2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዛሬ 15 ዓመት ገደማ በፈረንጆቹ ግንቦት 2011፣ በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት የምትገኝ አንዲት ትንሽ ከተማ በአሰቃቂ ድርጊት ተናወጠች። ከትውልድ አገሯ ኢትዮጵያ የተሻለ ሕይወትና ፍቅር ፍለጋ የመጣችው የ13 ዓመቷ ታዳጊ ሃና አለሙ (Hana Williams)፣ ማንም ሰብዓዊ ፍጡር ሊሸከመው የማይችለውን ስቃይና ፍጹም ጭካኔ በአሳዳጊ ወላጆቿ እጅ ካስተናገደች በኋላ፣ በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት በጭቃ ላይ ወድቃ ሕይወቷ አለፈ።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
19 days ago
ለሜሲ ያማል!
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኒውዮርክ ሰማይ ስር የእግር ኳስ ታሪክ አዲስ ንጉስ መውለዱን ለዓለም አውጇል።
የሊዮኔል ሜሲን የመጨረሻ ዳንስ ለመመልከት በተሰበሰበው የዓለም ሕዝብ ፊት ሳይጠበቅ የመጣው የስፔን የአዳጊዎች ስብስብ የክብር ዘውዱን ነጥቋል።
ይህ ድል የስፔን ብቻ አይደለም፤ በሜሲ እጅ ገላውን ታጥቦ ያደገው የላሚን ያማል የንግስና ዘመን ይፋዊ ማብሰሪያ ጭምር እንጂ፡፡
ታሪካዊው ፍልሚያ ከመጀመሩ በፊት ዓለም ሁሉ ትኩረቱን በሜሲና በአዳጊው ያማል የ2007 ድንቅ የፎቶ ትዝታ ላይ አድርጎ ነበር።
ሜሲ በበጎ አድራጎት መርሐ ግብር ላይ ገላውን ያጠበው የያኔው ሕፃኑ ያማል፥ ዛሬ በ19 ዓመቱ ድንቅ ጥበብ እያሳየ ለአርጀንቲና ፈተና ሆኖ ቀረበ።
በኒውዮርክ ስታዲየም የታየው ትዕይንት ድንቅ ነበር፤ ሜሲ ዘውዱን ለተተኪው አስረክቦ የዓለም ዋንጫውን ሲያጠናቅቅ ያማል ደግሞ አዲሱ የዓለም እግር ኳስ መሪ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ የስፔን ወጣት ስብስብ በውድድሩ ጉዞው ቀላል አልነበረም።
ገና ከጅምሩ በጥንካሬና በማይበገረው የኬፕ ቨርዴ ስብስብ ብርቱ ፈተና ገጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ ያንን አስቸጋሪ ውቅያኖስ በፅናት ተሻግሯል።
ሜሲ እና የአርጀንቲናው ወርቃማ ትውልድ የስፔንን የወጣቶች ስብስብ የዋንጫ ጥማት ግን ሊገቱት አልቻሉም።
ቫሞስ! አዲሱ ዘመን ጀምሯል።
"ለሜሲ ያማል" የሚለው ድምጽ አሁን በስታዲየሙ ውስጥ ያስተጋባል።
በአንድ በኩል ለታላቁ ንጉስ ሜሲ የመጨረሻ ጉዞ የተሰማ ቁጭት ሲሆን፥ በሌላ በኩል ደግሞ በላሚን ያማል መነሳት የተፈጠረ አዲስ እምቅ ስሜት ነው።
የስፔን ከዋክብት "ቫሞስ" እያሉ ዋንጫውን ወደ ሰማይ ሲያነሱ፥ እግር ኳስ አዲስ ምዕራፍ መጀመሯን አረጋግጣለች።
ታሪኩ ተፈጽሟል፤ ንጉሱ ሜሲ በታላቅ ክብር ተሰናብቷል፤ አዲሱ ንጉስ ያማል ደግሞ በኒውዮርክ ሰማይ ስር ዘውዱን ደፍቷል፡፡
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኒውዮርክ ሰማይ ስር የእግር ኳስ ታሪክ አዲስ ንጉስ መውለዱን ለዓለም አውጇል።
የሊዮኔል ሜሲን የመጨረሻ ዳንስ ለመመልከት በተሰበሰበው የዓለም ሕዝብ ፊት ሳይጠበቅ የመጣው የስፔን የአዳጊዎች ስብስብ የክብር ዘውዱን ነጥቋል።
ይህ ድል የስፔን ብቻ አይደለም፤ በሜሲ እጅ ገላውን ታጥቦ ያደገው የላሚን ያማል የንግስና ዘመን ይፋዊ ማብሰሪያ ጭምር እንጂ፡፡
ታሪካዊው ፍልሚያ ከመጀመሩ በፊት ዓለም ሁሉ ትኩረቱን በሜሲና በአዳጊው ያማል የ2007 ድንቅ የፎቶ ትዝታ ላይ አድርጎ ነበር።
ሜሲ በበጎ አድራጎት መርሐ ግብር ላይ ገላውን ያጠበው የያኔው ሕፃኑ ያማል፥ ዛሬ በ19 ዓመቱ ድንቅ ጥበብ እያሳየ ለአርጀንቲና ፈተና ሆኖ ቀረበ።
በኒውዮርክ ስታዲየም የታየው ትዕይንት ድንቅ ነበር፤ ሜሲ ዘውዱን ለተተኪው አስረክቦ የዓለም ዋንጫውን ሲያጠናቅቅ ያማል ደግሞ አዲሱ የዓለም እግር ኳስ መሪ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ የስፔን ወጣት ስብስብ በውድድሩ ጉዞው ቀላል አልነበረም።
ገና ከጅምሩ በጥንካሬና በማይበገረው የኬፕ ቨርዴ ስብስብ ብርቱ ፈተና ገጥሞት የነበረ ቢሆንም፤ ያንን አስቸጋሪ ውቅያኖስ በፅናት ተሻግሯል።
ሜሲ እና የአርጀንቲናው ወርቃማ ትውልድ የስፔንን የወጣቶች ስብስብ የዋንጫ ጥማት ግን ሊገቱት አልቻሉም።
ቫሞስ! አዲሱ ዘመን ጀምሯል።
"ለሜሲ ያማል" የሚለው ድምጽ አሁን በስታዲየሙ ውስጥ ያስተጋባል።
በአንድ በኩል ለታላቁ ንጉስ ሜሲ የመጨረሻ ጉዞ የተሰማ ቁጭት ሲሆን፥ በሌላ በኩል ደግሞ በላሚን ያማል መነሳት የተፈጠረ አዲስ እምቅ ስሜት ነው።
የስፔን ከዋክብት "ቫሞስ" እያሉ ዋንጫውን ወደ ሰማይ ሲያነሱ፥ እግር ኳስ አዲስ ምዕራፍ መጀመሯን አረጋግጣለች።
ታሪኩ ተፈጽሟል፤ ንጉሱ ሜሲ በታላቅ ክብር ተሰናብቷል፤ አዲሱ ንጉስ ያማል ደግሞ በኒውዮርክ ሰማይ ስር ዘውዱን ደፍቷል፡፡
በኃይለኢየሱስ መኮንን
21 days ago
የባሕር በር ፍላጎት፤ ለትውልድ ምንዳ እንጂ ዕዳ ላለማውረስ የተጀመረ ጉዞ
********
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ነፃነትና የፖለቲካ ልዕልና በጥብቅ ከተፈጥሮ በረከቶችና ከጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ ጋር የተሳሰሩ በመሆናቸው፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበርና የሀገርን ክብር ለመመለስ የጀመረችው የባሕር በር ስትራቴጂ ታሪካዊ እርምጃ ነው።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ አቀማመጧ እና በረጅም ታሪኳ የባሕር በር ባለቤት ሆና፣ ሀገረ መንግሥቷም በየጊዜው እየሰፋ በመጣ የመሬትና ተፈጥሯዊ የባሕር ግዛት ባለቤት በመሆን፣ ከተለያዩ ሥልጣኔዎችና መንግሥታት ጋር ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመሠረተች ሀገር ነበረች።
ሆኖም ግን የቅኝ ግዛት እንቅስቃሴና በየዘመናቱ በነበሩ የውስጥና የውጭ የሴራ ኃይሎች ምክንያት፣ ላለፉት ዓመታት የባሕር በር አልባና የሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጥገኛ እንድትሆን ተደርጋ ቆይታለች።
ይህም ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትን ሀገር ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ኪሳራና ለደህንነት ስጋት የዳረገ ሲሆን፤ በየዓመቱ ለወደብ ኪራይና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድትከፍል በማስገደድ የንግድ ተወዳዳሪነቷንና የኢኮኖሚ ዕድገቷን የያዘ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
በሕዝብ ገፊነትና በአመራር ሳቢነት እውን የሆነው ሀገራዊ ለውጥ ይህንን የዘመናት እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ ቆራጥ አቋም ይዟል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግሥት፣ የባሕር በር ጥያቄን ማንሳት እንደማይቻልና እንደ ወንጀል ተቆጥሮ የኖረበትን ሥነ-ልቦናዊ ስብራት የቀየረ ስትራቴጂ ቀርጿል።
ስትራቴጂው በሰላማዊ መንገድ፣ በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ በመመሥረት የተጀመረ ሲሆን፤ ሀገራችንን በጥገኝነት ቀንበር ስር ጠፍረው ለማቆየትና በረብሻ ለማትረፍ የፈለጉ የውስጥና የውጭ ጠላቶችን እቅድ አክሽፏል።
ይህ ስትራቴጂ የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገር ክብርና የማንነት መገለጫ ጭምር ነው። የኢትዮጵያን የባሕር ኃይል መልሶ በማደራጀትና ጠንካራ የባሕር ላይ መከላከያ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ቀጣና አስተማማኝ የፀጥታና የደህንነት አጋር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ያላትን መሪነት በፅኑ መሠረት ላይ ለመጣል መንገድ ከፍቷል።
የኢትዮጵያ ጥያቄ ፍትሐዊና በዓለም አቀፉ የሉላዊነት መርህ ማለትም ሀብትን በጋራና በፍትሐዊነት የመጠቀም እሴት ላይ የተመሠረተ ነዉ።
"ለትውልድ ምንዳ እንጂ ዕዳ አናወርስም" በሚለው ሀገራዊ መርህ መሠረት፣ ይህ የትውልድ የዘመናት ቁጭት የፈታ ታሪካዊ እርምጃ እስከ መጨረሻው ግቡ እንዲደርስ የሁሉም ኢትዮጵያውያን አንድነትና ቁርጠኝነት ወሳኝ ነዉ።
መላው ሕዝብ አጀንዳውን በባለቤትነት አጥብቆ በመያዝ፣ ኢትዮጵያ የራሷን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ብቻ ሳይሆን ዓለም ለሁሉም ፍትሐዊ እንድትሆን የራሷን ደማቅ የታሪክ ዐሻራ እንድታስቀምጥና ትውልዱም በታሪክ የባሕር በር በማስገኘት ረገድ በጋራ መትጋት ይገባል።
በብሌን ደምበሎ
#ባሕርበር #ethiopianaccesstothesea #nationalinterest #ethiopianbroadcastingcorporation
********
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ነፃነትና የፖለቲካ ልዕልና በጥብቅ ከተፈጥሮ በረከቶችና ከጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ ጋር የተሳሰሩ በመሆናቸው፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበርና የሀገርን ክብር ለመመለስ የጀመረችው የባሕር በር ስትራቴጂ ታሪካዊ እርምጃ ነው።
ኢትዮጵያ በተፈጥሮ አቀማመጧ እና በረጅም ታሪኳ የባሕር በር ባለቤት ሆና፣ ሀገረ መንግሥቷም በየጊዜው እየሰፋ በመጣ የመሬትና ተፈጥሯዊ የባሕር ግዛት ባለቤት በመሆን፣ ከተለያዩ ሥልጣኔዎችና መንግሥታት ጋር ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመሠረተች ሀገር ነበረች።
ሆኖም ግን የቅኝ ግዛት እንቅስቃሴና በየዘመናቱ በነበሩ የውስጥና የውጭ የሴራ ኃይሎች ምክንያት፣ ላለፉት ዓመታት የባሕር በር አልባና የሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጥገኛ እንድትሆን ተደርጋ ቆይታለች።
ይህም ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትን ሀገር ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ኪሳራና ለደህንነት ስጋት የዳረገ ሲሆን፤ በየዓመቱ ለወደብ ኪራይና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር እንድትከፍል በማስገደድ የንግድ ተወዳዳሪነቷንና የኢኮኖሚ ዕድገቷን የያዘ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
በሕዝብ ገፊነትና በአመራር ሳቢነት እውን የሆነው ሀገራዊ ለውጥ ይህንን የዘመናት እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ ቆራጥ አቋም ይዟል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው የመደመር መንግሥት፣ የባሕር በር ጥያቄን ማንሳት እንደማይቻልና እንደ ወንጀል ተቆጥሮ የኖረበትን ሥነ-ልቦናዊ ስብራት የቀየረ ስትራቴጂ ቀርጿል።
ስትራቴጂው በሰላማዊ መንገድ፣ በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ በመመሥረት የተጀመረ ሲሆን፤ ሀገራችንን በጥገኝነት ቀንበር ስር ጠፍረው ለማቆየትና በረብሻ ለማትረፍ የፈለጉ የውስጥና የውጭ ጠላቶችን እቅድ አክሽፏል።
ይህ ስትራቴጂ የኢኮኖሚ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሀገር ክብርና የማንነት መገለጫ ጭምር ነው። የኢትዮጵያን የባሕር ኃይል መልሶ በማደራጀትና ጠንካራ የባሕር ላይ መከላከያ በመገንባት፣ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ቀጣና አስተማማኝ የፀጥታና የደህንነት አጋር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ያላትን መሪነት በፅኑ መሠረት ላይ ለመጣል መንገድ ከፍቷል።
የኢትዮጵያ ጥያቄ ፍትሐዊና በዓለም አቀፉ የሉላዊነት መርህ ማለትም ሀብትን በጋራና በፍትሐዊነት የመጠቀም እሴት ላይ የተመሠረተ ነዉ።
"ለትውልድ ምንዳ እንጂ ዕዳ አናወርስም" በሚለው ሀገራዊ መርህ መሠረት፣ ይህ የትውልድ የዘመናት ቁጭት የፈታ ታሪካዊ እርምጃ እስከ መጨረሻው ግቡ እንዲደርስ የሁሉም ኢትዮጵያውያን አንድነትና ቁርጠኝነት ወሳኝ ነዉ።
መላው ሕዝብ አጀንዳውን በባለቤትነት አጥብቆ በመያዝ፣ ኢትዮጵያ የራሷን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ብቻ ሳይሆን ዓለም ለሁሉም ፍትሐዊ እንድትሆን የራሷን ደማቅ የታሪክ ዐሻራ እንድታስቀምጥና ትውልዱም በታሪክ የባሕር በር በማስገኘት ረገድ በጋራ መትጋት ይገባል።
በብሌን ደምበሎ
#ባሕርበር #ethiopianaccesstothesea #nationalinterest #ethiopianbroadcastingcorporation
23 days ago
እንግሊዝ በዓለም ዋንጫ፤ ለ60 ዓመታት ያልተፈታው ህልም፣ ያልተመለሰው ጥያቄ!
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
Sponsored by
Surafel
23 days ago
“ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገሬ እንድመክር ጠርታኛለች”
- የሐመሯ እናት ሙዶ አኮ ያስተጋቡት የሰላም ጥሪ
#ethiopia | በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ከደቡብ ኦሞ ዞን፣ ከሐመር ወረዳ፣ ከካራ ብሔረሰብ የተገኙት ወይዘሮ ሙዶ አኮ ያደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ እናቶችን የሰላም ጥማትና ተስፋ በማንጸባረቅ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ለብዙ ዘመናት ሴቶች የታሪክ ተመልካች ብቻ ሆነው መቆየታቸውን ያስታወሱት ወይዘሮ ሙዶ፣ ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸውን እንዲያሰሙና ከሀገራቸው ጋር እንዲመክሩ መጋበዛቸው ለርሳቸው ትልቅ ክብርና ደስታ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ ሙዶ በንግግራቸው፣ ባለመነጋገራችን ምክንያት ያተረፍነው ነገር ቢኖር እንባን፣ መቃብርን፣ ተጨማሪ ጥላቻንና በቀልን ብቻ መሆኑን በቁጭት ተናግረዋል።
ይህ ድምፅ የእሳቸው ብቻ ሳይሆን፣ እስካሁን ማንም ያልሰማቸውና ያልጠየቃቸው የሩቅ እናቶች ሁሉ ድምፅ መሆኑን በማስታወስ፣ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመን በኖረችው አለመግባባት የከፈለችውን ዋጋ በግልጽ አስቀምጠዋል።
“እሳት ቤት ቢገነባ ኖሮ ኢትዮጵያ ከዘመናት በፊት በገነባች ነበር፤ ነገር ግን ቤት የሚገነባው እጆች ሲተባበሩና ልቦች ሲደማመጡ ብቻ ነው” ሲሉ የአንድነትን አስፈላጊነት ያስገነዘቡት እናት፣ ተመካካሪዎች ይዘውት የመጡትን የቁጣና የጥላቻ ቋጠሮ በመድረኩ ላይ ፈተው እንዲመለሱ አጥብቀው ተማጽነዋል።
በብሔረሰቡ ባህላዊ ልብስ ደምቀው የተገኙት ወይዘሮ ሙዶ፣ “ማን ያሸንፋል?” በሚለው እልህ ውስጥ ከመግባት ይልቅ “ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ” የሚለው የብዙ እናቶች ህልም እውን እንዲሆን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የሰላም እሴትን የሚያጎላው ይህ ንግግር፣ የሀገራዊ ምክክሩን ዋና ግብ በማስታወስ የበርካታ ታዳሚዎችን ልብ የነካና አዎንታዊ ምላሽ ያገኘ ነበር።
- የሐመሯ እናት ሙዶ አኮ ያስተጋቡት የሰላም ጥሪ
#ethiopia | በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ከደቡብ ኦሞ ዞን፣ ከሐመር ወረዳ፣ ከካራ ብሔረሰብ የተገኙት ወይዘሮ ሙዶ አኮ ያደረጉት ንግግር የኢትዮጵያ እናቶችን የሰላም ጥማትና ተስፋ በማንጸባረቅ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ለብዙ ዘመናት ሴቶች የታሪክ ተመልካች ብቻ ሆነው መቆየታቸውን ያስታወሱት ወይዘሮ ሙዶ፣ ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ድምፃቸውን እንዲያሰሙና ከሀገራቸው ጋር እንዲመክሩ መጋበዛቸው ለርሳቸው ትልቅ ክብርና ደስታ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ ሙዶ በንግግራቸው፣ ባለመነጋገራችን ምክንያት ያተረፍነው ነገር ቢኖር እንባን፣ መቃብርን፣ ተጨማሪ ጥላቻንና በቀልን ብቻ መሆኑን በቁጭት ተናግረዋል።
ይህ ድምፅ የእሳቸው ብቻ ሳይሆን፣ እስካሁን ማንም ያልሰማቸውና ያልጠየቃቸው የሩቅ እናቶች ሁሉ ድምፅ መሆኑን በማስታወስ፣ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመን በኖረችው አለመግባባት የከፈለችውን ዋጋ በግልጽ አስቀምጠዋል።
“እሳት ቤት ቢገነባ ኖሮ ኢትዮጵያ ከዘመናት በፊት በገነባች ነበር፤ ነገር ግን ቤት የሚገነባው እጆች ሲተባበሩና ልቦች ሲደማመጡ ብቻ ነው” ሲሉ የአንድነትን አስፈላጊነት ያስገነዘቡት እናት፣ ተመካካሪዎች ይዘውት የመጡትን የቁጣና የጥላቻ ቋጠሮ በመድረኩ ላይ ፈተው እንዲመለሱ አጥብቀው ተማጽነዋል።
በብሔረሰቡ ባህላዊ ልብስ ደምቀው የተገኙት ወይዘሮ ሙዶ፣ “ማን ያሸንፋል?” በሚለው እልህ ውስጥ ከመግባት ይልቅ “ኢትዮጵያን አሸናፊ እናድርግ” የሚለው የብዙ እናቶች ህልም እውን እንዲሆን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
የሰላም እሴትን የሚያጎላው ይህ ንግግር፣ የሀገራዊ ምክክሩን ዋና ግብ በማስታወስ የበርካታ ታዳሚዎችን ልብ የነካና አዎንታዊ ምላሽ ያገኘ ነበር።
26 days ago
የ69 ዓመታቸው አዛውንት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ገብተዋል።
በትምህርት ዓለም ውስጥ ዕድሜ ገደብ እንደሌለው በተግባር ያሳዩት የ69 ዓመቱ አዛውንት አባባ ወልደየስ አያና አሻቦ ዘንድሮ በሚሰጠው 4ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ላይ በመቀመጥ አዲስ ታሪክ አስመዝግበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ልዩ ስሟ ዳንጋራ ሳላጣ በተባለች ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አባባ ወልደየስ፣ ቀደም ሲል ማህበረሰባቸውን በቀበሌ አስተዳዳሪነት ከስድስት ዓመታት በላይ በታማኝነት ያገለገሉ የሀገር ሽማግሌ ናቸው።
በደርግ ዘመን በትውልድ አካባቢያቸው እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ ተምረው ቢያጠናቅቁም፣ በወቅቱ በነበረው የትምህርት አደረጃጀት፣ የአገዛዝ ሥርዓትና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው አለመኖር ምክንያት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደው ነበር።
ይሁን እንጂ ለትምህርት ያላቸው ፍቅርና ቁጭት ሳይቀንስ ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ በ2015 ዓ.ም ወደ ገበታ በመመለስ ከ9ኛ ክፍል ጀምረው በመማር ዛሬ ለዚህ ትልቅ ሀገር አቀፍ ፈተና ለመብቃት ችለዋል።
አባባ ወልደየስ የ6 ልጆች አባት ሲሆኑ፣ የቤተሰብ ኃላፊነትንና የማህበረሰብ አገልግሎትን ከትምህርት ጉዟቸው ጋር ጎን ለጎን አስማምተው ማስኬዳቸው ልዩ ያደርጋቸዋል።
ይበልጡኑ ደግሞ ከገዛ ልጆቻቸው ጋር በአንድ የመማሪያ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው መማራቸውና ለፈተናውም በጋራ መዘጋጀታቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገራሉ።
እኩዮቻቸው ወደ ጡረታ በሚገቡበት ዕድሜ መጽሐፍ አንግበው ወደ ትምህርት ቤት የተመላለሱበት ዋና ዓላማ በመንግሥት ተቀጥሮ ለመሥራት ሳይሆን፣ አሁን የሚሰሩትን የግብርና ሥራ በዘመናዊ መንገድ ለማሻሻልና በተሻለ ሁኔታ ለማምረት የሚያስችላቸውን ሳይንሳዊ ዕውቀት ለማግኘት እንደሆነ ያስረዳሉ።
ይህ አስደናቂ ታሪክ “የተማረ ሰው የሥራ ዕድል ፈጣሪ እንጂ ተቀጣሪ ብቻ መሆን የለበትም” የሚለውን ዘመናዊ ትርክት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በትጋትና በጽናት ከተጓዙ ዕድሜ ለማንኛውም ስኬት እንቅፋት ሊሆን እንደማይችል ለሚያነበውና ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ መነሳሻ እንደሚሆን ይታመናል።
የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኝነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እንዲሁም መላው የፈተና አስተባባሪ ግብረ-ሃይል ለአባባ ወልደየስ መልካም ምኞቱን እየገለጸ፣ ይህ ፈተና የረጅም ጊዜ ራዕያቸውን የሚያሳኩበት እንዲሆን ተመኝቷል።
Via ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ
Seledadotio
Seledadotio
በትምህርት ዓለም ውስጥ ዕድሜ ገደብ እንደሌለው በተግባር ያሳዩት የ69 ዓመቱ አዛውንት አባባ ወልደየስ አያና አሻቦ ዘንድሮ በሚሰጠው 4ኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ላይ በመቀመጥ አዲስ ታሪክ አስመዝግበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ልዩ ስሟ ዳንጋራ ሳላጣ በተባለች ቀበሌ ተወልደው ያደጉት አባባ ወልደየስ፣ ቀደም ሲል ማህበረሰባቸውን በቀበሌ አስተዳዳሪነት ከስድስት ዓመታት በላይ በታማኝነት ያገለገሉ የሀገር ሽማግሌ ናቸው።
በደርግ ዘመን በትውልድ አካባቢያቸው እስከ 8ኛ ክፍል ድረስ ተምረው ቢያጠናቅቁም፣ በወቅቱ በነበረው የትምህርት አደረጃጀት፣ የአገዛዝ ሥርዓትና የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው አለመኖር ምክንያት ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደው ነበር።
ይሁን እንጂ ለትምህርት ያላቸው ፍቅርና ቁጭት ሳይቀንስ ከረጅም ዓመታት ቆይታ በኋላ በ2015 ዓ.ም ወደ ገበታ በመመለስ ከ9ኛ ክፍል ጀምረው በመማር ዛሬ ለዚህ ትልቅ ሀገር አቀፍ ፈተና ለመብቃት ችለዋል።
አባባ ወልደየስ የ6 ልጆች አባት ሲሆኑ፣ የቤተሰብ ኃላፊነትንና የማህበረሰብ አገልግሎትን ከትምህርት ጉዟቸው ጋር ጎን ለጎን አስማምተው ማስኬዳቸው ልዩ ያደርጋቸዋል።
ይበልጡኑ ደግሞ ከገዛ ልጆቻቸው ጋር በአንድ የመማሪያ ክፍል ውስጥ ተቀምጠው መማራቸውና ለፈተናውም በጋራ መዘጋጀታቸው ልዩ ደስታ እንደፈጠረላቸው ይናገራሉ።
እኩዮቻቸው ወደ ጡረታ በሚገቡበት ዕድሜ መጽሐፍ አንግበው ወደ ትምህርት ቤት የተመላለሱበት ዋና ዓላማ በመንግሥት ተቀጥሮ ለመሥራት ሳይሆን፣ አሁን የሚሰሩትን የግብርና ሥራ በዘመናዊ መንገድ ለማሻሻልና በተሻለ ሁኔታ ለማምረት የሚያስችላቸውን ሳይንሳዊ ዕውቀት ለማግኘት እንደሆነ ያስረዳሉ።
ይህ አስደናቂ ታሪክ “የተማረ ሰው የሥራ ዕድል ፈጣሪ እንጂ ተቀጣሪ ብቻ መሆን የለበትም” የሚለውን ዘመናዊ ትርክት በተግባር የሚያሳይ ነው።
በትጋትና በጽናት ከተጓዙ ዕድሜ ለማንኛውም ስኬት እንቅፋት ሊሆን እንደማይችል ለሚያነበውና ለወጣቱ ትውልድ ትልቅ መነሳሻ እንደሚሆን ይታመናል።
የዩኒቨርሲቲው ህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኝነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት እንዲሁም መላው የፈተና አስተባባሪ ግብረ-ሃይል ለአባባ ወልደየስ መልካም ምኞቱን እየገለጸ፣ ይህ ፈተና የረጅም ጊዜ ራዕያቸውን የሚያሳኩበት እንዲሆን ተመኝቷል።
Via ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ
Seledadotio
Seledadotio
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እ.ኤ.አ በ2030 በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ ያቀረበው ሀሳብ ከወዲሁ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ትችት እያስተናገደ ይገኛል።
የውድድሩን የማጣሪያ ሂደት ትርጉም አልባ ያደርገዋል በሚል በስፋት የተተቸው ይህ ዕቅድ፣ በተለይም በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ቼፈሪን ዘንድ "መጥፎ ሀሳብ" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ቼፈሪን ሀሳቡ ውድድሩንም ሆነ የአውሮፓን የማጣሪያ ውድድሮች በእጅጉ እንደሚጎዳ ተናግረዋል። የሰሜን አሜሪካው ፕሬዝዳንት ቪክቶር ሞንታግሊያኒም በተመሳሳይ ውሳኔውን "ጥሩ ሀሳብ አይደለም" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው የ48 ሀገራት ውድድር ላይ የጋና ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ካርሎስ ኬይሮዝ የቡድን ድልድል ጨዋታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ፣ የቡድኖች ቁጥር መጨመር የማጣሪያውን ሂደት ዋጋ እንዳሳጣውና ውድድሩን "ተራ እና ዝቅተኛ" እንዳደረገው በቁጭት ገልጸዋል። ከፊፋ 210 አባል ሀገራት መካከል ከሩቡ በላይ የሚሆኑትን በአንድ ውድድር ላይ ማሳተፍ፣ የክልላዊ ማጣሪያዎችን ፉክክር ሙሉ በሙሉ ያጠፋዋል የሚለው ስጋት የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኗል።
እነዚህ ሁሉ ጠንካራ ተቃውሞዎች ቢኖሩም፣ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በኋላ ይህ የ64 ሀገራት ተሳትፎ ጉዳይ በሚመለከታቸው ኮሚቴዎች በቁምነገር እንደሚታይ አረጋግጠዋል። ኢንፋንቲኖ "እያንዳንዱ ሀገር በዓለም ዋንጫው የመሳተፍ ህልም እንዲኖረው ሊፈቀድለት ይገባል፤ ለትናንሽ ሀገራት እድል ካልሰጠን ራሳቸውን ለማሻሻል የሚያስችል መነሳሳት አይኖራቸውም" በማለት ዕቅዱን ተከላከለዋል። ዘንድሮ ወደ 48 ያደገውን ውድድርም "100 በመቶ ስኬታማ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
ይህ የ64 ሀገራት ውድድር ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የመነጨው በደቡብ አሜሪካ የእግር ኳስ ባለስልጣናት ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በ2030 ውድድር ላይ ያላቸውን የማስተናገድ ሚና ለማሳደግ ነው። የ2030 የዓለም ዋንጫ በሶስት አህጉራት እና በስድስት ሀገራት (ሞሮኮ፣ ፖርቹጋል፣ ስፔን እንዲሁም በደቡብ አሜሪካ ኡራጓይ፣ አርጀንቲና እና ፓራጓይ) የሚካሄድ ሲሆን፣ በአሁኑ ድልድል የደቡብ አሜሪካ ሀገራቱ እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግዱ ነው የተወሰነው። ሀገራቱን ወደ 64 በማሳደግ ግን እያንዳንዳቸው ሙሉ የምድብ ጨዋታዎችን ማስተናገድ ይችላሉ የሚል እሳቤ አላቸው። የኮንሜቦል ፕሬዝዳንት አሌሃንድሮ ዶሚንጌዝ ይህንን ሀሳብ "ዓለምን ቢያንስ ለአንድ ጊዜ አንድ የሚያደርግ ህልሜ ነው" ብለውታል።
የዓለም ዋንጫው ከ1998 እስከ 2022 ድረስ በ32 ሀገራት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊዎቹ ወደ 48 ማደጋቸው ይታወቃል።
በሌላ ዜና የፊፋው ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር "በየቀኑ ማለት ይቻላል" እየተነጋገሩ መሆኑን እና ትራምፕ እስካሁን በአካል ተገኝተው ጨዋታ ባይመለከቱም በቴሌቪዥን እያንዳንዱን ጨዋታ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ ላይ በአካል ታድመው ለአሸናፊው ቡድን ታላቁን ዋንጫ እንደሚያበረክቱም ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የውድድሩን የማጣሪያ ሂደት ትርጉም አልባ ያደርገዋል በሚል በስፋት የተተቸው ይህ ዕቅድ፣ በተለይም በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ቼፈሪን ዘንድ "መጥፎ ሀሳብ" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ቼፈሪን ሀሳቡ ውድድሩንም ሆነ የአውሮፓን የማጣሪያ ውድድሮች በእጅጉ እንደሚጎዳ ተናግረዋል። የሰሜን አሜሪካው ፕሬዝዳንት ቪክቶር ሞንታግሊያኒም በተመሳሳይ ውሳኔውን "ጥሩ ሀሳብ አይደለም" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው የ48 ሀገራት ውድድር ላይ የጋና ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ካርሎስ ኬይሮዝ የቡድን ድልድል ጨዋታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ፣ የቡድኖች ቁጥር መጨመር የማጣሪያውን ሂደት ዋጋ እንዳሳጣውና ውድድሩን "ተራ እና ዝቅተኛ" እንዳደረገው በቁጭት ገልጸዋል። ከፊፋ 210 አባል ሀገራት መካከል ከሩቡ በላይ የሚሆኑትን በአንድ ውድድር ላይ ማሳተፍ፣ የክልላዊ ማጣሪያዎችን ፉክክር ሙሉ በሙሉ ያጠፋዋል የሚለው ስጋት የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኗል።
እነዚህ ሁሉ ጠንካራ ተቃውሞዎች ቢኖሩም፣ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በኋላ ይህ የ64 ሀገራት ተሳትፎ ጉዳይ በሚመለከታቸው ኮሚቴዎች በቁምነገር እንደሚታይ አረጋግጠዋል። ኢንፋንቲኖ "እያንዳንዱ ሀገር በዓለም ዋንጫው የመሳተፍ ህልም እንዲኖረው ሊፈቀድለት ይገባል፤ ለትናንሽ ሀገራት እድል ካልሰጠን ራሳቸውን ለማሻሻል የሚያስችል መነሳሳት አይኖራቸውም" በማለት ዕቅዱን ተከላከለዋል። ዘንድሮ ወደ 48 ያደገውን ውድድርም "100 በመቶ ስኬታማ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
ይህ የ64 ሀገራት ውድድር ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የመነጨው በደቡብ አሜሪካ የእግር ኳስ ባለስልጣናት ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በ2030 ውድድር ላይ ያላቸውን የማስተናገድ ሚና ለማሳደግ ነው። የ2030 የዓለም ዋንጫ በሶስት አህጉራት እና በስድስት ሀገራት (ሞሮኮ፣ ፖርቹጋል፣ ስፔን እንዲሁም በደቡብ አሜሪካ ኡራጓይ፣ አርጀንቲና እና ፓራጓይ) የሚካሄድ ሲሆን፣ በአሁኑ ድልድል የደቡብ አሜሪካ ሀገራቱ እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግዱ ነው የተወሰነው። ሀገራቱን ወደ 64 በማሳደግ ግን እያንዳንዳቸው ሙሉ የምድብ ጨዋታዎችን ማስተናገድ ይችላሉ የሚል እሳቤ አላቸው። የኮንሜቦል ፕሬዝዳንት አሌሃንድሮ ዶሚንጌዝ ይህንን ሀሳብ "ዓለምን ቢያንስ ለአንድ ጊዜ አንድ የሚያደርግ ህልሜ ነው" ብለውታል።
የዓለም ዋንጫው ከ1998 እስከ 2022 ድረስ በ32 ሀገራት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊዎቹ ወደ 48 ማደጋቸው ይታወቃል።
በሌላ ዜና የፊፋው ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር "በየቀኑ ማለት ይቻላል" እየተነጋገሩ መሆኑን እና ትራምፕ እስካሁን በአካል ተገኝተው ጨዋታ ባይመለከቱም በቴሌቪዥን እያንዳንዱን ጨዋታ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ ላይ በአካል ታድመው ለአሸናፊው ቡድን ታላቁን ዋንጫ እንደሚያበረክቱም ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋግጠዋል።
28 days ago
የ2026 የዓለም ዋንጫ ድራማዊ እና አስደናቂ ትዕይንቶች በከፍተኛ ስሜት ቀጥለዋል። የዓለም ሻምፒዮኗ አርጀንቲና፣ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ በአስደናቂ ፅናት ስትታገል የነበረችውን እና በሁለተኛው አጋማሽ በ10 ተጫዋቾች ለመጫወት የተገደደችውን ስዊዘርላንድን በከባድ ፉክክር 3ለ1 በመርታት ወደ ግማሽ ፍፃሜው ማለፏን አረጋግጣለች። ይህንን ታሪካዊ ድል ተከትሎ... አርጀንቲና በሴሚ ፋይናሉ ኖርዌይን በአስጨናቂ ሁኔታ አሸንፋ የደረሰችውን የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።
የጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ግን ለገለልተኛ ተመልካች ያን ያህል ማራኪና ሳቢ አልነበረም። ስዊዘርላንዶች ወደ ፊት ተጭነው በመጫወት በጥሩ የሜዳው ክፍሎች ላይ ኳሶችን በተደጋጋሚ መንጠቅ ቢችሉም፣ ወደ አርጀንቲና የግብ ክልል ሲደርሱ ግን የሚያስፈልገው ጥራት እና የማጥቃት መጨረሻ በከፍተኛ ሁኔታ ጎድሏቸው ታይቷል። ይሁንና በመጀመሪያው አጋማሽ የአርጀንቲናውን እምብርት ሊዮኔል ሜሲን ጸጥ በማሰኘት እና ከጨዋታው ውጪ በማድረግ በኩል የስዊዘርላንድ ተከላካዮች ፍጹም ድንቅ ስራ ሰርተው ነበር።
ጨዋታው ለእረፍት ሲወጣ ግን በአርጀንቲና ካምፕ ውስጥ ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሮ ነበር። መሪው ሊዮኔል ሜሲ ከዓይኑ ጥቂት ከፍ ብሎ በደረሰበት አስቀያሚ እና ከባድ የመቆረጥ አደጋ ምክንያት በውሃ እረፍት ሰዓቱ ላይ በሀኪሞች ከፍተኛ የሕክምና እርዳታ ሲደረግለት ተስተውሏል። አርጀንቲና ጨዋታውን ለመቆጣጠር ተጨማሪ ግቦች እንደሚያስፈልጓት በግልጽ በታየበት በዚያ ፈታኝ ወቅት፣ የሜሲ መጎዳት የቡድኑን የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ ጥሎት ነበር።
በሁለተኛው አጋማሽ ግን የጨዋታው መልክ ሙሉ በሙሉ ተቀየረ። የጨዋታው ትልቅ ማዕበል የተነሳው የስዊዘርላንዱ አጥቂ ብሪል እምቦሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ መባረሩን ተከትሎ ስዊዘርላንድ በ10 ተጫዋች እንድትቀጥል ስትገደድ ነው። እምቦሎ በቡድን አጋሮቹ እየተፅናና በእንባ ታጥቦ ሜዳውን የለቀቀ ሲሆን፣ ስዊዘርላንድ ተአምር ሰርታ ብታልፍ እንኳ እሱ በግማሽ ፍጻሜው መሰለፍ እንደማይችል በማወቁ የተሰማው ከባድ ሀዘን በግልጽ ይታይ ነበር። ይህንን የቁጥር ብልጫ በአግባቡ የተጠቀሙት አርጀንቲናውያን፣ የአጥቂ መስመራቸውን በማስፋት የስዊዘርላንድን የተከላካይ ግንብ ሰብረው በመግባት ጨዋታውን 3ለ1 በሆነ አስገራሚ ውጤት ሊያጠናቅቁ ችለዋል።
ዳኛው የጨዋታውን ማጠናቀቂያ ፊሽካ ሲነፉ በመላው ስታዲየም ውስጥ ያለው የደጋፊዎች ጩኸትና ሁካታ በአንድ ጊዜ በአስደናቂ ሁኔታ ፈንድቷል! አርጀንቲና ድሉን ሙሉ በሙሉ በማረጋገጥ ጉዳዩን ቋጭታዋለች። በአንጻሩ ስዊዘርላንዶች ያላቸውን አቅም፣ ጉልበትና ጥረት ሁሉ በሜዳው ላይ አፍስሰው እስከ መጨረሻው ሰከንድ ድረስ የተዋጉ ቢሆንም በመጨረሻ ግን መሸነፋቸው አይቀሬ ሆኗል። ጨዋታው እንደተጠናቀቀ በርካታ የስዊዘርላንድ ተጫዋቾች ፍፁም በሆነ ሐዘንና ቁጭት ተሰብረው በጉልበታቸው ሜዳው ላይ ተንበርክከው ታይተዋል።
ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት በመላው ስታዲየም ውስጥ "ሜሲ፣ ሜሲ፣ ሜሲ" የሚለው የሺዎች ደጋፊዎች ነጎድጓዳዊ የክብር ጩኸት እና መዝሙር በአስደናቂ ሁኔታ አስተጋብቷል። አርጀንቲና አሁን ወደ ግማሽ ፍፃሜው ተሻግራለች። ይህ ድል አርጀንቲናን እና እንግሊዝን እ.ኤ.አ ከ2005 ዓ.ም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የሚያገናኝ ታሪካዊ አጋጣሚን ፈጥሯል። የፊታችን ረቡዕ የሚጠበቀው ይህ የአርጀንቲና እና የእንግሊዝ ፍልሚያ፣ የሊዮኔል ሜሲ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ክብር እና በጁድ ቤሊንግሃም የሚመራው የአዲሱ ትውልድ የእንግሊዝ ሃይል የሚጋጩበት እውነተኛ የእግር ኳስ ክላሲክ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም።
የጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ግን ለገለልተኛ ተመልካች ያን ያህል ማራኪና ሳቢ አልነበረም። ስዊዘርላንዶች ወደ ፊት ተጭነው በመጫወት በጥሩ የሜዳው ክፍሎች ላይ ኳሶችን በተደጋጋሚ መንጠቅ ቢችሉም፣ ወደ አርጀንቲና የግብ ክልል ሲደርሱ ግን የሚያስፈልገው ጥራት እና የማጥቃት መጨረሻ በከፍተኛ ሁኔታ ጎድሏቸው ታይቷል። ይሁንና በመጀመሪያው አጋማሽ የአርጀንቲናውን እምብርት ሊዮኔል ሜሲን ጸጥ በማሰኘት እና ከጨዋታው ውጪ በማድረግ በኩል የስዊዘርላንድ ተከላካዮች ፍጹም ድንቅ ስራ ሰርተው ነበር።
ጨዋታው ለእረፍት ሲወጣ ግን በአርጀንቲና ካምፕ ውስጥ ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሮ ነበር። መሪው ሊዮኔል ሜሲ ከዓይኑ ጥቂት ከፍ ብሎ በደረሰበት አስቀያሚ እና ከባድ የመቆረጥ አደጋ ምክንያት በውሃ እረፍት ሰዓቱ ላይ በሀኪሞች ከፍተኛ የሕክምና እርዳታ ሲደረግለት ተስተውሏል። አርጀንቲና ጨዋታውን ለመቆጣጠር ተጨማሪ ግቦች እንደሚያስፈልጓት በግልጽ በታየበት በዚያ ፈታኝ ወቅት፣ የሜሲ መጎዳት የቡድኑን የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ ጥሎት ነበር።
በሁለተኛው አጋማሽ ግን የጨዋታው መልክ ሙሉ በሙሉ ተቀየረ። የጨዋታው ትልቅ ማዕበል የተነሳው የስዊዘርላንዱ አጥቂ ብሪል እምቦሎ በቀይ ካርድ ከሜዳ መባረሩን ተከትሎ ስዊዘርላንድ በ10 ተጫዋች እንድትቀጥል ስትገደድ ነው። እምቦሎ በቡድን አጋሮቹ እየተፅናና በእንባ ታጥቦ ሜዳውን የለቀቀ ሲሆን፣ ስዊዘርላንድ ተአምር ሰርታ ብታልፍ እንኳ እሱ በግማሽ ፍጻሜው መሰለፍ እንደማይችል በማወቁ የተሰማው ከባድ ሀዘን በግልጽ ይታይ ነበር። ይህንን የቁጥር ብልጫ በአግባቡ የተጠቀሙት አርጀንቲናውያን፣ የአጥቂ መስመራቸውን በማስፋት የስዊዘርላንድን የተከላካይ ግንብ ሰብረው በመግባት ጨዋታውን 3ለ1 በሆነ አስገራሚ ውጤት ሊያጠናቅቁ ችለዋል።
ዳኛው የጨዋታውን ማጠናቀቂያ ፊሽካ ሲነፉ በመላው ስታዲየም ውስጥ ያለው የደጋፊዎች ጩኸትና ሁካታ በአንድ ጊዜ በአስደናቂ ሁኔታ ፈንድቷል! አርጀንቲና ድሉን ሙሉ በሙሉ በማረጋገጥ ጉዳዩን ቋጭታዋለች። በአንጻሩ ስዊዘርላንዶች ያላቸውን አቅም፣ ጉልበትና ጥረት ሁሉ በሜዳው ላይ አፍስሰው እስከ መጨረሻው ሰከንድ ድረስ የተዋጉ ቢሆንም በመጨረሻ ግን መሸነፋቸው አይቀሬ ሆኗል። ጨዋታው እንደተጠናቀቀ በርካታ የስዊዘርላንድ ተጫዋቾች ፍፁም በሆነ ሐዘንና ቁጭት ተሰብረው በጉልበታቸው ሜዳው ላይ ተንበርክከው ታይተዋል።
ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት በመላው ስታዲየም ውስጥ "ሜሲ፣ ሜሲ፣ ሜሲ" የሚለው የሺዎች ደጋፊዎች ነጎድጓዳዊ የክብር ጩኸት እና መዝሙር በአስደናቂ ሁኔታ አስተጋብቷል። አርጀንቲና አሁን ወደ ግማሽ ፍፃሜው ተሻግራለች። ይህ ድል አርጀንቲናን እና እንግሊዝን እ.ኤ.አ ከ2005 ዓ.ም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊት ለፊት የሚያገናኝ ታሪካዊ አጋጣሚን ፈጥሯል። የፊታችን ረቡዕ የሚጠበቀው ይህ የአርጀንቲና እና የእንግሊዝ ፍልሚያ፣ የሊዮኔል ሜሲ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ክብር እና በጁድ ቤሊንግሃም የሚመራው የአዲሱ ትውልድ የእንግሊዝ ሃይል የሚጋጩበት እውነተኛ የእግር ኳስ ክላሲክ እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም።
1 month ago
*ከመረጥነው የህይወት አቅጣጫ ይልቅ ያልመረጥነው ለምን የተሻለ መስሎ ይታየን ይሆን?*
ሶረን ኬርኬጋርድ የሚባል የዴኒሽ ፈላስፋ ትዝብቱን ሲያስቀምጥ እንዲህ ይላል "ማንኛውም ወሳኝ የሆነ የህይወት ውሳኔ የራሱ የሆነ ትርፍና ኪሳራ ይዞ ይመጣል"። ውሳኔያችን ምንም ይሁን በአንድ በኩል የእድል በር ሲከፍትልን በሌላው በኩል ግን በዚህ ውሳኔያችን ምክንያት እንደሚዘጋ ሌላ በር መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ብዙ ሰዎች የሆነ ብቸኛ ውሳኔ በራሱ ደስተኛ የሚያረጋቸው ይመስል ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔ ለሠወሰን ህይወታቸውን ሙሉ ሲባዝኑ እናያለን። እውነታው ግን እያንዳንዱ የህይወት ውሳኔ እርካታን ብቻ ሳይሆን ቁጭትም ይኖሩታል።
ካሉት አማራጮች ውስጥ አንዱን መንገድ በመረጥን ሰአት ሌለኛውን መንገድ ተሰናብተን እንሄዳለን። በማንኛውም ምርጫችን የምናገኘው በረከት ሌለኛውን በረከት መስዋት አድርገን ነው።
እዚህ ላይ ችግሩ ውሳኔያችን ራሱ አይደለም። ዋናው ችግር ሣንመርጥ የቀረነውንና የውሳኔያችን አካል ባለመሆኑ ምክንያት ያልኖርነውን ህይወት መመኘታችን ነው።
የተውነው መንገድ የተሻለ፣ ቀለል ያለ፣ ደስታን የሚያጎናጽፍ ፣ ወይም የበለጠ ስኬታማ ሊያረገን ይችል እንደነበረ አርገን እናስብና ያን መንገድ መርጠነው ቢሆን ኖሮ አብሮት ሊመጡ ይችሉ የነበሩትን ችግሮች እንዘነጋለን።
ምርጫችን ምንም ይሁን ምን - ያን መንገድ ተከትዬ ቢሆንስ ኖሮ ምን ይከሰት ይሆን? የሚል ጥያቄ በውስጣችን መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ይህ አስተሳሰብ ግን መጥፎ ውሳኔ ወስነን ነበር ማለት ሳይሆን የተለመደ ሰውኛ ባሕሪ እያሳየን ነው።
ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔ እወስናለሁ ብለን የማይሳካ እቅድ ይዘን ህይወታችንን ሙሉ ከምንባዝን እጃችን ላይ ባለው መረጃ ላይ ተንተርሰን መተግበር የምንችለውን ጥሩ ውሳኔ መወሰን ይመረጣል።
ሁሉም የህይወት መንገዶች መስዋዕትነት እንዳለባቸው በመረዳት የመረጥነውን መንገድ አጥብቀን ይዘን ውጤታማ ለመሆን መጣር ብልህነት ነው።
ደስተኛ ሰዎች በውሳኔዎቻቸው ላይ ጥያቄ የማያነሱቱ ሳይሆኑ የራሳየውን ህይወት ካልተጨበጠና ሊሆን ይችል ነበር ከሚሉት ነገር ጋር የማያወዳድሩት ናቸው።
ውስጣዊ ሰላም የሚመጣው ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔን ወስኖ ከመገኘት ሳይሆን የመረጥነውን መንገድ ከልብ ተቀብለን መኖር ስንጀምር ነው።
ዶክተር ሲራክ ሀይሉ
ካይሮፕራኽተር
ከሚኔሶታ
ሶረን ኬርኬጋርድ የሚባል የዴኒሽ ፈላስፋ ትዝብቱን ሲያስቀምጥ እንዲህ ይላል "ማንኛውም ወሳኝ የሆነ የህይወት ውሳኔ የራሱ የሆነ ትርፍና ኪሳራ ይዞ ይመጣል"። ውሳኔያችን ምንም ይሁን በአንድ በኩል የእድል በር ሲከፍትልን በሌላው በኩል ግን በዚህ ውሳኔያችን ምክንያት እንደሚዘጋ ሌላ በር መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል።
ብዙ ሰዎች የሆነ ብቸኛ ውሳኔ በራሱ ደስተኛ የሚያረጋቸው ይመስል ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔ ለሠወሰን ህይወታቸውን ሙሉ ሲባዝኑ እናያለን። እውነታው ግን እያንዳንዱ የህይወት ውሳኔ እርካታን ብቻ ሳይሆን ቁጭትም ይኖሩታል።
ካሉት አማራጮች ውስጥ አንዱን መንገድ በመረጥን ሰአት ሌለኛውን መንገድ ተሰናብተን እንሄዳለን። በማንኛውም ምርጫችን የምናገኘው በረከት ሌለኛውን በረከት መስዋት አድርገን ነው።
እዚህ ላይ ችግሩ ውሳኔያችን ራሱ አይደለም። ዋናው ችግር ሣንመርጥ የቀረነውንና የውሳኔያችን አካል ባለመሆኑ ምክንያት ያልኖርነውን ህይወት መመኘታችን ነው።
የተውነው መንገድ የተሻለ፣ ቀለል ያለ፣ ደስታን የሚያጎናጽፍ ፣ ወይም የበለጠ ስኬታማ ሊያረገን ይችል እንደነበረ አርገን እናስብና ያን መንገድ መርጠነው ቢሆን ኖሮ አብሮት ሊመጡ ይችሉ የነበሩትን ችግሮች እንዘነጋለን።
ምርጫችን ምንም ይሁን ምን - ያን መንገድ ተከትዬ ቢሆንስ ኖሮ ምን ይከሰት ይሆን? የሚል ጥያቄ በውስጣችን መፈጠሩ አይቀሬ ነው። ይህ አስተሳሰብ ግን መጥፎ ውሳኔ ወስነን ነበር ማለት ሳይሆን የተለመደ ሰውኛ ባሕሪ እያሳየን ነው።
ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔ እወስናለሁ ብለን የማይሳካ እቅድ ይዘን ህይወታችንን ሙሉ ከምንባዝን እጃችን ላይ ባለው መረጃ ላይ ተንተርሰን መተግበር የምንችለውን ጥሩ ውሳኔ መወሰን ይመረጣል።
ሁሉም የህይወት መንገዶች መስዋዕትነት እንዳለባቸው በመረዳት የመረጥነውን መንገድ አጥብቀን ይዘን ውጤታማ ለመሆን መጣር ብልህነት ነው።
ደስተኛ ሰዎች በውሳኔዎቻቸው ላይ ጥያቄ የማያነሱቱ ሳይሆኑ የራሳየውን ህይወት ካልተጨበጠና ሊሆን ይችል ነበር ከሚሉት ነገር ጋር የማያወዳድሩት ናቸው።
ውስጣዊ ሰላም የሚመጣው ፍፁማዊ የሆነ ውሳኔን ወስኖ ከመገኘት ሳይሆን የመረጥነውን መንገድ ከልብ ተቀብለን መኖር ስንጀምር ነው።
ዶክተር ሲራክ ሀይሉ
ካይሮፕራኽተር
ከሚኔሶታ
1 month ago
ሰው አጠፋው፤ ሰው አለማው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰው “ አጠፋው ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰው “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገው።
የቀበና ወንዝ ለዘመናት በዘፈን እና በትዝታ ብቻ ስሙ ሲነሳና ሲወደስ ኖሮ ዛሬ ግን ዳግም እንዲወለድ አድርገን አለማነዉ!!
አርቲስት ፀሀዬ ዮሀንስ “ቢሻን ቀበና” እያለ ብዙዎች እየዋኙ ያደጉበትን የልጅነት ትዝታን ሲቀሰቅስ፣ የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ “ቢሻን አዲስ አበባ“ እያለ ሲያደናንቅ በዘመናት ውስጥ ግን ትዝታን ብቻ ተሸክሞ የወንዙ ተፈጥሯዊ ማንነት ጠፍቶ፣ የፍሳሽ መውረጃና የቆሻሻ መጣያ ሆኖ፣ ጠረኑ አላስጠጋ ብሎ ተረስቶ የኖረ ወንዝ ነበር።
እነሆ እነዚህ የብክለት ፣ የበሽታ ምንጭና የቆሻሻ ማጠራቀሚያ የነበሩትን ወንዞቻችንን ዛሬ ላይ በትጋት እና በላብ እየታከሙ፣ ለነዋሪው ተስፋን ሀሴትን የሚለግሱ የደስታ ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡
በአጭር ጊዜ የተገነባው ይህ ድንቅ ፕሮጀክት፣ ከሌሎች የከተማዋ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ጋር ተዳምሮ አዲስ አበባን የውበት ማማ አድርጓታል።
ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰው “ አጠፋው ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰው “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገው።
የቀበና ወንዝ ለዘመናት በዘፈን እና በትዝታ ብቻ ስሙ ሲነሳና ሲወደስ ኖሮ ዛሬ ግን ዳግም እንዲወለድ አድርገን አለማነዉ!!
አርቲስት ፀሀዬ ዮሀንስ “ቢሻን ቀበና” እያለ ብዙዎች እየዋኙ ያደጉበትን የልጅነት ትዝታን ሲቀሰቅስ፣ የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ “ቢሻን አዲስ አበባ“ እያለ ሲያደናንቅ በዘመናት ውስጥ ግን ትዝታን ብቻ ተሸክሞ የወንዙ ተፈጥሯዊ ማንነት ጠፍቶ፣ የፍሳሽ መውረጃና የቆሻሻ መጣያ ሆኖ፣ ጠረኑ አላስጠጋ ብሎ ተረስቶ የኖረ ወንዝ ነበር።
እነሆ እነዚህ የብክለት ፣ የበሽታ ምንጭና የቆሻሻ ማጠራቀሚያ የነበሩትን ወንዞቻችንን ዛሬ ላይ በትጋት እና በላብ እየታከሙ፣ ለነዋሪው ተስፋን ሀሴትን የሚለግሱ የደስታ ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡
በአጭር ጊዜ የተገነባው ይህ ድንቅ ፕሮጀክት፣ ከሌሎች የከተማዋ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ጋር ተዳምሮ አዲስ አበባን የውበት ማማ አድርጓታል።
1 month ago
በእድሜ ያልተገደበ የቀለም ጉዞ
* ድንቅ ቁጪት ከTTI...እስከ- 2-PHD*(2-ዶክትሬት ) ውጤታማ ዕድሜ
#ethiopia | ዶ/ር ማናዬ አበራ ሸመሎ ይባላሉ ከምሁራን መፍለቂያ አምባ፣ ከከምባቶች እናት አብራክ የተገኙ ፣ በስንዴ ምርቷ ከምትታወቅ ከከምባታዋ ዶዮገና የበቀሉ ድንቅ ቀለሜ ናቸው ።
ስለ አካዳሚክ ቅድመ ታሪካቸው የመጀመሪያ TTI ከደብረብርሃን መምህራን ማሰልጠኛ፣ ድፕሎማቻውን ከሀዋሳ መምህራን ማስልጠኛ ኮሌጅ፣ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከድላ ዩኒቨርስቲ፣ 2ኛ ድግሪያቸውን ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቀብለዋል፤ ለትምህርት ካላቸው ቁጭት የተነሳ 1ኛውን PHD (Philosophy of Higher Diploma) በትምህርት ዕቅድና አመራር ደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል።
ዶ/ር ማናዬ መቼ በዛው አበቁና ዛሬ ደግሞ 2ኛውን ዶክተሬት ድግሪያቸውን ከአዲስአበባ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ በትምህርት አመራር በስኬት አጠናቀው ተመርቀዋል ።
የዶክተር ማናዬ አበራ የቁጭት ጉዞ በድል ማጠናቀቅ የመጀመሪያው በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ለሀገራችን ብዙ አበርክቶ ያበረከቱ መሆናቸውን ብቻ ሰይሆን ለአዲሱ ትውልድ የጥንካሬ ተምሳሌትም ናቸው።
የዶ/ር ማናዬ ህይወት ጉዞ ለብዙዎቻችን እጅግ አስተማሪ ጉዞ ስሆን ለዚህ ድንቅ ቀን እና ድንቅ ደረጃ በመብቃትዎ እንኳን ደስ አልዎ !! ለማለት እፈልጋለሁ !!
Congratulations ❤❤❤
Ambaye Aberra
* ድንቅ ቁጪት ከTTI...እስከ- 2-PHD*(2-ዶክትሬት ) ውጤታማ ዕድሜ
#ethiopia | ዶ/ር ማናዬ አበራ ሸመሎ ይባላሉ ከምሁራን መፍለቂያ አምባ፣ ከከምባቶች እናት አብራክ የተገኙ ፣ በስንዴ ምርቷ ከምትታወቅ ከከምባታዋ ዶዮገና የበቀሉ ድንቅ ቀለሜ ናቸው ።
ስለ አካዳሚክ ቅድመ ታሪካቸው የመጀመሪያ TTI ከደብረብርሃን መምህራን ማሰልጠኛ፣ ድፕሎማቻውን ከሀዋሳ መምህራን ማስልጠኛ ኮሌጅ፣ የመጀመሪያ ድግሪያቸውን ከድላ ዩኒቨርስቲ፣ 2ኛ ድግሪያቸውን ከአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተቀብለዋል፤ ለትምህርት ካላቸው ቁጭት የተነሳ 1ኛውን PHD (Philosophy of Higher Diploma) በትምህርት ዕቅድና አመራር ደቡብ አፍሪካ ከሚገኘው ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል።
ዶ/ር ማናዬ መቼ በዛው አበቁና ዛሬ ደግሞ 2ኛውን ዶክተሬት ድግሪያቸውን ከአዲስአበባ ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ በትምህርት አመራር በስኬት አጠናቀው ተመርቀዋል ።
የዶክተር ማናዬ አበራ የቁጭት ጉዞ በድል ማጠናቀቅ የመጀመሪያው በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ለሀገራችን ብዙ አበርክቶ ያበረከቱ መሆናቸውን ብቻ ሰይሆን ለአዲሱ ትውልድ የጥንካሬ ተምሳሌትም ናቸው።
የዶ/ር ማናዬ ህይወት ጉዞ ለብዙዎቻችን እጅግ አስተማሪ ጉዞ ስሆን ለዚህ ድንቅ ቀን እና ድንቅ ደረጃ በመብቃትዎ እንኳን ደስ አልዎ !! ለማለት እፈልጋለሁ !!
Congratulations ❤❤❤
Ambaye Aberra
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ቱርክ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫው ያሳለፈው ጊዜ አንገት አስደፊና ልብ ሰባሪ ቢሆንም፣ በስብስቡ ውስጥ ስላለው አስደናቂ ጥራትና ክህሎት ግን ማንም ሊጠራጠር አይችልም።
እንደ አርዳ ጉለር፣ ኬናን ዪልዲዝና ፌርዲ ካዲዮግሉን የመሳሰሉ ተጫዋቾች በአውሮፓ እግር ኳስ መድረክ እጅግ ማራኪና ተስፋ ሰጪ ከሚባሉ ወጣት ኮከቦች ተርታ የሚሰለፉ ናቸው። ይህ ደግሞ ቡድኑ ከውድድሩ በጊዜ መሰናበቱ የፈጠረውን ሀዘን አሽሽቶ፣ ለደጋፊዎቹ እውነተኛ የተስፋ ብርሃን ፈንጥቆላቸዋል።
በአሁኑ ሰዓት በቡድኑ ዙሪያ ያለው ስሜት በከፍተኛ ሀዘንና ቁጭት የተዋጠ መሆኑ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በቱርክ ውስጥ ይህ ድንቅ ትውልድ አቅሙ ተሟጦ ማብቂያው ላይ ደርሷል ብሎ የሚያስብ ሰው ፈጽሞ አይገኝም። ከዚህ ይልቅ.. የብዙዎች ቀልብና ትኩረት በእንግሊዝ እና አየርላንድ አዘጋጅነት ወደሚካሄደው የ2028ቱ የአውሮፓ ዋንጫ (ዩሮ 2028) ማቅናት ጀምሯል።
ከዚህ ስብስብ እየፈለቀ ያለውን ደማቅ ተሰጥኦ፣ እንዲሁም የቱርክ ደጋፊዎች ቡድናቸውን ተከትለው የትም በመሄድ ያላቸውን አስገራሚ ስሜት ቀስቃሽነትና ዝና ስንመለከት፣ ቡድኑ በቀጣዩ ታላቅ የውድድር መድረክ ላይ እጅግ ገዝፎ እና በከፍተኛ ጥንካሬ ተመልሶ እንደሚመጣ ብዙዎች በፅኑ ያምናሉ።
እንደ አርዳ ጉለር፣ ኬናን ዪልዲዝና ፌርዲ ካዲዮግሉን የመሳሰሉ ተጫዋቾች በአውሮፓ እግር ኳስ መድረክ እጅግ ማራኪና ተስፋ ሰጪ ከሚባሉ ወጣት ኮከቦች ተርታ የሚሰለፉ ናቸው። ይህ ደግሞ ቡድኑ ከውድድሩ በጊዜ መሰናበቱ የፈጠረውን ሀዘን አሽሽቶ፣ ለደጋፊዎቹ እውነተኛ የተስፋ ብርሃን ፈንጥቆላቸዋል።
በአሁኑ ሰዓት በቡድኑ ዙሪያ ያለው ስሜት በከፍተኛ ሀዘንና ቁጭት የተዋጠ መሆኑ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በቱርክ ውስጥ ይህ ድንቅ ትውልድ አቅሙ ተሟጦ ማብቂያው ላይ ደርሷል ብሎ የሚያስብ ሰው ፈጽሞ አይገኝም። ከዚህ ይልቅ.. የብዙዎች ቀልብና ትኩረት በእንግሊዝ እና አየርላንድ አዘጋጅነት ወደሚካሄደው የ2028ቱ የአውሮፓ ዋንጫ (ዩሮ 2028) ማቅናት ጀምሯል።
ከዚህ ስብስብ እየፈለቀ ያለውን ደማቅ ተሰጥኦ፣ እንዲሁም የቱርክ ደጋፊዎች ቡድናቸውን ተከትለው የትም በመሄድ ያላቸውን አስገራሚ ስሜት ቀስቃሽነትና ዝና ስንመለከት፣ ቡድኑ በቀጣዩ ታላቅ የውድድር መድረክ ላይ እጅግ ገዝፎ እና በከፍተኛ ጥንካሬ ተመልሶ እንደሚመጣ ብዙዎች በፅኑ ያምናሉ።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የልጅነት እንባ እና የድል መንገድ - ሮናልዶ ከትላንት እስከ ዛሬ
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
**********************
የ2004 አውሮፓ ዋንጫ ብዙ ትዝታዎች አሉት። የኦቶ ሪሃግሎቹ ግሪኮች ፖርቹጋሎችን በጥብቅ መከላከል በገዛ ሜዳቸው የአውሮፓ ዋንጫውን መንጠቃቸው ብቻ ሳይሆን፤ ሊመጣ ብቅ እያለ ያለው አዲስ ኮከብ ትኩስ እንባ በሊዝበኑ ስታዲዮ ዳሉዝ ሲፈስ ትዝታው ዛሬም ርቆ ያልራቀ ቅርብ ነው።
ያን የዘመናዊ እግር ኳስ ህልው ትዝታ አስታከን ወደ ዛሬ እንዘልቃለን። ብዙ ውብ ትላንቶችን፣ ደማቅ ቀኖችን እና ውብ ምሽቶችን አልፎ እውን ወደሆነው ዛሬ እንመጣለን። ትዝታ ቢርቅም አያረጀምና፣ በዘመን መፈራረቅም አይደበዝዝምና ብትውስታ ጎዳና እንመላለሳለን።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ዶስ ሳንቶስ አቪየሮ የሚባል ስም፣ በአባቱ መሻት የሮናልድ ሬገንን መጠሪያ እንዲጋራ የሆነ፣ በልጅነቱ አይጋፈጡትን ፈተና የተጋፈጠ፣ የሊዝበን ሰዎች በአፍላነቱ ሳይጠግቡ የተለዩት፣ የላንክ ሻየር ሰዎች ደግሞ ውብ ማለዳውን የተጋሩት፣ ውለታን የማይረሳው ዛሬም በስኬት ደጃፎች እየተመላለሰ ያለ ህያው ኮከብ ነው።
በሰር አሌክስ ፈርጉሰን እና በማንቸስተር ዩናይትድ መልማዮች ዓይን ውስጥ ከገባባት ከዚያች የወዳጅነት ጨዋታ ዕለት አንስቶ ዘመናዊ እግር ኳስ ሌላ መልክ ነው የያዘው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከዚህ ኮከብ ጋር በበርካታ ዋንጫዎች የተገመደ ብዙ የድል ቀናትን አልፏል።
ወደ ሎስ ብላንኮዎቹ ቅፅር ዘልቆም በነጩ መለያ ለሪያል ማድሪድ በሀገር ውስጥም በአውሮፓ መድረክም የሚደረገውን ሁሉ አድርጓል። ቱሪንም እጇን ዘርግታ ነው የተቀበለችው። እዚያም ስኬት ከእርሱ ጋር ነበረች።
በድኅረ ኮቪድ 19 የመጀመሪያ ወቅቶች ወደ ኦልድትራፎርድ ሲመለስ የቀዮቹ ደጋፊዎች ትዝታቸውን እንደሸከፉ ነበርና “እንኳን መጣህልን” ነበር ያሉት።
ሆኖም የማቸስተር ዩናይትድ ዳግም ምልሰቱ እንደ ትላንት ስል፣ እንደ ዕድሜውም በውጤት ብስል አልሆነም። ከኤሪክ ቴንሀግ ጋር የጋባበት መቃቃር ደግሞ ወደ መውጫው በር እንዲያማትር ዋነኛ ምክኒያት ሆነ።
ወደ መካከለኛው ምስራቅ ዘለቀ፤ በእግር ኳስ ብዙ መዋዕለ ንዋይ አፍስሳ ግዙፍ ለውጥ ወደ ሻተችው ሳዑዲ አረቢያ አቀና። ከሳምንታት በፊትም ለሦስት ዓመታት የተጠበቀውን የሳዑዲ ፕሮ ሊግ ሻምፒዮንነት ከክለቡ ዐል-ናስር ጋር አነሳ።
ሆኖም ጥያቄ ነበር። እነዚህን ሁሉ ቁጥራቸው የበረከቱ ስኬቶች ወደ ብሔራዊ ቡድን የሚተረጉማቸውስ መቼ ነው? የሚል።
በእርግጥ የ2016ቱን አውሮፓ ዋንጫ ሲያነሳ ይህ ጥያቄ በከፊል የተመለሰ መስሎ ነበር። የአውሮፓ ሀገራት ዋንጫ/ ኔሽንስ ሊግንም አንስቷል።
ግን ግዙፉ የዓለም ዋንጫስ? እግር ኳስ በታሪኩ ካስመለከታቸው ኮከቦች ለምሉዕነት አንድ መስፈርቱ ይኸው መድረክ ነውና፤ የእርሱስ ቀን አይመጣም ወይ? ተብሎ ተጠብቋል። እስካሁን ያ ቀን አልመጣም።
በእርግጥ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ በተቆጠሩ ግቦች ከሊዮኔል ሜሲ እና ከኢራናዊው ዓሊ ዳይ በእጅጉ ርቋል። በዚህ በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ደግሞ በመድረኩ ከተሳተፉ አንጋፋ ተጫዋቾች አንዱ ሆኖ ወደ አሜሪካ ምድር ሲዘልቅ ብዙ ጥበቃዎች ነበሩ። እነዛ ጥበቃዎች ግን በመጀመሪያው የምድብ ጨዋታ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ያለግብ ሲለያዩ ጥርጣሬ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገ ሆነ። በርከት ያሉ ትችቶች እርሱም ሆነ የቡድን አጋሮቹ ላይ መሰንዘራቸው አልቀረም።
ቀን ጠብቆ በአሉታ ለተቹትም፣ በበጎ ለጠበቁትም ምላሽ ሰጥቷል። ኡዝቤኪስታንን 5 ለ 0 በረቱበት ጨዋታ ከመረብ ያሳረፋቸው እነዚያ ሁለት ግቦች ትችቶቹን አቅጣጫ ማስቀየሪያ ብቻ አልሆኑም። አዳዲስ ክብረ ወሰኖችንም አስከትለዋል።
ሮናልዶ ከካሜሩናዊው ሮጀር ሚላ በመቀጠል በመድረኩ ግብ ያስቆጠረ አንጋፋ ተጫዋች ተሰኝቷል፤ ከ2006 የጀርመን ዓለም ዋንጫ እስከ 23ኛው የአሜሪካ ምድር ዓለም ዋንጫ በተሳተፈባቸው 6 ውድድሮች በሁሉም ግብ በማስቆጠር ደግሞ የመጀመሪያው ተጫዋች ሆኗል።
በጨዋታ ዘመኑ ያስቆጠራቸው ግቦችም 975 ደርሰዋል። በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ደግሞ 145ኛ ግቡን በማስቆጠር ከተከታዩ ሊዮኔል ሜሲ ጋር ያለውን ልዩነት ወደ 23 አስፍቷል።
በጨለማ ከመሰለው አስቸጋሪ ሳምንት በኋላ፣ ትችት ከበረከተባቸው ሰሞናት በኋላ “ተመልሰናል” ብሏል ሮናልዶ። በግል የሚመዘገቡ ክብረ ወሰኖች መልካም ቢሆኑም፤ ቀዳሚ ግቡ ግን ቡድኑን መርዳትና ለአሸናፊነት ማብቃት መሆኑን ነው የገለፀው።
ያ መንገድ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዛሬም ቀጥሏል። እንደ ትላንቱ ባይሰላም ለተባለው ሁሉ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጠ አለ። የትችት ወጀብ ሳይገታው፣ የዕድሜ መግፋትም ሳይረታው እንደ ጥንቱ ስል ባይሆንም አለሁ እያለ ነው።
ዋይኒ ሩኒ የተናገው ይህን በሚገባ ይገልፃል።ሮናልዶ ትችትን ማስተናገድ፣ ለትችቱም አስፈላጊውን ተግባራዊ ምለሽ መስጠት በእግር ኳስ ዘመኑ ሁሉ የተጓዘበት እውነት ነው።
“ትዝታ አያረጅም” ሲባል በጎም ይሁን መጥፎ በአዕምሮ ጓዳ ደጋግሞ ስለሚመላለስ ነው። ሮናልዶ ግን ያለፈ ትዝታ፤ ያላለፈ ዛሬ ነው።
እነዚያ በፅናት የተጓዘባቸው ውጤታማ ዓመታት፣ ያንን የሊዝበን ሰታዲየም እንባ ይገልፃሉ። ያ የእልህ እና የቁጭት እንባ፤ ከዓመታት በኋላ ዛሬም ትኩስ ነው፣ አልቀዘቀዘም!
በእድሪስ አህመድ
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #sports #ronaldo #football
1 month ago
ልብ ሰባሪው የሞት ዜና
#fastmereja I ከሁለት ወር በኋላ በጋብቻ ለመቀላቀል እና አዲስ ህይወትን ለመጀመር ተስፋ ሰንቀው የነበሩ ጥንዶች፣ ባልታሰበ የሞት ዜና መለያየታቸው ታወቀ። እጮኛዋን በሞት የተነጠቀችው ወጣት፣ በሃዘን የተሞላ የመሰናበቻ መልዕክቷን በማህበራዊ ሚዲያ ይፋ አድርጋለች።
ወጣቷ ሙሽራ በፃፈችው የሃዘን መግለጫ፣ የሟች እጮኛዋን መልካም ስነ-ምግባር እና ለእሷ የነበረውን ፍቅር በቁጭት ገልጻለች። “ያንተን ያህል የሚወድ፣ የሚያከብርና በጸሎቱ የሚጠብቀኝ ቅን ሰው አጣሁ” ስትል ስሜቷን ተናግራለች። በአጭር ጊዜ ውስጥ ለእሷ እውነተኛ ደስታን የሰጠ መሆኑን የጠቀሰችው ወጣቷ፣ በጋራ ለመመስረት ያሰቡት ህይወት በሞት መቋረጡን በሃዘን አስታውሳለች።
የሟች እጮኛዋን በሰላም እንዲያርፍ መልካም ምኞቷን የገለጸችው ወጣቷ፣ በልቧ እና በፀሎቷ ሁሌም እንደምትዘክረው በመግለጽ የመጨረሻ የፍቅር አደራዋን አስተላልፋለች።
ለሟች ቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሙሽራይቱ መጽናናትን እንመኛለን።
#fastmereja I ከሁለት ወር በኋላ በጋብቻ ለመቀላቀል እና አዲስ ህይወትን ለመጀመር ተስፋ ሰንቀው የነበሩ ጥንዶች፣ ባልታሰበ የሞት ዜና መለያየታቸው ታወቀ። እጮኛዋን በሞት የተነጠቀችው ወጣት፣ በሃዘን የተሞላ የመሰናበቻ መልዕክቷን በማህበራዊ ሚዲያ ይፋ አድርጋለች።
ወጣቷ ሙሽራ በፃፈችው የሃዘን መግለጫ፣ የሟች እጮኛዋን መልካም ስነ-ምግባር እና ለእሷ የነበረውን ፍቅር በቁጭት ገልጻለች። “ያንተን ያህል የሚወድ፣ የሚያከብርና በጸሎቱ የሚጠብቀኝ ቅን ሰው አጣሁ” ስትል ስሜቷን ተናግራለች። በአጭር ጊዜ ውስጥ ለእሷ እውነተኛ ደስታን የሰጠ መሆኑን የጠቀሰችው ወጣቷ፣ በጋራ ለመመስረት ያሰቡት ህይወት በሞት መቋረጡን በሃዘን አስታውሳለች።
የሟች እጮኛዋን በሰላም እንዲያርፍ መልካም ምኞቷን የገለጸችው ወጣቷ፣ በልቧ እና በፀሎቷ ሁሌም እንደምትዘክረው በመግለጽ የመጨረሻ የፍቅር አደራዋን አስተላልፋለች።
ለሟች ቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እና ለሙሽራይቱ መጽናናትን እንመኛለን።
2 months ago
ቄራ ላይ ታላቅ ሕዝባዊ የእግር ክኳስ ክለብ ተቋቋመ!
#ethiopia | በኢትዮጵያ እግር ካስ ታሪክ ውስጥ አንጋፋና ታላቅ ስም ያለው የቄራ አንበሳ ክለብ ዳግም ተቋቁሟል። ይህ ክለብ መሠረቱ በታላቋ ቄራ አልማዝዬ ሜዳ ሲሆን ከሃምሳ ስምንት አመት በኋላ ተጠናክሮ መጥቷል።
ባሳለፍነው እሁድ ከአንድ ሺህ በላይ የቄራና አካባቢው ነዎሪዎች በተለይም ቡድኑ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ጋር ተስተካካይ ዕድሜ ላይ እንደመገኘቱ በዚህ መልክ ወደኋላ መቅረቱ ቁጭት የፈጠረባቸው በምሥረታ ጉባኤ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።
አልማዝዬ ሜዳ ያፈራቻቸው ለብሔራዊና ለክለብ የተጫወቱ በርካታ ተጫዋቾች እጅ ለእጅ በመያያዝ ለክለቡ ድጋፍ ለማድረግ በዕለቱ ቃል ገብተዋል።
የቄራ አንበሳ ቀደም ሲል ፕሪሚየር ሊግ ለመግባት ጫፍ የደረሰ ቢሆንም በፋይናንስ ችግር ከውድድር ርቆ ለመቆየት ተገዷል።
አሁን ግን በአካባቢው ባለሀብቶች እየታገዘ ጥሩ ደረጃ ላይ ሲገኝ የአልማዝዬ የታዳጊ ፕሮጄክት አንዱ ማሳዬ ነው።
" ቄራ ተወልዳችሁ በእግር ኳስ ያለፋችሁ አካባቢያችሁን አልፋችሁ ውበት የለም። ስለሆነም ቄራ ታስገድዳችሁለች" በሚል ለብሄራዊ እና ክለብ ተጫዋች ለሆኑ የአልማዝዬ ሜዳ ፈርጦች ትልቅ የቤት ሥራ ተሰጥቶአቸዋል።
አልማዝዬ ሜዳ በዚህ መልኩ ዘመናዊ ሆኖ ለቄራ ማሕበረስብ እንዲያገለግል ያደረጉት ክብርት ከንቲባ አዳነች አቢቤ በጉባኤው ተመስግነዋል።
https://youtu.be/ytB-gccE6...
#ethiopia | በኢትዮጵያ እግር ካስ ታሪክ ውስጥ አንጋፋና ታላቅ ስም ያለው የቄራ አንበሳ ክለብ ዳግም ተቋቁሟል። ይህ ክለብ መሠረቱ በታላቋ ቄራ አልማዝዬ ሜዳ ሲሆን ከሃምሳ ስምንት አመት በኋላ ተጠናክሮ መጥቷል።
ባሳለፍነው እሁድ ከአንድ ሺህ በላይ የቄራና አካባቢው ነዎሪዎች በተለይም ቡድኑ ከቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና ጋር ተስተካካይ ዕድሜ ላይ እንደመገኘቱ በዚህ መልክ ወደኋላ መቅረቱ ቁጭት የፈጠረባቸው በምሥረታ ጉባኤ ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።
አልማዝዬ ሜዳ ያፈራቻቸው ለብሔራዊና ለክለብ የተጫወቱ በርካታ ተጫዋቾች እጅ ለእጅ በመያያዝ ለክለቡ ድጋፍ ለማድረግ በዕለቱ ቃል ገብተዋል።
የቄራ አንበሳ ቀደም ሲል ፕሪሚየር ሊግ ለመግባት ጫፍ የደረሰ ቢሆንም በፋይናንስ ችግር ከውድድር ርቆ ለመቆየት ተገዷል።
አሁን ግን በአካባቢው ባለሀብቶች እየታገዘ ጥሩ ደረጃ ላይ ሲገኝ የአልማዝዬ የታዳጊ ፕሮጄክት አንዱ ማሳዬ ነው።
" ቄራ ተወልዳችሁ በእግር ኳስ ያለፋችሁ አካባቢያችሁን አልፋችሁ ውበት የለም። ስለሆነም ቄራ ታስገድዳችሁለች" በሚል ለብሄራዊ እና ክለብ ተጫዋች ለሆኑ የአልማዝዬ ሜዳ ፈርጦች ትልቅ የቤት ሥራ ተሰጥቶአቸዋል።
አልማዝዬ ሜዳ በዚህ መልኩ ዘመናዊ ሆኖ ለቄራ ማሕበረስብ እንዲያገለግል ያደረጉት ክብርት ከንቲባ አዳነች አቢቤ በጉባኤው ተመስግነዋል።
https://youtu.be/ytB-gccE6...
2 months ago
"የምሁራን ዝምታ ያሳሰበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም!"
- ፕ/ር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፣ አሁን ያለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ምሁራን ዳር ቆመው የሚመለከቱበት ጊዜ እንዳልሆነ በቁጭት ገለጹ።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በዋናነት የምሁራንን ዕውቀትና የሰላ ሀሳብ የሚፈልግ ቢሆንም፣ ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ ከማድረግ ይልቅ "ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡ" በእጅጉ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ፣ የምሁራንን ሚና አስፈላጊነት ለማስረዳት ሲሉ ለምክክር ሂደቱ የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ለመለየት የተጓዙበትን ፈታኝ ሂደት እንደ አብነት ጠቅሰዋል። ይህም ምሁራን ለሀገራዊ ጉዳዮች ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለባቸው ያሳያል ብለዋል።
ምሁራኑ በዝምታ ቢታቀቡም፣ በሌላ በኩል በየአካባቢው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጓቸው ጉዞዎች ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎችን መመልከታቸውን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፦
የህዝብ አንድነት
ኢትዮጵያውያን በቋንቋና በባህል ልዩነቶች ቢኖሩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና በኢትዮጵያዊነት ስሜት የተሳሰሩ መሆናቸውን ታዝበዋል።
የህዝብ ተስፋና ቅሬታ
አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ለገጠማት ችግር እንደ ዋነኛ ምንጭ የሚቆጥረው "ምሁራንንና የፖለቲካ ልሂቃንን" ነው። ህዝቡ መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የምክክር ሂደቱ አስፈላጊነት
ፕ/ር መስፍን አያይዘውም፣ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት ተወያይተው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው፣ ሂደቱ ለራሱ ታሪካዊና አስተማሪ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ" የምሁራኑን ዝምታ በመስበር ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ፕ/ር መስፍን
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ
- ፕ/ር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፣ አሁን ያለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ምሁራን ዳር ቆመው የሚመለከቱበት ጊዜ እንዳልሆነ በቁጭት ገለጹ።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በዋናነት የምሁራንን ዕውቀትና የሰላ ሀሳብ የሚፈልግ ቢሆንም፣ ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ ከማድረግ ይልቅ "ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡ" በእጅጉ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ፣ የምሁራንን ሚና አስፈላጊነት ለማስረዳት ሲሉ ለምክክር ሂደቱ የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ለመለየት የተጓዙበትን ፈታኝ ሂደት እንደ አብነት ጠቅሰዋል። ይህም ምሁራን ለሀገራዊ ጉዳዮች ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለባቸው ያሳያል ብለዋል።
ምሁራኑ በዝምታ ቢታቀቡም፣ በሌላ በኩል በየአካባቢው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጓቸው ጉዞዎች ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎችን መመልከታቸውን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፦
የህዝብ አንድነት
ኢትዮጵያውያን በቋንቋና በባህል ልዩነቶች ቢኖሩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና በኢትዮጵያዊነት ስሜት የተሳሰሩ መሆናቸውን ታዝበዋል።
የህዝብ ተስፋና ቅሬታ
አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ለገጠማት ችግር እንደ ዋነኛ ምንጭ የሚቆጥረው "ምሁራንንና የፖለቲካ ልሂቃንን" ነው። ህዝቡ መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የምክክር ሂደቱ አስፈላጊነት
ፕ/ር መስፍን አያይዘውም፣ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት ተወያይተው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው፣ ሂደቱ ለራሱ ታሪካዊና አስተማሪ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ" የምሁራኑን ዝምታ በመስበር ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ፕ/ር መስፍን
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ
2 months ago
የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም አሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ፡፡
መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ ኮሚሽኑን ተቀላቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያደረጓቸው ጉዞዎች አዲስና ተስፋ ሰጪ እይታ እንደጨመሩላቸው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በቋንቋ፣ በባህልና በጥቂት ሥነ ልቦናዊ ሁኔታዎች ቢለያዩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት ባላቸው አመለካከት በሚያስገርም ሁኔታ መመሳሰላቸው ትልቅ ተስፋ እንደሰጣቸው አውስተዋል፡፡
በአንጻሩ አብዛኛው የማሕበረሰብ ክፍል በሀገሪቱ የታዩት ችግሮች ምንጭ "ምሁራን እና የፖለቲካ ልሒቃን ናቸው" ብሎ እንደሚያምን እና መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
"ሕዝቡ ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ እኛም ተካትተን መመካከር መቻላችን ትልቅ ዕድል ነው" እያለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የምሁራኑ ለዘብተኝነትና ዳር ሆኖ መመልከት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ዋና ኮሚሽነሩ በቁጭት ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክሩ ሒደት በብዛት የምሁራንን ዕውቀትና ግብዓት የሚሻ ቢሆንም ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡን በማንሳት፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ አሁን ዳር ቆሞ የመመልከቻ ጊዜ አይደለም" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ ምክንያት አብነት አድርገው የጠቀሱት ኮሚሽኑ ሒደቱን ለመምራት የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ፍለጋ ፈታኝ ጊዜ ማሳለፉን ነው፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት መክረው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው ሒደቱ በራሱ ትልቅ አስተማሪና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት፡፡
ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም አሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ፡፡
መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ ኮሚሽኑን ተቀላቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያደረጓቸው ጉዞዎች አዲስና ተስፋ ሰጪ እይታ እንደጨመሩላቸው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በቋንቋ፣ በባህልና በጥቂት ሥነ ልቦናዊ ሁኔታዎች ቢለያዩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት ባላቸው አመለካከት በሚያስገርም ሁኔታ መመሳሰላቸው ትልቅ ተስፋ እንደሰጣቸው አውስተዋል፡፡
በአንጻሩ አብዛኛው የማሕበረሰብ ክፍል በሀገሪቱ የታዩት ችግሮች ምንጭ "ምሁራን እና የፖለቲካ ልሒቃን ናቸው" ብሎ እንደሚያምን እና መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
"ሕዝቡ ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ እኛም ተካትተን መመካከር መቻላችን ትልቅ ዕድል ነው" እያለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የምሁራኑ ለዘብተኝነትና ዳር ሆኖ መመልከት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ዋና ኮሚሽነሩ በቁጭት ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክሩ ሒደት በብዛት የምሁራንን ዕውቀትና ግብዓት የሚሻ ቢሆንም ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡን በማንሳት፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ አሁን ዳር ቆሞ የመመልከቻ ጊዜ አይደለም" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ ምክንያት አብነት አድርገው የጠቀሱት ኮሚሽኑ ሒደቱን ለመምራት የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ፍለጋ ፈታኝ ጊዜ ማሳለፉን ነው፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት መክረው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው ሒደቱ በራሱ ትልቅ አስተማሪና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት፡፡
ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtube.com/watch?...
2 months ago
ዛሬ ቀኑ ነው‼️
🎂 ዛሬ የእሱ ቀን ነው፦
በኦሊምፒክ 3 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሻምፒዮና 5 ወርቅ እና 1 ነሃስ ሜዳሊያ
በአለም ሀገር አቋራጭ 11 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሜጀር ማራቶን 2 ወርቅ 2 ብር እና 2 ነሀስ ሜዳሊያ
🎂 ዛሬ የጀግናው ቀን ነው፦
የ2004/5 የአለም የአመቱ ምርጥ አትሌት
የ2004/5 የትራክና ፊልድ ኒውስ የአመቱ ምርጥ አትሌት
የየኢኤስፒኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቁጥር አንድ አትሌት
ከስድስት በላይ የአለም ክብረወሰኖችን የሰበረ አትሌት
🎂 ዛሬ እለቱ ነው፦
ሱሉልታ ላይ ዘመናዊ ትራክ ያለው
አዲስ አበባ፣ ሱሉልታና አሰላ ላይ የሆቴሎች ባለቤት
ሱሉልታ ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት የከፈተ
በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ያሰራ
በበጎ አድራጎት ተግባራት ቀድሞ የሚገኝ
ታዳጊ አትሌቶችን በገንዘብና በትጥቅ የሚደግፍ
🎂 ዛሬ የእሱ ቅዳሜ ነው፦
ከቤተሰቡ 6 ፍሬዎች መካከል 2ኛ ልጅ የሆነ
3 ወንድምና 2 እህቶች ያሉት
ከባለቤቱ ዳናዊት ገ/እግዚአብሔር 2 ሴት እና 1 ወንድ ልጅ ያፈራ
🎂 ዛሬ የዝምተኛው ገዳይ ቀን ነው፦
በ27 አመታት የሩጫ አለም ቆይታው ከ200 በላይ ውድድሮችን ያደረገ፥ ብሄራዊ መዝሙራችንን በአለም ፊት ደጋግሞ ያዘመረ፥ ሰንደቃችንን ከፍ አድርጎ ያሰቀለ፥ ከአርሲ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት የተቀበለ፥ በአዲስ ስፖርት ፓርክ የክብር ሃውልት የቆመለት፥ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሰራ
🎂 ዛሬ የቀነኒ ኬኛ እለት ነው
የትዕግስት፣ የቁጭት፣ የፅናት፣ የጥረት፣ የተስፋ፣ የእልህ፣ የልፋት ከዛ የስኬት ተምሳሌት ኢትዮጵያዊው ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 6/2018 ልደቱ ነው
44 አመት ሞላው🎂
ቀነኒ ኬኛ ለኢትዮጵያ እንኳን ተወለድክላት! መልካም ልደት!
Via: ታምሩ ዓለሙ
🎂 ዛሬ የእሱ ቀን ነው፦
በኦሊምፒክ 3 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሻምፒዮና 5 ወርቅ እና 1 ነሃስ ሜዳሊያ
በአለም ሀገር አቋራጭ 11 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሜጀር ማራቶን 2 ወርቅ 2 ብር እና 2 ነሀስ ሜዳሊያ
🎂 ዛሬ የጀግናው ቀን ነው፦
የ2004/5 የአለም የአመቱ ምርጥ አትሌት
የ2004/5 የትራክና ፊልድ ኒውስ የአመቱ ምርጥ አትሌት
የየኢኤስፒኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቁጥር አንድ አትሌት
ከስድስት በላይ የአለም ክብረወሰኖችን የሰበረ አትሌት
🎂 ዛሬ እለቱ ነው፦
ሱሉልታ ላይ ዘመናዊ ትራክ ያለው
አዲስ አበባ፣ ሱሉልታና አሰላ ላይ የሆቴሎች ባለቤት
ሱሉልታ ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት የከፈተ
በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ያሰራ
በበጎ አድራጎት ተግባራት ቀድሞ የሚገኝ
ታዳጊ አትሌቶችን በገንዘብና በትጥቅ የሚደግፍ
🎂 ዛሬ የእሱ ቅዳሜ ነው፦
ከቤተሰቡ 6 ፍሬዎች መካከል 2ኛ ልጅ የሆነ
3 ወንድምና 2 እህቶች ያሉት
ከባለቤቱ ዳናዊት ገ/እግዚአብሔር 2 ሴት እና 1 ወንድ ልጅ ያፈራ
🎂 ዛሬ የዝምተኛው ገዳይ ቀን ነው፦
በ27 አመታት የሩጫ አለም ቆይታው ከ200 በላይ ውድድሮችን ያደረገ፥ ብሄራዊ መዝሙራችንን በአለም ፊት ደጋግሞ ያዘመረ፥ ሰንደቃችንን ከፍ አድርጎ ያሰቀለ፥ ከአርሲ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት የተቀበለ፥ በአዲስ ስፖርት ፓርክ የክብር ሃውልት የቆመለት፥ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሰራ
🎂 ዛሬ የቀነኒ ኬኛ እለት ነው
የትዕግስት፣ የቁጭት፣ የፅናት፣ የጥረት፣ የተስፋ፣ የእልህ፣ የልፋት ከዛ የስኬት ተምሳሌት ኢትዮጵያዊው ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 6/2018 ልደቱ ነው
44 አመት ሞላው🎂
ቀነኒ ኬኛ ለኢትዮጵያ እንኳን ተወለድክላት! መልካም ልደት!
Via: ታምሩ ዓለሙ
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ቀያይ ሰይጣኖቹ ለፕሪሚየር ሊጉ ባስገቡት የዘንድሮ የተጫዋቾች ዝርዝር መሰረት በኦልድ ትራፎርድ ግርማ ሞገስ ነበራቸው የተባሉ ተጫዋቾች የማንቸስተር ቆይታቸው ማብቃቱ በይፋ ተረጋግጧል። ከነዚህም መካከል ዋነኛው እንግሊዛዊው የክንፍ ተጫዋች ጃዶን ሳንቾ ነው። ማንቸስተር ዩናይትድ ከ73 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ካዝናውን አራቁቶ ያመጣው ይህ ኮከብ፣ ከክለቡ ጋር የነበረው ቆይታ እጅግ አሳዛኝ እና ኪሳራ የበዛበት ሆኖ አልፏል። አቋሙን ማግኘት ተስኖት ከቀድሞ አሰልጣኞች ጋር ጭምር እሰጥ አገባ ውስጥ ገብቶ የነበረው ሳንቾ.. በመጨረሻም የክለቡን በር ለዘለቄታው ዘግቶ ወጥቷል። ከእሱ ጋርም ብራዚላዊው አንጋፋ አማካይ ካሴሚሮ እና ታይረል ማላሲያ ስንብታቸው ተረጋግጧል።
ማንቸስተር ዩናይትድ ባወጣው ይፋዊ የመሰናበቻ መግለጫ "ጃዶን ሳንቾ በ2021 ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ የ2023ቱን የካራባኦ ካፕ ካነሳው ስብስብ አንዱ ነበር። ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በውሰት ከመመለሱ፣ እንዲሁም በቼልሲ እና አስቶን ቪላ ጊዜያዊ ቆይታዎችን ከማድረጉ በፊት ለክለቡ 83 ጨዋታዎችን አድርጓል። ክለባችን ካሴሚሮ፣ ታይረል እና ጃዶን ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመሰገነ፣ ለቀጣይ የእግር ኳስ ህይወታቸው መልካሙን ሁሉ ይመኛል" ብሏል።
የማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ ከብዶት የታየው የ26 ዓመቱ አጥቂ፣ በአምስት ዓመት የዩናይትድ ቆይታው በሁሉም ውድድሮች ማግባት የቻለው 12 ጎሎችን እና 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ማቀበል ብቻ ነው። ይህ ደካማ አቋሙ የቀድሞ የክለቡን ተጫዋቾች ሳይቀር አበሳጭቷል። በተለይም ሉዊስ ሳሃ፣ ሳንቾን "በማንቸስተር ዩናይትድ ታሪክ እጅግ አሳዛኙ ፈራሚ" ሲል ከባድ ትችት ሰንዝሮበታል።
ሳሃ በቁጭት ስሜት ሲናገር... "ከመምጣቱ በፊት በቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያሳየው አስገራሚ ብቃት እና የነበረው ተሰጥኦ ታላቅ ተስፋ ሰጥቶን ነበር፤ እንግሊዝ መጥቶ ያ ሁሉ መጥፋቱ ግን እንቆቅልሽ ሆኖብኛል። እኔ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆኔ እድለኛ ነበርኩ፣ ግን በጉዳት ብዙ ጊዜ አሳልፌያለሁ። በእሱ ዕድሜ እና ተሰጥኦ የሱን ያህል ጨዋታዎችን መጫወት ብችል ምንኛ መታደል ነበር... አስገራሚ ነገሮችን ማድረግ የሚችል ልጅ ነው፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ችሎታው እና የተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሲባክኑ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል" ብሏል።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቢቸገርም በጀርመን ምድር ግን ሳንቾ አሁንም ትልቅ ከበሬታ እና ስም አለው። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፣ ተጫዋቹ ከ2021 ጀምሮ የጠፋበትን የእግር ኳስ ህይወቱን ዳግም ለማንሰራራት ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ለማምራት በሩን ክፍት አድርጓል። የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ኒኮ ኮቫችም ለዚህ ዝውውር አረንጓዴ መብራት አብርተዋል እየተባለ ይገኛል።
ሳንቾ የህይወቱን ምርጥ ጊዜ ያሳለፈው በዚሁ በሲግናል ኢዱና ፓርክ ሲሆን.. በመጀመሪያ ቆይታው በ137 ጨዋታዎች በ114 ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበረው። በ2024 በውሰት ተመልሶ ክለቡን እስከ ዌምብሌዩ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ማድረሱም አይዘነጋም። ወደ ቡንደስሊጋው መመለሱ፣ ከ2021 ጀምሮ ለተለየው የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ዳግም እንዲጠራ የሚያስችለውን መተማመን ሊሰጠው ይችላል።
የፋይናንስ መዛግብቱን ለማስተካከል እና አዲስ ጠንካራ ስብስብ ለመገንባት ቆርጦ የተነሳው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮቹን እያጸዳ ይገኛል። ከሳንቾ በተጨማሪ አንጋፋው ብራዚላዊ አማካይ ካሴሚሮ እና የግራ መስመር ተከላካዩ ታይረል ማላሲያ በኮንትራት መጠናቀቅ ምክንያት ተሰናብተዋል። ከሪያል ማድሪድ መጥቶ በአራት የውድድር ዘመናት ቆይታው የካራባኦ ካፕ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎችን ያነሳው ካሴሚሮ፤ እንዲሁም ከ2022 የፌይኖርድ ዝውውሩ በኋላ በጉዳት እየታመሰ 50 ጨዋታዎችን ብቻ ማድረግ የቻለው ማላሲያ የክለቡን በር ዘግተው ወጥተዋል።
አዲሱ የማንቸስተር ዩናይትድ የስፖርት አመራር እነዚህን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ተጫዋቾች ማሰናበቱ፣ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አዳዲስ እና ወጣት ደም ለማስገባት በደመወዝ በጀቱ ላይ ሰፊ የፋይናንስ ነጻነትን ፈጥሮለታል። አሁን የሁሉም አይን ዩናይትድ ይህንን ክፍተት በማን እንደሚተካው ላይ አርፏል!
ማንቸስተር ዩናይትድ ባወጣው ይፋዊ የመሰናበቻ መግለጫ "ጃዶን ሳንቾ በ2021 ወደ ኦልድ ትራፎርድ ከመጣ በኋላ የ2023ቱን የካራባኦ ካፕ ካነሳው ስብስብ አንዱ ነበር። ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ በውሰት ከመመለሱ፣ እንዲሁም በቼልሲ እና አስቶን ቪላ ጊዜያዊ ቆይታዎችን ከማድረጉ በፊት ለክለቡ 83 ጨዋታዎችን አድርጓል። ክለባችን ካሴሚሮ፣ ታይረል እና ጃዶን ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመሰገነ፣ ለቀጣይ የእግር ኳስ ህይወታቸው መልካሙን ሁሉ ይመኛል" ብሏል።
የማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ ከብዶት የታየው የ26 ዓመቱ አጥቂ፣ በአምስት ዓመት የዩናይትድ ቆይታው በሁሉም ውድድሮች ማግባት የቻለው 12 ጎሎችን እና 6 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ማቀበል ብቻ ነው። ይህ ደካማ አቋሙ የቀድሞ የክለቡን ተጫዋቾች ሳይቀር አበሳጭቷል። በተለይም ሉዊስ ሳሃ፣ ሳንቾን "በማንቸስተር ዩናይትድ ታሪክ እጅግ አሳዛኙ ፈራሚ" ሲል ከባድ ትችት ሰንዝሮበታል።
ሳሃ በቁጭት ስሜት ሲናገር... "ከመምጣቱ በፊት በቦሩሲያ ዶርትሙንድ ያሳየው አስገራሚ ብቃት እና የነበረው ተሰጥኦ ታላቅ ተስፋ ሰጥቶን ነበር፤ እንግሊዝ መጥቶ ያ ሁሉ መጥፋቱ ግን እንቆቅልሽ ሆኖብኛል። እኔ እግር ኳስ ተጫዋች በመሆኔ እድለኛ ነበርኩ፣ ግን በጉዳት ብዙ ጊዜ አሳልፌያለሁ። በእሱ ዕድሜ እና ተሰጥኦ የሱን ያህል ጨዋታዎችን መጫወት ብችል ምንኛ መታደል ነበር... አስገራሚ ነገሮችን ማድረግ የሚችል ልጅ ነው፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ችሎታው እና የተሰለፈባቸው ጨዋታዎች ሲባክኑ ማየት በእጅጉ ያሳዝናል" ብሏል።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቢቸገርም በጀርመን ምድር ግን ሳንቾ አሁንም ትልቅ ከበሬታ እና ስም አለው። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከሆነ፣ ተጫዋቹ ከ2021 ጀምሮ የጠፋበትን የእግር ኳስ ህይወቱን ዳግም ለማንሰራራት ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ቦሩሲያ ዶርትሙንድ ለማምራት በሩን ክፍት አድርጓል። የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ኒኮ ኮቫችም ለዚህ ዝውውር አረንጓዴ መብራት አብርተዋል እየተባለ ይገኛል።
ሳንቾ የህይወቱን ምርጥ ጊዜ ያሳለፈው በዚሁ በሲግናል ኢዱና ፓርክ ሲሆን.. በመጀመሪያ ቆይታው በ137 ጨዋታዎች በ114 ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ነበረው። በ2024 በውሰት ተመልሶ ክለቡን እስከ ዌምብሌዩ የሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ ማድረሱም አይዘነጋም። ወደ ቡንደስሊጋው መመለሱ፣ ከ2021 ጀምሮ ለተለየው የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ዳግም እንዲጠራ የሚያስችለውን መተማመን ሊሰጠው ይችላል።
የፋይናንስ መዛግብቱን ለማስተካከል እና አዲስ ጠንካራ ስብስብ ለመገንባት ቆርጦ የተነሳው ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮቹን እያጸዳ ይገኛል። ከሳንቾ በተጨማሪ አንጋፋው ብራዚላዊ አማካይ ካሴሚሮ እና የግራ መስመር ተከላካዩ ታይረል ማላሲያ በኮንትራት መጠናቀቅ ምክንያት ተሰናብተዋል። ከሪያል ማድሪድ መጥቶ በአራት የውድድር ዘመናት ቆይታው የካራባኦ ካፕ እና የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫዎችን ያነሳው ካሴሚሮ፤ እንዲሁም ከ2022 የፌይኖርድ ዝውውሩ በኋላ በጉዳት እየታመሰ 50 ጨዋታዎችን ብቻ ማድረግ የቻለው ማላሲያ የክለቡን በር ዘግተው ወጥተዋል።
አዲሱ የማንቸስተር ዩናይትድ የስፖርት አመራር እነዚህን ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ ተጫዋቾች ማሰናበቱ፣ በቀጣዩ የዝውውር መስኮት አዳዲስ እና ወጣት ደም ለማስገባት በደመወዝ በጀቱ ላይ ሰፊ የፋይናንስ ነጻነትን ፈጥሮለታል። አሁን የሁሉም አይን ዩናይትድ ይህንን ክፍተት በማን እንደሚተካው ላይ አርፏል!
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የነፃነት ማኅተም፦ ከተረጂነት ወደ አምራችነት
************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እና ታላቅነቷን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብሔራዊ ክብር እና የሀገር ሉዓላዊነት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል።
ያለፉት ዘመናት መከራ እና የዕርዳታ ጥገኝነት ዛሬ ላይ የውስጥ አቅማችንን እንድንፈትሽ እና ወደ አዲስ የአርበኝነት ምዕራፍ እንድንሻገር ብርቱ ቁጭትን ፈጥሮብናል።
የሀገር ሉዓላዊነት የሚጸናው ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር በምግብ ራስን በመቻል፣ በቴክኖሎጂ እና በበጀት ሉዓላዊነት ምሰሶዎች ላይ መሆኑን በተግባር የተረዳንበት ወቅት ላይ እንገኛለን።
ይህን ታላቅ ዓላማ ለማሳካት ደግሞ ከተረጂነት መንፈስ ተላቅቆ ወደ ምርታማነት መሸጋገርን የሚጠይቅ አዲስ ዓይነት የኢኮኖሚ ዐርበኝነት የግድ ያስፈልገናል።
ሀገራችን “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት” በሚለው መሪ ዕሳቤ መሠረት፣ ሰብዓዊ ድጋፍን ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆ ወደ ዘላቂ አምራችነት የሚያሸጋግር የክብር መርሐ ግብር በቁርጠኝነት ወደ ተግባር አስገብታለች።
በሴፍቲኔት የሚደገፉ ዜጎች ከተረጂነት ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉ የድጋፍ እና የሥራ ዕድል የመፍጠር ሥራዎች በስፋት ተከውነዋል።
ክልሎች እና ዞኖች የራሳቸውን የምግብ መጠባበቂያ እንዲያዘጋጁ መደረጉም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ትልቅ መዋቅራዊ አቅም ፈጥሯል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ በምግብ ብቻ ሳይሆን ሀገራችን በመድኃኒት ምርትም ራሷን እንድትችል የሚደረገውን ጥረት ያጠቃልላል። ያለንን የተፈጥሮ ጸጋ እና አቅም ወደ ተጨባጭ ምርት ለመቀየር በተደረገው የላቀ ጥረት በስንዴ ልማት መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ከተመጽዋችነት እና ከልመና ታሪክ ያወጣ ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህን መልካም ተሞክሮ በሌሎች የግብርና ዘርፎችም ለመድገም በሩዝ፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ፣ በሻይ ቅጠል እና በሌሎች ሰብሎች ላይ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ ይገኛሉ።
የቀጣይ ዓመታት የመንግሥት ዋና ተግባር የሚሆነውም በሀገር ደረጃ የሚካሄደውን የሰብዓዊ ድጋፍ አሰጣጥ በማጠናከር፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች የሚመጡ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ሥራዎች ላይ ማተኮር እንደ ሆነ ተነግሯል። ይህም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂያዊ የምግብ ክምችት በሁሉም ደረጃ እንዲኖር ያስችላል።
ከዚህም አልፎ፣ “ኢትዮጵያዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያዊነት” የሚለው የትብብር ማዕቀፍ እየተጠናከረ ይሄዳል። ለዚህም በመገባደድ ላይ ባለው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሰብዓዊ ድጋፍን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለመሸፈን በትጋት እየተሠራ ነው።
ይህ ተግባር የጥገኝነትን እና የልመናን የቆየ ፖለቲካዊ ዕሳቤ ሙሉ በሙሉ የሚሽር፣ የኢትዮጵያን የአምራችነት እና የማንሰራራት ወርቃማ ዘመን የሚያበሥር ነው።
የታሪክ አውራ የሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሀብቶች፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና ለሥራ ትጉ የሆነ ሰፊ የወጣት ኃይል የታደለች ናት። ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በቁጭት እና በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ካመረትን የማይታለፍ አቀበት፣ የማይሸነፍ የድህነት ታሪክ አይኖርም።
ብሔራዊ መጠባበቂያን በማደራጀት እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በመተግበር፣ ኢትዮጵያ አምራች ሀገር ሆና በምግብ ሉዓላዊነቷ የተከበረች እንድትሆን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል።
እስካሁን ሀገራችንን ከጠላቶቿ ለመጠበቅ እና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር የደም ዋጋ ጭምር ከፍለን እንዳቆየናት ሁሉ፣ በቀጣይም ሌት ተቀን ሠርተን በማምረት ሀገራችንን ከምግብ ተረጂነት እና ከጥገኝነት ማላቀቅ የታሪካዊ ግዴታችን ማኅተም ሊሆን ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #selfrelience
************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እና ታላቅነቷን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብሔራዊ ክብር እና የሀገር ሉዓላዊነት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል።
ያለፉት ዘመናት መከራ እና የዕርዳታ ጥገኝነት ዛሬ ላይ የውስጥ አቅማችንን እንድንፈትሽ እና ወደ አዲስ የአርበኝነት ምዕራፍ እንድንሻገር ብርቱ ቁጭትን ፈጥሮብናል።
የሀገር ሉዓላዊነት የሚጸናው ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር በምግብ ራስን በመቻል፣ በቴክኖሎጂ እና በበጀት ሉዓላዊነት ምሰሶዎች ላይ መሆኑን በተግባር የተረዳንበት ወቅት ላይ እንገኛለን።
ይህን ታላቅ ዓላማ ለማሳካት ደግሞ ከተረጂነት መንፈስ ተላቅቆ ወደ ምርታማነት መሸጋገርን የሚጠይቅ አዲስ ዓይነት የኢኮኖሚ ዐርበኝነት የግድ ያስፈልገናል።
ሀገራችን “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት” በሚለው መሪ ዕሳቤ መሠረት፣ ሰብዓዊ ድጋፍን ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆ ወደ ዘላቂ አምራችነት የሚያሸጋግር የክብር መርሐ ግብር በቁርጠኝነት ወደ ተግባር አስገብታለች።
በሴፍቲኔት የሚደገፉ ዜጎች ከተረጂነት ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉ የድጋፍ እና የሥራ ዕድል የመፍጠር ሥራዎች በስፋት ተከውነዋል።
ክልሎች እና ዞኖች የራሳቸውን የምግብ መጠባበቂያ እንዲያዘጋጁ መደረጉም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ትልቅ መዋቅራዊ አቅም ፈጥሯል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ በምግብ ብቻ ሳይሆን ሀገራችን በመድኃኒት ምርትም ራሷን እንድትችል የሚደረገውን ጥረት ያጠቃልላል። ያለንን የተፈጥሮ ጸጋ እና አቅም ወደ ተጨባጭ ምርት ለመቀየር በተደረገው የላቀ ጥረት በስንዴ ልማት መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ከተመጽዋችነት እና ከልመና ታሪክ ያወጣ ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህን መልካም ተሞክሮ በሌሎች የግብርና ዘርፎችም ለመድገም በሩዝ፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ፣ በሻይ ቅጠል እና በሌሎች ሰብሎች ላይ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ ይገኛሉ።
የቀጣይ ዓመታት የመንግሥት ዋና ተግባር የሚሆነውም በሀገር ደረጃ የሚካሄደውን የሰብዓዊ ድጋፍ አሰጣጥ በማጠናከር፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች የሚመጡ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ሥራዎች ላይ ማተኮር እንደ ሆነ ተነግሯል። ይህም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂያዊ የምግብ ክምችት በሁሉም ደረጃ እንዲኖር ያስችላል።
ከዚህም አልፎ፣ “ኢትዮጵያዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያዊነት” የሚለው የትብብር ማዕቀፍ እየተጠናከረ ይሄዳል። ለዚህም በመገባደድ ላይ ባለው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሰብዓዊ ድጋፍን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለመሸፈን በትጋት እየተሠራ ነው።
ይህ ተግባር የጥገኝነትን እና የልመናን የቆየ ፖለቲካዊ ዕሳቤ ሙሉ በሙሉ የሚሽር፣ የኢትዮጵያን የአምራችነት እና የማንሰራራት ወርቃማ ዘመን የሚያበሥር ነው።
የታሪክ አውራ የሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሀብቶች፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና ለሥራ ትጉ የሆነ ሰፊ የወጣት ኃይል የታደለች ናት። ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በቁጭት እና በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ካመረትን የማይታለፍ አቀበት፣ የማይሸነፍ የድህነት ታሪክ አይኖርም።
ብሔራዊ መጠባበቂያን በማደራጀት እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በመተግበር፣ ኢትዮጵያ አምራች ሀገር ሆና በምግብ ሉዓላዊነቷ የተከበረች እንድትሆን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል።
እስካሁን ሀገራችንን ከጠላቶቿ ለመጠበቅ እና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር የደም ዋጋ ጭምር ከፍለን እንዳቆየናት ሁሉ፣ በቀጣይም ሌት ተቀን ሠርተን በማምረት ሀገራችንን ከምግብ ተረጂነት እና ከጥገኝነት ማላቀቅ የታሪካዊ ግዴታችን ማኅተም ሊሆን ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #selfrelience
2 months ago
የታላቋን ሀገር በጂኦግራፊ እስር ቤት መቆየት የማይፈቅደው የቀይ ባሕር ትውልድ
******************
ኢትዮጵያ በዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከ130 ሚሊዮን በላይ የሚሆን እጅግ ሰፊ ሕዝብ ይዛ የባሕር በር አልባ ሆና እንድትቀጥል የተፈረደባት ብቸኛ ሀገር ናት።
ይህ ታሪካዊ ኢ-ፍትሐዊነት ትውልዱ ላይ ጥልቅ ቁጭት እና የሕልውና ጥያቄ የፈጠረ እና ምላሽ የሚሻ ነው።
ከቅድመ አክሱም ዘመን ጀምሮ እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ ኢትዮጵያን እና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም።
ከ1985 ዓ.ም እስከ 'መደመር ትውልድ' መነሣት ድረስ ያለው ትውልድ ግን በታሪክ "የሥነ-ልቦና ስብራት" ዘመን ተብሎ የሚታወቅበትን የባዶነት እና የቁጭት ጊዜ አሳልፏል።
በወቅቱ ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተመሳጥረው ታሪኩን የነጠቁት ያ ትውልድ፣ የባሕር በር ማጣትን እንደማይቀየር ቋሚ ዕጣ ፈንታ በመቁጠር ሲብሰለሰል ኖሯል።
ከ12 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም የንግድ እንቅስቃሴ የሚተላለፍበትን እና በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውን ቀይ ባሕርን ዝም ብሎ ማየት ያንገፈገፈው "የመደመር ትውልድ" ዛሬ ተፈጥሯል።
የመደመር ትውልድ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነውን አምራች እና ወጣት ሕዝብ የሚወክለው የቀይ ባሕር ትውልድ ነው።
ይህ ትውልድ የባሕር በር አልባነትን እንደ ቋሚ ዕጣ ፈንታ ሳይሆን እንደ ታሪካዊ እና ሕጋዊ ስህተት ይመለከተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ በ2050 ዓ.ም የሕዝብ ብዛቷ ወደ 150 ሚሊዮን ተብሎ የምትገመተዋ ታላቅ ሀገር መተንፈሻ አልባ ሆና መቀጠል አትችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋግመው እንደገለጹት ይህን ያህል ግዙፍ ሕዝብ ያላትን ሀገር በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ውስጥ አስገብቶ ለቀጣዩ ትውልድ ማውረስ የታሪክ ባለእዳነት ነው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪክን የማረም እና የታላቋን ኢትዮጵያን ትክክለኛ የጂኦግራፊ እና የኢኮኖሚ ስፍራ የመመለስ ታሪካዊ አደራ ወድቆበታል።
ይህ ትውልድ የባሕር በር ጥያቄ የፖለቲካ ቅንጦት ሳይሆን፣ የ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሕልውና እና የዕድገት መሠረት መሆኑን በሚገባ የተገነዘበ ጠንካራ ሥነ-ልቦና አለው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪካዊ ስህተቶችን ለማረም የሚንቀሳቀሰው በጦርነት አዙሪት ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በኢኮኖሚያዊ ውህደት እና በብልህ የፓን-አፍሪካኒዝም ዲፕሎማሲ ነው።
ትውልዱ ኢትዮጵያ የምትገነባቸውን ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከቀይ ባሕር ጂኦ-ፖለቲካዊ ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር፣ ቀጣናውን የጋራ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ይተጋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redseageneration #hornofafrica #medemergeneration #seaaccess #historicjustice
******************
ኢትዮጵያ በዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከ130 ሚሊዮን በላይ የሚሆን እጅግ ሰፊ ሕዝብ ይዛ የባሕር በር አልባ ሆና እንድትቀጥል የተፈረደባት ብቸኛ ሀገር ናት።
ይህ ታሪካዊ ኢ-ፍትሐዊነት ትውልዱ ላይ ጥልቅ ቁጭት እና የሕልውና ጥያቄ የፈጠረ እና ምላሽ የሚሻ ነው።
ከቅድመ አክሱም ዘመን ጀምሮ እስከ 1985 ዓ.ም ድረስ ኢትዮጵያን እና ቀይ ባሕር ተነጣጥለው አያውቁም።
ከ1985 ዓ.ም እስከ 'መደመር ትውልድ' መነሣት ድረስ ያለው ትውልድ ግን በታሪክ "የሥነ-ልቦና ስብራት" ዘመን ተብሎ የሚታወቅበትን የባዶነት እና የቁጭት ጊዜ አሳልፏል።
በወቅቱ ሥልጣንን የተቆጣጠሩት ኃይሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ተመሳጥረው ታሪኩን የነጠቁት ያ ትውልድ፣ የባሕር በር ማጣትን እንደማይቀየር ቋሚ ዕጣ ፈንታ በመቁጠር ሲብሰለሰል ኖሯል።
ከ12 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም የንግድ እንቅስቃሴ የሚተላለፍበትን እና በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውን ቀይ ባሕርን ዝም ብሎ ማየት ያንገፈገፈው "የመደመር ትውልድ" ዛሬ ተፈጥሯል።
የመደመር ትውልድ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነውን አምራች እና ወጣት ሕዝብ የሚወክለው የቀይ ባሕር ትውልድ ነው።
ይህ ትውልድ የባሕር በር አልባነትን እንደ ቋሚ ዕጣ ፈንታ ሳይሆን እንደ ታሪካዊ እና ሕጋዊ ስህተት ይመለከተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ በ2050 ዓ.ም የሕዝብ ብዛቷ ወደ 150 ሚሊዮን ተብሎ የምትገመተዋ ታላቅ ሀገር መተንፈሻ አልባ ሆና መቀጠል አትችልም።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደጋግመው እንደገለጹት ይህን ያህል ግዙፍ ሕዝብ ያላትን ሀገር በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ውስጥ አስገብቶ ለቀጣዩ ትውልድ ማውረስ የታሪክ ባለእዳነት ነው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪክን የማረም እና የታላቋን ኢትዮጵያን ትክክለኛ የጂኦግራፊ እና የኢኮኖሚ ስፍራ የመመለስ ታሪካዊ አደራ ወድቆበታል።
ይህ ትውልድ የባሕር በር ጥያቄ የፖለቲካ ቅንጦት ሳይሆን፣ የ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ሕልውና እና የዕድገት መሠረት መሆኑን በሚገባ የተገነዘበ ጠንካራ ሥነ-ልቦና አለው።
የቀይ ባሕር ትውልድ ታሪካዊ ስህተቶችን ለማረም የሚንቀሳቀሰው በጦርነት አዙሪት ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በኢኮኖሚያዊ ውህደት እና በብልህ የፓን-አፍሪካኒዝም ዲፕሎማሲ ነው።
ትውልዱ ኢትዮጵያ የምትገነባቸውን ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ከቀይ ባሕር ጂኦ-ፖለቲካዊ ስትራቴጂ ጋር በማስተሳሰር፣ ቀጣናውን የጋራ ብልጽግና ማዕከል ለማድረግ ይተጋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redseageneration #hornofafrica #medemergeneration #seaaccess #historicjustice
2 months ago
"እስከ መቼ?"
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
2 months ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
Sponsored by
Surafel
2 months ago
"ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ... አገር ሆና እንድትቀጥል ለማየት ነው ምኞታችንና ጸሎታችን!!"
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።
በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።
በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።
"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።
መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።
በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።
ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።
እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።
አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።
ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።
አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!
ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።
እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!
ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!
ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።
ሰላም!!
በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤
2 months ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ፔዤ ዳግም ሻምፒዮን
መድፉ በክብር ተሸንፏል ! OHO BIG GABI ...
እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች መሃል ! Champions League Classic .
በኤፍሬም የማነ
#ethiopia | በእነዛ ሽርፍራፊ ሰከንዶች የፔናሊቲ ድራማ ራያ ኤዜን አዳነ ። ራያ አርሰናል አዳነ ። መድፉ ሞቶ ተነሳ ። የፔናሊቲው ድራማ ከቡዳፔስት ቀጠለ ። ከሜንዴዝ መሳት በኋላ ፔዤ ብልጫውን ወሰደ ። የመድፉ ለ120 ደቂቃ የዘለቀ የጀግንነት ተጋድሎ በBig Gabi አምስተኛዋ ወሳኝ ፔናሊቲ ላይ ተወሰነ ። መድፈኞቹ ተጨነቁ ። ዓለም በስሜት ከፍ ዝቅ አለ ። የመድፉ የድል አባት አርሴን ቬንገር ከማጋሊሽ ወሳኝ ፔናሊቲ ጋር በጭንቅ ታጥፈው ታዩ ። ንጉስ ኦነሪ በCBS ስቱዱዮ አርሰናል ከተባለ እናት ሀገሩ ጋር በስሜት ተንቆራጠጠ ። ማጋሊሽ በቀጥታ ፔናሊቲ ተመቶበት ካላዳነው የፔዤው በረኛ ሳፋኖቭ ተፈጠጠ ። ፀንቶ ለአርሰናል ድል ሲዋደቅ የዋለው ብራዚላዊ የመድፉ ግድግዳ ወሳኝ ፔናሊቲ በዛች አጋጣሚ ከቡዳፔስት ሰማይ ስር በረረች ። ፔዤ ሻምፒዮን ሆነ ። አርሰናል በጀግንነት ተዋድቆ ተሸነፈ ። እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች ተሞላች ። የፀናው የመድፉ የድል ምኞት ትጋት በመጨረሻ ከብቃት ባሻገር እንደ ሎተሪም በሆነው ፔናሊቲ ታጠፈ ። አርሰናል ሁለት ወደ ፎሪና ሰማይ በለቀቃቸው ፔናሊቲዎች አማካኝነት የህይወት ዘመን ወደር አልባው የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ህልሙን ሳያሳካ ቀረ ። መድፉ በክብር ተሸነፈ ። መድፉ በክብር ተዋድቆ ተረታ ። ከፑሽካሽ አሬና እግር ኳስ በሁለቱ ኋያላን ፍጥጫ ለ120 ደቂቃ ዘልቆ ለፔናሊቲ በተዳረገ የህይወት ገፅ ተመሠለ ። ስሜት ከፍ አለ ። ተስፋ ነገሰ ። መውጣት መውረድ መውደቅ መነሳት ፀፀት ደስታ ቁጭት እንባ ከቡዳፔስት ተፈራረቁ ። ማግኘት ማጣት መሳት ማዳን በሚሊዮኖች ላይ በእነዛ የፔናሊቲ ቅፅበቶች ተፈራረቁ ። በመጨረሻም 120 ደቂቃዎች ተሻግሮ ለፔናሊቲ የደረሰው ድራማ ፓሬዚያኑን ዳግም አነገሰ ። አርሰናል በክብር እጅ የሰጠው አሳዛኙ ተሸናፊ ሆነ ። እግር ኳስ ኳስ ይዞ መሽከርከር ብቻ እንዳልሆነ መድፉ በፀና ተደናቂ የመከላከል ቅርፁ አረጋገጠ ።
በላቀ የጨዋታ ዝግጅነት የዳበረው በታክቲክ የታጠረው ትንቅንቅ የዘመናዊው እግር ኳስ ሁለት የእግር ኳስ ቀለሞችን አሳየ ። እግር ኳስ በመድፉ የመከላከል ከፍታ ውስጥ የፔዤ የማጥቃት አቅምን አፈዘዘ ። ፓሬዚያኑ ከመድፉ ካቴና ፊት ተቆልፈው ዋሉ ። ድራማ ከቡዳፔስት ክዋክብቶቹ ከሜዳው ለድል ተዋደቁ ። ከመድፉ ግድግዳ ፊት እንደወትሮው እንደልቡ መንፈላሰስ ለፓሬዚያኑ ብርቅም ሆነ ። የመድፉ ባስ ከፓሬዚያኑ ፊት ፀንቶ ቆመ ። አርቴታ ከመጀመሪያ ቋሚ አሰላለፉ አንስቶ የመረጠው የጨዋታ ስትራቴጂው በአግባቡ ሲያዋጣው ታየ ። የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አውራ ጆዜን መሰለ ። አርሰናል የጣሊያንን አዙሪ ካቴናን አስናቀ ። ፔዤ እንደወትሮው መንቀሳቀስ ተሳነው ። ፓሬዚያኑ የአቻ ጎል ለማግኘት ያውም በፔናሊቲ 65 ደቂቃ ታተሩ ። የመድፉ የደረጀ የመከላከል ቅርፅ የፔዤ የማጥቃት ጥራትን ለአፋልጉኝ ማስታወቂያ አበቃ ። የመድፉ ካቴና ጀገነ ። የመጫወቺያ ቦታ የተነፈጉት የፔዤ ኮኮቦች እንደ ወትሮው ማንፀባረቅ ተሳናቸው ። ዘንድሮ ብቻ በቻምፒዮንስ ሊጉ 44 ጎል አዝንቦ ለቡዳፔስት ፍፃሜ የደረሰው ፔዤ ከመድፉ ግድግዳ ፊት ህይወት ከበደው ። ተጋጣሚዎቹ ላይ እንደ ልቡ በጎሎቹ የሚዘንጠው ፔዤ የአቻዋን ጎል በዴምቤሌ ፔናሊቲ አገኘ ። ፔዤ 75 በመቶ ኳስ ተቆጣጥሮ በዘለቀው ጨዋታ የመድፉ የዳበረ አጥርን መጣስም ተሳነው ። ለጨዋታው ቀልብ ገዢ ፉክክር የሚያዋጣውን የጨዋታ ቅኝት በቡድኑ ዓመቱን ሙሉ በነበረ ጥንካሬ ላይ ተመርኩዞ ተግባራዊ ያደረገው አርቴታ የፓሬዚያኑ የተለመደ ህበረ ትርዒትን አከሰመ ። ፔዤ 21 ወደ ጎል ሞክሮ 4 ብቻ ታርጌታቸውን የጠበቁ ሆኑ ። የመድፉ የፀና የLow Block ኮንክሪትን ጥሶ ማለፍ ለእነ ክቫራ ዴምቤሌ ዱዌ ብርቅ ሆነ ። ተቀይሮ የገባው ብራኮላ የተሻለ ራያን ቀረበ ። ያለ ኳስ ቁጥጥር ተጋጣሚው አርሰናል በጨዋታ መሃል ያለውን ጥንካሬ ከጨዋታው በፊትም የመሰከረው ሉዊስ ኤኔሪኬ ምርጡ ስብስቡ ከመድፉ ኮንክሪት ፊት ከመቼውም ግዜ በላይ የማጥቃት ሀሳቦች ተፋልሰው ታዩ ።
የተፈራው ክቫራ በማስኬራ ተቆለፈ ። ዱዌ ዴምቤሌ ፈዘዙ ። የፔዤ ፍሬ አልባ የኳስ ቁጥጥር ፉርሽ ሆነ ። መከላከል ጀገነ ። አርሰናል ፔዤን አሰረ ። ከሰሜን ለንደን ቡዳፔስት የደረሰው የመድፉ አውቶብስም በjose park the Bus ስታይል ሉዊስ ኤኔሪኬን አቁነጠነጠ ። የመድፉ እንደ አለት የጠነከሩ የፀኑ አጥሮች የሆኑት ማጋሊሽና ሳሊባ በራይስ እና ስኬሊ ሽፋን ለፓሬዚያኑ ፈተና ሆነ ። ጉዳት ያጋጠመው ሄንካፔ ቅያሪ ቀድሞ በጨረሰው አርቴታ እስከመጨረሻው በጀግንነት ተሰዋ ። እንደ ጨዋታ ዕቅዱ ጥሩ አጀማመሩ የመጨረሻዎቹ የጨዋታ ሂደቶች ላይ ጠንቃቃው አርቴታ በቁልፍ የጨዋታው ቅያሪ ውሳኔዎቹ ተፈተነ ። አርቴታ ከ120 ደቂቃ በኋላ ተጋድሎ በኋላ ከመጨረሻው የፔናሊቲ መቺ ምርጫ ውሳኔዎቹ የመዱፉ የክብር ሽንፈት አይረሴው ቁጭት ሆኑ ። ከፔናሊቲው ድራማ በፊት በተጨማሪው 30 ደቂቃ ዴክላን ራይስን ጨርቅ ያስጣለች ማይክ አርቴታን ያሳበደች የሜንዴዝ ማዱኬ ፋወል ከVAR የዳኛው ዕይታ መታለፍ ጋር ሌላው አነጋጋሪም ነበር ። ይህ የመድፉ አርሰናል ወርቃማው የውድድር ዓመት መልክ ነው ። ይህ የፓሬዚያኑ እንደ ልብ ከኳስ ጋር የሚፈነጩ ክዋክብቶችን ከጎሉ ፊት ቆልፎ የዋለው የመድፉ ካቴና ታላቁ ተጋድሎ ነው ። ይህ አርሰናል ወደ ፎሪ እና ወደ ሰማይ በላካቸው ሁለት ፔናሊቲዎች ፀፀት ታጅቦ በጀግንነት እስከ መጨረሻው ተዋድቆ እጅ የሰጠበት የመድፉ የህይወት ከፍታ ጉዞ አሳዛኙ ሌላኛው የቻምፒየንስ ሊግ ምሽት የክብር ገፁ ነው ። ፔዤ ሻምፒዮን ። ናስር አልከሊፋ የፔዤው ቢሊየነር አባት ሉዊስ ኤኔሪኬ ቀምሞ ባወቀረው ቡድናቸው እንደፎከሩት ሁለተኛውን የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ በተከታታይ ድል ነስተዋል ። የፈረንሳይ ሊግም ምስጋና ለፓሬዚያኑ እያለ በድጋሜ በትልቁ የክዋክብቶች መድረክ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ላይ ዳግም ነግሷል ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
መድፉ በክብር ተሸንፏል ! OHO BIG GABI ...
እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች መሃል ! Champions League Classic .
በኤፍሬም የማነ
#ethiopia | በእነዛ ሽርፍራፊ ሰከንዶች የፔናሊቲ ድራማ ራያ ኤዜን አዳነ ። ራያ አርሰናል አዳነ ። መድፉ ሞቶ ተነሳ ። የፔናሊቲው ድራማ ከቡዳፔስት ቀጠለ ። ከሜንዴዝ መሳት በኋላ ፔዤ ብልጫውን ወሰደ ። የመድፉ ለ120 ደቂቃ የዘለቀ የጀግንነት ተጋድሎ በBig Gabi አምስተኛዋ ወሳኝ ፔናሊቲ ላይ ተወሰነ ። መድፈኞቹ ተጨነቁ ። ዓለም በስሜት ከፍ ዝቅ አለ ። የመድፉ የድል አባት አርሴን ቬንገር ከማጋሊሽ ወሳኝ ፔናሊቲ ጋር በጭንቅ ታጥፈው ታዩ ። ንጉስ ኦነሪ በCBS ስቱዱዮ አርሰናል ከተባለ እናት ሀገሩ ጋር በስሜት ተንቆራጠጠ ። ማጋሊሽ በቀጥታ ፔናሊቲ ተመቶበት ካላዳነው የፔዤው በረኛ ሳፋኖቭ ተፈጠጠ ። ፀንቶ ለአርሰናል ድል ሲዋደቅ የዋለው ብራዚላዊ የመድፉ ግድግዳ ወሳኝ ፔናሊቲ በዛች አጋጣሚ ከቡዳፔስት ሰማይ ስር በረረች ። ፔዤ ሻምፒዮን ሆነ ። አርሰናል በጀግንነት ተዋድቆ ተሸነፈ ። እግር ኳስ ከቡዳፔስት በስሜት ሀዘንና ደስታ ቅፅበታዊ ልውውጦች ተሞላች ። የፀናው የመድፉ የድል ምኞት ትጋት በመጨረሻ ከብቃት ባሻገር እንደ ሎተሪም በሆነው ፔናሊቲ ታጠፈ ። አርሰናል ሁለት ወደ ፎሪና ሰማይ በለቀቃቸው ፔናሊቲዎች አማካኝነት የህይወት ዘመን ወደር አልባው የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ህልሙን ሳያሳካ ቀረ ። መድፉ በክብር ተሸነፈ ። መድፉ በክብር ተዋድቆ ተረታ ። ከፑሽካሽ አሬና እግር ኳስ በሁለቱ ኋያላን ፍጥጫ ለ120 ደቂቃ ዘልቆ ለፔናሊቲ በተዳረገ የህይወት ገፅ ተመሠለ ። ስሜት ከፍ አለ ። ተስፋ ነገሰ ። መውጣት መውረድ መውደቅ መነሳት ፀፀት ደስታ ቁጭት እንባ ከቡዳፔስት ተፈራረቁ ። ማግኘት ማጣት መሳት ማዳን በሚሊዮኖች ላይ በእነዛ የፔናሊቲ ቅፅበቶች ተፈራረቁ ። በመጨረሻም 120 ደቂቃዎች ተሻግሮ ለፔናሊቲ የደረሰው ድራማ ፓሬዚያኑን ዳግም አነገሰ ። አርሰናል በክብር እጅ የሰጠው አሳዛኙ ተሸናፊ ሆነ ። እግር ኳስ ኳስ ይዞ መሽከርከር ብቻ እንዳልሆነ መድፉ በፀና ተደናቂ የመከላከል ቅርፁ አረጋገጠ ።
በላቀ የጨዋታ ዝግጅነት የዳበረው በታክቲክ የታጠረው ትንቅንቅ የዘመናዊው እግር ኳስ ሁለት የእግር ኳስ ቀለሞችን አሳየ ። እግር ኳስ በመድፉ የመከላከል ከፍታ ውስጥ የፔዤ የማጥቃት አቅምን አፈዘዘ ። ፓሬዚያኑ ከመድፉ ካቴና ፊት ተቆልፈው ዋሉ ። ድራማ ከቡዳፔስት ክዋክብቶቹ ከሜዳው ለድል ተዋደቁ ። ከመድፉ ግድግዳ ፊት እንደወትሮው እንደልቡ መንፈላሰስ ለፓሬዚያኑ ብርቅም ሆነ ። የመድፉ ባስ ከፓሬዚያኑ ፊት ፀንቶ ቆመ ። አርቴታ ከመጀመሪያ ቋሚ አሰላለፉ አንስቶ የመረጠው የጨዋታ ስትራቴጂው በአግባቡ ሲያዋጣው ታየ ። የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አውራ ጆዜን መሰለ ። አርሰናል የጣሊያንን አዙሪ ካቴናን አስናቀ ። ፔዤ እንደወትሮው መንቀሳቀስ ተሳነው ። ፓሬዚያኑ የአቻ ጎል ለማግኘት ያውም በፔናሊቲ 65 ደቂቃ ታተሩ ። የመድፉ የደረጀ የመከላከል ቅርፅ የፔዤ የማጥቃት ጥራትን ለአፋልጉኝ ማስታወቂያ አበቃ ። የመድፉ ካቴና ጀገነ ። የመጫወቺያ ቦታ የተነፈጉት የፔዤ ኮኮቦች እንደ ወትሮው ማንፀባረቅ ተሳናቸው ። ዘንድሮ ብቻ በቻምፒዮንስ ሊጉ 44 ጎል አዝንቦ ለቡዳፔስት ፍፃሜ የደረሰው ፔዤ ከመድፉ ግድግዳ ፊት ህይወት ከበደው ። ተጋጣሚዎቹ ላይ እንደ ልቡ በጎሎቹ የሚዘንጠው ፔዤ የአቻዋን ጎል በዴምቤሌ ፔናሊቲ አገኘ ። ፔዤ 75 በመቶ ኳስ ተቆጣጥሮ በዘለቀው ጨዋታ የመድፉ የዳበረ አጥርን መጣስም ተሳነው ። ለጨዋታው ቀልብ ገዢ ፉክክር የሚያዋጣውን የጨዋታ ቅኝት በቡድኑ ዓመቱን ሙሉ በነበረ ጥንካሬ ላይ ተመርኩዞ ተግባራዊ ያደረገው አርቴታ የፓሬዚያኑ የተለመደ ህበረ ትርዒትን አከሰመ ። ፔዤ 21 ወደ ጎል ሞክሮ 4 ብቻ ታርጌታቸውን የጠበቁ ሆኑ ። የመድፉ የፀና የLow Block ኮንክሪትን ጥሶ ማለፍ ለእነ ክቫራ ዴምቤሌ ዱዌ ብርቅ ሆነ ። ተቀይሮ የገባው ብራኮላ የተሻለ ራያን ቀረበ ። ያለ ኳስ ቁጥጥር ተጋጣሚው አርሰናል በጨዋታ መሃል ያለውን ጥንካሬ ከጨዋታው በፊትም የመሰከረው ሉዊስ ኤኔሪኬ ምርጡ ስብስቡ ከመድፉ ኮንክሪት ፊት ከመቼውም ግዜ በላይ የማጥቃት ሀሳቦች ተፋልሰው ታዩ ።
የተፈራው ክቫራ በማስኬራ ተቆለፈ ። ዱዌ ዴምቤሌ ፈዘዙ ። የፔዤ ፍሬ አልባ የኳስ ቁጥጥር ፉርሽ ሆነ ። መከላከል ጀገነ ። አርሰናል ፔዤን አሰረ ። ከሰሜን ለንደን ቡዳፔስት የደረሰው የመድፉ አውቶብስም በjose park the Bus ስታይል ሉዊስ ኤኔሪኬን አቁነጠነጠ ። የመድፉ እንደ አለት የጠነከሩ የፀኑ አጥሮች የሆኑት ማጋሊሽና ሳሊባ በራይስ እና ስኬሊ ሽፋን ለፓሬዚያኑ ፈተና ሆነ ። ጉዳት ያጋጠመው ሄንካፔ ቅያሪ ቀድሞ በጨረሰው አርቴታ እስከመጨረሻው በጀግንነት ተሰዋ ። እንደ ጨዋታ ዕቅዱ ጥሩ አጀማመሩ የመጨረሻዎቹ የጨዋታ ሂደቶች ላይ ጠንቃቃው አርቴታ በቁልፍ የጨዋታው ቅያሪ ውሳኔዎቹ ተፈተነ ። አርቴታ ከ120 ደቂቃ በኋላ ተጋድሎ በኋላ ከመጨረሻው የፔናሊቲ መቺ ምርጫ ውሳኔዎቹ የመዱፉ የክብር ሽንፈት አይረሴው ቁጭት ሆኑ ። ከፔናሊቲው ድራማ በፊት በተጨማሪው 30 ደቂቃ ዴክላን ራይስን ጨርቅ ያስጣለች ማይክ አርቴታን ያሳበደች የሜንዴዝ ማዱኬ ፋወል ከVAR የዳኛው ዕይታ መታለፍ ጋር ሌላው አነጋጋሪም ነበር ። ይህ የመድፉ አርሰናል ወርቃማው የውድድር ዓመት መልክ ነው ። ይህ የፓሬዚያኑ እንደ ልብ ከኳስ ጋር የሚፈነጩ ክዋክብቶችን ከጎሉ ፊት ቆልፎ የዋለው የመድፉ ካቴና ታላቁ ተጋድሎ ነው ። ይህ አርሰናል ወደ ፎሪ እና ወደ ሰማይ በላካቸው ሁለት ፔናሊቲዎች ፀፀት ታጅቦ በጀግንነት እስከ መጨረሻው ተዋድቆ እጅ የሰጠበት የመድፉ የህይወት ከፍታ ጉዞ አሳዛኙ ሌላኛው የቻምፒየንስ ሊግ ምሽት የክብር ገፁ ነው ። ፔዤ ሻምፒዮን ። ናስር አልከሊፋ የፔዤው ቢሊየነር አባት ሉዊስ ኤኔሪኬ ቀምሞ ባወቀረው ቡድናቸው እንደፎከሩት ሁለተኛውን የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ በተከታታይ ድል ነስተዋል ። የፈረንሳይ ሊግም ምስጋና ለፓሬዚያኑ እያለ በድጋሜ በትልቁ የክዋክብቶች መድረክ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ላይ ዳግም ነግሷል ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ዛሬ ምሽት በተካሄደው የምዕራቡ ዞን የፍጻሜ ማጣሪያ ሰባተኛ እና ወሳኝ ጨዋታ.. ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ ኦክላሆማ ሲቲ ታንደርን 111 ለ 103 በሆነ ውጤት በማሸነፍ አጓጊውን ተከታታይ ፍልሚያ በድል አጠናቋል። ይህ የሁለቱ ወጣት እና ሀያል የቅርጫት ኳስ ቡድኖች ግጥሚያ፣ የብሔራዊ የቅርጫት ኳስ ማህበሩን የወደፊት እጣ ፈንታ ማን ይቆጣጠራል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ድንቅ መድረክ ነበር። አሸናፊው ስፐርስ በመጪው ረቡዕ ከኒው ዮርክ ኒክስ ጋር ታላቁን የፍጻሜ ጨዋታ ይጀምራል።
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የዲጂታል ዲፕሎማሲ አዲስ ምዕራፍ፦ የኢትዮጵያ ገጽታ በዓለም አደባባይ
***************
ዓለም ከተለመደው የሚዲያ እና የሕዝብ ግንኙነት አሠራር ወጥታ፣ ፈጣን ወደሆነው የዲጂታል ሚዲያ ዓለም ተሻግራለች።
በዚህ ዘመን ሀገርን ለማስተዋወቅ ዲፕሎማቶችን ማሰማራት እና መደበኛ መገናኛ ሚዲያን ‘ሎቢ’ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም።
ዘመኑን ለመዋጀት በደቂቃዎች ውስጥ ሚሊዮኖችን የሚደርሰውን የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጭ መጠቀም ብልህነት ነው።
በርካታ ሀገራት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሰዎች ዓይን በሚያርፍባቸው ታዋቂ መድረኮች ላይ ማስታወቂያዎችን ይገዛሉ።
ለዚህም ለታዋቂው የአርሴናል እግር ኳስ ክለብ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በመክፈል፣ "ሩዋንዳን ይጎብኙ" (Visit Rwanda) በሚል ራሷን እያስተዋወቀች ያለችው ሩዋንዳ ተጠቃሽ ምሳሌ ናት።
የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ገፅታ ለዓመታት በምዕራባውያን ሚዲያዎች በተዛባ ትርክት ስር ወድቆ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህ ኢትዮጵያን የችግር እና የጉስቁልና ተምሳሌት ብቻ አድርጎ የሳለው ትርክት፣ ከሀገራቸው የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ሁልጊዜም በቁጭት የሚያነሱት ጉዳይ ነው።
በአሁኑ ወቅት ግን ሀገራችን በጀመረችው አዲስ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ስትራቴጂ፣ እውነተኛ እና ብሩህ ገፅታዋን ለዓለም ማሳየት ጀምራለች።
ከተለመዱት የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻዎች በመውጣት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮች ባሏቸው ዓለም አቀፍ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አማካኝነት የራሷን ታሪክ በራሷ አንደበት እየተረከች ትገኛለች።
በቅርቡ ታዋቂው አሜሪካዊ ዩቲዩበር ‘አይሾውስፒድ’ በአዲስ አበባ ባደረገው እና አህጉራዊ የተመልካች ክብረ ወሰንን በሰበረው የቀጥታ ሥርጭት የከተማዋን ዘመናዊነት አስተዋውቋል።
ይህ የ‘አይሾውስፒድ’ የቀጥታ ሥርጭት በ20 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 10 ሚሊዮን እይታዎችን ከማስመዝገቡም በላይ፣ ሥርጭቱ በነበረበት ወቅት ከ260 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን አግኝቷል።
በተመሳሳይ በቲክቶክ የዜና አቅራቢነቱ የሚታወቀው ዲለን ፔጅ (ኒውስ ዳዲ) እና የጉዞ ቪሎገሩ ድሩ ቢንስኪ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎችን በመጎብኘት፣ ሀገራችን ያላትን ጥንታዊ የታሪክ በረከት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለዓለም ሕዝብ አጋርተዋል።
ከዚህም ባሻገር ታዋቂው ጋናዊ ዩቲዩበር ዎዴ ማያ በሁለት የተለያዩ የጉብኝት መርሐ ግብሮቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማሳየት በግድቡ ላይ የሚነዛውን አሉታዊ ትርክት ሰብሯል።
ዎዴ ማያ ከሕዳሴ ግድብ በተጨማሪ እስከ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የነጻነት ችቦ የለኮሰችበትን ታሪካዊ ምድር ጎብኝቷል።
በርካታ ታላላቅ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ለዓለም በማሳየት የምዕራባውያንን አሉታዊ ትርክት ከማክሸፉም በላይ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ትብብርን አጉልቶ አሳይቷል።
ይህ የትርክት ለውጥ በቅርቡ አዲስ አበባ ባስተናገደችው የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይበልጥ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝ ተደርጓል።
ከ321 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏቸው 61 የአፍሪካ ይዘት ፈጣሪዎች በተሳተፉበት በዚህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲጂታል ትርክት ማዕከል መሆኗ ተረጋግጧል።
እነዚህ ስኬቶች እውን ሊሆኑ የቻሉት ደግሞ እንደ አዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ባሉ ሰፊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች አማካኝነት ነው።
ውበትን እየተላበሰች እና እየዘመነች ያለችው አዲስ አበባ ለዲጂታል ቀረጻ ምቹና ማራኪ ከመሆኗም በላይ፣ የአፍሪካ መዲናነቷን በተግባር እያረጋገጠች መምጣቷ የእነዚህን ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቀልብ ሊገዛ ችሏል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #digitaldiplomacy #visitethiopia #nationbranding #wodemaya #africa #addisababa
***************
ዓለም ከተለመደው የሚዲያ እና የሕዝብ ግንኙነት አሠራር ወጥታ፣ ፈጣን ወደሆነው የዲጂታል ሚዲያ ዓለም ተሻግራለች።
በዚህ ዘመን ሀገርን ለማስተዋወቅ ዲፕሎማቶችን ማሰማራት እና መደበኛ መገናኛ ሚዲያን ‘ሎቢ’ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም።
ዘመኑን ለመዋጀት በደቂቃዎች ውስጥ ሚሊዮኖችን የሚደርሰውን የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጭ መጠቀም ብልህነት ነው።
በርካታ ሀገራት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሰዎች ዓይን በሚያርፍባቸው ታዋቂ መድረኮች ላይ ማስታወቂያዎችን ይገዛሉ።
ለዚህም ለታዋቂው የአርሴናል እግር ኳስ ክለብ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በመክፈል፣ "ሩዋንዳን ይጎብኙ" (Visit Rwanda) በሚል ራሷን እያስተዋወቀች ያለችው ሩዋንዳ ተጠቃሽ ምሳሌ ናት።
የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ገፅታ ለዓመታት በምዕራባውያን ሚዲያዎች በተዛባ ትርክት ስር ወድቆ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህ ኢትዮጵያን የችግር እና የጉስቁልና ተምሳሌት ብቻ አድርጎ የሳለው ትርክት፣ ከሀገራቸው የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ሁልጊዜም በቁጭት የሚያነሱት ጉዳይ ነው።
በአሁኑ ወቅት ግን ሀገራችን በጀመረችው አዲስ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ስትራቴጂ፣ እውነተኛ እና ብሩህ ገፅታዋን ለዓለም ማሳየት ጀምራለች።
ከተለመዱት የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻዎች በመውጣት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮች ባሏቸው ዓለም አቀፍ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አማካኝነት የራሷን ታሪክ በራሷ አንደበት እየተረከች ትገኛለች።
በቅርቡ ታዋቂው አሜሪካዊ ዩቲዩበር ‘አይሾውስፒድ’ በአዲስ አበባ ባደረገው እና አህጉራዊ የተመልካች ክብረ ወሰንን በሰበረው የቀጥታ ሥርጭት የከተማዋን ዘመናዊነት አስተዋውቋል።
ይህ የ‘አይሾውስፒድ’ የቀጥታ ሥርጭት በ20 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 10 ሚሊዮን እይታዎችን ከማስመዝገቡም በላይ፣ ሥርጭቱ በነበረበት ወቅት ከ260 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን አግኝቷል።
በተመሳሳይ በቲክቶክ የዜና አቅራቢነቱ የሚታወቀው ዲለን ፔጅ (ኒውስ ዳዲ) እና የጉዞ ቪሎገሩ ድሩ ቢንስኪ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎችን በመጎብኘት፣ ሀገራችን ያላትን ጥንታዊ የታሪክ በረከት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለዓለም ሕዝብ አጋርተዋል።
ከዚህም ባሻገር ታዋቂው ጋናዊ ዩቲዩበር ዎዴ ማያ በሁለት የተለያዩ የጉብኝት መርሐ ግብሮቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማሳየት በግድቡ ላይ የሚነዛውን አሉታዊ ትርክት ሰብሯል።
ዎዴ ማያ ከሕዳሴ ግድብ በተጨማሪ እስከ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የነጻነት ችቦ የለኮሰችበትን ታሪካዊ ምድር ጎብኝቷል።
በርካታ ታላላቅ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ለዓለም በማሳየት የምዕራባውያንን አሉታዊ ትርክት ከማክሸፉም በላይ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ትብብርን አጉልቶ አሳይቷል።
ይህ የትርክት ለውጥ በቅርቡ አዲስ አበባ ባስተናገደችው የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይበልጥ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝ ተደርጓል።
ከ321 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏቸው 61 የአፍሪካ ይዘት ፈጣሪዎች በተሳተፉበት በዚህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲጂታል ትርክት ማዕከል መሆኗ ተረጋግጧል።
እነዚህ ስኬቶች እውን ሊሆኑ የቻሉት ደግሞ እንደ አዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ባሉ ሰፊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች አማካኝነት ነው።
ውበትን እየተላበሰች እና እየዘመነች ያለችው አዲስ አበባ ለዲጂታል ቀረጻ ምቹና ማራኪ ከመሆኗም በላይ፣ የአፍሪካ መዲናነቷን በተግባር እያረጋገጠች መምጣቷ የእነዚህን ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቀልብ ሊገዛ ችሏል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #digitaldiplomacy #visitethiopia #nationbranding #wodemaya #africa #addisababa
Comments