26 days ago
ምድርን ከአረንጓዴ ልባስ፣ አርሶ አደሩን ከገቢ ምንጭ ጋር ያገናኘው አረንጓዴ ዐሻራ
**************
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ምድርን በአረንጓዴ ተክሎች ከመሸፈንና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ ሀገራዊ የምግብ ዋስትናንና ምርታማነትን ወደማረጋገጥ የተሸጋገረ ታላቅ ስኬት እየመዘገበ ይገኛል።
ቀደም ሲል ለደን ጥበቃና ለተራቆቱ መሬቶች ማገገሚያ ብቻ ትኩረት ይሰጥ የነበረው ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ፣ አሁን ላይ ስትራቴጂካዊ ለውጥ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃን ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ጋር ያቀናጀ የኢኮኖሚ ምሶሶ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ስኬት በጉልህ ከሚታይባቸውና ትልቅ እመርታ ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል የፍራፍሬ ምርት ልማት ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የተሻሻሉና ፍሬያማ የሆኑ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና የኮምጣጤ ፍራፍሬዎች ዝርያዎች በስፋት እንዲተከሉ መደረጉ በየደረጃው ለሚገኙ አርሶ አደሮችና አምራቾች አዲስ የገቢ ምንጭ ፈጥሯል።
ንቅናቄው የአፈር መሸርሸርን በዘላቂነት ከመግታት ባለፈ፣ የመሬትን ለምነት በማሻሻልና የከርሰ-ምድር ውኃን በመጠበቅ ለፍራፍሬ ልማትና ለተሻሻለ ግብርና እጅግ ምቹ የሆነ ሥነ-ምህዳራዊ ሁኔታን ፈጥሯል።
ይህ የምርታማነት እመርታ አርሶ አደሩን ከራስ-አልፎ ለገበያ እንዲያመርት ከማስቻሉም በላይ፣ በከተሞች የሚስተዋለውን የፍራፍሬ አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረት እያቃለለ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር፣ ጥራቱን የጠበቀ የፍራፍሬ ምርት በስፋት መመረቱ የኢትዮጵያን የኤክስፖርት አቅም በማሳደግና ወደ ውጭ የመላክ ዕድሎችን በማስፋት የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት የራሱን የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ተፈጥሮን ከመንከባከብና ምድርን ከማልበስ ባለፈ፣ የዜጎችን ማዕድ በሥርዓተ-ምግብ እራስን ወደመቻል ያሸጋገረ ፕሮጀክት ነው። የአካባቢ ጥበቃና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዴት እጅና ጓንት ሆነው እንደሚጓዙ እና የአየር ንብረት መከላከል ወደ ተጨባጭ ምርታማነት እንዴት እንደሚቀየር ያሳየ ሕያው ሀገራዊ ማረጋገጫ ሆኗል።
#greenlegacy #ethiopianbroadcastingcorporation #agricultureethiopia #foodsecurity #greeneconomy
**************
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ምድርን በአረንጓዴ ተክሎች ከመሸፈንና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ ሀገራዊ የምግብ ዋስትናንና ምርታማነትን ወደማረጋገጥ የተሸጋገረ ታላቅ ስኬት እየመዘገበ ይገኛል።
ቀደም ሲል ለደን ጥበቃና ለተራቆቱ መሬቶች ማገገሚያ ብቻ ትኩረት ይሰጥ የነበረው ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ፣ አሁን ላይ ስትራቴጂካዊ ለውጥ በማድረግ የአካባቢ ጥበቃን ከኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ጋር ያቀናጀ የኢኮኖሚ ምሶሶ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ስኬት በጉልህ ከሚታይባቸውና ትልቅ እመርታ ከተመዘገበባቸው ዘርፎች መካከል የፍራፍሬ ምርት ልማት ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይይዛል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የተሻሻሉና ፍሬያማ የሆኑ የአቮካዶ፣ የማንጎ፣ የፓፓያ እና የኮምጣጤ ፍራፍሬዎች ዝርያዎች በስፋት እንዲተከሉ መደረጉ በየደረጃው ለሚገኙ አርሶ አደሮችና አምራቾች አዲስ የገቢ ምንጭ ፈጥሯል።
ንቅናቄው የአፈር መሸርሸርን በዘላቂነት ከመግታት ባለፈ፣ የመሬትን ለምነት በማሻሻልና የከርሰ-ምድር ውኃን በመጠበቅ ለፍራፍሬ ልማትና ለተሻሻለ ግብርና እጅግ ምቹ የሆነ ሥነ-ምህዳራዊ ሁኔታን ፈጥሯል።
ይህ የምርታማነት እመርታ አርሶ አደሩን ከራስ-አልፎ ለገበያ እንዲያመርት ከማስቻሉም በላይ፣ በከተሞች የሚስተዋለውን የፍራፍሬ አቅርቦት እጥረትና የዋጋ ንረት እያቃለለ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር፣ ጥራቱን የጠበቀ የፍራፍሬ ምርት በስፋት መመረቱ የኢትዮጵያን የኤክስፖርት አቅም በማሳደግና ወደ ውጭ የመላክ ዕድሎችን በማስፋት የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት የራሱን የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ተፈጥሮን ከመንከባከብና ምድርን ከማልበስ ባለፈ፣ የዜጎችን ማዕድ በሥርዓተ-ምግብ እራስን ወደመቻል ያሸጋገረ ፕሮጀክት ነው። የአካባቢ ጥበቃና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዴት እጅና ጓንት ሆነው እንደሚጓዙ እና የአየር ንብረት መከላከል ወደ ተጨባጭ ምርታማነት እንዴት እንደሚቀየር ያሳየ ሕያው ሀገራዊ ማረጋገጫ ሆኗል።
#greenlegacy #ethiopianbroadcastingcorporation #agricultureethiopia #foodsecurity #greeneconomy
2 months ago
The Secret Behind 48 Billion Trees
#greenlegacy #ethiopia #unclimate #foodsecurity #climateaction #48billiontrees ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
The Secret Behind 48 Billion Trees
#greenlegacy #ethiopia #unclimate #foodsecurity #climateaction #48billiontrees
2 months ago
ከተፈጥሮ ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት
***************
ባለፉት ዓመታት የብዝሃ ሕይወት መመናመን፣ የመሬት መራቆት፣ የምርታማነት መቀነስ እንዲሁም የውኃ አካላት በደለል መሞላትና መጥፋት ማኅበረሰባችንን ለድርቅ፣ ለጎርፍ እና ለምግብ ዋስትና ችግሮች ተጋላጭ አድርጎት መቆየቱ ይታወሳል።
ይህን ታሳቢ በማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገር በቀል ዕፅዋትንና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ለውጥን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ግንባር ቀደም የለውጥ መሠረት መሆን ችሏል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት በተሰሩ ብርቱ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በመርሐ ግብሩ እስካሁን 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የሀገራችን አረንጓዴ ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል።
ይህ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ተፅዕኖን በመቀነስ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ታላቅ ተግባርም ጭምር ነው።
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ ዛፎችና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ዕፅዋት ላይ ትኩረት መደረጉ ለምግብ ዋስትና እና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻል ለሚደረገው ጉዞ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
መርሐ ግብሩ የውኃ እጥረትን በከፍተኛ ደረጃ ከመቅረፉና የውኃ አካላት በደለል እንዳይሞሉ ከመከላከሉ ጋር ተያይዞ፣ አርሶ አደሮች ከክረምት ወቅት ጥገኝነት ወጥተው በበጋ ወቅትም በመስኖ በዓመት ሁለቴና ከዚያም በላይ እንዲያመርቱ ሰፊ ዕድል ከፍቷል።
ስለሆነም ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገበት የሚገኘው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የነገዋን ኢትዮጵያ ገጽታ የሚወስን ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህንን መርሐ-ግብር በታቀደለት መንገድ ማሳካት የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ አረንጓዴና የተደላደለች ሀገርን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ዋነኛው መሣሪያ በመሆኑ "ነገን ዛሬ እንትከል፣ የነገው አረንጓዴ አሻራ የዛሬው እጃችን ሥራ ነው"።
በብሌን ደምበሎ
#greenlegacy #climateaction #foodsecurity #economicdiplomacy #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
ባለፉት ዓመታት የብዝሃ ሕይወት መመናመን፣ የመሬት መራቆት፣ የምርታማነት መቀነስ እንዲሁም የውኃ አካላት በደለል መሞላትና መጥፋት ማኅበረሰባችንን ለድርቅ፣ ለጎርፍ እና ለምግብ ዋስትና ችግሮች ተጋላጭ አድርጎት መቆየቱ ይታወሳል።
ይህን ታሳቢ በማድረግ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገር በቀል ዕፅዋትንና የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ለውጥን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ግንባር ቀደም የለውጥ መሠረት መሆን ችሏል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት በተሰሩ ብርቱ ሥራዎች አበረታች ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በመርሐ ግብሩ እስካሁን 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል የሀገራችን አረንጓዴ ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ተችሏል።
ይህ የኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ ልማት ከተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ባለፈ፣ የአየር ንብረት ተፅዕኖን በመቀነስ ለሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊና ዲፕሎማሲያዊ መስኮች ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እያስገኘ ይገኛል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ተፈጥሮን የመንከባከብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትና የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ታላቅ ተግባርም ጭምር ነው።
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ ዛፎችና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ባላቸው ዕፅዋት ላይ ትኩረት መደረጉ ለምግብ ዋስትና እና ለሥርዓተ ምግብ መሻሻል ለሚደረገው ጉዞ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
መርሐ ግብሩ የውኃ እጥረትን በከፍተኛ ደረጃ ከመቅረፉና የውኃ አካላት በደለል እንዳይሞሉ ከመከላከሉ ጋር ተያይዞ፣ አርሶ አደሮች ከክረምት ወቅት ጥገኝነት ወጥተው በበጋ ወቅትም በመስኖ በዓመት ሁለቴና ከዚያም በላይ እንዲያመርቱ ሰፊ ዕድል ከፍቷል።
ስለሆነም ዘንድሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት እየተደረገበት የሚገኘው 7ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የነገዋን ኢትዮጵያ ገጽታ የሚወስን ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህንን መርሐ-ግብር በታቀደለት መንገድ ማሳካት የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ፣ አረንጓዴና የተደላደለች ሀገርን በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት ዋነኛው መሣሪያ በመሆኑ "ነገን ዛሬ እንትከል፣ የነገው አረንጓዴ አሻራ የዛሬው እጃችን ሥራ ነው"።
በብሌን ደምበሎ
#greenlegacy #climateaction #foodsecurity #economicdiplomacy #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1235u1295u12f4 u1270u12d3u121du122du1361 u12a8u12a0u1235u1218u132au1290u1275 u12c8u12f0 u12cdu132d u120bu12aau1290u1275 u12e8u1270u12f0u1228u1308u12cdu1309u12de
#wheattransformation #ethiopianagriculture #greenlegacy #ethiopia #foodsecurity ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የኢትዮጵያ ስንዴ ተዓምር፡ ከአስመጪነት ወደ ውጭ ላኪነት የተደረገውጉዞ
#wheattransformation #ethiopianagriculture #greenlegacy #ethiopia #foodsecurity
7 months ago
በኢትዮጵያ የምግብ ፍላጎት መጨመር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል
📌ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችላትን የ10 ዓመት የጥምር ደን እርሻ (አግሮፎርስትሪ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
#ethiopia | የግብርና ሚኒስቴር የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን ብሔራዊ የአግሮፎርስትሪ (ጥምር ደን እርሻ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገ።
ይህ ከ2026 እስከ 2035 እ.ኤ.አ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የሚያገለግለው ስትራቴጂ፣ ሚኒስቴሩ ከበርካታ የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ተገልጿል።
የስትራቴጂው አስፈላጊነት፦🖊
በግብርና ሚኒስቴር የሥራ አመራር ተወካይ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ጫላ ሆርዶፋ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የአፈር መሸርሸር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና እየጨመረ የመጣው የምግብ ፍላጎት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
ይህ ስትራቴጂም፦🔎
* የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል፣
* የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣
* የተቀናጀ የግብርና ስራን ለማስፋፋት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በረሃማነትን የመከላከል ፋይዳ፦
በስትራቴጂው ዝግጅት ላይ የተሳተፈው የዓለም ጥምር ደን እርሻ ምርምር ማዕከል (ICRAF) ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር አቶ እዮብ ጌታሁን ለብስራት ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል እርጥበት አዘል የነበሩ አካባቢዎች ወደ ደረቅ መሬትነት እየተቀየሩና በረሃማነት እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይፋ የሆነው ስትራቴጂ አርሶ አደሮች ዛፎችን ከሰብልና ከእንስሳት እርባታ ጋር አጣምረው እንዲያለሙ (Agroforestry System) በማድረግ፣ የመሬትን ምርታማነት እንዲጨምሩና የአካባቢን አየር ንብረት እንዲያስተካክሉ ይረዳል ተብሏል።
ስትራቴጂው ተግባራዊ መደረጉ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሯን በዘላቂነት ለማስቀጠል ለምታደርገው ጥረት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agriculture #agroforestry #climatechange #greenlegacy #foodsecurity #sustainablefarming #news
📌ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችላትን የ10 ዓመት የጥምር ደን እርሻ (አግሮፎርስትሪ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
#ethiopia | የግብርና ሚኒስቴር የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን ብሔራዊ የአግሮፎርስትሪ (ጥምር ደን እርሻ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገ።
ይህ ከ2026 እስከ 2035 እ.ኤ.አ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የሚያገለግለው ስትራቴጂ፣ ሚኒስቴሩ ከበርካታ የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ተገልጿል።
የስትራቴጂው አስፈላጊነት፦🖊
በግብርና ሚኒስቴር የሥራ አመራር ተወካይ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ጫላ ሆርዶፋ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የአፈር መሸርሸር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና እየጨመረ የመጣው የምግብ ፍላጎት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
ይህ ስትራቴጂም፦🔎
* የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል፣
* የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣
* የተቀናጀ የግብርና ስራን ለማስፋፋት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በረሃማነትን የመከላከል ፋይዳ፦
በስትራቴጂው ዝግጅት ላይ የተሳተፈው የዓለም ጥምር ደን እርሻ ምርምር ማዕከል (ICRAF) ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር አቶ እዮብ ጌታሁን ለብስራት ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል እርጥበት አዘል የነበሩ አካባቢዎች ወደ ደረቅ መሬትነት እየተቀየሩና በረሃማነት እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይፋ የሆነው ስትራቴጂ አርሶ አደሮች ዛፎችን ከሰብልና ከእንስሳት እርባታ ጋር አጣምረው እንዲያለሙ (Agroforestry System) በማድረግ፣ የመሬትን ምርታማነት እንዲጨምሩና የአካባቢን አየር ንብረት እንዲያስተካክሉ ይረዳል ተብሏል።
ስትራቴጂው ተግባራዊ መደረጉ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሯን በዘላቂነት ለማስቀጠል ለምታደርገው ጥረት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agriculture #agroforestry #climatechange #greenlegacy #foodsecurity #sustainablefarming #news
Comments