1 day ago
ከዛሬ ባሻገር ለትውልዶች የሚሻገር ዘላቂ ሀብት፤ የአረንጓዴ ዐሻራ ዘርፈ-ብዙ ስኬቶች
********************
ዓለም በተፈጥሮ ሀብት መመናመንና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እያስተናገደቻቸው ያሉ አሉታዊ ተጽዕኖዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመጡበት በአሁኑ ወቅት ይህንን ተግዳሮት ለመቋቋም የተፈጥሮ ሚዛንን መጠበቅና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ሆኗል።
በዚህ ረገድ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ ትልቅ ሀገራዊ ስኬት ማስመዝገብ ችሏል።
የዚህ አመት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገር አቀፍ መርሃ ግብር በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ከተያዘው እቅድ በላይ 805.3 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
ይህም ሀገራችን የራሷን ክብረ ወሰን በድጋሚ በማሻሻል ለተቀረው ዓለም የተፈጥሮ ጥበቃ አርአያነትን በተግባር ማሳየት የቻለችበት ሁነት ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማገገም የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግና የደን ሽፋንን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በኩል የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ይህ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ከኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምሰሶ ከሆነው ከግብርና ዘርፍ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ በርካታ ጠቀሜታዎችን አስግኝቷል።
በየዓመቱ የሚተከሉት ችግኞች የአፈር ለምነትን በመጠበቅ የመሬት ምርታማነትን ከመጨመራቸውም በላይ ለምግብነት የሚውሉ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞችን እንዲሁም የቡና ተክሎችን በማካተት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የዜጎችን የገቢ ምንጭ ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ሀገሪቱ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር ምርቶችን ለማሳደግ እንዲሁም በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት በምግብ ራስን ለመቻልና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ለምታደርገው ጥረት ጠንካራ መሠረት ጥሏል።
ከአካባቢ ጥበቃና ከኢኮኖሚ በላይ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የኢትዮጵያውያንን ማህበራዊ መስተጋብርና ሀገራዊ አንድነት ያጠናከረ ታላቅ ድል ነው።
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ አረንጓዴ አሻራም ኢትዮጵያውያን በመደመር ዕሳቤ ሲተባበሩና አብረው ሲቆሙ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለአፍሪካና ለዓለም ያረጋገጡበት አዲስ ምዕራፍ ነው።
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሥነ ምህዳርን ከመጠበቅና የምግብ ዋስትናን ከመደገፍ ባሻገር ተስፋን፣ የሀገር ፍቅርንና ለአዲሱ ትውልድ ዘላቂ ሀብት የማውረስ ዕሴትን በማጠናከር ኢትዮጵያ የምትናገረውን የምትፈጽም ሀገር መሆኗን በተግባር ያስመሰከረ ብሔራዊ ንቅናቄ መሆን ችሏል፡፡
በብሌን ደምበሎ
********************
ዓለም በተፈጥሮ ሀብት መመናመንና በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት እያስተናገደቻቸው ያሉ አሉታዊ ተጽዕኖዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመሩ በመጡበት በአሁኑ ወቅት ይህንን ተግዳሮት ለመቋቋም የተፈጥሮ ሚዛንን መጠበቅና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ ሆኗል።
በዚህ ረገድ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሳተፍ ትልቅ ሀገራዊ ስኬት ማስመዝገብ ችሏል።
የዚህ አመት "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገር አቀፍ መርሃ ግብር በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞች ለመትከል ከተያዘው እቅድ በላይ 805.3 ሚሊዮን በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
ይህም ሀገራችን የራሷን ክብረ ወሰን በድጋሚ በማሻሻል ለተቀረው ዓለም የተፈጥሮ ጥበቃ አርአያነትን በተግባር ማሳየት የቻለችበት ሁነት ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማገገም የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የከርሰ ምድር ውሃ እንዲበለጽግ በማድረግና የደን ሽፋንን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ በኩል የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ይህ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ሥራ ከኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምሰሶ ከሆነው ከግብርና ዘርፍ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ በመሆኑ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችሉ በርካታ ጠቀሜታዎችን አስግኝቷል።
በየዓመቱ የሚተከሉት ችግኞች የአፈር ለምነትን በመጠበቅ የመሬት ምርታማነትን ከመጨመራቸውም በላይ ለምግብነት የሚውሉ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞችን እንዲሁም የቡና ተክሎችን በማካተት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የዜጎችን የገቢ ምንጭ ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው።
ይህ መርሃ ግብር ሀገሪቱ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር ምርቶችን ለማሳደግ እንዲሁም በበጋ መስኖ የስንዴ ልማት በምግብ ራስን ለመቻልና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ለምታደርገው ጥረት ጠንካራ መሠረት ጥሏል።
ከአካባቢ ጥበቃና ከኢኮኖሚ በላይ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የኢትዮጵያውያንን ማህበራዊ መስተጋብርና ሀገራዊ አንድነት ያጠናከረ ታላቅ ድል ነው።
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ አረንጓዴ አሻራም ኢትዮጵያውያን በመደመር ዕሳቤ ሲተባበሩና አብረው ሲቆሙ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ለአፍሪካና ለዓለም ያረጋገጡበት አዲስ ምዕራፍ ነው።
መርሐ ግብሩ የተፈጥሮ ሥነ ምህዳርን ከመጠበቅና የምግብ ዋስትናን ከመደገፍ ባሻገር ተስፋን፣ የሀገር ፍቅርንና ለአዲሱ ትውልድ ዘላቂ ሀብት የማውረስ ዕሴትን በማጠናከር ኢትዮጵያ የምትናገረውን የምትፈጽም ሀገር መሆኗን በተግባር ያስመሰከረ ብሔራዊ ንቅናቄ መሆን ችሏል፡፡
በብሌን ደምበሎ
1 day ago
በፋብሪካ የሚመረቱ አልኮሎችና ትንባሆ ላይ የኤክሳይዝ ታክስ መጣል የምርቶቹን ዋጋ አንዲጨምር በማድረጉ የምርቶቹ የተጠቃሚዎች ቁጥር መቀነሱን ጥናት አሳየ፡፡
በሌላ በኩል ግን ጠጅ ፣ ጠላ ፣ አረቄ የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሚያቸው መብዛቱን በጥናቱ ግኝት ተጠቅሷል፡፡
ጥናቱን ያጠናው በጤናው መስክ ጥናትና ምርምሮችን የሚያካሂደው ፍኖት የተሰኘ ድርጅት ነው ።
ድርጅቱ ይህን ጥናት ይፋ ያደረገው ከስድስት ዓመት በፊት በአልኮል እና በትንባሆ ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ ምን ውጤት እንዳመጣ በአማራ፣ኦሮሚያና በአዲስ አበባ ላይ ያካሄደው ዳሰሳዊ ጥናት ነው ።
በአልኮልና በትንባሆ ምርቶች ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ የተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ10 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጓል ሲሉ በፍኖት አሶሼት የሄልዝ ኬር ፋይናንሲንግ ባለሙያና አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አስማማው አጥናፉ የጥናቱን ውጤት ጠቅሰው ነግረውናል፡፡
በሌላ በኩል መንግስት የሚያገኘው ገቢ እንዲያድግ ማስቻሉንም በጥናቱ አረጋግጠናል ይላሉ።
የፍኖት አሶሼት መስራች አባል እና የፍኖት ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ፅኑኤል ግርማ በበኩላቸው
እንደ ትንባሆ እና ሲጋራ ምርቶች በህገወጥ መንገድ አሁንም እየገቡ መሆኑን ነግረውናል።
በፍኖት አሶሼት የፋይናንሲንግ ም/ ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ ደዬ በፋብሪካዎች የማይመረቱ፣ የአልኮል መጠናቸውም በማይታወቁ እንደ ጠላ፣ ጠጅ እና አረቄ ያሉ መጠጦች በሰዎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያመጡ ነው ብለዋል ።
በሌላ በኩል በህገወጥ የሚገቡ ምርቶችን መቆጣጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
Via Sheger Fm
በሌላ በኩል ግን ጠጅ ፣ ጠላ ፣ አረቄ የመሳሰሉት ምርቶች ተጠቃሚያቸው መብዛቱን በጥናቱ ግኝት ተጠቅሷል፡፡
ጥናቱን ያጠናው በጤናው መስክ ጥናትና ምርምሮችን የሚያካሂደው ፍኖት የተሰኘ ድርጅት ነው ።
ድርጅቱ ይህን ጥናት ይፋ ያደረገው ከስድስት ዓመት በፊት በአልኮል እና በትንባሆ ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ ምን ውጤት እንዳመጣ በአማራ፣ኦሮሚያና በአዲስ አበባ ላይ ያካሄደው ዳሰሳዊ ጥናት ነው ።
በአልኮልና በትንባሆ ምርቶች ላይ የተጣለው ኤክሳይዝ ታክስ የተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ10 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጓል ሲሉ በፍኖት አሶሼት የሄልዝ ኬር ፋይናንሲንግ ባለሙያና አማካሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አስማማው አጥናፉ የጥናቱን ውጤት ጠቅሰው ነግረውናል፡፡
በሌላ በኩል መንግስት የሚያገኘው ገቢ እንዲያድግ ማስቻሉንም በጥናቱ አረጋግጠናል ይላሉ።
የፍኖት አሶሼት መስራች አባል እና የፍኖት ፕሮጀክት ዳይሬክተር ዶ/ር ፅኑኤል ግርማ በበኩላቸው
እንደ ትንባሆ እና ሲጋራ ምርቶች በህገወጥ መንገድ አሁንም እየገቡ መሆኑን ነግረውናል።
በፍኖት አሶሼት የፋይናንሲንግ ም/ ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ ደዬ በፋብሪካዎች የማይመረቱ፣ የአልኮል መጠናቸውም በማይታወቁ እንደ ጠላ፣ ጠጅ እና አረቄ ያሉ መጠጦች በሰዎች ጤና ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያመጡ ነው ብለዋል ።
በሌላ በኩል በህገወጥ የሚገቡ ምርቶችን መቆጣጠር እንደሚገባም ጠቁመዋል ።
Via Sheger Fm
4 days ago
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የጋምቤላን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ነው፦ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
**********************
በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኙ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሯ ይህንን ያብራሩት በዛሬው ዕለት ከፍተኛ የክልል አመራሮች እና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ተሳትፎ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘውን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት፣ የጋምቤላ ክልል ማህበረሰብም ከማለዳው ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ ልዩ ልዩ ጠቀሜታ ያላቸውን የደንና የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል ላይ ይገኛል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተከናወኑ ተግባራት የደን ሽፋኑ እንዲጨምር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በተለይም የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች ለቤት ውስጥ ምግብነት ከመዋል አልፈው ለገበያ በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሯ፣ ይህም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በቀጣይም በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ሊሆኑ የሚችሉ የደንና የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት የመትከል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ የመትከል እና የመንከባከብ ባህል በሚገባ እየዳበረ በመምጣቱ፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የታቀደውን ግብ በማሳካት የላቀ ስኬት ይመዘገባል ተብሎ በከፍተኛ ተስፋ ይጠበቃል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#greenlegacy #gambella #ethiopia #treeplanting #climateaction
**********************
በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኙ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሯ ይህንን ያብራሩት በዛሬው ዕለት ከፍተኛ የክልል አመራሮች እና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ተሳትፎ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘውን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት፣ የጋምቤላ ክልል ማህበረሰብም ከማለዳው ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ ልዩ ልዩ ጠቀሜታ ያላቸውን የደንና የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል ላይ ይገኛል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተከናወኑ ተግባራት የደን ሽፋኑ እንዲጨምር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በተለይም የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች ለቤት ውስጥ ምግብነት ከመዋል አልፈው ለገበያ በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሯ፣ ይህም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በቀጣይም በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ሊሆኑ የሚችሉ የደንና የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት የመትከል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ የመትከል እና የመንከባከብ ባህል በሚገባ እየዳበረ በመምጣቱ፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የታቀደውን ግብ በማሳካት የላቀ ስኬት ይመዘገባል ተብሎ በከፍተኛ ተስፋ ይጠበቃል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#greenlegacy #gambella #ethiopia #treeplanting #climateaction
8 days ago
"18 ሰው ቀርቶብናል፥ እናትና ልጅም ይገኙበታል፥ ለአዘጋጆቹ ወዲያው አሳውቀናል" - የፕሮጀክቱ መስራች
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
Sponsored by
Surafel
15 days ago
የዝናብ ሁኔታ‼️
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ።
በቀጣዮቹ አስር ቀናት የተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለጸ።
ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ መሰረት፣ ከሐምሌ 14 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት አስር ቀናት ውስጥ የዝናብ ሁኔታን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች የበለጠ እየተጠናከሩ እንደሚሄዱ አሰታወቋል።
በዚህም መሰረት በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን፣ መካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቷ ክፍሎች የተሻለ የዝናብ ሥርጭት መጠን ይኖራቸዋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብና ሰሜን የሀገራችን አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በመካከለኛው፣ ሰሜን ምስራቅ፣ ምስራቅ እና ደቡብ የሀገሪቷ አካባቢዎች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያመለክታሉ ብሏል።
በሚቀጥሉት አስር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም ነው ኢንስቲትዩቱ የጠቆመው።
በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ ሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቷ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ገልጿል።
በተጨማሪም በኤሊ ዳር፣ ዱብቲ፣ ሰመራ፣ ቡሬ፣ አሳይታ፣ ሁንዱፎ፣ ገዋኔ፣ ሚሌ፣ ዳሊፋጊ፣ አይሻ፣ ጉሊና፣ አዋሽ አርባ፣ ባቲ፣ ዶሎ አዶ፣ ዳዋ፣ አሶሶ፣ ጎዴ፣ ቋራ፣ አዋሽ ፈንታሌ፣ ጭፍራ፣ ላሬ፣ መተሀራ እና፣ ላሬ፣ ፉኙዶ አካባቢዎች ከሚኖረው የቀን ከፍተኛ የፀሀይ ሀይል ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ሙቀት ይኖራቸዋል።
ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ ቀናት የሚኖረውን መልካም አጋጣሚዎችን ለመጠቀም እና የሚጠበቁ አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክር ሀሳብን ከወዲሁ መተግበር እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
17 days ago
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሚመራባቸው መርሖች
**************
✅ በአወያይ የመናገር ዕድል ሳይሰጥ ያለመናገር
✅ ተመካካሪዎች አድማጭና ሃሳብ አመንጪ ሆኖ መሳተፍ
✅ ሀሳብን ግልጽና አጭር አድርጎ ማቅረብ
✅ የሀሳብ ልዩነትን ማክበር
✅ የሌላውን ሀሳብ ለመረዳት መጣር
✅ ሀገራዊ መግባባት ላይ መድረስን ከግምት ማስገባት
✅ አሉታዊ ከሆኑ ትችቶችና ፍረጃዎች መቆጠብ
✅ አወያዮች ተመካካሪዎች ለምክክሩ የመገኘታቸውን አስፈላጊነት ዕውቅና መስጠት፣ መደማመጥና መከባበርን መሠረት ማድረግ
✅ በምክክሩ ወቅት ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
**************
✅ በአወያይ የመናገር ዕድል ሳይሰጥ ያለመናገር
✅ ተመካካሪዎች አድማጭና ሃሳብ አመንጪ ሆኖ መሳተፍ
✅ ሀሳብን ግልጽና አጭር አድርጎ ማቅረብ
✅ የሀሳብ ልዩነትን ማክበር
✅ የሌላውን ሀሳብ ለመረዳት መጣር
✅ ሀገራዊ መግባባት ላይ መድረስን ከግምት ማስገባት
✅ አሉታዊ ከሆኑ ትችቶችና ፍረጃዎች መቆጠብ
✅ አወያዮች ተመካካሪዎች ለምክክሩ የመገኘታቸውን አስፈላጊነት ዕውቅና መስጠት፣ መደማመጥና መከባበርን መሠረት ማድረግ
✅ በምክክሩ ወቅት ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
21 days ago
የአጭር ጊዜ ቪዲዮዎች (TikTok እና Reels) ራስን የመቆጣጠር እና የዲሲፕሊን ክህሎትን የሚገነባውን የአንጎል ክፍል ስራ እንደሚያደናቅፉ አዲስ ጥናት አመለከተ
ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይደሰቱም፥ ቪዲዮዎቹ በአንጎል ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አይቀሬ መሆኑ ተረጋግጧል።
ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ እነዚህ ምስል-ወለድ ይዘቶች የተመልካቹን ቀልብ አንዴ ከሳቡ በኋላ ፈጣን የዶፓሚን ሆርሞን መለቀቅን ያስከትላሉ።
ይህም የአንጎልን የተፈጥሮ ውሳኔ ሰጪነት በማደንዘዝ፣ ከዕፅ ሱስ የጠነከረ ከፍተኛ የሱስ የመለከፍ አደጋ ይፈጥራል።
ይህ የፈጣን መዝናኛ አባዜ የሰውን ልጅ ወደ ማገናዘብ የማይችል “ዞምቢ” እየቀየረው መሆኑን ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል።
ራስን የመግዛት አቅምን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መገደብ ወሳኝ እንደሆነም ተመክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
ተጠቃሚዎች በምስሎቹ ቢደሰቱም ባይደሰቱም፥ ቪዲዮዎቹ በአንጎል ላይ የሚያሳድሩት አሉታዊ ተፅዕኖ አይቀሬ መሆኑ ተረጋግጧል።
ጥናቱ እንደሚያሳየው፣ እነዚህ ምስል-ወለድ ይዘቶች የተመልካቹን ቀልብ አንዴ ከሳቡ በኋላ ፈጣን የዶፓሚን ሆርሞን መለቀቅን ያስከትላሉ።
ይህም የአንጎልን የተፈጥሮ ውሳኔ ሰጪነት በማደንዘዝ፣ ከዕፅ ሱስ የጠነከረ ከፍተኛ የሱስ የመለከፍ አደጋ ይፈጥራል።
ይህ የፈጣን መዝናኛ አባዜ የሰውን ልጅ ወደ ማገናዘብ የማይችል “ዞምቢ” እየቀየረው መሆኑን ተመራማሪዎች አስጠንቅቀዋል።
ራስን የመግዛት አቅምን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም መገደብ ወሳኝ እንደሆነም ተመክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኮሎምቢያው ተጨዋች በአገሩ በደረሰበት የግድያ ዛቻ ለመደበቅ ተገደደ፡፡ ጉዳዩ የሚጀምረው ባለፈው ሳምንት ጁላይ 8 በቫንኮቨር ስታዲየም ኮሎምቢያና ስዊዘርላንድ ካደረጉት የጥሎ ማለፍ ግጥሚያ ነው፡፡ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ያለምንም ግብ በመጠናቀቁ ወደተጨማሪ ሰአት ይሸጋገራሉ፡፡ ተጨማሪው ሰአትም ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት የኮሎምቢያው ጃሚንተን ካምፓዝ ከስዊዘርላንድ ግብ ጠባቂ ጋር ብቻ የተገናኘበት አጋጣሚ ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ጎል ማስቆጠር ሳይችል መቅረቱ ይታወሳል፡፡
በመሆኑም ወደፍፁም ቅጣት ምት ተሸጋግረው ኮሎምቢያ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋ ወደሩብ ፍፃሜው ማለፍ ተስኗታል፡፡ ፍፁም ቅጣት ምቱን ከሳቱት የኮሎምቢያ ሶስት ተጨዋቾች መካከል ደግሞ ካምፓዝ አንዱ ነው፡፡ ለአርጀንቲናው ሮዛሪዮ ሴንትራል ክለብ የሚጫወተው ይህ የ26 አመቱ ተጨዋች ከዚህ ሽንፈት በኋላ ወደአገሩ አልተመለሰም፡፡ ምክንያቱም የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቹ አሉታዊ አስተያየቶችና በግድያ ዛቻዎች ተጥለቅልቀዋል፡፡
የማህበራዊ ሚዲያዎቹን አስተያየት መስጫ የዘጋው ይህ ተጨዋች ከቡድን አጋሮቹ ጋር ወደኮሎምቢያ ከመሄድ በመቆጠብ መደበቅን መርጧል፡፡ ካምፓዝ በኢንስታግራም ገፁ ላይ ለአገሩ ደጋፊዎች ባስተላለፈው የይቅርታ መልእክት ‹‹ሁላችንም ተስፋ ያደረግነውን ልሰጣችሁ ባለመቻሌ አዝናለሁ፡፡ ነገር ግን ለዚህ ማሊያ ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት አሳንሼበት እንደማላውቅ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡ በሜዳ ላይ ያለኝን ሁሉ ሰጥቻለሁ፡፡ ይህንን ደግሞ ለአገሬ ሺህ ጊዜ አደርገዋለሁ፡፡›› ያለ ሲሆን አያይዞም ፍፁም ቅጣት ምት በሳተበት ወቅት ፊቱን በእጁ ሸፍኖ ሲቆጭ የሚያሳየውን ፎቶግራፍ ለጥፏል፡፡ እግር ኳስ አስቸጋሪ በመሆኑ ብስጭትና ሀዘን እንደሚያስከትል ገልፆም ይህንን ወደጥላቻ መቀየር እንደማያስፈልግ አሳስቧል፡፡
የኮሎምቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በዚህ አማካኝ ተጨዋች ላይ የተደረገው የግድያ ዛቻ እንዲመረመር አሳስቧል፡፡ ፌዴሬሽኑ ጨምሮም አቃቤ ህግ በአስቸኳይ ይህንን ዛቻ ያደረሱትን ግለሰቦች መርምሮ ለፍርድ እንዲያቀርብም ጠይቋል፡፡ እንዲሁም ‹‹የካምፓዝን ህይወትና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ዛቻዎችን ፈፅሞ እናወግዛለን›› ያለው መግለጫው ኮሎምቢያን ወክለው በአለም ዋንጫው ላይ የተሰለፉ ተጨዋቾች በሙሉ ለአገራቸው ያላቸውን ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ታማኝነት ማሳየታቸውን ገልጿል፡፡
ይህ ክስተት በኮሎምቢያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የተፈጠረውን ጥቁር ምእራፍ የሚያስታውስ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ1994 በአሜሪካ በተደረገው የአለም ዋንጫ ወቅት ኮሎምቢያ በአዘጋጇ አገር 2 ለ 1 በተሸነፈችበት ወቅት የኮሎምቢያው ተከላካይ አንድሬስ ስኮባር በራሱ ጎል ላይ ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡ ይሁንና ብሄራዊ ቡድኑ ወደአገሩ ከተመለሰ በኋላ ኢስኮባር በጠራራ ፀሀይ መገደሉ አይዘነጋም፡፡ የኮሎምቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዚህ መግለጫው ‹‹እግር ኳስ ለአንድነት፣ ለአክብሮትና ለተስፋ ክፍተት መስጠት ይኖርበታል እንጂ የጥላቻ፣ የማስፈራራትና የአመፅ መድረክ መሆን የለበትም›› ሲል የገለፀውም ለዚህ ነው፡፡
በመሆኑም ወደፍፁም ቅጣት ምት ተሸጋግረው ኮሎምቢያ 4 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፋ ወደሩብ ፍፃሜው ማለፍ ተስኗታል፡፡ ፍፁም ቅጣት ምቱን ከሳቱት የኮሎምቢያ ሶስት ተጨዋቾች መካከል ደግሞ ካምፓዝ አንዱ ነው፡፡ ለአርጀንቲናው ሮዛሪዮ ሴንትራል ክለብ የሚጫወተው ይህ የ26 አመቱ ተጨዋች ከዚህ ሽንፈት በኋላ ወደአገሩ አልተመለሰም፡፡ ምክንያቱም የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቹ አሉታዊ አስተያየቶችና በግድያ ዛቻዎች ተጥለቅልቀዋል፡፡
የማህበራዊ ሚዲያዎቹን አስተያየት መስጫ የዘጋው ይህ ተጨዋች ከቡድን አጋሮቹ ጋር ወደኮሎምቢያ ከመሄድ በመቆጠብ መደበቅን መርጧል፡፡ ካምፓዝ በኢንስታግራም ገፁ ላይ ለአገሩ ደጋፊዎች ባስተላለፈው የይቅርታ መልእክት ‹‹ሁላችንም ተስፋ ያደረግነውን ልሰጣችሁ ባለመቻሌ አዝናለሁ፡፡ ነገር ግን ለዚህ ማሊያ ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት አሳንሼበት እንደማላውቅ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡ በሜዳ ላይ ያለኝን ሁሉ ሰጥቻለሁ፡፡ ይህንን ደግሞ ለአገሬ ሺህ ጊዜ አደርገዋለሁ፡፡›› ያለ ሲሆን አያይዞም ፍፁም ቅጣት ምት በሳተበት ወቅት ፊቱን በእጁ ሸፍኖ ሲቆጭ የሚያሳየውን ፎቶግራፍ ለጥፏል፡፡ እግር ኳስ አስቸጋሪ በመሆኑ ብስጭትና ሀዘን እንደሚያስከትል ገልፆም ይህንን ወደጥላቻ መቀየር እንደማያስፈልግ አሳስቧል፡፡
የኮሎምቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መግለጫ በዚህ አማካኝ ተጨዋች ላይ የተደረገው የግድያ ዛቻ እንዲመረመር አሳስቧል፡፡ ፌዴሬሽኑ ጨምሮም አቃቤ ህግ በአስቸኳይ ይህንን ዛቻ ያደረሱትን ግለሰቦች መርምሮ ለፍርድ እንዲያቀርብም ጠይቋል፡፡ እንዲሁም ‹‹የካምፓዝን ህይወትና ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥሉ ዛቻዎችን ፈፅሞ እናወግዛለን›› ያለው መግለጫው ኮሎምቢያን ወክለው በአለም ዋንጫው ላይ የተሰለፉ ተጨዋቾች በሙሉ ለአገራቸው ያላቸውን ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ታማኝነት ማሳየታቸውን ገልጿል፡፡
ይህ ክስተት በኮሎምቢያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የተፈጠረውን ጥቁር ምእራፍ የሚያስታውስ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ1994 በአሜሪካ በተደረገው የአለም ዋንጫ ወቅት ኮሎምቢያ በአዘጋጇ አገር 2 ለ 1 በተሸነፈችበት ወቅት የኮሎምቢያው ተከላካይ አንድሬስ ስኮባር በራሱ ጎል ላይ ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡ ይሁንና ብሄራዊ ቡድኑ ወደአገሩ ከተመለሰ በኋላ ኢስኮባር በጠራራ ፀሀይ መገደሉ አይዘነጋም፡፡ የኮሎምቢያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዚህ መግለጫው ‹‹እግር ኳስ ለአንድነት፣ ለአክብሮትና ለተስፋ ክፍተት መስጠት ይኖርበታል እንጂ የጥላቻ፣ የማስፈራራትና የአመፅ መድረክ መሆን የለበትም›› ሲል የገለፀውም ለዚህ ነው፡፡
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ መዝናኛ ዜና) ታዋቂው ራፐር ጄይ-ዚ (ትክክለኛ ስሙ ሾን ካርተር) የ30ኛ ዓመት የምስረታ በዓል የኮንሰርት ጉዞውን ከባለቤቱ ቢዮንሴ እና ከልጁ ብሉ አይቪ ካርተር ጋር በመሆን ጀምሯል። ትላንት አርብ፣ ጁላይ 10 የ56 ዓመቱ ራፐር በያንግኪ ስታዲየም ባቀረበው ኮንሰርት፣ በመጀመሪያ ሜሪ ጄ. ብላይጅ የተሳተፈችበትን ታዋቂውን "Can't Knock the Hustle" የተሰኘ ዘፈን ተጫውቷል። በወቅቱም የሜሪ ጄ. ብላይጅን የዘፈን ክፍል ቢዮንሴ ተክታ ያቀረበችው ሲሆን፣ በመድረክ ላይ በልበ ሙሉነት እየተራመደች ዘፈኑን በድንቅ ሁኔታ ተጫውታዋለች። የዘፈኑን ክፍል አጠናቃ ስትጨርስ ጄይ-ዚ "ኦህ፣ መዝፈን ትችላለች እኮ!" ሲል አድናቆቱን የገለጸ ሲሆን፣ እሷም በበኩሏ ለተመልካቹ "ለፍቅረኛዬ ሞቅ ያለ አቀባበል አድርጉለት" በማለት ጄይ-ዚን በፈገግታ አሞካሽተዋለች።
ኮንሰርቱ ሲቀጥል፣ የ14 ዓመቷ ልጁ ብሉ አይቪ "Feelin' It" በተሰኘው የ1996ቱ ዝነኛ ዘፈን ላይ አባቷን በመድረክ ተቀላቅላለች። ብሉ አይቪ በዘፈኑ ማጠቃለያ ላይ የፒያኖ ሰለዋን በብቃት በመጫወት ተመልካቹን ያስደመመች ሲሆን፣ ጄይ-ዚም "ለታዋቂዋ ብሉ አይቪ ካርተር ድምጻችሁን አሰሙ" ካለ በኋላ ከልጁ ጋር ረዘም ላለ ጊዜ ተቃቅፈዋል።
የብሉ አይቪ የፒያኖ ብቃት የታየው፣ ጄይ-ዚ ባለፈው ማርች ወር ለጂኪው (GQ) መጽሔት በሰጠው ቃለ መጠይቅ "አስገራሚ የፒያኖ ተጫዋች" መሆኗን ከተናገረ በኋላ ነው። በወቅቱም "አስተማሪ እንድንቀጥርላት አትፈልግም፤ ስራ እንዲሆንባት አትፈልግም። ነገር ግን ፍጹም የሆነ የድምጽ የመለየት አቅም አላት። አንድን ዘፈን ከሰማች 'እንደገና አጫውተው' ትልና ራሷን ታስተምራለች" ብሎ ነበር። አክሎም፣ "ይህ የተፈጥሮ ተሰጥኦ ነው።... በጣም የምትፈልገውን ነገር ለማድረግ በመታገሏ ኩራት ይሰማኛል። አሁን ከመድረክ ላይ ልናወርዳት የምንችል አይመስለኝም" ሲል ገልጿል።
ብሉ አይቪ ከዚህ ቀደም በ2023ቱ "Renaissance World Tour" እና በ2025ቱ "Cowboy Carter World Tour" ላይ እናቷን በመድረክ ተቀላቅላ ነበር። በ2023ቱ ኮንሰርት ለአንድ ምሽት ብቻ እንድትታይ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ከመጀመሪያው ትርኢቷ በኋላ የተሰጡ አንዳንድ አሉታዊ አስተያየቶችን ተመልክታ፣ የ11 ዓመቷ ታዳጊ ዳግም ለመሞከር ወስና እንቅስቃሴዋን እስክታሻሽል ጠንክራ ሰርታለች።
ለ2025ቱ ኮንሰርት ደግሞ የ13 ዓመቷ ታዳጊ በተሻለ ዝግጁነት ወደ መድረክ ተመልሳ፣ ለሶስት ወራት በተካሄዱ 32 የኮንሰርት ትርኢቶች ላይ ከእናቷ ጋር ስትጨፍር ቆይታለች። በወቅቱም የቢዮንሴን የ2006 "Déjà Vu" ዘፈን የዳንስ እንቅስቃሴ ለብቻዋ በመድረክ መሃል በመጫወት ተመልካቾችን ያስደመመች ሲሆን፣ አድናቂዎችም እንቅስቃሴዋን "Dèjà Blue" በሚል ስያሜ አሞካሽተውታል።
እነዚህ ዝነኛ የጥበብ ጥንዶች ብሉ አይቪን ጨምሮ የ9 ዓመት መንታ ልጆች (ሩሚ እና ሰር) እንዳሏቸው ይታወቃል።
ኮንሰርቱ ሲቀጥል፣ የ14 ዓመቷ ልጁ ብሉ አይቪ "Feelin' It" በተሰኘው የ1996ቱ ዝነኛ ዘፈን ላይ አባቷን በመድረክ ተቀላቅላለች። ብሉ አይቪ በዘፈኑ ማጠቃለያ ላይ የፒያኖ ሰለዋን በብቃት በመጫወት ተመልካቹን ያስደመመች ሲሆን፣ ጄይ-ዚም "ለታዋቂዋ ብሉ አይቪ ካርተር ድምጻችሁን አሰሙ" ካለ በኋላ ከልጁ ጋር ረዘም ላለ ጊዜ ተቃቅፈዋል።
የብሉ አይቪ የፒያኖ ብቃት የታየው፣ ጄይ-ዚ ባለፈው ማርች ወር ለጂኪው (GQ) መጽሔት በሰጠው ቃለ መጠይቅ "አስገራሚ የፒያኖ ተጫዋች" መሆኗን ከተናገረ በኋላ ነው። በወቅቱም "አስተማሪ እንድንቀጥርላት አትፈልግም፤ ስራ እንዲሆንባት አትፈልግም። ነገር ግን ፍጹም የሆነ የድምጽ የመለየት አቅም አላት። አንድን ዘፈን ከሰማች 'እንደገና አጫውተው' ትልና ራሷን ታስተምራለች" ብሎ ነበር። አክሎም፣ "ይህ የተፈጥሮ ተሰጥኦ ነው።... በጣም የምትፈልገውን ነገር ለማድረግ በመታገሏ ኩራት ይሰማኛል። አሁን ከመድረክ ላይ ልናወርዳት የምንችል አይመስለኝም" ሲል ገልጿል።
ብሉ አይቪ ከዚህ ቀደም በ2023ቱ "Renaissance World Tour" እና በ2025ቱ "Cowboy Carter World Tour" ላይ እናቷን በመድረክ ተቀላቅላ ነበር። በ2023ቱ ኮንሰርት ለአንድ ምሽት ብቻ እንድትታይ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ ከመጀመሪያው ትርኢቷ በኋላ የተሰጡ አንዳንድ አሉታዊ አስተያየቶችን ተመልክታ፣ የ11 ዓመቷ ታዳጊ ዳግም ለመሞከር ወስና እንቅስቃሴዋን እስክታሻሽል ጠንክራ ሰርታለች።
ለ2025ቱ ኮንሰርት ደግሞ የ13 ዓመቷ ታዳጊ በተሻለ ዝግጁነት ወደ መድረክ ተመልሳ፣ ለሶስት ወራት በተካሄዱ 32 የኮንሰርት ትርኢቶች ላይ ከእናቷ ጋር ስትጨፍር ቆይታለች። በወቅቱም የቢዮንሴን የ2006 "Déjà Vu" ዘፈን የዳንስ እንቅስቃሴ ለብቻዋ በመድረክ መሃል በመጫወት ተመልካቾችን ያስደመመች ሲሆን፣ አድናቂዎችም እንቅስቃሴዋን "Dèjà Blue" በሚል ስያሜ አሞካሽተውታል።
እነዚህ ዝነኛ የጥበብ ጥንዶች ብሉ አይቪን ጨምሮ የ9 ዓመት መንታ ልጆች (ሩሚ እና ሰር) እንዳሏቸው ይታወቃል።
27 days ago
"የብራዚል እግር ኳስ ስብራት ገጥሞታል!"
የፔሌ ልጅ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ አስተዳደር በብልሹ አሰራር በመውደቁ እግርኳሱ ስብራት ገጥሞታል ስትል የፔሌ ልጅ ተናግራለች።
የአስተዳደሩ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የጎደለው አሰራር በብሔራዊ ቡድኑ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብላለች።
የእግርኳሱ ኮኮብ የፔሌ ታላቅ ሴት ልጅ አክቲቪስት እና የፊልም ባለሙያ የሆነችው ኬሊ ናሲሜንቶ ፔሌ ለሮይተርስ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ብሔራዊ ቡድኑ የገጠመውን ችግር ተናግራለች።
የብራዚል እግር ኳስ ተበላሽቷል
ሙስናና ሌላም ችግር በአስተዳደሩ ይነጸባረቃል ይህ በጣም ግልጽ ነው ብላለች።
ሁሉም ሰው አስተዳደሩ ለምን እንደማይሰራ ያውቃል ነገር ግን አንድም አካል ሊያስተካክለው አልቻለም ስትል ናሲሜንቶ ገልጻለች።
የብራዚል እግር ኳስ አሁንም ተሰጥኦ ያላቸው ምርጥ ተጫዋቾችን ማፍራቱን ቢቀጥልም በዓለም አቀፍ መድረክ የሚያሳዩት ደካማ አፈጻጸም ግን ሥር የሰደዱ መዋቅራዊ ችግሮች ውጤት መሆኑን ገልጻለች።
ብራዚል እሁድ ዕለት በኖርዌይ 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ይታወሳል።
ይህ ውጤት ብራዚል ከ1990 ወዲህ ለሩብ ፍጻሜ ማለፍ ሳትችል ስትቀር የመጀመሪያዋ ነው።
ሀገሪቱ ሪከርድ የሆነውን አምስተኛ የዓለም ዋንጫዋን ያሸነፈችው እ.ኤ.አ በ2002 ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #brazilfootball #reuters #greatpeledaughter #kelynascimento #activistfilmmaker
የፔሌ ልጅ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ አስተዳደር በብልሹ አሰራር በመውደቁ እግርኳሱ ስብራት ገጥሞታል ስትል የፔሌ ልጅ ተናግራለች።
የአስተዳደሩ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የጎደለው አሰራር በብሔራዊ ቡድኑ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብላለች።
የእግርኳሱ ኮኮብ የፔሌ ታላቅ ሴት ልጅ አክቲቪስት እና የፊልም ባለሙያ የሆነችው ኬሊ ናሲሜንቶ ፔሌ ለሮይተርስ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ብሔራዊ ቡድኑ የገጠመውን ችግር ተናግራለች።
የብራዚል እግር ኳስ ተበላሽቷል
ሙስናና ሌላም ችግር በአስተዳደሩ ይነጸባረቃል ይህ በጣም ግልጽ ነው ብላለች።
ሁሉም ሰው አስተዳደሩ ለምን እንደማይሰራ ያውቃል ነገር ግን አንድም አካል ሊያስተካክለው አልቻለም ስትል ናሲሜንቶ ገልጻለች።
የብራዚል እግር ኳስ አሁንም ተሰጥኦ ያላቸው ምርጥ ተጫዋቾችን ማፍራቱን ቢቀጥልም በዓለም አቀፍ መድረክ የሚያሳዩት ደካማ አፈጻጸም ግን ሥር የሰደዱ መዋቅራዊ ችግሮች ውጤት መሆኑን ገልጻለች።
ብራዚል እሁድ ዕለት በኖርዌይ 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ይታወሳል።
ይህ ውጤት ብራዚል ከ1990 ወዲህ ለሩብ ፍጻሜ ማለፍ ሳትችል ስትቀር የመጀመሪያዋ ነው።
ሀገሪቱ ሪከርድ የሆነውን አምስተኛ የዓለም ዋንጫዋን ያሸነፈችው እ.ኤ.አ በ2002 ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #brazilfootball #reuters #greatpeledaughter #kelynascimento #activistfilmmaker
Sponsored by
Surafel
30 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) እ.ኤ.አ ጁን 2026 በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስተባባሪነት የተቋቋመው “Pulse of Africa” የተሰኘው ሚዲያ አንድ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ተቋም ከአንድ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የዲፕሎማሲ አካዳሚ ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን የሚገልጽ ዜና አውጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ ዜናው ስምምነት ያደረጉትን ተቋማት ስም ሆን ብሎ የደበቀ እና እጅግ አሻሚ ቃላትን የተጠቀመ መሆኑ ከፍተኛ ትኩረት ስቧል። በኤምሬትስ በኩል ያለው ተቋም አንዋር ጋርጋሽ የዲፕሎማሲ አካዳሚ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በኩል ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋዊ የምርምር እና የስልጠና ተቋም የሆነው የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ነበር። ዜናው የተፈረመበትን ሂሊ ክልላዊ የውይይት መድረክ ሳይቀር ዝም ብሎ አንድ ክልላዊ መድረክ በማለት ሸፍኖታል።
በአንጻሩ የኤምሬትሱ ጋርጋሽ አካዳሚ በዲጂታል መድረኮቹ ላይ ስምምነቱን በይፋ እና በዝርዝር አውጥቶታል። የስምምነቱ ዓላማም በሁለቱ ወገኖች መካከል በውጭ ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ምርምር እና ጥናቶችን ማካሄድ፣ ስትራቴጂካዊ ውይይቶችን ማደራጀት፣ የዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን መስጠት እና የባለሙያዎች ልውውጥ ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ክስተት ብዙዎችን ያነጋገረው፣ ሚዲያው የተቋቋመው ስለ አፍሪካ የሚነገሩ አሉታዊ ትርክቶችን ለመቀልበስ እና አህጉሪቱ ከውጭ ሞግዚትነት ነጻ የሆነ የራሷን ትርክት እንድትቀርጽ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ከተናገሩ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ ለኤምሬትስ ጥቅም ሲባል መረጃዎችን መደበቁ ነው።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ዜናውን የደበቀበት ምክንያት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርምር ክንፍ ከኤምሬትስ አካዳሚ የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያገኘ መሆኑን በይፋ ማመኑ፣ መንግስት ከሚገነባው የብሔራዊ ኩራት እና የነጻ ውሳኔ ሰጪነት ትርክት ጋር ስለሚጋጭ ነው።
ይህም የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ግንኙነት ከትብብር አልፎ ወደ ስትራቴጂካዊ ጥገኝነት እያመራ መሆኑን እንደሚያሳይ ባለሙያዎች ይሞግታሉ። ይህ የጥገኝነት መዋቅር በዋናነት የተገነባው በፋይናንስ፣ በወታደራዊ ሎጅስቲክስ እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ነው። በ2018 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ሀገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስትታመስ፣ አቡ ዳቢ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ3 ቢሊዮን ዶላር ተቀማጭ በማድረግ ትልቅ የፋይናንስ ድጋፍ አድርጋለች። በ2021 የትግራይ ጦርነት በተባባሰበት እና የአዲስ አበባ መውደቅ ስጋት በነበረበት ወቅት ደግሞ፣ ኤምሬትስ ድሮኖችን እና ወታደራዊ ትጥቆችን በማቅረብ የጦርነቱን ሚዛን ለመቀልበስ ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። ከዚህም በተጨማሪ በኢነርጂ፣ በግብርና፣ እና የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ከኤምሬትስ ወደብ አስተዳደሮች ጋር በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ተደርጓል።
አሁን የተፈረመው የዲፕሎማሲ ስልጠና ስምምነትም፣ የዚህ ጥገኝነት አራተኛው እና ረቂቁ ምዕራፍ መሆኑ ይገለጻል። ይህም ኤምሬትስ የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲፕሎማት ትውልድ በመቅረጽ እና የውጭ ፖሊሲዋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ በማሳረፍ የረጅም ጊዜ ፍላጎቷን እያስጠበቀች መሆኑን ያመላክታል። በተጨማሪም ባለፈው ጥር ወር ሚድል ኢስት አይ ባወጣው የምርመራ ዘገባ፣ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ አማካሪ የነበሩ ግለሰብን ጠቅሶ፣ ኢትዮጵያ በሱዳን፣ በቀይ ባህር (አሰብ ወደብ)፣ እና በኤርትራ ጉዳይ ላይ ከኤምሬትስ ውጭ የራሷን ነጻ ውሳኔ ማሳለፍ እስኪያቅታት ድረስ ጫና ውስጥ መውደቋን አስነብቧል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጠናው ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ገለልተኛ የውሳኔ ሰጪነት ሚና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው።
በአንጻሩ የኤምሬትሱ ጋርጋሽ አካዳሚ በዲጂታል መድረኮቹ ላይ ስምምነቱን በይፋ እና በዝርዝር አውጥቶታል። የስምምነቱ ዓላማም በሁለቱ ወገኖች መካከል በውጭ ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ምርምር እና ጥናቶችን ማካሄድ፣ ስትራቴጂካዊ ውይይቶችን ማደራጀት፣ የዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን መስጠት እና የባለሙያዎች ልውውጥ ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ክስተት ብዙዎችን ያነጋገረው፣ ሚዲያው የተቋቋመው ስለ አፍሪካ የሚነገሩ አሉታዊ ትርክቶችን ለመቀልበስ እና አህጉሪቱ ከውጭ ሞግዚትነት ነጻ የሆነ የራሷን ትርክት እንድትቀርጽ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ከተናገሩ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ ለኤምሬትስ ጥቅም ሲባል መረጃዎችን መደበቁ ነው።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ዜናውን የደበቀበት ምክንያት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርምር ክንፍ ከኤምሬትስ አካዳሚ የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያገኘ መሆኑን በይፋ ማመኑ፣ መንግስት ከሚገነባው የብሔራዊ ኩራት እና የነጻ ውሳኔ ሰጪነት ትርክት ጋር ስለሚጋጭ ነው።
ይህም የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ግንኙነት ከትብብር አልፎ ወደ ስትራቴጂካዊ ጥገኝነት እያመራ መሆኑን እንደሚያሳይ ባለሙያዎች ይሞግታሉ። ይህ የጥገኝነት መዋቅር በዋናነት የተገነባው በፋይናንስ፣ በወታደራዊ ሎጅስቲክስ እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ነው። በ2018 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ሀገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስትታመስ፣ አቡ ዳቢ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ3 ቢሊዮን ዶላር ተቀማጭ በማድረግ ትልቅ የፋይናንስ ድጋፍ አድርጋለች። በ2021 የትግራይ ጦርነት በተባባሰበት እና የአዲስ አበባ መውደቅ ስጋት በነበረበት ወቅት ደግሞ፣ ኤምሬትስ ድሮኖችን እና ወታደራዊ ትጥቆችን በማቅረብ የጦርነቱን ሚዛን ለመቀልበስ ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። ከዚህም በተጨማሪ በኢነርጂ፣ በግብርና፣ እና የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ከኤምሬትስ ወደብ አስተዳደሮች ጋር በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ተደርጓል።
አሁን የተፈረመው የዲፕሎማሲ ስልጠና ስምምነትም፣ የዚህ ጥገኝነት አራተኛው እና ረቂቁ ምዕራፍ መሆኑ ይገለጻል። ይህም ኤምሬትስ የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲፕሎማት ትውልድ በመቅረጽ እና የውጭ ፖሊሲዋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ በማሳረፍ የረጅም ጊዜ ፍላጎቷን እያስጠበቀች መሆኑን ያመላክታል። በተጨማሪም ባለፈው ጥር ወር ሚድል ኢስት አይ ባወጣው የምርመራ ዘገባ፣ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ አማካሪ የነበሩ ግለሰብን ጠቅሶ፣ ኢትዮጵያ በሱዳን፣ በቀይ ባህር (አሰብ ወደብ)፣ እና በኤርትራ ጉዳይ ላይ ከኤምሬትስ ውጭ የራሷን ነጻ ውሳኔ ማሳለፍ እስኪያቅታት ድረስ ጫና ውስጥ መውደቋን አስነብቧል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጠናው ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ገለልተኛ የውሳኔ ሰጪነት ሚና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው።
1 month ago
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ብጹዕ አባታችን አቡነ መርቆሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
ብጹዕ አባታችን አቡነ መርቆሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
1 month ago
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ብጹዕ አባታችን አቡነ መቃሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
ብጹዕ አባታችን አቡነ መቃሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
1 month ago
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ብጹዕ አባታችን አቡነ መቃሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
ብጹዕ አባታችን አቡነ መቃሪዮስ ፣ የካናዳ ሐገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
መንፈሳዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ልዑል እግዚአብሔር በሰጣችሁ ጸጋ በተለያየ ስፍራ የምታገለግሉ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን
ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዳዎች ፣
የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት ፣
ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።
"ጾም የነፍስ ምግብ ነው፤ ለፈተናም መቋቋሚያ ጥንካሬን ይሰጣል።" እንዲል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ።" እኛ ኦርቶዶክሳዊያን የሐዋሪያት ጾም ላይ እንገኛለን፡፡
የሰኔ ጾም (ጾመ ሐዋርያት) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰባቱ አዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን፣ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉና ለስብከተ ወንጌል ከመሰማራታቸው በፊት የጾሙት ጾም ነው።ይህ ጾም እንደ እምነቱ አስተምህሮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ የበረከት ጾም ነው። ይህን ጾም እንድንካፈል ለፈቀደልን ለልዑል እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው፤ለጾሙ ፍችም በሰላም ያድርሰን እያልኩ፣መግለጫው የተዘጋጀው በጽሁፍ ስለሆነ በተዘጋጀበት አግባብ ይቀርባል፡፡
በወልድ ውሉድ ፣ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባለ ሁሉ ፣ አምላኩን በንጽሐ ነፍስ ፣ በንጽሐ ሥጋ የሚያገለግልበት እና ፣ ከራሱ ከፈጣሪው መድሐኒዓለም ክርስቶስ ዘንድ የተሰጠው የጸጋ አገልግሎት፣ነገር ግን ጥቂቶች ብቻ የሚያገኙት ፤ መጨከንን ፣ ጥብዓትን ፣ ትሕርምትን እና ትዕግሥትን የሚጠይቅ ሕይወት ፣ የምንኩስና ሕይወት እና ሥርዓት ነው።የምንኩስና ሕይወት እና የገዳማዊ ሥርዓት በቅዱሳን አባቶች አባ እንጦንስ እና አባ መቃርስ የተጀመረ ሲሆን ፣ ሕይወቱም ሥርዓቱም በቀኖና ቤተክርስቲያን የተደነገገ እና የጸደቀ ሕግ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ፣ ገዳም የእኔ የግሌ የሚሉት ንብረት የሌለበት፣ ሁሉ በማኅበር በአንድነት በጸሎት በስራ እየተጉ ፍጹም የዓለምን ኃላፊነት ተረድተው ፣ የማታልፍ የእግዚአብሔር መንግስት እንዳለች በመገንዘብ ዘወትር በቀኖና ተወስነው የሚኖሩበት የቅዱሳን መኖሪያና ጸጋ እግዚአብሔር የማይለይበት የዲያቢሎስ ፈተና የሚበዛበት ስፍራ ነው።
ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ በመሆኑ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ አርአያ ሆኖን ፣ በገዳመ ቆሮንጦስ ከዲያቢሎስ ይፈተን ዘንድ ተቀመጠ (ማቴ. 4፡ 1-11) ፈታኝ ዲያቢሎስንም ድል አደረገው ፣ ገዳምና ገዳማዊ ሕይወት አስፈላጊ ሆኖ የመሰረተልን አምላካችን አርአያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዛሬም እርሱን በመከተል ገዳማዊ ሕይወት ለትሩፋት መስሪያ ፣ ለንስሃ ሕይወት ማቆያ ፣ ለበረከት ለረድኤት የአምላካችንን አርአያነት ተከትለው አባቶች እናቶች በገዳም ተወስነው ይገኛሉ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥና ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትናገራለች።
ገዳማት የቤተ-ክርስቲያናችን ስውር ጓዳዎችና የሚስጢር መዝገቦች ፣ የመማጸኛ ቅዱስ ስፍራዎች ፣ የቤ-ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎት መሰረት ፣ የተግባራዊ ክርስትና ምሳሌዎች እና የታላላቅ የቤተ-ክርስቲያን ሊቃውንት መፍለቂያዎች ናቸው።
እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ ፣ ትውልድንም በክርስቲያናዊ ስነ-ምግባር እያነጹ ይቀጥሉ ዘንድ ገቢ ያስፈልጋቸዋል። ይህንን ገቢያቸውን ከሚያገኙባቸው መንገዶች መካከል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጡት መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ።
ይሁንና አንዳንዴ ተፈጥሮ ፊቷን ስታዞር እና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ሲበረቱ ሰው ሰራሽ ችግሮችም ሲጨመሩ፣ገዳማት የገቢ ምንጫቸውና ህልውናቸው ሙሉ በሙሉ ህዝበ ክርስቲያኑ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል ፤ ከ160 በላይ ገዳማዊያን የሚገኙበት ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግርም በዚህ ደረጃ የሚገለጽ ነው።
በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማውያን ከፀሃይ ፣ ከብርድ ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ ፣ ገዳማውያኑ ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡ እና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ ፣ በጠቅላይ ቤተ-ክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው ፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን ፣ ገዳሙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት ፣ በሐገረ ስብከት እና በጠቅላይ ቤተ-ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
“ከእግዚአብሔር ዐይን የተሰወረ ምንም ፍጥረት የለም፤ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት በሚገባን በርሱ ፊት ሁሉም ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው” (ዕብራውያን 4:13) እንዲል ቃሉ፣እኛም አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የተሰሩ ስራዎችን፣የተደረገውን ድጋፍ፣ በቀጣይ ስለሚከናወኑ ስራዎች እና ተያያዥ ጉዳዮችን በተለያዩ ጊዜያት ለምዕመኑ ይፋ እያደረግን፣እያሳወቅን ዛሬ ላይ ደርሰናል፡፡ዛሬ ስለ ፕሮጀክቱ እና የደረሰበትን ደረጃ በሚመለከት የምንሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለ4ኛ ጊዜ ሲሆን ይህም ምዕመኑ ፕሮጀክቱ የደረሰበትን ወቅታዊ የስራ ደረጃን እንዲገነዘብ ለማድረግ በማሰብ ነው፡፡
በገዳሙ የተያዙ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ ስንቀሳቀስ ቆይተናል፣አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ
በቴሌቪዥን ጥራታቸውን የጠበቁና ገላጭ የሆኑ ዶክመንተሪዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥረት ተደርጓል።
ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል፤እየተደረገም ይገኛል። በዚህም እስከ አሁን 52,640,000 ብር ( ሃምሳ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ አርባ ሽህ ብር)የገንዘብ ድጋፍ እና 11,320,000 ብር ( አስራ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ ሽህ ብር) የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።
በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 2 ዓመት ከ 6 ወር ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው እና በሁለተኛው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን 65 % በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛል።
ለገዳማውያኑ እንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
የእናቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶለት እየተገለገሉበት ይገኛል።
ገዳማት መንፈሳዊ እና ማኅበራዊ ኃላፊነት የሚወጡበት ፣ በተፈጥሮ እና ሰው - ሰራሽ አደጋዎች የተጎዱ ማኅበረሰቦችን የሚረዱበት እና ሕገ ወንጌልን የሚፈጽሙበት አቅምን ለማግኘት ፣ የኢኮኖሚ ነጻነት አስፈላጊ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ “ገዳማዊ ሕይወት ጠንካራ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ እንዲሁ ጠንካራ ትሆናለች ፤ ነገር ግን ገዳማዊ ሕይወት መዳከም ከጀመረ ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ትደክማለች።” በማለት የገዳማት መጠንከርን አጽንዖት ሰጥቶ ይናገራል።
በዚህም መሰረት ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ፣ ገዳማውያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ እየሰሩበት ይገኛሉ እንዲሁም አዲስ አበባ ላይ ደረጃውን የጠበቀ ሱቅ ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የእርሻ መሬት በመከራየት የእህል እና የጥጥ ምርቶችን በስፋ እያመረቱ ይገኛሉ፡፡
ገዳሙ በሃሙሲት ከተማ ላይ የእህል መጋዘን በመከራየት ያመረታቸው ምርቶች እንዲሁም ከገበሬ በመረከብ ለአከባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በስፋት እያቀረበ ይገኛል፡፡
ግሸን እና ላሊበላ እንዲሁም የተለያዩ አብያተክርስቲያናት እና ገዳማት ላይ ገዳሙ ያመረታቸው ምርቶች ለሽያጭ እያቀረበ ይገኛል፡፡
ምንኩስና በምድር ላይ እየኖሩ ከምድራውያን ተለይቶ ከሰማያውያን ቅዱሳን መላእክት ጋር ኅብረት የሚፈጥሩበት እና የሚገናኙበት መንገድ ነው።ሥራ ደግሞ የቅድስና መድረሻ የዲያብሎስ ውጊያን ማምለጫ መንገድ ነው። እንደ ሃገራችን አባባል “ሥራ የፈታ መነኩሴ ቆቡን ቀዶ ይሰፋል።” እንዲል ፣ ያለ ሥራ መቀመጥ በገዛ ፍቃድ አዕምሮን ለሰይጣን ቤተ ሙከራነት ማስረከብ ነውና ፣ ሁሌ ትጥቃቸውን ይዘው ከእግሩ በታች በመሆን የሚተጉ ንቁዓን ወታደሮች ፤ ሀብት ንብረታቸውን ትተው ለዓለሙ ሙት የሆኑ መነኮሳት በተሰበሰቡበት ገዳም፦ እርሻ ፣ የእጅ ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራትን የሚያከናውኑበት ቦታ ሊኖራቸው ግድ ነው። ነገር ግን በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ያለው መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ እና በረሃማነት ፣ ለእርሻ ሥራ ምቹ ባይሆንም ሴት መነኮሳዪያት የሚሠሩበት የተግባር ቤት ግንባታ ተጠናቆ ፣ የእደ ጥበብ ማምረቻ ማሽኖች ገብተው ገዳሙ ገቢ የሚያገኝበት እና ፣ መነኮሳዪታት የሰይጣንን ፈተና ድል የሚነሱበት ምቹ የሥራ ቦታ ተፈጥሯል። ከ20 ላላነሱ መነኮሳዪያት ሙያዊ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ቦታ ድረስ በማቅረብ ለረጅም ወራት ሥልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ስራ ገብተዋል።
የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል፣ በስፋት ለሽያጭ እየቀረበም ይገኛል፡፡
ገዳማት ከተፈጥሮ ጋር ባላቸው ትስስር ገዳማውያን ለሱባኤ የሚመርጡት ከከተማ የወጡ ፣ ዙርያቸውን በዕፀዋት የተሸፈኑ ገዳማትን ነው። ቤተክርስቲያን የነፍስን ቁስል ስታክም የተፈጥሮ መንፈስን ታድሳለች። ይህን ተመጋጋቢ ሂደት መነጠል የማይቻል ሲሆን ፣ በሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም ምድረበዳነት ይህን ሂደት አስቀርቶ ለዓመታት ቢቆይም ፣ በተሰሩ የአካባቢ ጥበቃ እና የአረንጓዴ ልማት ስራዎች ገዳሙ በእጽዋት እንዲሸፈን ከማድረጉም ባሻገር የአካባቢ የአየር ንብረት ጥበቃ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ማለት ይቻላል።
ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ እናቶች እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለግንባታ አገልግሎት የሚውሉ የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽን ፣ ዊንች ማሽን ፣ ኮንክሪት ቫይብሬተር፣ኮምፓክተር እንዲሁም ዘመናዊ የብሎኬት ማምረቻ ማሽን ግዥ ተፈጽሞ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሙሉ ለሙሉ በራስ አቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታውን የመከለል፣የማስፋፋት እና ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት|ቤት ፣ ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ እንዲሁም 717 (ሰባት መቶ አስራ ሰባት) ካሬ ሜትር ለገበያ ማዕከል ግንባታ የሚውል ቦታ ከመንግስት በሊዝ ግዥ ተከናውኗል፡፡
ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የሚመለከታቸው የወረዳ ቤተ ክህነት፣ የሃገረ ስብከት እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት አመራሮች ፣መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪዎች ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን ፣ ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙንም ለማስተዋወቅ በዘማሪ ዲያቆን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የተሰኘ ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ቲዩብ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፤ አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን፣ተራራው እየተቆረጠ የአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ፤ 260 ሜትር የሚሆን መንገድ ስራው ተጠናቆ ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ሆኖ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
የአባቶች እና የሊቃውንት በዓት የግንባታ ሥራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ለአባቶች መነኮሳት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አስፈላጊው ቁሳቁስ ተሟቶለት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡
መነኮሳቱ ጉባኤዎችን፣ውይይቶችን ለማድረግ፣መንፈሳዊ ትምህርትን ለመስጠት የሚገለገሉበት ደረጃውን የጠበቀ የመሰብሰቢያ አዳራሽም ግንባታው ተጠናቆ እየተገለገሉበት ይገኛሉ፡፡
ዓይነ ስውራን እና የማየት እክል ያለባቸው ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ፣ የጸሎት መጻሕፍት እና ሌሎች መንፈሳዊ መጻሕፍትን በራሳቸው እንዲያነቡ፣በአምልኮ ሕይወት በእኩልነት እንዲሳተፉ እና ሁሉም ምዕመናን የመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽነት እንዲያገኙ ለማስቻል የብሬል መጽሐፍ ቅዱስ ፣ውዳሴ ማርያም እና መዝሙረ ዳዊት ግዢ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ/ም በሚኒሊየም አዳራሽ ተጋባዥ እንግዶች እና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ገዳሙን ለማስተዋወቅ እንዲሁም ያለበትን ደረጃ ለማሳየት መርሃ ግብር ተዘጋጅቶ ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡
“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት፤ ተስፋን ሳንቆርጥ በጊዜው እናጭዳለንና፤ እንዲል (ገላትያ 6፥9) ።” ጅምራቸው መልካም፣ግንባታቸውም በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ የሚገኙ ስራዎችም ይገኛሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስቲያን ትሩፋት” በሚል ንቅናቄ እየተሠሩ ካሉ ሥራዎች መካከል፡-
በገዳሙ ውስጥ የሚገኘው እና ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚፈጸምበት በቅዱስ ሚካኤል ስም የተሰየመው ህንጻ ቤተ ክርስቲያን “ቤተ መቅደስ” ፣ እጅግ ጠባብ እና ከጥቂት ጊዜያት በኃላ የመፍረስ አደጋ የተጋረጠበት መሆኑ ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት፣የጥንታዊውን የቤተ ክርስቲያን ቅርጽ ባልተወ መልኩ ፣ወደ ፊት የመነኮሳት እና ምዕመናን ቁጥር እንደሚጨምር በማሰብ ካለበት ስፋት በመጨመር እና ፣ መሰረታዊ የግንባታ ንድፍ በማውጣት፣ የሰርቬ ስራ በማከናወን ግንባታው ተጀምሮ የግንባታ ስራው ከ25 በመቶ በላይ ተከናውኗል፡፡
የግብጽ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ታሪካዊ ክሥተቶች ተፈትና በነበረችበት ወቅት፣ ዳግም ሕዳሴዋን ያስገኙላት ሦስት ዐበይት ጉዳዮች ነበሩ። እነርሱም፦ የሥነ መለኮት ኮሌጅ መከፈት ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ እና የበጎ አድራጊ ምዕመናን መገኘት ናቸው።
ከዚህ የለውጥ ፋና ጀርባ የነበረውም ሊቀ ዲያቆናት ማር ሀቢብ ጊዮርጊስ ፣ ለትምህርት ሥርዓት ትኩረት በመስጠቱ ዛሬ ያሉ ግብጻውያን ከሀገራቸው አልፈው በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ፣ ቤተ ክርስቲያንን በማስፋፋት ፣ የተማረ እና ለቤተ ክርስቲያን ፍቅር የጸናበት ትውልድ በማፍራት ጠንካራ ሥርዓትን መዘርጋት ችለዋል።
ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም መንፈሳዊ አገልጋዮችን ለማፍራት እና የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም የዕውቀት ማዕከል ለመሆን፣ ከመንግሥት ግዥ በፈጸምነው የሊዝ መሬት ላይ G+3 የአብነት ትምህርት ቤት ስራን እያከናወነ ሲሆን የግንባታ ስራውንም ከ70 በመቶ በላይ ማሳካት ተችሏል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ያጋጠሟትን ችግሮች ያለፈችው በዓለማዊውም በመንፈሳዊውም ዕውቀት በበቁ ልጆቿ ነውና፣ በሁለት እንደተሳለ ሰይፍ ፍጹም በተሰማሩበት ሁሉ ስኬትን የሚጎናጸፉ አገልጋዮችን ለማፍራት ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ 12ኛ ክፍል የአስኳላ ትምህርት ቤት እየተሰራ ሲሆን ግንባታው የፊኒሽንግ ስራ ላይ የደረሰ እና ለትምህርት ቤቱ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን በማሟላት ላይ ይገኛል፡፡እንዲሁም የትምህርት ቤቱ ካሪኩለም ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል
የጸበልተኞች እና የሱባኤ ማረፊያ ቤት ግንባታ ለማከናወን አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ፤ ማለትም የከርሰ ምድር ውሃ የማውጣት እና 8 ኪሎ ሜትር የሚረዝም የመብራት ዝርጋታ ስራ የሚከናወን ይሆናል፡፡
ከፍተኛ ደረጃ ክሊኒክ፣የንጽህና መጠበቂያ ውጤቶች ማምረቻ መጋዘን፣የምግብ ማቀነባበሪያ እየተሰሩ ካሉ እና በቀጣይ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል ናቸው፡፡
በገዳሙ የተከናወነው የልማት ስራ አበረታች የሚባል ቢሆንም በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ያደረጉ ተግዳሮቶችም ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሬ።
በገበያ ላይ የእቃዎች አቅርቦት እጥረት።
ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
የነዳጅ እና የትራንስፖርት ዋጋ በእጅጉ መጨመር።
በሶሻል ሚዲያ በተለይም ቲክቶክ ላይ ትክክለኛ ያልሆኑ፣ተጨባጭ ማስረጃ ሳይያዝ፣ የገዳሙ አባቶችንም ሆነ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ያሉ የሚመለከታቸውን አካላት ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁ ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ዛሬም እያጋጠመ ያለ ችግር ነው፡፡
እነዚህን ከላይ የተጠቀሱት በገዳሙ ላይ ሊሰሩ የታስቡ ፕሮጀክቶች በሁለት ዓመት ሰርተን የምናጠናቅቅ ሲሆን በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍፃሜ አድርሶ ገዳማውያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እራሳቸውን እንዲችሉ እና ከልመና እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚስሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 ብር (ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን ብር) የሚያስፈልግ ሲሆን ይህን የማሰባሰብ ሥራም የተጀመሩ የልማት ሥራዎች ተፈፃሚ እስኪሆኑ ድረስ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ ፥ በጽድቄም ቀኝ እጅ እደግፍሃለሁ፤ (ኢሳይያስ 41:10)።” እንዲል ቃሉ፤ የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ሁሉ በሃያሉ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት ፣ በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት እየታለፉ ገዳማዊያኑን ካለባቸው የዓለም ፈተና ለመታደግ አሁንም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ድንቅ ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡
ጠቢቡ ሰሎሞንም “ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል ፣ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል” ይላል፡፡ ቅዱሳን አባቶች ጀምረው ሳይፈጽሙት የተውት ስራ የለምና እኛም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት እና የቃል ኪዳን ልጆች በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድኅነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው ጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።
የገዳማውያኑ ጸሎት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን !
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም
ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ
1 month ago
የመደመር አንቀጽ
የትውልድን ትኩረት የሚሻ አካባቢ
ትውልዱ የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትን መመልከቻ መነጽሩ በሦስት ተያያዥነት ባላቸው ነጥቦች ላይ የሚቃኝ ነው።
የመጀመሪያው ለሀገራችን ባለው ቅርበት ነው። በዚህ መልከአ ምድራዊ ቅርበትና ግንኙነት የተነሣ የሃይማኖት፣ የባህል እና የሥልጣኔ መወራረስ ተፈጥሯል።
በአንዱ አካባቢ የተፈጠረ ነገር በሌላው አካባቢ አዎንታዊም ይሁን አሉታዊ ተፅዕኖ ኖሮታል።
ሁለተኛው ያለው መቀራረብ በአዳዲስ ለውጦችንና ከሥተቶች ታጅቦ፤ ይበልጥ እርስ በእርስ እየተሳሰረ የመጣ ጂኦፖለቲካ መፈጠሩ ነው።
በዚህም ውስጥ በጋራ ልንሠራባቸው ወይም የልዩነት ነጥብ ሊሆኑ የሚችሉ፤ እኛም እነርሱ ላይ፡ እነርሱም እኛ ላይ የተለያዩ ፍላጎቶች ያለን መሆኑ ነው።
ሦስተኛው ደግሞ እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ፤ ካካበቱት ዐቅም የተነሣ ይበልጥ የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ኃይል ሆነው የመውጣት ዕድል ያላቸው መሆኑ ነው።
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ በተሳሰረ ጂኦፖለቲካ ውስጥ፤ ጠንካራ አካባቢያዊ ኃይል መኖሩን የሚገነዘብ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 259
የትውልድን ትኩረት የሚሻ አካባቢ
ትውልዱ የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትን መመልከቻ መነጽሩ በሦስት ተያያዥነት ባላቸው ነጥቦች ላይ የሚቃኝ ነው።
የመጀመሪያው ለሀገራችን ባለው ቅርበት ነው። በዚህ መልከአ ምድራዊ ቅርበትና ግንኙነት የተነሣ የሃይማኖት፣ የባህል እና የሥልጣኔ መወራረስ ተፈጥሯል።
በአንዱ አካባቢ የተፈጠረ ነገር በሌላው አካባቢ አዎንታዊም ይሁን አሉታዊ ተፅዕኖ ኖሮታል።
ሁለተኛው ያለው መቀራረብ በአዳዲስ ለውጦችንና ከሥተቶች ታጅቦ፤ ይበልጥ እርስ በእርስ እየተሳሰረ የመጣ ጂኦፖለቲካ መፈጠሩ ነው።
በዚህም ውስጥ በጋራ ልንሠራባቸው ወይም የልዩነት ነጥብ ሊሆኑ የሚችሉ፤ እኛም እነርሱ ላይ፡ እነርሱም እኛ ላይ የተለያዩ ፍላጎቶች ያለን መሆኑ ነው።
ሦስተኛው ደግሞ እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ፤ ካካበቱት ዐቅም የተነሣ ይበልጥ የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ኃይል ሆነው የመውጣት ዕድል ያላቸው መሆኑ ነው።
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ በተሳሰረ ጂኦፖለቲካ ውስጥ፤ ጠንካራ አካባቢያዊ ኃይል መኖሩን የሚገነዘብ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 259
1 month ago
ኤአይ የሚያስከትለውን አደጋ ለማስቀረት በህግ መመራት አለበት - አንቶኒዮ ጉተሬዝ
የሰውሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በተለይም በህጻናት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለማስቀረት በህግ መመራት እንዳለበት የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አሳሰቡ፡፡
ዋና ጸኃፊው ይህን ያሉት በሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዙሪያ በመንግሥታት ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጄኔቫ በተካሄደው ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ነው፡፡
ቴክኖሎጂው የዓለምን ኢኮኖሚ፣ ምርጫ፣ የስራ እድል እንዲሁም የጸጥታና ደህንነት ሁኔታ የመወሰን አቅም እንዳለው ገልጸው፥ ነገር ግን ቴክኖሎጂውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጭምር ሊቆጣጠሩት በማይችሉት ፍጥነት እያደገ ነው ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተዋል፡፡
የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የሚያበረክተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ ይበልጥ እንዲጠናከርና በተለይም በህጻናት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ለማስቀረት የሚመራበት ዓለም አቀፍ ህግ ተግባራዊ መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
መድረኩ የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የሚያስከትለውን ጉዳት ለማስቀረትና መልካም እድሎቹን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችሉ ህጎች በሚዘጋጁበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
40 አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን በቴክኖሎጂው ትግበራ ዙሪያ ባከናወነው ጥናት መሰረት ሳይንሳዊ ግኝቶችን በመድረኩ ላይ ማቅረቡም ነው የተገለጸው፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የሰውሰራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በተለይም በህጻናት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አሉታዊ ተጽዕኖ ለማስቀረት በህግ መመራት እንዳለበት የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አሳሰቡ፡፡
ዋና ጸኃፊው ይህን ያሉት በሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዙሪያ በመንግሥታት ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጄኔቫ በተካሄደው ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ነው፡፡
ቴክኖሎጂው የዓለምን ኢኮኖሚ፣ ምርጫ፣ የስራ እድል እንዲሁም የጸጥታና ደህንነት ሁኔታ የመወሰን አቅም እንዳለው ገልጸው፥ ነገር ግን ቴክኖሎጂውን የሚጠቀሙ ሰዎች ጭምር ሊቆጣጠሩት በማይችሉት ፍጥነት እያደገ ነው ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተዋል፡፡
የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የሚያበረክተው አዎንታዊ አስተዋጽኦ ይበልጥ እንዲጠናከርና በተለይም በህጻናት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ለማስቀረት የሚመራበት ዓለም አቀፍ ህግ ተግባራዊ መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
መድረኩ የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የሚያስከትለውን ጉዳት ለማስቀረትና መልካም እድሎቹን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችሉ ህጎች በሚዘጋጁበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
40 አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን በቴክኖሎጂው ትግበራ ዙሪያ ባከናወነው ጥናት መሰረት ሳይንሳዊ ግኝቶችን በመድረኩ ላይ ማቅረቡም ነው የተገለጸው፡፡
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የመደመር አንቀጽ
የአፍሪካ ቀንድ ለመካከለኛው ምሥራቅ መካከለኛው ምሥራቅ ለአፍሪካ ቀንድ እጅግ አስፈላጊ አካባቢ ናቸው።
በታሪክም ሁለቱ አካባቢዎች በሕዝቦች እንቅስቃሴ፣ በንግድ፣ በወታደራዊ ንቅናቄ፣ በሃይማኖትና በባህል ሲገናኙ ኖረዋል።
አሁንም በሁለቱ አካባቢ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እየሰፋና እየተጠናከረ መጥቷል።
ከዚህም በኋላ በሚኖሩ ትውልዶች ዘንድ፤ በሁለቱ አካባቢዎች ሀገራት መካካል የሚኖረው ግንኙነት፤ በአሉታም ይሁን በአዎንታ እጅግ የገዘፈ ተፅዕኖ ይኖረዋል።
ይኽ ግንኙነት በብልሐት ከተያዘ ሊጠቅም የሚችል፤ እንዲሁም አያያዙ ከተበላሸ ብዙ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ሊያስከትል የሚችል ነው።
ስለዚህም ግንኙነቱ ሊፈጥረው ከሚችለው ዕድልም ይሁን አደጋ አንጻር፤ በነባራዊ እንዲሁም በቀጣይ ዘመናት በቀንዱ እጅግ ትኩረት ከሚፈልጉ ግንኙነቶች መካከል ነው።
የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት የተፅዕኖ እንቅስቃሴና ደኅንነታቸውን ለማስጠበቅ ትኩረት ካደረጉባቸው አካባቢዎች ዓይናቸው በዋናነት ያረፈው፤ ወደ ሌላኛው የቀይባሕር ዳርቻ፤ የአፍሪካ ቀንድ ነው።
ይኽ ባሕርን ተሻግሮ ተፅዕኖን የማስፋት ፍላጎት አሁን የተጀመረ ሳይሆን፤ በየዘመኑ በሁለቱም ዳርቻ የነበሩ ሀገራት ትኩረት ያደረጉበት የዘመናት ስትራቴጂ ነው፡፡
ከጥንት ጀምሮ በቀይ ባሕር ሁለት ጫፍ ያሉ ሀገራት፤ ባሕርን ተሻገርው ሌላኛውን የቀይ ባሕር ወሰን ለመቆጣጠርና ግንኙነት ለመፍጠር የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ነበረ።
ይኸም በአንደኛው የቀይ ባሕር በኩል የሚፈጠር አደጋም ሆነ ዕድል፤ በሌላኛው የቀይባሕር በኩል ተፅዕኖ እንደሚያደርስ ከመገንዘብ የሚመነጭ ነው።
በአክሱም ሥልጣኔ ዘመን፤ የእኛው ዐፄ ካሌብ ቀይ ባሕርን ተሻግሮ ደቡብ ዓረቢያን ለመቆጣጠር ችሎ ነበር።
ዓረቦች የአካባቢው ኃያላን ሆነው በተነሡበት ከ8ኛው እስከ 14ኛው መክዘ በነበረው ጊዜ፤ ቀይ ባሕርን ተሻግረው የአፍሪካን ቀንድ ለመያዝ ሞክረው ነበር።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 245/246
የአፍሪካ ቀንድ ለመካከለኛው ምሥራቅ መካከለኛው ምሥራቅ ለአፍሪካ ቀንድ እጅግ አስፈላጊ አካባቢ ናቸው።
በታሪክም ሁለቱ አካባቢዎች በሕዝቦች እንቅስቃሴ፣ በንግድ፣ በወታደራዊ ንቅናቄ፣ በሃይማኖትና በባህል ሲገናኙ ኖረዋል።
አሁንም በሁለቱ አካባቢ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እየሰፋና እየተጠናከረ መጥቷል።
ከዚህም በኋላ በሚኖሩ ትውልዶች ዘንድ፤ በሁለቱ አካባቢዎች ሀገራት መካካል የሚኖረው ግንኙነት፤ በአሉታም ይሁን በአዎንታ እጅግ የገዘፈ ተፅዕኖ ይኖረዋል።
ይኽ ግንኙነት በብልሐት ከተያዘ ሊጠቅም የሚችል፤ እንዲሁም አያያዙ ከተበላሸ ብዙ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ሊያስከትል የሚችል ነው።
ስለዚህም ግንኙነቱ ሊፈጥረው ከሚችለው ዕድልም ይሁን አደጋ አንጻር፤ በነባራዊ እንዲሁም በቀጣይ ዘመናት በቀንዱ እጅግ ትኩረት ከሚፈልጉ ግንኙነቶች መካከል ነው።
የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት የተፅዕኖ እንቅስቃሴና ደኅንነታቸውን ለማስጠበቅ ትኩረት ካደረጉባቸው አካባቢዎች ዓይናቸው በዋናነት ያረፈው፤ ወደ ሌላኛው የቀይባሕር ዳርቻ፤ የአፍሪካ ቀንድ ነው።
ይኽ ባሕርን ተሻግሮ ተፅዕኖን የማስፋት ፍላጎት አሁን የተጀመረ ሳይሆን፤ በየዘመኑ በሁለቱም ዳርቻ የነበሩ ሀገራት ትኩረት ያደረጉበት የዘመናት ስትራቴጂ ነው፡፡
ከጥንት ጀምሮ በቀይ ባሕር ሁለት ጫፍ ያሉ ሀገራት፤ ባሕርን ተሻገርው ሌላኛውን የቀይ ባሕር ወሰን ለመቆጣጠርና ግንኙነት ለመፍጠር የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ነበረ።
ይኸም በአንደኛው የቀይ ባሕር በኩል የሚፈጠር አደጋም ሆነ ዕድል፤ በሌላኛው የቀይባሕር በኩል ተፅዕኖ እንደሚያደርስ ከመገንዘብ የሚመነጭ ነው።
በአክሱም ሥልጣኔ ዘመን፤ የእኛው ዐፄ ካሌብ ቀይ ባሕርን ተሻግሮ ደቡብ ዓረቢያን ለመቆጣጠር ችሎ ነበር።
ዓረቦች የአካባቢው ኃያላን ሆነው በተነሡበት ከ8ኛው እስከ 14ኛው መክዘ በነበረው ጊዜ፤ ቀይ ባሕርን ተሻግረው የአፍሪካን ቀንድ ለመያዝ ሞክረው ነበር።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 245/246
1 month ago
የኢትዮጵያ ዲጂታል ሥራዎች ለሳይበር ደህንነት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የዲጂታል ሥራዎች ለሳይበር ደህንነት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ ነው አሉ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ጉታ፡፡
አቶ ዳንኤል ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን መከላከል አንዱ ቁልፍ ሀገራዊ ተልዕኮ በመሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው፡፡
የሳይበር ጥቃት መከላከል አቅምን ለማሳደግም ከውስጥ ያለውን አቅም ከውጭ ተሞክሮዎች ጋር በማቀናጀት በየዓመቱ የተሻለ ቁመና ለመገንባት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከሳይበር ጥቃት በመከላከል ረገድ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት፡፡
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የሳይበር ጥቃት ሙከራ ተደርጎ እንደነበር ጠቁመው÷ ይሁን እንጂ ሙከራውን በተቀናጀ አቅም ማክሸፍ መቻሉን አብራርተዋል፡፡
በዘርፉ ከቀጣናው ሀገራት የተሻለ አቅምን ለማጎልበት በሰው ሃይል፣ በቴክኖሎጂ እና ዘመኑን በዋጀ እውቀት እንዲሁም ክህሎት በመታገዝ የዳታ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እና ለሳይበር ጥቃት የማይበገር ምሕዳር ለመፍጠር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው ያመላከቱት፡፡
የሚከናወኑ ሥራዎች የሳይበር ደህንነት ሥጋትን ለመከላከልና ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችል ትልቅ ተቋም መገንባት ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለይም ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ ፋይዳ መታወቂያ፣ ዲጂታል የክፍያ ሥርዓቶች፣ ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እና ሌሎች የዲጂታል ሥራዎች ለሳይበር ደህንነት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙ አውስተዋል፡፡
ሳይበር የሰው ልጅ የእርስ በርስ ግንኙነቱ ማደግ የፈጠረው የቴክኖሎጂ ውጤት ነው ፤ የመሰረተ-ልማት፣ የመረጃ፣ የሰዎች እንዲሁም የማሕበረሰብ መስተጋበር የሚገለጽበት ምሕዳር እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የሳይበር ደህንነት መረጃን፣ የመረጃ መሰረተ ልማትን እንዲሁም ሰዎችን አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚፈጥሩ ጥቃቶች መጠበቅን ያለመ ሲሆን÷ በዋናነትም የመረጃ እና መሰረተ ልማትን ምስጢራዊነት፣ ተአማኒነትን እንዲሁም ተደራሽነትን ማረጋገጥ ላይ የሚያተኩር ነው።
በመላኩ ገድፍ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ የዲጂታል ሥራዎች ለሳይበር ደህንነት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ ነው አሉ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ም/ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል ጉታ፡፡
አቶ ዳንኤል ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ የሳይበር ደህንነት ሥጋትን መከላከል አንዱ ቁልፍ ሀገራዊ ተልዕኮ በመሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው፡፡
የሳይበር ጥቃት መከላከል አቅምን ለማሳደግም ከውስጥ ያለውን አቅም ከውጭ ተሞክሮዎች ጋር በማቀናጀት በየዓመቱ የተሻለ ቁመና ለመገንባት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የኢትዮጵያ ቁልፍ መሰረተ ልማቶችን ከሳይበር ጥቃት በመከላከል ረገድ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለጹት፡፡
በበጀት ዓመቱ በተለያዩ ዘርፎች የሳይበር ጥቃት ሙከራ ተደርጎ እንደነበር ጠቁመው÷ ይሁን እንጂ ሙከራውን በተቀናጀ አቅም ማክሸፍ መቻሉን አብራርተዋል፡፡
በዘርፉ ከቀጣናው ሀገራት የተሻለ አቅምን ለማጎልበት በሰው ሃይል፣ በቴክኖሎጂ እና ዘመኑን በዋጀ እውቀት እንዲሁም ክህሎት በመታገዝ የዳታ ሉዓላዊነታችንን ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እና ለሳይበር ጥቃት የማይበገር ምሕዳር ለመፍጠር የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው ያመላከቱት፡፡
የሚከናወኑ ሥራዎች የሳይበር ደህንነት ሥጋትን ለመከላከልና ሊከሰቱ ለሚችሉ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችል ትልቅ ተቋም መገንባት ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በተለይም ኢትዮጵያ እያከናወነቻቸው የሚገኙ ፋይዳ መታወቂያ፣ ዲጂታል የክፍያ ሥርዓቶች፣ ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እና ሌሎች የዲጂታል ሥራዎች ለሳይበር ደህንነት መረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እያበረከቱ እንደሚገኙ አውስተዋል፡፡
ሳይበር የሰው ልጅ የእርስ በርስ ግንኙነቱ ማደግ የፈጠረው የቴክኖሎጂ ውጤት ነው ፤ የመሰረተ-ልማት፣ የመረጃ፣ የሰዎች እንዲሁም የማሕበረሰብ መስተጋበር የሚገለጽበት ምሕዳር እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የሳይበር ደህንነት መረጃን፣ የመረጃ መሰረተ ልማትን እንዲሁም ሰዎችን አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚፈጥሩ ጥቃቶች መጠበቅን ያለመ ሲሆን÷ በዋናነትም የመረጃ እና መሰረተ ልማትን ምስጢራዊነት፣ ተአማኒነትን እንዲሁም ተደራሽነትን ማረጋገጥ ላይ የሚያተኩር ነው።
በመላኩ ገድፍ
1 month ago
ከወሳኙ ፍልሚያ በፊት የግብፁ አሰልጣኝ ለኢራን አጋርነታቸውን ገለጹ
#ethiopia | ከኢራን ብሔራዊ ቡድን ጋር ከሚያደርጉት ወሳኝ የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጠቃለያ ጨዋታ በፊት የግብጹ ዋና አሰልጣኝ ሆሳም ሀሰን ለተጋጣሚያቸው ያልተጠበቀ አጋርነትና አክብሮት ሰጡ።
አሰልጣኙ የፊፋን “ፍትሃዊ ጨዋታ” መርሆዎችን በመጥቀስ በውድድሩ ላይ የመሳተፍ መብት ያላቸው ሁሉም ቡድኖች እኩልና ፍትሃዊ መስተንግዶ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በሴያትል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
ይህ አስተያየት የውድድሩ ተባባሪ አስተናጋጅ የሆነችው አሜሪካ በኢራን ቡድን ላይ በጣለችው ጥብቅ የጉዞና የጊዜ ሰሌዳ ገደብ ምክንያት በተፈጠረው ቅሬታ ላይ የተሰነዘረ ሲሆን ለተጋጣሚ ቡድን የተሰጠ ስፖርታዊ ድጋፍም ጭምር ነው።
የኢራን ብሔራዊ ቡድን በአሜሪካ ማዕቀብ ምክንያት የልምምድ ካምፑን በሜክሲኮ ለማድረግ የተገደደ ሲሆን ጨዋታው ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ብቻ ወደ አሜሪካ እንዲገባና ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ወዲያውኑ ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ መደረጉ በቡድኑ የአካል ብቃትና ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን የኢራኑ አሰልጣኝ አሚር ጋሌኖይ ገልጸዋል። አሜሪካ ለዚህ ጨዋታ ገደቡን በትንሹ በማላላት ቡድኑ ሁለት ቀን ቀድሞ ሴያትል እንዲገባ ብታደርግም፣ አሰልጣኝ ጋሌኖይ ግን ያሉትን የፖለቲካና የጉዞ ተግዳሮቶች በሙሉ ወደ ጎን በመተው ሜዳ ላይ ውጤት ለማምጣት እንደሚጫወቱ አስታውቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ከኢራን ብሔራዊ ቡድን ጋር ከሚያደርጉት ወሳኝ የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጠቃለያ ጨዋታ በፊት የግብጹ ዋና አሰልጣኝ ሆሳም ሀሰን ለተጋጣሚያቸው ያልተጠበቀ አጋርነትና አክብሮት ሰጡ።
አሰልጣኙ የፊፋን “ፍትሃዊ ጨዋታ” መርሆዎችን በመጥቀስ በውድድሩ ላይ የመሳተፍ መብት ያላቸው ሁሉም ቡድኖች እኩልና ፍትሃዊ መስተንግዶ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በሴያትል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
ይህ አስተያየት የውድድሩ ተባባሪ አስተናጋጅ የሆነችው አሜሪካ በኢራን ቡድን ላይ በጣለችው ጥብቅ የጉዞና የጊዜ ሰሌዳ ገደብ ምክንያት በተፈጠረው ቅሬታ ላይ የተሰነዘረ ሲሆን ለተጋጣሚ ቡድን የተሰጠ ስፖርታዊ ድጋፍም ጭምር ነው።
የኢራን ብሔራዊ ቡድን በአሜሪካ ማዕቀብ ምክንያት የልምምድ ካምፑን በሜክሲኮ ለማድረግ የተገደደ ሲሆን ጨዋታው ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ብቻ ወደ አሜሪካ እንዲገባና ጨዋታው እንደተጠናቀቀ ወዲያውኑ ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ መደረጉ በቡድኑ የአካል ብቃትና ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን የኢራኑ አሰልጣኝ አሚር ጋሌኖይ ገልጸዋል። አሜሪካ ለዚህ ጨዋታ ገደቡን በትንሹ በማላላት ቡድኑ ሁለት ቀን ቀድሞ ሴያትል እንዲገባ ብታደርግም፣ አሰልጣኝ ጋሌኖይ ግን ያሉትን የፖለቲካና የጉዞ ተግዳሮቶች በሙሉ ወደ ጎን በመተው ሜዳ ላይ ውጤት ለማምጣት እንደሚጫወቱ አስታውቀዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
የፌዴራል መንግስት በዋናነት በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ በ2019 የሚኖረውን የበጀት ጉድለት ለመሙላት አስቤያለሁ ብሏል፡፡
ትላልቆቹን ጨምሮ የገንዘብ ተቋማት በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ ለመንግስት የሚያበድሩ ከሆነ የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ እጥረት ሊገጥመው እንደሚችል ባለሞያዎች እየተናገሩ ነው።
ለካፒታል የተመደበው በጀት ከቀዳሚው ዓመት ብዙም ዕድገት አለማሳየቱም የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ተጠቅሷል።
የ2019 የፌዴራል መንግስት አጠቃላይ በጀት 2 ነጥብ 34 ትሪሊየን ብር እንዲሆን ረቂቅ ተዘጋጅቷል።
ከዚህ በጀት 1 ነጥብ 8 ትሪሊየን ብሩ ከሀገር ውስጥ በሚሰበሰብ ገቢ እንዲሸፈን መታሰቡን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ በረቂቁ ዙሪያ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ማብራሪያ ሲሰጡ ተናግረዋል።
ቀሪውን 522 ቢሊየን ብር ደግሞ በዋናነት በመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድ ለመሙላት እንደታሰበ ጠቅሰዋል።
ጉድለቱን ለመሙላት ከብሄራዊ ባንክ የሚወሰድ ብድር ግን አይኖርም ተብሏል።
የምጣኔ ሃብት ባለሙያ አቶ ዋስይሁን በላይ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድም የግሉ ዘርፍ በቂ ብድር እንዳያገኝ ሊያደርግ እንደሚችል ይናገራሉ።
በባንኮች የብድር ጣሪያ ላይ ከተቀመጠው ገደብ እና በየጊዜው ከሚካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ጋር ሲደመር አሰራሩ የግሉ ዘርፍ ብድር የማግኘት ዕድል ጫና አለው ብለዋል።
በሌላ በኩል ለአመቱ ከተያዘው በጀት 568 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ ለካፒታል ወጪ የተመደበ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በ2018 ለካፒታል ወጪ ተመድቦ የነበረው 415 ቢሊዮን ብር ነው ። ልዩነቱ ሲታይ ለካፒታል ወጪ የተመደበው ገንዘብ ብዙም ዕድገት አለማሳየቱን መረዳት ይቻላል።
ሁኔታው መንግስት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን መጀመር ላይ ትንሽ ያዝ ማድረግ መፈለጉን ያሳያል የሚሉት አቶ ዋሲሁን ትኩረቱ የነበሩትን መጨረስ ላይ አድርጓል ሲሉም አክለዋል፡፡
መንግስት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ቆጠብ ሲል ሊፈጠር የሚችል የስራ ዕድልም አብሮ ይቀንሳል የሚሉት ፤የምጣኔ ሃብት ባለሞያው አቶ ዋሲሁን አማራጩ የግሉ ዘርፍ ማሳተፍ እንደሆነ ተናግረዋል።
ክልሎች ከፌዴራል መንግስት ያገኙትን በጀት ለካፒታል ወጪ ማዞር ከቻሉ ግን ገንዘቡ ትንሽ እንዳልሆነ አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል።
ዋናው ጉዳይ የተመደበው የካፒታል በጀት ስራ መፍጠር እና የወጪ ንግድን ለሚያሳድጉ ዘርፎች መዋሉ ነው ብለዋል።
ለካፒታል ወጪ ከፍተኛ ገንዘብ ቢመደበም የሚሰበሰበው ገቢ ካላደገ የበጀት ጉድለቱ ከፍ ከማለት ውጪ ሊተገገበር እንደማይችል የምጣኔ ሃብት ባለሞያው አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል።
Sheger Fm
ትላልቆቹን ጨምሮ የገንዘብ ተቋማት በግምጃ ቤት ሰነድ ሽያጭ ለመንግስት የሚያበድሩ ከሆነ የግሉ ዘርፍ የፋይናንስ እጥረት ሊገጥመው እንደሚችል ባለሞያዎች እየተናገሩ ነው።
ለካፒታል የተመደበው በጀት ከቀዳሚው ዓመት ብዙም ዕድገት አለማሳየቱም የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ተጠቅሷል።
የ2019 የፌዴራል መንግስት አጠቃላይ በጀት 2 ነጥብ 34 ትሪሊየን ብር እንዲሆን ረቂቅ ተዘጋጅቷል።
ከዚህ በጀት 1 ነጥብ 8 ትሪሊየን ብሩ ከሀገር ውስጥ በሚሰበሰብ ገቢ እንዲሸፈን መታሰቡን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ በረቂቁ ዙሪያ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ማብራሪያ ሲሰጡ ተናግረዋል።
ቀሪውን 522 ቢሊየን ብር ደግሞ በዋናነት በመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድ ለመሙላት እንደታሰበ ጠቅሰዋል።
ጉድለቱን ለመሙላት ከብሄራዊ ባንክ የሚወሰድ ብድር ግን አይኖርም ተብሏል።
የምጣኔ ሃብት ባለሙያ አቶ ዋስይሁን በላይ የመንግስት የግምጃ ቤት ሰነድም የግሉ ዘርፍ በቂ ብድር እንዳያገኝ ሊያደርግ እንደሚችል ይናገራሉ።
በባንኮች የብድር ጣሪያ ላይ ከተቀመጠው ገደብ እና በየጊዜው ከሚካሄደው የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ጋር ሲደመር አሰራሩ የግሉ ዘርፍ ብድር የማግኘት ዕድል ጫና አለው ብለዋል።
በሌላ በኩል ለአመቱ ከተያዘው በጀት 568 ነጥብ 2 ቢሊየን ብሩ ለካፒታል ወጪ የተመደበ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በ2018 ለካፒታል ወጪ ተመድቦ የነበረው 415 ቢሊዮን ብር ነው ። ልዩነቱ ሲታይ ለካፒታል ወጪ የተመደበው ገንዘብ ብዙም ዕድገት አለማሳየቱን መረዳት ይቻላል።
ሁኔታው መንግስት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን መጀመር ላይ ትንሽ ያዝ ማድረግ መፈለጉን ያሳያል የሚሉት አቶ ዋሲሁን ትኩረቱ የነበሩትን መጨረስ ላይ አድርጓል ሲሉም አክለዋል፡፡
መንግስት አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ቆጠብ ሲል ሊፈጠር የሚችል የስራ ዕድልም አብሮ ይቀንሳል የሚሉት ፤የምጣኔ ሃብት ባለሞያው አቶ ዋሲሁን አማራጩ የግሉ ዘርፍ ማሳተፍ እንደሆነ ተናግረዋል።
ክልሎች ከፌዴራል መንግስት ያገኙትን በጀት ለካፒታል ወጪ ማዞር ከቻሉ ግን ገንዘቡ ትንሽ እንዳልሆነ አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል።
ዋናው ጉዳይ የተመደበው የካፒታል በጀት ስራ መፍጠር እና የወጪ ንግድን ለሚያሳድጉ ዘርፎች መዋሉ ነው ብለዋል።
ለካፒታል ወጪ ከፍተኛ ገንዘብ ቢመደበም የሚሰበሰበው ገቢ ካላደገ የበጀት ጉድለቱ ከፍ ከማለት ውጪ ሊተገገበር እንደማይችል የምጣኔ ሃብት ባለሞያው አቶ ዋሲሁን ተናግረዋል።
Sheger Fm
Sponsored by
Surafel
1 month ago
አገር አቀፍ ፈተና እና የሴቶች #የወርአበባ ንፅህና መጠበቂያ
በወር አበባ ምክንያት #ሴት ተማሪ መሸማቀቅ የለባትም!
#ethiopia | እንደሚታወቀው የሰኔ ወር የ 6ኛ; የ 8 ኛ እና የ 12 ኛ ክፍሎች የአገር አቀፍ እና ክልላዊ ፈተናዎች የሚሰጥበት ወቅት ነው።
ከሰኔ ወርም ቀደም ተብሎ የመንግስትና የግል ት/ቤቶች እና የትምህርት ሚኒስቴር; ቢሮዎችና ፅ/ቤቶች ተማሪዎች በጥሩ ውጤት ፈተናዎቹን እንዲያልፉ በትጋት ተማሪዎቻቸውን ያዘጋጃሉ።
የፈተና ቁሳቁሶች; ጥያቄዎች; የመፈተኛ ት/ቤቶች; ፈታኝ መምህራን እና ሌሎችንም ቀድመው ለማዘጋጀት የሚደረገው ርብርብ የሚደነቅ ነው። ለወላጆችም/ለቤተሰቦችም ልጆቻችንን ለፈተናዎቹ በአግባቡ እንድናዘጋጅ ተደጋጋሚ መልእክቶችና ማስጠንቀቂያዎች ይላኩልናል።
በተለይ ፈተናዎቹ ቀናቸው እየቀረበ ሲመጣ ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ ይዘው መምጣት ያለባቸው እና ይዘው ለመምጣት የሚከለከሉ ቁሳቁሶች ለተማሪዎቹም ተደጋግሞ ይነገራቸዋል ለእኛም ለወላጆች/ቤተሰቦች ማስጠንቀቂያ ይላክልናል።
ተማሪዎቹ በፈተና ቦታው ይዘው መምጣት የሚፈቀድላቸው :-
1)እርሳስ ; ላጲስ; መቅረጫ
2)የት/ቤት መታወቂያ እና admission card #ብቻ ነው።
አንድ ትልቅ ነገር ግን ተረስቷል #ሞዴስ !
እንደ አገር ትልቅ ዝግጅት የምናደርግለት አገር አቀፍ ፈተና ላይ ሴት ተማሪዎች በፈተና ወቅት #የወር አበባ ላይ ከሆኑ የንፅህና መጠበቂያ #ሞዴስ እንደሚያስፈልጋቸው መዘንጋት ማለት የፈተናው ዝግጅት; ሂደት እና አፈፃፀም #በስርአተ -ፆታ እይታ እንዳልተቃኘ ማሳያ ነው።
እንኳን ፈተና ተጨምሮበት ይቅርና ወር አበባ ሴት ታዳጊዎች ላይ ከባድ የአካል #ህመም ; #የሆርሞን መዛባት እና #የስነልቦና ጫና ያሳድርባቸዋል።
ስለዚህ የወር አበባ + ፈተና የትምህርት ዘርፉ እና ት/ቤቶች ለሴት ተማሪዎች የተለየ ትኩረት እንዲሰጡ ግድ የሚላቸው ጉዳይ ነው።
ፈተና እየተፈተኑ ድንገት የወር አበባቸው የሚመጣባቸው እና የወር አበባ የሚበዛባቸው /heavy flow period / ሴት ተማሪዎች ቶሎ #ምዴስ መቀየር ወይም መጠቀም ሰላለባቸው በፈተና ወቅት ሞዴስ ይዘው እንዲገቡ ባልተፈቀደበት ሁኔታ ሴት ተማሪዎቹ ከአሁን አሁን ልብሴ ተበላሸ ብለው #ሲሳቀቁ ለፈተናው የሚሰጡት #ትኩረት ይጎዳል ።በዚህም የተነሳ ውጤታቸው ላይ #አሉታዊ ተፅእኖ ያመጣል።
ታዲያ የፈተናው ጣቢያዎች ለሴት ተማሪዎች በመፈተኛ ክፍሎች ውስጥ የድንገተኛ ግዜ #ሞዴስ /emergency sanitary pad / ሊያስቀምጡ ይገባል። አለበለዚያ ፈተናው ለሴት ተማሪዎች #ኢፍትሀዊ ይሆናል።
አንዲትም #ሴት ተማሪ #በተፈጥሮ ምክንያት #ከወንድ ተማሪዎች ወደኋላ መቅረት የለባትም!
የህግ ባለሙያ ሜሮን አራጋው
በወር አበባ ምክንያት #ሴት ተማሪ መሸማቀቅ የለባትም!
#ethiopia | እንደሚታወቀው የሰኔ ወር የ 6ኛ; የ 8 ኛ እና የ 12 ኛ ክፍሎች የአገር አቀፍ እና ክልላዊ ፈተናዎች የሚሰጥበት ወቅት ነው።
ከሰኔ ወርም ቀደም ተብሎ የመንግስትና የግል ት/ቤቶች እና የትምህርት ሚኒስቴር; ቢሮዎችና ፅ/ቤቶች ተማሪዎች በጥሩ ውጤት ፈተናዎቹን እንዲያልፉ በትጋት ተማሪዎቻቸውን ያዘጋጃሉ።
የፈተና ቁሳቁሶች; ጥያቄዎች; የመፈተኛ ት/ቤቶች; ፈታኝ መምህራን እና ሌሎችንም ቀድመው ለማዘጋጀት የሚደረገው ርብርብ የሚደነቅ ነው። ለወላጆችም/ለቤተሰቦችም ልጆቻችንን ለፈተናዎቹ በአግባቡ እንድናዘጋጅ ተደጋጋሚ መልእክቶችና ማስጠንቀቂያዎች ይላኩልናል።
በተለይ ፈተናዎቹ ቀናቸው እየቀረበ ሲመጣ ተማሪዎች ለፈተና ሲመጡ ይዘው መምጣት ያለባቸው እና ይዘው ለመምጣት የሚከለከሉ ቁሳቁሶች ለተማሪዎቹም ተደጋግሞ ይነገራቸዋል ለእኛም ለወላጆች/ቤተሰቦች ማስጠንቀቂያ ይላክልናል።
ተማሪዎቹ በፈተና ቦታው ይዘው መምጣት የሚፈቀድላቸው :-
1)እርሳስ ; ላጲስ; መቅረጫ
2)የት/ቤት መታወቂያ እና admission card #ብቻ ነው።
አንድ ትልቅ ነገር ግን ተረስቷል #ሞዴስ !
እንደ አገር ትልቅ ዝግጅት የምናደርግለት አገር አቀፍ ፈተና ላይ ሴት ተማሪዎች በፈተና ወቅት #የወር አበባ ላይ ከሆኑ የንፅህና መጠበቂያ #ሞዴስ እንደሚያስፈልጋቸው መዘንጋት ማለት የፈተናው ዝግጅት; ሂደት እና አፈፃፀም #በስርአተ -ፆታ እይታ እንዳልተቃኘ ማሳያ ነው።
እንኳን ፈተና ተጨምሮበት ይቅርና ወር አበባ ሴት ታዳጊዎች ላይ ከባድ የአካል #ህመም ; #የሆርሞን መዛባት እና #የስነልቦና ጫና ያሳድርባቸዋል።
ስለዚህ የወር አበባ + ፈተና የትምህርት ዘርፉ እና ት/ቤቶች ለሴት ተማሪዎች የተለየ ትኩረት እንዲሰጡ ግድ የሚላቸው ጉዳይ ነው።
ፈተና እየተፈተኑ ድንገት የወር አበባቸው የሚመጣባቸው እና የወር አበባ የሚበዛባቸው /heavy flow period / ሴት ተማሪዎች ቶሎ #ምዴስ መቀየር ወይም መጠቀም ሰላለባቸው በፈተና ወቅት ሞዴስ ይዘው እንዲገቡ ባልተፈቀደበት ሁኔታ ሴት ተማሪዎቹ ከአሁን አሁን ልብሴ ተበላሸ ብለው #ሲሳቀቁ ለፈተናው የሚሰጡት #ትኩረት ይጎዳል ።በዚህም የተነሳ ውጤታቸው ላይ #አሉታዊ ተፅእኖ ያመጣል።
ታዲያ የፈተናው ጣቢያዎች ለሴት ተማሪዎች በመፈተኛ ክፍሎች ውስጥ የድንገተኛ ግዜ #ሞዴስ /emergency sanitary pad / ሊያስቀምጡ ይገባል። አለበለዚያ ፈተናው ለሴት ተማሪዎች #ኢፍትሀዊ ይሆናል።
አንዲትም #ሴት ተማሪ #በተፈጥሮ ምክንያት #ከወንድ ተማሪዎች ወደኋላ መቅረት የለባትም!
የህግ ባለሙያ ሜሮን አራጋው
1 month ago
በሃሪ ኬን ላይ ‘እርግማን’ አድርጌ ነበር ያለው ጋናዊው ጠንቋይ እርግማኑን ሊያነሳ መሆኑን ገለጸ
#fastmereja I የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከጋና ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ከተለያየ በኋላ፣ በሃሪ ኬን ላይ "እርግማን" አድርጌ ነበር ያለው ጋናዊው ጠንቋይ ናና ክዋኩ ቦንሳም አሁን በእንግሊዝ ካፒቴን ላይ የጫነውን ድግምት ሊያነሳ መሆኑን አስታውቋል። ጠንቋዩ ይህንን የገለጸው ሃሪ ኬን በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በቀላሉ ሊያስቆጥረው የሚችለውን ወሳኝ የግብ ዕድል ሳያጠቀምበት መቅረቱን ተከትሎ በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) ላይ ነው።
ናና ክዋኩ ቦንሳም በቪዲዮው ላይ “እኔ በዓለም ላይ ካሉ መንፈሳውያን ሁሉ እጅግ በጣም ኃያል ነኝ፤ አሁን ግን ሃሪ ኬን በቀጣይ ጨዋታው ግብ ማስቆጠር እንዲችል መልቀቂያ እሰጠዋለሁ” ብሏል። ጠንቋዩ ከጨዋታው በፊት ለዴይሊ ስታር ጋዜጣ በሰጠው አስተያየት፣ ሃሪ ኬን በጋና ላይ ጉዳት እንዳያደርስና ለአገሩ እንዲጠቅም ብቻ የተወሰነ ተጽዕኖ ለማድረግ እየሰራ እንደነበር መናገሩ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ታዋቂው ኢሉዥኒስት ኡሪ ጌለር የጠንቋዩን አሉታዊ ጉልበት ለማክሸፍ የራሱን ኃይል እንደሚጠቀም አስታውቆ ነበር።
በሌላ በኩል፣ የእንግሊዝ ቡድን ከጋና ጋር ያደረገው ጨዋታ ያሳየው ደካማ እንቅስቃሴ በስፖርት ተንታኞች ዘንድ ከፍተኛ ትችት እያስተናገደ ይገኛል። የቀድሞው ተጫዋች ሚካ ሪቻርድስ የእንግሊዝን አጠቃላይ አሰላለፍ እና አጨዋወት "በቀላሉ ሊነበብ የሚችል" ሲል የገለጠው ሲሆን፣ አፈጻጸሙን የቀድሞውን አሰልጣኝ ጋሬዝ ሳውዝጌትን አሰልቺ የአጨዋወት ስልት የሚያስታውስ ነው ሲል ነቅፎታል። ይሁን እንጂ የቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች ጁድ ቤሊንግሃም ውጤቱ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በአዎንታዊ ስሜት መቀጠል እንደሚያስፈልግ ለሚዲያዎች በሰጠው አስተያየት አሳስቧል።
#fastmereja I የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከጋና ጋር ያለ ምንም ግብ አቻ ከተለያየ በኋላ፣ በሃሪ ኬን ላይ "እርግማን" አድርጌ ነበር ያለው ጋናዊው ጠንቋይ ናና ክዋኩ ቦንሳም አሁን በእንግሊዝ ካፒቴን ላይ የጫነውን ድግምት ሊያነሳ መሆኑን አስታውቋል። ጠንቋዩ ይህንን የገለጸው ሃሪ ኬን በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በቀላሉ ሊያስቆጥረው የሚችለውን ወሳኝ የግብ ዕድል ሳያጠቀምበት መቅረቱን ተከትሎ በፌስቡክ ገጹ ባሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) ላይ ነው።
ናና ክዋኩ ቦንሳም በቪዲዮው ላይ “እኔ በዓለም ላይ ካሉ መንፈሳውያን ሁሉ እጅግ በጣም ኃያል ነኝ፤ አሁን ግን ሃሪ ኬን በቀጣይ ጨዋታው ግብ ማስቆጠር እንዲችል መልቀቂያ እሰጠዋለሁ” ብሏል። ጠንቋዩ ከጨዋታው በፊት ለዴይሊ ስታር ጋዜጣ በሰጠው አስተያየት፣ ሃሪ ኬን በጋና ላይ ጉዳት እንዳያደርስና ለአገሩ እንዲጠቅም ብቻ የተወሰነ ተጽዕኖ ለማድረግ እየሰራ እንደነበር መናገሩ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ታዋቂው ኢሉዥኒስት ኡሪ ጌለር የጠንቋዩን አሉታዊ ጉልበት ለማክሸፍ የራሱን ኃይል እንደሚጠቀም አስታውቆ ነበር።
በሌላ በኩል፣ የእንግሊዝ ቡድን ከጋና ጋር ያደረገው ጨዋታ ያሳየው ደካማ እንቅስቃሴ በስፖርት ተንታኞች ዘንድ ከፍተኛ ትችት እያስተናገደ ይገኛል። የቀድሞው ተጫዋች ሚካ ሪቻርድስ የእንግሊዝን አጠቃላይ አሰላለፍ እና አጨዋወት "በቀላሉ ሊነበብ የሚችል" ሲል የገለጠው ሲሆን፣ አፈጻጸሙን የቀድሞውን አሰልጣኝ ጋሬዝ ሳውዝጌትን አሰልቺ የአጨዋወት ስልት የሚያስታውስ ነው ሲል ነቅፎታል። ይሁን እንጂ የቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች ጁድ ቤሊንግሃም ውጤቱ ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም አሁንም ቢሆን በአዎንታዊ ስሜት መቀጠል እንደሚያስፈልግ ለሚዲያዎች በሰጠው አስተያየት አሳስቧል።
2 months ago
መሶብ ለአገልጋይነታችን፡ የዲጂታል ትጋትና የሕዝብ አደራ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ቴክኖሎጂ የአንድን ሀገር የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት የሚያጠናክርና የዜጎችን ሕይወት በብዙ መንገድ የሚቀይር እውነተኛ የለውጥ ሞተር ነው።
በተለይም የመንግሥት አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ ለዜጎች የሚሰጠውን ክብር፣ የጊዜና የገንዘብ ትርፍ ስንመለከት እንዲሁም በተቋማት መካከል የሚፈጥረውን ቅንጅት ስናስተውል ሀገራችን በለውጥና በዕድገት ጎዳና ላይ መሆኗን በግልጽ ያሳያል።
ይሁንናይህ አስደማሚ ጅማሮና በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡት ድሎች የዜጎችን እርካታ ጫፍ ላይ አድርሰዋል ማለት አይደለም ገና ብዙ የሚቀሩና ትኩረት የሚሹ የቤት ሥራዎች እንዳሉብን መዘንጋት የለብንም።
በባህላችን «መሶብ» የጥጋብ፣ የአንድነት መገለጫ ነው።በዚህ እሳቤ የተገነባው የ«መሶብ» መተግበሪያም የሀገርን በረከትና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ የቴክኖሎጂ ውጤት ነው።
መሶቡ የበረከት ምንጭ እንዲሆንና አገልግሎቱ ሙሉዕነት እንዲኖረው ከተፈለገ፣ በውስጡ የሚቀመጠው «እንጀራ» ማለትም የአሠራር ሥርዓቱና አስፈጻሚው አገልጋይ—ከሌብነት፣ ከሙስናና ከእጅ መንሻ የጠራ መሆን አለበት።
እጅግ ዘመናዊና የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በየተቋማቱ ቢዘረጋም፣ በአገልጋዩ ዘንድ ያለው የቆየ ልማድ፣ የሌብነት አስተሳሰብና የአገልግሎት መስተጓጎል ካልተወገደ የቴክኖሎጂው ፋይዳ ለዜጎች ትርጉም አልባ ሆኖ ይቀራል።
በመሆኑም በመሶብ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩትን እጅ መንሻዎችና ሕገ-ወጥ አሠራሮች ሙሉ በሙሉ ማስወገድ የነገ የማይባል ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
ቴክኖሎጂ ጊዜንና ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ዜጎች በቢሮክራሲ ብስጭትና በጭንቀት የሚሸከሙትን አሉታዊ ኃይል አስወግዶ ደስተኛ ማኅበረሰብ የመፍጠር ትልቅ አቅም አለው።
ይህንን አቅም ወደ መሬት ማውረድ የሚቻለው ደግሞ እያንዳንዱ አገልጋይና የመንግሥት ተቋም የኃላፊነት ስሜቱን በተግባር ሲያሳይ ነው። የዚህ ሁሉ ጥረትና ስኬት ማዕከል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።
ባለፈው ምርጫ ሕዝባችን ከሌሊት እስከ ሌሊት በሰላማዊ መንገድ ተሰልፎ ስለ ሀገሩ ያለውን ፍቅር፣ ለተቋማዊ ዕድገትና ለመበልጸግ ያለውን ጉጉት በተግባር አሳይቷል።
ይህንን ታላቅ እምነትና አደራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መወጣት ግድ ይላል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በግልጽ እንዳሳሰቡት "የኢትዮጵያ ሕዝብ ስላከበረን አብዝተን ልናከብረው፣ ስላከበረን አብዝተን ልናገለግለው፣ ባከበረን ልክ ታምነን ልንገኝ ይገባል።"
«ያበደረ መልሶ ያገኛል፣ የዘራ ያጭዳል» እንደሚባለው የሕዝቡን ክብርና አመኔታ መመለስ የሚቻለው በታማኝነትና በቅንነት በማገልገል ብቻ ነው።
እስካሁን የተመዘገበው ስኬት ከዜጎችን ሰፊ ፍላጎት አንድ በመቶ (1%) ያህል ብቻ በመሆኑ፣ በቀሪው ሰፊ መንገድ ላይ በፍጥነት ለመራመድ በተሻለ ቁመና መገኘት፣ ራስን ከብልሹ አሠራር ማጥራትና በበለጠ ትጋት መረባረብ ያስፈልጋል።
መላው የሥራ ኃላፊዎችና በየተቋማቱ የምትገኙ አገልጋዮች በመደመርና በአንድነት በመቆም፣ የዜጎችን እሮሮ ማክሰምና የሀገራችንን ብልጽግና በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ይጠበቅባችኋል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #mesob #ethiopia #መሶብ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ቴክኖሎጂ የአንድን ሀገር የኢኮኖሚ መሠረተ ልማት የሚያጠናክርና የዜጎችን ሕይወት በብዙ መንገድ የሚቀይር እውነተኛ የለውጥ ሞተር ነው።
በተለይም የመንግሥት አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ ለዜጎች የሚሰጠውን ክብር፣ የጊዜና የገንዘብ ትርፍ ስንመለከት እንዲሁም በተቋማት መካከል የሚፈጥረውን ቅንጅት ስናስተውል ሀገራችን በለውጥና በዕድገት ጎዳና ላይ መሆኗን በግልጽ ያሳያል።
ይሁንናይህ አስደማሚ ጅማሮና በዲጂታል ዘርፉ የተመዘገቡት ድሎች የዜጎችን እርካታ ጫፍ ላይ አድርሰዋል ማለት አይደለም ገና ብዙ የሚቀሩና ትኩረት የሚሹ የቤት ሥራዎች እንዳሉብን መዘንጋት የለብንም።
በባህላችን «መሶብ» የጥጋብ፣ የአንድነት መገለጫ ነው።በዚህ እሳቤ የተገነባው የ«መሶብ» መተግበሪያም የሀገርን በረከትና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለሕዝብ ለማቅረብ ያለመ የቴክኖሎጂ ውጤት ነው።
መሶቡ የበረከት ምንጭ እንዲሆንና አገልግሎቱ ሙሉዕነት እንዲኖረው ከተፈለገ፣ በውስጡ የሚቀመጠው «እንጀራ» ማለትም የአሠራር ሥርዓቱና አስፈጻሚው አገልጋይ—ከሌብነት፣ ከሙስናና ከእጅ መንሻ የጠራ መሆን አለበት።
እጅግ ዘመናዊና የተራቀቀ ቴክኖሎጂ በየተቋማቱ ቢዘረጋም፣ በአገልጋዩ ዘንድ ያለው የቆየ ልማድ፣ የሌብነት አስተሳሰብና የአገልግሎት መስተጓጎል ካልተወገደ የቴክኖሎጂው ፋይዳ ለዜጎች ትርጉም አልባ ሆኖ ይቀራል።
በመሆኑም በመሶብ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚታዩትን እጅ መንሻዎችና ሕገ-ወጥ አሠራሮች ሙሉ በሙሉ ማስወገድ የነገ የማይባል ቀዳሚ ተግባራችን ነው።
ቴክኖሎጂ ጊዜንና ገንዘብን ከመቆጠብ ባለፈ፣ ዜጎች በቢሮክራሲ ብስጭትና በጭንቀት የሚሸከሙትን አሉታዊ ኃይል አስወግዶ ደስተኛ ማኅበረሰብ የመፍጠር ትልቅ አቅም አለው።
ይህንን አቅም ወደ መሬት ማውረድ የሚቻለው ደግሞ እያንዳንዱ አገልጋይና የመንግሥት ተቋም የኃላፊነት ስሜቱን በተግባር ሲያሳይ ነው። የዚህ ሁሉ ጥረትና ስኬት ማዕከል ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው።
ባለፈው ምርጫ ሕዝባችን ከሌሊት እስከ ሌሊት በሰላማዊ መንገድ ተሰልፎ ስለ ሀገሩ ያለውን ፍቅር፣ ለተቋማዊ ዕድገትና ለመበልጸግ ያለውን ጉጉት በተግባር አሳይቷል።
ይህንን ታላቅ እምነትና አደራ በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መወጣት ግድ ይላል። ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በግልጽ እንዳሳሰቡት "የኢትዮጵያ ሕዝብ ስላከበረን አብዝተን ልናከብረው፣ ስላከበረን አብዝተን ልናገለግለው፣ ባከበረን ልክ ታምነን ልንገኝ ይገባል።"
«ያበደረ መልሶ ያገኛል፣ የዘራ ያጭዳል» እንደሚባለው የሕዝቡን ክብርና አመኔታ መመለስ የሚቻለው በታማኝነትና በቅንነት በማገልገል ብቻ ነው።
እስካሁን የተመዘገበው ስኬት ከዜጎችን ሰፊ ፍላጎት አንድ በመቶ (1%) ያህል ብቻ በመሆኑ፣ በቀሪው ሰፊ መንገድ ላይ በፍጥነት ለመራመድ በተሻለ ቁመና መገኘት፣ ራስን ከብልሹ አሠራር ማጥራትና በበለጠ ትጋት መረባረብ ያስፈልጋል።
መላው የሥራ ኃላፊዎችና በየተቋማቱ የምትገኙ አገልጋዮች በመደመርና በአንድነት በመቆም፣ የዜጎችን እሮሮ ማክሰምና የሀገራችንን ብልጽግና በጽኑ መሠረት ላይ መገንባት ይጠበቅባችኋል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #mesob #ethiopia #መሶብ
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አስመጪዎች በጉምሩክ ሲስተም በመላሸት የተነሳ ከፍተኛ ኪሳራና መጉላላት እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የኤሌክትሮኒክስ አንድ መስኮት አገልግሎት ወይንም ኢኤስደብሊው ሲስተሙ ከተበላሸ አንድ ወር አስቆጥሯል፡፡ ኮሚሽኑ ግንቦት 20 ቀን 2018 በፃፈው ደብዳቤ በሲስተሙ ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ችግሩ እስከሚፈታ ለአስመጪዎች በማንዋል አገልግሎት እንዲሰጥ የሚል መመሪያ አስተላልፏል፡፡ አስመጪዎች እንደሚናገሩት ይህ መመሪያ ንብረታቸውን በወቅቱ አውጥተው ለመስራት የሚያስችል ባለመሆኑ ለከፍተኛ እንግልትና ኪሳራ እየተዳረጉ ነው፡፡
አስመጪዎቹ ሲናገሩ ‹‹ይህ አሰራር ላኪዎችን ብቻ በመጥቀም አስመጪዎችን ሆነ ብሎ ለከፍተኛ መጉላላት አሳልፎ የሰጠ ይመስላል›› ያሉ ሲሆን ሲስተሙ ባለመስራቱ በጉምሩክ መስሪያ ቤቶችና በባንኮች ለረጅም ሰአታት ወረፋ በመጠበቅ ለድካምና እንግልት እንደዳረጋቸው አስረድተዋል፡፡ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የገዟቸውና ወደአገር ውስጥ ያስገቧቸው እቃዎች በወቅቱ ባለመውጣታቸው በየወደቡና በየመጋዘኑ እየተበላሹና ለጉዳት እየተዳረጉ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ላኪዎች በማንዋል እንዲስተናገዱ እየተደረገ ባለበት ወቅት አስመጪዎችን በተመሳሳይ መንገድ ለምን ማስተናገድ አልተቻለም? የሚል ጥያቄ ያነሳሉ፡፡
ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ይህ በጉምሩክና በባንኮች መካከል ያለው የአሰራር መጓተትና የአማራጭ መፍትሄ እጥረት በአስቸኳይ ካልተቀረፈ በአገሪቱ ውስጥ የገበያ አቅርቦትና የዋጋ ንረት ላይ የራሱን አሉታዊ ጥላ ሊያሳርፍ ይችላል፡፡
አስመጪዎቹ ሲናገሩ ‹‹ይህ አሰራር ላኪዎችን ብቻ በመጥቀም አስመጪዎችን ሆነ ብሎ ለከፍተኛ መጉላላት አሳልፎ የሰጠ ይመስላል›› ያሉ ሲሆን ሲስተሙ ባለመስራቱ በጉምሩክ መስሪያ ቤቶችና በባንኮች ለረጅም ሰአታት ወረፋ በመጠበቅ ለድካምና እንግልት እንደዳረጋቸው አስረድተዋል፡፡ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የገዟቸውና ወደአገር ውስጥ ያስገቧቸው እቃዎች በወቅቱ ባለመውጣታቸው በየወደቡና በየመጋዘኑ እየተበላሹና ለጉዳት እየተዳረጉ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ ላኪዎች በማንዋል እንዲስተናገዱ እየተደረገ ባለበት ወቅት አስመጪዎችን በተመሳሳይ መንገድ ለምን ማስተናገድ አልተቻለም? የሚል ጥያቄ ያነሳሉ፡፡
ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ይህ በጉምሩክና በባንኮች መካከል ያለው የአሰራር መጓተትና የአማራጭ መፍትሄ እጥረት በአስቸኳይ ካልተቀረፈ በአገሪቱ ውስጥ የገበያ አቅርቦትና የዋጋ ንረት ላይ የራሱን አሉታዊ ጥላ ሊያሳርፍ ይችላል፡፡
2 months ago
ሚዲያዎች የማኅበረሰብ ትስስርን በማጉላት ለሀገራዊ አንድነት መጠናከር ሊሰሩ ይገባል፡- የሰላም ሚኒስቴር
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
2 months ago
በጉምሩክ የቴክኖሎጂ ሥርዓት መቋረጥ ሳቢያ አስመጪዎች ለከፍተኛ እንግልትና ለገንዘብ ኪሳራ መዳረጋቸውን አስታወቁ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጉምሩክ ዲጂታል አሠራር ወይም የኤሌክትሮኒክስ ሲንግል ዊንዶው ሲስተም አገልግሎት ማቋረጡን ተከትሎ፣ ወደ ሀገር ውስጥ ዕቃ የሚያስገቡ ነጋዴዎች ንብረቶቻቸውን በወቅቱ መረከብ ባለመቻላቸው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ባወጣው ይፋዊ መመሪያ፣ በቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቅረፍ እንደ ጊዜያዊ መፍትሔ ለላኪዎች ብቻ በእጅ ወይም በማንዋል እንዲስተናገዱ ፈቅዷል።
ሆኖም ይህ አማራጭ አሠራር ለአስመጪዎች ባለመፈቀዱ የተነሳ በነጋዴዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
በርካታ አስመጪዎች እንደሚናገሩት፣ ይህ ውሳኔ ላኪዎችን ብቻ ለይቶ የጠቀመና አስመጪዎችን ለአላስፈላጊ መጉላላት አሳልፎ የሰጠ ነው። በሲስተሙ መበላሸት ምክንያት አስመጪዎች የሚከተሉት ችግሮች እየገጠሟቸው ይገኛሉ፡
የመጀመሪያው፣
በጉምሩክ መሥሪያ ቤቶችና በባንኮች ረጅም ሰዓታትን በሰልፍ በማሳለፍ ለከፍተኛ ድካም መዳረጋቸው ነው።
ሁለተኛው፣
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር የገቡ ዕቃዎች በወቅቱ ባለመውጣታቸው በየወደቦቹና በማከማቻ ቦታዎች ላይ እየተበላሹና እየጠፉ መሆኑ ነው።
ሦስተኛው
የንግድና የማምረት እንቅስቃሴዎች ሙሉ በሙሉ በመስተጓጎላቸው በየቀኑ በሰው ኃይልና በጊዜ ረገድ የማይተካ የገንዘብ ኪሳራ እየደረሰባቸው መሆኑ ነው።
የአስመጪዎች ጥሪ
ላኪዎች በማንዋል እንዲስተናገዱ ከተደረገ፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍተኛ የሀገር ሀብት የወጣባቸው የአስመጪዎች ዕቃዎች በማንዋል ተስተናግደው እንዲወጡ ለምን አልተደረገም ሲሉ ነጋዴዎቹ በምሬት ይጠይቃሉ።
በጉምሩክና በባንኮች መካከል ያለው የአሠራር መዘግየትና የአማራጭ መፍትሔ እጥረት በአስቸኳይ ካልተቀረፈ፣ በሀገሪቱ የገበያ አቅርቦትና በኑሮ ውድነት ላይ የራሱን አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳረፉ እንደማይቀር የዘርፉ ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
ስለሆነም የሚመለከተው የመንግሥት አካል ለአስመጪዎችም አስቸኳይና ፍትሐዊ አማራጭ አሠራር በመዘርጋት ሕዝብንና ሀገርን ከኪሳራ እንዲታደግ ጥሪ ቀርቧል።
#customsethiopia #tradeethiopia #economyethiopia #importersethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጉምሩክ ዲጂታል አሠራር ወይም የኤሌክትሮኒክስ ሲንግል ዊንዶው ሲስተም አገልግሎት ማቋረጡን ተከትሎ፣ ወደ ሀገር ውስጥ ዕቃ የሚያስገቡ ነጋዴዎች ንብረቶቻቸውን በወቅቱ መረከብ ባለመቻላቸው ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
የጉምሩክ ኮሚሽን ባወጣው ይፋዊ መመሪያ፣ በቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ላይ ያጋጠመውን ችግር ለመቅረፍ እንደ ጊዜያዊ መፍትሔ ለላኪዎች ብቻ በእጅ ወይም በማንዋል እንዲስተናገዱ ፈቅዷል።
ሆኖም ይህ አማራጭ አሠራር ለአስመጪዎች ባለመፈቀዱ የተነሳ በነጋዴዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
በርካታ አስመጪዎች እንደሚናገሩት፣ ይህ ውሳኔ ላኪዎችን ብቻ ለይቶ የጠቀመና አስመጪዎችን ለአላስፈላጊ መጉላላት አሳልፎ የሰጠ ነው። በሲስተሙ መበላሸት ምክንያት አስመጪዎች የሚከተሉት ችግሮች እየገጠሟቸው ይገኛሉ፡
የመጀመሪያው፣
በጉምሩክ መሥሪያ ቤቶችና በባንኮች ረጅም ሰዓታትን በሰልፍ በማሳለፍ ለከፍተኛ ድካም መዳረጋቸው ነው።
ሁለተኛው፣
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር የገቡ ዕቃዎች በወቅቱ ባለመውጣታቸው በየወደቦቹና በማከማቻ ቦታዎች ላይ እየተበላሹና እየጠፉ መሆኑ ነው።
ሦስተኛው
የንግድና የማምረት እንቅስቃሴዎች ሙሉ በሙሉ በመስተጓጎላቸው በየቀኑ በሰው ኃይልና በጊዜ ረገድ የማይተካ የገንዘብ ኪሳራ እየደረሰባቸው መሆኑ ነው።
የአስመጪዎች ጥሪ
ላኪዎች በማንዋል እንዲስተናገዱ ከተደረገ፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍተኛ የሀገር ሀብት የወጣባቸው የአስመጪዎች ዕቃዎች በማንዋል ተስተናግደው እንዲወጡ ለምን አልተደረገም ሲሉ ነጋዴዎቹ በምሬት ይጠይቃሉ።
በጉምሩክና በባንኮች መካከል ያለው የአሠራር መዘግየትና የአማራጭ መፍትሔ እጥረት በአስቸኳይ ካልተቀረፈ፣ በሀገሪቱ የገበያ አቅርቦትና በኑሮ ውድነት ላይ የራሱን አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳረፉ እንደማይቀር የዘርፉ ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
ስለሆነም የሚመለከተው የመንግሥት አካል ለአስመጪዎችም አስቸኳይና ፍትሐዊ አማራጭ አሠራር በመዘርጋት ሕዝብንና ሀገርን ከኪሳራ እንዲታደግ ጥሪ ቀርቧል።
#customsethiopia #tradeethiopia #economyethiopia #importersethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ከፈተና ወደ ከፍታ፦ “ኢትዮጵያን ማንም አያሸንፍም” የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል በተግባር ሲገለጥ
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የአዲሱ ታርጋ ክፍያ በአሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ ጫና በመፍጠር የኑሮ ውድነቱን እንደሚያባብሰው ተገለጸ
የአዲሱ ታርጋ ክፍያ በአሽከርካሪዎች ላይ ድንገተኛና ከባድ የፋይናንስ ጫና በመፍጠር የመንቀሳቀስ አቅምን ሊገድብ እንደሚችል የፋይናንስ እና የሕግ ባለሙያዎች ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታወቁ።
አዲሱ የታርጋ ክፍያ ከቀድሞው አንጻር ሲነጻጸር እጅግ የተጋነነ በመሆኑ፣ በአሽከርካሪዎች ላይ ድንገተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር የፋይናንስ ባለሙያው ዶክተር ሰውአለ አባተ ገልጸዋል።
ዋጋው አሽከርካሪዎች ተሽከርካሪያቸውን በነጻነት እንዳያንቀሳቅሱ የሚገድብና ክፍያውን መክፈል የማይችሉ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን አቁመው የሕዝብ ትራንስፖርት እንዲጠቀሙ የሚያስገድድ በመሆኑ፣ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴና በምርታማነት ላይ አሉታዊ መስተጓጎል እንደሚያስከትል ተናግረዋል። በመሆኑም መንግሥት የክፍያ ተመን ሲያወጣ የሕዝቡን የመግዛት አቅምና የኢኮኖሚውን የመሸከም አቅም ሊያገናዝብ እንደሚገባ ዶክተር ሰውአለ አሳስበዋል።
ያለምንም ቅድመ ዝግጅት የሚወሰኑ መሰል ድንገተኛ ወጪዎች የንግድ እንቅስቃሴን በማቀዝቀዝ፣ ምርታማነትን በመቀነስና በማኅበረሰቡ ላይ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ በመፍጠር አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖራቸውም ባለሙያው ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል አዲሱ ዋጋ የሕዝብን የኢኮኖሚ አቅም ያላገናዘበና ፍትሐዊነት የጎደለው ነው የሚሉት ደግሞ የሕግ ባለሙያው አቶ ታረቀኝ አበራ ናቸው።
በኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ ተሽከርካሪ ለሥራና ለሀገር ኢኮኖሚ መሠረታዊ በመሆኑ ሊበረታታ እንጂ ተስፋ በሚያስቆርጥ የተጋነነ የታርጋ ክፍያ ሊገደብ እንደማይገባ የገለጹት ባለሙያው፣ የወጣው መመሪያ የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች የሚጋፋ መሆኑ ከተረጋገጠ ማስተካከያ ሊደረግበት የሚችል የሕግ አግባብ መኖሩን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ መንግሥት መሰል ድንገተኛ ውሳኔዎችን ሲያስተላልፍ፣ የኅብረተሰቡን ተጨባጭ የመግዛት አቅምና የኢኮኖሚውን ነባራዊ ሁኔታ ያማከለ ሊሆን እንደሚገባ ባለሙያዎቹ በአፅንዖት አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲሱ ታርጋ ክፍያ በአሽከርካሪዎች ላይ ድንገተኛና ከባድ የፋይናንስ ጫና በመፍጠር የመንቀሳቀስ አቅምን ሊገድብ እንደሚችል የፋይናንስ እና የሕግ ባለሙያዎች ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታወቁ።
አዲሱ የታርጋ ክፍያ ከቀድሞው አንጻር ሲነጻጸር እጅግ የተጋነነ በመሆኑ፣ በአሽከርካሪዎች ላይ ድንገተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር የፋይናንስ ባለሙያው ዶክተር ሰውአለ አባተ ገልጸዋል።
ዋጋው አሽከርካሪዎች ተሽከርካሪያቸውን በነጻነት እንዳያንቀሳቅሱ የሚገድብና ክፍያውን መክፈል የማይችሉ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቻቸውን አቁመው የሕዝብ ትራንስፖርት እንዲጠቀሙ የሚያስገድድ በመሆኑ፣ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴና በምርታማነት ላይ አሉታዊ መስተጓጎል እንደሚያስከትል ተናግረዋል። በመሆኑም መንግሥት የክፍያ ተመን ሲያወጣ የሕዝቡን የመግዛት አቅምና የኢኮኖሚውን የመሸከም አቅም ሊያገናዝብ እንደሚገባ ዶክተር ሰውአለ አሳስበዋል።
ያለምንም ቅድመ ዝግጅት የሚወሰኑ መሰል ድንገተኛ ወጪዎች የንግድ እንቅስቃሴን በማቀዝቀዝ፣ ምርታማነትን በመቀነስና በማኅበረሰቡ ላይ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ በመፍጠር አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖራቸውም ባለሙያው ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል አዲሱ ዋጋ የሕዝብን የኢኮኖሚ አቅም ያላገናዘበና ፍትሐዊነት የጎደለው ነው የሚሉት ደግሞ የሕግ ባለሙያው አቶ ታረቀኝ አበራ ናቸው።
በኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ ተሽከርካሪ ለሥራና ለሀገር ኢኮኖሚ መሠረታዊ በመሆኑ ሊበረታታ እንጂ ተስፋ በሚያስቆርጥ የተጋነነ የታርጋ ክፍያ ሊገደብ እንደማይገባ የገለጹት ባለሙያው፣ የወጣው መመሪያ የዜጎችን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች የሚጋፋ መሆኑ ከተረጋገጠ ማስተካከያ ሊደረግበት የሚችል የሕግ አግባብ መኖሩን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ መንግሥት መሰል ድንገተኛ ውሳኔዎችን ሲያስተላልፍ፣ የኅብረተሰቡን ተጨባጭ የመግዛት አቅምና የኢኮኖሚውን ነባራዊ ሁኔታ ያማከለ ሊሆን እንደሚገባ ባለሙያዎቹ በአፅንዖት አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ከተፈጥሮ ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት
***************
ባለፉት ዓመታት የብዝሃ ሕይወት መመናመን፣ የመሬት መራቆት፣ የምርታማነት መቀነስ እንዲሁም የውኃ አካላት በደለል መሞላትና መጥፋት ማኅበረሰባችንን ለድርቅ፣ ለጎርፍ እና ለምግብ ዋስትና ችግሮች ተጋላጭ አድርጎት መቆየቱ ይታወሳል።
ይህን ታሳቢ በማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገር በቀል ዕፅዋትንና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ለውጥን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ግንባር ቀደም የለውጥ መሠረት መሆን ችሏል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት በተሰሩ ብርቱ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በመርሐ ግብሩ እስካሁን 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የሀገራችን አረንጓዴ ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል።
ይህ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ተፅዕኖን በመቀነስ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ታላቅ ተግባርም ጭምር ነው።
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ ዛፎችና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ዕፅዋት ላይ ትኩረት መደረጉ ለምግብ ዋስትና እና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻል ለሚደረገው ጉዞ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
መርሐ ግብሩ የውኃ እጥረትን በከፍተኛ ደረጃ ከመቅረፉና የውኃ አካላት በደለል እንዳይሞሉ ከመከላከሉ ጋር ተያይዞ፣ አርሶ አደሮች ከክረምት ወቅት ጥገኝነት ወጥተው በበጋ ወቅትም በመስኖ በዓመት ሁለቴና ከዚያም በላይ እንዲያመርቱ ሰፊ ዕድል ከፍቷል።
ስለሆነም ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገበት የሚገኘው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የነገዋን ኢትዮጵያ ገጽታ የሚወስን ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህንን መርሐ-ግብር በታቀደለት መንገድ ማሳካት የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ አረንጓዴና የተደላደለች ሀገርን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ዋነኛው መሣሪያ በመሆኑ "ነገን ዛሬ እንትከል፣ የነገው አረንጓዴ አሻራ የዛሬው እጃችን ሥራ ነው"።
በብሌን ደምበሎ
#greenlegacy #climateaction #foodsecurity #economicdiplomacy #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
ባለፉት ዓመታት የብዝሃ ሕይወት መመናመን፣ የመሬት መራቆት፣ የምርታማነት መቀነስ እንዲሁም የውኃ አካላት በደለል መሞላትና መጥፋት ማኅበረሰባችንን ለድርቅ፣ ለጎርፍ እና ለምግብ ዋስትና ችግሮች ተጋላጭ አድርጎት መቆየቱ ይታወሳል።
ይህን ታሳቢ በማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገር በቀል ዕፅዋትንና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ለውጥን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ግንባር ቀደም የለውጥ መሠረት መሆን ችሏል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት በተሰሩ ብርቱ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በመርሐ ግብሩ እስካሁን 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የሀገራችን አረንጓዴ ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል።
ይህ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ተፅዕኖን በመቀነስ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ታላቅ ተግባርም ጭምር ነው።
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ ዛፎችና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ዕፅዋት ላይ ትኩረት መደረጉ ለምግብ ዋስትና እና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻል ለሚደረገው ጉዞ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
መርሐ ግብሩ የውኃ እጥረትን በከፍተኛ ደረጃ ከመቅረፉና የውኃ አካላት በደለል እንዳይሞሉ ከመከላከሉ ጋር ተያይዞ፣ አርሶ አደሮች ከክረምት ወቅት ጥገኝነት ወጥተው በበጋ ወቅትም በመስኖ በዓመት ሁለቴና ከዚያም በላይ እንዲያመርቱ ሰፊ ዕድል ከፍቷል።
ስለሆነም ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገበት የሚገኘው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የነገዋን ኢትዮጵያ ገጽታ የሚወስን ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህንን መርሐ-ግብር በታቀደለት መንገድ ማሳካት የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ አረንጓዴና የተደላደለች ሀገርን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ዋነኛው መሣሪያ በመሆኑ "ነገን ዛሬ እንትከል፣ የነገው አረንጓዴ አሻራ የዛሬው እጃችን ሥራ ነው"።
በብሌን ደምበሎ
#greenlegacy #climateaction #foodsecurity #economicdiplomacy #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አገራዊ የምክክር ኮሚሽን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን አገራዊ የምክክር ጉባዔ ከቀጣዩ ሐምሌ 8 ጀምሮ በአዲስ አበባው አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል እንደሚያካሂድ አስታውቋል። አራት ሺሕ ገደማ ጉባኤተኞች ይሳተፉበታል የተባለውና ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ ታሪካዊ ጉባዔ፣ አገሪቱን ለዘመናት ሲያተራምሱ በቆዩ እና እጅግ ስሱ በሆኑ ፖለቲካዊ አጀንዳዎች ላይ የመጨረሻውን ምክክር እንደሚያደርግ ተገልጿል።
በዚህ አገር አቀፍ መድረክ ላይ ውሳኔ እና የጋራ መግባባት ይደረግባቸዋል ተብለው ከተያዙት አጀንዳዎች ክብደት አንጻር፣ ጉባዔው የኢትዮጵያን የፖለቲካ መሰረት ሊያናውጡ ወይም ሊያስተካክሉ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ ይወያያል። የሕገመንግሥት ማሻሻያ፣ ለዘመናት ምላሽ ያላገኙ የማንነት ጥያቄዎች፣ የክልሎች የድንበር አከላለል ውዝግቦች፣ የፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጉዳይ፣ እንዲሁም ከብሔራዊ ሠንደቅ ዓላማ ጋር ተያይዞ ያለው የሰላ የፖለቲካ ልዩነት የጉባዔው ዋነኛ የትኩረት ነጥቦች ናቸው። ይሁን እንጂ እነዚህን መሰረታዊ እና ለጦርነት ሳይቀር ምክንያት የሆኑ ጥልቅ የፖለቲካ ልዩነቶችን በ15 ቀናት ጉባዔ ብቻ እልባት መስጠት ይቻላል ወይ? የሚለው ጉዳይ በፖለቲካ ተንታኞች ዘንድ ክሪቲካል ጥያቄ ሆኖ ብቅ ብሏል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ባደረገው የምክክር ሂደት 1 ሺሕ 234 የአገሪቱን ወረዳዎች ያሳተፈ መሆኑን እና በአጠቃላይ 93 በመቶ የሚሆነውን የአገሪቱን ክፍል መሸፈኑን እንደ ትልቅ ስኬት አንስቷል። ይህ አሃዛዊ መረጃ የኮሚሽኑን ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቢሆንም፣ የትግራይ ክልል በዚህ አገር አቀፍ የምክክር ሂደት ውስጥ ሙሉ በሙሉ አለመሳተፉ የሂደቱን "አገራዊነት" እና አሳታፊነት በጽኑ የሚፈታተን ትልቅ ክፍተት ነው።
በትግራይ ክልል ምንም አይነት የምክክር ሂደት አለመካሄዱ እና የክልሉ የፖለቲካ ኃይሎችም ሆኑ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በጉባዔው አለመሳተፋቸው፣ በተለይም እንደ ሕገመንግሥት ማሻሻያ እና የድንበር አከላለል ባሉ አጀንዳዎች ላይ የሚደረገውን ብሔራዊ መግባባት ጎዶሎ ያደርገዋል። አገሪቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከገባችበት ጥልቅ የፖለቲካ እና የጸጥታ አዘቅት ለመውጣት በሚደረገው በዚህ ወሳኝ ጉባዔ ላይ፣ የትግራይ ድምጽ አለመካተቱ በቀጣይ አገራዊ ዕርቅ እና የፖለቲካ መረጋጋት ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ የራሱን አሉታዊ ጥላ ማጥላቱ አይቀርም።
ይህ ጉባዔ የኢትዮጵያን የፖለቲካ አቅጣጫ ለመቀየር ወሳኝ እርምጃ ተደርጎ ቢወሰድም፣ የሁሉም ባለድርሻ አካላት በተለይም የትግራይ አለመሳተፍ፣ እንዲሁም የአጀንዳዎቹ እጅግ ውስብስብነት፣ የኮሚሽኑን የመጨረሻ ግብ ስኬት በፈተና ውስጥ የሚጥለው መሆኑ አያጠራጥርም።
በዚህ አገር አቀፍ መድረክ ላይ ውሳኔ እና የጋራ መግባባት ይደረግባቸዋል ተብለው ከተያዙት አጀንዳዎች ክብደት አንጻር፣ ጉባዔው የኢትዮጵያን የፖለቲካ መሰረት ሊያናውጡ ወይም ሊያስተካክሉ የሚችሉ ጉዳዮች ላይ ይወያያል። የሕገመንግሥት ማሻሻያ፣ ለዘመናት ምላሽ ያላገኙ የማንነት ጥያቄዎች፣ የክልሎች የድንበር አከላለል ውዝግቦች፣ የፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ጉዳይ፣ እንዲሁም ከብሔራዊ ሠንደቅ ዓላማ ጋር ተያይዞ ያለው የሰላ የፖለቲካ ልዩነት የጉባዔው ዋነኛ የትኩረት ነጥቦች ናቸው። ይሁን እንጂ እነዚህን መሰረታዊ እና ለጦርነት ሳይቀር ምክንያት የሆኑ ጥልቅ የፖለቲካ ልዩነቶችን በ15 ቀናት ጉባዔ ብቻ እልባት መስጠት ይቻላል ወይ? የሚለው ጉዳይ በፖለቲካ ተንታኞች ዘንድ ክሪቲካል ጥያቄ ሆኖ ብቅ ብሏል።
ኮሚሽኑ እስካሁን ባደረገው የምክክር ሂደት 1 ሺሕ 234 የአገሪቱን ወረዳዎች ያሳተፈ መሆኑን እና በአጠቃላይ 93 በመቶ የሚሆነውን የአገሪቱን ክፍል መሸፈኑን እንደ ትልቅ ስኬት አንስቷል። ይህ አሃዛዊ መረጃ የኮሚሽኑን ሰፊ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ቢሆንም፣ የትግራይ ክልል በዚህ አገር አቀፍ የምክክር ሂደት ውስጥ ሙሉ በሙሉ አለመሳተፉ የሂደቱን "አገራዊነት" እና አሳታፊነት በጽኑ የሚፈታተን ትልቅ ክፍተት ነው።
በትግራይ ክልል ምንም አይነት የምክክር ሂደት አለመካሄዱ እና የክልሉ የፖለቲካ ኃይሎችም ሆኑ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች በጉባዔው አለመሳተፋቸው፣ በተለይም እንደ ሕገመንግሥት ማሻሻያ እና የድንበር አከላለል ባሉ አጀንዳዎች ላይ የሚደረገውን ብሔራዊ መግባባት ጎዶሎ ያደርገዋል። አገሪቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከገባችበት ጥልቅ የፖለቲካ እና የጸጥታ አዘቅት ለመውጣት በሚደረገው በዚህ ወሳኝ ጉባዔ ላይ፣ የትግራይ ድምጽ አለመካተቱ በቀጣይ አገራዊ ዕርቅ እና የፖለቲካ መረጋጋት ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ላይ የራሱን አሉታዊ ጥላ ማጥላቱ አይቀርም።
ይህ ጉባዔ የኢትዮጵያን የፖለቲካ አቅጣጫ ለመቀየር ወሳኝ እርምጃ ተደርጎ ቢወሰድም፣ የሁሉም ባለድርሻ አካላት በተለይም የትግራይ አለመሳተፍ፣ እንዲሁም የአጀንዳዎቹ እጅግ ውስብስብነት፣ የኮሚሽኑን የመጨረሻ ግብ ስኬት በፈተና ውስጥ የሚጥለው መሆኑ አያጠራጥርም።
Comments