Logo
EBC
ከመሸመት ወደ ማምረት፡ የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ ስኬቶች
*************************

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የኢኮኖሚ መዋቅሯን ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር ግዙፍና ታሪካዊ እርምጃዎችን እየወሰደች ትገኛለች።

ይህ የሽግግር ጉዞ የሀገራችንን የብልጽግና ራዕይ ከማሳካት ባለፈ፣ ዘላቂ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና ራስን ለመቻል እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ምሰሶ ተወስዷል።

መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ልዩ ትኩረትና ተግባራዊ የተደረጉት አዳዲስ ፖሊሲዎች፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ከነበረበት የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ ወጥቶ ወደ ተሻለ የማምረት አቅም እንዲሸጋገር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል።

የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት እንደሚያሳየው፤ የዘርፉ ዓመታዊ ዕድገት ቀደም ሲል ከነበረበት 4.8 በመቶ በአሁኑ ወቅት ወደ 10.7 በመቶ በመመንጠቅ ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።

ሙሉ ዘገባውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል።

በለሚ ታደሰ
#ethiopia #industry #manufacturing #madeinethiopia #ebc

29 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.