4 days ago
ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ሙሉ እምነት አላት - አምባሳደር ዳረን ዌልች
**********************
የዩናይትድ ኪንግደም በአፍሪካ አህጉር ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለውን፣ የላቀ የሰነድ ማጭበርበር (ፎርጀሪ) መመርመሪያ የኤቪዬሽን ደኅንነት ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አበርክታለች።
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት፣ ይህ የቴክኒክ ድጋፍ የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ ወዳጅነት እና ስትራቴጂያዊ አጋርነት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በእንግሊዝ ሀገር የተመረተው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረጉንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
ይህም ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ያላትን ሙሉ እምነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አክለዋል።
ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁልፍ የዓለም አቀፍ መተላለፊያ ማዕከል መሆኑን ያነሱት አምባሳደሩ፣ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የእንግሊዝ ዜጎችን ጨምሮ የዓለምን ማኅበረሰብ ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያደርጉትን የላቀ ጥረት አድንቀዋል።
"ሁላችንም ደኅንነታችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የማንም ደኅንነት የተጠበቀ አይሆንም" በማለትም የጋራ ደኅንነትን ፅንሰ-ሀሳብ አስምረውበታል።
ይህ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና ትብብር ድንበር ዘለል የተደራጁ ወንጀሎችን ለመከላከል እንዲሁም የጉዞ መስመሮችን ከሕገ-ወጥ ድርጊቶች ነጻ ለማድረግ የላቀ ሚና ይጫወታል።
አምባሳደሩ እንዳብራሩት የሁለቱ ሀገራት አጋርነት በደኅንነት ዘርፍ ብቻ ሳይወሰን፤ በጤና፣ በትምህርት እና በኢኮኖሚ ልማት ጭምር ሰፊ መሠረት ያለው ነው።
በቀጣይም በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዲዛይን እና ግንባታ ላይ የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዓለም ላይ ካሉ ደኅንነታቸው እጅግ ከተጠበቁ ተርሚናሎች አንዱ እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም አምባሳደሩ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ወደ ሂትሮው፣ ማንችስተር፣ ጋትዊክ እና ግላስኮ የሚደረጉ ዕለታዊ እና መደበኛ በረራዎች የሁለቱን ሀገራት የንግድ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ይበልጥ እያሳደጉት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጠው ይህ የደኅንነት ትብብር ውጤታማነቱ ታይቶ በቀጣይም ተጨማሪ የቴክኖሎጂ ድጋፎች እንደሚደረጉ አመላክተዋል።
#ethiopia #uk #cooperation #aviationsecurity #aviationtech #ethiopianairlines #boleairport #niss #ebc
**********************
የዩናይትድ ኪንግደም በአፍሪካ አህጉር ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የሚውለውን፣ የላቀ የሰነድ ማጭበርበር (ፎርጀሪ) መመርመሪያ የኤቪዬሽን ደኅንነት ቴክኖሎጂ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አበርክታለች።
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት፣ ይህ የቴክኒክ ድጋፍ የሁለቱን ሀገራት የጠበቀ ወዳጅነት እና ስትራቴጂያዊ አጋርነት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በእንግሊዝ ሀገር የተመረተው ይህ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረጉንም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።
ይህም ዩናይትድ ኪንግደም በኢትዮጵያ የደኅንነት አቅም ላይ ያላትን ሙሉ እምነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አክለዋል።
ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቁልፍ የዓለም አቀፍ መተላለፊያ ማዕከል መሆኑን ያነሱት አምባሳደሩ፣ የተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች የእንግሊዝ ዜጎችን ጨምሮ የዓለምን ማኅበረሰብ ደኅንነት ለመጠበቅ የሚያደርጉትን የላቀ ጥረት አድንቀዋል።
"ሁላችንም ደኅንነታችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የማንም ደኅንነት የተጠበቀ አይሆንም" በማለትም የጋራ ደኅንነትን ፅንሰ-ሀሳብ አስምረውበታል።
ይህ የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና ትብብር ድንበር ዘለል የተደራጁ ወንጀሎችን ለመከላከል እንዲሁም የጉዞ መስመሮችን ከሕገ-ወጥ ድርጊቶች ነጻ ለማድረግ የላቀ ሚና ይጫወታል።
አምባሳደሩ እንዳብራሩት የሁለቱ ሀገራት አጋርነት በደኅንነት ዘርፍ ብቻ ሳይወሰን፤ በጤና፣ በትምህርት እና በኢኮኖሚ ልማት ጭምር ሰፊ መሠረት ያለው ነው።
በቀጣይም በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዲዛይን እና ግንባታ ላይ የራሳቸውን ድርሻ ለመወጣት ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዓለም ላይ ካሉ ደኅንነታቸው እጅግ ከተጠበቁ ተርሚናሎች አንዱ እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ዩናይትድ ኪንግደም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላትም አምባሳደሩ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ወደ ሂትሮው፣ ማንችስተር፣ ጋትዊክ እና ግላስኮ የሚደረጉ ዕለታዊ እና መደበኛ በረራዎች የሁለቱን ሀገራት የንግድ እና የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ይበልጥ እያሳደጉት መሆኑን አምባሳደሩ አንስተዋል።
የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጠው ይህ የደኅንነት ትብብር ውጤታማነቱ ታይቶ በቀጣይም ተጨማሪ የቴክኖሎጂ ድጋፎች እንደሚደረጉ አመላክተዋል።
#ethiopia #uk #cooperation #aviationsecurity #aviationtech #ethiopianairlines #boleairport #niss #ebc
12 days ago
ከባንክ ሰልፍ ወደ አንድ ንክኪ፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ እውነታዎች
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
2 months ago
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የኮምዩኒኬሽን የትስስር ገጾችን ይጎብኙ፡፡ ለሀገርዎ ብሔራዊ ደኅንነት መረጋገጥ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ!
ኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም፡- https://niss.gov.et
ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/61574...
ኤክስ (ትዊተር)፡- https://x.com/NissEthiopia
ዩቲዩብ፡- https://www.youtube.com/@N...
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
2 months ago
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የኮምዩኒኬሽን የትስስር ገጾችን ይጎብኙ፡፡ ለሀገርዎ ብሔራዊ ደኅንነት መረጋገጥ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ!
ኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም፡- https://niss.gov.et
ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/61574...
ኤክስ (ትዊተር)፡- https://x.com/NissEthiopia
ዩቲዩብ፡- https://www.youtube.com/@N...
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
ኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም፡- https://niss.gov.et
ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/61574...
ኤክስ (ትዊተር)፡- https://x.com/NissEthiopia
ዩቲዩብ፡- https://www.youtube.com/@N...
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
2 months ago
ለሀገርዎ ብሔራዊ ደኅንነት መረጋገጥ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ!
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት የኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም እና የማኅበራዊ ትስስር ገጾችንም ይጎብኙ፡፡
ኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም፡- https://niss.gov.et
ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/61574...
ኤክስ (ትዊተር)፡- https://x.com/NissEthiopia
ዩቲዩብ፡- https://www.youtube.com/@N...
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት
7 months ago
ከ100 ቢሊየን ብር በላይ በመሰወር ወንጀል የተጠረጠሩ የስፖርት አወራራጅ ድርጅት ባለቤቶችና ተባባሪዎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ገልጿል።
መ/ቤቱ ፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን መቆየቱን አመልክቷል።
በዚህም ፦
- ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት የማይሠሩ፣
- በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው
- ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው መገኘታቸውን ገልጿል።
ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።
በተለይ በሕጋዊነት ሽፋን ፈቃድ ያወጡት ድርጅቶች ላይ ክትትል ለማድረግ ሙከራ በተደረገበት ወቅት ሁሉም ፈቃድ ሲያወጡ ይዘውት ከነበረው ቢሮ መልቀቃቸውና አድራሻቸውን መሰወራቸው መረጋገጡን ገልጿል።
የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ተብለው ከሚጠሩ የፋይናንስ ስርዓቶችን ከሚያሳልጡላቸው የሀገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማት ጋር በመመሳጠር በአጠቃላይ ሲያንቀሳቅሱት ከነበረው የገንዘብ መጠን መንግሥት በተለያዩ የገቢ አማራጮች ማግኘት የነበረበትን 100 ቢሊየን ብር በላይ መሰወራቸው እንደተደረሰበት አመላክቷል፡፡
የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ በተለያዩ የገንዘብ ክፍያ ስርዓቶች አማካይነት የሚሰበስቡትንና የሚያዘዋውሩትን የገንዘብ መጠን ያማከለ ግብር አለመክፈላቸው እንደተደረሰበት ጠቁሟል።
እንዲሁም በክሪፕቶከረንሲ እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሃዋላ ገንዘብ ማስተላላፊያ አማራጮች አማካኝነት የሚያገኙትን ገቢ በውጭ ምንዛሪ በመቀየር ሲሰውሩና ከሀገር እንዲወጣ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጷል።
ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር የሚባሉት የሀገር ውስጥ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማቱ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፤ የደንበኛን ምስጢር መጠበቅ የሚል ሙያዊ አሠራርን እንደ ሽፋን ተጠቅመው የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን የገንዘብ መጠን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አስፈፃሚ ተቋማት በመደበቅ ወይም አሳንሶ በማቅረብ በግብር ስወራ እንዲሁም ከፍተኛ የሀገር ሀብትን ወደ ውጭ በማሸሽ ወንጀል ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው አመልክቷል።
የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ገለሠቦች ጭምር ከኢትዮጵያ ውጪ ሆነው ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተባባሪዎቻችው ውክልና በመስጠት ሕገ-ወጥ ድርጊቱን ሲፈጸሙ መቆየታቸው እንዲሁም ውጭ ሀገር የበለጸጉ ሶፍትዌሮች ጥቅም ላይ መዋላቸውና ድርጅቶቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው መሆኑ ወንጀሉን ውስብስብና ለቁጥጥር አስቸጋሪ አድርጎት እንደቆየ ገልጿል።
ምንም እንኳን ጉዳዩ ውስብስብ ቢሆንም የደኅንነት ተቋሙ ከሌሎች የመረጃና የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ተጠርጣሪዎቹን መያዙን አመልክቷል።
ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ስለ ተጠርጣሪዎች ማንነት እንዲሁም ስለ ቤቲንግ ድርጅቶቹ (ስም) ፣ በህገወጥ ስራ ተሰማርተው የተገኙት የትኞቹ የፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ድርጅቶች እንደሆኑ ለጊዜው በይፋ ያለው ነገር የለም።
#fmc
#niss
መ/ቤቱ ፤ በቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶችና ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር በሚባሉ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተባባሪ ተቋማት ዙሪያ ጥናትና ክትትል ሲከናወን መቆየቱን አመልክቷል።
በዚህም ፦
- ፈቃድ ያላቸውና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በገቡት ውል መሰረት የማይሠሩ፣
- በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው በመገኘታቸው ፈቃዳቸው የተሰረዘባቸው
- ምንም አይነት ፈቃድ ሳይኖራቸው በስፖርት አወራራጅነት ተሰማርተው የነበሩ አካላት በዓለም አቀፍ የኢንተርኔት ትስስር አማካይነት በሕገ-ወጥ ድርጊት ተሰማርተው መገኘታቸውን ገልጿል።
ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የፀጥታ አካላት እንዲሁም በኅብረተሰቡ ትብብር 24 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።
በተለይ በሕጋዊነት ሽፋን ፈቃድ ያወጡት ድርጅቶች ላይ ክትትል ለማድረግ ሙከራ በተደረገበት ወቅት ሁሉም ፈቃድ ሲያወጡ ይዘውት ከነበረው ቢሮ መልቀቃቸውና አድራሻቸውን መሰወራቸው መረጋገጡን ገልጿል።
የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ተብለው ከሚጠሩ የፋይናንስ ስርዓቶችን ከሚያሳልጡላቸው የሀገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማት ጋር በመመሳጠር በአጠቃላይ ሲያንቀሳቅሱት ከነበረው የገንዘብ መጠን መንግሥት በተለያዩ የገቢ አማራጮች ማግኘት የነበረበትን 100 ቢሊየን ብር በላይ መሰወራቸው እንደተደረሰበት አመላክቷል፡፡
የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶቹ በተለያዩ የገንዘብ ክፍያ ስርዓቶች አማካይነት የሚሰበስቡትንና የሚያዘዋውሩትን የገንዘብ መጠን ያማከለ ግብር አለመክፈላቸው እንደተደረሰበት ጠቁሟል።
እንዲሁም በክሪፕቶከረንሲ እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሃዋላ ገንዘብ ማስተላላፊያ አማራጮች አማካኝነት የሚያገኙትን ገቢ በውጭ ምንዛሪ በመቀየር ሲሰውሩና ከሀገር እንዲወጣ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጷል።
ፊንቴክ ወይም አግሪጌተር የሚባሉት የሀገር ውስጥ የገንዘብ ክፍያ ስርዓት አቅራቢ ተቋማቱ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በመውሰድ የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፤ የደንበኛን ምስጢር መጠበቅ የሚል ሙያዊ አሠራርን እንደ ሽፋን ተጠቅመው የቤቲንግ የስፖርት አወራራጅ ድርጅቶች የሚያንቀሳቅሱትን የገንዘብ መጠን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አስፈፃሚ ተቋማት በመደበቅ ወይም አሳንሶ በማቅረብ በግብር ስወራ እንዲሁም ከፍተኛ የሀገር ሀብትን ወደ ውጭ በማሸሽ ወንጀል ላይ ተሳትፎ እንዳላቸው አመልክቷል።
የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ገለሠቦች ጭምር ከኢትዮጵያ ውጪ ሆነው ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተባባሪዎቻችው ውክልና በመስጠት ሕገ-ወጥ ድርጊቱን ሲፈጸሙ መቆየታቸው እንዲሁም ውጭ ሀገር የበለጸጉ ሶፍትዌሮች ጥቅም ላይ መዋላቸውና ድርጅቶቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው መሆኑ ወንጀሉን ውስብስብና ለቁጥጥር አስቸጋሪ አድርጎት እንደቆየ ገልጿል።
ምንም እንኳን ጉዳዩ ውስብስብ ቢሆንም የደኅንነት ተቋሙ ከሌሎች የመረጃና የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ተጠርጣሪዎቹን መያዙን አመልክቷል።
ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ስለ ተጠርጣሪዎች ማንነት እንዲሁም ስለ ቤቲንግ ድርጅቶቹ (ስም) ፣ በህገወጥ ስራ ተሰማርተው የተገኙት የትኞቹ የፊንቴክ ወይም አግሪጌተር ድርጅቶች እንደሆኑ ለጊዜው በይፋ ያለው ነገር የለም።
#fmc
#niss
Sponsored by
Surafel
7 months ago
"519 የባንክ አካውንቶች ታግደዋል " - አገልግሎት መ/ቤቱ
➡ " 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። "
⚫ " የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይ ርምጃ ተወስዷል። "
#ethiopia | የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ፤ በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ተደረሰባቸው ያላቸውን 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፥ ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በሕብረተሰቡ ጥቆማ በፋይናንስ አሻጥር ላይ በተሰማሩ አካላት ላይ ስምሪት መደረጉን አመልክቷል።
በዚህም 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ገልጿል፡፡
ከሕገ ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው 519 የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውንም ጠቅሷል፡፡
° ሕገ ወጥ ሃዋላዎች ፣
° የገንዘብ ዝውውሮች፣
° የውጭ ምንዛሪ ስወራዎች ፣
° የግብር ስወራዎች፣
° ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን አመልክቷል።
በተለይም ፦
- ሕገ ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፣
- ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፣
- የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፣
- ሕገ ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፣
- በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ጠቁሟል።
በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም ርምጃው እንደተወሰደባቸው አሳውቋል።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ አመልክቷል።
የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም ርምጃ እንደተወሰደ አመልክቷል።
አሁንም የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎቱ በላከልን መግለጫ አሳውቋል ያለው ቲክቫህ ነው።
➡ " 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። "
⚫ " የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይ ርምጃ ተወስዷል። "
#ethiopia | የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ፤ በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ተደረሰባቸው ያላቸውን 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፥ ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በሕብረተሰቡ ጥቆማ በፋይናንስ አሻጥር ላይ በተሰማሩ አካላት ላይ ስምሪት መደረጉን አመልክቷል።
በዚህም 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ገልጿል፡፡
ከሕገ ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው 519 የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውንም ጠቅሷል፡፡
° ሕገ ወጥ ሃዋላዎች ፣
° የገንዘብ ዝውውሮች፣
° የውጭ ምንዛሪ ስወራዎች ፣
° የግብር ስወራዎች፣
° ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን አመልክቷል።
በተለይም ፦
- ሕገ ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፣
- ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፣
- የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፣
- ሕገ ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፣
- በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ጠቁሟል።
በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም ርምጃው እንደተወሰደባቸው አሳውቋል።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ አመልክቷል።
የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም ርምጃ እንደተወሰደ አመልክቷል።
አሁንም የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎቱ በላከልን መግለጫ አሳውቋል ያለው ቲክቫህ ነው።
7 months ago
" 519 የባንክ አካውንቶች ታግደዋል " - አገልግሎት መ/ቤቱ
➡ " 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። "
⚫ " የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይ ርምጃ ተወስዷል። "
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ፤ በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ተደረሰባቸው ያላቸውን 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፥ ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በሕብረተሰቡ ጥቆማ በፋይናንስ አሻጥር ላይ በተሰማሩ አካላት ላይ ስምሪት መደረጉን አመልክቷል።
በዚህም 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ገልጿል፡፡
ከሕገ ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው 519 የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውንም ጠቅሷል፡፡
° ሕገ ወጥ ሃዋላዎች ፣
° የገንዘብ ዝውውሮች፣
° የውጭ ምንዛሪ ስራዎች ፣
° የግብር ስራዎች፣
° ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን አመልክቷል።
በተለይም ፦
- ሕገ ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፣
- ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፣
- የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፣
- ሕገ ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፣
- በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ጠቁሟል።
በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም ርምጃው እንደተወሰደባቸው አሳውቋል።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ አመልክቷል።
የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም ርምጃ እንደተወሰደ አመልክቷል።
አሁንም የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎቱ አሳውቋል።
seledadotio
seledadotio
➡ " 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። "
⚫ " የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይ ርምጃ ተወስዷል። "
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ፤ በተቀናጀ መንገድ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ተደረሰባቸው ያላቸውን 112 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገለጸ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፥ ከፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በሕብረተሰቡ ጥቆማ በፋይናንስ አሻጥር ላይ በተሰማሩ አካላት ላይ ስምሪት መደረጉን አመልክቷል።
በዚህም 112 ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ገልጿል፡፡
ከሕገ ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው 519 የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውንም ጠቅሷል፡፡
° ሕገ ወጥ ሃዋላዎች ፣
° የገንዘብ ዝውውሮች፣
° የውጭ ምንዛሪ ስራዎች ፣
° የግብር ስራዎች፣
° ሕገ ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን አመልክቷል።
በተለይም ፦
- ሕገ ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፣
- ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፣
- የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፣
- ሕገ ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፣
- በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ ርምጃ መወሰዱን ጠቁሟል።
በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም ርምጃው እንደተወሰደባቸው አሳውቋል።
በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ አመልክቷል።
የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም ርምጃ እንደተወሰደ አመልክቷል።
አሁንም የሚወሰደው ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አገልግሎቱ አሳውቋል።
seledadotio
seledadotio
9 months ago
አስመሳዩ 'ደህንነት' በቁጥጥር ስር ዋለ‼️
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት (NISS) አባል ነኝ እያለ ህብረተሰቡን ሲያስፈራራና ሲያግት ገንዘብ ሲቀበል የነበረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ዳዊት ጥላሁን ወይም ምንተስኖት ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ሐሰተኛ የNISS መታወቂያ በመጠቀም ወንጀሉን ይፈጽም ነበር። ከህብረተሰቡ የመጣውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የአዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ ባደረጉት ክትትል፣ ግለሰቡ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ውሏል።
ይህ ተጠርጣሪ ከሜክሲኮ ወደ ጋርመንት በታክሲ እየተጓዘች የነበረችውን ሳሮን ተስፋዬ የተባለች ግል ተበዳይን 'ደህንነት ነኝ' በማለት በማስፈራራት እና በመደብደብ ጉዳት ያደረሰባት ሲሆን፣ ጉዳዩ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱ ይታወሳል። ፖሊስ ግለሰቡ በፈጸመው ጉዳት በህግ እንደሚጠየቅ አስታውቋል።
በቁጥጥር ስር በዋለበት ወቅትም ሐሰተኛ መታወቂያው ተይዟል።
ጥሪ ለህብረተሰቡ
የአዲስ አበባ ፖሊስ በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የተፈጸመበት ግለሰብ ወይም ስለ ተጠርጣሪው ማንኛውም መረጃ ያለው ሰው ለመምሪያው በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
እንዲሁም፣ የጸጥታ አካላት አባል ነን በማለት የሚያስፈራሩና ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ግለሰቦች ሲያጋጥሙ በወቅቱ ለፖሊስ እንዲያሳውቁ መልዕክት አስተላልፏል።
የደህንነት አካል ነኝ ብለው የሚያስፈራሩ ግለሰቦችን ሲያጋጥም ምን ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ጥንቃቄ ያድርጉ እና ሪፖርት ያድርጉ!
Via AAP
seledadotio
seledadotio
የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት (NISS) አባል ነኝ እያለ ህብረተሰቡን ሲያስፈራራና ሲያግት ገንዘብ ሲቀበል የነበረ ግለሰብ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።
ዳዊት ጥላሁን ወይም ምንተስኖት ጥላሁን የተባለው ተጠርጣሪ ሐሰተኛ የNISS መታወቂያ በመጠቀም ወንጀሉን ይፈጽም ነበር። ከህብረተሰቡ የመጣውን ጥቆማ መሰረት በማድረግ፣ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የአዲስ አበባ ፖሊስ በጋራ ባደረጉት ክትትል፣ ግለሰቡ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ውሏል።
ይህ ተጠርጣሪ ከሜክሲኮ ወደ ጋርመንት በታክሲ እየተጓዘች የነበረችውን ሳሮን ተስፋዬ የተባለች ግል ተበዳይን 'ደህንነት ነኝ' በማለት በማስፈራራት እና በመደብደብ ጉዳት ያደረሰባት ሲሆን፣ ጉዳዩ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱ ይታወሳል። ፖሊስ ግለሰቡ በፈጸመው ጉዳት በህግ እንደሚጠየቅ አስታውቋል።
በቁጥጥር ስር በዋለበት ወቅትም ሐሰተኛ መታወቂያው ተይዟል።
ጥሪ ለህብረተሰቡ
የአዲስ አበባ ፖሊስ በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የተፈጸመበት ግለሰብ ወይም ስለ ተጠርጣሪው ማንኛውም መረጃ ያለው ሰው ለመምሪያው በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
እንዲሁም፣ የጸጥታ አካላት አባል ነን በማለት የሚያስፈራሩና ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ግለሰቦች ሲያጋጥሙ በወቅቱ ለፖሊስ እንዲያሳውቁ መልዕክት አስተላልፏል።
የደህንነት አካል ነኝ ብለው የሚያስፈራሩ ግለሰቦችን ሲያጋጥም ምን ማድረግ እንዳለብዎ ያውቃሉ? ጥንቃቄ ያድርጉ እና ሪፖርት ያድርጉ!
Via AAP
seledadotio
seledadotio
Comments