27 days ago
"የብራዚል እግር ኳስ ስብራት ገጥሞታል!"
የፔሌ ልጅ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ አስተዳደር በብልሹ አሰራር በመውደቁ እግርኳሱ ስብራት ገጥሞታል ስትል የፔሌ ልጅ ተናግራለች።
የአስተዳደሩ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የጎደለው አሰራር በብሔራዊ ቡድኑ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብላለች።
የእግርኳሱ ኮኮብ የፔሌ ታላቅ ሴት ልጅ አክቲቪስት እና የፊልም ባለሙያ የሆነችው ኬሊ ናሲሜንቶ ፔሌ ለሮይተርስ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ብሔራዊ ቡድኑ የገጠመውን ችግር ተናግራለች።
የብራዚል እግር ኳስ ተበላሽቷል
ሙስናና ሌላም ችግር በአስተዳደሩ ይነጸባረቃል ይህ በጣም ግልጽ ነው ብላለች።
ሁሉም ሰው አስተዳደሩ ለምን እንደማይሰራ ያውቃል ነገር ግን አንድም አካል ሊያስተካክለው አልቻለም ስትል ናሲሜንቶ ገልጻለች።
የብራዚል እግር ኳስ አሁንም ተሰጥኦ ያላቸው ምርጥ ተጫዋቾችን ማፍራቱን ቢቀጥልም በዓለም አቀፍ መድረክ የሚያሳዩት ደካማ አፈጻጸም ግን ሥር የሰደዱ መዋቅራዊ ችግሮች ውጤት መሆኑን ገልጻለች።
ብራዚል እሁድ ዕለት በኖርዌይ 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ይታወሳል።
ይህ ውጤት ብራዚል ከ1990 ወዲህ ለሩብ ፍጻሜ ማለፍ ሳትችል ስትቀር የመጀመሪያዋ ነው።
ሀገሪቱ ሪከርድ የሆነውን አምስተኛ የዓለም ዋንጫዋን ያሸነፈችው እ.ኤ.አ በ2002 ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #brazilfootball #reuters #greatpeledaughter #kelynascimento #activistfilmmaker
የፔሌ ልጅ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ አስተዳደር በብልሹ አሰራር በመውደቁ እግርኳሱ ስብራት ገጥሞታል ስትል የፔሌ ልጅ ተናግራለች።
የአስተዳደሩ ግልጽነት እና ተጠያቂነት የጎደለው አሰራር በብሔራዊ ቡድኑ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል ብላለች።
የእግርኳሱ ኮኮብ የፔሌ ታላቅ ሴት ልጅ አክቲቪስት እና የፊልም ባለሙያ የሆነችው ኬሊ ናሲሜንቶ ፔሌ ለሮይተርስ በሰጠችው ቃለ መጠይቅ ብሔራዊ ቡድኑ የገጠመውን ችግር ተናግራለች።
የብራዚል እግር ኳስ ተበላሽቷል
ሙስናና ሌላም ችግር በአስተዳደሩ ይነጸባረቃል ይህ በጣም ግልጽ ነው ብላለች።
ሁሉም ሰው አስተዳደሩ ለምን እንደማይሰራ ያውቃል ነገር ግን አንድም አካል ሊያስተካክለው አልቻለም ስትል ናሲሜንቶ ገልጻለች።
የብራዚል እግር ኳስ አሁንም ተሰጥኦ ያላቸው ምርጥ ተጫዋቾችን ማፍራቱን ቢቀጥልም በዓለም አቀፍ መድረክ የሚያሳዩት ደካማ አፈጻጸም ግን ሥር የሰደዱ መዋቅራዊ ችግሮች ውጤት መሆኑን ገልጻለች።
ብራዚል እሁድ ዕለት በኖርዌይ 2 ለ 1 ከተሸነፈች በኋላ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ይታወሳል።
ይህ ውጤት ብራዚል ከ1990 ወዲህ ለሩብ ፍጻሜ ማለፍ ሳትችል ስትቀር የመጀመሪያዋ ነው።
ሀገሪቱ ሪከርድ የሆነውን አምስተኛ የዓለም ዋንጫዋን ያሸነፈችው እ.ኤ.አ በ2002 ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #brazilfootball #reuters #greatpeledaughter #kelynascimento #activistfilmmaker
5 months ago
⚽️ በብራዚል የእግር ኳስ ሜዳ ወደ ጦር አውድማነት ተቀየረ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ በችሎታ ብቻ ሳይሆን በስሜትም የታወቀ ቢሆንም፣ በካምፒዮናቶ ሚኔሮ የክልል ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የታየው ክስተት ግን መላውን ዓለም አስደንግጧል። በታሪካዊ ተቀናቃኞቹ ክሩዜሮ እና አትሌቲኮ ሚኔሮ መካከል የተደረገው ጨዋታ፣ ስፖርታዊ ጨዋነት በጎደለው ድብድብ ተቋጭቶ ሪከርድ የሆነ 23 ቀይ ካርዶችን አስተናግዷል።
🥊 ግጭቱ እንዴት ተቀሰቀሰ?
ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰከንዶች ብቻ ሲቀሩት፣ የአትሌቲኮ ሚኔሮው ግብ ጠባቂ ኤቨርሰን የክሩዜሮውን አማካይ ክርስቲያንን መሬት ላይ ዘርሮ በጉልበቱ ደረቱ ላይ መውጣቱ ሁኔታውን ወደ አመጽ ቀይሮታል። ይህን ተከትሎ ተቀያሪ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ወደ ሜዳ በመፍለቃቸው ሜዳው የቦክስ መድረክ መስሏል። ሁኔታው ከቁጥጥር ውጪ በመሆኑ ወታደራዊ ፖሊሶች ሳይቀሩ ጣልቃ ለመግባት ተገደዋል።
🟥 የካርድ ናዳው
ዳኛው ማቲውስ ዴልጋዶ በግርግሩ ወቅት ካርድ ባያሳዩም፣ ከጨዋታው በኋላ በቪዲዮ (VAR) በመታገዝ በወሰዱት እርምጃ የሚከተሉት ተቀጥተዋል፦
* ከክሩዜሮ፦ የድሉን ግብ ያስቆጠረው ካዮ ጆርጅን ጨምሮ 12 ተጫዋቾች።
* ከአትሌቲኮ ሚኔሮ፦ አንጋፋው ሁልክ እና ሬናን ሎዲን ጨምሮ 11 ተጫዋቾች።
🏆 የድልና የውርደት ድብልቅ
አሰልጣኝ ቲቴ የሚመሩት ክሩዜሮዎች በካዮ ጆርጅ ግብ 1 ለ 0 አሸንፈው ከ2019 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የክልሉ ሻምፒዮን መሆን ቢችሉም፣ ድሉ በጸጸት የታጀበ ሆኗል። ኮከቡ ሁልክ ድርጊቱን "ለዓለም የምናሳየው መጥፎ ምስል ነው" ሲል ኮንኖታል።
በአሁኑ ወቅት ሁለቱም ክለቦች በብራዚል ሴሪ አ (Serie A) የደረጃ ሰንጠረዥ ግርጌ ላይ (17ኛ እና 19ኛ) የሚገኙ ሲሆን፣ ይህ የዲሲፕሊን እርምጃ በቀጣይ ጉዟቸው ላይ ተጨማሪ ፈተና እንደሚሆንባቸው ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #brazilfootball #cruzeiro #atleticomineiro #redcardrecord #footballnews #tite #hulk #sportsviolence #soccerupdates #campeonatomineiro
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ በችሎታ ብቻ ሳይሆን በስሜትም የታወቀ ቢሆንም፣ በካምፒዮናቶ ሚኔሮ የክልል ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የታየው ክስተት ግን መላውን ዓለም አስደንግጧል። በታሪካዊ ተቀናቃኞቹ ክሩዜሮ እና አትሌቲኮ ሚኔሮ መካከል የተደረገው ጨዋታ፣ ስፖርታዊ ጨዋነት በጎደለው ድብድብ ተቋጭቶ ሪከርድ የሆነ 23 ቀይ ካርዶችን አስተናግዷል።
🥊 ግጭቱ እንዴት ተቀሰቀሰ?
ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ሰከንዶች ብቻ ሲቀሩት፣ የአትሌቲኮ ሚኔሮው ግብ ጠባቂ ኤቨርሰን የክሩዜሮውን አማካይ ክርስቲያንን መሬት ላይ ዘርሮ በጉልበቱ ደረቱ ላይ መውጣቱ ሁኔታውን ወደ አመጽ ቀይሮታል። ይህን ተከትሎ ተቀያሪ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ወደ ሜዳ በመፍለቃቸው ሜዳው የቦክስ መድረክ መስሏል። ሁኔታው ከቁጥጥር ውጪ በመሆኑ ወታደራዊ ፖሊሶች ሳይቀሩ ጣልቃ ለመግባት ተገደዋል።
🟥 የካርድ ናዳው
ዳኛው ማቲውስ ዴልጋዶ በግርግሩ ወቅት ካርድ ባያሳዩም፣ ከጨዋታው በኋላ በቪዲዮ (VAR) በመታገዝ በወሰዱት እርምጃ የሚከተሉት ተቀጥተዋል፦
* ከክሩዜሮ፦ የድሉን ግብ ያስቆጠረው ካዮ ጆርጅን ጨምሮ 12 ተጫዋቾች።
* ከአትሌቲኮ ሚኔሮ፦ አንጋፋው ሁልክ እና ሬናን ሎዲን ጨምሮ 11 ተጫዋቾች።
🏆 የድልና የውርደት ድብልቅ
አሰልጣኝ ቲቴ የሚመሩት ክሩዜሮዎች በካዮ ጆርጅ ግብ 1 ለ 0 አሸንፈው ከ2019 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የክልሉ ሻምፒዮን መሆን ቢችሉም፣ ድሉ በጸጸት የታጀበ ሆኗል። ኮከቡ ሁልክ ድርጊቱን "ለዓለም የምናሳየው መጥፎ ምስል ነው" ሲል ኮንኖታል።
በአሁኑ ወቅት ሁለቱም ክለቦች በብራዚል ሴሪ አ (Serie A) የደረጃ ሰንጠረዥ ግርጌ ላይ (17ኛ እና 19ኛ) የሚገኙ ሲሆን፣ ይህ የዲሲፕሊን እርምጃ በቀጣይ ጉዟቸው ላይ ተጨማሪ ፈተና እንደሚሆንባቸው ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #brazilfootball #cruzeiro #atleticomineiro #redcardrecord #footballnews #tite #hulk #sportsviolence #soccerupdates #campeonatomineiro
Comments