3 days ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጅቡቲ በባቢል መንደብ ባህረ-ሰላጤ በሚያልፉ መርከቦች ላይ በአንድ ወገን ውሳኔ ብቻ ቀረጥ ወይም የመተላለፊያ ክፍያ ለመጣል የሚደረገውን ማንኛውንም ሙከራ አጥብቃ እንደምትቃወም አስታወቀች። መንግስት ይህ እርምጃ ዓለም አቀፍ ህግን የሚጥስ እና ከዓለም ቁልፍ የባህር ላይ የንግድ መስመሮች አንዱ የሆነውን መስመር አደጋ ላይ የሚጥል ነው ሲል አስጠንቅቋል።
የጅቡቲ መንግስት ረቡዕ ምሽት ባወጣው መግለጫ፣ በአፍሪካ ቀንድ እና በየመን ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ መካከል በሚገኘው በዚህ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ በማናለኝነት ክፍያ ለመጫን የሚደረገውን ጥረት አውግዟል። ይህ መግለጫ የወጣው፣ የየመን ሁቲ እንቅስቃሴ በቀይ ባህር፣ በአደን ባህረ-ሰላጤ እና በህንድ ውቅያኖስ መካከል በሚያገናኘው በዚህ ወሳኝ የንግድ እና የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ላይ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የመተላለፊያ ክፍያ ለማስከፈል እያሰበ መሆኑን የሚያሳዩ ሪፖርቶች መውጣታቸውን ተከትሎ ነው።
ጅቡቲ መርከቦች በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት እና ባህረ-ሰላጤዎችን በሚያስተዳድረው ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ህግ ሙሉ በሙሉ እንደምትገዛ አረጋግጣለች። በመግለጫዋም "ባቢል መንደብ በአፍሪካ እና በእስያ የባህር ዳርቻዎች መካከል የሚጋራ የዓለም አቀፍ ፍላጎት ማዕከል ነው። ከአንድ የባህር ዳርቻ ብቻ ተነስቶ በመርከቦች ላይ የክፍያ ወይም የቀረጥ ስርዓት ለመጫን የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ዓለም አቀፍ ህግን የሚጻረር፣ አዋሳኝ ሀገራትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ እና ለዓለም አቀፍ ንግድ እና የኃይል አቅርቦት ወሳኝ የሆኑትን የባህር መስመሮች ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው" ስትል አብራርታለች።
በቀጠናው ያለውን ነባራዊ እና ተሰባሪ ሰላም ይበልጥ ሊያሻክር የሚችለውን ይህንን ድርጊት ለመመከት ሀገሪቱ ሉዓላዊ መብቷን ለማስከበር፣ የባህር ላይ ጉዞ ነጻነትን ለመጠበቅ እና በቀይ ባህር ያለውን መረጋጋት ለማስቀጠል ዲፕሎማሲያዊ፣ ህጋዊ እና የጸጥታ እርምጃዎችን—በግሏም ሆነ ከቀጣናው እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመቀናጀት—የመውሰድ መብቷ የተጠበቀ መሆኑን አስታውቃለች። በተጨማሪም፣ ባህረ-ሰላጤው የጥቂቶች የግል ፍላጎት ማራመጃ መሳሪያ ከመሆን ይልቅ፣ ዓለም አቀፍ ህግን የተከተለ፣ ክፍት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ኮሪደር ሆኖ እንዲቀጥል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ተጠቃሚ ሀገራት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርባለች።
ይህ የባቢል መንደብ ባህረ-ሰላጤ ውጥረት በተለይ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ የደህንነት እና የኢኮኖሚ ትርጉም አለው። የባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግዷ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የምትመካው በጅቡቲ ወደቦች እና በቀይ ባህር ኮሪደር ያልተቆራረጠ የጭነት ፍሰት ላይ በመሆኑ፣ ይህ በቀጠናው የተደቀነው አዲስ ስጋት ሀገሪቱን በቀጥታ የሚመለከታት ጉዳይ መሆኑን ባለሙያዎች ያስገነዝባሉ።
የጅቡቲ መንግስት ረቡዕ ምሽት ባወጣው መግለጫ፣ በአፍሪካ ቀንድ እና በየመን ምዕራባዊ የባህር ዳርቻ መካከል በሚገኘው በዚህ ስትራቴጂካዊ የውሃ መስመር ላይ በማናለኝነት ክፍያ ለመጫን የሚደረገውን ጥረት አውግዟል። ይህ መግለጫ የወጣው፣ የየመን ሁቲ እንቅስቃሴ በቀይ ባህር፣ በአደን ባህረ-ሰላጤ እና በህንድ ውቅያኖስ መካከል በሚያገናኘው በዚህ ወሳኝ የንግድ እና የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ላይ በሚያልፉ መርከቦች ላይ የመተላለፊያ ክፍያ ለማስከፈል እያሰበ መሆኑን የሚያሳዩ ሪፖርቶች መውጣታቸውን ተከትሎ ነው።
ጅቡቲ መርከቦች በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት እና ባህረ-ሰላጤዎችን በሚያስተዳድረው ዓለም አቀፍ የባህር ላይ ህግ ሙሉ በሙሉ እንደምትገዛ አረጋግጣለች። በመግለጫዋም "ባቢል መንደብ በአፍሪካ እና በእስያ የባህር ዳርቻዎች መካከል የሚጋራ የዓለም አቀፍ ፍላጎት ማዕከል ነው። ከአንድ የባህር ዳርቻ ብቻ ተነስቶ በመርከቦች ላይ የክፍያ ወይም የቀረጥ ስርዓት ለመጫን የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ ዓለም አቀፍ ህግን የሚጻረር፣ አዋሳኝ ሀገራትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ እና ለዓለም አቀፍ ንግድ እና የኃይል አቅርቦት ወሳኝ የሆኑትን የባህር መስመሮች ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ነው" ስትል አብራርታለች።
በቀጠናው ያለውን ነባራዊ እና ተሰባሪ ሰላም ይበልጥ ሊያሻክር የሚችለውን ይህንን ድርጊት ለመመከት ሀገሪቱ ሉዓላዊ መብቷን ለማስከበር፣ የባህር ላይ ጉዞ ነጻነትን ለመጠበቅ እና በቀይ ባህር ያለውን መረጋጋት ለማስቀጠል ዲፕሎማሲያዊ፣ ህጋዊ እና የጸጥታ እርምጃዎችን—በግሏም ሆነ ከቀጣናው እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመቀናጀት—የመውሰድ መብቷ የተጠበቀ መሆኑን አስታውቃለች። በተጨማሪም፣ ባህረ-ሰላጤው የጥቂቶች የግል ፍላጎት ማራመጃ መሳሪያ ከመሆን ይልቅ፣ ዓለም አቀፍ ህግን የተከተለ፣ ክፍት እና ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ኮሪደር ሆኖ እንዲቀጥል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ተጠቃሚ ሀገራት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርባለች።
ይህ የባቢል መንደብ ባህረ-ሰላጤ ውጥረት በተለይ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ የደህንነት እና የኢኮኖሚ ትርጉም አለው። የባህር በር አልባዋ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ንግዷ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የምትመካው በጅቡቲ ወደቦች እና በቀይ ባህር ኮሪደር ያልተቆራረጠ የጭነት ፍሰት ላይ በመሆኑ፣ ይህ በቀጠናው የተደቀነው አዲስ ስጋት ሀገሪቱን በቀጥታ የሚመለከታት ጉዳይ መሆኑን ባለሙያዎች ያስገነዝባሉ።
9 days ago
የኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ የባህር በር
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሮ ጊዜ ነገስታት የተለያዩ ሰዎችን ወደ ማህበረሰቡ እየላኩ "ሕዝቡ ምን አለ" በማለት ይጠይቁ እንደነበር ይነገራል፡፡
ይህ ዛሬም አለ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለ ህይወት እንደሚገባው የሚያምነው ይህ መንግሥት ሕዝቡ ምን ይላል ሲል ይጠይቃል፤ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስም ይሰራል፡፡
ሕዝቡ ወጣት ልጆቹ ለስደትና እንግልት እንዳይዳረጉ፤ ይልቁንም በሀገራቸው ላይ የስራ እድልና በቂ ገቢ ማግኘት እንዳለባቸው ያምናል፡፡
ኢትዮጵያ እንድታድግና በቀደመው የሚያኮራ ማንነቷ እንድትታወቅ፤ እንደቀድሞው ሁሉ ለሌሎች ተምሳሌትነቷ እንዲቀጥል የሕዝብ ፍላጎት ነው፡፡
ሕዝብ ከዓለም ወደ ኋለ መቅረት ምርጫው አይደለም፤ የኢንተርኔት አገልግሎትን በበቂ ሁኔታ መጠቀም እንዲችል ዘመናዊና የሰለጠነ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖረው ይሻል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለልጆቹ ድህነትን ማውረስ አይፈልግም፤ አንዳንድ ሀገራት እንደሚያደርጉት ዛሬ የተገባን ኑሮ ከመኖር አልፎ ለነገ ትውልድ የሚተርፍ ሀብት ማስቀመጥ ምርጫው ነው፡፡
ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ቀጥተኛ የንግድ ግንኙነት ኖሯት ለሌሎች ሀገራት የሚሆኑ ምርቶችን መላክ እንድትችል፣ የውጪ ንግዷ አድጎ ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም እንዲኖረን የሕዝባችን ጽኑ ፍላጎት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ተጽእኖ ፈጣሪነቷ እንዲጨምርና የዲፕሎማሲ አቅሟ እንዲያድግ እንዲሁም በራሷ ጉዳይ ላይ የሌሎች ጣልቃ ገብነት የሌለበት ውሳኔ ሰጪነት አቅም እንዲኖራት ይፈልጋል፡፡
ጠንካራ መሰረት ያላት የደህንነት አቅሟን የገነባች ሀገር ይፈልጋል፡፡
ከምንም በላይ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ያለአግባብ ለተፈጸመበት ታሪካዊ በደል የማይጓደል ፍትህን ይሻል፡፡
ይህን ጥያቄውን ሊያስመልስለት የሚችለውን ያለግባብ በሆነና ህጋዊ መሰረት በሌለው መንገድ የተነጠቀውን፣ በታሪክና ህግ የሚደገፈውን የባሕር በር የባለቤትነት መብቱን ከማስመለስ ወደ ኋላ አይልም፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ እየጠየቀች ያለችውን የባህር በር ጥያቄ መመለስ የኢትዮጵያውያንን የታሪክ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የህዝብ ስነ ልቦናን ለመጠበቅ ሚናው ትልቅ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት "የባሕር በር አልባነት፤ ገመና አልባነት ነው፡፡"
የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ከመደበቅ ልምምድ ወጥቶ መፍትሄ ለመስጠት በሚሄድባቸው መንገዶች ሁሉ የባሕር በር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል አማራጭ አልባ መፍትሄ ነው፡፡
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሮ ጊዜ ነገስታት የተለያዩ ሰዎችን ወደ ማህበረሰቡ እየላኩ "ሕዝቡ ምን አለ" በማለት ይጠይቁ እንደነበር ይነገራል፡፡
ይህ ዛሬም አለ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተሻለ ህይወት እንደሚገባው የሚያምነው ይህ መንግሥት ሕዝቡ ምን ይላል ሲል ይጠይቃል፤ የሕዝብን ጥያቄ ለመመለስም ይሰራል፡፡
ሕዝቡ ወጣት ልጆቹ ለስደትና እንግልት እንዳይዳረጉ፤ ይልቁንም በሀገራቸው ላይ የስራ እድልና በቂ ገቢ ማግኘት እንዳለባቸው ያምናል፡፡
ኢትዮጵያ እንድታድግና በቀደመው የሚያኮራ ማንነቷ እንድትታወቅ፤ እንደቀድሞው ሁሉ ለሌሎች ተምሳሌትነቷ እንዲቀጥል የሕዝብ ፍላጎት ነው፡፡
ሕዝብ ከዓለም ወደ ኋለ መቅረት ምርጫው አይደለም፤ የኢንተርኔት አገልግሎትን በበቂ ሁኔታ መጠቀም እንዲችል ዘመናዊና የሰለጠነ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖረው ይሻል፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለልጆቹ ድህነትን ማውረስ አይፈልግም፤ አንዳንድ ሀገራት እንደሚያደርጉት ዛሬ የተገባን ኑሮ ከመኖር አልፎ ለነገ ትውልድ የሚተርፍ ሀብት ማስቀመጥ ምርጫው ነው፡፡
ኢትዮጵያ በምግብ ራስን ከመቻል አልፎ ቀጥተኛ የንግድ ግንኙነት ኖሯት ለሌሎች ሀገራት የሚሆኑ ምርቶችን መላክ እንድትችል፣ የውጪ ንግዷ አድጎ ጠንካራ የኢኮኖሚ አቅም እንዲኖረን የሕዝባችን ጽኑ ፍላጎት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ተጽእኖ ፈጣሪነቷ እንዲጨምርና የዲፕሎማሲ አቅሟ እንዲያድግ እንዲሁም በራሷ ጉዳይ ላይ የሌሎች ጣልቃ ገብነት የሌለበት ውሳኔ ሰጪነት አቅም እንዲኖራት ይፈልጋል፡፡
ጠንካራ መሰረት ያላት የደህንነት አቅሟን የገነባች ሀገር ይፈልጋል፡፡
ከምንም በላይ ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ያለአግባብ ለተፈጸመበት ታሪካዊ በደል የማይጓደል ፍትህን ይሻል፡፡
ይህን ጥያቄውን ሊያስመልስለት የሚችለውን ያለግባብ በሆነና ህጋዊ መሰረት በሌለው መንገድ የተነጠቀውን፣ በታሪክና ህግ የሚደገፈውን የባሕር በር የባለቤትነት መብቱን ከማስመለስ ወደ ኋላ አይልም፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬ እየጠየቀች ያለችውን የባህር በር ጥያቄ መመለስ የኢትዮጵያውያንን የታሪክ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥያቄ ከመፍታት ባሻገር የህዝብ ስነ ልቦናን ለመጠበቅ ሚናው ትልቅ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት "የባሕር በር አልባነት፤ ገመና አልባነት ነው፡፡"
የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግሩን ከመደበቅ ልምምድ ወጥቶ መፍትሄ ለመስጠት በሚሄድባቸው መንገዶች ሁሉ የባሕር በር የሁሉንም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ለመመለስ የሚያስችል አማራጭ አልባ መፍትሄ ነው፡፡
በቤተልሔም ግርማ
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኋይት ሀውስ ማክሰኞ ዕለት ሊገናኙ ነው። ይህ ስብሰባ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ሁለተኛውን የሥልጣን ዘመናቸውን ከያዙ ወዲህ ለስምንተኛ ጊዜ የሚያደርጉት ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ ግን የመጀመሪያቸው ነው። ሁለቱ መሪዎች ቀደም ሲል በየአስር ሳምንቱ ልዩነት ይገናኙ እንደነበር ሲታወስ፣ የአሁኑ የቆይታ ጊዜ በሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ የልዩነት ስፋት የሚያሳይ ነው ተብሏል። ኔታንያሁ የኋይት ሀውስ ግብዣን ለማግኘት ለሳምንታት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፣ ጉብኝታቸውን በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩት የሪፐብሊካን ሴናተር ሊንድሴይ ግራሃም የቀብር ሥነ-ሥርዓት ጋር አጋጥመውታል። ሁለቱ መሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት እ.ኤ.አ. በየካቲት ወር ሲሆን፣ ከዚያ ስብሰባ ከሁለት ሳምንታት በኋላ በኢራን የኒውክሌር፣ የባሊስቲክ ሚሳይል እና የፕሮክሲ መዋቅሮች ላይ ያተኮረ ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ በጋራ መክፈታቸው ይታወሳል።
በኢራን ላይ የተከፈተው የጋራ ወታደራዊ ዘመቻ፣ ኢራን የሆርሙዝ የባህር በርን በመዝጋቷና የዓለምን ኢኮኖሚ በማነቆ ውስጥ በመጣሏ ምክንያት በፕሬዝዳንት ትራምፕ አዛዥነት ባለፈው ሚያዝያ ወር በድንገት እንዲቆም ተደርጓል። ዘመቻው የተፈለገውን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግብ ሳያሳካ መቆሙ ለኔታንያሁ ያልተጠበቀ ውሳኔ የነበረ ሲሆን፣ በአንጻሩ ለትራምፕ ከፍተኛ የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ዋጋ አስከፍሏቸዋል። የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ ኔታንያሁ በኋይት ሀውስ ውይይታቸው በቅርቡ በተሾሙት የኢራን አዲስ ጠቅላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ ስር ኢራን እያደረገች ያለችውን የኒውክሌር እና የወታደራዊ አቅም ማገገሚያ እንቅስቃሴ የሚያሳይ አዲስ የደህንነት መረጃ ለትራምፕ በማቅረብ፣ ወታደራዊ እርምጃው እንደገና እንዲቀጥል ለማሳመን አቅደዋል።
ሆኖም ትራምፕን ከዲፕሎማሲያዊ መንገድ መልሶ ወደ ከባድ ወታደራዊ ዘመቻ ማምጣት ከባድ እንደሚሆን ተገምቷል። ሁለቱም መሪዎች ከፊታቸው ለሚጠብቋቸው ወሳኝ ምርጫዎች ማለትም ለእስራኤል የጥቅምት አጠቃላይ ምርጫ እና ለአሜሪካው የእስከመካከለኛው ዘመን (Midterm) ምርጫ የሚጠቅሟቸውን ተቃራኒ ስትራቴጂዎች ይዘው ቀርበዋል። ኔታንያሁ በኢራን ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ በመውሰድ የኒውክሌር ስጋቱን በማስወገድ ይህንን ውጤት መጪውን ምርጫ ለማሸነፍ ለሕዝባቸው እንደ ትልቅ ስኬት ማቅረብ ሲፈልጉ፣ ትራምፕ በበኩላቸው ውጥረቱን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ በማርገብ የነዳጅ ዋጋን ማረጋጋት እና ለአሜሪካውያን መራጮች የኢኮኖሚ እፎይታ መስጠትን ይሻሉ።
የኔታንያሁ የፖለቲካ ተጽእኖ በዋሽንግተን ዘንድ ከቀደመው ጊዜ በእጅጉ መቀነሱ ይታያል። ትራምፕ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእስራኤልን ፍላጎት የሚጻረሩ በርካታ ውሳኔዎችን አስተላልፈዋል። ከእነዚህም መካከል በኢራን ላይ የተከፈተውን ዘመቻ በድንገት ማቆም፣ ለቱርክ የጦር ጄቶችን ለመሸጥ ፍላጎት ማሳየት እና ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር የሲቪል ኒውክሌር ስምምነት መፈረም ይገኙበታል። በዚህ ስብሰባ ኔታንያሁ አሜሪካን እንደገና ወደ ጦርነት እንድትገባ ማሳመን ባይችሉ እንኳ፣ ሌሎች አማራጭ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ይሞክራሉ። በዋናነት የዲፕሎማሲው መንገድ ካልሰራ እስራኤል በራሷ አቅም በኢራን እና በሂዝቦላ ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንድትወስድ ከአሜሪካ ፈቃድ ማግኘት፣ እንዲሁም አሜሪካ ከሳዑዲ ጋር የጀመረችውን የኒውክሌር ትብብር ከእስራኤል ጋር ግንኙነት የመመስረት ቅድመ-ሁኔታ ጋር ማያያዝ ዋነኛ አላማዎቻቸው ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ ሀማስ እና ሂዝቦላ በሊባኖስ እና በጋዛ የተቀመጡትን የሰላም ማዕቀፎች ካፈረሱ አሜሪካ ወታደራዊ ምላሽን እንድትደግፍ የጋራ ስምምነት መፍጠርም ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው። በመሆኑም ማክሰኞ ዕለት የሚደረገው የሁለቱ መሪዎች ስብሰባ፣ ከጦርነቱ በኋላ ያለውን አዲሱን የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን የሚቃኝ እና የመጪውን የጥቅምት እና የህዳር ምርጫዎች የፖለቲካ አቅጣጫ የሚወስን ወሳኝ ኩነት ይሆናል።
በኢራን ላይ የተከፈተው የጋራ ወታደራዊ ዘመቻ፣ ኢራን የሆርሙዝ የባህር በርን በመዝጋቷና የዓለምን ኢኮኖሚ በማነቆ ውስጥ በመጣሏ ምክንያት በፕሬዝዳንት ትራምፕ አዛዥነት ባለፈው ሚያዝያ ወር በድንገት እንዲቆም ተደርጓል። ዘመቻው የተፈለገውን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ግብ ሳያሳካ መቆሙ ለኔታንያሁ ያልተጠበቀ ውሳኔ የነበረ ሲሆን፣ በአንጻሩ ለትራምፕ ከፍተኛ የሀገር ውስጥ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ዋጋ አስከፍሏቸዋል። የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ ኔታንያሁ በኋይት ሀውስ ውይይታቸው በቅርቡ በተሾሙት የኢራን አዲስ ጠቅላይ መሪ ሙጅተባ ኻመነኢ ስር ኢራን እያደረገች ያለችውን የኒውክሌር እና የወታደራዊ አቅም ማገገሚያ እንቅስቃሴ የሚያሳይ አዲስ የደህንነት መረጃ ለትራምፕ በማቅረብ፣ ወታደራዊ እርምጃው እንደገና እንዲቀጥል ለማሳመን አቅደዋል።
ሆኖም ትራምፕን ከዲፕሎማሲያዊ መንገድ መልሶ ወደ ከባድ ወታደራዊ ዘመቻ ማምጣት ከባድ እንደሚሆን ተገምቷል። ሁለቱም መሪዎች ከፊታቸው ለሚጠብቋቸው ወሳኝ ምርጫዎች ማለትም ለእስራኤል የጥቅምት አጠቃላይ ምርጫ እና ለአሜሪካው የእስከመካከለኛው ዘመን (Midterm) ምርጫ የሚጠቅሟቸውን ተቃራኒ ስትራቴጂዎች ይዘው ቀርበዋል። ኔታንያሁ በኢራን ላይ ጠንካራ ወታደራዊ እርምጃ በመውሰድ የኒውክሌር ስጋቱን በማስወገድ ይህንን ውጤት መጪውን ምርጫ ለማሸነፍ ለሕዝባቸው እንደ ትልቅ ስኬት ማቅረብ ሲፈልጉ፣ ትራምፕ በበኩላቸው ውጥረቱን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ በማርገብ የነዳጅ ዋጋን ማረጋጋት እና ለአሜሪካውያን መራጮች የኢኮኖሚ እፎይታ መስጠትን ይሻሉ።
የኔታንያሁ የፖለቲካ ተጽእኖ በዋሽንግተን ዘንድ ከቀደመው ጊዜ በእጅጉ መቀነሱ ይታያል። ትራምፕ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእስራኤልን ፍላጎት የሚጻረሩ በርካታ ውሳኔዎችን አስተላልፈዋል። ከእነዚህም መካከል በኢራን ላይ የተከፈተውን ዘመቻ በድንገት ማቆም፣ ለቱርክ የጦር ጄቶችን ለመሸጥ ፍላጎት ማሳየት እና ከሳዑዲ ዓረቢያ ጋር የሲቪል ኒውክሌር ስምምነት መፈረም ይገኙበታል። በዚህ ስብሰባ ኔታንያሁ አሜሪካን እንደገና ወደ ጦርነት እንድትገባ ማሳመን ባይችሉ እንኳ፣ ሌሎች አማራጭ ስትራቴጂካዊ ግቦችን ለማሳካት ይሞክራሉ። በዋናነት የዲፕሎማሲው መንገድ ካልሰራ እስራኤል በራሷ አቅም በኢራን እና በሂዝቦላ ላይ ወታደራዊ እርምጃ እንድትወስድ ከአሜሪካ ፈቃድ ማግኘት፣ እንዲሁም አሜሪካ ከሳዑዲ ጋር የጀመረችውን የኒውክሌር ትብብር ከእስራኤል ጋር ግንኙነት የመመስረት ቅድመ-ሁኔታ ጋር ማያያዝ ዋነኛ አላማዎቻቸው ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ ሀማስ እና ሂዝቦላ በሊባኖስ እና በጋዛ የተቀመጡትን የሰላም ማዕቀፎች ካፈረሱ አሜሪካ ወታደራዊ ምላሽን እንድትደግፍ የጋራ ስምምነት መፍጠርም ሌላው የትኩረት አቅጣጫ ነው። በመሆኑም ማክሰኞ ዕለት የሚደረገው የሁለቱ መሪዎች ስብሰባ፣ ከጦርነቱ በኋላ ያለውን አዲሱን የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል ሚዛን የሚቃኝ እና የመጪውን የጥቅምት እና የህዳር ምርጫዎች የፖለቲካ አቅጣጫ የሚወስን ወሳኝ ኩነት ይሆናል።
10 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽና ቀጣናዊ ፋይዳው
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
Sponsored by
Surafel
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ከቴህራን ጋር ውይይት እያደረገች መሆኑን ገልጸው፣ በሂደቱ "መልካም ነገሮች ሊፈጠሩ ይችላሉ" ሲሉ ተናገሩ። ፕሬዝዳንቱ ከኢራን ጋር አዲስ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሰፊ ጊዜ እና ብዙ ትዕግስት እንዳላቸውም አረጋግጠዋል።
ኢራን በዋናው የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ ለማስተጓጎል በቅርቡ ያደረገችው ሙከራ ቢኖርም፣ የሆርሙዝ የባህር በር ደህንነት "በጣም በጥሩ ሁኔታ" ላይ እንደሚገኝ ትራምፕ ጠቁመዋል። አክለውም ኢራን በአማላጆች በኩል እንዲሁም በቀጥታ ከአሜሪካ ጋር ለመገናኘት ጥያቄ ማቅረቧን አብራርተዋል።
በወቅቱ አንድ ጋዜጠኛ ለነገሮች ምን ያህል ትዕግስት እንዳላቸው ላቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ "ብዙ ትዕግስት አለኝ፤ በቂ ጊዜም አለኝ" ብለዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ "ጥሩ ውይይቶች" እየተደረጉ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ "አንድ ነገር ሊፈጠር የሚችልበት ጥሩ አጋጣሚ አለ ብዬ አስባለሁ። ከተሳካ ጥሩ ነው፤ ካልተሳካ ደግሞ ከሁለት ቀናት በፊት ወደምናደርገው ነገር እንመለሳለን" በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
ኢራን በዋናው የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ ለማስተጓጎል በቅርቡ ያደረገችው ሙከራ ቢኖርም፣ የሆርሙዝ የባህር በር ደህንነት "በጣም በጥሩ ሁኔታ" ላይ እንደሚገኝ ትራምፕ ጠቁመዋል። አክለውም ኢራን በአማላጆች በኩል እንዲሁም በቀጥታ ከአሜሪካ ጋር ለመገናኘት ጥያቄ ማቅረቧን አብራርተዋል።
በወቅቱ አንድ ጋዜጠኛ ለነገሮች ምን ያህል ትዕግስት እንዳላቸው ላቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ "ብዙ ትዕግስት አለኝ፤ በቂ ጊዜም አለኝ" ብለዋል። በሁለቱ ሀገራት መካከል አሁን ላይ "ጥሩ ውይይቶች" እየተደረጉ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ "አንድ ነገር ሊፈጠር የሚችልበት ጥሩ አጋጣሚ አለ ብዬ አስባለሁ። ከተሳካ ጥሩ ነው፤ ካልተሳካ ደግሞ ከሁለት ቀናት በፊት ወደምናደርገው ነገር እንመለሳለን" በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
12 days ago
"በዚህ በቀይ ባህር፣ ኤርትራ ረጅም የባህር በር ያላት ሀገር ናት። የቀይ ባህርን ዳርቻ መቆጣጠር የምትፈልግ፣ የወቅቱ የመካከለኛው ምስራቅ ኃያል ለመሆን ግብግብ ውስጥ እየገጠመች ያለች ሀገር አለች፣ አረብ ኤምሬት የምትባል ሀገር። ስለዚህ ኤርትራ ላይ የጠላትነትን እንዲሰለፍ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ሳይሆን የአረብ ኤምሬትስ ኢንተረስት (ፍላጎት) ነው። በዚህ ምክንያት... አረብ ኤምሬት እኮ የአሰብ ወደብን ለማልማት ወስዳ ነበር። በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው በሰዓታት፣ 48 ሰዓት እንደዚህ አካባቢ ነው ለቃችሁ ውጡ የተባሉት። ያልሆነ ነገር ሲያደርጉ ተገኝተው ይመስለኛል - ያው ግልጽ ባይደረግም ብዙ ጊዜ። የአረብ ኤምሬትን ተልዕኮ ለማስፈጸም ሲል ነው ከኤርትራ ጋር እዚህ ውስጥ የገባው"
የቀድሞ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ከኢኤምኤስ ሚዲያ ጋር ካደረጉት ቃለምልልስ
የቀድሞ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው
ከኢኤምኤስ ሚዲያ ጋር ካደረጉት ቃለምልልስ
21 days ago
የባህር በር፤ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የህልውና አጀንዳ
*************
የባሕር በር ባለቤት መሆን ከኢኮኖሚያዊ ፍላጎት ባሻገር፣ የሕዝብን አመለካከትና የሀገርን ዕጣ ፈንታ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር የሥልጣኔ ቁልፍ ነው። ለኢትዮጵያም የባህር በር ጥያቄ የንግድ ማሳለጫ ወይንም የዕቃዎች መላኪያና መቀበያ መስመር ፍለጋ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፉ የንግድ መድረክ ላይ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን የፖለቲካ ነፃነት ዋስትና ነው።
ይህ ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን መጻኢ ዕድል የሚወስን፣ የብልጽግና ጉዞዋን የሚያቀና እና የሀገሪቱን ክብርና ሉዓላዊነት በተግባር የሚያረጋግጥ የህልውና ጉዳይም ነው። ከታሪክ ማህደር እስከ ነገው የትውልድ ተስፋ ድረስ የባህር በር ባለቤትነት ለኢትዮጵያ የነፃነት ሙሉነት መገለጫም ሆኖ ይታያል።
በዓለም ታሪክ ውስጥ የባህር በር ያላቸው ሀገራት የባህር ዳርቻዎቻቸውን ለዘመናዊ ሎጀስቲክስ፣ ለግዙፍ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ለዓለም አቀፍ የሽርሽር መርከቦች ማረፊያ በማዋል የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን በከፍተኛ ደረጃ አረጋግጠዋል። የባህር ጠረፍን ማልማት የሀገር ውስጥ ገቢን ከማሳደግ ባለፈ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰማያዊ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ የሰማያዊ ኢኮኖሚ ተጠቃሚ በመሆን የአሳ ሀብት ልማትን፣ የባህር ላይ ቱሪዝምን እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ያላት አማራጭ የባህር በር ባለቤትነትን ዳግም በማረጋገጥ ላይ የተመሰረተ ነው። የራስ ወደብ መኖር በየዓመቱ ለኪራይና ለታሪፍ የሚባክነውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት፣ ያንን ከፍተኛ ሀብት ለሀገር ውስጥ መሠረተ-ልማት ግንባታ፣ ለትምህርትና ለጤና ዘርፍ ለማዋል ብቸኛው ስልታዊ መንገድ ነው።
የባህር በር ባለቤትነት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ በዓለም አቀፉ የንግድ መድረክ ላይ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን የፖለቲካ ነፃነት ዋስትና ነው።
በፍጥነት እያደገ የመጣውን ሰፊ የሕዝብ ቁጥር መመገብ፣ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በወቅቱ ማስገባት እና የሀገሪቱን ብሔራዊ ደኅንነት በዘላቂነት ማስጠበቅ የሚቻለው የባህር በርን እንደ ቀዳሚ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ አጀንዳ በመያዝ ነው። ይህ ጥያቄ የሌሎችን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት እና በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤትነት ሲረጋገጥ የሚሳካ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል በመገንባት የአፍሪካ ቀንድን ደኅንነት ለመጠበቅና የዓለም አቀፍ የባህር ላይ ንግድ መስመሮችን ከስጋት ነፃ ለማድረግ የምታበረክተው አስተዋፅኦ የሚጎላው የራሷ የባህር በር ሲኖራት ብቻ ነው። ወደብ አልባ መሆን የሚፈጥረውን የጂኦ-ፖለቲካ ጫና በመስበር፣ ሀገሪቱን በቀይ ባህርና በአደን ባህረ-ሰላጤ አካባቢ ወሳኝ የፖለቲካና የደኅንነት ውሳኔ ሰጪ እንድትሆን ያደርጋታል።
የኢትዮጵያ የባህር ላይ ታላቅነት የአክሱም ሥልጣኔ ታሪካዊ ቅርስና የአባቶቻችን የነፃነት አሻራ መሆኑ አይዘነጋም። ይህ ትውልድ ያንን የተዘጋ ታሪካዊ በር በሰላማዊ ዲፕሎማሲ፣ በጋራ ልማት ስምምነቶችና በብስለት በመክፈት የኢትዮጵያን ትንሳኤ የሚያረጋግጥበት ጊዜ ላይ ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ ጥረት የኢትዮጵያን ዘላለማዊ ክብር የሚያድስ፣ ኢኮኖሚዋን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና ለመጪው ትውልድ ብሩህና አስተማማኝ ነገን የሚያሰናዳ ትልቅ አሻራ ሆኖ በታሪክ ማህደር ላይ በደማቁ ይመዘገባል።
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea #sovereignty
*************
የባሕር በር ባለቤት መሆን ከኢኮኖሚያዊ ፍላጎት ባሻገር፣ የሕዝብን አመለካከትና የሀገርን ዕጣ ፈንታ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር የሥልጣኔ ቁልፍ ነው። ለኢትዮጵያም የባህር በር ጥያቄ የንግድ ማሳለጫ ወይንም የዕቃዎች መላኪያና መቀበያ መስመር ፍለጋ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፉ የንግድ መድረክ ላይ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን የፖለቲካ ነፃነት ዋስትና ነው።
ይህ ጥያቄ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን መጻኢ ዕድል የሚወስን፣ የብልጽግና ጉዞዋን የሚያቀና እና የሀገሪቱን ክብርና ሉዓላዊነት በተግባር የሚያረጋግጥ የህልውና ጉዳይም ነው። ከታሪክ ማህደር እስከ ነገው የትውልድ ተስፋ ድረስ የባህር በር ባለቤትነት ለኢትዮጵያ የነፃነት ሙሉነት መገለጫም ሆኖ ይታያል።
በዓለም ታሪክ ውስጥ የባህር በር ያላቸው ሀገራት የባህር ዳርቻዎቻቸውን ለዘመናዊ ሎጀስቲክስ፣ ለግዙፍ የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ለዓለም አቀፍ የሽርሽር መርከቦች ማረፊያ በማዋል የኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን በከፍተኛ ደረጃ አረጋግጠዋል። የባህር ጠረፍን ማልማት የሀገር ውስጥ ገቢን ከማሳደግ ባለፈ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰማያዊ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ የሰማያዊ ኢኮኖሚ ተጠቃሚ በመሆን የአሳ ሀብት ልማትን፣ የባህር ላይ ቱሪዝምን እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ያላት አማራጭ የባህር በር ባለቤትነትን ዳግም በማረጋገጥ ላይ የተመሰረተ ነው። የራስ ወደብ መኖር በየዓመቱ ለኪራይና ለታሪፍ የሚባክነውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት፣ ያንን ከፍተኛ ሀብት ለሀገር ውስጥ መሠረተ-ልማት ግንባታ፣ ለትምህርትና ለጤና ዘርፍ ለማዋል ብቸኛው ስልታዊ መንገድ ነው።
የባህር በር ባለቤትነት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን፣ በዓለም አቀፉ የንግድ መድረክ ላይ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን የፖለቲካ ነፃነት ዋስትና ነው።
በፍጥነት እያደገ የመጣውን ሰፊ የሕዝብ ቁጥር መመገብ፣ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን በወቅቱ ማስገባት እና የሀገሪቱን ብሔራዊ ደኅንነት በዘላቂነት ማስጠበቅ የሚቻለው የባህር በርን እንደ ቀዳሚ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ አጀንዳ በመያዝ ነው። ይህ ጥያቄ የሌሎችን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት እና በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ባለቤትነት ሲረጋገጥ የሚሳካ ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ነው።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል በመገንባት የአፍሪካ ቀንድን ደኅንነት ለመጠበቅና የዓለም አቀፍ የባህር ላይ ንግድ መስመሮችን ከስጋት ነፃ ለማድረግ የምታበረክተው አስተዋፅኦ የሚጎላው የራሷ የባህር በር ሲኖራት ብቻ ነው። ወደብ አልባ መሆን የሚፈጥረውን የጂኦ-ፖለቲካ ጫና በመስበር፣ ሀገሪቱን በቀይ ባህርና በአደን ባህረ-ሰላጤ አካባቢ ወሳኝ የፖለቲካና የደኅንነት ውሳኔ ሰጪ እንድትሆን ያደርጋታል።
የኢትዮጵያ የባህር ላይ ታላቅነት የአክሱም ሥልጣኔ ታሪካዊ ቅርስና የአባቶቻችን የነፃነት አሻራ መሆኑ አይዘነጋም። ይህ ትውልድ ያንን የተዘጋ ታሪካዊ በር በሰላማዊ ዲፕሎማሲ፣ በጋራ ልማት ስምምነቶችና በብስለት በመክፈት የኢትዮጵያን ትንሳኤ የሚያረጋግጥበት ጊዜ ላይ ይገኛል።
ይህ ታሪካዊ ጥረት የኢትዮጵያን ዘላለማዊ ክብር የሚያድስ፣ ኢኮኖሚዋን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እና ለመጪው ትውልድ ብሩህና አስተማማኝ ነገን የሚያሰናዳ ትልቅ አሻራ ሆኖ በታሪክ ማህደር ላይ በደማቁ ይመዘገባል።
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea #sovereignty
22 days ago
የጂኦግራፊ እስረኝነትን መስበር፡ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ እና የአፍሪካ ቀንድ እጣ-ፈንታ
******************************
የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በአጋጣሚ የተከሰተ የታሪክ ግድፈት ሳይሆን የረዥም ዘመን የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካዊ ሴራ፣ የቅኝ ግዛት ሽግሽግና የውስጥ ፖለቲካዊ ስብራት የወለደው መሪር ሀቅ ነው።
በአስራ ዘጠነኛውና በሃያኛው ክፍለ ዘመን የአውሮፓ ሀያላን መንግሥታት የአፍሪካ ቀንድን ሲቀራመቱ ኢትዮጵያን ደካማና የጂኦግራፊ እስረኛ ለማድረግ የተቀየሰው ዋነኛ ስትራቴጂ ከቀይ ባህር በማራቅ ወደብ አልባ ማድረግ ነበር። ይህ የቅኝ ግዛታዊ አሻራ፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላም በቀዝቃዛው ጦርነት አሰላለፍ ውስጥ በነበሩ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት ይበልጥ ስር የሰደደ ነበር ።
ይሁን እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአጽንኦት እንዳስገነዘቡት ለሺህ ዘመናት በባለቤትነት የያዝነውን የባህር በር ያጣነው በውጭ ጠላት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን በውስጥ መዘናጋት፣ በመከፋፈልና ባልተመረጡ መንግሥታት የፖለቲካ ሸፍጥ ምክንያት ነው።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መሻትና ስትራቴጂካዊ ጥቅም ማስቆም የሚችል ምድራዊ ኃይል ባይኖርም ያልተሳካልን በውስጥ ችግራችን እንጂ አቅም በማጣት አይደለም።
በመሆኑም አሁን ላይ የሚታዩት የውስጥ አለመግባባቶች ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የባህር ተጠቃሚነት ለማግለል የሚደረግ የፕሮፓጋንዳ ሴራ አካል መሆናቸውን ተገንዝቦ፣ መላው ሕዝብ ለብሔራዊ ጥቅም በጋራ መቆም ግድ ይለዋል።
ከመቶ ሰላሳ ሚሊዮን በላይ የሕዝብ ቁጥር ያላት ግዙፍ አገር፣ በባህር አልባነት ታፍና እንድትኖር መፍረድ በተፈጥሮ ሕግም ሆነ በዘመናዊ የኢኮኖሚ ስሌት ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ርዕዮት ነው።
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ላይ መዋቅራዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆንም ይህ ለውጥ ለጎረቤት አገራት የስጋት ምንጭ ሳይሆን የጋራ ብልጽግናን የሚያረጋግጥ የትብብር ማገር ነው።
ሠላም በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ ሳይሆን ሁሉን አቀፍ በሆነ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ትስስር የሚረጋገጥ ነው። ጎረቤት አገራት ያላቸውን ሰፊ የባህር ጠረፍ ወደ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሞተር ለመቀየር፣ የኢትዮጵያን ግዙፍ ገበያ እና እያደገ የመጣውን የኢንዱስትሪ ምርታማነት አጥብቀው ይሻሉ።
ኢትዮጵያ የባህር በር ስታገኝ፣ በመሠረተ ልማት፣ በባቡር መስመር እና በኃይል አቅርቦት በጽኑ የምትተሳሰር በመሆኑ የአገራቱ እጣ ፈንታ ወደማይነጣጠል የጋራ ጥገኝነት ያድጋል። በዚህም አንዱ አገር የሌላውን ሠላም እንደ ራሱ ህልውና በመጠበቅ፣ ቀጣናውን ከእርስ በርስ ግጭት አዙሪት ይታደገዋል።
በተጨማሪም የዓለም ንግድ አስር በመቶ የሚተላለፍበት ቀይ ባህር፣ በሽብርተኝነትና በህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር በእጅጉ እየታመሰ ይገኛል። በዚህ ስትራቴጂካዊ ቀጣና ውስጥ ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል፣ የአንድ አገር ወታደራዊ የበላይነትን ለማንገስ ሳይሆን አፍሪካዊ የጋራ የፀጥታ ትብብርን ለማጎልበት ነው።
የኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን፣ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በመግታት፣ የአፍሪካ ቀንድን ወደ አንድ የተደራጀ የጂኦ-ፖለቲካዊ ኃይልና የኢኮኖሚ ትብብር ያሸጋግረዋል።
በዓመት ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚደርሰውን የሎጂስቲክስ ወጪ በጋራ ኢንቨስትመንት መልክ በጎረቤት አገራት ወደቦች ላይ ማፍሰስ ቢቻል የጠቅላላውን ቀጣና የመሠረተ ልማት ገጽታ ሙሉ ለሙሉ ይቀይረዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የአንድ አገር የቅንጦት ፍላጎት ሳይሆን የታሪክ መዛባትን የሚያስተካክል፣ የስነ-ልቦና ስብራትን የሚጠግን፣ የሎጂስቲክስ ማነቆን በመፍታት ወጣቱን ከጦርነት አውድማ ወደ ልማት የሚያሸጋግርና መላውን የአፍሪካ ቀንድ ከድህነት አዘቅት የሚያወጣ ታሪካዊ የድልድይ ስራ ነው።
ይህንን እውነት በድርድርና በመተማመን ላይ በተመሰረተ ስምምነት እውን ማድረግ የዘመኑ ትውልድ የማይታለፍ ታሪካዊ አደራ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ አገራት በተናጠል ሲቆሙ ለውጭ ሀያላን ጣልቃ ገብነትና የዉኪልና ጦርነት ተጋላጭነታቸው የሰፋ ነው።የኢትዮጵያ ወደብ አልባነትና የሌሎቹ ሀገራት የኢኮኖሚ ድክመት ይህንን የስጋት በር በሰፊው ከፍቶታል።
ስለሆነም የባህር በር ጥያቄው ከአሸናፊና ተሸናፊ ፖለቲካዊ ስሌት ሙሉ በሙሉ በመውጣት፣ ቀጣናውን ከባዕዳን ጥገኝነትና ከዘለዓለማዊ የግጭት አዙሪት የሚያላቅቅ የጋራ የመዳን ስትራቴጂ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባዋል።
ዘላቂ ሰላምና የተረጋገጠ ብልጽግናን ለማምጣት፣ ይህ የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ መሻት ለጎረቤት አገራት ሉዓላዊነት ስጋት ሳይሆን በእኩልነትና በመከባበር ላይ የተገነባ የነገው የጋራ ብሩህ ተስፋችን የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ማረጋገጥ የግድ ይላል። ይህም ለአዲሱ ትውልድ የላቀ ትሩፋት ነው።
በረከት ሽመልስ
******************************
የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት በአጋጣሚ የተከሰተ የታሪክ ግድፈት ሳይሆን የረዥም ዘመን የውጭ ኃይሎች የጂኦ-ፖለቲካዊ ሴራ፣ የቅኝ ግዛት ሽግሽግና የውስጥ ፖለቲካዊ ስብራት የወለደው መሪር ሀቅ ነው።
በአስራ ዘጠነኛውና በሃያኛው ክፍለ ዘመን የአውሮፓ ሀያላን መንግሥታት የአፍሪካ ቀንድን ሲቀራመቱ ኢትዮጵያን ደካማና የጂኦግራፊ እስረኛ ለማድረግ የተቀየሰው ዋነኛ ስትራቴጂ ከቀይ ባህር በማራቅ ወደብ አልባ ማድረግ ነበር። ይህ የቅኝ ግዛታዊ አሻራ፣ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላም በቀዝቃዛው ጦርነት አሰላለፍ ውስጥ በነበሩ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነት ይበልጥ ስር የሰደደ ነበር ።
ይሁን እንጂ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአጽንኦት እንዳስገነዘቡት ለሺህ ዘመናት በባለቤትነት የያዝነውን የባህር በር ያጣነው በውጭ ጠላት ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን በውስጥ መዘናጋት፣ በመከፋፈልና ባልተመረጡ መንግሥታት የፖለቲካ ሸፍጥ ምክንያት ነው።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መሻትና ስትራቴጂካዊ ጥቅም ማስቆም የሚችል ምድራዊ ኃይል ባይኖርም ያልተሳካልን በውስጥ ችግራችን እንጂ አቅም በማጣት አይደለም።
በመሆኑም አሁን ላይ የሚታዩት የውስጥ አለመግባባቶች ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ የባህር ተጠቃሚነት ለማግለል የሚደረግ የፕሮፓጋንዳ ሴራ አካል መሆናቸውን ተገንዝቦ፣ መላው ሕዝብ ለብሔራዊ ጥቅም በጋራ መቆም ግድ ይለዋል።
ከመቶ ሰላሳ ሚሊዮን በላይ የሕዝብ ቁጥር ያላት ግዙፍ አገር፣ በባህር አልባነት ታፍና እንድትኖር መፍረድ በተፈጥሮ ሕግም ሆነ በዘመናዊ የኢኮኖሚ ስሌት ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ርዕዮት ነው።
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ላይ መዋቅራዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆንም ይህ ለውጥ ለጎረቤት አገራት የስጋት ምንጭ ሳይሆን የጋራ ብልጽግናን የሚያረጋግጥ የትብብር ማገር ነው።
ሠላም በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ ሳይሆን ሁሉን አቀፍ በሆነ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ትስስር የሚረጋገጥ ነው። ጎረቤት አገራት ያላቸውን ሰፊ የባህር ጠረፍ ወደ ግዙፍ የኢኮኖሚ ሞተር ለመቀየር፣ የኢትዮጵያን ግዙፍ ገበያ እና እያደገ የመጣውን የኢንዱስትሪ ምርታማነት አጥብቀው ይሻሉ።
ኢትዮጵያ የባህር በር ስታገኝ፣ በመሠረተ ልማት፣ በባቡር መስመር እና በኃይል አቅርቦት በጽኑ የምትተሳሰር በመሆኑ የአገራቱ እጣ ፈንታ ወደማይነጣጠል የጋራ ጥገኝነት ያድጋል። በዚህም አንዱ አገር የሌላውን ሠላም እንደ ራሱ ህልውና በመጠበቅ፣ ቀጣናውን ከእርስ በርስ ግጭት አዙሪት ይታደገዋል።
በተጨማሪም የዓለም ንግድ አስር በመቶ የሚተላለፍበት ቀይ ባህር፣ በሽብርተኝነትና በህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር በእጅጉ እየታመሰ ይገኛል። በዚህ ስትራቴጂካዊ ቀጣና ውስጥ ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል፣ የአንድ አገር ወታደራዊ የበላይነትን ለማንገስ ሳይሆን አፍሪካዊ የጋራ የፀጥታ ትብብርን ለማጎልበት ነው።
የኢትዮጵያ በቀይ ባህር ላይ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን፣ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በመግታት፣ የአፍሪካ ቀንድን ወደ አንድ የተደራጀ የጂኦ-ፖለቲካዊ ኃይልና የኢኮኖሚ ትብብር ያሸጋግረዋል።
በዓመት ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚደርሰውን የሎጂስቲክስ ወጪ በጋራ ኢንቨስትመንት መልክ በጎረቤት አገራት ወደቦች ላይ ማፍሰስ ቢቻል የጠቅላላውን ቀጣና የመሠረተ ልማት ገጽታ ሙሉ ለሙሉ ይቀይረዋል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የአንድ አገር የቅንጦት ፍላጎት ሳይሆን የታሪክ መዛባትን የሚያስተካክል፣ የስነ-ልቦና ስብራትን የሚጠግን፣ የሎጂስቲክስ ማነቆን በመፍታት ወጣቱን ከጦርነት አውድማ ወደ ልማት የሚያሸጋግርና መላውን የአፍሪካ ቀንድ ከድህነት አዘቅት የሚያወጣ ታሪካዊ የድልድይ ስራ ነው።
ይህንን እውነት በድርድርና በመተማመን ላይ በተመሰረተ ስምምነት እውን ማድረግ የዘመኑ ትውልድ የማይታለፍ ታሪካዊ አደራ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ አገራት በተናጠል ሲቆሙ ለውጭ ሀያላን ጣልቃ ገብነትና የዉኪልና ጦርነት ተጋላጭነታቸው የሰፋ ነው።የኢትዮጵያ ወደብ አልባነትና የሌሎቹ ሀገራት የኢኮኖሚ ድክመት ይህንን የስጋት በር በሰፊው ከፍቶታል።
ስለሆነም የባህር በር ጥያቄው ከአሸናፊና ተሸናፊ ፖለቲካዊ ስሌት ሙሉ በሙሉ በመውጣት፣ ቀጣናውን ከባዕዳን ጥገኝነትና ከዘለዓለማዊ የግጭት አዙሪት የሚያላቅቅ የጋራ የመዳን ስትራቴጂ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባዋል።
ዘላቂ ሰላምና የተረጋገጠ ብልጽግናን ለማምጣት፣ ይህ የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ መሻት ለጎረቤት አገራት ሉዓላዊነት ስጋት ሳይሆን በእኩልነትና በመከባበር ላይ የተገነባ የነገው የጋራ ብሩህ ተስፋችን የማዕዘን ድንጋይ መሆኑን ማረጋገጥ የግድ ይላል። ይህም ለአዲሱ ትውልድ የላቀ ትሩፋት ነው።
በረከት ሽመልስ
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያ የባህር በር ማጣት ዋና ምክንያት የውጭ ኃይሎች ተጽዕኖ ሳይሆን የሀገሪቱ የውስጥ የፖለቲካ መከፋፈል መሆኑን በድጋሚ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ በአዲስ አበባ በተከፈተው «የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ» መድረክ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
በንግግራቸው ኢትዮጵያ የባህር በርን «ለሺህ ዓመታት አስተዳድራ፣ በባለቤትነት ይዛ እና ተጠቅማበት እንደነበር» አስታውሰው፣ አሁን ላለችበት የባህር በር አልባነት ሁኔታ ተጠያቂው «የውጭ ኃይሎች ሳይሆን የእኛ የውስጥ ድክመት ነው» ብለዋል። «በዚህ ጉዞ ውስጥ በራሳችን ውስጣዊ ድክመት እና በሌሎች ዕድለኝነት የባህር በራችንን አጥተናል» ሲሉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያን በቋሚነት ከብሔራዊ ጥቅሟ ሊያግዳት የሚችል የውጭ ኃይል እንዳልነበረ አክለዋል።
በንግግራቸው አንዳንድ የውጭ ኃይሎችን «በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ እንደሚንሳፈፉ አሞራዎች» የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህ አካላት ኢትዮጵያ በምትገነባበት ጊዜ እንደማይገኙና በተቃራኒው በውስጥ ግጭት ስትታመስ ግን ተገኝተው ድጋፍና ፕሮፓጋንዳ እንደሚያቀርቡ ከሰዋል። «ለእነዚህ አሞራዎች መልእክቴ ይህ ነው፤ ከብቱን የምንገዛው እኛ፣ የምንቆራርጠው እኛ ነን፤ እኛ በፈቃዳችን ካልሰጠን በቀር ማንም አሞራ ከጠረጴዛችን ላይ በኃይል ሊወስድ አይችልም» ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ትብብር ለመፍጠር ሁልጊዜም ዝግጁ እንደሆነች ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ነገር ግን አንድነት ያላት ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ትለቃለች ተብሎ መጠበቅ «ከንቱ ተስፋ» እንደሆነ አስምረውበታል።
በሌላ በኩል፣ ሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየባትን አለመግባባቶችን በኃይል የመፍታት ባህል በመቀየር በሰላማዊ ውይይት የመፍታት ልምድ የምታዳብርበት እንደሆነ ጠቁመዋል። «የፖለቲካችን በጠንካራ ቃል ይጀምራል፣ በኃይል እርምጃ ያልቃል፤ ይህንን ስብራት በአንዴ ልንፈውሰው ይገባል» ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የምክክር ባህልን ማዳበር የሀገሪቱን አንድነት ከማጠናከሩም በላይ የውጭ ጣልቃ-ገብነትን እንደሚቀንስ ገልጸዋል።
ንግግራቸውን ሲያገባድዱም በጉባኤው ለተሳተፉት ከአራት ሺህ በላይ ታዳሚዎች ባስተላለፉት መልእክት፣ «ስለ ምን ጉዳይ ብንከራከርም በውይይት መፍታት እንችላለን፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለውጭ ኃይሎች የምታሳልፍበት አደገኛ ታሪካዊ አረም ላለመሆን ሁላችንም መጣር አለብን» በማለት ጥሪ አቅርበዋል።
በንግግራቸው ኢትዮጵያ የባህር በርን «ለሺህ ዓመታት አስተዳድራ፣ በባለቤትነት ይዛ እና ተጠቅማበት እንደነበር» አስታውሰው፣ አሁን ላለችበት የባህር በር አልባነት ሁኔታ ተጠያቂው «የውጭ ኃይሎች ሳይሆን የእኛ የውስጥ ድክመት ነው» ብለዋል። «በዚህ ጉዞ ውስጥ በራሳችን ውስጣዊ ድክመት እና በሌሎች ዕድለኝነት የባህር በራችንን አጥተናል» ሲሉ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያን በቋሚነት ከብሔራዊ ጥቅሟ ሊያግዳት የሚችል የውጭ ኃይል እንዳልነበረ አክለዋል።
በንግግራቸው አንዳንድ የውጭ ኃይሎችን «በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ እንደሚንሳፈፉ አሞራዎች» የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እነዚህ አካላት ኢትዮጵያ በምትገነባበት ጊዜ እንደማይገኙና በተቃራኒው በውስጥ ግጭት ስትታመስ ግን ተገኝተው ድጋፍና ፕሮፓጋንዳ እንደሚያቀርቡ ከሰዋል። «ለእነዚህ አሞራዎች መልእክቴ ይህ ነው፤ ከብቱን የምንገዛው እኛ፣ የምንቆራርጠው እኛ ነን፤ እኛ በፈቃዳችን ካልሰጠን በቀር ማንም አሞራ ከጠረጴዛችን ላይ በኃይል ሊወስድ አይችልም» ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ትብብር ለመፍጠር ሁልጊዜም ዝግጁ እንደሆነች ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ነገር ግን አንድነት ያላት ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ትለቃለች ተብሎ መጠበቅ «ከንቱ ተስፋ» እንደሆነ አስምረውበታል።
በሌላ በኩል፣ ሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ኢትዮጵያ ለዘመናት የቆየባትን አለመግባባቶችን በኃይል የመፍታት ባህል በመቀየር በሰላማዊ ውይይት የመፍታት ልምድ የምታዳብርበት እንደሆነ ጠቁመዋል። «የፖለቲካችን በጠንካራ ቃል ይጀምራል፣ በኃይል እርምጃ ያልቃል፤ ይህንን ስብራት በአንዴ ልንፈውሰው ይገባል» ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የምክክር ባህልን ማዳበር የሀገሪቱን አንድነት ከማጠናከሩም በላይ የውጭ ጣልቃ-ገብነትን እንደሚቀንስ ገልጸዋል።
ንግግራቸውን ሲያገባድዱም በጉባኤው ለተሳተፉት ከአራት ሺህ በላይ ታዳሚዎች ባስተላለፉት መልእክት፣ «ስለ ምን ጉዳይ ብንከራከርም በውይይት መፍታት እንችላለን፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለውጭ ኃይሎች የምታሳልፍበት አደገኛ ታሪካዊ አረም ላለመሆን ሁላችንም መጣር አለብን» በማለት ጥሪ አቅርበዋል።
Sponsored by
Surafel
26 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ለቀጣናዊ ሰላም
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
28 days ago
ለቀጣናው ዋስትና እየሆነች ያለች ሀገር
የኢትዮጵያ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ሰብአዊ አቅምን በማስተባበር በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የጎላ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እና በፌደራል ፖሊስ የተገነባው ይህ አስተማማኝ አቅም ቀጣናዊ የሽብር አደጋዎችን እና ሕገ-ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመከላከል ረገድ ለአፍሪካ ቀንድ የማይተካ የደኅንነት ዋስትና ሆኗል።
የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጡ፣ በተለዋዋጭ የደኅንነት ምኅዳር እና በተለያዩ የድንበር ተሻጋሪ አደጋዎች የተከበበ ነው።
በእነዚህ ፈተናዎች መካከል ኢትዮጵያ ታሪካዊ ክብሯን እና የሕዝቦቿን ሰላም ለማስጠበቅ የገነባቻቸው የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት፤ በማንኛውም ዓይነት የውስጥም ሆነ የውጭ ሤራ የማትበገር ጽኑ ሀገር መሆኗን በተግባር እያሳዩ ይገኛሉ።
ተቋማቱ በሰው ኃይልና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አቅም በመገንባታቸው ተልዕኳቸውን በብቃት እየተወጡ ይገኛሉ።
ባለፉት ሀገራዊ የለውጥ ዓመታት ውስጥ መንግሥት ከተገበራቸው የሪፎርም አምዶች አንዱ ጠንካራና ገለልተኛ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማትን መገንባት ነበር።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት በቴክኖሎጂ፣ በመረጃና በሳይበር ሥርዓት የዘመነ አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል።
ሰራዊቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናን ያተረፈ ሲሆን፣ ኢትዮጵያን ለቀጣናው ሀገራት መከታና የሰላም ምሰሶ አድርጓታል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በበኩሉ የቀጣናውን የፀጥታ ሁኔታ በጥልቀት በመተንተን አሸባሪ ቡድኖችና አደገኛ አውታረ መረቦችን ቀድሞ በመምታት ሀገራዊና ቀጣናዊ ሰላምን በማስጠበቅ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስልታዊ ድሮኖችን በመታጠቅ የአየር ክልሉን ፍፁም የማይደፈር አድርጎታል።
የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ደግሞ ኢትዮጵያ በግፍ ወደ ተነጠቀችው የባህር በር ለመመለስና የኢትዮጵያን የወደፊት የኢኮኖሚና የደኅንነት ጥቅም ለመጠበቅ በንቃት ራሱን አደራጅቶ ለተልእኮ እየተዘጋጀ ይገኛል።
በአጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ ለዓለም አቀፍ የሽብር ቡድኖች፣ ለሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያና የሰዎች ዝውውር ተጋላጭ ነው።
የኢትዮጵያ የፀጥታ ተቋማት መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና በማክሸፍ በቀጣናው ላይ ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀርተዋል።
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ሴኪዩሪቲ አሰራሮች ምንም ዓይነት የስጋት ደረጃ እንደሌለባቸው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ያረጋገጠው፣ ተቋማቱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አሳይቷል።
አዳዲስ ጦርነቶች በሳይበር ሥርዓት እና በፈጣን መረጃ ልውውጥ ላይ በተመሰረቱበት በዚህ ዘመን፣ የሀገሪቱ የሳይበር ደኅንነት ተቋማት ሀገራዊና ቀጣናዊ መሠረተ ልማቶችን ከአደጋ በመጠበቅ አስተማማኝ ዋስትና ሆነዋል።
የኢትዮጵያ የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ልማት ከማረጋገጥ ባለፈ ለቀጣናው አፍሪካ ቀንድ የሰላምና መረጋጋት ትልቅ ዋስትና ናቸው።
ተቋማቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በሰለጠነ የሰው ኃይል እና በብቃት በመታገዛቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የፖለቲካና የደኅንነት አጋርነት አጠናክረው የሚያስቀጥሉ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማት ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ሰብአዊ አቅምን በማስተባበር በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ለማስፈን የጎላ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት እና በፌደራል ፖሊስ የተገነባው ይህ አስተማማኝ አቅም ቀጣናዊ የሽብር አደጋዎችን እና ሕገ-ወጥ የሰዎችና የጦር መሳሪያ ዝውውርን በመከላከል ረገድ ለአፍሪካ ቀንድ የማይተካ የደኅንነት ዋስትና ሆኗል።
የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና በጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጡ፣ በተለዋዋጭ የደኅንነት ምኅዳር እና በተለያዩ የድንበር ተሻጋሪ አደጋዎች የተከበበ ነው።
በእነዚህ ፈተናዎች መካከል ኢትዮጵያ ታሪካዊ ክብሯን እና የሕዝቦቿን ሰላም ለማስጠበቅ የገነባቻቸው የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት፤ በማንኛውም ዓይነት የውስጥም ሆነ የውጭ ሤራ የማትበገር ጽኑ ሀገር መሆኗን በተግባር እያሳዩ ይገኛሉ።
ተቋማቱ በሰው ኃይልና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ አቅም በመገንባታቸው ተልዕኳቸውን በብቃት እየተወጡ ይገኛሉ።
ባለፉት ሀገራዊ የለውጥ ዓመታት ውስጥ መንግሥት ከተገበራቸው የሪፎርም አምዶች አንዱ ጠንካራና ገለልተኛ የፀጥታና የደኅንነት ተቋማትን መገንባት ነበር።
የሀገር መከላከያ ሠራዊት በቴክኖሎጂ፣ በመረጃና በሳይበር ሥርዓት የዘመነ አቅም በመገንባት ላይ ይገኛል።
ሰራዊቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናን ያተረፈ ሲሆን፣ ኢትዮጵያን ለቀጣናው ሀገራት መከታና የሰላም ምሰሶ አድርጓታል።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በበኩሉ የቀጣናውን የፀጥታ ሁኔታ በጥልቀት በመተንተን አሸባሪ ቡድኖችና አደገኛ አውታረ መረቦችን ቀድሞ በመምታት ሀገራዊና ቀጣናዊ ሰላምን በማስጠበቅ ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ስልታዊ ድሮኖችን በመታጠቅ የአየር ክልሉን ፍፁም የማይደፈር አድርጎታል።
የኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ደግሞ ኢትዮጵያ በግፍ ወደ ተነጠቀችው የባህር በር ለመመለስና የኢትዮጵያን የወደፊት የኢኮኖሚና የደኅንነት ጥቅም ለመጠበቅ በንቃት ራሱን አደራጅቶ ለተልእኮ እየተዘጋጀ ይገኛል።
በአጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ ለዓለም አቀፍ የሽብር ቡድኖች፣ ለሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያና የሰዎች ዝውውር ተጋላጭ ነው።
የኢትዮጵያ የፀጥታ ተቋማት መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና በማክሸፍ በቀጣናው ላይ ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን አስቀርተዋል።
የኢትዮጵያ አቪዬሽን ሴኪዩሪቲ አሰራሮች ምንም ዓይነት የስጋት ደረጃ እንደሌለባቸው የዓለም አቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ያረጋገጠው፣ ተቋማቱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውን አሳይቷል።
አዳዲስ ጦርነቶች በሳይበር ሥርዓት እና በፈጣን መረጃ ልውውጥ ላይ በተመሰረቱበት በዚህ ዘመን፣ የሀገሪቱ የሳይበር ደኅንነት ተቋማት ሀገራዊና ቀጣናዊ መሠረተ ልማቶችን ከአደጋ በመጠበቅ አስተማማኝ ዋስትና ሆነዋል።
የኢትዮጵያ የደኅንነትና የፀጥታ ተቋማት ሁለንተናዊ አቅም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ ሰላምና ልማት ከማረጋገጥ ባለፈ ለቀጣናው አፍሪካ ቀንድ የሰላምና መረጋጋት ትልቅ ዋስትና ናቸው።
ተቋማቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ፣ በሰለጠነ የሰው ኃይል እና በብቃት በመታገዛቸው ኢትዮጵያ በቀጣናው ያላትን የፖለቲካና የደኅንነት አጋርነት አጠናክረው የሚያስቀጥሉ ናቸው፡፡
30 days ago
የኤርትራ መንግስት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ዛሬ በፓርላማ ቀርበው ለሰጡት ማብራሪያ እና በተለይ ከኤርትራ (ሻዕቢያ)፣ ከሕወሓት እና ከሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ላነሷቸው ነጥቦች በማስታወቂያ ሚኒስቴሩ በኩል ፈጣንና ጠንከር ያለ ምላሽ ሰጥቷል።
ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል።
"የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ነው ሲል ገልጿል።
ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል።
የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች።
Seledadotio
Seledadotio
ሁለቱ ወገኖች በቀጠናው ሰላምና በጎረቤት ሀገራት ጣልቃ ገብነት ዙሪያ እርስ በርሳቸው ተቃራኒ የሆኑ ክሶችን ሰንዝረዋል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ንግግራቸው በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ወጣቶችን በጉልበት እያፈሱ ለሱዳን ጦርነት "እየሸጡ" መሆኑን ገልጸዋል።
"የትግራይ ወጣቶች በማያውቁት ጉዳይ በሱዳን ጦርነት ውስጥ ህይወታቸውን እያጡ ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ድርጊት የህዝቡን መከራ የሚያባብስ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
በተቃራኒው የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ለሱዳን ግጭት መባባስ ተጠያቂው የኢትዮጵያ መንግስት ራሱ ነው ሲል ገልጿል።
ኢትዮጵያ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይሎች (RSF) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈርና ማሰልጠኛ በመስጠት በቀጥታ በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እያደረገች መሆኑንና ለዚህም "ግልጽ ማስረጃዎች አሉ" ሲል አጸፋዊ ክስ ሰንዝሯል።
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በንግግራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም አይነት "ትንኮሳ" ለመመከት መንግስታቸው ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። የኤርትራ መንግስት በበኩሉ፣ ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ህግጋትንና የቀጠናውን ሀገራት ሉዓላዊነት እየጣሰች ያለችው "የባህር በር ባለቤትነት" በሚል በምታሳየው የግዛት ማስፋፋት ፍላጎት ነው ብሏል።
የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ በኩል "ጥቃት አድራሽ" በሌላ በኩል ደግሞ "ተጠቂ" ሆኖ የመቅረብ ድራማ እየሰራ ነው ስትልም ወርፋለች።
Seledadotio
Seledadotio
30 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) እ.ኤ.አ ጁን 2026 በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስተባባሪነት የተቋቋመው “Pulse of Africa” የተሰኘው ሚዲያ አንድ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ተቋም ከአንድ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የዲፕሎማሲ አካዳሚ ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን የሚገልጽ ዜና አውጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ ዜናው ስምምነት ያደረጉትን ተቋማት ስም ሆን ብሎ የደበቀ እና እጅግ አሻሚ ቃላትን የተጠቀመ መሆኑ ከፍተኛ ትኩረት ስቧል። በኤምሬትስ በኩል ያለው ተቋም አንዋር ጋርጋሽ የዲፕሎማሲ አካዳሚ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በኩል ያለው ደግሞ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋዊ የምርምር እና የስልጠና ተቋም የሆነው የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ነበር። ዜናው የተፈረመበትን ሂሊ ክልላዊ የውይይት መድረክ ሳይቀር ዝም ብሎ አንድ ክልላዊ መድረክ በማለት ሸፍኖታል።
በአንጻሩ የኤምሬትሱ ጋርጋሽ አካዳሚ በዲጂታል መድረኮቹ ላይ ስምምነቱን በይፋ እና በዝርዝር አውጥቶታል። የስምምነቱ ዓላማም በሁለቱ ወገኖች መካከል በውጭ ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ምርምር እና ጥናቶችን ማካሄድ፣ ስትራቴጂካዊ ውይይቶችን ማደራጀት፣ የዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን መስጠት እና የባለሙያዎች ልውውጥ ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ክስተት ብዙዎችን ያነጋገረው፣ ሚዲያው የተቋቋመው ስለ አፍሪካ የሚነገሩ አሉታዊ ትርክቶችን ለመቀልበስ እና አህጉሪቱ ከውጭ ሞግዚትነት ነጻ የሆነ የራሷን ትርክት እንድትቀርጽ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ከተናገሩ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ ለኤምሬትስ ጥቅም ሲባል መረጃዎችን መደበቁ ነው።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ዜናውን የደበቀበት ምክንያት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርምር ክንፍ ከኤምሬትስ አካዳሚ የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያገኘ መሆኑን በይፋ ማመኑ፣ መንግስት ከሚገነባው የብሔራዊ ኩራት እና የነጻ ውሳኔ ሰጪነት ትርክት ጋር ስለሚጋጭ ነው።
ይህም የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ግንኙነት ከትብብር አልፎ ወደ ስትራቴጂካዊ ጥገኝነት እያመራ መሆኑን እንደሚያሳይ ባለሙያዎች ይሞግታሉ። ይህ የጥገኝነት መዋቅር በዋናነት የተገነባው በፋይናንስ፣ በወታደራዊ ሎጅስቲክስ እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ነው። በ2018 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ሀገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስትታመስ፣ አቡ ዳቢ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ3 ቢሊዮን ዶላር ተቀማጭ በማድረግ ትልቅ የፋይናንስ ድጋፍ አድርጋለች። በ2021 የትግራይ ጦርነት በተባባሰበት እና የአዲስ አበባ መውደቅ ስጋት በነበረበት ወቅት ደግሞ፣ ኤምሬትስ ድሮኖችን እና ወታደራዊ ትጥቆችን በማቅረብ የጦርነቱን ሚዛን ለመቀልበስ ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። ከዚህም በተጨማሪ በኢነርጂ፣ በግብርና፣ እና የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ከኤምሬትስ ወደብ አስተዳደሮች ጋር በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ተደርጓል።
አሁን የተፈረመው የዲፕሎማሲ ስልጠና ስምምነትም፣ የዚህ ጥገኝነት አራተኛው እና ረቂቁ ምዕራፍ መሆኑ ይገለጻል። ይህም ኤምሬትስ የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲፕሎማት ትውልድ በመቅረጽ እና የውጭ ፖሊሲዋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ በማሳረፍ የረጅም ጊዜ ፍላጎቷን እያስጠበቀች መሆኑን ያመላክታል። በተጨማሪም ባለፈው ጥር ወር ሚድል ኢስት አይ ባወጣው የምርመራ ዘገባ፣ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ አማካሪ የነበሩ ግለሰብን ጠቅሶ፣ ኢትዮጵያ በሱዳን፣ በቀይ ባህር (አሰብ ወደብ)፣ እና በኤርትራ ጉዳይ ላይ ከኤምሬትስ ውጭ የራሷን ነጻ ውሳኔ ማሳለፍ እስኪያቅታት ድረስ ጫና ውስጥ መውደቋን አስነብቧል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጠናው ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ገለልተኛ የውሳኔ ሰጪነት ሚና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው።
በአንጻሩ የኤምሬትሱ ጋርጋሽ አካዳሚ በዲጂታል መድረኮቹ ላይ ስምምነቱን በይፋ እና በዝርዝር አውጥቶታል። የስምምነቱ ዓላማም በሁለቱ ወገኖች መካከል በውጭ ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ምርምር እና ጥናቶችን ማካሄድ፣ ስትራቴጂካዊ ውይይቶችን ማደራጀት፣ የዲፕሎማሲ አቅም ግንባታ ፕሮግራሞችን መስጠት እና የባለሙያዎች ልውውጥ ማድረግ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ክስተት ብዙዎችን ያነጋገረው፣ ሚዲያው የተቋቋመው ስለ አፍሪካ የሚነገሩ አሉታዊ ትርክቶችን ለመቀልበስ እና አህጉሪቱ ከውጭ ሞግዚትነት ነጻ የሆነ የራሷን ትርክት እንድትቀርጽ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋ ከተናገሩ ከአንድ ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ፣ ለኤምሬትስ ጥቅም ሲባል መረጃዎችን መደበቁ ነው።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ዜናውን የደበቀበት ምክንያት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምርምር ክንፍ ከኤምሬትስ አካዳሚ የአቅም ግንባታ ድጋፍ እያገኘ መሆኑን በይፋ ማመኑ፣ መንግስት ከሚገነባው የብሔራዊ ኩራት እና የነጻ ውሳኔ ሰጪነት ትርክት ጋር ስለሚጋጭ ነው።
ይህም የኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ግንኙነት ከትብብር አልፎ ወደ ስትራቴጂካዊ ጥገኝነት እያመራ መሆኑን እንደሚያሳይ ባለሙያዎች ይሞግታሉ። ይህ የጥገኝነት መዋቅር በዋናነት የተገነባው በፋይናንስ፣ በወታደራዊ ሎጅስቲክስ እና በኢኮኖሚያዊ ትስስር ነው። በ2018 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን በመጡበት ወቅት ሀገሪቱ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ስትታመስ፣ አቡ ዳቢ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የ3 ቢሊዮን ዶላር ተቀማጭ በማድረግ ትልቅ የፋይናንስ ድጋፍ አድርጋለች። በ2021 የትግራይ ጦርነት በተባባሰበት እና የአዲስ አበባ መውደቅ ስጋት በነበረበት ወቅት ደግሞ፣ ኤምሬትስ ድሮኖችን እና ወታደራዊ ትጥቆችን በማቅረብ የጦርነቱን ሚዛን ለመቀልበስ ወሳኝ ሚና ተጫውታለች። ከዚህም በተጨማሪ በኢነርጂ፣ በግብርና፣ እና የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ከኤምሬትስ ወደብ አስተዳደሮች ጋር በማስተሳሰር ረገድ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ተደርጓል።
አሁን የተፈረመው የዲፕሎማሲ ስልጠና ስምምነትም፣ የዚህ ጥገኝነት አራተኛው እና ረቂቁ ምዕራፍ መሆኑ ይገለጻል። ይህም ኤምሬትስ የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲፕሎማት ትውልድ በመቅረጽ እና የውጭ ፖሊሲዋ ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ በማሳረፍ የረጅም ጊዜ ፍላጎቷን እያስጠበቀች መሆኑን ያመላክታል። በተጨማሪም ባለፈው ጥር ወር ሚድል ኢስት አይ ባወጣው የምርመራ ዘገባ፣ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ አማካሪ የነበሩ ግለሰብን ጠቅሶ፣ ኢትዮጵያ በሱዳን፣ በቀይ ባህር (አሰብ ወደብ)፣ እና በኤርትራ ጉዳይ ላይ ከኤምሬትስ ውጭ የራሷን ነጻ ውሳኔ ማሳለፍ እስኪያቅታት ድረስ ጫና ውስጥ መውደቋን አስነብቧል። ይህም ኢትዮጵያ በቀጠናው ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ያላትን ገለልተኛ የውሳኔ ሰጪነት ሚና ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው።
1 month ago
ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተነሡ ጥያቄዎች፦
በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል፡
አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ?
የሰላም የጸጥታ እና የፖለቲካ ውድቀት በግልጽ በባለፈው በጀት አመት ታይቷል ይሄንን ለማሻሻል ምን ምን ጉዳዮችን ለመስራት ታቅዷል?
የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን?
የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል?
ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል?
ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው?
መንግስት የተደበቀ እዳን በተመለከተ ያለውን ሁኔታ ለማሳየት ምን ያህል ግልጽነት ይታይበታል ?
የመንግስት የትምህርት ጥራት በተመለከተ የሰራቸው ስራዎቸ ምን ያህል ችግር ቀራፊ ነበሩ ይሄንን ድጋሚ ለመከለስ ምን ምን እቅዶች ተይዘዋል? የሚሉት ይገኙበታል
ከምክር ቤቱ አባላት እየቀረቡ ባሉ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Seledadotio
Seledadotio
በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከተነሱት ጥያቄዎች መካከል፡
አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ?
የሰላም የጸጥታ እና የፖለቲካ ውድቀት በግልጽ በባለፈው በጀት አመት ታይቷል ይሄንን ለማሻሻል ምን ምን ጉዳዮችን ለመስራት ታቅዷል?
የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን?
የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል?
ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል?
ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው?
መንግስት የተደበቀ እዳን በተመለከተ ያለውን ሁኔታ ለማሳየት ምን ያህል ግልጽነት ይታይበታል ?
የመንግስት የትምህርት ጥራት በተመለከተ የሰራቸው ስራዎቸ ምን ያህል ችግር ቀራፊ ነበሩ ይሄንን ድጋሚ ለመከለስ ምን ምን እቅዶች ተይዘዋል? የሚሉት ይገኙበታል
ከምክር ቤቱ አባላት እየቀረቡ ባሉ ጥያቄዎች ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ምላሽ እና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
የቀይ ባሕር ጥሪ እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ትንሳኤ
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቶችና የኃያላን የሽኩቻ መድረክ በሆነው በአፍሪካ ቀንድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ህልውና እና ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከቀይ ባህርና ከባህር በር ጥያቄ ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ነው።
ተፈጥሮና መልክዓ-ምድራዊ እውነታዎች በግልጽ እንደሚያሳዩት ቀይ ባህርና አባይ የዚች ታላቅ ሀገር የደም ስሮች ናቸው።
ከዚህ ተፈጥሯዊ ትስስር ባሻገር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር ህግ አንቀጽ 69 እና 125 የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት በአካባቢያቸው ካለው ባሕር የተፈጥሮ ሀብት እኩል የመጠቀም እና የመሸጋገሪያ አለም አቀፍ መብት እንዳላቸው በግልጽ ይደነግጋል።
ኢትዮጵያ ይህንን ህጋዊና ተፈጥሯዊ መብቷን ለማስከበር ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያከናወናቻቸው ስራዎች የሀገራችን መጻኢ ዕድል አዲስ አቅጣጫ ላይ ያስቀመጣት ሆነዋል።
በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በባህርና ቀጠናዊ ተወዳዳሪነት ዙሪያ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ዋነኛውና ደማቅ ስኬት ሆኖ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ባህር ኃይል እንደገና መመስረቱና መዋቀሩ ነው።
ለሶስት አስርት ዓመታት ተዘንግቶ የነበረውን ይህንን ወሳኝ ዘርፍ በቁርጠኝነት ዳግም በማንሳት የባህር ኃይል አድሚራል በመሾም ተቋማዊ ኃይሏን በተግባር አጠናክራለች።
ይህ ስኬት በምኞት የተገነባ ሳይሆን አለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ አጋርነቶችን በመጠቀም፣ ለባህር ኃይሉ ዘመናዊ ስልጠናና ሁለንተናዊ የቴክኒክ ድጋፍ በማሰባሰብ የተመዘገበ ታላቅ ውጤት ነው።
ይህ ተቋማዊ ትንሳኤ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ኮሪደር ላይ ሊኖራት የሚገባውን ስትራቴጂካዊ ተፅዕኖ እና የተጠቃሚነት ፍላጎት በፅኑ መሠረት ላይ ያቆመ ኩነት ነው።
የተከናወኑት እነዚህ ስራዎች የባህር በር ጉዳይን ከስሜታዊነት በራቀ፣ በጥንቃቄና በመርህ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እሳቤ መሆኑን ለአለም ማህበረሰብ ያሳዩ ናቸው።
10 በመቶ የሚሆነው የአለም ንግድ በሚያልፍበት፣ በዘይትና በከበሩ ማዕድናት በበለፀገው እና በቢሊዮኖች የሚቆጠር የንግድ እንቅስቃሴ በሚስተናገድበት በቀይ ባህር ቀጠና ውስጥ፣ ኢትዮጵያ የነበራትን የጥገኝነት መገለጫ በመቀየር የራሷን የባህር ኃይል መገንባቷ ወደፊት ለሚደረጉ የዲፕሎማሲ ድርድሮች ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
ይህ ስኬት የቀድሞ መሪዎች ስለ አባይ መብት ሲናገሩ "እኔ አቅም የለኝም ልጆቼ ይሰራሉ" እንዳሉት ሁሉ ዛሬ የተጣለው መሠረትም ትውልዱ የቀይ ባህርን መብት በሰላማዊ መንገድና በአለም አቀፍ ህግጋት መሠረት አስከብሮ እንዲረከብ የሚያስችል አርቆ አሳቢ እርምጃ ነው።
ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ ጦር ሳትሰብቅ፣ የወንድማማች ሀገራትን ሉዓላዊነት ሳትደፍር፣ የራሷን ስትራቴጂካዊ ቦታ የምታስከብርበትን መዋቅር የፈጠሩ ናቸው። የባህር ኃይሉ መደራጀት ሀገራችን በአለም አቀፍ የባህር ህግ የተሰጧትን መብቶች በተግባር ለመተርጎም ያላትን ዝግጁነት ያረጋገጠ ሲሆን ለቀጣዩ ትውልድም ከስሜት ነጻ በሆነ መንገድ የተሰላ፣ የታመቀ አቅም እና ብሩህ የባህር በር ተስፋን የጫረ ታሪካዊ ስራ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረቶችና የኃያላን የሽኩቻ መድረክ በሆነው በአፍሪካ ቀንድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ህልውና እና ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከቀይ ባህርና ከባህር በር ጥያቄ ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ነው።
ተፈጥሮና መልክዓ-ምድራዊ እውነታዎች በግልጽ እንደሚያሳዩት ቀይ ባህርና አባይ የዚች ታላቅ ሀገር የደም ስሮች ናቸው።
ከዚህ ተፈጥሯዊ ትስስር ባሻገር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባህር ህግ አንቀጽ 69 እና 125 የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት በአካባቢያቸው ካለው ባሕር የተፈጥሮ ሀብት እኩል የመጠቀም እና የመሸጋገሪያ አለም አቀፍ መብት እንዳላቸው በግልጽ ይደነግጋል።
ኢትዮጵያ ይህንን ህጋዊና ተፈጥሯዊ መብቷን ለማስከበር ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያከናወናቻቸው ስራዎች የሀገራችን መጻኢ ዕድል አዲስ አቅጣጫ ላይ ያስቀመጣት ሆነዋል።
በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ በባህርና ቀጠናዊ ተወዳዳሪነት ዙሪያ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል ዋነኛውና ደማቅ ስኬት ሆኖ የሚጠቀሰው የኢትዮጵያ ባህር ኃይል እንደገና መመስረቱና መዋቀሩ ነው።
ለሶስት አስርት ዓመታት ተዘንግቶ የነበረውን ይህንን ወሳኝ ዘርፍ በቁርጠኝነት ዳግም በማንሳት የባህር ኃይል አድሚራል በመሾም ተቋማዊ ኃይሏን በተግባር አጠናክራለች።
ይህ ስኬት በምኞት የተገነባ ሳይሆን አለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ አጋርነቶችን በመጠቀም፣ ለባህር ኃይሉ ዘመናዊ ስልጠናና ሁለንተናዊ የቴክኒክ ድጋፍ በማሰባሰብ የተመዘገበ ታላቅ ውጤት ነው።
ይህ ተቋማዊ ትንሳኤ ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ኮሪደር ላይ ሊኖራት የሚገባውን ስትራቴጂካዊ ተፅዕኖ እና የተጠቃሚነት ፍላጎት በፅኑ መሠረት ላይ ያቆመ ኩነት ነው።
የተከናወኑት እነዚህ ስራዎች የባህር በር ጉዳይን ከስሜታዊነት በራቀ፣ በጥንቃቄና በመርህ ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እሳቤ መሆኑን ለአለም ማህበረሰብ ያሳዩ ናቸው።
10 በመቶ የሚሆነው የአለም ንግድ በሚያልፍበት፣ በዘይትና በከበሩ ማዕድናት በበለፀገው እና በቢሊዮኖች የሚቆጠር የንግድ እንቅስቃሴ በሚስተናገድበት በቀይ ባህር ቀጠና ውስጥ፣ ኢትዮጵያ የነበራትን የጥገኝነት መገለጫ በመቀየር የራሷን የባህር ኃይል መገንባቷ ወደፊት ለሚደረጉ የዲፕሎማሲ ድርድሮች ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
ይህ ስኬት የቀድሞ መሪዎች ስለ አባይ መብት ሲናገሩ "እኔ አቅም የለኝም ልጆቼ ይሰራሉ" እንዳሉት ሁሉ ዛሬ የተጣለው መሠረትም ትውልዱ የቀይ ባህርን መብት በሰላማዊ መንገድና በአለም አቀፍ ህግጋት መሠረት አስከብሮ እንዲረከብ የሚያስችል አርቆ አሳቢ እርምጃ ነው።
ባለፉት ዓመታት በዘርፉ የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ ጦር ሳትሰብቅ፣ የወንድማማች ሀገራትን ሉዓላዊነት ሳትደፍር፣ የራሷን ስትራቴጂካዊ ቦታ የምታስከብርበትን መዋቅር የፈጠሩ ናቸው። የባህር ኃይሉ መደራጀት ሀገራችን በአለም አቀፍ የባህር ህግ የተሰጧትን መብቶች በተግባር ለመተርጎም ያላትን ዝግጁነት ያረጋገጠ ሲሆን ለቀጣዩ ትውልድም ከስሜት ነጻ በሆነ መንገድ የተሰላ፣ የታመቀ አቅም እና ብሩህ የባህር በር ተስፋን የጫረ ታሪካዊ ስራ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
1 month ago
የኢትዮጵያ የባሕር በር ታሪካዊ መብትና የፍትህ ጥያቄ
******************
የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ከባህር በሮቿ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው ሲሆን፣ ለቀይ ባህር በቀረበች ቁጥር የከፍታ ዘመኗን ስታረጋግጥ ቆይታለች።
የኢትዮጵያ የህልውና ጥያቄ የሆነው የባህር በር ጉዳይ የሌላ ሀገር ግዛት የመውሰድ ጉዳይ አይደለም፤ በፍትሀዊነት መብቷን የመጠየቅ እንጂ፡፡ ለዚህ ማሳያ ደግሞ ከዲፕሎማሲ አንፃር አስፈላጊ አለም አቀፍ ድርጅቶች የተለያዩ መርሆችን አስቀምጠዋል።
በ1982 የፀደቀው የተባበሩት መንግስታት የባህር ሕግ ስምምነት (UNCLOS) የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ወደ ባህር የመድረስና የትራንዚት መብት እንዳላቸው ያስቀምጣል። ሆኖም ይህ መብት በጎረቤት ሀገራት ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በማክበር እንዲፈጸም ይደነግጋል።
የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ የአፍሪካ ሀገራት ሉዓላዊነትና ድንበር መከበርን እያጎላ በተመሳሳይ ጊዜ የክልል ትስስር፣ የንግድ ትብብር እና የጋራ ልማት እንዲጠናከር ያበረታታል።
የመንግስታቱ የልማት ድርጅት (UNCTAD) ደግሞ የባህር በር አልባ ሀገራት ከፍተኛ የመጓጓዣ ወጪ እንደሚሸከሙና ይህም የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚጎዳ ይገልጻል።
የዓለም ባንክም በምሥራቅ አፍሪካ የወደብ ተደራሽነት፣ የባቡር መስመሮች እና የንግድ ኮሪደሮች መጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ እድገት እንደሚያፋጥን ያሳያል።
ኢትዮጵያ ለወደብ አገልግሎት፣ ለትራንስፖርት እና ለሎጂስቲክስ በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮችን የምታወጣ ሲሆን፤ የሕዝብ ቁጥሯ እየጨመረ እና ኢኮኖሚዋ እየሰፋ ባለበት ሁኔታ ደግሞ ይህ ወጪ የበለጠ እየጨመረ ይሄዳል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከ95 በመቶ በላይ የውጭ ንግዷን በጅቡቲ ወደብ በኩል ታከናውናለች። ይህም በአንድ መስመር ላይ ያለ ከፍተኛ ጥገኝነት ነው።
ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ በዓለም ላይ በሕዝብ ብዛት ትልቋ የባህር በር አልባ ሀገር ናት። የራሷ ወደብ ሳይኖራት ለውጭ ንግድ እና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት በጎረቤት ሀገራት ወደቦች ላይ ተመርኩዛ ቆይታለች።
ይህም በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮች የሚያስወጣ ከመሆኑም በላይ የንግድ፣ የኢኮኖሚ፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የቀጠናዊ መረጋጋት ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል።
የባህር በር ማለት አንድ ሀገር ከዓለም አቀፍ የባህር ንግድ መስመሮች ጋር በቀጥታ የምትገናኝበት መዳረሻ ነው።
ዛሬ ከዓለም አቀፍ ንግድ 80 በመቶ በላይ በባህር መንገድ የሚከናወን በመሆኑ፣ ወደብ ለሀገራት የኢኮኖሚ መተንፈሻ በር ተደርጎ ይታያል።
የባህር ማጓጓዣ የአለም ኢኮኖሚ ፍፁም የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየአመቱ ከ11 ቢሊዮን ቶን በላይ ጥሬ እቃዎች፣ ሃይል እና የፍጆታ እቃዎች ይንቀሳቀሳል።
ውቅያኖሶች 70% የሚሆነውን የምድርን ገጽ ስለሚሸፍኑ መርከቦች ከባድ እና ግዙፍ ጭነትን ረጅም ርቀት ለማንቀሳቀስ በጣም ወጪ ቆጣቢ እና ቀልጣፋ መንገድ ይሰጣሉ።
ኢትዮጵያ የባህር ባለቤት ስትሆን ተጠቃሚዋ እሷ ብቻ አትሆንም። የጎረቤት ሀገራት ወደቦች ተጨማሪ ገቢ ያገኛሉ፤ ንግድ ይስፋፋል፤ መሠረተ ልማት ይጠናከራል፤ የቀጠናው የኢኮኖሚ ትስስርም ይጨምራል።
ይህም የዜሮ ድምር ጨዋታ ሳይሆን ሁሉም ተጠቃሚ የሚሆኑበት የጋራ ልማት እድል ነው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፖለቲካ አይደለም፤ የመላው ኢትዮጵያዊ የህልውና ጉዳይ እንጂ። ይህ ጥያቄ በጦርነት ሳይሆን በዲፕሎማሲ፣ በህግ እና በጋራ ጥቅም መርህ ሊመለስ የሚችል ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #seaoutlet #redsea #ethiopiandiplomacy #geopolitics
******************
የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ከባህር በሮቿ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው ሲሆን፣ ለቀይ ባህር በቀረበች ቁጥር የከፍታ ዘመኗን ስታረጋግጥ ቆይታለች።
የኢትዮጵያ የህልውና ጥያቄ የሆነው የባህር በር ጉዳይ የሌላ ሀገር ግዛት የመውሰድ ጉዳይ አይደለም፤ በፍትሀዊነት መብቷን የመጠየቅ እንጂ፡፡ ለዚህ ማሳያ ደግሞ ከዲፕሎማሲ አንፃር አስፈላጊ አለም አቀፍ ድርጅቶች የተለያዩ መርሆችን አስቀምጠዋል።
በ1982 የፀደቀው የተባበሩት መንግስታት የባህር ሕግ ስምምነት (UNCLOS) የባህር በር የሌላቸው ሀገራት ወደ ባህር የመድረስና የትራንዚት መብት እንዳላቸው ያስቀምጣል። ሆኖም ይህ መብት በጎረቤት ሀገራት ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት በማክበር እንዲፈጸም ይደነግጋል።
የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ የአፍሪካ ሀገራት ሉዓላዊነትና ድንበር መከበርን እያጎላ በተመሳሳይ ጊዜ የክልል ትስስር፣ የንግድ ትብብር እና የጋራ ልማት እንዲጠናከር ያበረታታል።
የመንግስታቱ የልማት ድርጅት (UNCTAD) ደግሞ የባህር በር አልባ ሀገራት ከፍተኛ የመጓጓዣ ወጪ እንደሚሸከሙና ይህም የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚጎዳ ይገልጻል።
የዓለም ባንክም በምሥራቅ አፍሪካ የወደብ ተደራሽነት፣ የባቡር መስመሮች እና የንግድ ኮሪደሮች መጠናከር የክልሉን ኢኮኖሚ እድገት እንደሚያፋጥን ያሳያል።
ኢትዮጵያ ለወደብ አገልግሎት፣ ለትራንስፖርት እና ለሎጂስቲክስ በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮችን የምታወጣ ሲሆን፤ የሕዝብ ቁጥሯ እየጨመረ እና ኢኮኖሚዋ እየሰፋ ባለበት ሁኔታ ደግሞ ይህ ወጪ የበለጠ እየጨመረ ይሄዳል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከ95 በመቶ በላይ የውጭ ንግዷን በጅቡቲ ወደብ በኩል ታከናውናለች። ይህም በአንድ መስመር ላይ ያለ ከፍተኛ ጥገኝነት ነው።
ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ በዓለም ላይ በሕዝብ ብዛት ትልቋ የባህር በር አልባ ሀገር ናት። የራሷ ወደብ ሳይኖራት ለውጭ ንግድ እና ለሎጂስቲክስ አገልግሎት በጎረቤት ሀገራት ወደቦች ላይ ተመርኩዛ ቆይታለች።
ይህም በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮች የሚያስወጣ ከመሆኑም በላይ የንግድ፣ የኢኮኖሚ፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የቀጠናዊ መረጋጋት ጉዳይ ሆኖ ቀጥሏል።
የባህር በር ማለት አንድ ሀገር ከዓለም አቀፍ የባህር ንግድ መስመሮች ጋር በቀጥታ የምትገናኝበት መዳረሻ ነው።
ዛሬ ከዓለም አቀፍ ንግድ 80 በመቶ በላይ በባህር መንገድ የሚከናወን በመሆኑ፣ ወደብ ለሀገራት የኢኮኖሚ መተንፈሻ በር ተደርጎ ይታያል።
የባህር ማጓጓዣ የአለም ኢኮኖሚ ፍፁም የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየአመቱ ከ11 ቢሊዮን ቶን በላይ ጥሬ እቃዎች፣ ሃይል እና የፍጆታ እቃዎች ይንቀሳቀሳል።
ውቅያኖሶች 70% የሚሆነውን የምድርን ገጽ ስለሚሸፍኑ መርከቦች ከባድ እና ግዙፍ ጭነትን ረጅም ርቀት ለማንቀሳቀስ በጣም ወጪ ቆጣቢ እና ቀልጣፋ መንገድ ይሰጣሉ።
ኢትዮጵያ የባህር ባለቤት ስትሆን ተጠቃሚዋ እሷ ብቻ አትሆንም። የጎረቤት ሀገራት ወደቦች ተጨማሪ ገቢ ያገኛሉ፤ ንግድ ይስፋፋል፤ መሠረተ ልማት ይጠናከራል፤ የቀጠናው የኢኮኖሚ ትስስርም ይጨምራል።
ይህም የዜሮ ድምር ጨዋታ ሳይሆን ሁሉም ተጠቃሚ የሚሆኑበት የጋራ ልማት እድል ነው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፖለቲካ አይደለም፤ የመላው ኢትዮጵያዊ የህልውና ጉዳይ እንጂ። ይህ ጥያቄ በጦርነት ሳይሆን በዲፕሎማሲ፣ በህግ እና በጋራ ጥቅም መርህ ሊመለስ የሚችል ነው።
በልዩ እሸቱ
#ethiopia #seaoutlet #redsea #ethiopiandiplomacy #geopolitics
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በሆርሙዝ ስትሬት የባህር በር ላይ የተፈጠረው የትራንስፖርት መስተጓጎል የዓለምን የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ በማስወደዱ፣ ታዳጊ ሀገራት በስፋት ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EVs) እንዲያዘነብሉ አስገድዷል። ይህ ሁኔታ በተለይም የቻይና የመኪና አምራቾች በእስያ እና በአፍሪካ ገበያዎች ላይ ያላቸውን ተጽዕኖ በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
አዲሱን የነዳጅ ቀውስ ተከትሎ የቻይና የኤሌክትሪክ መኪኖች ኤክስፖርት በሚያዝያ ወር ክብረ ወሰን በመስበር 9.4 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ በግንቦት ወር ብቻ ከ435 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን ወደ ተለያዩ ሀገራት ልካለች። በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚሸጡ የኤሌክትሪክ መኪኖች ውስጥ 60 በመቶውን የምታቀርበው ቻይና ስትሆን፣ የነዳጅ ወጪን ለመቀነስ ሲሉ እንደ ላኦስ እና ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እገዳ እስከመጣል የሚደርስ ፖሊሲ ተግባራዊ አድርገዋል።
የኤሌክትሪክ መኪኖች ግዢ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ቢመጣም፣ ተሽከርካሪዎቹን ቻርጅ ለማድረግ የሚያስችል በቂ የመሰረተ ልማት አቅርቦት አለመኖሩ ትልቅ ፈተና ሆኗል። ባለሙያዎች እንደሚሉት ይህ "የዶሮ እና እንቁላል" አይነት ችግር ሲሆን፣ ተሽከርካሪዎቹ ከቻርጅንግ ጣቢያዎቹ እጅግ ፈጥነው በመበራከታቸው አሽከርካሪዎች ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ።
ይህንን ችግር ለመፍታት በአፍሪካ እና በእስያ የሚገኙ የመንግስት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋማት የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን የመገንባቱን ኃላፊነት በስፋት እየወሰዱ ነው። ለአብነት ያህል፣ ነዳጅ የሚጠቀሙ መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ያገደችው ኢትዮጵያ፣ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ፍላጎት ለማሟላት ከ1,170 በላይ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንደሚያስፈልጓት የገመተች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ 40 ጣቢያዎች በግንባታ ላይ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው የመንግስት ተቋም ከ4,500 በላይ ጣቢያዎችን የገነባ ሲሆን፣ የኬንያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበኩሉ በቀጣዩ ዓመት 44 የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ማቀዱ ተገልጿል።
በአጠቃላይ የነዳጅ ዋጋ መናር ታዳጊ ሀገራትን በፍጥነት ከነዳጅ ጥገኝነት እያላቀቃቸው ቢሆንም፣ የሽግግሩ ስኬት ግን ሀገራቱ በሚገነቡት የኤሌክትሪክ ኃይል እና የቻርጅንግ መሰረተ ልማት ጥንካሬ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ እንደሚሆን ተንታኞች ያስገነዝባሉ።
አዲሱን የነዳጅ ቀውስ ተከትሎ የቻይና የኤሌክትሪክ መኪኖች ኤክስፖርት በሚያዝያ ወር ክብረ ወሰን በመስበር 9.4 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን፣ በግንቦት ወር ብቻ ከ435 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን ወደ ተለያዩ ሀገራት ልካለች። በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚሸጡ የኤሌክትሪክ መኪኖች ውስጥ 60 በመቶውን የምታቀርበው ቻይና ስትሆን፣ የነዳጅ ወጪን ለመቀነስ ሲሉ እንደ ላኦስ እና ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እገዳ እስከመጣል የሚደርስ ፖሊሲ ተግባራዊ አድርገዋል።
የኤሌክትሪክ መኪኖች ግዢ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ቢመጣም፣ ተሽከርካሪዎቹን ቻርጅ ለማድረግ የሚያስችል በቂ የመሰረተ ልማት አቅርቦት አለመኖሩ ትልቅ ፈተና ሆኗል። ባለሙያዎች እንደሚሉት ይህ "የዶሮ እና እንቁላል" አይነት ችግር ሲሆን፣ ተሽከርካሪዎቹ ከቻርጅንግ ጣቢያዎቹ እጅግ ፈጥነው በመበራከታቸው አሽከርካሪዎች ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ።
ይህንን ችግር ለመፍታት በአፍሪካ እና በእስያ የሚገኙ የመንግስት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ ተቋማት የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን የመገንባቱን ኃላፊነት በስፋት እየወሰዱ ነው። ለአብነት ያህል፣ ነዳጅ የሚጠቀሙ መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ያገደችው ኢትዮጵያ፣ እያደገ የመጣውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ፍላጎት ለማሟላት ከ1,170 በላይ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች እንደሚያስፈልጓት የገመተች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ 40 ጣቢያዎች በግንባታ ላይ ይገኛሉ።
በተመሳሳይ የኢንዶኔዥያው የመንግስት ተቋም ከ4,500 በላይ ጣቢያዎችን የገነባ ሲሆን፣ የኬንያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበኩሉ በቀጣዩ ዓመት 44 የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ማቀዱ ተገልጿል።
በአጠቃላይ የነዳጅ ዋጋ መናር ታዳጊ ሀገራትን በፍጥነት ከነዳጅ ጥገኝነት እያላቀቃቸው ቢሆንም፣ የሽግግሩ ስኬት ግን ሀገራቱ በሚገነቡት የኤሌክትሪክ ኃይል እና የቻርጅንግ መሰረተ ልማት ጥንካሬ ላይ በእጅጉ የተመሰረተ እንደሚሆን ተንታኞች ያስገነዝባሉ።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዱራህማን መሀመድ አብዱላሂ (ኢሮ)፣ አስተዳደራቸው ተጨማሪ ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት በማለም ከአሜሪካ እና ከኢትዮጵያ ጋር ክፍት የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንዳለው አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት በኢየሩሳሌም ከሚገኘው 'አይ24ኒውስ' የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ነው። የፕሬዝዳንት ኢሮ ይፋዊ ጉብኝት፣ እስራኤል ባለፈው ዓመት መገባደጃ ላይ ለሶማሌላንድ ይፋዊ እውቅና መስጠቷን ተከትሎ የተካሄደ ነው።
የዲፕሎማሲያዊ እውቅናን በተመለከተ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ስላላቸው የግንኙነት መስመር ተጠይቀው፣ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ "ክፍት የሆኑ የግንኙነት መስመሮች አሉን" ሲሉ መልሰዋል። አክለውም እንደ ኢትዮጵያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ኬንያ የመሳሰሉ የቀጠናው አገራት አሁንም የሃርጌሳ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቀዳሚ ትኩረቶች መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "አዎ ናቸው፤ ለእነሱም ቢሆን ክፍት የግንኙነት መስመሮች አሉን" ብለዋል።
ይህ የዲፕሎማሲያዊ ግፊት የሚመጣው ሶማሌላንድ በእስራኤል ህልውናዋን እያጠናከረች ባለችበት ወቅት ነው። ፕሬዝዳንቱ በቃለ ምልልሳቸው የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት በማንሳት፣ ሶማሌላንድ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻ በወጣችበት እ.ኤ.አ ሰኔ 26 ቀን 1960 እስራኤል እውቅና ሰጥታት እንደነበር አስታውሰዋል።
በግንቦት 2025 ሃርጌሳ ለ193 አገራት በጻፈችው ጥያቄ መሰረት፣ እስራኤል በታህሳስ 26 ቀን 2025 ለሶማሌላንድ ለሁለተኛ ጊዜ እውቅና ሰጥታለች። ፕሬዝዳንት አብዱላሂ እንዳሉት፣ እስራኤል የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ውሳኔዎቿን በቀጠናዊ እውነታዎች ላይ በመመስረት ለጥያቄው ምላሽ የሰጠች ብቸኛ አገር ሆናለች። በመሆኑም ሃርጌሳ ስትራቴጂዋን ለማስፈጸም በኢየሩሳሌም ኤምባሲዋን እየከፈተች ሲሆን፣ በአንጻሩ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ቀንድ የንግድ በር የሆነውን የበርበራ ወደብ መጠቀም የሚያስችል እድል እያቀረበች ትገኛለች።
ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ሶማሌላንድ "ከሶማሊያ የተገነጠለች ክልል ነች" ተብላ የምትጠራበትን አገላለጽ ውድቅ በማድረግ፣ ግዛቷ በ1960 ሶማሊያ መንግስት ከመመስረቷ በፊት የራሷን ሉዓላዊነት ተቀዳጅታ እንደነበር ሞግተዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የባህር በር ተደራሽነትን እና የፖለቲካ እውቅናን ያካተተ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) እ.ኤ.አ ጥር 1 ቀን 2024 መፈራረማቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ከአፍሪካ ህብረት እየጨመረ የመጣው ቀጠናዊ የዲፕሎማሲ ጫና፣ እንዲሁም በአንካራው ስምምነት መሰረት በቱርክ አሸማጋይነት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተካሄደው ድርድር የስምምነቱን ትግበራ አግዶታል። ይህ ሁኔታ ኢትዮጵያን የቀይ ባህር ተደራሽነት ለማግኘት ሌሎች ስትራቴጂካዊ አማራጮችን እንድትመረምር አስገድዷታል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት በኢየሩሳሌም ከሚገኘው 'አይ24ኒውስ' የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ነው። የፕሬዝዳንት ኢሮ ይፋዊ ጉብኝት፣ እስራኤል ባለፈው ዓመት መገባደጃ ላይ ለሶማሌላንድ ይፋዊ እውቅና መስጠቷን ተከትሎ የተካሄደ ነው።
የዲፕሎማሲያዊ እውቅናን በተመለከተ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ስላላቸው የግንኙነት መስመር ተጠይቀው፣ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ "ክፍት የሆኑ የግንኙነት መስመሮች አሉን" ሲሉ መልሰዋል። አክለውም እንደ ኢትዮጵያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና ኬንያ የመሳሰሉ የቀጠናው አገራት አሁንም የሃርጌሳ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ቀዳሚ ትኩረቶች መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "አዎ ናቸው፤ ለእነሱም ቢሆን ክፍት የግንኙነት መስመሮች አሉን" ብለዋል።
ይህ የዲፕሎማሲያዊ ግፊት የሚመጣው ሶማሌላንድ በእስራኤል ህልውናዋን እያጠናከረች ባለችበት ወቅት ነው። ፕሬዝዳንቱ በቃለ ምልልሳቸው የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት በማንሳት፣ ሶማሌላንድ ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ነጻ በወጣችበት እ.ኤ.አ ሰኔ 26 ቀን 1960 እስራኤል እውቅና ሰጥታት እንደነበር አስታውሰዋል።
በግንቦት 2025 ሃርጌሳ ለ193 አገራት በጻፈችው ጥያቄ መሰረት፣ እስራኤል በታህሳስ 26 ቀን 2025 ለሶማሌላንድ ለሁለተኛ ጊዜ እውቅና ሰጥታለች። ፕሬዝዳንት አብዱላሂ እንዳሉት፣ እስራኤል የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ውሳኔዎቿን በቀጠናዊ እውነታዎች ላይ በመመስረት ለጥያቄው ምላሽ የሰጠች ብቸኛ አገር ሆናለች። በመሆኑም ሃርጌሳ ስትራቴጂዋን ለማስፈጸም በኢየሩሳሌም ኤምባሲዋን እየከፈተች ሲሆን፣ በአንጻሩ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ቀንድ የንግድ በር የሆነውን የበርበራ ወደብ መጠቀም የሚያስችል እድል እያቀረበች ትገኛለች።
ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ሶማሌላንድ "ከሶማሊያ የተገነጠለች ክልል ነች" ተብላ የምትጠራበትን አገላለጽ ውድቅ በማድረግ፣ ግዛቷ በ1960 ሶማሊያ መንግስት ከመመስረቷ በፊት የራሷን ሉዓላዊነት ተቀዳጅታ እንደነበር ሞግተዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በተመለከተ፣ ኢትዮጵያ እና ሶማሌላንድ የባህር በር ተደራሽነትን እና የፖለቲካ እውቅናን ያካተተ የመግባቢያ ስምምነት (MoU) እ.ኤ.አ ጥር 1 ቀን 2024 መፈራረማቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ከአፍሪካ ህብረት እየጨመረ የመጣው ቀጠናዊ የዲፕሎማሲ ጫና፣ እንዲሁም በአንካራው ስምምነት መሰረት በቱርክ አሸማጋይነት በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል የተካሄደው ድርድር የስምምነቱን ትግበራ አግዶታል። ይህ ሁኔታ ኢትዮጵያን የቀይ ባህር ተደራሽነት ለማግኘት ሌሎች ስትራቴጂካዊ አማራጮችን እንድትመረምር አስገድዷታል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢራን የሆርሙዝ ስትሬትን መዝጋቷን አስታወቀች በአሜሪካ እና በእስራኤል በኩል የተቃውሞ ምላሽ ተሰጥቷል
ኢራን በዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያለውና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላትን የሆርሙዝ የባህር በር (Strait of Hormuz) ሙሉ በሙሉ መዝጋቷን አስታወቀች።
ቴህራን ለዚህ ውሳኔዋ እንደ ምክንያት የጠቀሰችው እስራኤል በሊባኖስ ውስጥ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሳለች የሚል እና አሜሪካ በሁለቱ አገራት መካከል የተደረሰውን ጊዜያዊ የሰላም ስምምነት የመጀመሪያ አንቀጽ ተግባራዊ ሳታደርግ ቀርታለች የሚል ነው።
ሆኖም የአሜሪካ ጦር የኢራንን የባህር በር የመቆጣጠር ይገባኛል ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ባወጣው መግለጫ ኢራን የሆርሙዝ የባህር በርን የመቆጣጠር ስልጣን እንደሌላትና በዓለም አቀፉ የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ ያለምንም መስተጓጎል እንዲቀጥል እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የሰላም ንግግሩ እና የቪፒ ጄዲ ቫንስ ወደ ስዊዘርላንድ መጓዝ
ይህ ውጥረት በተፈጠረበት ወቅት የቴህራን እና የዋሽንግተን ባለስልጣናት በስዊዘርላንድ በሚደረገው የሰላም ድርድር ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የአሜሪካውን የልዑካን ቡድን ለመምራትም ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ቅዳሜ ዕለት ወደ ስዊዘርላንድ ተጉዘዋል።
አስታራቂ ወገኖች ውይይቱ ሳይሰናከል እንዲቀጥልና በመጀመሪያው ስምምነት በተቀመጠው የ60 ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ ዘላቂ የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ተስፋ አድርገዋል።
በሊባኖስ የቀጠለው የአየር ጥቃት የዲፕሎማሲውን ሂደት ስጋት ላይ ጥሎታል
በእስራኤል ጦር እና በሄዝቦላህ መካከል የቀጠለው አስከፊ ውጊያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ ላይ ትልቅ ስጋት ደቅኗል።
በደቡባዊ ሊባኖስ ላይ እስራኤል በሰነዘረችው አዲስ የአየር ጥቃት ቢያንስ 16 ሰዎች መገደላቸው ተረጋግጧል።
እስራኤል ጥቃቱን የሰነዘረችው ሄዝቦላህ አስቀድሞ ላደረገው ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጻለች። ይህ ቀጣይነት ያለው ግጭትም አገራቱ የደረሱበትን የሰላም ሂደት ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይወስደው ተሰግቷል።
ኢራን በዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያለውና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላትን የሆርሙዝ የባህር በር (Strait of Hormuz) ሙሉ በሙሉ መዝጋቷን አስታወቀች።
ቴህራን ለዚህ ውሳኔዋ እንደ ምክንያት የጠቀሰችው እስራኤል በሊባኖስ ውስጥ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሳለች የሚል እና አሜሪካ በሁለቱ አገራት መካከል የተደረሰውን ጊዜያዊ የሰላም ስምምነት የመጀመሪያ አንቀጽ ተግባራዊ ሳታደርግ ቀርታለች የሚል ነው።
ሆኖም የአሜሪካ ጦር የኢራንን የባህር በር የመቆጣጠር ይገባኛል ጥያቄ ውድቅ አድርጓል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ባወጣው መግለጫ ኢራን የሆርሙዝ የባህር በርን የመቆጣጠር ስልጣን እንደሌላትና በዓለም አቀፉ የውሃ መስመር ላይ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ ያለምንም መስተጓጎል እንዲቀጥል እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የሰላም ንግግሩ እና የቪፒ ጄዲ ቫንስ ወደ ስዊዘርላንድ መጓዝ
ይህ ውጥረት በተፈጠረበት ወቅት የቴህራን እና የዋሽንግተን ባለስልጣናት በስዊዘርላንድ በሚደረገው የሰላም ድርድር ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የአሜሪካውን የልዑካን ቡድን ለመምራትም ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ቅዳሜ ዕለት ወደ ስዊዘርላንድ ተጉዘዋል።
አስታራቂ ወገኖች ውይይቱ ሳይሰናከል እንዲቀጥልና በመጀመሪያው ስምምነት በተቀመጠው የ60 ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ ዘላቂ የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ተስፋ አድርገዋል።
በሊባኖስ የቀጠለው የአየር ጥቃት የዲፕሎማሲውን ሂደት ስጋት ላይ ጥሎታል
በእስራኤል ጦር እና በሄዝቦላህ መካከል የቀጠለው አስከፊ ውጊያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ ላይ ትልቅ ስጋት ደቅኗል።
በደቡባዊ ሊባኖስ ላይ እስራኤል በሰነዘረችው አዲስ የአየር ጥቃት ቢያንስ 16 ሰዎች መገደላቸው ተረጋግጧል።
እስራኤል ጥቃቱን የሰነዘረችው ሄዝቦላህ አስቀድሞ ላደረገው ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጻለች። ይህ ቀጣይነት ያለው ግጭትም አገራቱ የደረሱበትን የሰላም ሂደት ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይወስደው ተሰግቷል።
2 months ago
ሰላም፣ ደህና አደራችሁ?
ታሪክና መልክዓ ምድር ያቆራኛቸው የኢትዮጵያና የቀይ ባሕር ግንኙነት ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ቢሆንም፣ ከቅርብ አሥርት ዓመታት ወዲህ ግን ይህ እውነታ ተቀይሮ ቆይቷል።
በታሪካዊ ስሕተቶችና በሴራ መንገዶች የባሕር በሯን ያጣችው ኢትዮጵያ ጉዳዩን ማንሳት እንኳን እንደ ነውር ወደሚቆጠርበት የስነ-ልቦና ስብራት ውስጥ ገብታ ነበር።
ይህ ሁኔታ ሀገሪቱ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ አድርጓታል።
ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የባሕር በር ጉዳይ ከነበረበት የመዘንጋት አዙሪት ወጥቶ የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ አጀንዳ ወደ መሆን ተሸጋግሯል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለት ውሃዎች (የዓባይ ወንዝ እና የቀይ ባሕር) ፖሊሲን ይፋ በማድረግ ይህንን ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አዳዲስና ቁርጠኛ እንቅስቃሴዎች በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ይሁንታ እየተቸረው ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይን የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ሀገራዊ አጀንዳ እንዲሆን በማድረግ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት እንዲቆሙ መንገድ ጠርገዋል።
የኢትዮጵያን ዕጣ ፈንታ የሚበይኑትን የዓባይ ወንዝ እና የቀይ ባሕር ጉዳይን በተመለከተ የሁለት ውሃዎች ፖሊሲን ይፋ አድርገው ኢትዮጵያ በሴራ ያጣችውን የባሕር በር በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማስመለስ የሚያስችል እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገባ የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል።
ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ተዋሳኝነቷን ስታጣ በሰነድ የተደገፈ ምንም ዓይነት ማስረጃ አለመኖሩ ውሳኔው ሕጋዊ እንዳልሆነ እና ኢትዮጵያ በብዙዎች ርብርብ የባሕር በር ማጣቷን ያሳያል።
በባህር በር ጉዳይ መጠየቅ ነውርና ትክክል እንዳልሆነ የሚመለከት ትርክት በመፈጠር የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ለመጋረድ ቢሞክርም አሁን ላይ በሰከነ መንገድ በውይይት የባሕር በር ማግኘት እንደሚቻል ግልጽ እየሆነ መጥቷል።
5 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የቀይ ባሕር ከ20 ሚሊየን የማይበልጥ ህዝብ ባላቸው ሀገራት መሸፈኑ ፍትሃዊ አለመሆን፥ ቀይ ባሕር እና ኢትዮጵያ ለዘለዓለሙ ተነጣጥለው መኖር እንደማይችሉ የሚያመላክት ነው።
130 ሚሊየን ሕዝብ የያዘችው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ድርሻ ሊኖራት ግድ በመሆኑ ብሔራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን ለማረጋገጥ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ማግኘት አለበት።
ለዚህ ደግሞ መፍትሔው ጦርነት ሳይሆን ውይይትና ዲፕሎማሲ ቀዳሚው አማራጭ ሆኖ በስፋት እየተሰራበት ይገኛል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች መካከል የአሰብ ወደብን ለማልማት በተደጋጋሚ ንግግር ቢደረግም ከኤርትራ መንግሥት በኩል ምላሽ ለመስጠት ዝግጁነት የለም።
የባሕር በር ጉዳይ በውይይት እንዲሁም በገበያ ህግ ድርድር እልባት እንዲያገኝ አቋም ያላት ኢትዮጵያ፤ የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ማንም ፈለገም አልፈለገም ኢትዮጵያ ተዘግታ አትኖርም።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅምና የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ ለጥያቄው ምላሽ ማግኘት ሁሉም ኢትዮጵያውያን የቤት ስራ አለባቸው።
ታሪክና መልክዓ ምድር ያቆራኛቸው የኢትዮጵያና የቀይ ባሕር ግንኙነት ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረ ቢሆንም፣ ከቅርብ አሥርት ዓመታት ወዲህ ግን ይህ እውነታ ተቀይሮ ቆይቷል።
በታሪካዊ ስሕተቶችና በሴራ መንገዶች የባሕር በሯን ያጣችው ኢትዮጵያ ጉዳዩን ማንሳት እንኳን እንደ ነውር ወደሚቆጠርበት የስነ-ልቦና ስብራት ውስጥ ገብታ ነበር።
ይህ ሁኔታ ሀገሪቱ ለከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና ለደህንነት ስጋት እንድትጋለጥ አድርጓታል።
ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የባሕር በር ጉዳይ ከነበረበት የመዘንጋት አዙሪት ወጥቶ የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ አጀንዳ ወደ መሆን ተሸጋግሯል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የሁለት ውሃዎች (የዓባይ ወንዝ እና የቀይ ባሕር) ፖሊሲን ይፋ በማድረግ ይህንን ታሪካዊ፣ ሕጋዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ በሰላማዊና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት አዳዲስና ቁርጠኛ እንቅስቃሴዎች በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ይሁንታ እየተቸረው ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይን የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ሀገራዊ አጀንዳ እንዲሆን በማድረግ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት እንዲቆሙ መንገድ ጠርገዋል።
የኢትዮጵያን ዕጣ ፈንታ የሚበይኑትን የዓባይ ወንዝ እና የቀይ ባሕር ጉዳይን በተመለከተ የሁለት ውሃዎች ፖሊሲን ይፋ አድርገው ኢትዮጵያ በሴራ ያጣችውን የባሕር በር በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማስመለስ የሚያስችል እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገባ የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል።
ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ተዋሳኝነቷን ስታጣ በሰነድ የተደገፈ ምንም ዓይነት ማስረጃ አለመኖሩ ውሳኔው ሕጋዊ እንዳልሆነ እና ኢትዮጵያ በብዙዎች ርብርብ የባሕር በር ማጣቷን ያሳያል።
በባህር በር ጉዳይ መጠየቅ ነውርና ትክክል እንዳልሆነ የሚመለከት ትርክት በመፈጠር የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን ለመጋረድ ቢሞክርም አሁን ላይ በሰከነ መንገድ በውይይት የባሕር በር ማግኘት እንደሚቻል ግልጽ እየሆነ መጥቷል።
5 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የቀይ ባሕር ከ20 ሚሊየን የማይበልጥ ህዝብ ባላቸው ሀገራት መሸፈኑ ፍትሃዊ አለመሆን፥ ቀይ ባሕር እና ኢትዮጵያ ለዘለዓለሙ ተነጣጥለው መኖር እንደማይችሉ የሚያመላክት ነው።
130 ሚሊየን ሕዝብ የያዘችው ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ድርሻ ሊኖራት ግድ በመሆኑ ብሔራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን ለማረጋገጥ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ማግኘት አለበት።
ለዚህ ደግሞ መፍትሔው ጦርነት ሳይሆን ውይይትና ዲፕሎማሲ ቀዳሚው አማራጭ ሆኖ በስፋት እየተሰራበት ይገኛል።
ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች መካከል የአሰብ ወደብን ለማልማት በተደጋጋሚ ንግግር ቢደረግም ከኤርትራ መንግሥት በኩል ምላሽ ለመስጠት ዝግጁነት የለም።
የባሕር በር ጉዳይ በውይይት እንዲሁም በገበያ ህግ ድርድር እልባት እንዲያገኝ አቋም ያላት ኢትዮጵያ፤ የባሕር በር የማግኘቷ ጉዳይ አይቀሬ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ማንም ፈለገም አልፈለገም ኢትዮጵያ ተዘግታ አትኖርም።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅምና የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ ለጥያቄው ምላሽ ማግኘት ሁሉም ኢትዮጵያውያን የቤት ስራ አለባቸው።
2 months ago
ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠረ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ለመቀጠል ካይሮ ገቡ
የኔታ ሚዲያ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ወደ ግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ አቅንተዋል።
ይህ ጉዞ ግብፅ እና ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በኢትዮጵያ ላይ የጀመሩትን የዲፕሎማሲ እና የደህንነት ከበባ ይበልጥ ለማጥበቅ የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹት ይገኛሉ።
የኤርትራ ማዕከላዊ መረጃ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ በካይሮ ቆይታቸው ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ትብብር በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ይመክራሉ።
ይሁን እንጂ የሁለቱ መሪዎች የውይይት ማዕከል የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ የሱዳን ቀውስ እና የቀይ ባህር ደህንነት መሆናቸው ተገልጿል።
ይህም ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና ለማገዝ እና ኢትዮጵያ በቅርቡ ያደረገችውን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ጥረት በጋራ ለመቃወም የተወጠነ ስልታዊ ሴራ እንደሆነ በስፋት እየተነገረ ነው።
ካይሮ እና አስመራ ከዚህ ቀደም ከሞቃዲሾ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ የሶስትዮሽ ጥምረት መፍጠራቸው የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስብሰባም ይሄንኑ የኃይል አሰላለፍ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በተለይም "የቀይ ባህር ደህንነት ጥበቃ የባህር ዳርቻው ባለቤት ለሆኑ ሀገራት ብቻ የተተወ መሆን አለበት" በሚል የሚያነሱት አቋም የኢትዮጵያን ስልታዊ ጥቅም እና የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት ያላገናዘበ ይልቁንም ለአካባቢው አለመረጋጋት በር የሚከፍት አካሄድ መሆኑን ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
የኔታ ሚዲያ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ወደ ግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ አቅንተዋል።
ይህ ጉዞ ግብፅ እና ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በኢትዮጵያ ላይ የጀመሩትን የዲፕሎማሲ እና የደህንነት ከበባ ይበልጥ ለማጥበቅ የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹት ይገኛሉ።
የኤርትራ ማዕከላዊ መረጃ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ በካይሮ ቆይታቸው ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ትብብር በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ይመክራሉ።
ይሁን እንጂ የሁለቱ መሪዎች የውይይት ማዕከል የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ የሱዳን ቀውስ እና የቀይ ባህር ደህንነት መሆናቸው ተገልጿል።
ይህም ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና ለማገዝ እና ኢትዮጵያ በቅርቡ ያደረገችውን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ጥረት በጋራ ለመቃወም የተወጠነ ስልታዊ ሴራ እንደሆነ በስፋት እየተነገረ ነው።
ካይሮ እና አስመራ ከዚህ ቀደም ከሞቃዲሾ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ የሶስትዮሽ ጥምረት መፍጠራቸው የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስብሰባም ይሄንኑ የኃይል አሰላለፍ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በተለይም "የቀይ ባህር ደህንነት ጥበቃ የባህር ዳርቻው ባለቤት ለሆኑ ሀገራት ብቻ የተተወ መሆን አለበት" በሚል የሚያነሱት አቋም የኢትዮጵያን ስልታዊ ጥቅም እና የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት ያላገናዘበ ይልቁንም ለአካባቢው አለመረጋጋት በር የሚከፍት አካሄድ መሆኑን ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
2 months ago
"ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች"
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የእጥፋት ዘመን፡ የኢትዮጵያ መጪው አምስት ዓመታት
***************
( የዕለቱ መልዕክት)
በታሪካዊ እጥፋቶችና ስር በሰደዱ መዋቅራዊ ማነቆዎች ውስጥ ስትመላለስ የኖረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ከትናንት የዳተኝነት ቀንበር ተላቃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለመሻገር የሚያስችላትን ታሪካዊ መሠረት ጥላለች። የሀገራችን የልማትና የለውጥ ጉዞ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ የጥርጣሬና የፈተና ድንጋዮች ቢወረወሩበትም ዛሬ ግን ኢትዮጵያ በፈጣን እና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር ሂደት ውስጥ ትገኛለች።
ለብዙ አስርት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ የቆየውን ባህላዊ የግብርና መር ሞዴል ወደ ላቀ የኢንዱስትሪ፣ የቴክኖሎጂ እና የአገልግሎት ዘርፍ ለማሸጋገር የተነደፉት ግዙፍና ሁለንተናዊ የልማት ፕሮጀክቶች መሬት በመያዝ ላይ ናቸው።
ይህ ስልታዊ እርምጃ ተራ የድንጋይና የኮንክሪት ክምችት ሳይሆን የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ስር የሰደደውን የንግድ ሚዛን መዛባት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማስፈን የታለመ የሉዓላዊነት ማህተም ነው።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለች ብትሆንም የኢኮኖሚ ዕድገቷን የገደቡ ሦስት ዋና ዋና መዋቅራዊ እጥረቶች ነበሩባት። የመጀመሪያው ወደ ውጭ ከምትልካቸው ጥሬ የግብርና ምርቶች የምታገኘው ገቢና ለውጭ መሠረታዊ ቁሳቁሶች የምታወጣው ወጪ አለመመጣጠን የወለደው የንግድ ሚዛን መዛባት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው።
ሁለተኛው ብሔራዊ የምግብ ዋስትናን ሁልጊዜም ለአደጋ የሚያጋልጠውና በየዓመቱ ከዓለም አቀፍ ገበያ በሚመጣ ማዳበሪያ ላይ የተንጠለጠለው የግብርና ዘርፍ የውጭ ጥገኝነት ነው።
ሦስተኛውና ታሪካዊው ተግዳሮት ደግሞ የባህር በር ማጣት ያስከተለው የሎጂስቲክስ ጫና እና ከአንድ የጅቡቲ ወደብ ኮሪደር ጋር ብቻ መተሳሰር የፈጠረው የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ነው። እነዚህን ስር የሰደዱ ችግሮች ለመቅረፍ ባለፉት ዓመታት በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጪ አስመጪነት ወደ ላኪነት የተደረገው ሽግግር፣ “የማይሞቅ ፍም አይነድም፣ የማይሆን ነገር አይሆንም” የሚሉትን የጥርጣሬ ድምፆች በተግባር ያፈረሰ ተምሳሌታዊ ስኬት ሆኗል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ከሰጡ በኋላ እንዳመለከቱት መጪው አምስት ዓመት የኢትዮጵያ በርካታ የታሪክ እጥፋት የሚታይበት ዘመን ነው።
"የትናንትናዋን ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አምስት ዓመት አናያትም። የተቀየረች፣ የተለወጠች፣ ቢያንስ የማትለምን፣ ራሷን ችላ የምትቆም፣ በቀጠናው መልህቅ የሆነች አገር ለማየት ብዙ ልፋት ይፈልጋል" ማለታቸው የዚህን ሽግግር ጥልቀትና የሚጠይቀውን ብሔራዊ ቁርጠኝነት ያሳያል።
በመሆኑም መጪው አምስት ዓመት የምክንያትና የውጤት ትስስር የሚታይበት፣ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩት ስልታዊና ትላልቅ ስራዎች ፍሬ የሚያፈሩበት ወርቃማ ምዕራፍ ይሆናል።
በዚህም መሠረት በኃይልና ታዳሽ ኢነርጂ ዘርፍ እንደ የኮይሻ ሃይድሮ-ኤሌክትሪክ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የቀጠናዉ የኃይል ማማ ከማድረግ ባለፈ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት አስተማማኝና ርካሽ ግብዓት ይፈጥራል።
በፔትሮ-ኬሚካልና ማምረቻ ዘርፍ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝና የሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ፋብሪካ ስራ መጀመር የግብርናውን ዘርፍ ከውጭ ጥገኝነት በማላቀቅ የውጭ ምንዛሬን በከፍተኛ ሁኔታ ይታደጋል። በአቪዬሽንና ግሎባል ትራንስፖርት ዘርፍ አዲሱ የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ግንባታ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የሎጂስቲክስና የትራንዚት ማእከልነቷን ያጠናክራል።
በከተማ ውበትና የቦታ ልማት ኢኮኖሚ ረገድ ደግሞ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የገበታ ለትዉልድ ፕሮጀክቶች ከተሞችን የቱሪስት መዳረሻና የኢኮኖሚ መፈልፈያ ማዕከል በማድረግ ረገድ ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን ታላቅ አህጉራዊ ተስፋ እውን ለማድረግና ኢትዮጵያን በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ድምፅዋ ጎልቶ የሚሰማ ግዙፍ የአፍሪካ ኃያል ሀገር ለማድረግ የሚቻለው ቀጣናዊና ሀገራዊ የቤት ስራዎችን በብልሃት መወጣት ሲቻል ነው።
በመሆኑም መዋቅራዊ ሽግግሩን በስኬት ለማጠናቀቅ የሀገር ውስጥ ሰላምና ጸጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ማስቀጠል፣ የማክሮኢኮኖሚ መረጋጋትን መፍጠር፣ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር እና የፋይናንስ አቅርቦቶችን የበለጠ ማሻሻል ድርድር የማይገባባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊና ጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተፈጥሮ ፀጋ በአግባቡ ከተጠቀመች መጪው አምስት ዓመት የልመና ታሪኳ የሚያበቃበት ራሷን ችላ የምትቆምበት እና የበለፀገች ሀገር የመሆን ጉዞዋ በተጨባጭ የሚረጋገጥበት ዘመን እንደሚሆን አያጠራጥርም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #dot #ebc
***************
( የዕለቱ መልዕክት)
በታሪካዊ እጥፋቶችና ስር በሰደዱ መዋቅራዊ ማነቆዎች ውስጥ ስትመላለስ የኖረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ከትናንት የዳተኝነት ቀንበር ተላቃ ወደ ላቀ ምዕራፍ ለመሻገር የሚያስችላትን ታሪካዊ መሠረት ጥላለች። የሀገራችን የልማትና የለውጥ ጉዞ በመጀመሪያው ምዕራፍ ላይ የጥርጣሬና የፈተና ድንጋዮች ቢወረወሩበትም ዛሬ ግን ኢትዮጵያ በፈጣን እና መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር ሂደት ውስጥ ትገኛለች።
ለብዙ አስርት ዓመታት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ የቆየውን ባህላዊ የግብርና መር ሞዴል ወደ ላቀ የኢንዱስትሪ፣ የቴክኖሎጂ እና የአገልግሎት ዘርፍ ለማሸጋገር የተነደፉት ግዙፍና ሁለንተናዊ የልማት ፕሮጀክቶች መሬት በመያዝ ላይ ናቸው።
ይህ ስልታዊ እርምጃ ተራ የድንጋይና የኮንክሪት ክምችት ሳይሆን የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ስር የሰደደውን የንግድ ሚዛን መዛባት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማስፈን የታለመ የሉዓላዊነት ማህተም ነው።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ ላይ ያለች ብትሆንም የኢኮኖሚ ዕድገቷን የገደቡ ሦስት ዋና ዋና መዋቅራዊ እጥረቶች ነበሩባት። የመጀመሪያው ወደ ውጭ ከምትልካቸው ጥሬ የግብርና ምርቶች የምታገኘው ገቢና ለውጭ መሠረታዊ ቁሳቁሶች የምታወጣው ወጪ አለመመጣጠን የወለደው የንግድ ሚዛን መዛባት እና የውጭ ምንዛሬ እጥረት ነው።
ሁለተኛው ብሔራዊ የምግብ ዋስትናን ሁልጊዜም ለአደጋ የሚያጋልጠውና በየዓመቱ ከዓለም አቀፍ ገበያ በሚመጣ ማዳበሪያ ላይ የተንጠለጠለው የግብርና ዘርፍ የውጭ ጥገኝነት ነው።
ሦስተኛውና ታሪካዊው ተግዳሮት ደግሞ የባህር በር ማጣት ያስከተለው የሎጂስቲክስ ጫና እና ከአንድ የጅቡቲ ወደብ ኮሪደር ጋር ብቻ መተሳሰር የፈጠረው የብሔራዊ ደህንነት ስጋት ነው። እነዚህን ስር የሰደዱ ችግሮች ለመቅረፍ ባለፉት ዓመታት በተለይም በግብርናው ዘርፍ የበጋ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ ከውጪ አስመጪነት ወደ ላኪነት የተደረገው ሽግግር፣ “የማይሞቅ ፍም አይነድም፣ የማይሆን ነገር አይሆንም” የሚሉትን የጥርጣሬ ድምፆች በተግባር ያፈረሰ ተምሳሌታዊ ስኬት ሆኗል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ከሰጡ በኋላ እንዳመለከቱት መጪው አምስት ዓመት የኢትዮጵያ በርካታ የታሪክ እጥፋት የሚታይበት ዘመን ነው።
"የትናንትናዋን ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አምስት ዓመት አናያትም። የተቀየረች፣ የተለወጠች፣ ቢያንስ የማትለምን፣ ራሷን ችላ የምትቆም፣ በቀጠናው መልህቅ የሆነች አገር ለማየት ብዙ ልፋት ይፈልጋል" ማለታቸው የዚህን ሽግግር ጥልቀትና የሚጠይቀውን ብሔራዊ ቁርጠኝነት ያሳያል።
በመሆኑም መጪው አምስት ዓመት የምክንያትና የውጤት ትስስር የሚታይበት፣ ባለፉት ዓመታት የተጀመሩት ስልታዊና ትላልቅ ስራዎች ፍሬ የሚያፈሩበት ወርቃማ ምዕራፍ ይሆናል።
በዚህም መሠረት በኃይልና ታዳሽ ኢነርጂ ዘርፍ እንደ የኮይሻ ሃይድሮ-ኤሌክትሪክ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማጠናቀቅ ኢትዮጵያን የቀጠናዉ የኃይል ማማ ከማድረግ ባለፈ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት አስተማማኝና ርካሽ ግብዓት ይፈጥራል።
በፔትሮ-ኬሚካልና ማምረቻ ዘርፍ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝና የሀገር ውስጥ የማዳበሪያ ፋብሪካ ስራ መጀመር የግብርናውን ዘርፍ ከውጭ ጥገኝነት በማላቀቅ የውጭ ምንዛሬን በከፍተኛ ሁኔታ ይታደጋል። በአቪዬሽንና ግሎባል ትራንስፖርት ዘርፍ አዲሱ የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ግንባታ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቁልፍ የሎጂስቲክስና የትራንዚት ማእከልነቷን ያጠናክራል።
በከተማ ውበትና የቦታ ልማት ኢኮኖሚ ረገድ ደግሞ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የገበታ ለትዉልድ ፕሮጀክቶች ከተሞችን የቱሪስት መዳረሻና የኢኮኖሚ መፈልፈያ ማዕከል በማድረግ ረገድ ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው።
ይህንን ታላቅ አህጉራዊ ተስፋ እውን ለማድረግና ኢትዮጵያን በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ድምፅዋ ጎልቶ የሚሰማ ግዙፍ የአፍሪካ ኃያል ሀገር ለማድረግ የሚቻለው ቀጣናዊና ሀገራዊ የቤት ስራዎችን በብልሃት መወጣት ሲቻል ነው።
በመሆኑም መዋቅራዊ ሽግግሩን በስኬት ለማጠናቀቅ የሀገር ውስጥ ሰላምና ጸጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ማስቀጠል፣ የማክሮኢኮኖሚ መረጋጋትን መፍጠር፣ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር እና የፋይናንስ አቅርቦቶችን የበለጠ ማሻሻል ድርድር የማይገባባቸው ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው።
ኢትዮጵያ ያላትን ስትራቴጂካዊና ጂኦ-ፖለቲካዊ አቀማመጥ እና የተፈጥሮ ፀጋ በአግባቡ ከተጠቀመች መጪው አምስት ዓመት የልመና ታሪኳ የሚያበቃበት ራሷን ችላ የምትቆምበት እና የበለፀገች ሀገር የመሆን ጉዞዋ በተጨባጭ የሚረጋገጥበት ዘመን እንደሚሆን አያጠራጥርም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #dot #ebc
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ እያካሄዱት ያለው ጦርነት ገና "እንዳላበቃ" ገልጸው፣ ሆኖም ቴህራን በውጊያው በእጅጉ "መዳከሟን" አጥብቀው ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሳወቁት ለሲኤንቢሲ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት መግለጫ ላይ ነው። በወቅቱ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በየሁለት ቀኑ አንዴ እንደሚነጋገሩ የገለጹት ኔታንያሁ፣ "አልፎ አልፎ በስልታዊ ጉዳዮች ላይ የሐሳብ ልዩነቶች ቢኖሩንም፣ ሁልጊዜም መፍትሔ ላይ እንደርሳለን" ሲሉ የሁለቱን አገራት የጠበቀ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት አብራርተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ኃይሎች አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በኢራን ውስጥ ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ወደፊት ስለሚወሰደው ከባድ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውሳኔ ሲያስረዱም፣ "በቀጠናው ያለውን ውጥረት ማባባስ አስፈላጊ መሆን አለመሆኑን እንዲሁም የሆርሙዝ ስትሬትን (የባህር በር) በወታደራዊ ኃይል ማስከፈት ይቻል እንደሆነ የመወሰኑን ስልጣን ለትራምፕ ትተነዋል" ሲሉ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የመሪነት ሚና በእስራኤል በኩል ተቀባይነት እንዳለው የሚያንጸባርቅ ሐሳብ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ የእስራኤል እና የአሜሪካ የጦር ኃይሎች አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በኢራን ውስጥ ማንኛውንም እርምጃ ለመውሰድ በተጠንቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ወደፊት ስለሚወሰደው ከባድ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ውሳኔ ሲያስረዱም፣ "በቀጠናው ያለውን ውጥረት ማባባስ አስፈላጊ መሆን አለመሆኑን እንዲሁም የሆርሙዝ ስትሬትን (የባህር በር) በወታደራዊ ኃይል ማስከፈት ይቻል እንደሆነ የመወሰኑን ስልጣን ለትራምፕ ትተነዋል" ሲሉ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የመሪነት ሚና በእስራኤል በኩል ተቀባይነት እንዳለው የሚያንጸባርቅ ሐሳብ ሰጥተዋል።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሪፐብሊካን ፓርቲው የአሜሪካ ምክር ቤት አባል ቶማስ ማሲ መንግስታቸው ለእስራኤል እያደረገ ያለውን የገንዘብ ድጋፍ አጥብቀው የተቹ ሲሆን፣ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ መካከል ተፈጥሯል የተባለውን የከረረ የቃላት ልውውጥ "ባዶ ወሬ ነው" ሲሉ አጣጥለውታል።
ህግ አውጭው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "ሁሉ ነገር ወሬ ነው። ለእስራኤል የሚሰጠውን የውጭ እርዳታ ለአንድ ወር ብቻ ብታቋርጡት ጎረቤቶቻቸውን በቦምብ መደብደብ ያቆማሉ። ያኔ ፈጣን ሰላም ይመጣል፣ የሆርሙዝ ስትሬት (የባህር በር) ክፍት ይሆናል፣ እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ በአንድ ጋሎን 2 ዶላር ይቀንሳል" ብለዋል።
አክለውም "እስራኤል ከአሜሪካ ግብር ከፋዮች ከፍተኛውን የእርዳታ ገንዘብ የምትቀበል ሀገር ሆና ቆይታለች፤ አሁንም ያንኑ በመቀጠል ላይ ትገኛለች" ሲሉ የሀገራቸውን የውጭ ፖሊሲ አጥብቀው ተችተዋል።
ህግ አውጭው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "ሁሉ ነገር ወሬ ነው። ለእስራኤል የሚሰጠውን የውጭ እርዳታ ለአንድ ወር ብቻ ብታቋርጡት ጎረቤቶቻቸውን በቦምብ መደብደብ ያቆማሉ። ያኔ ፈጣን ሰላም ይመጣል፣ የሆርሙዝ ስትሬት (የባህር በር) ክፍት ይሆናል፣ እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ በአንድ ጋሎን 2 ዶላር ይቀንሳል" ብለዋል።
አክለውም "እስራኤል ከአሜሪካ ግብር ከፋዮች ከፍተኛውን የእርዳታ ገንዘብ የምትቀበል ሀገር ሆና ቆይታለች፤ አሁንም ያንኑ በመቀጠል ላይ ትገኛለች" ሲሉ የሀገራቸውን የውጭ ፖሊሲ አጥብቀው ተችተዋል።
2 months ago
#ethiopia | የአርሲ ዋይታ | የአይጥ መርዝ | ግብፅ የኢትዮጵያን የባህር በር ለማደናቀፍ እያሴረች | አዲስ አበባ የአሜሪካ የቪዛ ማዕከል
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
Comments