ኢትዮ ቴሌኮም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማሳደግና የገበያ ትስስርን ለማጠናከር የሚያስችሉ የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራረመ
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
ኩባንያችን በአራተኛው የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ ላይ ከመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ፣ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት እንዲሁም ከኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማኅበራት ጋር የ(B2G) የመግባቢያ ስምምነቶችን ተፈራርሟል።
ስምምነቶቹ ኩባንያችን ለቴሌኮም እና ለኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማስፋፊያ ሥራዎች የሚውሉ የፋይበር ኦፕቲክስ፣ የኃይል እና የዳታ ኬብሎችን፣ ልዩ ልዩ መለዋወጫዎችን እና የሠራተኞች የደንብ ልብሶችን ከአገር ውስጥ አምራቾች ለመረከብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ይህም ኩባንያችን አስተማማኝና ጥራት ያላቸውን ግብዓቶች በአገር ውስጥ እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ አምራቾች ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶችን እንዲያቀርቡና የአቅርቦት ሰንሰለት ማነቆዎችን እንዲቀርፉ ምቹ ዕድል የሚፈጥር ነው።
በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን የማምረት አቅም ለማሳደግ፣ ፈጠራን ለማበረታታትና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ምርቶች በመተካት የውጭ ምንዛሬን ለመቆጠብ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ እና ዘላቂ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ለማረጋገጥ ጉልህ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
ኩባንያችን ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለሀገራዊ ዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ ጉል ፋይዳ ያለው በአምራቾች መካከል ያለውን የገበያ ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ "ኢ-ታምርት" የተሰኘ የB2B የኢ-ኮሜርስ ፕላትፎርም ሥራ ላይ ማዋሉ ይታወሳል።
#ethiotelecom #ministryofindustry #telebirr #ethiopiatamirt #b2bplatform #digitaleconomy #localmanufacturing #gsma #itu #worldbank #madeinethiopia Ethiopian Ministry of Industry
1 month ago