ በኤክስፖው ላይ ከ13 በላይ የተለያዩ የተሽከርካሪ ሞዴሎችን ይዞ መቅረቡን የድርጅቱ ተወካዮች ገልጸዋል።
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በገበያው ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሱትን የውሊንግ (Wuling) ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ ለቤተሰብ፣ ለታክሲ አገልግሎት፣ ለድርጅቶች ሰርቪስ እንዲሁም ለጭነትና ለካርጎ አገልግሎት የሚውሉ ፒክአፖችንና ቫኖችን ማቅረቡን አስታውቋል።
የሽያጭ ሂደቱንና የተጠቃሚዎችን አቅም በተመለከተ ከድርጅቱ ተወካዮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ፍላጎት ያላቸው ደንበኞች ክፍያውን በጥሬ ገንዘብ (ካሽ) መፈጸም የሚችሉ ሲሆን፣ በተለዋጭ አማራጭ ደግሞ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ30% እስከ 50% የሚሆነውን ቅድመ ክፍያ በመክፈል ተሽከርካሪዎቹን በብድር መውሰድ የሚያስችል አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል።
1 month ago