2 months ago
በኢንዱስትሪ ሽግግር ጉዟችን ተጨባጭ ለውጥ እያመጣንባቸው ያሉት ተኪ ምርቶቻችን
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
3 months ago
ኢትዮጵያ ታመርታለች፤ ምሉዕ ሉዓላዊነቷን የማረጋገጥ ጉዞዋን በሁሉም መስክ አጠናክራ ትቀጥላለች። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ደግሞ የዚህ መርኃችን ዋነኛ ዓምድ ነው።
#ኢትዮጵያታምርት #madeinethiopia #ethiopiatamrit #economicsovereignty #ethiopiandevelopment #manufacturing #industrialrevolution #homegrowneconomy
3 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፈረሙት ለምንድን ነው?
*“ኢትዮጵያን የአፍሪካ የፋሽን ተምሳሌት እናደርጋታለን” — አቶ ዘላለም መራዊ
የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት
#ethiopia | በ“ኢትዮጵያ ታምርት” የንግድ ትርኢት ላይ የተሳተፉት የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች አቶ ዘላለም መራዊ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድርጅታቸውን የፈጠራ ስራዎች መጎብኘታቸውንና ከፍተኛ አድናቆት መቸራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በየዓመቱ በሚያደርጉት ጉብኝት በምርቶቹ ላይ የሚታየው መሻሻልና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንዳስደመሟቸው በድርጅቱ የክብር መዝገብ ላይ በፊርማቸው ጭምር አረጋግጠዋል።
በዓለም ላይ ያለው የፋሽን ኢንዱስትሪ እስከ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያንቀሳቅስ የገለጹት አቶ ዘላለም፣ ኢትዮጵያ እንደ ጣልያንና ፈረንሳይ የራሷን የፋሽን “ብራንድ” በመገንባት ከዚህ ገበያ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል።
ኬሬዠ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከውጭ ይገቡ የነበሩ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የቆዳ ውጤቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ለተለያዩ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰጡ የክብር ስጦታዎችን እያቀረበ ይገኛል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን በፋሽንና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ ላይ የማድረስ ጉጉት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አቶ ዘላለም የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች ከመሆናቸው ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን መላው ዘርፍ በቴክኖሎጂ፣ በስልጠናና በጥሬ እቃ አቅርቦት እንዲሻሻል በንቃት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት (ቆዳ) እና የሰው ኃይል በመጠቀም ኢትዮጵያን በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በመላው አፍሪካ ገበያዎች ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ ታላቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን የስራ መሪው በኩራት ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #amn
#የኢትዮጵያታምርት #ቆዳናየቆዳውጤቶች #ዘላለምመራዊ #ኢትዮጵያ #ፋሽን #የሀገርውስጥምርት #ethiopiatamrit #ethiopianfashion #leatherindustry
*“ኢትዮጵያን የአፍሪካ የፋሽን ተምሳሌት እናደርጋታለን” — አቶ ዘላለም መራዊ
የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት
#ethiopia | በ“ኢትዮጵያ ታምርት” የንግድ ትርኢት ላይ የተሳተፉት የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች አቶ ዘላለም መራዊ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድርጅታቸውን የፈጠራ ስራዎች መጎብኘታቸውንና ከፍተኛ አድናቆት መቸራቸውን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በየዓመቱ በሚያደርጉት ጉብኝት በምርቶቹ ላይ የሚታየው መሻሻልና አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች እንዳስደመሟቸው በድርጅቱ የክብር መዝገብ ላይ በፊርማቸው ጭምር አረጋግጠዋል።
በዓለም ላይ ያለው የፋሽን ኢንዱስትሪ እስከ 300 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያንቀሳቅስ የገለጹት አቶ ዘላለም፣ ኢትዮጵያ እንደ ጣልያንና ፈረንሳይ የራሷን የፋሽን “ብራንድ” በመገንባት ከዚህ ገበያ ተጠቃሚ መሆን እንዳለባት ጠቁመዋል።
ኬሬዠ ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከውጭ ይገቡ የነበሩ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን የቆዳ ውጤቶች በሀገር ውስጥ በማምረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ለተለያዩ የአፍሪካ መሪዎች የሚሰጡ የክብር ስጦታዎችን እያቀረበ ይገኛል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን በፋሽንና በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ ላይ የማድረስ ጉጉት እንዳላቸው ገልጸዋል።
አቶ ዘላለም የኬሬዠ ኢትዮጵያ መስራች ከመሆናቸው ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን መላው ዘርፍ በቴክኖሎጂ፣ በስልጠናና በጥሬ እቃ አቅርቦት እንዲሻሻል በንቃት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ፣ የሀገሪቱን የተፈጥሮ ሀብት (ቆዳ) እና የሰው ኃይል በመጠቀም ኢትዮጵያን በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በመላው አፍሪካ ገበያዎች ውስጥ ተወዳዳሪ ለማድረግ ታላቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን የስራ መሪው በኩራት ተናግረዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #amn
#የኢትዮጵያታምርት #ቆዳናየቆዳውጤቶች #ዘላለምመራዊ #ኢትዮጵያ #ፋሽን #የሀገርውስጥምርት #ethiopiatamrit #ethiopianfashion #leatherindustry
3 months ago
ከምኞት ወደ እውነት፦ የኢትዮጵያ አዲሱ የሉዓላዊነት ጉዞ በ21ኛው ክፍለ ዘመን
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
Comments