6 hours ago
የቀብር ሥነ-ሥርዓት መርሃ-ግብር
(ሰኞ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም — ቢሾፍቱ)
#ethiopia | ለኢንጂነር ያደሳ እምሩ አጋ ዕረፍት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን እየገለጽን፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።
የጸሎት እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት:
ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በደብረ ዘይት መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን
ግብዓተ መሬት:
ከቀኑ 7:30 ሰዓት በቃጂማ መካነ ኢየሱስ መካነ መቃብር
"የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
— መዝሙረ ዳዊት 116፥15
እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በገነት ያኑር፤ ለቤተሰቡና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥ።
(ሰኞ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም — ቢሾፍቱ)
#ethiopia | ለኢንጂነር ያደሳ እምሩ አጋ ዕረፍት የተሰማንን ጥልቅ ኀዘን እየገለጽን፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።
የጸሎት እና የሽኝት ሥነ-ሥርዓት:
ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በደብረ ዘይት መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን
ግብዓተ መሬት:
ከቀኑ 7:30 ሰዓት በቃጂማ መካነ ኢየሱስ መካነ መቃብር
"የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።"
— መዝሙረ ዳዊት 116፥15
እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በገነት ያኑር፤ ለቤተሰቡና ለወዳጆቹም መፅናናትን ይስጥ።
2 days ago
ሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ኩባንያዎቹ ምን እየሰሩ ነው?
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
3 days ago
አዲሱ ተርሚናል የአማራ ክልልን ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት በማበልፀግ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፦ አቶ መስፍን ጣሰው
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
Sponsored by
Surafel
4 days ago
የኢትዮጵያ ትንሳኤ !
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብስራት አድማስ እና የዓለም ዓይኖች ማረፊያ እየሆነች ትገኛለች።
እሷ የታሪክ እምብርት፣ የሰው ዘር መገኛ እና የነፃነት ማኅተም ናት። ዛሬ ደግሞ በልጆቿ ጽናት እና በማይበገረው ህዝባዊ ወኔያቸው አዲስ የትንሳኤ ምዕራፍ እየተቀኘች ትገኛለች።
ይህ የትንሳኤ ብርሃን ለራሷ ብቻ ሳይሆን፣ ለመላው ጥቁር ህዝብ እና ለአፍሪካ አህጉር አዲስ የብስራት አድማስ እየቀደደ ነው።
የዚህች ታላቅ ሀገር ትንሳኤ ከባዶ የተነሳ ሳይሆን፣ ከጥንታዊው የክብር ሥርዓቷ እና ካልተደፈረው ማንነቷ የተቀዳ ነው። አፍሪካ በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ሥር በነበረችበት የጨለማ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ብቸኛ ፋኖስ ሆና እንዳበራች ሁሉ፣ ዛሬም ያ የወርቃማ ታሪክ በዘመናዊው ትውልድ ልብ ውስጥ እንደገና እየተቀጣጠለ ይገኛል።
በመሆኑም ይህች የአናብስት ምድር የገጠሟትን ዘመናዊ ፈተናዎች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎች እና ማህበራዊ ውጣ ውረዶች በራሷ ልጆች ጥረት እና ጥንካሬ እያሸነፈች ትገኛለች።
የኢትዮጵያ ህዝብ ታታሪነቱ፣ ለነጻነት ቀናኢነቱ፣ የማይበገረው ፅናቱ እና ለሀገሩ ያለው ጥልቅ ፍቅር አዲሱን የትንሳኤ መንገድ እያቀናው ነው።
በዚህ ጽናት ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ትንሳኤ የመላው አፍሪካም ትንሳኤ ነው። አፍሪካ ለዘመናት የድህነት፣ የጦርነት እና የተስፋ መቁረጥ ምድር ተደርጋ በምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ስትሳል ብትኖርም፤ ኢትዮጵያ ይህንን የተሳሳተ ትረካ በተግባር እየቀየረችው ትገኛለች።
ከኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እስከ ቢሾፍቱ የአውሮፕላን ማረፊያ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶቿ፣ በአረንጓዴ ዐሻራዋ እና በኢኮኖሚ መነቃቃቷ አህጉራዊ ተምሳሌትነቷን በማደስ ላይ ትገኛለች።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ አፍሪካውያን በራሳቸው አቅም ማደግ፣ መበልጸግ እና የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው መወሰን እንደሚችሉ የሚያሳይ ትልቅ የብስራት አድማስ ሆኖ፣ አህጉሪቱ ወደ አዲስ የነፃነት እና የብልጽግና ምዕራፍ እንድትሻገር ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው።
በዚህም የምክንያት ዛሬ የዓለም ዓይኖች ወደ እሷ እየተመለከቱ ነው። በዓለም ከሚታወቁት ግዙፍ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው የአሜሪካው ሲኤንኤን የሰሞኑ ዘገባው ይህን ያመለክታል። ይህ ዘገባ የአድናቆት እና የግርምት እይታ ነው።
በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በአቪየሽን እንዲሁም አጠቃላይ በልማት እያስመዘገበቸው ያለውን ዕምርታ በጥልቀት የዳሰሰው ሚዲያው የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ ያሳዬ ነበር፡፡ በዚህም ሀገራችን የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን እና ቱሪስቶች ቀልብ ስባለች።
ሰፊው የገበያ እምቅ አቅሟ እና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ የዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል እያደረጋት ሲሆን ፤ ከተፈጥሮ ውበቷ እስከ ጥንታዊ ስልጣኔዎቿ፣ ከላሊበላ እስከ አክሱም ዘመናትን የተሸገሩ ቅርሶቿ ደግሞ ዓለምን ማስደመማቸውን ቀጥለዋል።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ የሩቅ ህልም ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታ እየሆነ የመጣ ተጨባጭ ክስተት ነው። በራሷ ውስጣዊ ዕምቅ አቅም፣ በህዝቦቿ ላብ እና ጥረት የምታስመዘግበው ስኬት የዓለምን መድረክ እየማረከ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ትናንት የነፃነት ምልክት እንደነበረች ሁሉ፤ ዛሬ ደግሞ የብልጽግና እና የብስራት አድማስ ሆና በዓለም ፊት በኩራት ቆማለች ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ የብስራት አድማስ እና የዓለም ዓይኖች ማረፊያ እየሆነች ትገኛለች።
እሷ የታሪክ እምብርት፣ የሰው ዘር መገኛ እና የነፃነት ማኅተም ናት። ዛሬ ደግሞ በልጆቿ ጽናት እና በማይበገረው ህዝባዊ ወኔያቸው አዲስ የትንሳኤ ምዕራፍ እየተቀኘች ትገኛለች።
ይህ የትንሳኤ ብርሃን ለራሷ ብቻ ሳይሆን፣ ለመላው ጥቁር ህዝብ እና ለአፍሪካ አህጉር አዲስ የብስራት አድማስ እየቀደደ ነው።
የዚህች ታላቅ ሀገር ትንሳኤ ከባዶ የተነሳ ሳይሆን፣ ከጥንታዊው የክብር ሥርዓቷ እና ካልተደፈረው ማንነቷ የተቀዳ ነው። አፍሪካ በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ሥር በነበረችበት የጨለማ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ብቸኛ ፋኖስ ሆና እንዳበራች ሁሉ፣ ዛሬም ያ የወርቃማ ታሪክ በዘመናዊው ትውልድ ልብ ውስጥ እንደገና እየተቀጣጠለ ይገኛል።
በመሆኑም ይህች የአናብስት ምድር የገጠሟትን ዘመናዊ ፈተናዎች፣ የኢኮኖሚ ጫናዎች እና ማህበራዊ ውጣ ውረዶች በራሷ ልጆች ጥረት እና ጥንካሬ እያሸነፈች ትገኛለች።
የኢትዮጵያ ህዝብ ታታሪነቱ፣ ለነጻነት ቀናኢነቱ፣ የማይበገረው ፅናቱ እና ለሀገሩ ያለው ጥልቅ ፍቅር አዲሱን የትንሳኤ መንገድ እያቀናው ነው።
በዚህ ጽናት ላይ የተገነባው የኢትዮጵያ ትንሳኤ የመላው አፍሪካም ትንሳኤ ነው። አፍሪካ ለዘመናት የድህነት፣ የጦርነት እና የተስፋ መቁረጥ ምድር ተደርጋ በምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ስትሳል ብትኖርም፤ ኢትዮጵያ ይህንን የተሳሳተ ትረካ በተግባር እየቀየረችው ትገኛለች።
ከኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ እስከ ቢሾፍቱ የአውሮፕላን ማረፊያ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶቿ፣ በአረንጓዴ ዐሻራዋ እና በኢኮኖሚ መነቃቃቷ አህጉራዊ ተምሳሌትነቷን በማደስ ላይ ትገኛለች።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ አፍሪካውያን በራሳቸው አቅም ማደግ፣ መበልጸግ እና የራሳቸውን ዕድል በራሳቸው መወሰን እንደሚችሉ የሚያሳይ ትልቅ የብስራት አድማስ ሆኖ፣ አህጉሪቱ ወደ አዲስ የነፃነት እና የብልጽግና ምዕራፍ እንድትሻገር ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች ነው።
በዚህም የምክንያት ዛሬ የዓለም ዓይኖች ወደ እሷ እየተመለከቱ ነው። በዓለም ከሚታወቁት ግዙፍ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው የአሜሪካው ሲኤንኤን የሰሞኑ ዘገባው ይህን ያመለክታል። ይህ ዘገባ የአድናቆት እና የግርምት እይታ ነው።
በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በአቪየሽን እንዲሁም አጠቃላይ በልማት እያስመዘገበቸው ያለውን ዕምርታ በጥልቀት የዳሰሰው ሚዲያው የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ ያሳዬ ነበር፡፡ በዚህም ሀገራችን የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን እና ቱሪስቶች ቀልብ ስባለች።
ሰፊው የገበያ እምቅ አቅሟ እና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጧ የዓለም አቀፍ የንግድ ማዕከል እያደረጋት ሲሆን ፤ ከተፈጥሮ ውበቷ እስከ ጥንታዊ ስልጣኔዎቿ፣ ከላሊበላ እስከ አክሱም ዘመናትን የተሸገሩ ቅርሶቿ ደግሞ ዓለምን ማስደመማቸውን ቀጥለዋል።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ የሩቅ ህልም ሳይሆን የዕለት ተዕለት እውነታ እየሆነ የመጣ ተጨባጭ ክስተት ነው። በራሷ ውስጣዊ ዕምቅ አቅም፣ በህዝቦቿ ላብ እና ጥረት የምታስመዘግበው ስኬት የዓለምን መድረክ እየማረከ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ትናንት የነፃነት ምልክት እንደነበረች ሁሉ፤ ዛሬ ደግሞ የብልጽግና እና የብስራት አድማስ ሆና በዓለም ፊት በኩራት ቆማለች ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
4 days ago
ከቡና ባሻገር፦ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ትኩረት ውስጥ
#ethiopia | የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የዜና አውታር CNN በ«Connecting Africa» ፕሮግራሙ ላይ ኢትዮጵያ ከቡና ባሻገር እየገነባችው ስላለው አዲስ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ሰፊ ዘገባ አቅርቧል።
ዘገባው የቡና ታሪካዊ ሚናን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ ዛሬ በወርቅ፣ በኃይል ልማት፣ በአቪዬሽን እና በግዙፍ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ እየከፈተች መሆኑን ያሳያል።
በዘመናዊ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ታሪክ ለብዙ ዓመታት ቡና ዋናው የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ነበር። ይሁን እንጂ ባለፈው ዓመት ወርቅ በውጭ ገቢ ቡናን በመብለጥ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱ የኢኮኖሚው እየተለዋወጠ መምጣቱን ያመለክታል።
ወርቅ፤ አዲሱ የውጭ ምንዛሬ ኃይል
የሲኤንኤን ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘውን የኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ጎብኝታለች። ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፈሰሰበት ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ትልልቅ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ሲሆን፣ በዓመት 9 ቶን ወርቅ የማምረት አቅም እንዳለው ተገልጿል። ፕሮጀክቱ በዓመት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እንደሚያመጣ ይጠበቃል።
ይህ እድገት ሌሎች ዓለም አቀፍ የማዕድን ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ እምነት እየፈጠረ መሆኑም ተጠቅሷል።
የህዳሴ ግድብ፤ የኃይልና የክልላዊ ትስስር ማዕከል
CNN በዘገባው ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በስፋት አስተውሏል። ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን በማሳደግ ኢንዱስትሪን ለማጠናከር፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት ኃይል በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት እና የክልል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና እንዳለው አመልክቷል።
ቢሾፍቱ አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ
ዘገባው በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለውን ግዙፍ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያም በሰፊው ያቀረበ ሲሆን፣ ይህ ፕሮጀክት 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የአፍሪካ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት እንደሆነ ገልጿል። የመጀመሪያ ደረጃው 60 ሚሊዮን ተሳፋሪዎችን በዓመት የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 110 ሚሊዮን ተሳፋሪዎችን በዓመት የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም ኢትዮጵያን የአፍሪካ ዋና የአቪዬሽን ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው።
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የሚሉት
ከCNN ባሻገር ሌሎች ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችም ኢትዮጵያ በወርቅ፣ በኃይል፣ በአቪዬሽን እና በመሠረተ ልማት እያደረገች ያለውን ለውጥ በተደጋጋሚ እየዘገቡ ነው። ትኩረታቸውም ኢትዮጵያ ከባህላዊ የቡና ኢኮኖሚ ወደ የተለያዩ የገቢ ምንጮች የተመሰረተ ኢኮኖሚ እየተሸጋገረች መሆኗን ያሳያል።
መደምደሚያ
ቡና አሁንም የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መለያ ሆኖ ቢቀጥልም፣ የወርቅ ማዕድን፣ የህዳሴ ግድብ፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደ አዲስ አቅጣጫ እየመሩት እንደሆነ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እያመለከቱ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች በተሳካ ሁኔታ ከተጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የአቪዬሽን እና የኃይል ማዕከል የመሆን እድሏን የበለጠ ታጠናክራለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የአሜሪካው ዓለም አቀፍ የዜና አውታር CNN በ«Connecting Africa» ፕሮግራሙ ላይ ኢትዮጵያ ከቡና ባሻገር እየገነባችው ስላለው አዲስ የኢኮኖሚ አቅጣጫ ሰፊ ዘገባ አቅርቧል።
ዘገባው የቡና ታሪካዊ ሚናን በመጥቀስ፣ ኢትዮጵያ ዛሬ በወርቅ፣ በኃይል ልማት፣ በአቪዬሽን እና በግዙፍ መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ያተኮረ አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ እየከፈተች መሆኑን ያሳያል።
በዘመናዊ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ታሪክ ለብዙ ዓመታት ቡና ዋናው የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ነበር። ይሁን እንጂ ባለፈው ዓመት ወርቅ በውጭ ገቢ ቡናን በመብለጥ አዲስ ምዕራፍ መክፈቱ የኢኮኖሚው እየተለዋወጠ መምጣቱን ያመለክታል።
ወርቅ፤ አዲሱ የውጭ ምንዛሬ ኃይል
የሲኤንኤን ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባዲሪ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘውን የኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ጎብኝታለች። ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፈሰሰበት ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ትልልቅ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ሲሆን፣ በዓመት 9 ቶን ወርቅ የማምረት አቅም እንዳለው ተገልጿል። ፕሮጀክቱ በዓመት ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እንደሚያመጣ ይጠበቃል።
ይህ እድገት ሌሎች ዓለም አቀፍ የማዕድን ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ እምነት እየፈጠረ መሆኑም ተጠቅሷል።
የህዳሴ ግድብ፤ የኃይልና የክልላዊ ትስስር ማዕከል
CNN በዘገባው ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በስፋት አስተውሏል። ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን በማሳደግ ኢንዱስትሪን ለማጠናከር፣ ወደ ጎረቤት ሀገራት ኃይል በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት እና የክልል ኢኮኖሚያዊ ትስስርን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና እንዳለው አመልክቷል።
ቢሾፍቱ አዲሱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ
ዘገባው በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለውን ግዙፍ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያም በሰፊው ያቀረበ ሲሆን፣ ይህ ፕሮጀክት 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት የአፍሪካ ትልቁ የአቪዬሽን መሠረተ ልማት እንደሆነ ገልጿል። የመጀመሪያ ደረጃው 60 ሚሊዮን ተሳፋሪዎችን በዓመት የሚያስተናግድ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ 110 ሚሊዮን ተሳፋሪዎችን በዓመት የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። ይህም ኢትዮጵያን የአፍሪካ ዋና የአቪዬሽን ማዕከል ለማድረግ ያለመ ነው።
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የሚሉት
ከCNN ባሻገር ሌሎች ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችም ኢትዮጵያ በወርቅ፣ በኃይል፣ በአቪዬሽን እና በመሠረተ ልማት እያደረገች ያለውን ለውጥ በተደጋጋሚ እየዘገቡ ነው። ትኩረታቸውም ኢትዮጵያ ከባህላዊ የቡና ኢኮኖሚ ወደ የተለያዩ የገቢ ምንጮች የተመሰረተ ኢኮኖሚ እየተሸጋገረች መሆኗን ያሳያል።
መደምደሚያ
ቡና አሁንም የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ መለያ ሆኖ ቢቀጥልም፣ የወርቅ ማዕድን፣ የህዳሴ ግድብ፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደ አዲስ አቅጣጫ እየመሩት እንደሆነ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እያመለከቱ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች በተሳካ ሁኔታ ከተጠናቀቁ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የአቪዬሽን እና የኃይል ማዕከል የመሆን እድሏን የበለጠ ታጠናክራለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
4 days ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
5 days ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአቪየሽን ዘርፍ መሪነቷን እንደታጠናክር ያስችላታል - ሲኤንኤን
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
***********************
የዓለማችን ታዋቂው የዜና መረብ ሲኤንኤን (CNN) "ኮኔክቲንግ አፍሪካ" በተሰኘው ዝነኛ ፕሮግራሙ፣ የአፍሪካ የአቪዬሽን መሪ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ እየመራው ያለውን ታላቅ የመሠረተ ልማት፣ የኢኮኖሚ እና የቱሪዝም እምርታ በሰፊው ዳስሷል።
ዘገባው እንደ አመላከተው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአህጉሪቱ ምሳሌ የሚሆን የዕድገት ሞተር ከመሆኑም በላይ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ ትስስር ማዕከል በማድረግ ረገድ ወደ አዲስ እየተሸጋገረ ይገኛል።
ዘገባው ኢትዮጵያ የአቪዬሽን ዘርፏን ዘመናዊ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣናን (AfCFTA) ተግባራዊነት በማፋጠን እና የተፈጥሮ ሀብቶቿን ለዓለም አስተዋውቃ የቱሪዝም አቅሟን በመገንባት በኩል እያከናወነቻቸው ያሉትን ዐበይት ተግባራት በስፋት አሳይቷል።
በዘገባው ጎልተው ከተካተቱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል በ12.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ግንባታው የተጀመረው እና በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሜጋ ፕሮጀክት ቀዳሚው ነው።
ይህ ዘመናዊ የአቪዬሽን መንደር የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ በዓመት እስከ 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ እና 4 ሚሊዮን ቶን ካርጎ የማጓጓዝ ከፍተኛ አቅም ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ከሲኤንኤን ዘጋቢ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ አዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ አፍሪካውያንን እርስ በእርስ በማስተሳሰር ረገድ የመሪነት ሚናውን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በተጨማሪም አየር መንገዱ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጣናን ስኬታማ ለማድረግ እና አህጉራዊ የንግድ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ቁልፍ ሞተር መሆኑን አስረድተዋል።
በዘገባው ላይ እንደተጠቆመው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሀብቶች ለዓለም አቀፍ እና ለአህጉራችን ጎብኚዎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመናዊ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ ደረጃቸውን የጠበቁ የማረፊያ ስፍራዎች እና አዳዲስ የመንገድ ዝርጋታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ይህም ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ የምታገኘውን የኢኮኖሚ ጥቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
የሲኤንኤን ዘገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአቪዬሽን ዘርፍ እያመጣ ያለውን ብሩህ ተስፋ እና በአቪዬሽን መሠረተ ልማት አህጉራዊ መሪነቷን በጽኑ የምታረጋግጥበትን የልማት ጉዞ በግልጽ ያሳየ ነው።
የአፍሪካ ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሀገራችን የአህጉሪቱ ዋና የንግድ፣ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ መገናኛ ማዕከል በማድረግ ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #bishoftuairport #ethiopianairlines #connectingafrica #cnn
6 days ago
የቢሾፍቱው ግዙፍ ኤርፖርት የገንዘብ ድጋፍ ማጽደቅ ስምንት ወራት ይፈጃል ተባለ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚገነባው አዲስ ሜጋ ኤርፖርት የሚያስፈልገውን የቢሊዮን ዶላር ብድር የማጽደቅ ሂደት ስምንት ወራት እንደሚፈጅና እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።
አየር መንገዱ የመሬት መንጥር እና የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት፣ የግንባታ ተቋራጮች ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቃቸው የኮንትራክተሮች መረጣ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከነሐሴ ወር ወደ መጪው ጥር መራዘሙን አስረድተዋል።
Via capital
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚገነባው አዲስ ሜጋ ኤርፖርት የሚያስፈልገውን የቢሊዮን ዶላር ብድር የማጽደቅ ሂደት ስምንት ወራት እንደሚፈጅና እስከ መጋቢት 2019 ዓ.ም ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስታወቀ።
አየር መንገዱ የመሬት መንጥር እና የተፈናቀሉ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ስራዎች በከፍተኛ ሁኔታ መጠናቀቃቸውን ገልጿል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት፣ የግንባታ ተቋራጮች ተጨማሪ ጊዜ በመጠየቃቸው የኮንትራክተሮች መረጣ ማጠናቀቂያ ጊዜ ከነሐሴ ወር ወደ መጪው ጥር መራዘሙን አስረድተዋል።
Via capital
9 days ago
በቢሾፍቱ ከተማ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተከሉ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከጤና ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር «ጤናማ ምግብ ለአስተማማኝ ህይወት፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ ትውልድ!» በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ አድራጎት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የኮፕ 32 (COP 32) አየር ንብረት ጉባኤን ከማገዝ ባሻገር አገር በቀል፣ ፍራፍሬ እና ለመድኃኒትነት የሚውሉ ተክሎችን በመትከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዕለቱም ከሰባት ነጥብ አንድ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከምግብነት ባለፈ ለመድኃኒትነት ጭምር የሚጠቅሙ እንደ ማንጎ እና አቮካዶ ያሉ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄራን ገርባ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን አቅም ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን በምታደርገው ጥረት ውስጥ የመድኃኒትነት እጽዋትን መንከባከብ ትልቅ ድርሻ አለው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ለዕድገታቸው ተገቢውን ቋሚ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ይህንን አረንጓዴ ልማት ከምርምርና ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅምን ለማጠናከር እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በበኩላቸው፣ የጤና ሴክተሩ በበጎ ፈቃደኝነት መርሃ ግብሩ አጠቃላይ ከሁለት መቶ ኃምሳ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን አንስተዋል።
ከአዲስ አበባ እስከ ቢሾፍቱ ባለው የፍጥነት መንገድ ዳርቻ የተጀመረው ይህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከአንድ ዓመት በኋላ ከፍተኛ የእጽዋት ሽፋን እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ የተተከሉትን ችግኞች በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ለታለመለት ዓላማ ማብቃት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#greenlegacyethiopia#ethiopia
#bishoftu #climateaction #healthylife
#cop32 #healthsector #treeplanting
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከጤና ሚኒስቴር እና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመተባበር «ጤናማ ምግብ ለአስተማማኝ ህይወት፣ አረንጓዴ ልማት ለነገ ትውልድ!» በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ አድራጎት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቢሾፍቱ ከተማ አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የባለሥልጣኑ ሠራተኞች የተገኙ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የኮፕ 32 (COP 32) አየር ንብረት ጉባኤን ከማገዝ ባሻገር አገር በቀል፣ ፍራፍሬ እና ለመድኃኒትነት የሚውሉ ተክሎችን በመትከል የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች ተከናውነዋል።
በዕለቱም ከሰባት ነጥብ አንድ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ከምግብነት ባለፈ ለመድኃኒትነት ጭምር የሚጠቅሙ እንደ ማንጎ እና አቮካዶ ያሉ ከአምስት ሺህ በላይ ችግኞች ተተክለዋል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄራን ገርባ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ መድኃኒት አምራቾችን አቅም ለማሳደግ እና የጥሬ ዕቃ አቅርቦትን በራስ አቅም ለመሸፈን በምታደርገው ጥረት ውስጥ የመድኃኒትነት እጽዋትን መንከባከብ ትልቅ ድርሻ አለው።
ችግኞችን ከመትከል ባለፈ ለዕድገታቸው ተገቢውን ቋሚ እንክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ፣ ይህንን አረንጓዴ ልማት ከምርምርና ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር የሀገር ውስጥ መድኃኒት ማምረት አቅምን ለማጠናከር እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በበኩላቸው፣ የጤና ሴክተሩ በበጎ ፈቃደኝነት መርሃ ግብሩ አጠቃላይ ከሁለት መቶ ኃምሳ ሺህ በላይ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን አንስተዋል።
ከአዲስ አበባ እስከ ቢሾፍቱ ባለው የፍጥነት መንገድ ዳርቻ የተጀመረው ይህ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከአንድ ዓመት በኋላ ከፍተኛ የእጽዋት ሽፋን እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ የተተከሉትን ችግኞች በባለቤትነት ስሜት በመንከባከብ ለታለመለት ዓላማ ማብቃት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#greenlegacyethiopia#ethiopia
#bishoftu #climateaction #healthylife
#cop32 #healthsector #treeplanting
Sponsored by
Surafel
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዋሽንግተን በአፍሪካ ያላትን የመሰረተ ልማት እና የኢንቨስትመንት ተጽእኖ ከቻይና እና ሌሎች ኃያላን ሀገራት ጋር እያወዳደረች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፣ አሜሪካ ኩባንያዎቿ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚገነባው የ12.5 ቢሊዮን ዶላሩ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ ሚና እንዲኖራቸው እንደምትፈልግ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ የንግድ ሚኒስቴር ባለስልጣን ረቡዕ ዕለት አስታወቁ።
በመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ የአሜሪካ የንግድ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በአየር ማረፊያው ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካን ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቅርበት እየሰራች ነው። ሚቼል ይህንን የተናገሩት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስ እና ኮሙዩኒኬሽን ሲምፖዚየም ላይ በበይነ-መረብ በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል። የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ ምን ዓይነት ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ በግልጽ ባያስቀምጡም፣ ይህ ተሳትፎ በጄኔራል ኤሌክትሪክ ሞተሮች የሚሰሩ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖችን ወደ መግዛት ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል። አየር መንገዱ ባለፈው ሚያዝያ ወር ቀደም ሲል ካዘዛቸው 20 ጄቶች በተጨማሪ ስድስት ተጨማሪ የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለመግዛት መስማማቱ ይታወሳል።
ከአዲስ አበባ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ የሚገኘው እና ባለ አራት የመሮጫ መንገድ ያለው ይህ የአየር ማረፊያ ግንባታ ባለፈው ጥር ወር የተጀመረ ሲሆን፣ በ2030 ሲጠናቀቅ "የአፍሪካ ዱባይ" ለማድረግ የታለመ ነው። ለዚህ ግዙፍ ፕሮጀክት የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላር የገባ ሲሆን፣ ቀሪውን 8.7 ቢሊዮን ዶላር የማፈላለጉን ጥረት እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባለፈው ሚያዝያ ወር እንደተናገሩት፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሚቼል፣ የአሜሪካን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ጥረት አካል በመሆን የንግድ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ የአሜሪካ የንግድ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በአየር ማረፊያው ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካን ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቅርበት እየሰራች ነው። ሚቼል ይህንን የተናገሩት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስ እና ኮሙዩኒኬሽን ሲምፖዚየም ላይ በበይነ-መረብ በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል። የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ ምን ዓይነት ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ በግልጽ ባያስቀምጡም፣ ይህ ተሳትፎ በጄኔራል ኤሌክትሪክ ሞተሮች የሚሰሩ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖችን ወደ መግዛት ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል። አየር መንገዱ ባለፈው ሚያዝያ ወር ቀደም ሲል ካዘዛቸው 20 ጄቶች በተጨማሪ ስድስት ተጨማሪ የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለመግዛት መስማማቱ ይታወሳል።
ከአዲስ አበባ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ የሚገኘው እና ባለ አራት የመሮጫ መንገድ ያለው ይህ የአየር ማረፊያ ግንባታ ባለፈው ጥር ወር የተጀመረ ሲሆን፣ በ2030 ሲጠናቀቅ "የአፍሪካ ዱባይ" ለማድረግ የታለመ ነው። ለዚህ ግዙፍ ፕሮጀክት የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላር የገባ ሲሆን፣ ቀሪውን 8.7 ቢሊዮን ዶላር የማፈላለጉን ጥረት እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባለፈው ሚያዝያ ወር እንደተናገሩት፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሚቼል፣ የአሜሪካን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ጥረት አካል በመሆን የንግድ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።
12 days ago
የዓድዋ ገድል በአረንጓዴ አሻራ ሲደገም
*****************
በኢትዮጵያ እየተተገበረ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገርን የተፈጥሮ ሀብት ከመጠበቅ ባሻገር፣ ሉዓላዊነትን የማስከበር ዋነኛ ማሳያ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ሉዓላዊነት በሁለት መንገዶች ሊደፈር እንደሚችል ማንሳታቸው ይታወሳል።
የመጀመሪያው በውጭ ወራሪ ሀይል በኩል ድንበር ጥሶ በመግባት የሚፈጸም ሲሆን፤ ይህንንም ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ጦርነትና በሌሎችም አውዶች በደም መስዋዕትነት አስጠብቀዋል።
ሁለተኛውና ጸጥተኛው የሉዓላዊነት መደፈር ግን፣ እንደ አፈር ያለ ወደፊት በቀላሉ የማይተካ ውድ የተፈጥሮ ሀብት በጎርፍና በመሸርሸር ድንበር አቋርጦ ሲወጣ የሚከሰት ነው።
የሚሸረሸር አፈር፣ የሚደርቅ ሀይቅ፣ የሚጠፋ ደን፣ እንዲሁም የሚመናመን የምግብ ዋስትና በዝምታ የሚፈጸሙ የሉዓላዊነት መሸርሸር ማሳያዎች ናቸው።
ለዘመናት በውሃና በንፋስ ምክንያት ሲጠፋ የነበረው ለም አፈር የገበሬውን ምርት፣ የምግብ ዋስትናን፣ የወደፊቱን ኢኮኖሚ እንዲሁም የትውልድን ተስፋ አብሮ ይዞ የሚወጣ በመሆኑ፤ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ይህንን ጸጥተኛ ወረራ የመቀልበስ ሀገራዊ ስትራቴጂ ሆኖ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸውን እንደ ቡና፣ አቮካዶ፣ ማካዴሚያ፣ ካካዎ እና ሮማን የመሳሰሉ ሰብሎችን በማስፋፋት ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ሀይቆች ሲያገግሙ፣ አእዋፋት ወደ መኖሪያቸው ሲመለሱና ደኖች ሲለሙ ለኢኮ-ቱሪዝም መስፋፋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ሲሆን ይህም በዜጎች ገቢና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ያስችላል።
የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የተጀመረባት ቢሾፍቱ፣ እስከ አዋሽ ያለው ቀጠና የሀይቆች ስርዓት የአእዋፍ ብዝሃ ሕይወትና የተፈጥሮ ገጽታ ለኢኮ ቱሪዝም ትልቅ እምቅ አቅም እንዳለው ያሳያል። ተፈጥሮ ሲጠበቅ ቱሪዝም ያድጋል፤ ቱሪዝም ሲያድግ ደግሞ ለዜጎች ሥራ፣ ገቢና ኢኮኖሚያዊ እድል ይፈጥራል።
ትውልድ በታሪክ የሚታወሰው የሠራው ስራ በሚያስቀረው ውርስ ነው። የዓድዋ ትውልድ ነፃነትን አውርሶናል፤ የዛሬው ትውልድ ደግሞ አረንጓዴ ኢትዮጵያን የመተው ኃላፊነት አለበት። የሚተከለው ችግኝ ዛሬ ትንሽ ቢመስልም ነገ የልጆቻችን ጥላ፣ ሀብት፣ ምግብ፣ ቱሪዝምና የአገር ክብር ይሆናል።
የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ የችግኝ ተከላ ብቻ አይደለም፤ የሉዓላዊነት ጥበቃ፣ የኢኮኖሚ ማንሰራራት፣ የምግብ ዋስትና፣ የቱሪዝም እድገት፣ የአካባቢ ጥበቃና የትውልድ ውርስ በአንድ ላይ የሚገናኙበት ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው።
የአባቶቻችን ገድል ነፃነትን አስጠብቆልናል፤ የዛሬው አረንጓዴ ገድል ደግሞ ያንን ነፃነት በለምለም ምድር፣ በበለጸገ ኢኮኖሚና በዘላቂ ልማት ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።
በልዩ እሸቱ
*****************
በኢትዮጵያ እየተተገበረ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገርን የተፈጥሮ ሀብት ከመጠበቅ ባሻገር፣ ሉዓላዊነትን የማስከበር ዋነኛ ማሳያ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ሉዓላዊነት በሁለት መንገዶች ሊደፈር እንደሚችል ማንሳታቸው ይታወሳል።
የመጀመሪያው በውጭ ወራሪ ሀይል በኩል ድንበር ጥሶ በመግባት የሚፈጸም ሲሆን፤ ይህንንም ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ጦርነትና በሌሎችም አውዶች በደም መስዋዕትነት አስጠብቀዋል።
ሁለተኛውና ጸጥተኛው የሉዓላዊነት መደፈር ግን፣ እንደ አፈር ያለ ወደፊት በቀላሉ የማይተካ ውድ የተፈጥሮ ሀብት በጎርፍና በመሸርሸር ድንበር አቋርጦ ሲወጣ የሚከሰት ነው።
የሚሸረሸር አፈር፣ የሚደርቅ ሀይቅ፣ የሚጠፋ ደን፣ እንዲሁም የሚመናመን የምግብ ዋስትና በዝምታ የሚፈጸሙ የሉዓላዊነት መሸርሸር ማሳያዎች ናቸው።
ለዘመናት በውሃና በንፋስ ምክንያት ሲጠፋ የነበረው ለም አፈር የገበሬውን ምርት፣ የምግብ ዋስትናን፣ የወደፊቱን ኢኮኖሚ እንዲሁም የትውልድን ተስፋ አብሮ ይዞ የሚወጣ በመሆኑ፤ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ይህንን ጸጥተኛ ወረራ የመቀልበስ ሀገራዊ ስትራቴጂ ሆኖ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸውን እንደ ቡና፣ አቮካዶ፣ ማካዴሚያ፣ ካካዎ እና ሮማን የመሳሰሉ ሰብሎችን በማስፋፋት ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ሀይቆች ሲያገግሙ፣ አእዋፋት ወደ መኖሪያቸው ሲመለሱና ደኖች ሲለሙ ለኢኮ-ቱሪዝም መስፋፋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ሲሆን ይህም በዜጎች ገቢና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ያስችላል።
የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የተጀመረባት ቢሾፍቱ፣ እስከ አዋሽ ያለው ቀጠና የሀይቆች ስርዓት የአእዋፍ ብዝሃ ሕይወትና የተፈጥሮ ገጽታ ለኢኮ ቱሪዝም ትልቅ እምቅ አቅም እንዳለው ያሳያል። ተፈጥሮ ሲጠበቅ ቱሪዝም ያድጋል፤ ቱሪዝም ሲያድግ ደግሞ ለዜጎች ሥራ፣ ገቢና ኢኮኖሚያዊ እድል ይፈጥራል።
ትውልድ በታሪክ የሚታወሰው የሠራው ስራ በሚያስቀረው ውርስ ነው። የዓድዋ ትውልድ ነፃነትን አውርሶናል፤ የዛሬው ትውልድ ደግሞ አረንጓዴ ኢትዮጵያን የመተው ኃላፊነት አለበት። የሚተከለው ችግኝ ዛሬ ትንሽ ቢመስልም ነገ የልጆቻችን ጥላ፣ ሀብት፣ ምግብ፣ ቱሪዝምና የአገር ክብር ይሆናል።
የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ የችግኝ ተከላ ብቻ አይደለም፤ የሉዓላዊነት ጥበቃ፣ የኢኮኖሚ ማንሰራራት፣ የምግብ ዋስትና፣ የቱሪዝም እድገት፣ የአካባቢ ጥበቃና የትውልድ ውርስ በአንድ ላይ የሚገናኙበት ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው።
የአባቶቻችን ገድል ነፃነትን አስጠብቆልናል፤ የዛሬው አረንጓዴ ገድል ደግሞ ያንን ነፃነት በለምለም ምድር፣ በበለጸገ ኢኮኖሚና በዘላቂ ልማት ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።
በልዩ እሸቱ
15 days ago
በቢሾፍቱ የኢትዮ ቴሌኮም የመሰረተ ልማት አውታር ላይ ዘረፋ የፈጸሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ‼️
በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ውስጥ በኢትዮ ቴሌኮም የመሰረተ ልማት አውታር ላይ ዘረፋ የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በእስራት እንዲቀጡ ተወስኗል።የከተማው አቃቤ ሕግ ጽሕፈት ቤት የኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ምርመራ ሂደት እንዳስታወቀው፣ ተከሳሾች ሃሮን ዮሴፍ እና ተገኔ ተሾመ የኢትዮ ቴሌኮም ንብረት የሆኑ የሲሲቲቪ ኬብል ሽቦዎችን ዘርፈው ሊሰወሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ወንጀሉ የተፈጸመው በቢሾፍቱ ከተማ ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ኤረር ወረዳ «ጎልደን ሆቴል» ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ ሰባት ሰዓት ላይ መሆኑ ተገልጿል።ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቤ ሕግ የላከ ሲሆን፣ አቃቤ ሕግም የኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 464/2005 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 4ን በመጥቀስ በቁጥጥር ስር በዋሉት ግለሰቦች ላይ ክስ መስርቶባቸዋል።
ጉዳዩን የተመለከተው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ተከሳሾቹ በሕዝብ መሰረተ ልማት ላይ የፈጸሙት የዘረፋ ወንጀል በአቃቤ ሕግ ማስረጃ በበቂ ሁኔታ በመረጋገጡ እያንዳንዳቸው በ4 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፋል።
Seledadotio
Seledadotio
በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ውስጥ በኢትዮ ቴሌኮም የመሰረተ ልማት አውታር ላይ ዘረፋ የፈጸሙ ሁለት ግለሰቦች በእስራት እንዲቀጡ ተወስኗል።የከተማው አቃቤ ሕግ ጽሕፈት ቤት የኢኮኖሚ ነክ ወንጀሎች ምርመራ ሂደት እንዳስታወቀው፣ ተከሳሾች ሃሮን ዮሴፍ እና ተገኔ ተሾመ የኢትዮ ቴሌኮም ንብረት የሆኑ የሲሲቲቪ ኬብል ሽቦዎችን ዘርፈው ሊሰወሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ወንጀሉ የተፈጸመው በቢሾፍቱ ከተማ ጨለለቃ ክፍለ ከተማ ኤረር ወረዳ «ጎልደን ሆቴል» ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ ሰባት ሰዓት ላይ መሆኑ ተገልጿል።ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ ለአቃቤ ሕግ የላከ ሲሆን፣ አቃቤ ሕግም የኢትዮ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መሰረተ ልማቶችን ለመጠበቅ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 464/2005 አንቀጽ 4 ንኡስ አንቀጽ 4ን በመጥቀስ በቁጥጥር ስር በዋሉት ግለሰቦች ላይ ክስ መስርቶባቸዋል።
ጉዳዩን የተመለከተው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ተከሳሾቹ በሕዝብ መሰረተ ልማት ላይ የፈጸሙት የዘረፋ ወንጀል በአቃቤ ሕግ ማስረጃ በበቂ ሁኔታ በመረጋገጡ እያንዳንዳቸው በ4 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፋል።
Seledadotio
Seledadotio
16 days ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ተቋማዊ ሪፎርም ተጠናክሮ ቀጥሏል
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ በማድረግ ለበርካታ ዓመታት ሲተገብረው የቆየውን ተቋማዊ ሪፎርም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በ2019 በጀት ዓመትም ሪፎርሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትን በቢሾፍቱ ከተማ ለሁለት ቀናት ያካሄደ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን 97 በመቶ ማሳካቱ ተገልጿል። በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በአፈጻጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር የተመዘገቡ ውጤቶችም የተቋሙን የለውጥ ጉዞ እንዳጠናከሩ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን ለማስጠበቅ በተደረጉ የፍርድ ቤት ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።
በውጭ ገበያ መስፋፋትን በተመለከተም፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ የቤት ልማት ፕሮጀክት ለማከናወን ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰውን ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በፕሮጀክቶች ዘርፍ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ ዘመናዊ 3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የመጀመሪያ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በሂደት ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓት መጠናከሩን እና ከደንበኞች ጋር በትብብር የተገነቡ የንግድ ቤቶች ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት መጀመራቸው ተጠቁሟል።
ኮርፖሬሽኑ በ50ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት የተቋሙን የግማሽ ምዕተ ዓመት ታሪክና ስኬቶች የሚያሳዩ መርሃ ግብሮችን ለአራት ተከታታይ ቀናት በድምቀት ማካሄዱ ተገልጿል። ይህም የተቋሙን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ለመቀየር አስተዋጽኦ እንዳደረገ ተጠቅሷል።
በ2019 በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይልና የአሠራር አቅምን ማጠናከር መሆናቸው ተገልጿል።
ኮርፖሬሽኑም እነዚህን ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ለሀገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሁለንተናዊ ሀገራዊ ለውጡን መነሻ በማድረግ ለበርካታ ዓመታት ሲተገብረው የቆየውን ተቋማዊ ሪፎርም በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል አስታውቋል። በ2019 በጀት ዓመትም ሪፎርሙን የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
ኮርፖሬሽኑ የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ውይይትን በቢሾፍቱ ከተማ ለሁለት ቀናት ያካሄደ ሲሆን፣ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎችን 97 በመቶ ማሳካቱ ተገልጿል። በገቢ ዕድገት፣ በቤት ልማት፣ በአፈጻጸም አቅም እና በቤት አስተዳደር የተመዘገቡ ውጤቶችም የተቋሙን የለውጥ ጉዞ እንዳጠናከሩ ተጠቁሟል።
በተጨማሪም የሕዝብና የመንግሥት ጥቅምን ለማስጠበቅ በተደረጉ የፍርድ ቤት ክርክሮች በርካታ ይዞታዎችን ማስመለስ መቻሉ ተገልጿል።
በውጭ ገበያ መስፋፋትን በተመለከተም፣ በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ የቤት ልማት ፕሮጀክት ለማከናወን ከደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያል ስቴት ጋር የተደረሰውን ስምምነት ወደ ተግባር ለማስገባት ሥራዎች በመካሄድ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በፕሮጀክቶች ዘርፍ የፒያሳ እና የጎልድ ሳይት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ አገልግሎት መግባታቸው የተጠቀሰ ሲሆን፣ ዘመናዊ 3ዲ የግንባታ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት የመጀመሪያ የሙከራ ቤቶች ግንባታም በሂደት ላይ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም የቤቶች ቆጠራና የመረጃ ማሰባሰብ ሥራ በመጠናቀቁ ዘመናዊ የቤት አስተዳደር ሥርዓት መጠናከሩን እና ከደንበኞች ጋር በትብብር የተገነቡ የንግድ ቤቶች ወደ ኪራይ አገልግሎት በመግባታቸው ከፍተኛ ገቢ ማስገኘት መጀመራቸው ተጠቁሟል።
ኮርፖሬሽኑ በ50ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓሉ ወቅት የተቋሙን የግማሽ ምዕተ ዓመት ታሪክና ስኬቶች የሚያሳዩ መርሃ ግብሮችን ለአራት ተከታታይ ቀናት በድምቀት ማካሄዱ ተገልጿል። ይህም የተቋሙን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ለመቀየር አስተዋጽኦ እንዳደረገ ተጠቅሷል።
በ2019 በጀት ዓመት የሚተገበሩ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ዘመናዊና ፈጣን የግንባታ ቴክኖሎጂዎችን በስፋት ሥራ ላይ ማዋል፣ የቤት አቅርቦትን ለማሳደግ ሰፋፊ የቤት ልማት ፕሮግራሞችን መተግበር፣ የገቢ ምንጮችንና የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋፋት እንዲሁም የሰው ኃይልና የአሠራር አቅምን ማጠናከር መሆናቸው ተገልጿል።
ኮርፖሬሽኑም እነዚህን ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በመተግበር ለሀገራዊ የቤት ልማት ዕቅድ ስኬት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል።
25 days ago
“ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ ” ቢሾፍቱ ከተማ ሊገነባ ነው
#ethiopia | ለዓመታት በልብ ህክምና በጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማራው “ኸርት አታክ ኢትዮጵያ”፣ የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን ይበልጥ ዘላቂና ተደራሽ ለማድረግ “ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ” የተሰኘ የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታወቀ።
ቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርፖርት አቅራቢያ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክት፣ ትርፍንና በጎ አድራጎትን ባጣመረ ማህበራዊ የንግድ ስራ መርህ የሚመራ ነው።
የፕሮጀክቱ መጀመር ይፋ የሆነው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ ስምምነት በተፈራረመበት ወቅት ሲሆን፣ በፊርማ ስነ-ስርዓቱም ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ፣ እና የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የድርጅቱ ተባባሪ መስራችና የልብ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ እንደገለጹት፣ ሃርት አታክ ኢትዮጵያ እስካሁን የ660 ታካሚዎችን ህይወት መታደግ ቢችልም፣ ካለው ሰፊ የልብ ህመም ችግር አንጻር የበጎ አድራጎት ስራ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ወደዚህ አዲስ አሠራር መሸጋገር አስፈልጓልብለዋል።
ይህ አዲስ መዋቅር አቅም ያላቸው ታካሚዎች እየከፈሉ እንዲታከሙ፣ አቅም የሌላቸው ደግሞ በነጻ የህክምና እድል እንዲያገኙ በማድረግ ዘላቂነት ያለው ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረገው ስምምነት የኢትዮጵያውያንን የውጭ ሀገር የህክምና ፍሰት ከመቀነስ ባለፈ፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ታካሚዎችን ወደ ሀገሪቱ ለመሳብ የሚያስችል “ፍላይት ቱ ሂል” (Flight to Heal) የተሰኘ ፕሮግራም ለማስጀመር ትልቅ በር ይከፍታል። የልብ ህክምናን ጨምሮ የእናቶችና ህጻናት ጤናን፣ ካንሰርን፣ የነርቭ እና የድንገተኛ አደጋ ህክምናዎችን ያካተቱ ዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረቻን ለማስፋፋትና ባለሙያዎችን በህንድ ሀገር በልዩ ሁኔታ ለማሰልጠን አቅዷል።
በተጨማሪም በህክምና ከተማው ውስጥ የሚመሰረተው የህክምና ትምህርት ቤት ቀጣዩን የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ትውልድ በራሱ አቅም ለማስተማርና ለማብቃት ታላቅ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #intimahealthcity #heartattackethiopia #ethiopianairlines #medicaltourism #healthcareafrica #flighttoheal #africahealthcare
#ethiopia | ለዓመታት በልብ ህክምና በጎ አድራጎት ስራ ላይ የተሰማራው “ኸርት አታክ ኢትዮጵያ”፣ የበጎ አድራጎት አገልግሎቱን ይበልጥ ዘላቂና ተደራሽ ለማድረግ “ኢንቲማ ሄልዝ ኬር ሲቲ” የተሰኘ የህክምና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታወቀ።
ቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርፖርት አቅራቢያ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፈው ፕሮጀክት፣ ትርፍንና በጎ አድራጎትን ባጣመረ ማህበራዊ የንግድ ስራ መርህ የሚመራ ነው።
የፕሮጀክቱ መጀመር ይፋ የሆነው ድርጅቱ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ ስምምነት በተፈራረመበት ወቅት ሲሆን፣ በፊርማ ስነ-ስርዓቱም ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ፣ እና የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የድርጅቱ ተባባሪ መስራችና የልብ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ ተሊላ እንደገለጹት፣ ሃርት አታክ ኢትዮጵያ እስካሁን የ660 ታካሚዎችን ህይወት መታደግ ቢችልም፣ ካለው ሰፊ የልብ ህመም ችግር አንጻር የበጎ አድራጎት ስራ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ወደዚህ አዲስ አሠራር መሸጋገር አስፈልጓልብለዋል።
ይህ አዲስ መዋቅር አቅም ያላቸው ታካሚዎች እየከፈሉ እንዲታከሙ፣ አቅም የሌላቸው ደግሞ በነጻ የህክምና እድል እንዲያገኙ በማድረግ ዘላቂነት ያለው ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የተደረገው ስምምነት የኢትዮጵያውያንን የውጭ ሀገር የህክምና ፍሰት ከመቀነስ ባለፈ፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ታካሚዎችን ወደ ሀገሪቱ ለመሳብ የሚያስችል “ፍላይት ቱ ሂል” (Flight to Heal) የተሰኘ ፕሮግራም ለማስጀመር ትልቅ በር ይከፍታል። የልብ ህክምናን ጨምሮ የእናቶችና ህጻናት ጤናን፣ ካንሰርን፣ የነርቭ እና የድንገተኛ አደጋ ህክምናዎችን ያካተቱ ዘመናዊ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ የሚያስገባው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በሀገር ውስጥ የመድኃኒት ማምረቻን ለማስፋፋትና ባለሙያዎችን በህንድ ሀገር በልዩ ሁኔታ ለማሰልጠን አቅዷል።
በተጨማሪም በህክምና ከተማው ውስጥ የሚመሰረተው የህክምና ትምህርት ቤት ቀጣዩን የኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ትውልድ በራሱ አቅም ለማስተማርና ለማብቃት ታላቅ ራዕይ ሰንቆ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #intimahealthcity #heartattackethiopia #ethiopianairlines #medicaltourism #healthcareafrica #flighttoheal #africahealthcare
28 days ago
በአፍሪካ ቀዳሚው የኢትዮጵያ አቪዬሽን...
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዘርፍ በአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ያለ ግዙፍ የኢኮኖሚያዊ ሞተር ሆኗል።
ዘርፉ በሀገሪቱ የቱሪዝም እና የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለሀገር ውስጥ ምርት አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ከ165 በላይ እጅግ ዘመናዊና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ አውሮፕላኖች አሉት።
አማካይ የእድሜ ዘመናቸውም ከ7 ዓመት በታች ነው።
አየር መንገዱ ተጨማሪ 67 አዳዲስ አውሮፕላኖችንም አዝዟል።
በአፍሪካ ውስጥ ካሉ ማናቸውም አየር መንገዶች በላይ ወደ 131 የሚጠጉ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች፤ 63 የአፍሪካ ከተሞችን ጨምሮ መደበኛ የመንገደኞችና የጭነት በረራዎችን ያደርጋል።
በአቪዬሽን ዘርፉ ባሳየው ተከታታይ ስኬት፣ በ2024/2025 ብቻ 7.6 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ በማመንጨት 19 ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
በዚህ ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የቢሾፍቱው የአቡ ሴራ ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ከተማ ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ፕሮጀክቱ 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
ይህም በአፍሪካ ትልቁ ያደርገዋል።
ፕሮጀክቱ የአሁኑን የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መጨናነቅ በመቀነስ፣ ኢትዮጵያን እንደ ዱባይና ኢስታንቡል የዓለም አቀፍ ትራንዚት ዋና ማዕከል ያደርጋል።
በአሁኑ ወቅት አየር መንገዱ ራዕይ 2035 ስትራቴጂን ቀርጾ በመተግበር የሀገር ውስጥ የበረራ ተደራሽነቱን ወደ 26 አሳድጓል።
በዚህ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከ105 በላይ አዳዲስ አውሮፕላኖችን ከቦይንግ እና ኤርባስ ኩባንያዎች ጋር ውል ፈጽሞ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ይህም በሚቀጥሉት ዓመታት ጠቅላላ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ከ270 በላይ ለማድረስ ያለመ ነው።
በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ሦስት አዳዲስ ዘመናዊ የክልል አውሮፕላን ማረፊያዎች ተገንብተው ሥራ ጀምረዋል።
እነዚህም ነጌሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ጎሬ መቱ አውሮፕላን ማረፊያና ዛሬ የተመረቀው የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ናቸው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ትልቁን የጭነት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ በዓመት ከ248,400 ቶን በላይ ዕቃዎችን ያጓጉዛል።
ይህም የሀገሪቱን የወጪ ንግድ፣ የአበባ፣ ቡና፣ እና አትክልት በቀጥታ ከዓለም ገበያ ጋር በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ዋስትና ሆኗል።
እንደ ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ ያለው የአየር ጉዞ ፍላጎት በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ በሦስት እጥፍ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ዕድገት ከ527,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና በተዘዋዋሪ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዘርፍ በአፍሪካ ቀዳሚ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ ያለ ግዙፍ የኢኮኖሚያዊ ሞተር ሆኗል።
ዘርፉ በሀገሪቱ የቱሪዝም እና የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለሀገር ውስጥ ምርት አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ከ165 በላይ እጅግ ዘመናዊና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ አውሮፕላኖች አሉት።
አማካይ የእድሜ ዘመናቸውም ከ7 ዓመት በታች ነው።
አየር መንገዱ ተጨማሪ 67 አዳዲስ አውሮፕላኖችንም አዝዟል።
በአፍሪካ ውስጥ ካሉ ማናቸውም አየር መንገዶች በላይ ወደ 131 የሚጠጉ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች፤ 63 የአፍሪካ ከተሞችን ጨምሮ መደበኛ የመንገደኞችና የጭነት በረራዎችን ያደርጋል።
በአቪዬሽን ዘርፉ ባሳየው ተከታታይ ስኬት፣ በ2024/2025 ብቻ 7.6 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ በማመንጨት 19 ሚሊዮን መንገደኞችን አጓጉዟል።
በዚህ ዓመት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠለት የቢሾፍቱው የአቡ ሴራ ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ከተማ ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ፕሮጀክቱ 12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚፈጅ ሲሆን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
ይህም በአፍሪካ ትልቁ ያደርገዋል።
ፕሮጀክቱ የአሁኑን የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መጨናነቅ በመቀነስ፣ ኢትዮጵያን እንደ ዱባይና ኢስታንቡል የዓለም አቀፍ ትራንዚት ዋና ማዕከል ያደርጋል።
በአሁኑ ወቅት አየር መንገዱ ራዕይ 2035 ስትራቴጂን ቀርጾ በመተግበር የሀገር ውስጥ የበረራ ተደራሽነቱን ወደ 26 አሳድጓል።
በዚህ ስትራቴጂክ ዕቅድ ከ105 በላይ አዳዲስ አውሮፕላኖችን ከቦይንግ እና ኤርባስ ኩባንያዎች ጋር ውል ፈጽሞ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
ይህም በሚቀጥሉት ዓመታት ጠቅላላ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ከ270 በላይ ለማድረስ ያለመ ነው።
በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ሦስት አዳዲስ ዘመናዊ የክልል አውሮፕላን ማረፊያዎች ተገንብተው ሥራ ጀምረዋል።
እነዚህም ነጌሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ጎሬ መቱ አውሮፕላን ማረፊያና ዛሬ የተመረቀው የደብረ ማርቆስ ንጉሥ ተክለሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ናቸው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ትልቁን የጭነት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ በዓመት ከ248,400 ቶን በላይ ዕቃዎችን ያጓጉዛል።
ይህም የሀገሪቱን የወጪ ንግድ፣ የአበባ፣ ቡና፣ እና አትክልት በቀጥታ ከዓለም ገበያ ጋር በማስተሳሰር የኢኮኖሚ ዋስትና ሆኗል።
እንደ ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማኅበር ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ ያለው የአየር ጉዞ ፍላጎት በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ውስጥ በሦስት እጥፍ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ዕድገት ከ527,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቀጥተኛና በተዘዋዋሪ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
1 month ago
"ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
#fastmereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ወላጆች ከከተማ ውጪ የሚሰሩ ሥራዎችን ወጣቶች እንዲሞክሯቸው ማበረታታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ለአብነትም በግንባታ ላይ በሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቂ የሰው ኃይል ማግኘት አዳጋች መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ሰራተኝነት ሥራን የሚሰሩ ሰዎች ቁጥር እጅግ ጥቂት መሆኑን ጠቁመው፥ ለተመሳሳይ ሥራ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ከሀገር የወጡ ወጣቶች በቀን ለ16 ሰዓታት ያህል ሰርተው ራሳቸውን ሲለውጡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶች ግን ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም ክፍተት እንዳለባቸው ነው የገለጹት፡፡
በሁለት እና ሶስት የሥራ ፈረቃዎች በመስራት አቅምን ማሳደግና መተጋገዝ ካልተቻለ የኑሮ ውድነት ከዚህ በላይ ሊሆን አንደሚችል አመልክተዋል፡፡
#ፖለቲካ
#fastmereja I ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ሥራ ቢኖርም ሰራተኛ ማግኘት በጣም ከባድ ሆኗል አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፥ ወላጆች ከከተማ ውጪ የሚሰሩ ሥራዎችን ወጣቶች እንዲሞክሯቸው ማበረታታት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡
ለአብነትም በግንባታ ላይ በሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቂ የሰው ኃይል ማግኘት አዳጋች መሆኑን ነው ያስረዱት፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የቤት ሰራተኝነት ሥራን የሚሰሩ ሰዎች ቁጥር እጅግ ጥቂት መሆኑን ጠቁመው፥ ለተመሳሳይ ሥራ ከሀገር የሚወጡ ዜጎች ቁጥር ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡
ከሀገር የወጡ ወጣቶች በቀን ለ16 ሰዓታት ያህል ሰርተው ራሳቸውን ሲለውጡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ወጣቶች ግን ጊዜን በአግባቡ የመጠቀም ክፍተት እንዳለባቸው ነው የገለጹት፡፡
በሁለት እና ሶስት የሥራ ፈረቃዎች በመስራት አቅምን ማሳደግና መተጋገዝ ካልተቻለ የኑሮ ውድነት ከዚህ በላይ ሊሆን አንደሚችል አመልክተዋል፡፡
#ፖለቲካ
1 month ago
"በነገራችን ላይ፣ ዛሬ፣ በትግራይ ውስጥ ከሚኖር ትግራዋይ በላይ፣ በሰላም ወጥቶ መግባት የሚችል፣ አፈሳ የማይካሄድበት፣ በደሴ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በአዲስ አበባ፣ በቢሾፍቱ፣ አዳማ፣ አርባምንጭ፣ ሀዋሳ ያለ ትግራዋይ፣ ትግራይ ካለው ሰው በላይ ሰላም አለው። ትግራይ ካለው ሰው በላይ በሰላም ወጥቶ መግባት ይችላል። የሚያሳዝነው ይሄ ጉዳይ ግን ትግራይ ብቻ አይደለም። አማራ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች፣ 'ለአማራ ህዝብ ሰላም፣ ደህንነት፣ ጥቅም እንታገላለን' ብለው የሚሉ ሃይሎች በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች ካለው የአማራ ተወላጅ ይልቅ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሱማሌ ያለው አማራ ሰላም አለው። እነዚህ እንታገላለን የሚሉ ሃይሎች ያሉበት አካባቢ የበለጠ ፍራቻ፣ የበለጠ ግድያ፣ የበለጠ ዘረፋና መታገዶች አሉ።
"ኦሮሚያ አካባቢ ለኦሮሞ እንታገላለን ብለው የሚመሉ፣ የሚገዘቱ ሃይሎች ከሚንቀሳቀሱበት አካባቢ በላይ፣ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀስ፣ በሱማሌ የሚንቀሳቀስ፣ በአፋር የሚንቀሳቀስ ኦሮሞ የተሻለ ሰላም አለው። ዜጎች በገዛ ቀያቸው፣ መንደራቸው፣ በገዛ ልጆቻቸው እየታመሱ ይገኛሉ። ከቀያቸው ሸሽተው መኖር የተሻለ ሰላም የሚያገኙበት እየሆነ መጥቷል። ከህዝብ ተነጥሎ፣ ህዝብ አስለቅሶ፣ ህዝብ ዘርፎ፣ የሚደረግ ትግል ደግሞ የትም ማድረስ እንደማይችል ከታሪኮቻችን መማር የምንችል ይመስለኛል።
መንግስት አብዛኛውን ጉዳይ በትዕግስት የሚያየው፣ ወደ ግጭት የማይገባው፣ ለምንድነው ያላችሁ እንደሆነ፣ አላማ ቢስ ነው። አላማ የለውም። ይሄንን ግጭት ከፈጸምን በኋላ 'አሳካን' ብለን የምንናገረው አንዳች ቁምነገር የለም። በዚያም በዚህም ብንገል፣ ብንሞት ትርጉም የለውም። ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ ትግራይ አካባቢ ያለው የፖለቲካል አውድ የመጥረቢያ ፖለቲካ ሰለባ ነው ትግራዋይ እና ኢትዮጵያዊያን የሆኑት።"
ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በፓርላማው ከተናገሩት
"ኦሮሚያ አካባቢ ለኦሮሞ እንታገላለን ብለው የሚመሉ፣ የሚገዘቱ ሃይሎች ከሚንቀሳቀሱበት አካባቢ በላይ፣ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀስ፣ በሱማሌ የሚንቀሳቀስ፣ በአፋር የሚንቀሳቀስ ኦሮሞ የተሻለ ሰላም አለው። ዜጎች በገዛ ቀያቸው፣ መንደራቸው፣ በገዛ ልጆቻቸው እየታመሱ ይገኛሉ። ከቀያቸው ሸሽተው መኖር የተሻለ ሰላም የሚያገኙበት እየሆነ መጥቷል። ከህዝብ ተነጥሎ፣ ህዝብ አስለቅሶ፣ ህዝብ ዘርፎ፣ የሚደረግ ትግል ደግሞ የትም ማድረስ እንደማይችል ከታሪኮቻችን መማር የምንችል ይመስለኛል።
መንግስት አብዛኛውን ጉዳይ በትዕግስት የሚያየው፣ ወደ ግጭት የማይገባው፣ ለምንድነው ያላችሁ እንደሆነ፣ አላማ ቢስ ነው። አላማ የለውም። ይሄንን ግጭት ከፈጸምን በኋላ 'አሳካን' ብለን የምንናገረው አንዳች ቁምነገር የለም። በዚያም በዚህም ብንገል፣ ብንሞት ትርጉም የለውም። ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ ትግራይ አካባቢ ያለው የፖለቲካል አውድ የመጥረቢያ ፖለቲካ ሰለባ ነው ትግራዋይ እና ኢትዮጵያዊያን የሆኑት።"
ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በፓርላማው ከተናገሩት
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የ“እኔ እበልጥ” ትርክት ስብራትን በተጨባጭ እየጠገነ ያለው የ“መደመር” አካታች እሳቤ
*****************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ “እኔ እበልጣለሁ የሚል አግላይ አስተሳሰብ የዘመናት ድህነታችን ምንጭ ነው፤ ከዚህ ወጥተን እንደ አንድ ዜጋ ልንተባበር ይገባል” በማለት የችግራችንን መሠረት አስቀምጠዋል።
ይህ የበላይነት ስሜት እና አግላይ አስተሳሰብ የዜጎችን ማኅበራዊ እና ጂኦግራፊያዊ እንቅስቃሴ በመገደብ ሀገራዊ የገበያ ትስስርን የሚያደናቅፍ መዋቅራዊ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
የፖለቲካ ሥልጣንን እንደ ዜሮ-ድምር ፍልሚያ በሚቆጥር እሳቤ ውስጥ መኖር፣ ሀገራዊ ትብብርን እና የሰው ሀብት ልማትን በእጅጉ ይጎዳል።
ይህን ሥር የሰደደ አግላይ ትርክት ለመቀልበስ የለውጡ መንግሥት የ“መደመር” እሳቤን በማራመድ ዜሮ-ድምር የሆነውን የፖለቲካ ፉክክር በአካታች ሀገራዊ አንድነት ለመተካት እየሠራ ይገኛል።
ይህም ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርባምንጭ ከተማ ባደረጉት ንግግር በግልጽ ተንጸባርቋል።
በወቅቱም፣ እውነተኛ የብልጫ መለኪያ ተጨባጭ ወቅታዊ ሥራ እና ምርታማነት እንጂ ስም ወይም ታሪክ እንዳልሆነ አበክረው ገልጸዋል።
ሰላምን እንደ ኢኮኖሚያዊ እሴት በመቁጠር ቱሪስቶችን መንከባከብ፣ ሌብነትን መጸየፍ እና አካባቢን ማጽዳት ለጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
ሀገራዊ አንድነትን እና አካታችነትን ወደ ተጨባጭ ሀብት ለመቀየርም መንግሥት በ“ገበታ” ፕሮጀክቶች እና በብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ከእነዚህም መካከል ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችለው እና በአርባ ምንጭ ሐይቅ ላይ 360 ዲግሪ የሚሽከረከር ሬስቶራንትን ያካተተው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት አንዱ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደጠቀሱት፣ ከዚህ ቀደም አንድ የውጭ ባለሀብት አካባቢው ለቅንጦት ልማት ዝግጁ አይደለም ብሏቸው የነበረ ቢሆንም፤ መንግሥት የሀገር ውስጥ አቅምን በማስተባበር ይህን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርት እውን ማድረግ ችሏል።
ይህ ደግሞ ከመገፋፋት እና "እኔ እበልጥ" ከመባባል ይልቅ፣ ሀገራዊ አቅምን በማስተባበር ተዓምር መፍጠር እንደሚቻል ማሳያ ነው።
ከአርባምንጭ በተጨማሪ በሐዋሳ፣ በቢሾፍቱ፣ በጎንደር፣ በባሕር ዳር፣ በአፋር እና በደንዲ የተሠሩት ግዙፍ የመሠረተ ልማት እና የቱሪዝም ፕሮጀክቶች በሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገትን እኩል ለማዳረስ ያለሙ ናቸው።
እነዚህ ሥራዎች የሚያሳዩት “እኔ እበልጥ” ከሚል አግላይ ፖለቲካ ወጥተን በጋራ ስንቆም የውጭ ማረጋገጫ ሳያስፈልገን የሀገራችንን እምቅ ሀብት ወደ ተግባር መቀየር እንደምንችል ነው።
እውነተኛው የሀገር ግንባታ የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን የዕለት ተለት ተግባር ነው። አዎ፣ ሁላችንም በሕይወታችን፣ በሥራ ገበታችን እና በማኅበራዊ መስተጋብራችን "እኔ እበልጥ" ከሚል አግላይ አስተሳሰብ ወጥተን ሀገራችንን ለመገንባት መነሳት አለብን።
ትልቅ አቅም ያለን ሕዝቦች ነን፤ ከተባበርን እና አቅማችንን ካስተባበርን ልንደርስበት የማንችለው ከፍታ የለም።
የምታኮራ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ ዛሬውኑ በመደመር መንፈስ መነሳት ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆን አለበት፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #dineforgeneration #tourism #development #ebc
*****************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ “እኔ እበልጣለሁ የሚል አግላይ አስተሳሰብ የዘመናት ድህነታችን ምንጭ ነው፤ ከዚህ ወጥተን እንደ አንድ ዜጋ ልንተባበር ይገባል” በማለት የችግራችንን መሠረት አስቀምጠዋል።
ይህ የበላይነት ስሜት እና አግላይ አስተሳሰብ የዜጎችን ማኅበራዊ እና ጂኦግራፊያዊ እንቅስቃሴ በመገደብ ሀገራዊ የገበያ ትስስርን የሚያደናቅፍ መዋቅራዊ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
የፖለቲካ ሥልጣንን እንደ ዜሮ-ድምር ፍልሚያ በሚቆጥር እሳቤ ውስጥ መኖር፣ ሀገራዊ ትብብርን እና የሰው ሀብት ልማትን በእጅጉ ይጎዳል።
ይህን ሥር የሰደደ አግላይ ትርክት ለመቀልበስ የለውጡ መንግሥት የ“መደመር” እሳቤን በማራመድ ዜሮ-ድምር የሆነውን የፖለቲካ ፉክክር በአካታች ሀገራዊ አንድነት ለመተካት እየሠራ ይገኛል።
ይህም ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርባምንጭ ከተማ ባደረጉት ንግግር በግልጽ ተንጸባርቋል።
በወቅቱም፣ እውነተኛ የብልጫ መለኪያ ተጨባጭ ወቅታዊ ሥራ እና ምርታማነት እንጂ ስም ወይም ታሪክ እንዳልሆነ አበክረው ገልጸዋል።
ሰላምን እንደ ኢኮኖሚያዊ እሴት በመቁጠር ቱሪስቶችን መንከባከብ፣ ሌብነትን መጸየፍ እና አካባቢን ማጽዳት ለጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
ሀገራዊ አንድነትን እና አካታችነትን ወደ ተጨባጭ ሀብት ለመቀየርም መንግሥት በ“ገበታ” ፕሮጀክቶች እና በብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ሪፎርም በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ከእነዚህም መካከል ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎችን ማስተናገድ የሚችለው እና በአርባ ምንጭ ሐይቅ ላይ 360 ዲግሪ የሚሽከረከር ሬስቶራንትን ያካተተው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት አንዱ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደጠቀሱት፣ ከዚህ ቀደም አንድ የውጭ ባለሀብት አካባቢው ለቅንጦት ልማት ዝግጁ አይደለም ብሏቸው የነበረ ቢሆንም፤ መንግሥት የሀገር ውስጥ አቅምን በማስተባበር ይህን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርት እውን ማድረግ ችሏል።
ይህ ደግሞ ከመገፋፋት እና "እኔ እበልጥ" ከመባባል ይልቅ፣ ሀገራዊ አቅምን በማስተባበር ተዓምር መፍጠር እንደሚቻል ማሳያ ነው።
ከአርባምንጭ በተጨማሪ በሐዋሳ፣ በቢሾፍቱ፣ በጎንደር፣ በባሕር ዳር፣ በአፋር እና በደንዲ የተሠሩት ግዙፍ የመሠረተ ልማት እና የቱሪዝም ፕሮጀክቶች በሀገራችን የኢኮኖሚ ዕድገትን እኩል ለማዳረስ ያለሙ ናቸው።
እነዚህ ሥራዎች የሚያሳዩት “እኔ እበልጥ” ከሚል አግላይ ፖለቲካ ወጥተን በጋራ ስንቆም የውጭ ማረጋገጫ ሳያስፈልገን የሀገራችንን እምቅ ሀብት ወደ ተግባር መቀየር እንደምንችል ነው።
እውነተኛው የሀገር ግንባታ የሚጀምረው ከእያንዳንዳችን የዕለት ተለት ተግባር ነው። አዎ፣ ሁላችንም በሕይወታችን፣ በሥራ ገበታችን እና በማኅበራዊ መስተጋብራችን "እኔ እበልጥ" ከሚል አግላይ አስተሳሰብ ወጥተን ሀገራችንን ለመገንባት መነሳት አለብን።
ትልቅ አቅም ያለን ሕዝቦች ነን፤ ከተባበርን እና አቅማችንን ካስተባበርን ልንደርስበት የማንችለው ከፍታ የለም።
የምታኮራ እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስረከብ ዛሬውኑ በመደመር መንፈስ መነሳት ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆን አለበት፡፡
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #dineforgeneration #tourism #development #ebc
1 month ago
አድናቂም ወዳጅ ይሆናል!
ጊዜው በ90 ዎቹ መጀመሪያ ግድም ነው፡፡ በቢሾፍቱ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሳለን በሀገራችን ታዋቂ ከሚባሉት የሙዚቃ ባንዶች አንዱ የሜጋ አምፊ ቲያትር ራሚድ ባንድ ነበር።
አንድ ቀን ዝነኛው ራሚድ ባንድ የሙዚቃ ድግሱን ለማቅረብ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ መጥቶ ነበር፡፡ ከባንዱ ጋር ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ከመጡት ተወዳጅና ታዋቂ አርቲስቶች መካከል፡- ላፎንቴኖች ፣ ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ፣ መልካሙ ተበጀ ፣ ጀማል መሀመድ(አቺኩዳ)፣ ፀደንያ ገ/ማርቆስ ፣ ማናልቦሽ ዲቦ፣ ደረጀና ሀብቴ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ ዘውዱ በቀለና ፊሊፕ ማርቲን ይገኙበታል፡፡
የሙዚቃ ዝግጅቱን ለመታደም የከተማችን ነዋሪ በወረፋ ነበር ወደ አዳራሹ የገባው፡፡ እኔም ዝግጅቱን በገጉት ሲጠባበቁ ከነበሩት መካከል አንዱ ነኝ፡፡ አርቲስቶችን ለማስፈረም ሁሉ በኪሴ በቂ ወረቀቶችን ይዤ ነበር የገባሁት፡፡ በወቅቱ ሁሉንም አርቲስቶች የማደንቅ ቢሆንም፣ በተለይ ደግሞ ኮሜዲያን ደረጀንና ሃብቴን ለማየትና ከተቻለም ለማስፈረም በእጅጉ ጓጉቼ ነበር።
በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ በይፋ ተጀመረ፡፡ እውነት ለመናገር አንድም ቤቱ የቀረ የቢሾፍቱ ነዋሪ ያለ አይመስልም ነበር፡፡ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ የምናቃቸው ተወዳጅና ዝነኛ ድምጻውያን በየተራ መድረክ ላይ እየወጡ አቀነቀኑ፡፡ ታዳሚው አብሯቸው እየዘፈነ እንደጉድ ጨፈረ፡፡ አዳራሹን በአንድ እግሩ አቆመው፡፡
የመድረክ አጋፋሪው ጥላሁን እልፍነህ፣ በመቀጠል ሥራቸውን የሚያቀርቡት ሁለቱ ተወዳጅ ኮሜዲያን እንደሆኑ ሲያስተዋውቅ፣ ታዳሚው በጩኸትና በፉጨት ደስታውንና ፍቅሩን ገለጸ፡፡ ደረጀና ሃብቴም ወደ መድረኩ ወጥተው በማያልቀው ቀልዳቸውና ለዛቸው አዳራሹን በሳቅ ሞሉት፡፡
ሥራቸውን አቅርበው እንደጨረሱ ከተጠገጠገው ሰው መሃል እንዴት ተፈትልኬ እንደወጣሁ ሳላውቀው፣ ራሴን መድረኩ አጠገብ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አሻቅቤ ወደ ደረጀና ሃብቴ እየተመለከትኩ፣ "ፈርሙልኝ" አልኳቸው - ያዘጋጀሁትን ወረቀት ዘርግቼ፡፡ አንዳቸው ስሜን ጠየቁኝ፡፡ ነገርኳቸው፡፡ ከዚያም ከመድረኩ ጀርባ (ባክ ስቴጅ)ይዘውኝ ገቡ። እዚያ ሌሎችም ታዋቂ አርቲስቶች ነበሩ፡፡ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ሁሉንም አስፈረምኳቸው፡፡
ተልዕኮዬን አጠናቅቄ ከመሄዴ በፊት ግን ኮሜዲያን ሀብቴ ምትኩ ለእነርሱ ከተዘጋጀው ሳንዱች ላይ አንስቶ እንድበላ ጋበዘኝ፡፡ በጣም ነበር ደስ ያለኝ፡፡ በአንዳች በማላውቀው ስሜት ተጥለቅልቄ ነበር፡፡ በቲቪ ብቻ እያየኋቸው የማደንቃቸውና የምወዳቸው ደረጀና ሀብቴ፣ የቅርብ ጓደኞቼ የሆኑ ያህል ተሰምቶኝ ነበር ብል ፈጽሞ አላጋነንኩም፡፡
ከዚያን ጊዜ በኋላ ታዲያ ደረጀና ሃብቴ እንዲሁም ሌሎች አርቲስቶች የፈረሙልኝን ወረቀት ት/ቤት ድረስ በመውሰድ ለጓደኞቼ እያሳየሁ፣ "ደረጃዬን" እንዲያውቁልኝ እጋጋጥ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ "እኔኮ ከደረጄና ሃብቴ ጋር ጓደኛ ነኝ" እያልኩኝ፣ አብሬያቸው ሳንድዊች መብላቴን ሁሉ በማስረጃነት አቀርብ ነበር፡፡
ይሄ ሁሉ የሆነው በታዳጊነት ዕድሜ ላይ ነው - በተማሪነት ዘመን፡፡ ዛሬ ላይ ተወዳጁ ኮሜዲያን ደረጀ የቅርብ ጓደኛዬና ወዳጄ ብቻ ሳይሆን ወንድሜም ጭምር ነው፡፡
ደሬ፤ እንኳን ተወለድክልን !
ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልሃለሁ!
አክባሪህና ወዳጅህ ቴዎድሮስ ታደሰ አየለ
ጊዜው በ90 ዎቹ መጀመሪያ ግድም ነው፡፡ በቢሾፍቱ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሳለን በሀገራችን ታዋቂ ከሚባሉት የሙዚቃ ባንዶች አንዱ የሜጋ አምፊ ቲያትር ራሚድ ባንድ ነበር።
አንድ ቀን ዝነኛው ራሚድ ባንድ የሙዚቃ ድግሱን ለማቅረብ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ መጥቶ ነበር፡፡ ከባንዱ ጋር ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ከመጡት ተወዳጅና ታዋቂ አርቲስቶች መካከል፡- ላፎንቴኖች ፣ ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ፣ መልካሙ ተበጀ ፣ ጀማል መሀመድ(አቺኩዳ)፣ ፀደንያ ገ/ማርቆስ ፣ ማናልቦሽ ዲቦ፣ ደረጀና ሀብቴ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ ዘውዱ በቀለና ፊሊፕ ማርቲን ይገኙበታል፡፡
የሙዚቃ ዝግጅቱን ለመታደም የከተማችን ነዋሪ በወረፋ ነበር ወደ አዳራሹ የገባው፡፡ እኔም ዝግጅቱን በገጉት ሲጠባበቁ ከነበሩት መካከል አንዱ ነኝ፡፡ አርቲስቶችን ለማስፈረም ሁሉ በኪሴ በቂ ወረቀቶችን ይዤ ነበር የገባሁት፡፡ በወቅቱ ሁሉንም አርቲስቶች የማደንቅ ቢሆንም፣ በተለይ ደግሞ ኮሜዲያን ደረጀንና ሃብቴን ለማየትና ከተቻለም ለማስፈረም በእጅጉ ጓጉቼ ነበር።
በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ በይፋ ተጀመረ፡፡ እውነት ለመናገር አንድም ቤቱ የቀረ የቢሾፍቱ ነዋሪ ያለ አይመስልም ነበር፡፡ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ የምናቃቸው ተወዳጅና ዝነኛ ድምጻውያን በየተራ መድረክ ላይ እየወጡ አቀነቀኑ፡፡ ታዳሚው አብሯቸው እየዘፈነ እንደጉድ ጨፈረ፡፡ አዳራሹን በአንድ እግሩ አቆመው፡፡
የመድረክ አጋፋሪው ጥላሁን እልፍነህ፣ በመቀጠል ሥራቸውን የሚያቀርቡት ሁለቱ ተወዳጅ ኮሜዲያን እንደሆኑ ሲያስተዋውቅ፣ ታዳሚው በጩኸትና በፉጨት ደስታውንና ፍቅሩን ገለጸ፡፡ ደረጀና ሃብቴም ወደ መድረኩ ወጥተው በማያልቀው ቀልዳቸውና ለዛቸው አዳራሹን በሳቅ ሞሉት፡፡
ሥራቸውን አቅርበው እንደጨረሱ ከተጠገጠገው ሰው መሃል እንዴት ተፈትልኬ እንደወጣሁ ሳላውቀው፣ ራሴን መድረኩ አጠገብ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አሻቅቤ ወደ ደረጀና ሃብቴ እየተመለከትኩ፣ "ፈርሙልኝ" አልኳቸው - ያዘጋጀሁትን ወረቀት ዘርግቼ፡፡ አንዳቸው ስሜን ጠየቁኝ፡፡ ነገርኳቸው፡፡ ከዚያም ከመድረኩ ጀርባ (ባክ ስቴጅ)ይዘውኝ ገቡ። እዚያ ሌሎችም ታዋቂ አርቲስቶች ነበሩ፡፡ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ሁሉንም አስፈረምኳቸው፡፡
ተልዕኮዬን አጠናቅቄ ከመሄዴ በፊት ግን ኮሜዲያን ሀብቴ ምትኩ ለእነርሱ ከተዘጋጀው ሳንዱች ላይ አንስቶ እንድበላ ጋበዘኝ፡፡ በጣም ነበር ደስ ያለኝ፡፡ በአንዳች በማላውቀው ስሜት ተጥለቅልቄ ነበር፡፡ በቲቪ ብቻ እያየኋቸው የማደንቃቸውና የምወዳቸው ደረጀና ሀብቴ፣ የቅርብ ጓደኞቼ የሆኑ ያህል ተሰምቶኝ ነበር ብል ፈጽሞ አላጋነንኩም፡፡
ከዚያን ጊዜ በኋላ ታዲያ ደረጀና ሃብቴ እንዲሁም ሌሎች አርቲስቶች የፈረሙልኝን ወረቀት ት/ቤት ድረስ በመውሰድ ለጓደኞቼ እያሳየሁ፣ "ደረጃዬን" እንዲያውቁልኝ እጋጋጥ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ "እኔኮ ከደረጄና ሃብቴ ጋር ጓደኛ ነኝ" እያልኩኝ፣ አብሬያቸው ሳንድዊች መብላቴን ሁሉ በማስረጃነት አቀርብ ነበር፡፡
ይሄ ሁሉ የሆነው በታዳጊነት ዕድሜ ላይ ነው - በተማሪነት ዘመን፡፡ ዛሬ ላይ ተወዳጁ ኮሜዲያን ደረጀ የቅርብ ጓደኛዬና ወዳጄ ብቻ ሳይሆን ወንድሜም ጭምር ነው፡፡
ደሬ፤ እንኳን ተወለድክልን !
ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልሃለሁ!
አክባሪህና ወዳጅህ ቴዎድሮስ ታደሰ አየለ
1 month ago
ወደ ሊዮን ከተማ በረራ ተጀምሯል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ከተማ በረራ መጀመሩን ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመዳረሻ መረቡን የማስፋፋት ስትራቴጂው አካል የሆነውን ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ከተማ የሚያደርገውን አዲስ የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት በይፋ ማስጀመሩን አበሰረ።
ይህ አዲስ መስመር ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ ሶስተኛ፣ በአውሮፓ ሀገራት ደግሞ 23ኛ መዳረሻ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፤ በአጠቃላይ የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር ወደ 146 ከፍ አድርጎታል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የበረራ አገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ አፍሪካን ከዓለም ጋር የማገናኘት ተልዕኮውን ለማሳካት የተገኘ ተጨማሪ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም በረራው ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ሰፊ አማራጭ ከመፍጠሩም በላይ፣ በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትስስር በማጠናከር በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
አየር መንገዱ የዘመኑን ቴክኖሎጂ የታጠቁ ግዙፍ አውሮፕላኖችን በመጨመር የመዳረሻ መረቡን የማስፋፋት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ በበኩላቸው፣ ሊዮን የኢኮኖሚ እና የንግድ ማዕከል እንደመሆኗ መጠን ወደ ከተማዋ የተጀመረው በረራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
አምባሳደሩ አያይዘውም፣ በቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው አዲሱ አየር መንገድ የጥናት እና የቴክኒክ ስራዎች ላይ የፈረንሳይ ተቋማት እየተሳተፉ እንደሚገኙ በመግለጽ፣ በአቪየሽን ዘርፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ትብብር አድንቀዋል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፈረንሳይሊዮን #ጌጡተመስገንሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemesgenmediacommunication
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ከተማ በረራ መጀመሩን ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ የመዳረሻ መረቡን የማስፋፋት ስትራቴጂው አካል የሆነውን ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ከተማ የሚያደርገውን አዲስ የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት በይፋ ማስጀመሩን አበሰረ።
ይህ አዲስ መስመር ለአየር መንገዱ በፈረንሳይ ሶስተኛ፣ በአውሮፓ ሀገራት ደግሞ 23ኛ መዳረሻ ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን፤ በአጠቃላይ የዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ቁጥር ወደ 146 ከፍ አድርጎታል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ የበረራ አገልግሎቱ መጀመር አየር መንገዱ አፍሪካን ከዓለም ጋር የማገናኘት ተልዕኮውን ለማሳካት የተገኘ ተጨማሪ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
አክለውም በረራው ለዓለም አቀፍ ተጓዦች ሰፊ አማራጭ ከመፍጠሩም በላይ፣ በሀገራቱ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ትስስር በማጠናከር በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
አየር መንገዱ የዘመኑን ቴክኖሎጂ የታጠቁ ግዙፍ አውሮፕላኖችን በመጨመር የመዳረሻ መረቡን የማስፋፋት ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ በበኩላቸው፣ ሊዮን የኢኮኖሚ እና የንግድ ማዕከል እንደመሆኗ መጠን ወደ ከተማዋ የተጀመረው በረራ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
አምባሳደሩ አያይዘውም፣ በቢሾፍቱ እየተገነባ በሚገኘው አዲሱ አየር መንገድ የጥናት እና የቴክኒክ ስራዎች ላይ የፈረንሳይ ተቋማት እየተሳተፉ እንደሚገኙ በመግለጽ፣ በአቪየሽን ዘርፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ትብብር አድንቀዋል።
በሔኖክ ወ/ገብርኤል
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ፈረንሳይሊዮን #ጌጡተመስገንሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemesgenmediacommunication
2 months ago
የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ
#ethiopia | ባሌ፣ ሮቤ - የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገለጹ።
በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል አበይት ርዕስ ሚኒስትሩ “የመዳረሻ ልማት ብሔራዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ንግግር፣ መዳረሻዎች የቱሪዝም መስህቦች ብቻ ሳይሆኑ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የኢንቨስትመንት ማዕከላት፣ የማህበራዊ ለውጥ መድረኮች እና የብሔራዊ ማንነት መገለጫዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞቿ ውስጥ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ መሠረተ ልማትን ለማዘመን እና ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር እየሰራች ሲሆን፣ የመዳረሻ ልማት እነዚህን ግቦች በተግባር የሚያሳካ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሶፍ ኦማር ዋሻዎች፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ ዋንጪ፣ ሐረር፣ ሐዋሳ ሐይቅ፣ ጣና ሐይቅ፣ ገራልታ እና አርባምንጭን ጨምሮ የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ጎብኚዎችን፣ ባለሀብቶችን፣ ተመራማሪዎችን እና ፈጣሪዎችን ከዓለም ዙሪያ ለመሳብ ትልቅ አቅም እንዳላቸውም ተናግረዋል።
ዶ/ር አብርሃም የመዳረሻ ልማት በትራንስፖርት፣ ሎጂስቲክስ፣ ግብርና፣ ሪል እስቴት፣ መስተንግዶ እና አገልግሎት ዘርፎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን እንደሚያነቃቃ ገልጸው፣ በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትስስር እና መሠረተ ልማት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች የቱሪዝም፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሪል እስቴት ዕድሎችን እንደሚያሰፉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች እና የአካባቢ ማህበረሰቦች በመዳረሻ ልማት ዘርፍ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበው፣ የኢትዮጵያ መዳረሻዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የኢንቨስትመንትና የፈጠራ ማዕከላት ማድረግ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
#ethiopia #destinationdevelopment #tourism #investment #economicgrowth #getutemesgen #ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
#ethiopia | ባሌ፣ ሮቤ - የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገለጹ።
በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል አበይት ርዕስ ሚኒስትሩ “የመዳረሻ ልማት ብሔራዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ንግግር፣ መዳረሻዎች የቱሪዝም መስህቦች ብቻ ሳይሆኑ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የኢንቨስትመንት ማዕከላት፣ የማህበራዊ ለውጥ መድረኮች እና የብሔራዊ ማንነት መገለጫዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞቿ ውስጥ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ መሠረተ ልማትን ለማዘመን እና ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር እየሰራች ሲሆን፣ የመዳረሻ ልማት እነዚህን ግቦች በተግባር የሚያሳካ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሶፍ ኦማር ዋሻዎች፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ ዋንጪ፣ ሐረር፣ ሐዋሳ ሐይቅ፣ ጣና ሐይቅ፣ ገራልታ እና አርባምንጭን ጨምሮ የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ጎብኚዎችን፣ ባለሀብቶችን፣ ተመራማሪዎችን እና ፈጣሪዎችን ከዓለም ዙሪያ ለመሳብ ትልቅ አቅም እንዳላቸውም ተናግረዋል።
ዶ/ር አብርሃም የመዳረሻ ልማት በትራንስፖርት፣ ሎጂስቲክስ፣ ግብርና፣ ሪል እስቴት፣ መስተንግዶ እና አገልግሎት ዘርፎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን እንደሚያነቃቃ ገልጸው፣ በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትስስር እና መሠረተ ልማት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች የቱሪዝም፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሪል እስቴት ዕድሎችን እንደሚያሰፉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች እና የአካባቢ ማህበረሰቦች በመዳረሻ ልማት ዘርፍ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበው፣ የኢትዮጵያ መዳረሻዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የኢንቨስትመንትና የፈጠራ ማዕከላት ማድረግ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
#ethiopia #destinationdevelopment #tourism #investment #economicgrowth #getutemesgen #ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
ኢትዮጵያን ወደ አቪዬሽን ማዕከልነት…
የቢሾፍቱ አቡሴራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዓለምን ለማስተሳሰር የሚኖረው ሚና ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያን ከአህጉራዊ የትራንዚት ማዕከልነት ወደ መላው ዓለም ስልታዊ መገናኛ ድልድይነት ያሸጋግራታል፡፡
ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የአቪዬሽን መናኸሪያ ከማድረግ ባለፈ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር ኩራት የሚሆኑ የኢትዮጵያን ዘላቂ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያረጋግጡ በረከቶችን ይዞ እየመጣ ነው፡፡
ለግዙፉ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጦለት፣ በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያው ምዕራፍ የመሬት ማስተካከል ሥራዎች ቀንና ሌሊት በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑለት ይገኛል።
ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 12 ነጥብ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የሚደረግበት ሲሆን÷ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ትልቁ የአቪዬሽን ማዕከል ይሆናል።
በአሁኑ ወቅት ለቦታው መሬት ማስተካከል እና የዝግጅት ሥራዎች 610 ሚሊየን ዶላር ተመድቦ ሥራው በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
የመጀመሪያው ዙር የመሬት ዝግጅት ሥራ እንደተጠናቀቀ፣ ዋና ዋናዎቹ የግንባታ ተቋራጮች ወደ ስፍራው ገብተው ግንባታቸውን ይጀምራሉ። የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በፈረንጆቹ እስከ 2030 ድረስ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ግብ ተቀምጧል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ በዓመት 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ ግዙፍ አቅም ይኖረዋል። ይህም አሁን ካለው የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቅም በ4 ነጥብ 4 እጥፍ ይበልጣል። አየውሮፕላን ማረፊያው አራት ዘመናዊ ማኮብኮቢያዎች እና በአንድ ጊዜ እስከ 270 አውሮፕላኖችን ማቆም የሚችል ስፍራም ይኖረዋል።
አቡሴራ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ከአዲስ አበባ ቦሌ (2 ሺህ 334 ሜትር) በተሻለ ለአውሮፕላኖች መነሳትና ማረፍ እጅግ ምቹ የአየር ሁኔታን ይሰጣል።
የፕሮጀክቱ ዲዛይን በታዋቂው የለንደን ዘሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የተሰራ ሲሆን÷ በውስጡ ዘመናዊ ሆቴሎችን፣ የገበያ ማዕከላትን፣ የንግድና የዕቃ መጋዘን (Cargo) ኮምፕሌክሶችን ያካትታል። አዲሱ አየር ማረፊያ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር በፈጣን የኤክስፕረስ መንገድ እና በከፍተኛ ፍጥነት ተንቀሳቃሽ የባቡር መስመር እንደሚገናኝ ይጠበቃል፡፡
ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው የኢትዮጵያን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እድገት ለማሳለጥ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ሀገሪቱን ወደ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥን ዘላቂ ሞተር ይሆናል። ይህ ሜጋ ፕሮጀክት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ አበርክቶው ከፍተኛ ነው፡፡
በግንባታው ወቅት በሺህ የሚቆጠሩ መሃንዲሶችንና ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ ያለ ሲሆን÷ ሥራ ሲጀምር ደግሞ በአየር መንገዱ፣ በሆቴሎችና በሎጂስቲክስ ዘርፍ ለበርካታ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጥራል። በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን በማስተናገድ ከትራንዚት፣ ከቀረጥ ነፃ ንግድ እና ከአየር መንገድ አገልግሎቶች የሚገኘውን የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል። የአካባቢው የዶሮ፣ የወተት፣ የአትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች ለግዙፉ አውሮፕላን ማረፊያና ለሆቴሎቹ ምርቶቻቸውን በስፋት የሚያቀርቡበት ሰፊ የገበያ እድልም ይፈጥርላቸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ምርት እድገት፣ በውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትና በውጪ ምንዛሪም ማሳደግን ያስችላል፡፡ ማረፊያው በሚሊየን የሚቆጠሩ መንገደኞችን እና በሚሊየን የሚቆጠር ቶን ጭነት ማስተናገዱ በራሱ ለሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ቀጥተኛ እና ከፍተኛ ድርሻ ያበረክታል።
ምቹ፣ ፈጣን እና ዘመናዊ የአየር ትራንስፖርት እና የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማት መኖሩ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ኩባንያዎችና ፋብሪካዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ዋነኛ ማበረታቻ ይሆናል።
ከአገልግሎቶች፣ ከነዳጅ ሽያጭ፣ ከትራንዚት ሆቴሎች እና ከቀረጥ ነፃ የንግድ ማዕከላት የሚገኘው ገቢ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ እጥረት በዘላቂነት ይቀርፋል።
የወጪ ንግድ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እድገት በማሳለጥ ረገድም የላቀ ሚና ይጫወታል፡፡ እንደ አበባ፣ ፍራፍሬ፣ አትክልትና ስጋ ያሉ በቀላሉ ሊበላሹ የሚችሉ የኢትዮጵያ እና የሌሎች ሀገራት ወጪ ምርቶች ሳይዘገዩ በጥራት ለዓለም ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ የገበሬውንና የላኪውን ገቢ ያሳድጋል።
በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ እና በሀገሪቱ ያሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚያመርቷቸውን የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳ እና የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አውሮፓ፣ አሜሪካ እና እስያ ገበያዎች ለማጓጓዝ ምቹ የሎጂስቲክስ ሰንሰለት ይፈጥራል።የአህጉሪቱ የንግድና የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ ዋና ማስተላለፊያ ማዕከል በመሆን የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ተሰሚነት ያጠናክራል።
የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ደግሞ ሌላኛው ትሩፋቱ ይሆናል፡፡ አውሮፕላን ማረፊያው ከማረፊያነት ባለፈ ዘመናዊ ሆቴሎችን፣ የገበያ ማዕከላትን፣ የኤግዚቢሽን ማዕከላትንና የንግድ ህንጻዎችን የያዘ "የኤርፖርት ከተማ" ወይም አዲስ የኢኮኖሚ ከተማ ሆኖ ይገነባል።
አካባቢው ለቱሪዝም ምቹ በመሆኑም ዓለም አቀፍ ቱሪዝምን ይስባል፡፡ በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅሙ፣ በሚሊየን የሚቆጠሩ የትራንዚት መንገደኞች ቢያንስ ለጥቂት ቀናት በሀገሪቱ እንዲቆዩ እና የኢትዮጵያን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ መስህቦች እንዲጎበኙ በር ይከፍታል።
የቱሪስቶች ቁጥር መጨመር በሀገር ውስጥ ያሉ ሆቴሎች፣ ሪዞርቶች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች እና የባህል ምርቶች አቅራቢዎች ገቢያቸው እንዲያድግ እና ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ያደርጋል።
የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የሰው ኃይል ልማት ላይ የሚኖረው አንድምታም በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ አውሮፕላን ማረፊያው የሚገነባው እጅግ ዘመናዊ በሆኑ የኤክስሬይ፣ የደህንነት፣ የሮቦቲክስ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂዎች በመሆኑ የሀገር ውስጥ መሃንዲሶች እና ባለሙያዎች ከፍተኛ የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል።ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዞ የሚስፋፉት የአቪዬሽን ማሰልጠኛዎች እና የምርምር ማዕከላት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የእውቀት ማዕከል ያደርጓታል።
በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ክልላዊ የልማት መናኸሪያ ያደርጋታል፡፡ ፕሮጀክቱ ቢሾፍቱን፣ ሞጆን፣ ዱከምንና አዲስ አበባን የሚያስተሳስር አዲስ የኢኮኖሚ ኮሪደር ይፈጥራል። ይህ ከተሞች፣ የንፁህ ውሃ አቅርቦት፣ የኃይል እና የመገናኛ መሠረተ ልማቶችን በጥራት እንዲያድጉ ያደርጋል።
ከዚህ ባለፈም ዓለም አቀፋዊ ትስስርን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ የመጀመሪያው ሚና የዓለም አቀፍ አየር መንገዶች መዳረሻነት ነው፡፡ በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም የሚኖረው በመሆኑ፣ ከእስያ፣ ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ እና ከላቲን አሜሪካ የሚነሱ ተያያዥ በረራዎችን በአንድ ማዕከል ያስተናግዳል ፤ ይህም ግዙፍ የመንገደኞች ፍሰትን ይፈጥራል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል የሆነበት ስታር አሊያንስ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች አቡሴራን ዋና የምስራቅ አፍሪካ መሸጋገሪያ መናኸሪያቸው ያደርጉታል። የአሊያንስ ማዕከልነታችንንም የምናረጋግጥበት ይሆናል፡፡
ሁለተኛው ሚና የግሎባል ደቡብ ዋነኛ ትስስር ድልድይን መፍጠር ነው፡፡ አዲሱ ማረፊያ አፍሪካን ከላቲን አሜሪካ፣ ከእስያ (በተለይም ከቻይና እና ህንድ) እና ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር በቀጥታና በአጭር ሰዓት የሚያገናኝ ዋነኛ መስመር ይሆናል። ይህ ሲሆን ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን ከዓለም ጋር አስተሳሰርን ማለት ነው፡፡
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተፈፃሚነት ለማፋጠን ሰዎችንና የንግድ ዕቃዎችን ከአህጉሪቱ ጥግ እስከ ዓለም ጫፍ በፈጣን የሎጂስቲክስ ሰንሰለት ያገናኛል። ለአህጉር አቀፍ ንግድ መነቃቃት አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡
ሦስተኛው የዓለም አቀፍ የአየር ጭነት ማዕከልነታችንን ማረጋገጥ ነው፡፡ የሚገነባው ግዙፍና ዘመናዊ የካርጎ ተርሚናል የዓለም የንግድ ዕቃዎች እና የህክምና አቅርቦቶች ከአምራች ሀገራት ተነስተው ወደ ተጠቃሚዎች የሚሰራጩበት ዋነኛ የአየር ሎጂስቲክስ ማዕከል እንዲሆን ያደርገዋል። እንደ አበባ፣ ፍራፍሬ እና ስጋ ያሉ የኢትዮጵያና የጎረቤት ሀገራት ምርቶች ሳይበላሹ በጥራትና በከፍተኛ ፍጥነት ወደ መላው ዓለም ገበያ እንዲደርሱ ያስችላል።
ምቹ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እና የአቪዬሽን ብቃት ደግሞ ሌላኛው ሚናው ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም ካርታ ላይ ያላት ስልታዊ አቀማመጥ (በአውሮፓ፣ በእስያ እና በአፍሪካ መገናኛ መስመር ላይ መገኘቷ) አቡሴራን ለዓለም አቀፍ በረራዎች አጭርና ተመራጭ የመሸጋገሪያ መስመር ያደርገዋል።
የአቡሴራ ከፍታ ከአዲስ አበባ ቦሌ ያነሰ በመሆኑ፣ የዓለም አቀፍ በረራ አውሮፕላኖች ሙሉ ነዳጅና ጭነት ይዘው ረጅም ርቀት በቀጥታ እንዲበሩ ሰፊ የአቪዬሽን ምቹነትን ይሰጣል። የአውሮፕላኖች የመጫን አቅምን ጨመረ ማለት ነው።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ እንደ ዱባይ (DXB) እና ሲንጋፖር (Changi) ያሉ ታላላቅ የዓለም መገናኛ ማዕከላት ተርታ ያሰልፋታል።
በአጠቃላይ ሲታይ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን ስልታዊ፣ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ከማጠናከሩ ባሻገር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ፍጥነት የሚያሳልጥ ታላቅ ብሔራዊ ትሩፋት ነው።
ኢትዮጵያን ወደ አቪዬሽን ማዕከልነት…
የቢሾፍቱ አቡሴራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዓለምን ለማስተሳሰር የሚኖረው ሚና ከፍተኛ ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያን ከአህጉራዊ የትራንዚት ማዕከልነት ወደ መላው ዓለም ስልታዊ መገናኛ ድልድይነት ያሸጋግራታል፡፡
ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የአቪዬሽን መናኸሪያ ከማድረግ ባለፈ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር ኩራት የሚሆኑ የኢትዮጵያን ዘላቂ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚያረጋግጡ በረከቶችን ይዞ እየመጣ ነው፡፡
ለግዙፉ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጦለት፣ በአሁኑ ወቅት የመጀመሪያው ምዕራፍ የመሬት ማስተካከል ሥራዎች ቀንና ሌሊት በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወኑለት ይገኛል።
ይህ ሜጋ ፕሮጀክት በአጠቃላይ 12 ነጥብ 5 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ የሚደረግበት ሲሆን÷ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ትልቁ የአቪዬሽን ማዕከል ይሆናል።
በአሁኑ ወቅት ለቦታው መሬት ማስተካከል እና የዝግጅት ሥራዎች 610 ሚሊየን ዶላር ተመድቦ ሥራው በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
የመጀመሪያው ዙር የመሬት ዝግጅት ሥራ እንደተጠናቀቀ፣ ዋና ዋናዎቹ የግንባታ ተቋራጮች ወደ ስፍራው ገብተው ግንባታቸውን ይጀምራሉ። የፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በፈረንጆቹ እስከ 2030 ድረስ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ግብ ተቀምጧል።
የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ በዓመት 60 ሚሊዮን፣ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ደግሞ እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ ግዙፍ አቅም ይኖረዋል። ይህም አሁን ካለው የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቅም በ4 ነጥብ 4 እጥፍ ይበልጣል። አየውሮፕላን ማረፊያው አራት ዘመናዊ ማኮብኮቢያዎች እና በአንድ ጊዜ እስከ 270 አውሮፕላኖችን ማቆም የሚችል ስፍራም ይኖረዋል።
አቡሴራ ከአዲስ አበባ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከባሕር ጠለል በላይ በ1 ሺህ 910 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ከአዲስ አበባ ቦሌ (2 ሺህ 334 ሜትር) በተሻለ ለአውሮፕላኖች መነሳትና ማረፍ እጅግ ምቹ የአየር ሁኔታን ይሰጣል።
የፕሮጀክቱ ዲዛይን በታዋቂው የለንደን ዘሃ ሃዲድ አርክቴክትስ የተሰራ ሲሆን÷ በውስጡ ዘመናዊ ሆቴሎችን፣ የገበያ ማዕከላትን፣ የንግድና የዕቃ መጋዘን (Cargo) ኮምፕሌክሶችን ያካትታል። አዲሱ አየር ማረፊያ ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር በፈጣን የኤክስፕረስ መንገድ እና በከፍተኛ ፍጥነት ተንቀሳቃሽ የባቡር መስመር እንደሚገናኝ ይጠበቃል፡፡
ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው የኢትዮጵያን አጠቃላይ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እድገት ለማሳለጥ የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ሀገሪቱን ወደ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥን ዘላቂ ሞተር ይሆናል። ይህ ሜጋ ፕሮጀክት የሀገሪቱን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ አበርክቶው ከፍተኛ ነው፡፡
በግንባታው ወቅት በሺህ የሚቆጠሩ መሃንዲሶችንና ሰራተኞችን ቀጥሮ እያሰራ ያለ ሲሆን÷ ሥራ ሲጀምር ደግሞ በአየር መንገዱ፣ በሆቴሎችና በሎጂስቲክስ ዘርፍ ለበርካታ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጥራል። በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን በማስተናገድ ከትራንዚት፣ ከቀረጥ ነፃ ንግድ እና ከአየር መንገድ አገልግሎቶች የሚገኘውን የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል። የአካባቢው የዶሮ፣ የወተት፣ የአትክልትና ፍራፍሬ አምራቾች ለግዙፉ አውሮፕላን ማረፊያና ለሆቴሎቹ ምርቶቻቸውን በስፋት የሚያቀርቡበት ሰፊ የገበያ እድልም ይፈጥርላቸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግርን በሀገር ውስጥ ምርት እድገት፣ በውጪ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትና በውጪ ምንዛሪም ማሳደግን ያስችላል፡፡ ማረፊያው በሚሊየን የሚቆጠሩ መንገደኞችን እና በሚሊየን የሚቆጠር ቶን ጭነት ማስተናገዱ በራሱ ለሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ቀጥተኛ እና ከፍተኛ ድርሻ ያበረክታል።
ምቹ፣ ፈጣን እና ዘመናዊ የአየር ትራንስፖርት እና የሎጂስቲክስ መሠረተ ልማት መኖሩ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ኩባንያዎችና ፋብሪካዎች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ዋነኛ ማበረታቻ ይሆናል።
ከአገልግሎቶች፣ ከነዳጅ ሽያጭ፣ ከትራንዚት ሆቴሎች እና ከቀረጥ ነፃ የንግድ ማዕከላት የሚገኘው ገቢ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ እጥረት በዘላቂነት ይቀርፋል።
የወጪ ንግድ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እድገት በማሳለጥ ረገድም የላቀ ሚና ይጫወታል፡፡ እንደ አበባ፣ ፍራፍሬ፣ አትክልትና ስጋ ያሉ በቀላሉ ሊበላሹ የሚችሉ የኢትዮጵያ እና የሌሎች ሀገራት ወጪ ምርቶች ሳይዘገዩ በጥራት ለዓለም ገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ የገበሬውንና የላኪውን ገቢ ያሳድጋል።
በአውሮፕላን ማረፊያው አቅራቢያ እና በሀገሪቱ ያሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የሚያመርቷቸውን የጨርቃጨርቅ፣ የቆዳ እና የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች በከፍተኛ ፍጥነት ወደ አውሮፓ፣ አሜሪካ እና እስያ ገበያዎች ለማጓጓዝ ምቹ የሎጂስቲክስ ሰንሰለት ይፈጥራል።የአህጉሪቱ የንግድና የሎጂስቲክስ እንቅስቃሴ ዋና ማስተላለፊያ ማዕከል በመሆን የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ተሰሚነት ያጠናክራል።
የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ደግሞ ሌላኛው ትሩፋቱ ይሆናል፡፡ አውሮፕላን ማረፊያው ከማረፊያነት ባለፈ ዘመናዊ ሆቴሎችን፣ የገበያ ማዕከላትን፣ የኤግዚቢሽን ማዕከላትንና የንግድ ህንጻዎችን የያዘ "የኤርፖርት ከተማ" ወይም አዲስ የኢኮኖሚ ከተማ ሆኖ ይገነባል።
አካባቢው ለቱሪዝም ምቹ በመሆኑም ዓለም አቀፍ ቱሪዝምን ይስባል፡፡ በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅሙ፣ በሚሊየን የሚቆጠሩ የትራንዚት መንገደኞች ቢያንስ ለጥቂት ቀናት በሀገሪቱ እንዲቆዩ እና የኢትዮጵያን ታሪካዊና ተፈጥሯዊ መስህቦች እንዲጎበኙ በር ይከፍታል።
የቱሪስቶች ቁጥር መጨመር በሀገር ውስጥ ያሉ ሆቴሎች፣ ሪዞርቶች፣ አስጎብኚ ድርጅቶች እና የባህል ምርቶች አቅራቢዎች ገቢያቸው እንዲያድግ እና ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ያደርጋል።
የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የሰው ኃይል ልማት ላይ የሚኖረው አንድምታም በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ አውሮፕላን ማረፊያው የሚገነባው እጅግ ዘመናዊ በሆኑ የኤክስሬይ፣ የደህንነት፣ የሮቦቲክስ እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂዎች በመሆኑ የሀገር ውስጥ መሃንዲሶች እና ባለሙያዎች ከፍተኛ የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ያስችላል።ከፕሮጀክቱ ጋር ተያይዞ የሚስፋፉት የአቪዬሽን ማሰልጠኛዎች እና የምርምር ማዕከላት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ የእውቀት ማዕከል ያደርጓታል።
በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ክልላዊ የልማት መናኸሪያ ያደርጋታል፡፡ ፕሮጀክቱ ቢሾፍቱን፣ ሞጆን፣ ዱከምንና አዲስ አበባን የሚያስተሳስር አዲስ የኢኮኖሚ ኮሪደር ይፈጥራል። ይህ ከተሞች፣ የንፁህ ውሃ አቅርቦት፣ የኃይል እና የመገናኛ መሠረተ ልማቶችን በጥራት እንዲያድጉ ያደርጋል።
ከዚህ ባለፈም ዓለም አቀፋዊ ትስስርን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ የመጀመሪያው ሚና የዓለም አቀፍ አየር መንገዶች መዳረሻነት ነው፡፡ በዓመት እስከ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም የሚኖረው በመሆኑ፣ ከእስያ፣ ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ እና ከላቲን አሜሪካ የሚነሱ ተያያዥ በረራዎችን በአንድ ማዕከል ያስተናግዳል ፤ ይህም ግዙፍ የመንገደኞች ፍሰትን ይፈጥራል፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል የሆነበት ስታር አሊያንስ እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች አቡሴራን ዋና የምስራቅ አፍሪካ መሸጋገሪያ መናኸሪያቸው ያደርጉታል። የአሊያንስ ማዕከልነታችንንም የምናረጋግጥበት ይሆናል፡፡
ሁለተኛው ሚና የግሎባል ደቡብ ዋነኛ ትስስር ድልድይን መፍጠር ነው፡፡ አዲሱ ማረፊያ አፍሪካን ከላቲን አሜሪካ፣ ከእስያ (በተለይም ከቻይና እና ህንድ) እና ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር በቀጥታና በአጭር ሰዓት የሚያገናኝ ዋነኛ መስመር ይሆናል። ይህ ሲሆን ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን ከዓለም ጋር አስተሳሰርን ማለት ነው፡፡
የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተፈፃሚነት ለማፋጠን ሰዎችንና የንግድ ዕቃዎችን ከአህጉሪቱ ጥግ እስከ ዓለም ጫፍ በፈጣን የሎጂስቲክስ ሰንሰለት ያገናኛል። ለአህጉር አቀፍ ንግድ መነቃቃት አበርክቶው ከፍተኛ ይሆናል፡፡
ሦስተኛው የዓለም አቀፍ የአየር ጭነት ማዕከልነታችንን ማረጋገጥ ነው፡፡ የሚገነባው ግዙፍና ዘመናዊ የካርጎ ተርሚናል የዓለም የንግድ ዕቃዎች እና የህክምና አቅርቦቶች ከአምራች ሀገራት ተነስተው ወደ ተጠቃሚዎች የሚሰራጩበት ዋነኛ የአየር ሎጂስቲክስ ማዕከል እንዲሆን ያደርገዋል። እንደ አበባ፣ ፍራፍሬ እና ስጋ ያሉ የኢትዮጵያና የጎረቤት ሀገራት ምርቶች ሳይበላሹ በጥራትና በከፍተኛ ፍጥነት ወደ መላው ዓለም ገበያ እንዲደርሱ ያስችላል።
ምቹ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እና የአቪዬሽን ብቃት ደግሞ ሌላኛው ሚናው ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም ካርታ ላይ ያላት ስልታዊ አቀማመጥ (በአውሮፓ፣ በእስያ እና በአፍሪካ መገናኛ መስመር ላይ መገኘቷ) አቡሴራን ለዓለም አቀፍ በረራዎች አጭርና ተመራጭ የመሸጋገሪያ መስመር ያደርገዋል።
የአቡሴራ ከፍታ ከአዲስ አበባ ቦሌ ያነሰ በመሆኑ፣ የዓለም አቀፍ በረራ አውሮፕላኖች ሙሉ ነዳጅና ጭነት ይዘው ረጅም ርቀት በቀጥታ እንዲበሩ ሰፊ የአቪዬሽን ምቹነትን ይሰጣል። የአውሮፕላኖች የመጫን አቅምን ጨመረ ማለት ነው።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ እንደ ዱባይ (DXB) እና ሲንጋፖር (Changi) ያሉ ታላላቅ የዓለም መገናኛ ማዕከላት ተርታ ያሰልፋታል።
በአጠቃላይ ሲታይ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ያላትን ስልታዊ፣ ፖለቲካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ተሰሚነት ከማጠናከሩ ባሻገር የሀገሪቱን የኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ፍጥነት የሚያሳልጥ ታላቅ ብሔራዊ ትሩፋት ነው።
2 months ago
ከፈተና ወደ ከፍታ፦ “ኢትዮጵያን ማንም አያሸንፍም” የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል በተግባር ሲገለጥ
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
2 months ago
ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ሙሉ እምነት አላት - አምባሳደር ዳረን ዌልች
**********************
የዩናይትድ ኪንግደም በአፍሪካ አህጉር ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለውን፣ የላቀ የሰነድ ማጭበርበር (ፎርጀሪ) መመርመሪያ የኤቪዬሽን ደኅንነት ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አበርክታለች።
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት፣ ይህ የቴክኒክ ድጋፍ የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ ወዳጅነት እና ስትራቴጂያዊ አጋርነት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በእንግሊዝ ሀገር የተመረተው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረጉንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
ይህም ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ያላትን ሙሉ እምነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አክለዋል።
ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁልፍ የዓለም አቀፍ መተላለፊያ ማዕከል መሆኑን ያነሱት አምባሳደሩ፣ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የእንግሊዝ ዜጎችን ጨምሮ የዓለምን ማኅበረሰብ ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያደርጉትን የላቀ ጥረት አድንቀዋል።
"ሁላችንም ደኅንነታችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የማንም ደኅንነት የተጠበቀ አይሆንም" በማለትም የጋራ ደኅንነትን ፅንሰ-ሀሳብ አስምረውበታል።
ይህ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና ትብብር ድንበር ዘለል የተደራጁ ወንጀሎችን ለመከላከል እንዲሁም የጉዞ መስመሮችን ከሕገ-ወጥ ድርጊቶች ነጻ ለማድረግ የላቀ ሚና ይጫወታል።
አምባሳደሩ እንዳብራሩት የሁለቱ ሀገራት አጋርነት በደኅንነት ዘርፍ ብቻ ሳይወሰን፤ በጤና፣ በትምህርት እና በኢኮኖሚ ልማት ጭምር ሰፊ መሠረት ያለው ነው።
በቀጣይም በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዲዛይን እና ግንባታ ላይ የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዓለም ላይ ካሉ ደኅንነታቸው እጅግ ከተጠበቁ ተርሚናሎች አንዱ እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም አምባሳደሩ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ወደ ሂትሮው፣ ማንችስተር፣ ጋትዊክ እና ግላስኮ የሚደረጉ ዕለታዊ እና መደበኛ በረራዎች የሁለቱን ሀገራት የንግድ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ይበልጥ እያሳደጉት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጠው ይህ የደኅንነት ትብብር ውጤታማነቱ ታይቶ በቀጣይም ተጨማሪ የቴክኖሎጂ ድጋፎች እንደሚደረጉ አመላክተዋል።
#ethiopia #uk #cooperation #aviationsecurity #aviationtech #ethiopianairlines #boleairport #niss #ebc
**********************
የዩናይትድ ኪንግደም በአፍሪካ አህጉር ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለውን፣ የላቀ የሰነድ ማጭበርበር (ፎርጀሪ) መመርመሪያ የኤቪዬሽን ደኅንነት ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አበርክታለች።
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት፣ ይህ የቴክኒክ ድጋፍ የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ ወዳጅነት እና ስትራቴጂያዊ አጋርነት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በእንግሊዝ ሀገር የተመረተው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረጉንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
ይህም ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ያላትን ሙሉ እምነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አክለዋል።
ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁልፍ የዓለም አቀፍ መተላለፊያ ማዕከል መሆኑን ያነሱት አምባሳደሩ፣ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የእንግሊዝ ዜጎችን ጨምሮ የዓለምን ማኅበረሰብ ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያደርጉትን የላቀ ጥረት አድንቀዋል።
"ሁላችንም ደኅንነታችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የማንም ደኅንነት የተጠበቀ አይሆንም" በማለትም የጋራ ደኅንነትን ፅንሰ-ሀሳብ አስምረውበታል።
ይህ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና ትብብር ድንበር ዘለል የተደራጁ ወንጀሎችን ለመከላከል እንዲሁም የጉዞ መስመሮችን ከሕገ-ወጥ ድርጊቶች ነጻ ለማድረግ የላቀ ሚና ይጫወታል።
አምባሳደሩ እንዳብራሩት የሁለቱ ሀገራት አጋርነት በደኅንነት ዘርፍ ብቻ ሳይወሰን፤ በጤና፣ በትምህርት እና በኢኮኖሚ ልማት ጭምር ሰፊ መሠረት ያለው ነው።
በቀጣይም በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዲዛይን እና ግንባታ ላይ የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዓለም ላይ ካሉ ደኅንነታቸው እጅግ ከተጠበቁ ተርሚናሎች አንዱ እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም አምባሳደሩ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ወደ ሂትሮው፣ ማንችስተር፣ ጋትዊክ እና ግላስኮ የሚደረጉ ዕለታዊ እና መደበኛ በረራዎች የሁለቱን ሀገራት የንግድ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ይበልጥ እያሳደጉት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጠው ይህ የደኅንነት ትብብር ውጤታማነቱ ታይቶ በቀጣይም ተጨማሪ የቴክኖሎጂ ድጋፎች እንደሚደረጉ አመላክተዋል።
#ethiopia #uk #cooperation #aviationsecurity #aviationtech #ethiopianairlines #boleairport #niss #ebc
2 months ago
የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማሳደግና ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚያስችል የኤሌክትርክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማሳደግና ዲጅታል ኢትዮጵያን 2030 እውን ለማድረግ የሚያስችል የኤሌክትርክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ አስመርቆ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል፡፡
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተቋሙ ውጤታማ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋትና የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ በርካታ ዘመናዊ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው በተለይም የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የበኩሉን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡
አክለውም በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ ከተማ በበጀት ዓመቱ መጋቢት ወር ስራ ከጀመሩት የኮተቤ፣ የልቡ እና የፒያሳ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች በተጨማሪ፤ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር በአንድ ጊዜ ለ24 መኪኖች አገልግሎት መስጠት የሚችል እጅግ ፈጣንና ዘመናዊ የኃይል መሙያ ጣቢያ ግንባታን አጠናቆ ዛሬ በይፋ መመረቁን አብስረዋል።
ይህ ስራ በአዲስ አበባ ብቻ የሚገደብ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቅርብ ወራት ውስጥ በቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ ባቱ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ እና ሐዋሳ ከተሞች ላይ የሚገነቡት የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር ዶ/ር ፍሰሀ ይታገሱ በበኩላቸው የተመረቀው የኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን በሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ጉዞ ላይ ትልቅና ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ይህንን ታሳቢ በማድረግ ላከናወነው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።
አያይዘውም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማሳደግ የተቋሙ መለያ (ሎጎ) የሆነው «ኢኮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ» ከዚሁ የቻርጅ ስቴሽን ስራ ጋር ትልቅ እንድምታና ቁርኝት እንዳለው በመጠቆም፣ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው ግንኙነት እጅግ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የኢፌዴሪ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ በረኦ ሀሰን በበኩላቸው በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል ያለው ትብብር የሀገሪቱን መጻኢ ዕድል ለመወሰን እጅግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ የኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን ሥራ ለትራንስፖርት ዘርፉ ትልቅ መሠረት እንደሆነ የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው፣ በአሁኑ ሰዓት እንዲህ ያሉ የቻርጂንግ ስቴሽኖችን ማብዛትና በትኩረት መስራት ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ጉዞ የሰጠችውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አያይዘውም፣ የአየር ንብረት ለውጥን (ክላይሜት ቼንጅ) ለመከላከልና የአረንጓዴ አሻራ (ግሪን ሌጋሲ) ውጥኖችን ለማስቀጠል በዚህ ዘርፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ዋነኛውና ቁልፍ ስራ መሆኑን በመግለጽ፣ በዚህ አስደሳችና ተስፋ ሰጪ ስራ ውስጥ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ቁጥር 140 ሺህ የደረሰ ሲሆን ተቋሙ በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ 32 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች 8 በድምሩ 40 የቻርጂንግ ጣቢያዎች ለመገንባት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
ከኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን ምረቃው ጎን ለጎን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ ስራ መርሃ ግብርም ተካሂዷል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር የአረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማሳደግና ዲጅታል ኢትዮጵያን 2030 እውን ለማድረግ የሚያስችል የኤሌክትርክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ አስመርቆ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል፡፡
በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር ጌቱ ገረመው ተቋሙ ውጤታማ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋትና የደንበኞችን እርካታ ለማሳደግ በርካታ ዘመናዊ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው በተለይም የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ለማሳለጥና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የበኩሉን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ ነው ብለዋል፡፡
አክለውም በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ ከተማ በበጀት ዓመቱ መጋቢት ወር ስራ ከጀመሩት የኮተቤ፣ የልቡ እና የፒያሳ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች በተጨማሪ፤ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን (IPDC) ጋር በመተባበር በአንድ ጊዜ ለ24 መኪኖች አገልግሎት መስጠት የሚችል እጅግ ፈጣንና ዘመናዊ የኃይል መሙያ ጣቢያ ግንባታን አጠናቆ ዛሬ በይፋ መመረቁን አብስረዋል።
ይህ ስራ በአዲስ አበባ ብቻ የሚገደብ አይደለም ያሉት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቅርብ ወራት ውስጥ በቢሾፍቱ፣ ሞጆ፣ ባቱ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ እና ሐዋሳ ከተሞች ላይ የሚገነቡት የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ክቡር ዶ/ር ፍሰሀ ይታገሱ በበኩላቸው የተመረቀው የኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን በሀገሪቱ የማኑፋክቸሪንግ ጉዞ ላይ ትልቅና ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መኖራቸውን ጠቅሰው፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ይህንን ታሳቢ በማድረግ ላከናወነው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።
አያይዘውም የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማሳደግ የተቋሙ መለያ (ሎጎ) የሆነው «ኢኮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ» ከዚሁ የቻርጅ ስቴሽን ስራ ጋር ትልቅ እንድምታና ቁርኝት እንዳለው በመጠቆም፣ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው ግንኙነት እጅግ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
የኢፌዴሪ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ በረኦ ሀሰን በበኩላቸው በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት መካከል ያለው ትብብር የሀገሪቱን መጻኢ ዕድል ለመወሰን እጅግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ የኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን ሥራ ለትራንስፖርት ዘርፉ ትልቅ መሠረት እንደሆነ የጠቆሙት ሚኒስትር ዲኤታው፣ በአሁኑ ሰዓት እንዲህ ያሉ የቻርጂንግ ስቴሽኖችን ማብዛትና በትኩረት መስራት ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት ጉዞ የሰጠችውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
አያይዘውም፣ የአየር ንብረት ለውጥን (ክላይሜት ቼንጅ) ለመከላከልና የአረንጓዴ አሻራ (ግሪን ሌጋሲ) ውጥኖችን ለማስቀጠል በዚህ ዘርፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ዋነኛውና ቁልፍ ስራ መሆኑን በመግለጽ፣ በዚህ አስደሳችና ተስፋ ሰጪ ስራ ውስጥ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ቁጥር 140 ሺህ የደረሰ ሲሆን ተቋሙ በመጀመሪያው ምዕራፍ በአዲስ አበባ 32 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች 8 በድምሩ 40 የቻርጂንግ ጣቢያዎች ለመገንባት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡
ከኢቪ (EV) ቻርጅ ስቴሽን ምረቃው ጎን ለጎን በኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ቅጥር ግቢ ውስጥ የችግኝ ተከላ ስራ መርሃ ግብርም ተካሂዷል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
2 months ago
የነገዋ ዓለም መናኸሪያ - የቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ
#ethiopia | በዓለማችን ላይ ያሉ ታላላቅ እና ስመጥር አውሮፕላን ማረፊያዎችን ስንመለከት፣ እንደ አሜሪካው አትላንታ፣ የመካከለኛው ምሥራቁ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ወይም የቻይናው ቤጂንግ ዳክሲንግ የየሀገራቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ እና የደረሱበትን የሥልጣኔ እርከን የሚያንጸባርቁ ግዙፍ የትራንዚት ማዕከሎች ሆነው እናገኛቸዋለን።
በቢሾፍቱ አቡሴራ እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ከእነዚህ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ጋር ሲነጻጸር የሚለየው መሠረታዊ እውነት አለ።
ይኸውም አብዛኞቹ ያደጉ ሀገራት ፕሮጀክቶቻቸውን የሚገነቡት የትናንትን የኢኮኖሚ ድል እና የትራፊክ መጨናነቅን ለማስተናገድ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ግን ይህንን ግዙፍ ከተማ የምትገነባው የነገን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ የበላይነት ለመፍጠር እና ለመምራት መሆኑ ላይ ነው።
ይህ ባለ 110 ሚሊዮን የመንገደኛ አቅም ያለው የአቪዬሽን ከተማ (Aviation City)፣ ሀገራችን ምን ያህል ሩቅ አሻግራ እንደምታይ እና የወደፊቱን የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካዊ አሰላለፍ አስቀድማ ተረድታ ከወዲሁ የላቀ ስትራቴጂካዊ ሥራ እየሠራች መሆኗን በጉልህ የሚያሳይ ነው።
የብሔራዊ ጥቅማችን እና ሉዓላዊ አቅማችን ጽኑ ዐለት
ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ሲመዘን ቀላል የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን፣ የሀገራችን ሉዓላዊ የኢኮኖሚ አቅም የሚያረጋግጥ ጽኑ ዐለት ነው።
በዓለም አቀፉ መድረክ ላይ የሀገራት ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚለካው ሌሎችን ከራስ ጋር በማስተሳሰር በሚፈጠር ጠንካራ ትስስር (Connectivity) ነው።
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ነባር እና ታሪካዊ የበላይነት ወደ ማይቀለበስ ከፍተኛ ደረጃ በማሸጋገር፣ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኘው ብቸኛ እና አስተማማኝ ማዕከል ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ ትስስር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ፍጥነት ከመሳቡም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ ሀገራችን ያላትን የመደራደር አቅም በብዙ እጥፍ ያሳድገዋል።
ሌሎች ሀገራት በነባሩ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ሲዳከሩ፣ ኢትዮጵያ ግን የጨዋታውን ሕግ ራሷ ለመጻፍ የሚያስችላትን ግዙፍ ሀገራዊ መድረክ እያነጸች ትገኛለች።
ራዕይን በተግባር
የኢትዮጵያን ከፍታ እና የረጅም ጊዜ ራዕይ ከማሳካት አንጻር፣ የዚህ ሜጋ አየር ማረፊያ ፋይዳ እጅግ ጥልቅ ነው። መንግሥት ይህንን ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ያሳየው ወደር የለሽ ቁርጠኝነት፣ የሀገራችን ኢኮኖሚ ራሱን የቻለ ኃያል ለማድረግ ያለውን ጽኑ አቋም ያንጸባርቃል።
• ዘመናዊ መሠረተ ልማት፦ በአንድ ጊዜ በርካታ ግዙፍ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ማኮብኮቢያዎች፣ እጅግ ዘመናዊ የነጻ ንግድ ቀጠናዎች፣ እና ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የካርጎ መንደሮች ይኖሩታል።
• የቴክኖሎጂ መሪነት፦ እነዚህ መሠረተ ልማቶች ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ውድድር ጋር እኩል መራመድ ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት ተራምዳ የዘርፉ መሪ መሆን እንደምትችል በተግባር ያረጋግጣሉ።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ የብልጽግና ማረጋገጫ ማኅተም ነው።
ከዱባይ እና ቤጂንግ የትራንዚት ማዕከሎች ጋር ሲነጻጸር፣ የእኛ ፕሮጀክት የተነሣበት ዐውድ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የከፍታ ቦታ መልሳ ለመቀዳጀት የምታደርገውን ስኬታማ ትግል እና የላቀ ስትራቴጂካዊ የኮሙኒኬሽን ትርክት የሚያጎላ ነው።
ይህ የአቪዬሽን ማዕከል ሀገራችን በትውልዶች ቅብብሎሽ ውስጥ የምታስመዘግበው የድል አሻራ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም የምታስተዋውቅበት ግዙፍ መስኮት፣ እንዲሁም ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የሚፈጥር ብሔራዊ ሀብት ነው።
በረጅም ርቀት ራዕይ ላይ ተመሥርቶ እየተገነባ ያለው ይህ ሜጋ ፕሮጀክት፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ በማረጋገጥ በዓለም አደባባይ ደምቃ እንድትታይ የሚያደርግ፣ ዘመናትን የሚሻገር ታላቅ ታሪካዊ ክንውን ነው።
Credit : EBC
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በዓለማችን ላይ ያሉ ታላላቅ እና ስመጥር አውሮፕላን ማረፊያዎችን ስንመለከት፣ እንደ አሜሪካው አትላንታ፣ የመካከለኛው ምሥራቁ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ወይም የቻይናው ቤጂንግ ዳክሲንግ የየሀገራቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ እና የደረሱበትን የሥልጣኔ እርከን የሚያንጸባርቁ ግዙፍ የትራንዚት ማዕከሎች ሆነው እናገኛቸዋለን።
በቢሾፍቱ አቡሴራ እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ከእነዚህ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ጋር ሲነጻጸር የሚለየው መሠረታዊ እውነት አለ።
ይኸውም አብዛኞቹ ያደጉ ሀገራት ፕሮጀክቶቻቸውን የሚገነቡት የትናንትን የኢኮኖሚ ድል እና የትራፊክ መጨናነቅን ለማስተናገድ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ግን ይህንን ግዙፍ ከተማ የምትገነባው የነገን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ የበላይነት ለመፍጠር እና ለመምራት መሆኑ ላይ ነው።
ይህ ባለ 110 ሚሊዮን የመንገደኛ አቅም ያለው የአቪዬሽን ከተማ (Aviation City)፣ ሀገራችን ምን ያህል ሩቅ አሻግራ እንደምታይ እና የወደፊቱን የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካዊ አሰላለፍ አስቀድማ ተረድታ ከወዲሁ የላቀ ስትራቴጂካዊ ሥራ እየሠራች መሆኗን በጉልህ የሚያሳይ ነው።
የብሔራዊ ጥቅማችን እና ሉዓላዊ አቅማችን ጽኑ ዐለት
ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ሲመዘን ቀላል የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን፣ የሀገራችን ሉዓላዊ የኢኮኖሚ አቅም የሚያረጋግጥ ጽኑ ዐለት ነው።
በዓለም አቀፉ መድረክ ላይ የሀገራት ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚለካው ሌሎችን ከራስ ጋር በማስተሳሰር በሚፈጠር ጠንካራ ትስስር (Connectivity) ነው።
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ነባር እና ታሪካዊ የበላይነት ወደ ማይቀለበስ ከፍተኛ ደረጃ በማሸጋገር፣ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኘው ብቸኛ እና አስተማማኝ ማዕከል ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ ትስስር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ፍጥነት ከመሳቡም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ ሀገራችን ያላትን የመደራደር አቅም በብዙ እጥፍ ያሳድገዋል።
ሌሎች ሀገራት በነባሩ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ሲዳከሩ፣ ኢትዮጵያ ግን የጨዋታውን ሕግ ራሷ ለመጻፍ የሚያስችላትን ግዙፍ ሀገራዊ መድረክ እያነጸች ትገኛለች።
ራዕይን በተግባር
የኢትዮጵያን ከፍታ እና የረጅም ጊዜ ራዕይ ከማሳካት አንጻር፣ የዚህ ሜጋ አየር ማረፊያ ፋይዳ እጅግ ጥልቅ ነው። መንግሥት ይህንን ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ያሳየው ወደር የለሽ ቁርጠኝነት፣ የሀገራችን ኢኮኖሚ ራሱን የቻለ ኃያል ለማድረግ ያለውን ጽኑ አቋም ያንጸባርቃል።
• ዘመናዊ መሠረተ ልማት፦ በአንድ ጊዜ በርካታ ግዙፍ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ማኮብኮቢያዎች፣ እጅግ ዘመናዊ የነጻ ንግድ ቀጠናዎች፣ እና ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የካርጎ መንደሮች ይኖሩታል።
• የቴክኖሎጂ መሪነት፦ እነዚህ መሠረተ ልማቶች ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ውድድር ጋር እኩል መራመድ ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት ተራምዳ የዘርፉ መሪ መሆን እንደምትችል በተግባር ያረጋግጣሉ።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ የብልጽግና ማረጋገጫ ማኅተም ነው።
ከዱባይ እና ቤጂንግ የትራንዚት ማዕከሎች ጋር ሲነጻጸር፣ የእኛ ፕሮጀክት የተነሣበት ዐውድ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የከፍታ ቦታ መልሳ ለመቀዳጀት የምታደርገውን ስኬታማ ትግል እና የላቀ ስትራቴጂካዊ የኮሙኒኬሽን ትርክት የሚያጎላ ነው።
ይህ የአቪዬሽን ማዕከል ሀገራችን በትውልዶች ቅብብሎሽ ውስጥ የምታስመዘግበው የድል አሻራ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም የምታስተዋውቅበት ግዙፍ መስኮት፣ እንዲሁም ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የሚፈጥር ብሔራዊ ሀብት ነው።
በረጅም ርቀት ራዕይ ላይ ተመሥርቶ እየተገነባ ያለው ይህ ሜጋ ፕሮጀክት፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ በማረጋገጥ በዓለም አደባባይ ደምቃ እንድትታይ የሚያደርግ፣ ዘመናትን የሚሻገር ታላቅ ታሪካዊ ክንውን ነው።
Credit : EBC
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አዳዲስ የፍራፍሬ ዝርያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተዋል
***********************
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለምርታማነት የሚረዱ ከአሥር በላይ አዳዲስ የፍራፍሬ ችግኝ ዝርያዎች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በቢሾፍቱ ከተማ ሲያስጀምሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በመርሐ ግብሩ የተገኙ ዘላቂ በረከቶች መኖራቸውን ጠቁመው፣ የተለያዩ የካካዎ እና የሮማን ዝርያዎችን በማስገባት፣ በአሁኑ ወቅት ችግኞችን የማፍላትና የመትከል ሥራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት በካካዎ፣ በአዳዲስ የሮማን ዝርያዎች፣ ማካዴሚያ በተሰኘ ምርት እና ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ባልተለመዱ የፍራፍሬ ምርቶች ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ እንደምትቀላቀል አስገንዝበዋል።
"የምናባዛቸውና የምንተክላቸው የፍራፍሬ ዘሮች ምርታቸውን ለምግብ ዋስትናችን የምንጠቀምባቸው በመሆናቸው፤ ዘሮቹን ባገኘን ቁጥር ማፍላት፣ ማባዛትና መትከል ይገባናል። በዚህ ሂደት ውስጥም ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ከሁላችንም የሚጠበቅ ተግባር ነው" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለአፈር መሸርሸርና ለተፈጥሮ ጥበቃ ያለውን አስተዋፅኦ ያነሱት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ አፈራችንን ከስደት (ከመታጠብ) እንዲሁም ግድቦቻችንን ከደለል መከላከል ስንችል፣ የጎደሉ ሐይቆችና ኩሬዎች ይሞላሉ ብለዋል።
አምርቶ የመመገብ ባህልን በማሳደግ የኢትዮጵያ ግብርና ሊደርስበት የሚችለውን ታላቅ ከፍታ በተግባር ማሳየት እንደሚቻልም ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ethiopianbroadcastingcorporation #fruits #ethiopia #green #legacy
***********************
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለምርታማነት የሚረዱ ከአሥር በላይ አዳዲስ የፍራፍሬ ችግኝ ዝርያዎች ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በቢሾፍቱ ከተማ ሲያስጀምሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በመርሐ ግብሩ የተገኙ ዘላቂ በረከቶች መኖራቸውን ጠቁመው፣ የተለያዩ የካካዎ እና የሮማን ዝርያዎችን በማስገባት፣ በአሁኑ ወቅት ችግኞችን የማፍላትና የመትከል ሥራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት በካካዎ፣ በአዳዲስ የሮማን ዝርያዎች፣ ማካዴሚያ በተሰኘ ምርት እና ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ባልተለመዱ የፍራፍሬ ምርቶች ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ እንደምትቀላቀል አስገንዝበዋል።
"የምናባዛቸውና የምንተክላቸው የፍራፍሬ ዘሮች ምርታቸውን ለምግብ ዋስትናችን የምንጠቀምባቸው በመሆናቸው፤ ዘሮቹን ባገኘን ቁጥር ማፍላት፣ ማባዛትና መትከል ይገባናል። በዚህ ሂደት ውስጥም ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር ከሁላችንም የሚጠበቅ ተግባር ነው" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለአፈር መሸርሸርና ለተፈጥሮ ጥበቃ ያለውን አስተዋፅኦ ያነሱት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ አፈራችንን ከስደት (ከመታጠብ) እንዲሁም ግድቦቻችንን ከደለል መከላከል ስንችል፣ የጎደሉ ሐይቆችና ኩሬዎች ይሞላሉ ብለዋል።
አምርቶ የመመገብ ባህልን በማሳደግ የኢትዮጵያ ግብርና ሊደርስበት የሚችለውን ታላቅ ከፍታ በተግባር ማሳየት እንደሚቻልም ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ethiopianbroadcastingcorporation #fruits #ethiopia #green #legacy
Comments