2 hours ago
ጋዜጠኛ ያልተቀጠረለት ምስጥራዊው የሩሲያ የሬዲዮ ጣቢያ
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ሸገር የሬዲዮ ጣቢያን ካለ ዜና አልያ ካለ ፕሮግራም እና ሙዚቃ ውጭ እስቲ አስቡት? በዓለም ዙሪያ ያሉ የሬዲዮ መገናኛ አጥኚዎችን እና ተመራማሪዎችን ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያወዛግብ የቆየውና "ዘ ቡዘር" በመባል የሚታወቀው ምስጢራዊው የሩሲያ አጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ "ዩቪቢ-76" ፣ አሁንም ድረስ ትክክለኛ አላማው ሳይታወቅ ስርጭቱን እንደቀጠለ ነው።
በ4625 ኪሎ ኸርዝ (kHz) ሞገድ ላይ የሚሰራጨው ይህ ጣቢያ፣ በቀን ለ24 ሰዓታት አሰልቺ እና ተደጋጋሚ የሆነ የ"ቡዝ" ድምጽ ያሰማል። ጣቢያው ስርጭቱን ከጀመረበት ከ1970ዎቹ መገባደጃ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ድምፁ ድንገት ተቋርጦ በሩሲያኛ ቋንቋ ቁጥሮችን፣ ስሞችን እና አጫጭር መልእክቶችን የሚያነቡ ሰዎች ድምፅ ይሰማል። ሆኖም ግን የመልእክቶቹ ትርጉምም ሆነ የጣቢያው ትክክለኛ አገልግሎት እስካሁን በውል አልታወቀም።
ስለ ጣቢያው ምንነት እና አላማ ከተለያዩ አካላት በርካታ መላምቶች ያሉ ሲሆን
በርካቶች ጣቢያው በዓለም ዙሪያ ለተሰማሩ የሩሲያ ሰላዮች ምስጢራዊ መልእክቶችን ለማስተላለፍ እና ለሩሲያ ጦር ሰራዊት በተለይም ለምዕራባዊው ወታደራዊ እዝ እና ለተለያዩ የጦር ሰፈሮች መገናኛነት እንደሚያገለግል በስፋት ይገመታል።
አንዳንዶች ደግሞ ይህ ጣቢያ ሩሲያ የኒውክሌር ጥቃት ቢሰነዘርባት እና ከፍተኛ አመራሮቿ ቢገደሉ፣ በራስ ሰር የኒውክሌር አፀፋዊ ጥቃት እንዲሰነዘር የሚያደርገው ስርዓት አካል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።
ምንም እንኳን ጣቢያው ከቦታ ቦታ ከሞስኮ አቅራቢያ ወደ ሴንት ፒተርስበርግ አካባቢ መቀየሩ ቢታወቅም፣ የሩሲያ መንግስት ስለ ጣቢያው ህልውናም ሆነ አላማ እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም። በዘመናዊው የዲጂታል ኮሙኒኬሽን እና የሳተላይት መገናኛ ዘመን፣ ይህ አሮጌ የአጭር ሞገድ ሬዲዮ ጣቢያ ያለማቋረጥ ስርጭቱን መቀጠሉ አሁንም ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንቆቅልሽን እንደሆነ ቀጥሏል ቀጥሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 hours ago
በንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የዋጋ ቅናሽ በተግባር ባለመዋሉ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እንዲያደርግ ተጠየቀ
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የልማት አጋሮች በሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የችርቻሮ ዋጋ ቅናሽ ለተጠቃሚዎች በትክክል ተፈጻሚ ባለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እና የተጠያቂነት አሰራር እንዲዘረጋ አሳሰቡ።
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚሉት፤ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስ ቀደም ሲል የፊስካል ማሻሻያ እርምጃዎች ቢወሰዱም፣ መዋቅራዊ መሰናክሎች፣ ደካማ የአቅርቦት ሰንሰለት ቁጥጥር እና ዝቅተኛ ግንዛቤ ሂደቱን በማስተጓጎላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች እና ልጃገረዶች አሁንም ለችግር ተጋልጠዋል።
የኤች.አይ.ቪ ጤና ጥበቃ ፈንድ (AHF) ኢትዮጵያ የቅድመ መከላከል፣ የአፍሪካ ህብረት ግንኙነት እና የዕድገት ድጋፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ ኦላና ጉዳዩን በተመለከተ ለካፒታል ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የወር አበባ ጤና መጠበቂያ ምርቶች እጥረት እና ያለመገኘት በኢትዮጵያ የፆታ እኩልነት፣ ጤና፣ ትምህርት እና የኢኮኖሚ ምርታማነት ላይ ትልቅ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል።
በ 2017 የቀረበው እና በምርቶቹ ላይ የሚስተዋሉ መዋቅራዊ መሰናክሎችን ለማስወገድ በተዘጋጀው ረቂቅ የፖሊሲ ሰነድ ላይ ይህ ጉዳይ በስፋት ተዳሷል።
በጤና ሚኒስቴር፣ በትምህርት ሚኒስቴር እና ከ10 በላይ አጋር ድርጅቶች (AHF፣ ዩኒሴፍ እና ሌሎችም ጨምሮ) እንዲሁም በአገር ውስጥ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ ሞዴሶችን ከሚያመርቱ ድርጅቶች ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን ማግኘት የሚችሉት 30 በመቶ ያህሉ ሴቶች ብቻ ናቸው።
የዚህ እጥረት መዘዝ ከባድ መሆኑን የገለጹት አቶ ቶለሳ፣ ከ10 ታዳጊ ልጃገረዶች መካከል አንዷ በወር አበባ ምክንያት መደበኛ የትምህርት ቀናት የምታጣ ሲሆን፣ ብዙ ሴቶች ደግሞ በስራ ቦታቸው ላይ ምርታማነታቸው እንዲቀንስ ወይም ከስራ ለመቅረት ተገድደዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ቀደም ሲል የማስመጫ ታሪፎችን ቢያስተካክልም፣ ሊጣሉ በሚችሉ ሞዴሶች እና ሌሎች ምርቶች ላይ አሁንም 15 በመቶ ከፍተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ ይተገበራል። ችግሩ ይበልጥ የተወሳሰበው በተጠናቀቁ ምርቶች ላይ በሚጣለው 10 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ እና ለማምረቻነት በሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች ላይ በሚጣለው ከፍተኛ ታክስ ምክንያት ነው።
አቶ ቶለሳ ኦላና እንዳሉት፤ ከአስመጪዎች፣ ከችርቻሮ ነጋዴዎች እና ከማህበራዊ ማሻሻጫ አካላት ጋር ከፍተኛ የፖሊሲ ውይይቶች ቢደረጉም፣ በህብረተሰቡ ደረጃ የታየ ተጨባጭ ለውጥ የለም። ከአምራቾች፣ አስመጪዎች፣ አከፋፋዮች እና የማህበራዊ ማሻሻጫ መረቦች ጋር ሰፊ ውይይት ቢደረግም ስለ ታክስ ነፃ መብቶች ያለው ግንዛቤ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via capital
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና የልማት አጋሮች በሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶች ላይ የታለመው የችርቻሮ ዋጋ ቅናሽ ለተጠቃሚዎች በትክክል ተፈጻሚ ባለመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጥብቅ የገበያ ቁጥጥር እና የተጠያቂነት አሰራር እንዲዘረጋ አሳሰቡ።
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንደሚሉት፤ በሴቶች ላይ የሚደርሰውን የኢኮኖሚ ጫና ለመቀነስ ቀደም ሲል የፊስካል ማሻሻያ እርምጃዎች ቢወሰዱም፣ መዋቅራዊ መሰናክሎች፣ ደካማ የአቅርቦት ሰንሰለት ቁጥጥር እና ዝቅተኛ ግንዛቤ ሂደቱን በማስተጓጎላቸው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሴቶች እና ልጃገረዶች አሁንም ለችግር ተጋልጠዋል።
የኤች.አይ.ቪ ጤና ጥበቃ ፈንድ (AHF) ኢትዮጵያ የቅድመ መከላከል፣ የአፍሪካ ህብረት ግንኙነት እና የዕድገት ድጋፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ቶለሳ ኦላና ጉዳዩን በተመለከተ ለካፒታል ጋዜጣ እንደገለጹት፤ የወር አበባ ጤና መጠበቂያ ምርቶች እጥረት እና ያለመገኘት በኢትዮጵያ የፆታ እኩልነት፣ ጤና፣ ትምህርት እና የኢኮኖሚ ምርታማነት ላይ ትልቅ እንቅፋት እየሆነ መጥቷል።
በ 2017 የቀረበው እና በምርቶቹ ላይ የሚስተዋሉ መዋቅራዊ መሰናክሎችን ለማስወገድ በተዘጋጀው ረቂቅ የፖሊሲ ሰነድ ላይ ይህ ጉዳይ በስፋት ተዳሷል።
በጤና ሚኒስቴር፣ በትምህርት ሚኒስቴር እና ከ10 በላይ አጋር ድርጅቶች (AHF፣ ዩኒሴፍ እና ሌሎችም ጨምሮ) እንዲሁም በአገር ውስጥ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ ሞዴሶችን ከሚያመርቱ ድርጅቶች ጋር በጋራ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው፤ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ዘመናዊ የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን ማግኘት የሚችሉት 30 በመቶ ያህሉ ሴቶች ብቻ ናቸው።
የዚህ እጥረት መዘዝ ከባድ መሆኑን የገለጹት አቶ ቶለሳ፣ ከ10 ታዳጊ ልጃገረዶች መካከል አንዷ በወር አበባ ምክንያት መደበኛ የትምህርት ቀናት የምታጣ ሲሆን፣ ብዙ ሴቶች ደግሞ በስራ ቦታቸው ላይ ምርታማነታቸው እንዲቀንስ ወይም ከስራ ለመቅረት ተገድደዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን መንግስት ቀደም ሲል የማስመጫ ታሪፎችን ቢያስተካክልም፣ ሊጣሉ በሚችሉ ሞዴሶች እና ሌሎች ምርቶች ላይ አሁንም 15 በመቶ ከፍተኛ የተጨማሪ እሴት ታክስ ይተገበራል። ችግሩ ይበልጥ የተወሳሰበው በተጠናቀቁ ምርቶች ላይ በሚጣለው 10 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ እና ለማምረቻነት በሚያገለግሉ ጥሬ ዕቃዎች ላይ በሚጣለው ከፍተኛ ታክስ ምክንያት ነው።
አቶ ቶለሳ ኦላና እንዳሉት፤ ከአስመጪዎች፣ ከችርቻሮ ነጋዴዎች እና ከማህበራዊ ማሻሻጫ አካላት ጋር ከፍተኛ የፖሊሲ ውይይቶች ቢደረጉም፣ በህብረተሰቡ ደረጃ የታየ ተጨባጭ ለውጥ የለም። ከአምራቾች፣ አስመጪዎች፣ አከፋፋዮች እና የማህበራዊ ማሻሻጫ መረቦች ጋር ሰፊ ውይይት ቢደረግም ስለ ታክስ ነፃ መብቶች ያለው ግንዛቤ አሁንም ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።
Via capital
4 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ስምምነት ለማጠናቀቅ ጥረት እያደረጉ ባለበት ወቅት እስራኤል በቤይሩት ላይ ጥቃት በመክፈቷ፣ ለጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ "ምንም ዓይነት የማመዛዘን ችሎታ የለውም" በማለት በቁጣ መናገራቸውን ገለጹ።
ትራምፕ ከአክሲዮስ ዜና አውታር ጋር ባደረጉት የስልክ ቆይታ፣ "ቢቢ (ኔታንያሁ) ለምን ይህን ጥቃት መፈጸም አስፈለገው?" በማለት ጠይቀዋል። አክለውም "በጣም ተናድጄ ነበር። ይህንኑ ነግሬዋለሁ። ምንም ዓይነት የማመዛዘን ችሎታ የለውም፤ ይሄንንም በግልጽ አሳውቄዋለሁ" ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለአክሲዮስ እና ፎክስ ኒውስ እንዳረጋገጡት፣ ምንም እንኳን ጥቃቱ እንቅፋት ቢፈጥርም ዛሬውኑ ከኢራን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ይፈረማል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
ይህ የቤይሩት ጥቃት ባይፈጸም ኖሮ ስምምነቱ አሁን ተፈርሞ ይጠናቀቅ እንደነበር የገለጹት ትራምፕ "ጥቃቱ ሂደቱን አናግቶታል፤ ፊርማው በጥቂት ሰዓታት እንዲዘገይ አድርጓል። ልክ አሁን መፈረም ነበረበት፣ ነገር ግን አሁን ከጥቂት ሰዓታት በኋላ እንዲካሄድ ተዘዋውሯል" ብለዋል።
በመጨረሻም ትራምፕ፣ "ሁኔታው በጣም መጥፎ ነው። ስምምነቱን ልንፈራረም አንድ ሰዓት ሲቀረው እንዲህ ዓይነት ነገር ይፈጠራል ብዬ ማመን አልቻልኩም" በማለት ጥልቅ ቅሬታቸውን አንጸባርቀዋል።
ትራምፕ ከአክሲዮስ ዜና አውታር ጋር ባደረጉት የስልክ ቆይታ፣ "ቢቢ (ኔታንያሁ) ለምን ይህን ጥቃት መፈጸም አስፈለገው?" በማለት ጠይቀዋል። አክለውም "በጣም ተናድጄ ነበር። ይህንኑ ነግሬዋለሁ። ምንም ዓይነት የማመዛዘን ችሎታ የለውም፤ ይሄንንም በግልጽ አሳውቄዋለሁ" ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለአክሲዮስ እና ፎክስ ኒውስ እንዳረጋገጡት፣ ምንም እንኳን ጥቃቱ እንቅፋት ቢፈጥርም ዛሬውኑ ከኢራን ጋር የመግባቢያ ሰነድ ይፈረማል ብለው እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።
ይህ የቤይሩት ጥቃት ባይፈጸም ኖሮ ስምምነቱ አሁን ተፈርሞ ይጠናቀቅ እንደነበር የገለጹት ትራምፕ "ጥቃቱ ሂደቱን አናግቶታል፤ ፊርማው በጥቂት ሰዓታት እንዲዘገይ አድርጓል። ልክ አሁን መፈረም ነበረበት፣ ነገር ግን አሁን ከጥቂት ሰዓታት በኋላ እንዲካሄድ ተዘዋውሯል" ብለዋል።
በመጨረሻም ትራምፕ፣ "ሁኔታው በጣም መጥፎ ነው። ስምምነቱን ልንፈራረም አንድ ሰዓት ሲቀረው እንዲህ ዓይነት ነገር ይፈጠራል ብዬ ማመን አልቻልኩም" በማለት ጥልቅ ቅሬታቸውን አንጸባርቀዋል።
5 hours ago
የእሥራኤል 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን፤
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
5 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (ESL) ከ40 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገሪቱን የነዳጅ እና የፔትሮሊየም ምርቶች የማጓጓዝ ስራ በይፋ መጀመሩን ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ካፒታል እንግሊዘኛው ጋዜጣ ዘግቧል። ይህ ታሪካዊ ጅምር ኢትዮጵያ ከሱዳን ነዳጅ ማስገባት ካቆመች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአፍሪካ (ከአህጉሪቱ) ሀገር ነዳጅ ያገኘችበትንም አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
7 hours ago
የዓለም የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን እየተከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) "ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሃን ይመልሳል" በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን እየተከበረ ነው።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ሚኒስቴሩ ከበጎ ፈቃደኝነት ጋር በተያያዘ ሰፋፊ ስራዎች ሰርቷል።
በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ60 በላይ ደም ባንኮች መቋቋማቸውን አንስተው÷ የደም ልገሳ አሁን ላይ ባህል እየሆነ መጥቷል ብለዋል።
ደም የመለገስ ተግባር አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ደም እና ሕብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው÷ በበጀት ዓመቱ ከ441 ሺህ ዩኒት በላይ ደም መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል።
ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር የ19 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸው÷ በበጀት ዓመቱ 338 የዓይን ብሌን ለማሰባሰብ ታቅዶ ከ411 በላይ ማሰባሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።
የሰኔ ወር እስከሚጠናቀቅ ድረስ የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን በተለያዩ መርሐ ግብሮች እንደሚታሰብ ተመላክቷል።
በቅድስት ብርሃኑ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) "ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሃን ይመልሳል" በሚል መሪ ሐሳብ የዓለም የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን እየተከበረ ነው።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ሚኒስቴሩ ከበጎ ፈቃደኝነት ጋር በተያያዘ ሰፋፊ ስራዎች ሰርቷል።
በዚህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ60 በላይ ደም ባንኮች መቋቋማቸውን አንስተው÷ የደም ልገሳ አሁን ላይ ባህል እየሆነ መጥቷል ብለዋል።
ደም የመለገስ ተግባር አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ደም እና ሕብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት ዋና ስራ አስኪያጅ ዶ/ር አሸናፊ ታዘበው በበኩላቸው÷ በበጀት ዓመቱ ከ441 ሺህ ዩኒት በላይ ደም መሰብሰብ መቻሉን ጠቁመዋል።
ይህም ከባለፈው በጀት ዓመት አንጻር የ19 በመቶ እድገት እንዳለው ገልጸው÷ በበጀት ዓመቱ 338 የዓይን ብሌን ለማሰባሰብ ታቅዶ ከ411 በላይ ማሰባሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።
የሰኔ ወር እስከሚጠናቀቅ ድረስ የደም እና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን በተለያዩ መርሐ ግብሮች እንደሚታሰብ ተመላክቷል።
በቅድስት ብርሃኑ
10 hours ago
ጥርስን እንደገና የሚያሳድገው መድሃኒት‼️
ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️
በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በዶ/ር ካትሱ ታካሃሺ የሚመራው የጃፓን ተመራማሪዎች የጥርስን ተፈጥሯዊ እድገት የሚያነቃቃ ፈር ቀዳጅ የሆነ መድሃኒት ፈጥረዋል። መድሃኒቱ የሚሠራው የጥርስን እድገት የሚከላከለውን ዩኤስኤግ-1 የተባለውን ፕሮቲን በመግታት ነው።
ይህ መድሃኒት በአይጦች ላይ ሙከራ ተደርጎ አዲስ-ጥርሶችን በተሳካ ሁኔታ በማሳደጉ የምርምር ቡድኑ አሁን ይህን ለውጥ የሚያመጣ ህክምና በአስር አመታት ውስጥ ወደ ገበያ ለማውጣት በሰዎች ላይ ክሊኒካዊ ሙከራዎችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️
በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በዶ/ር ካትሱ ታካሃሺ የሚመራው የጃፓን ተመራማሪዎች የጥርስን ተፈጥሯዊ እድገት የሚያነቃቃ ፈር ቀዳጅ የሆነ መድሃኒት ፈጥረዋል። መድሃኒቱ የሚሠራው የጥርስን እድገት የሚከላከለውን ዩኤስኤግ-1 የተባለውን ፕሮቲን በመግታት ነው።
ይህ መድሃኒት በአይጦች ላይ ሙከራ ተደርጎ አዲስ-ጥርሶችን በተሳካ ሁኔታ በማሳደጉ የምርምር ቡድኑ አሁን ይህን ለውጥ የሚያመጣ ህክምና በአስር አመታት ውስጥ ወደ ገበያ ለማውጣት በሰዎች ላይ ክሊኒካዊ ሙከራዎችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
11 hours ago
የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ስጋት የሕክምናው ዘርፍ ፈተና
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
13 hours ago
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ውል ላይ ደረሰ
*************
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
በሌላ በኩል ኢራን አሜሪካ በዲፕሎማሲያዊ ሂደቱ ላይ በተደጋጋሚ ክህደት ፈጽማለች ስትል በመውቀስ፣ በዋሽንግተን ባህሪ ምክንያት የተገኘው መሻሻል ወደኋላ እየተመለሰ መሆኑን ገልጻለች።
ይሁን እንጂ ኢራን በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንና በመጨረሻው የውስጥ ግምገማ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስምምነቱ በመጪው እሁድ መጀመሪያ ላይ ሊፈረም እንደሚችል የገለጹ ሲሆን፣ ቴህራን በበኩሏ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ጥርጣሬ ቢኖራትም ፊርማው “በሚቀጥሉት ቀናት” ሊከናወን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥታለች።
ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት እንደሚሆንና አሜሪካም በመጨረሻ የኢራንን የኑክሌር ቁሳቁስ እንደምታገኝ ተጠቅሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢራን ማንኛውም የተኩስ አቁም ስምምነት እስከ ሊባኖስ ድረስ መዘርጋት አለበት ብላ ብታስረግጥም፣ የእስራኤል ጦር ጥቃቱን በመቀጠሉ በደቡብ ሊባኖስ በርካታ ፍንዳታዎች እየተከሰቱ ይገኛሉ ሲሉ ዘ ቴሌግራፍ እና አልጀዚራ በዘገባቸው ጠቅሰዋል።
በመሐመድ ፊጣሞ
#usiranpeacetalks #straitofhormuz #middleeastpeace #ethiopianbroadcastingcorporation
*************
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
በሌላ በኩል ኢራን አሜሪካ በዲፕሎማሲያዊ ሂደቱ ላይ በተደጋጋሚ ክህደት ፈጽማለች ስትል በመውቀስ፣ በዋሽንግተን ባህሪ ምክንያት የተገኘው መሻሻል ወደኋላ እየተመለሰ መሆኑን ገልጻለች።
ይሁን እንጂ ኢራን በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንና በመጨረሻው የውስጥ ግምገማ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስምምነቱ በመጪው እሁድ መጀመሪያ ላይ ሊፈረም እንደሚችል የገለጹ ሲሆን፣ ቴህራን በበኩሏ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ጥርጣሬ ቢኖራትም ፊርማው “በሚቀጥሉት ቀናት” ሊከናወን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥታለች።
ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት እንደሚሆንና አሜሪካም በመጨረሻ የኢራንን የኑክሌር ቁሳቁስ እንደምታገኝ ተጠቅሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢራን ማንኛውም የተኩስ አቁም ስምምነት እስከ ሊባኖስ ድረስ መዘርጋት አለበት ብላ ብታስረግጥም፣ የእስራኤል ጦር ጥቃቱን በመቀጠሉ በደቡብ ሊባኖስ በርካታ ፍንዳታዎች እየተከሰቱ ይገኛሉ ሲሉ ዘ ቴሌግራፍ እና አልጀዚራ በዘገባቸው ጠቅሰዋል።
በመሐመድ ፊጣሞ
#usiranpeacetalks #straitofhormuz #middleeastpeace #ethiopianbroadcastingcorporation
14 hours ago
በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ እንደሆነ በግልጽ እንዲታወቅ ተጠየቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
14 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ 80ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ዛሬ ታሪካዊ በሆነው የዋይት ሃውስ ደቡባዊ ግቢ ውስጥ የድብልቅ ማርሻል አርት (የአጥር ውስጥ) ፍልሚያ በማዘጋጀት እጅግ በደማቅ ሁኔታ ያከብራሉ። ይህ አይነቱ ዝግጅት በዋይት ሃውስ ውስጥ ይካሄዳል ተብሎ ከዚህ ቀደም ፈጽሞ የማይታሰብ ነበር።
በዚህ ሳምንት ግን የፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው እውነታዎች በዚህ የተንዛዛ የድብልቅ ማርሻል አርት ትርኢት ላይ ጥላ ያጠሉ ይመስላል። በዚህ የካጅ ፍልሚያ ላይ ተወዳዳሪዎች በስምንት ማዕዘን የብረት አጥር ውስጥ ተዘግተው እርስ በርሳቸው በመማታት እና በመደባደብ ለመሸናነፍ ይሞክራሉ።
በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት በሌለው እና ከፍተኛ ወጪ በሚጠይቀው የኢራን ጦርነት ውስጥ ተቀርቅረው ይገኛሉ። ግጭቱን ለማቆም የሚያስችል ስምምነት አፋፍ ላይ ቢደረስም፣ ወሳኝ የሆኑት ዝርዝር ጉዳዮች አሁንም ድርድር ይፈልጋሉ። ከዚህ በተጨማሪ ከልደቱ ድግስ አንድ ማይል ያህል ርቀት ላይ፣ ስያሜው ህገ-ወጥ ነው በሚል አንድ ዳኛ ባሳለፉት ውሳኔ መሰረት፣ ሰራተኞች የፕሬዝዳንቱን ስም ከኬኔዲ ማዕከል ህንጻ ላይ እያነሱ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ ተግዳሮቶች ቢኖሩም፣ ፕሬዝዳንቱ ከዋይት ሃውስ ሲወጡ በካቢኔ መሪዎች፣ በከፍተኛ የአስተዳደሩ ባለስልጣናት፣ በሪፐብሊካን የህግ አውጪዎች እና ድምጻቸው እስኪሰበር በሚጮሁ ከ4 ሺህ በላይ ተመልካቾች ይታጀባሉ። ዝግጅቱ "ዘ ክሎው" በተሰኘ፣ የጠፈር መንኮራኩር በሚመስል፣ በልዩ መብራቶች፣ የድምጽ መሳሪያዎች እና ግዙፍ ስክሪኖች በተገጠመለት ጊዜያዊ መድረክ ስር የሚካሄድ ነው። ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችም በአቅራቢያው ከሚገኘው ኤሊፕስ የተሰኘ ስፍራ ሆነው በግዙፍ ስክሪኖች ዝግጅቱን የሚከታተሉ ይሆናል።
ፕሬዝዳንቱ ከእኩለ ሌሊት አልፎ የሚቀጥሉ ሰባት ፍልሚያዎችን የሚያስተናግደውን ይህንን የልደት ዝግጅት፣ የአሜሪካ የነጻነት አዋጅ የተፈረመበትን 250ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት ከሚያከብሩት የበርካታ ወራት ሀገራዊ ክብረ በዓላት ጋር ለማስተሳሰር ሞክረዋል።
በዚህ ሳምንት ግን የፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው እውነታዎች በዚህ የተንዛዛ የድብልቅ ማርሻል አርት ትርኢት ላይ ጥላ ያጠሉ ይመስላል። በዚህ የካጅ ፍልሚያ ላይ ተወዳዳሪዎች በስምንት ማዕዘን የብረት አጥር ውስጥ ተዘግተው እርስ በርሳቸው በመማታት እና በመደባደብ ለመሸናነፍ ይሞክራሉ።
በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት በሌለው እና ከፍተኛ ወጪ በሚጠይቀው የኢራን ጦርነት ውስጥ ተቀርቅረው ይገኛሉ። ግጭቱን ለማቆም የሚያስችል ስምምነት አፋፍ ላይ ቢደረስም፣ ወሳኝ የሆኑት ዝርዝር ጉዳዮች አሁንም ድርድር ይፈልጋሉ። ከዚህ በተጨማሪ ከልደቱ ድግስ አንድ ማይል ያህል ርቀት ላይ፣ ስያሜው ህገ-ወጥ ነው በሚል አንድ ዳኛ ባሳለፉት ውሳኔ መሰረት፣ ሰራተኞች የፕሬዝዳንቱን ስም ከኬኔዲ ማዕከል ህንጻ ላይ እያነሱ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ ተግዳሮቶች ቢኖሩም፣ ፕሬዝዳንቱ ከዋይት ሃውስ ሲወጡ በካቢኔ መሪዎች፣ በከፍተኛ የአስተዳደሩ ባለስልጣናት፣ በሪፐብሊካን የህግ አውጪዎች እና ድምጻቸው እስኪሰበር በሚጮሁ ከ4 ሺህ በላይ ተመልካቾች ይታጀባሉ። ዝግጅቱ "ዘ ክሎው" በተሰኘ፣ የጠፈር መንኮራኩር በሚመስል፣ በልዩ መብራቶች፣ የድምጽ መሳሪያዎች እና ግዙፍ ስክሪኖች በተገጠመለት ጊዜያዊ መድረክ ስር የሚካሄድ ነው። ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾችም በአቅራቢያው ከሚገኘው ኤሊፕስ የተሰኘ ስፍራ ሆነው በግዙፍ ስክሪኖች ዝግጅቱን የሚከታተሉ ይሆናል።
ፕሬዝዳንቱ ከእኩለ ሌሊት አልፎ የሚቀጥሉ ሰባት ፍልሚያዎችን የሚያስተናግደውን ይህንን የልደት ዝግጅት፣ የአሜሪካ የነጻነት አዋጅ የተፈረመበትን 250ኛ ዓመት በታላቅ ድምቀት ከሚያከብሩት የበርካታ ወራት ሀገራዊ ክብረ በዓላት ጋር ለማስተሳሰር ሞክረዋል።
14 hours ago
ታዋቂዋ የአትሌቶች መፍለቂያ ቦቆጂ ከተማ የልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድርን በደመቀ ሁኔታ ማስተናገድ ጀመረች
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
16 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ጨዋታው እጅግ ከፍተኛ ጉልበት እና ፍጥነት የታየበት ማራኪ ፍልሚያ ሆኖ አምሽቷል። የመጀመሪያው አጋማሽ ሲጠናቀቅ አውስትራሊያ 1 ለ 0 መምራት የቻለች ሲሆን፣ አውስትራሊያዎች አስቀድሞ ሲጠበቅ እንደነበረው፣ እጅግ አደገኛ በሆነ የመልሶ ማጥቃት ስልት ቱርኮችን እየፈተኑ ይገኛሉ። የጨዋታውን ብቸኛ ግብ ኔስቶሪ ኢራንኩንዳ ከመረብ በማዋሃድ አውስትራሊያን መሪ አድርጓል። ከመሪነት ግቧ በኋላም አውስትራሊያዎች አደገኛነታቸውን አላቆሙም፤ ጆርዳን ቦስ ያሾለከለትን ኳስ ኢራንኩንዳ በፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ አግኝቶት የነበረ ቢሆንም፣ በመንሸራተቱ ምክንያት ቱርኮች ኳሷን መልሰው ሊነጥቁት ችለዋል። ብዙም ሳይቆይ ሌላ ዕድል ያገኘው ኢራንኩንዳ የመታው ኳስ በቀጥታ ወደ ግብ ጠባቂው እጅ ነው የገባው። በሌላ በኩል ጆርዳን ቦስ ከ30 ያርድ ርቀት ላይ ያደረገው አስገራሚ የበረረ ኳስ ሙከራ ወደ ላይ ቢወጣም፣ ለዓመታት በአውስትራሊያ የስፖርት ታሪክ ውስጥ በድምቀት ሲታወስ የሚኖር ድንቅ የግብ ሙከራ ነበር።
በቱርክ በኩል የተለመደው የኳስ ቁጥጥር ብልጫቸውን በመውሰድ አውስትራሊያን ጫና ውስጥ ለመክተት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ኳሷን እርስ በእርስ በሚያምር ሁኔታ እየተቀባበሉ የግብ ዕድል ለመፍጠር ቢሞክሩም፣ የአውስትራሊያ ተከላካዮች ግን እያንዳንዱን ክፍተት በመድፈን ወደር የሌለው ጀግንነት እያሳዩ ነው። በተለይም ወጣቱ ኮከብ አርዳ ጉለር ተከላካዮችን በሚያምር ክህሎት በማታለል ለማለፍ የሚያደርገው ጥረት እጅግ ማራኪ ነው። ሆኖም ኳሷን ባገኘ ቁጥር ከፊቱ ዘጠኝ የአውስትራሊያ ተጫዋቾች እንደ ግድግዳ ስለሚደረደሩበት ክፍተት ማግኘት ተስኖታል። ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ያደረገው አንድ ሙከራም ኢላማውን ሳይጠብቅ ወደ ውጭ ወጥቷል። ባሪስ ይልማዝ ከመስመር ወደ ውስጥ ለማሻማት ያደረገውን ጥረትም ጃኮብ ኢታሊያኖ በድንቅ የመንሸራተት ታክል (sliding tackle) አክሽፎበታል። ፈርዲ ካዲዮግሉ ያሻገረው ኳስም ወዲያውኑ በአውስትራሊያ ተከላካዮች ርቆ ተመልሷል።
ይህ ፍልሚያ በእውነትም እንቅልፍ የሚያስረሳ እና በማለዳ ቡና የማይፈልግ እጅግ ማራኪ እና ክፍት ጨዋታ ነው! ቱርኮች ጨዋታውን ለማስፋት እና ክፍተት ለመፍጠር ቢሞክሩም፣ አውስትራሊያዎች እያንዳንዱ ተጫዋች ከግቡ በ35 ያርድ ርቀት ውስጥ በመሰለፍ እጅግ የተደራጀ መከላከያ ገንብተዋል። ይሁን እንጂ አብዱልከሪም ባርዳክቺ ከረጅም ርቀት ያሾለካት እጅግ ኃይለኛ ኳስ የአውስትራሊያው ግብ ጠባቂ ፓትሪክ ቢች በጣቶቹ ነክቶ የግቡን ቋሚ ስትገጭ፣ ለቱርኮች እጅግ የሚያስቆጭ አጋጣሚ ነበረች።
የጨዋታው ዳኛም ለጨዋታው ፍሰት በሚመች መልኩ ውሳኔዎችን እያሳለፉ ጨዋታውን በሚገባ እየመሩት ይገኛሉ። በቀጣዩ 45 ደቂቃ አውስትራሊያ ተከላክላ ብቻ ለመጨረስ እንደማትፈልግ እና በመልሶ ማጥቃት አሁንም ከፍተኛ ስጋት እንደምትሆን ይጠበቃል። ቱርኮች በበኩላቸው ይህንን የኳስ የበላይነት ወደ ግብ ለመቀየር እና ጠንካራውን የአውስትራሊያ መከላከያ ለመስበር ተጨማሪ አጥቂ ወደ ሜዳ ሊያስገቡ እንደሚችሉ ይገመታል።
ውድ የዘ-ሐበሻ ቤተሰቦች፣ ከእረፍት በኋላ ውጤቱ ምን ይሆናል ብላችሁ ታስባላችሁ?
በቱርክ በኩል የተለመደው የኳስ ቁጥጥር ብልጫቸውን በመውሰድ አውስትራሊያን ጫና ውስጥ ለመክተት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ኳሷን እርስ በእርስ በሚያምር ሁኔታ እየተቀባበሉ የግብ ዕድል ለመፍጠር ቢሞክሩም፣ የአውስትራሊያ ተከላካዮች ግን እያንዳንዱን ክፍተት በመድፈን ወደር የሌለው ጀግንነት እያሳዩ ነው። በተለይም ወጣቱ ኮከብ አርዳ ጉለር ተከላካዮችን በሚያምር ክህሎት በማታለል ለማለፍ የሚያደርገው ጥረት እጅግ ማራኪ ነው። ሆኖም ኳሷን ባገኘ ቁጥር ከፊቱ ዘጠኝ የአውስትራሊያ ተጫዋቾች እንደ ግድግዳ ስለሚደረደሩበት ክፍተት ማግኘት ተስኖታል። ከፍጹም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ያደረገው አንድ ሙከራም ኢላማውን ሳይጠብቅ ወደ ውጭ ወጥቷል። ባሪስ ይልማዝ ከመስመር ወደ ውስጥ ለማሻማት ያደረገውን ጥረትም ጃኮብ ኢታሊያኖ በድንቅ የመንሸራተት ታክል (sliding tackle) አክሽፎበታል። ፈርዲ ካዲዮግሉ ያሻገረው ኳስም ወዲያውኑ በአውስትራሊያ ተከላካዮች ርቆ ተመልሷል።
ይህ ፍልሚያ በእውነትም እንቅልፍ የሚያስረሳ እና በማለዳ ቡና የማይፈልግ እጅግ ማራኪ እና ክፍት ጨዋታ ነው! ቱርኮች ጨዋታውን ለማስፋት እና ክፍተት ለመፍጠር ቢሞክሩም፣ አውስትራሊያዎች እያንዳንዱ ተጫዋች ከግቡ በ35 ያርድ ርቀት ውስጥ በመሰለፍ እጅግ የተደራጀ መከላከያ ገንብተዋል። ይሁን እንጂ አብዱልከሪም ባርዳክቺ ከረጅም ርቀት ያሾለካት እጅግ ኃይለኛ ኳስ የአውስትራሊያው ግብ ጠባቂ ፓትሪክ ቢች በጣቶቹ ነክቶ የግቡን ቋሚ ስትገጭ፣ ለቱርኮች እጅግ የሚያስቆጭ አጋጣሚ ነበረች።
የጨዋታው ዳኛም ለጨዋታው ፍሰት በሚመች መልኩ ውሳኔዎችን እያሳለፉ ጨዋታውን በሚገባ እየመሩት ይገኛሉ። በቀጣዩ 45 ደቂቃ አውስትራሊያ ተከላክላ ብቻ ለመጨረስ እንደማትፈልግ እና በመልሶ ማጥቃት አሁንም ከፍተኛ ስጋት እንደምትሆን ይጠበቃል። ቱርኮች በበኩላቸው ይህንን የኳስ የበላይነት ወደ ግብ ለመቀየር እና ጠንካራውን የአውስትራሊያ መከላከያ ለመስበር ተጨማሪ አጥቂ ወደ ሜዳ ሊያስገቡ እንደሚችሉ ይገመታል።
ውድ የዘ-ሐበሻ ቤተሰቦች፣ ከእረፍት በኋላ ውጤቱ ምን ይሆናል ብላችሁ ታስባላችሁ?
17 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ለ28 ዓመታት ከዓለም ዋንጫው ታላቅ መድረክ ርቃ የቆየችው ስኮትላንድ... ከ36 ረጅም ዓመታት በኋላ የመጀመሪያዋን ታሪካዊ የዓለም ዋንጫ ድል ማጣጣም ችላለች። በቦስተን ስታዲየም በከፍተኛ የልብ ትርታ እና ጭንቀት ውስጥ ዛሬ ምሽት፣ ሃይቲን ጠባብ በሆነ ውጤት በማሸነፍ ስኮትላንድን ወደ ምድብ ሦስት አናት ላይ ያወጣው ጀግናው የአስቶንቪላው አምበል ጆን ማክጊን ነበር። ይህ ታሪካዊ ድል ስኮትላንድ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ጥሎ ማለፉ ለመቀላቀል የምታደርገውን ጉዞ በከፍተኛ ተስፋ አብርቶታል።
የስኮትላንዱ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ስቲቭ ክላርክ ከጨዋታው በፊት እንደተናገሩት፣ በቅርቡ በተደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ላይ ድንቅ ብቃት ያሳየውን ራያን ክሪስቲን አስቀምጦ ጆን ማክጊንን በቋሚነት ማሰለፍ "በህይወቴ ከወሰንኳቸው ውሳኔዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ነበር" ብለው ነበር። ሆኖም የ31 ዓመቱ ማክጊን የአሰልጣኙን እምነት እና ድፍረት ወደ ሜዳ አውርዶ... በተግባር ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን በማስመስከር የሀገሩን ባለውለታነት ተወጥቷል።
ምንም እንኳን ስኮትላንዶች ጨዋታውን በንቃት ቢጀምሩም፣ ቀሪው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ግን ያሰቡትን ያህል አልጋ በአልጋ አልነበረም። ስኮትላንድ ኳስ በመቆጣጠር በኩል እጅግ ደካማ የነበረች ሲሆን፣ በተቃራኒው የካሪቢያኗ አገር ሃይቲ ወደ ግብ ክልል በርካታ አደገኛ ኳሶችን በማሻማት የፈጠረችው ጫና የስታዲየሙን ድባብ በጭንቀት አውጦት ነበር። በዚህም ምክንያት፣ በውድድሩ በዕድሜ አንጋፋ ከሆነው የ43 ዓመቱ ክሬግ ጎርደን ተመራጭ ሆኖ በቋሚነት የተሰለፈው ግብ ጠባቂው አንገስ ገን ከፍተኛ የትኩረት ፈተና ውስጥ ወድቆ አምሽቷል። ይህ የጭንቀት ስሜት በስኮትላንድ ደጋፊዎች አእምሮ ውስጥ ቀደም ሲል በኮስታሪካ፣ ኢራን እና ፔሩ ላይ የደረሱባቸውን ታሪካዊ ውድቀቶች ዳግም እንዲያስታውሱ አድርጓቸው ነበር።
በእርግጥ ጆን ማክጊን ጨዋታው ሊጠናቀቅ 20 ደቂቃዎች ሲቀሩት ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ ወደ ውጭ ቢሰድም፣ ቡድኑ እጅግ በፈለገው ወሳኝ ሰዓት ግን በውበት የታጀበ ባይሆንም እንኳ፣ "ሚትቦል" በሚለው ቅጽል ስሙ የሚጠራው ማክጊን ማሸነፊያዋን ወርቃማ ግብ አስቆጥሮ ለሀገሩ የድነት ብርሃን ሆኗል። በሌላ በኩል ጫና በበዛበት በዚህ ጨዋታ ላይ የቦርንማውዙ የመስመር አጥቂ ቤን ዶክ በቀኝ መስመር የሃይቲን ተከላካዮች ሲያምስ እና ሲፈትናቸው የነበረው አጓጊ ብቃት ሌላኛው የጨዋታው ድምቀት ነበር። ጨዋታው ገና ያለ ግብ እኩል በነበረበት ሰዓት ስኮት ማክቶሚናይ የመታው ኃይለኛ ኳስ የግቡን አግዳሚ ገጭቶ ሲመለስ፣ የፊት መስመር አጥቂዎቹ ቼ አዳምስ እና ላውረንስ ሻንክላንድ ግን በጨዋታው ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ ለማድረግ ተቸግረው ታይተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሃይቲዎች በኩል ፍራንትዝዲ ፒዬሮ በግንባሩ የገጨው እና ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣበት አደገኛ ሙከራ የስኮትላንድን ደጋፊዎች ልብ ያቆመ ክስተት ነበር።
"የተለየ" ሳምንት እያሳለፉ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኝ ክላርክ በውጤቱ እጅግ ቢደሰቱም.. ቡድናቸው በሜዳ ላይ ባሳየው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ግን ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። ምሽት ላይ 1 ለ 1 የተለያዩትን ብራዚልን እና ሞሮኮን በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያስተናግዱት ስኮትላንዶች፣ የፊታችን አርብ፣ ሰኔ 19 ወደ ቦስተን ተመልሰው ከሞሮኮ ጋር ከባድ ፍልሚያቸውን ያደርጋሉ። በቀጣይ ከሚያደርጓቸው ሁለት የምድብ ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ማሳካት ወደ ቀጣዩ ዙር እንደሚያሳልፋቸው ቢያውቁም፣ ይህ አሁን ያሳዩት ወላዋይ አቋም ግን ከታላላቆቹ ተጋጣሚዎቻቸው ጋር ቢገጥሙ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍላቸው እንደሚችል ተንታኞች አስጠንቅቀዋል።
የስኮትላንዱ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ስቲቭ ክላርክ ከጨዋታው በፊት እንደተናገሩት፣ በቅርቡ በተደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ላይ ድንቅ ብቃት ያሳየውን ራያን ክሪስቲን አስቀምጦ ጆን ማክጊንን በቋሚነት ማሰለፍ "በህይወቴ ከወሰንኳቸው ውሳኔዎች ሁሉ እጅግ ከባዱ ነበር" ብለው ነበር። ሆኖም የ31 ዓመቱ ማክጊን የአሰልጣኙን እምነት እና ድፍረት ወደ ሜዳ አውርዶ... በተግባር ትክክለኛ ውሳኔ መሆኑን በማስመስከር የሀገሩን ባለውለታነት ተወጥቷል።
ምንም እንኳን ስኮትላንዶች ጨዋታውን በንቃት ቢጀምሩም፣ ቀሪው የጨዋታው ክፍለ ጊዜ ግን ያሰቡትን ያህል አልጋ በአልጋ አልነበረም። ስኮትላንድ ኳስ በመቆጣጠር በኩል እጅግ ደካማ የነበረች ሲሆን፣ በተቃራኒው የካሪቢያኗ አገር ሃይቲ ወደ ግብ ክልል በርካታ አደገኛ ኳሶችን በማሻማት የፈጠረችው ጫና የስታዲየሙን ድባብ በጭንቀት አውጦት ነበር። በዚህም ምክንያት፣ በውድድሩ በዕድሜ አንጋፋ ከሆነው የ43 ዓመቱ ክሬግ ጎርደን ተመራጭ ሆኖ በቋሚነት የተሰለፈው ግብ ጠባቂው አንገስ ገን ከፍተኛ የትኩረት ፈተና ውስጥ ወድቆ አምሽቷል። ይህ የጭንቀት ስሜት በስኮትላንድ ደጋፊዎች አእምሮ ውስጥ ቀደም ሲል በኮስታሪካ፣ ኢራን እና ፔሩ ላይ የደረሱባቸውን ታሪካዊ ውድቀቶች ዳግም እንዲያስታውሱ አድርጓቸው ነበር።
በእርግጥ ጆን ማክጊን ጨዋታው ሊጠናቀቅ 20 ደቂቃዎች ሲቀሩት ያገኘውን ግሩም አጋጣሚ ወደ ውጭ ቢሰድም፣ ቡድኑ እጅግ በፈለገው ወሳኝ ሰዓት ግን በውበት የታጀበ ባይሆንም እንኳ፣ "ሚትቦል" በሚለው ቅጽል ስሙ የሚጠራው ማክጊን ማሸነፊያዋን ወርቃማ ግብ አስቆጥሮ ለሀገሩ የድነት ብርሃን ሆኗል። በሌላ በኩል ጫና በበዛበት በዚህ ጨዋታ ላይ የቦርንማውዙ የመስመር አጥቂ ቤን ዶክ በቀኝ መስመር የሃይቲን ተከላካዮች ሲያምስ እና ሲፈትናቸው የነበረው አጓጊ ብቃት ሌላኛው የጨዋታው ድምቀት ነበር። ጨዋታው ገና ያለ ግብ እኩል በነበረበት ሰዓት ስኮት ማክቶሚናይ የመታው ኃይለኛ ኳስ የግቡን አግዳሚ ገጭቶ ሲመለስ፣ የፊት መስመር አጥቂዎቹ ቼ አዳምስ እና ላውረንስ ሻንክላንድ ግን በጨዋታው ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ ለማድረግ ተቸግረው ታይተዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሃይቲዎች በኩል ፍራንትዝዲ ፒዬሮ በግንባሩ የገጨው እና ለጥቂት ወደ ውጭ የወጣበት አደገኛ ሙከራ የስኮትላንድን ደጋፊዎች ልብ ያቆመ ክስተት ነበር።
"የተለየ" ሳምንት እያሳለፉ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኝ ክላርክ በውጤቱ እጅግ ቢደሰቱም.. ቡድናቸው በሜዳ ላይ ባሳየው አጠቃላይ እንቅስቃሴ ግን ከፍተኛ ስጋት አድሮባቸዋል። ምሽት ላይ 1 ለ 1 የተለያዩትን ብራዚልን እና ሞሮኮን በቀጣይ ጨዋታዎች የሚያስተናግዱት ስኮትላንዶች፣ የፊታችን አርብ፣ ሰኔ 19 ወደ ቦስተን ተመልሰው ከሞሮኮ ጋር ከባድ ፍልሚያቸውን ያደርጋሉ። በቀጣይ ከሚያደርጓቸው ሁለት የምድብ ጨዋታዎች አንድ ነጥብ ማሳካት ወደ ቀጣዩ ዙር እንደሚያሳልፋቸው ቢያውቁም፣ ይህ አሁን ያሳዩት ወላዋይ አቋም ግን ከታላላቆቹ ተጋጣሚዎቻቸው ጋር ቢገጥሙ ከባድ ዋጋ ሊያስከፍላቸው እንደሚችል ተንታኞች አስጠንቅቀዋል።
1 day ago
ምክክር፦ ብቸኛው የፈተናዎቻችን ማለፊያ
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
1 day ago
የአሜሪካዊው ፋንቱ ማንዶዬ ሞርጋን ፍሪማን በጎ ልብ
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚማርክ ድምፃቸው እና አስደናቂ የትወና ብቃታቸው የሚታወቁት አንጋፋው ተዋናይ ሞርጋን ፍሪማን፣ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ ታዋቂ የሰብዓዊ መብትና የበጎ አድራጎት አምባሳደር መሆናቸው ይነገራል።
የሳቸው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር ያላቸውን ጥልቅ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
ከእነዚህም የጎላ አስተዋፅኦዎቻቸው መካከል በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉት ድጋፍ በዋናነት ይጠቀሳል። አውዳሚ የሆኑ አውሎ ነፋሶች ባስከተሉት አደጋ የተረፉ ሰዎችን ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሮችን በግንባር ቀደምትነት አስተባብረዋል።
በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ በተፈጥሮ አደጋ ለሚጎዱ ሰዎች ፈጣን እርዳታ ለማድረግ "የግሬናዳ የዕርዳታ ፈንድን" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ የነበራቸው ሲሆን፣ ይህ ተቋም አሁን ላይ “ፕላን ኢት ናው” ወደሚባል ዓለም አቀፍ ድርጅት ተሸጋግሯል።
ትምህርት የሌላኛው የበጎ አድራጎት ስራቸው የማዕዘን ድንጋይ ነው። እ.ኤ.አ. በ1991 በሚሲሲፒ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ታዳጊዎች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማስፋፋት ከልጃቸው ጋር በመሆን "የታላሃቺ ሪቨር ፋውንዴሽንን" መስርተዋል። ከዚህም ባሻገር፣ ለእንስሳት ደህንነት ልዩ ጥበቃ የሚያደርጉት ፍሪማን፤ እንደ 'ሚሲሲፒ የእንስሳት አድን ማህበር' ያሉ ድርጅቶችን በመደገፍ እና በእንስሳት ህክምና ኮሌጆች ውስጥ የጥናትና ምርምር ማዕከላትን በገንዘብ በማገዝ ላይ ይገኛሉ።
በእነዚህና መሰል ሰብዓዊ ተነሳሽነቶች፣ ሞርጋን ፍሪማን ተሰሚነታቸው እና ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ከፊልም ኢንዱስትሪው መድረክ እና ከካሜራ ዕይታ ውጭ ጭምር ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚማርክ ድምፃቸው እና አስደናቂ የትወና ብቃታቸው የሚታወቁት አንጋፋው ተዋናይ ሞርጋን ፍሪማን፣ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ ታዋቂ የሰብዓዊ መብትና የበጎ አድራጎት አምባሳደር መሆናቸው ይነገራል።
የሳቸው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር ያላቸውን ጥልቅ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
ከእነዚህም የጎላ አስተዋፅኦዎቻቸው መካከል በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉት ድጋፍ በዋናነት ይጠቀሳል። አውዳሚ የሆኑ አውሎ ነፋሶች ባስከተሉት አደጋ የተረፉ ሰዎችን ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሮችን በግንባር ቀደምትነት አስተባብረዋል።
በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ በተፈጥሮ አደጋ ለሚጎዱ ሰዎች ፈጣን እርዳታ ለማድረግ "የግሬናዳ የዕርዳታ ፈንድን" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ የነበራቸው ሲሆን፣ ይህ ተቋም አሁን ላይ “ፕላን ኢት ናው” ወደሚባል ዓለም አቀፍ ድርጅት ተሸጋግሯል።
ትምህርት የሌላኛው የበጎ አድራጎት ስራቸው የማዕዘን ድንጋይ ነው። እ.ኤ.አ. በ1991 በሚሲሲፒ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ታዳጊዎች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማስፋፋት ከልጃቸው ጋር በመሆን "የታላሃቺ ሪቨር ፋውንዴሽንን" መስርተዋል። ከዚህም ባሻገር፣ ለእንስሳት ደህንነት ልዩ ጥበቃ የሚያደርጉት ፍሪማን፤ እንደ 'ሚሲሲፒ የእንስሳት አድን ማህበር' ያሉ ድርጅቶችን በመደገፍ እና በእንስሳት ህክምና ኮሌጆች ውስጥ የጥናትና ምርምር ማዕከላትን በገንዘብ በማገዝ ላይ ይገኛሉ።
በእነዚህና መሰል ሰብዓዊ ተነሳሽነቶች፣ ሞርጋን ፍሪማን ተሰሚነታቸው እና ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ከፊልም ኢንዱስትሪው መድረክ እና ከካሜራ ዕይታ ውጭ ጭምር ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
1 day ago
አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት ተሰጣት
#ethiopia | ታዋቂዋ እና ተወዳጇ የረጅም ርቀት አትሌት ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሸላሚ ሆናለች።
ይህ የሹመት መርሃ ግብር የተከናወነው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት በዓል ባከበረበት ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው የክብር ስነ ሥርዓት ላይ የፍትህ ሚኒስትሯ ሀና አርዕያ ስላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገር መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ተወካዮች ታድመዋል።
ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የሀገሯን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋ ያወለበለበች መሪ አትሌት ናት።
በአራት የኦሎምፒክ መድረኮች ላይ በመሳተፍ 3 የወርቅ እና 1 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ያስመዘገበች ሲሆን በአጠቃላይ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ከ15 በላይ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገሯ በማበርከት ስሟ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ጀግና ናት።
ይህ አሁን የተሰጣት የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጥ ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ ከጥሩነሽ ዲባባ በተጨማሪ ለሌሎች የሀገር ባለውለታ የሆኑ አንጋፋ ስፖርተኞች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች የዕውቅና እና የሽልማት ስነ ሥርዓት ተካሂዶላቸዋል።
በዚህም መሰረት በአትሌቲክስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ጥቁር አፍሪካዊት የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ የማራቶን ጀግናዋ ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንትና የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እንዲሁም የሦስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ስለሺ ስህን፣ ኮማንደር ሰለሞን ባረጋ እና ምክትል ኮሚሽነር ሰንበሬ ተፈሪ የክብር ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በማሰልጠን ያገለገለው፣ በ7 ኦሎምፒክ እና በ12 የዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ በመሳተፍ በርካታ ስኬታማ አትሌቶችን ያፈራው አዳኙ አሰልጣኝ ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።
በኪነጥበብ ዘርፍም የኮሚሽኑ የሙዚቃና ቴያትር ቡድን አባላት የነበሩት ድምፃዊ ደመረ ለገሰ፣ ድምፃዊ ተፈራ ነጋሽ፣ ድምፃዊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ እንግዳ፣ አርቲስት ፍሬህይወት ስዩም፣ ሳክስፎኒስት ዘሪሁን በለጠ እና ሌሎች ባለሙያዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተገቢው ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
#tiruneshdibaba #athletics #sport #ethiopianathletics #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታዋቂዋ እና ተወዳጇ የረጅም ርቀት አትሌት ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሸላሚ ሆናለች።
ይህ የሹመት መርሃ ግብር የተከናወነው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት በዓል ባከበረበት ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው የክብር ስነ ሥርዓት ላይ የፍትህ ሚኒስትሯ ሀና አርዕያ ስላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገር መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ተወካዮች ታድመዋል።
ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የሀገሯን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋ ያወለበለበች መሪ አትሌት ናት።
በአራት የኦሎምፒክ መድረኮች ላይ በመሳተፍ 3 የወርቅ እና 1 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ያስመዘገበች ሲሆን በአጠቃላይ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ከ15 በላይ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገሯ በማበርከት ስሟ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ጀግና ናት።
ይህ አሁን የተሰጣት የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጥ ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ ከጥሩነሽ ዲባባ በተጨማሪ ለሌሎች የሀገር ባለውለታ የሆኑ አንጋፋ ስፖርተኞች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች የዕውቅና እና የሽልማት ስነ ሥርዓት ተካሂዶላቸዋል።
በዚህም መሰረት በአትሌቲክስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ጥቁር አፍሪካዊት የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ የማራቶን ጀግናዋ ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንትና የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እንዲሁም የሦስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ስለሺ ስህን፣ ኮማንደር ሰለሞን ባረጋ እና ምክትል ኮሚሽነር ሰንበሬ ተፈሪ የክብር ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በማሰልጠን ያገለገለው፣ በ7 ኦሎምፒክ እና በ12 የዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ በመሳተፍ በርካታ ስኬታማ አትሌቶችን ያፈራው አዳኙ አሰልጣኝ ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።
በኪነጥበብ ዘርፍም የኮሚሽኑ የሙዚቃና ቴያትር ቡድን አባላት የነበሩት ድምፃዊ ደመረ ለገሰ፣ ድምፃዊ ተፈራ ነጋሽ፣ ድምፃዊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ እንግዳ፣ አርቲስት ፍሬህይወት ስዩም፣ ሳክስፎኒስት ዘሪሁን በለጠ እና ሌሎች ባለሙያዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተገቢው ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
#tiruneshdibaba #athletics #sport #ethiopianathletics #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተዘረፈ
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ዝግጅት ለማድረግ ፍሎሪዳን ለቀው ካንሳስ ሲቲ እንደደረሱ፣ ባልታሰበ እና አስገራሚ የዘረፋ ወንጀል ሰለባ መሆናቸውን ታዋቂው የዴይሊ ሜይል (Daily Mail) ስፖርት ዘግቧል።
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በካንሳስ ሲቲ የመጀመሪያ የልምምድ ፕሮግራማቸውን ከማድረጋቸው በፊት፣ ቁሳቁሶቻቸውን ጭኖ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ሲጓዝ የነበረው መኪና ላይ “ዘረፋ” ተፈጽሟል።
በዚህም ምክንያት የቡድኑ ትልልቅ ኮከቦች (ሃሪ ኬን እና ጁድ ቤሊንግሃምን ጨምሮ) ለጨዋታ የሚጠቀሙባቸው የግል ጫማዎች፣ ለዓለም ዋንጫው የተዘጋጁ ልዩ ኳሶች እና ለልምምድ የሚያገለግሉ ትጥቆችና የተለያዩ ቁሳቁሶች ተሰርቀውባቸዋል።
ረቡዕ ዕለት ከክሮሺያ ጋር ለሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ ዝግጅት እያደረገ ለነበረው እና በቶማስ ቱሄል ለሚመራው የእንግሊዝ ስብስብ ይህ ትልቅ መስተጓጎል እና ራስ ምታት ሆኖባቸዋል።
የቡድኑ የደኅንነት ሠራተኞች ጥርጣሬና ምርመራ ያተኮረው እቃዎቹን እንዲያጓጉዙ ታምነው በተቀጠሩት አሽከርካሪዎች ላይ ሲሆን፣ ጉዳዩን የአካባቢው ፖሊስ በጥብቅ እየመረመረው ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር መዋሉም ተገልጿል።
ዘረፋውን አስደንጋጅ ያደረገው መኪናው ውስጥ ከተጫኑት በርካታ የልምምድ ኳሶች መካከል የተረፈችው “አንድ ኳስ ብቻ” መሆኗ ነው! የቱሄል ታክቲክ መጻፊያ ሰሌዳዎች እና የማሳጅ ጠረጴዛዎችም አብረው ተዘርፈዋል።
የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር (FA) እቃዎቹን ለማስመለስ ከካንሳስ ሲቲ ፖሊስ ጋር በቅርብ እየሠራ ቢሆንም፣ የልምምድ ሰዓቱ ስለደረሰ ሰራተኞቹ የተሰረቁትን እቃዎች በአስቸኳይ ለመተካት እና ፍለጋውን ለማፋጠን ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ገብተው ታይተዋል።
የቀድሞ ተጨዋችና የአሁኑ የእግር ኳስ ተንታኝ ጋሪ ሊንከር በአንድ ወቅት “እግር ኳስ ቀላል ጨዋታ ናት፤ መጨረሻ ላይ ግን ሁሌም ጀርመኖች ያሸንፋሉ” ብሎ ነበር... አሁን ግን ጀርመናዊው ቱሄል ጨዋታው ሳይጀመር ጫማ ፍለጋ ላይ ናችው።
ምንጭ፦ Daily Mail Sport
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫው የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ዝግጅት ለማድረግ ፍሎሪዳን ለቀው ካንሳስ ሲቲ እንደደረሱ፣ ባልታሰበ እና አስገራሚ የዘረፋ ወንጀል ሰለባ መሆናቸውን ታዋቂው የዴይሊ ሜይል (Daily Mail) ስፖርት ዘግቧል።
የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በካንሳስ ሲቲ የመጀመሪያ የልምምድ ፕሮግራማቸውን ከማድረጋቸው በፊት፣ ቁሳቁሶቻቸውን ጭኖ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ሲጓዝ የነበረው መኪና ላይ “ዘረፋ” ተፈጽሟል።
በዚህም ምክንያት የቡድኑ ትልልቅ ኮከቦች (ሃሪ ኬን እና ጁድ ቤሊንግሃምን ጨምሮ) ለጨዋታ የሚጠቀሙባቸው የግል ጫማዎች፣ ለዓለም ዋንጫው የተዘጋጁ ልዩ ኳሶች እና ለልምምድ የሚያገለግሉ ትጥቆችና የተለያዩ ቁሳቁሶች ተሰርቀውባቸዋል።
ረቡዕ ዕለት ከክሮሺያ ጋር ለሚያደርጉት የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ ዝግጅት እያደረገ ለነበረው እና በቶማስ ቱሄል ለሚመራው የእንግሊዝ ስብስብ ይህ ትልቅ መስተጓጎል እና ራስ ምታት ሆኖባቸዋል።
የቡድኑ የደኅንነት ሠራተኞች ጥርጣሬና ምርመራ ያተኮረው እቃዎቹን እንዲያጓጉዙ ታምነው በተቀጠሩት አሽከርካሪዎች ላይ ሲሆን፣ ጉዳዩን የአካባቢው ፖሊስ በጥብቅ እየመረመረው ይገኛል። በአሁኑ ሰዓት አንድ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር መዋሉም ተገልጿል።
ዘረፋውን አስደንጋጅ ያደረገው መኪናው ውስጥ ከተጫኑት በርካታ የልምምድ ኳሶች መካከል የተረፈችው “አንድ ኳስ ብቻ” መሆኗ ነው! የቱሄል ታክቲክ መጻፊያ ሰሌዳዎች እና የማሳጅ ጠረጴዛዎችም አብረው ተዘርፈዋል።
የእንግሊዝ እግር ኳስ ማኅበር (FA) እቃዎቹን ለማስመለስ ከካንሳስ ሲቲ ፖሊስ ጋር በቅርብ እየሠራ ቢሆንም፣ የልምምድ ሰዓቱ ስለደረሰ ሰራተኞቹ የተሰረቁትን እቃዎች በአስቸኳይ ለመተካት እና ፍለጋውን ለማፋጠን ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ገብተው ታይተዋል።
የቀድሞ ተጨዋችና የአሁኑ የእግር ኳስ ተንታኝ ጋሪ ሊንከር በአንድ ወቅት “እግር ኳስ ቀላል ጨዋታ ናት፤ መጨረሻ ላይ ግን ሁሌም ጀርመኖች ያሸንፋሉ” ብሎ ነበር... አሁን ግን ጀርመናዊው ቱሄል ጨዋታው ሳይጀመር ጫማ ፍለጋ ላይ ናችው።
ምንጭ፦ Daily Mail Sport
1 day ago
የትግራይ ኃይሎች ከኤርትራ ጋር በማበር አዲስ ጥቃት ለመሰንዘር አቅደዋል ተባለ
ኢትዮጵያ በትግራይ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ግንባር (ትህነግ) ውስጥ የሚገኙ አክራሪ አቋም ያላቸው አካላት በፌዴራል መንግሥቱ ላይ አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ለመሰንዘር እየተዘጋጁ ነው ስትል መክሰሰሷን ሶማሊ ሪፖርት ዘግቧል።
ይህ እቅድ አውዳሚውን የትግራይ ጦርነት ተከትሎ የተገኘውን ደካማ ሰላም አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል መንግሥት አስጠንቅቋል። በአልጀዚራ በተሰማው መረጃ መሰረት፥ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የትህነግ መሪዎች ከጎረቤት ኤርትራ በሚያገኙት ድጋፍ በመታገዝ በሚቀጥሉት ቀናት ጥቃት ለመሰንዘር እያቀዱ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ክስ የቀረበው የ600 ሺህ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውን የሁለት ዓመት ጦርነት ያቆመውን የ2022ቱን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በመጣስ ቡድኑ አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ እየሞከረ ባለበት ወቅት ነው ተብሏል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ትህነግን በፌዴራል መንግሥት የሚደገፈውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ፣ በምትኩ ሕገ-ወጥ የተባለ ክልላዊ አስተዳደር አቋቁሟል ስትል ከሳለች። ይህ ውንጀላ የመጣው ትህነግ ቀደም ሲል ታግዶ የነበረውን የክልል ምክር ቤት መልሶ ለማቋቋም ከወሰነ በኋላ ቢሆንም፥ ቡድኑ እስካሁን ለቀረበበት ክስ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም
በአዲስ አበባና በአስመራ መካከል ያለው ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተበላሸ መምጣቱ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚቀሰቀስ አዲስ አለመረጋጋት ለአጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ ሰፊ አንድምታ ሊኖረው ይችላል የሚል ሥጋት ፈጥሯል። ማንኛውም ዓይነት ወደ ከፍተኛ ውጊያ መመለስ አሁን ያለውን ተጋላጭ የሰላም ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥልና ቀጠናውን መልሶ ወደ አስከፊ ግጭት ውስጥ የመክተት ዕድል እንዳለው ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
ኢትዮጵያ በትግራይ ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ግንባር (ትህነግ) ውስጥ የሚገኙ አክራሪ አቋም ያላቸው አካላት በፌዴራል መንግሥቱ ላይ አዲስ ወታደራዊ ጥቃት ለመሰንዘር እየተዘጋጁ ነው ስትል መክሰሰሷን ሶማሊ ሪፖርት ዘግቧል።
ይህ እቅድ አውዳሚውን የትግራይ ጦርነት ተከትሎ የተገኘውን ደካማ ሰላም አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል መንግሥት አስጠንቅቋል። በአልጀዚራ በተሰማው መረጃ መሰረት፥ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የትህነግ መሪዎች ከጎረቤት ኤርትራ በሚያገኙት ድጋፍ በመታገዝ በሚቀጥሉት ቀናት ጥቃት ለመሰንዘር እያቀዱ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ ክስ የቀረበው የ600 ሺህ ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውን የሁለት ዓመት ጦርነት ያቆመውን የ2022ቱን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በመጣስ ቡድኑ አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ እየሞከረ ባለበት ወቅት ነው ተብሏል። በተጨማሪም ኢትዮጵያ ትህነግን በፌዴራል መንግሥት የሚደገፈውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በማፍረስ፣ በምትኩ ሕገ-ወጥ የተባለ ክልላዊ አስተዳደር አቋቁሟል ስትል ከሳለች። ይህ ውንጀላ የመጣው ትህነግ ቀደም ሲል ታግዶ የነበረውን የክልል ምክር ቤት መልሶ ለማቋቋም ከወሰነ በኋላ ቢሆንም፥ ቡድኑ እስካሁን ለቀረበበት ክስ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም
በአዲስ አበባና በአስመራ መካከል ያለው ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተበላሸ መምጣቱ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚቀሰቀስ አዲስ አለመረጋጋት ለአጠቃላይ የአፍሪካ ቀንድ ሰፊ አንድምታ ሊኖረው ይችላል የሚል ሥጋት ፈጥሯል። ማንኛውም ዓይነት ወደ ከፍተኛ ውጊያ መመለስ አሁን ያለውን ተጋላጭ የሰላም ሂደት አደጋ ላይ እንደሚጥልና ቀጠናውን መልሶ ወደ አስከፊ ግጭት ውስጥ የመክተት ዕድል እንዳለው ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የካርሎ አንቸሎቲ የጋዜጣዊ መግለጫ ሊጠናቀቅ ሲል.. ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ሁሌም በሚታወቁበት የሰከነ እና ጥልቅ በሆነ መንገድ ማንም ሊያነሳው ያልደፈረውን ጉዳይ አንስተው መናገር ጀመሩ። በግንቦት ወር መገባደጃ ላይ ብራዚል ከፓናማ ጋር ለምታደርገው የወዳጅነት ጨዋታ አስቀድሞ፣ አዲሱ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አንቸሎቲ እንዲህ አሉ፡...
"ሰዎች አሁን ላይ ብራዚል ኮከብ ተጫዋች የላትም ሲሉ እሰማለሁ። ምናልባት እውነት ሊሆን ይችላል። እንደ ፔሌ፣ ሮማሪዮ ወይም ሮናልዶ አይነት ተጫዋች ላይኖረን ይችላል፤ ነገር ግን የጋራ ኃላፊነት ስሜት ሊኖረን ይችላል፣ ያ ደግሞ እጅግ ኃይለኛ መሳሪያ ነው።"
ይህ የአንቸሎቲ ንግግር የብዙዎችን ቀልብ የሳበው፣ የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሽየስ ጁኒየር እስካሁን ድረስ የብሔራዊ ቡድኑ የማይነካ መሪ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ... በተግባር ግን ያ ባለመሆኑ ነው። በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በክሮኤሺያ በመለያ ምት ተሸንፈው ከወጡ ከአራት ዓመታት በኋላም.... በ25 ዓመቱ አጥቂ ላይ አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ይህ ጥርጣሬ ምን ያህል ከፍ እንዳለ ለማሳየት... በመጋቢት ወር ብራዚል በፈረንሳይ 2ለ1 መሸነፏን ተከትሎ፣ በሀገሪቱ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ "ቪኒሽየስ በመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ይገባዋል ወይ?" የሚል የከረረ ክርክር እስከመክፈት ደርሷል። በክለብ ደረጃ ለቪኒሽየስ እጅግ ስኬታማ ጊዜያትን ያመጣው እና ትልቅ ተጽዕኖ የፈጠረው አንቸሎቲ ብሔራዊ ቡድኑን ቢረከብም፣ "ቪኒሽየስ በሪያል ማድሪድ የሚያሳየውን ድንቅ አቋም ለምን በብሔራዊ ቡድን መድገም አቃተው?" የሚለው ጥያቄ አሁንም እንደ ጥላ እየተከተለው ነው።
በእርግጥም ቪኒሽየስ በዚህ የዓለም ዋንጫ ዑደት ውስጥ በብሔራዊ ቡድኑ ብዙ የግብ ተሳትፎ ያደረገ ተጫዋች ነው፤ ሆኖም በ28 ጨዋታዎች 7 ግቦችን እና 6 አሲስቶችን ብቻ ማስመዝገቡ ለሱ ደረጃ አነስተኛ ነው። በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫዎች የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ የነበረው ክሌበር ዣቪየር ይህንን ሲያብራራ "በክለብ ደረጃ የምታሳየውን አቋም በብሔራዊ ቡድን መድገም እጅግ ከባድ ነው። ክለብ ውስጥ የተለየ ልምምድ፣ የተለየ የጨዋታ መንገድ እና የዕለት ተዕለት ቆይታ አለ። ግልጹ ምሳሌ የሜሲ እና የአርጀንቲና ጉዳይ ነው። ሜሲ ሁሌም ይተች ነበር፣ ሊሳካለት የቻለው በ2022 ነው። ምክንያቱም አርጀንቲና ቡድን መገንባት ስለቻለች ነው። ለተጫዋች ተገቢውን መዋቅር መፍጠር ወሳኝ ነው" ይላል።
ቪኒሽየስም ይህንን እውነታ አይክድም። በቅርቡ ለካዜ ቲቪ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ፣ "በክለብ ውስጥ በየሶስት ቀኑ አዲስ ዕድል አለ። ከ10 ጨዋታዎች ሁለቱን መጥፎ ብጫወት ማንም ብዙ አያወራም። በብሔራዊ ቡድን ግን በአንድ ጨዋታ እና በሌላኛው መካከል ያለው ጊዜ ረጅም ነው፤ ጫናውም ሁልጊዜ ከፍተኛ ነው። ሰዎች ሁሌም በምርጥ አቋሜ ላይ እንድገኝ ይጠብቃሉ። ነገር ግን ወደ ዓለም ዋንጫ ሄጄ አራት ወይም አምስት ግቦችን አግብቼ ሻምፒዮን ብንሆን፣ ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ይቀየራል። ያኔ መጥፎ በተጫወትኩባቸው ጨዋታዎች ላይ እንኳን ለዓለም ዋንጫ እየተዘጋጀሁ እንደነበር አድርገው ያወራሉ" ብሏል።
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን መጫወት ለቪኒሽየስ ቀላል ሆኖ አያውቅም። አንድ የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እንዳሉት፣ የ2024 የባሎን ዶር ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ቪኒሽየስ፣ "ሁሌም ዋናው ተዋናይ የመሆን ከፍተኛ ጉጉት" ያጠቃዋል። ቪኒሽየስ በሙያ ዘመኑ ሁሉ የለመደውም ይሄንኑ የዋና ተዋናይነት ቦታ ነው።
ወደ ሁለተኛው የዓለም ዋንጫው ሲያቀና... ቪኒሽየስ 14 የንግድ ስምምነቶች ያሉት ሲሆን፣ ይህ ከማንኛውም ብራዚላዊ ተጫዋች የላቀ ነው። ከሜዳ ውጪ ይህ ሁሉ ስኬት ቢኖረውም፣ አሁንም ድረስ ኔማር ከብራዚል እግር ኳስ አፍቃሪ ህዝብ ጋር ያለውን አይነት ጥልቅ ስሜታዊ ቁርኝት እና ፍቅር ማግኘት አልቻለም። ይህ ሁኔታ እጅግ አስገራሚ ነው፤ አንደኛው (ኔማር) ኮከብነቱ እያለፈ ቢሆንም አሁንም በህዝቡ ልብ ውስጥ አለ፤ ሌላኛው (ቪኒሽየስ) ደግሞ በብቃቱ ጣሪያ ላይ ቢሆንም ያንን የህዝብ ፍቅር አላገኘም።
የግብይት ባለሙያ እና የቀድሞው የኔማር አማካሪ ኤድዋርዶ ሙሳ ይህንን ሲያብራራ፣ "ቪኒሽየስ በብራዚል ደጋፊዎች ይወደዳል፤ ነገር ግን እንደ ኔማር አይደለም። ኔማር አስቀድሞ በብሔራዊ ቡድኑ ግልጽ የሆነ ታሪክ (Legacy) ሰርቷል፤ የዘመናት ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ቪኒሽየስ ግን በሪያል ማድሪድ ያሳየውን ብቃት በብሔራዊ ቡድን ገና አላሳየም። ሌላው ነጥብ፣ ኔማር በሳንቶስ ቆይታው ብራዚላውያን በየሳምንቱ አስደናቂ ብቃቱን ይመለከቱ ነበር። ቪኒሽየስ ግን በፍላሜንጎ ቋሚ ተሰላፊ እንኳ ሳይሆን ነው በልጅነቱ ሀገር ለቆ የወጣው" ይላል።
ዳታፎልሃ የተሰኘው የብራዚል የምርምር ተቋም ባወጣው መረጃ፣ አሁንም 53 በመቶ የሚሆኑ ደጋፊዎች አንጋፋው ኔማር በዓለም ዋንጫው ስኳድ ውስጥ መካተቱን ይደግፋሉ።
"አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው"
የብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቪኒሽየስን የብሔራዊ ቡድኑ ማዕከል ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጓል። ባለፈው መጋቢት ወር ሮድሪጎ በጉዳት ከዓለም ዋንጫው ውጪ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ዝነኛዋን ቁጥር 10 ማልያ ለቪኒሽየስ ሰጥተውት ነበር። ዓላማው ግልጽ ነበር... ቪኒሽየስ የብራዚል ፊት እንዲሆን ማድረግ። ነገር ግን ኔማር ባልተጠበቀ ሁኔታ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ሲመለስ፣ የ34 ዓመቱ የሳንቶስ አጥቂ ዳግም የቁጥር 10 ማልያውን ተረክቧል።
ምንም እንኳን ኔማር ማልያውን ቢወስድም፣...በቅርብ ጊዜያት እያስተናገደው ያለው ተደጋጋሚ የአካል ብቃት ችግር ቀድሞ ይጣልበት የነበረውን ተስፋ አደብዝዞታል። አሁን የብዙዎች አይን ያረፈው ቪኒሽየስ ላይ ነው። ብራዚል 6ኛዋን የዓለም ዋንጫ ለማንሳት በምታደርገው ጉዞ ላይ ቪኒሽየስ የጥርጣሬ ደመናን ገፎ ደምቆ መውጣት ይኖርበታል።
ቪኒሽየስም ለዚህ የትኩረት ማዕከልነት ዝግጁ መሆኑን ይናገራል። "አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው፤ ምክንያቱም በሪያል ማድሪድ አምስት ወይም ስድስት ምርጥ የውድድር ዘመናትን አሳልፌያለሁ፣ ከዓለማችን ምርጥ ተጫዋቾች ተርታም ተሰልፌያለሁ። ይህ ደግሞ በተፈጥሮ ተጨማሪ ኃላፊነት ያመጣል። እኔም የምፈልገው ይሄንኑ ኃላፊነት ነው። አቅሜ የት ድረስ እንደሆነ አውቃለሁ፤ ምክንያቱም የኔ ጣሪያ ሁሌም በጣም ከፍተኛ ነው" በማለት ቆራጥነቱን አሳይቷል። ይህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሽየስ የብራዚል ደጋፊዎችን ልብ ሙሉ በሙሉ የሚያሸንፍበት ይሆን? ጊዜ የሚመልሰው ይሆናል።
"ሰዎች አሁን ላይ ብራዚል ኮከብ ተጫዋች የላትም ሲሉ እሰማለሁ። ምናልባት እውነት ሊሆን ይችላል። እንደ ፔሌ፣ ሮማሪዮ ወይም ሮናልዶ አይነት ተጫዋች ላይኖረን ይችላል፤ ነገር ግን የጋራ ኃላፊነት ስሜት ሊኖረን ይችላል፣ ያ ደግሞ እጅግ ኃይለኛ መሳሪያ ነው።"
ይህ የአንቸሎቲ ንግግር የብዙዎችን ቀልብ የሳበው፣ የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሽየስ ጁኒየር እስካሁን ድረስ የብሔራዊ ቡድኑ የማይነካ መሪ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ... በተግባር ግን ያ ባለመሆኑ ነው። በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በክሮኤሺያ በመለያ ምት ተሸንፈው ከወጡ ከአራት ዓመታት በኋላም.... በ25 ዓመቱ አጥቂ ላይ አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ይህ ጥርጣሬ ምን ያህል ከፍ እንዳለ ለማሳየት... በመጋቢት ወር ብራዚል በፈረንሳይ 2ለ1 መሸነፏን ተከትሎ፣ በሀገሪቱ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ "ቪኒሽየስ በመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ይገባዋል ወይ?" የሚል የከረረ ክርክር እስከመክፈት ደርሷል። በክለብ ደረጃ ለቪኒሽየስ እጅግ ስኬታማ ጊዜያትን ያመጣው እና ትልቅ ተጽዕኖ የፈጠረው አንቸሎቲ ብሔራዊ ቡድኑን ቢረከብም፣ "ቪኒሽየስ በሪያል ማድሪድ የሚያሳየውን ድንቅ አቋም ለምን በብሔራዊ ቡድን መድገም አቃተው?" የሚለው ጥያቄ አሁንም እንደ ጥላ እየተከተለው ነው።
በእርግጥም ቪኒሽየስ በዚህ የዓለም ዋንጫ ዑደት ውስጥ በብሔራዊ ቡድኑ ብዙ የግብ ተሳትፎ ያደረገ ተጫዋች ነው፤ ሆኖም በ28 ጨዋታዎች 7 ግቦችን እና 6 አሲስቶችን ብቻ ማስመዝገቡ ለሱ ደረጃ አነስተኛ ነው። በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫዎች የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ የነበረው ክሌበር ዣቪየር ይህንን ሲያብራራ "በክለብ ደረጃ የምታሳየውን አቋም በብሔራዊ ቡድን መድገም እጅግ ከባድ ነው። ክለብ ውስጥ የተለየ ልምምድ፣ የተለየ የጨዋታ መንገድ እና የዕለት ተዕለት ቆይታ አለ። ግልጹ ምሳሌ የሜሲ እና የአርጀንቲና ጉዳይ ነው። ሜሲ ሁሌም ይተች ነበር፣ ሊሳካለት የቻለው በ2022 ነው። ምክንያቱም አርጀንቲና ቡድን መገንባት ስለቻለች ነው። ለተጫዋች ተገቢውን መዋቅር መፍጠር ወሳኝ ነው" ይላል።
ቪኒሽየስም ይህንን እውነታ አይክድም። በቅርቡ ለካዜ ቲቪ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ፣ "በክለብ ውስጥ በየሶስት ቀኑ አዲስ ዕድል አለ። ከ10 ጨዋታዎች ሁለቱን መጥፎ ብጫወት ማንም ብዙ አያወራም። በብሔራዊ ቡድን ግን በአንድ ጨዋታ እና በሌላኛው መካከል ያለው ጊዜ ረጅም ነው፤ ጫናውም ሁልጊዜ ከፍተኛ ነው። ሰዎች ሁሌም በምርጥ አቋሜ ላይ እንድገኝ ይጠብቃሉ። ነገር ግን ወደ ዓለም ዋንጫ ሄጄ አራት ወይም አምስት ግቦችን አግብቼ ሻምፒዮን ብንሆን፣ ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ይቀየራል። ያኔ መጥፎ በተጫወትኩባቸው ጨዋታዎች ላይ እንኳን ለዓለም ዋንጫ እየተዘጋጀሁ እንደነበር አድርገው ያወራሉ" ብሏል።
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን መጫወት ለቪኒሽየስ ቀላል ሆኖ አያውቅም። አንድ የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እንዳሉት፣ የ2024 የባሎን ዶር ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ቪኒሽየስ፣ "ሁሌም ዋናው ተዋናይ የመሆን ከፍተኛ ጉጉት" ያጠቃዋል። ቪኒሽየስ በሙያ ዘመኑ ሁሉ የለመደውም ይሄንኑ የዋና ተዋናይነት ቦታ ነው።
ወደ ሁለተኛው የዓለም ዋንጫው ሲያቀና... ቪኒሽየስ 14 የንግድ ስምምነቶች ያሉት ሲሆን፣ ይህ ከማንኛውም ብራዚላዊ ተጫዋች የላቀ ነው። ከሜዳ ውጪ ይህ ሁሉ ስኬት ቢኖረውም፣ አሁንም ድረስ ኔማር ከብራዚል እግር ኳስ አፍቃሪ ህዝብ ጋር ያለውን አይነት ጥልቅ ስሜታዊ ቁርኝት እና ፍቅር ማግኘት አልቻለም። ይህ ሁኔታ እጅግ አስገራሚ ነው፤ አንደኛው (ኔማር) ኮከብነቱ እያለፈ ቢሆንም አሁንም በህዝቡ ልብ ውስጥ አለ፤ ሌላኛው (ቪኒሽየስ) ደግሞ በብቃቱ ጣሪያ ላይ ቢሆንም ያንን የህዝብ ፍቅር አላገኘም።
የግብይት ባለሙያ እና የቀድሞው የኔማር አማካሪ ኤድዋርዶ ሙሳ ይህንን ሲያብራራ፣ "ቪኒሽየስ በብራዚል ደጋፊዎች ይወደዳል፤ ነገር ግን እንደ ኔማር አይደለም። ኔማር አስቀድሞ በብሔራዊ ቡድኑ ግልጽ የሆነ ታሪክ (Legacy) ሰርቷል፤ የዘመናት ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ቪኒሽየስ ግን በሪያል ማድሪድ ያሳየውን ብቃት በብሔራዊ ቡድን ገና አላሳየም። ሌላው ነጥብ፣ ኔማር በሳንቶስ ቆይታው ብራዚላውያን በየሳምንቱ አስደናቂ ብቃቱን ይመለከቱ ነበር። ቪኒሽየስ ግን በፍላሜንጎ ቋሚ ተሰላፊ እንኳ ሳይሆን ነው በልጅነቱ ሀገር ለቆ የወጣው" ይላል።
ዳታፎልሃ የተሰኘው የብራዚል የምርምር ተቋም ባወጣው መረጃ፣ አሁንም 53 በመቶ የሚሆኑ ደጋፊዎች አንጋፋው ኔማር በዓለም ዋንጫው ስኳድ ውስጥ መካተቱን ይደግፋሉ።
"አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው"
የብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቪኒሽየስን የብሔራዊ ቡድኑ ማዕከል ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጓል። ባለፈው መጋቢት ወር ሮድሪጎ በጉዳት ከዓለም ዋንጫው ውጪ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ዝነኛዋን ቁጥር 10 ማልያ ለቪኒሽየስ ሰጥተውት ነበር። ዓላማው ግልጽ ነበር... ቪኒሽየስ የብራዚል ፊት እንዲሆን ማድረግ። ነገር ግን ኔማር ባልተጠበቀ ሁኔታ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ሲመለስ፣ የ34 ዓመቱ የሳንቶስ አጥቂ ዳግም የቁጥር 10 ማልያውን ተረክቧል።
ምንም እንኳን ኔማር ማልያውን ቢወስድም፣...በቅርብ ጊዜያት እያስተናገደው ያለው ተደጋጋሚ የአካል ብቃት ችግር ቀድሞ ይጣልበት የነበረውን ተስፋ አደብዝዞታል። አሁን የብዙዎች አይን ያረፈው ቪኒሽየስ ላይ ነው። ብራዚል 6ኛዋን የዓለም ዋንጫ ለማንሳት በምታደርገው ጉዞ ላይ ቪኒሽየስ የጥርጣሬ ደመናን ገፎ ደምቆ መውጣት ይኖርበታል።
ቪኒሽየስም ለዚህ የትኩረት ማዕከልነት ዝግጁ መሆኑን ይናገራል። "አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው፤ ምክንያቱም በሪያል ማድሪድ አምስት ወይም ስድስት ምርጥ የውድድር ዘመናትን አሳልፌያለሁ፣ ከዓለማችን ምርጥ ተጫዋቾች ተርታም ተሰልፌያለሁ። ይህ ደግሞ በተፈጥሮ ተጨማሪ ኃላፊነት ያመጣል። እኔም የምፈልገው ይሄንኑ ኃላፊነት ነው። አቅሜ የት ድረስ እንደሆነ አውቃለሁ፤ ምክንያቱም የኔ ጣሪያ ሁሌም በጣም ከፍተኛ ነው" በማለት ቆራጥነቱን አሳይቷል። ይህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሽየስ የብራዚል ደጋፊዎችን ልብ ሙሉ በሙሉ የሚያሸንፍበት ይሆን? ጊዜ የሚመልሰው ይሆናል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና)አሜሪካና ኢራን በ24 ሰአታት ውስጥ የሰላም ስምምነት እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች፡፡ የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሻህባዝ ሸሪፍ በአሜሪካና በኢራን መካከል ስምምነቱ በ24 ሰአታት ውስጥ እንደሚከናወን ገለፁ፡፡ ሚኒስትሩ በኤክስ ገፃቸው ላይ ‹‹ለወራት የዘለቀውን የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ለማስቆም በሚችለው የሰላም ረቂቅ አሜሪካና ኢራን ስምምነት ላይ ደርሰዋል›› ያሉ ሲሆን ፓኪስታን አሁን የኤሌክትሮኒክስ መፈራረሚያ ሰነድ እያዘጋጀች እንደምትገኝ አስታውቀዋል፡፡
በኤሌክትሮኒክስ የሚደረገው ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት 24 ሰአታት ውስጥ እንደሚፈረም ገልፀውም በመጪው ሳምንት ደግሞ በከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል የቴክኒክ ውይይቱ እንደሚጀመር አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ሁለቱም አገራት በቀጠናውና በአለም ሰላም እንዲመጣ በድርድሩ ወቅት ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው ደግሞ አሜሪካና ኢራን በነገው እለት በከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል በስምምነት ሰነዱ ላይ ይፈራረማሉ፡፡
በዚህ የፊርማ ስነስርአት ከአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንቱ ጄዲ ቫንስ እንደሚገኙና ከኢራን በኩል ደግሞ የፓርላማ አፈጉባኤው መሀመድ ባክር ጋሊባፍ እንደሚወከሉ የጠቀሰው ዘገባው የፊርማው ቦታ ምናልባትም ጄኔቭ እንደሚሆን አስረድቷል፡፡ የስምምነት ሰነዱ ምን እንዳካተተ የተባለ ነገር የለም፡፡ ይሁን እንጂ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አግካራቺ በአገራቸው ቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር ‹‹በስምምነቱ ስትራቴጂያዊ ስኬት አግኝተናል፡፡ በጦርነቱ ኢራን አሸንፋለች›› በማለት አስታውቀዋል፡፡
በኤሌክትሮኒክስ የሚደረገው ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት 24 ሰአታት ውስጥ እንደሚፈረም ገልፀውም በመጪው ሳምንት ደግሞ በከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል የቴክኒክ ውይይቱ እንደሚጀመር አስረድተዋል፡፡ ጨምረውም ሁለቱም አገራት በቀጠናውና በአለም ሰላም እንዲመጣ በድርድሩ ወቅት ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው ደግሞ አሜሪካና ኢራን በነገው እለት በከፍተኛ ባለስልጣናት መካከል በስምምነት ሰነዱ ላይ ይፈራረማሉ፡፡
በዚህ የፊርማ ስነስርአት ከአሜሪካ ምክትል ፕሬዝደንቱ ጄዲ ቫንስ እንደሚገኙና ከኢራን በኩል ደግሞ የፓርላማ አፈጉባኤው መሀመድ ባክር ጋሊባፍ እንደሚወከሉ የጠቀሰው ዘገባው የፊርማው ቦታ ምናልባትም ጄኔቭ እንደሚሆን አስረድቷል፡፡ የስምምነት ሰነዱ ምን እንዳካተተ የተባለ ነገር የለም፡፡ ይሁን እንጂ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አግካራቺ በአገራቸው ቴሌቪዥን ባሰሙት ንግግር ‹‹በስምምነቱ ስትራቴጂያዊ ስኬት አግኝተናል፡፡ በጦርነቱ ኢራን አሸንፋለች›› በማለት አስታውቀዋል፡፡
1 day ago
ዓለም በዝምታ ቢያዘግምም ኢትዮጵያ ምድርን እያከመች ነው!
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በአዲሱ በጀት ዓመት የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግ እንደሆነ በግልጽ እንዲታወቅ ተጠየቀ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
አቤል እስጢፋኖስ ethio fm 107.8
Seledadotio
Seledadotio
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የፌደራል መንግስትን የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት በተመለከተ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጥያቄያቸውን ለምክር ቤቱ ካቀረቡት አባላት መካከል የአብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) ፓርቲን ወክለው የምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ይገኙበታል።
ዶክተር ደሳለኝ በጥያቄያቸው፤ መንግስት ለ2019 በጀት ዓመት ለመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ያደርጋል ወይ? የሚለው ጉዳይ በግልጽ እንዲታወቅ ጠይቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ ጥያቄውን ባቀረቡበት ወቅት ባለፈው ዓመት የታዘቡትን አጋጣሚ በማስታወስ፤ "ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጥያቄ ለምክር ቤቱ አቅርቤ 'የደመወዝ ጭማሪ የለም' የሚል ምላሽ ከተሰጠኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ተደርጓል" ብለዋል። በመቀጠልም "ዘንድሮስ ጭማሪ የለም ካሉኝ ከአንድ ወር በኋላ ጭማሪ ይኖራል ወይ?" ሲሉ በሚኒስትሩ አገላለጽ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬ በፈገግታ የታጀበ ጥያቄ በማስከተል ሰንዝረዋል።
ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፤ መንግስት ቀደም ሲል በሁለት ዙር የደመወዝ ጭማሪ ማድረጉን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት በክልሎች በኩል በፐርሰንት ተሰርቶ የቀረበው የደመወዝ ጭማሪ ተመን እና ለጉዳዩ ከተመደበው በጀት ጋር ባለመመጣጠኑ ምክንያት፣ አሁንም ድረስ ተጨማሪ የማጥራትና የማስተካከል ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ለአባላቱ አስገንዝበዋል።
አቤል እስጢፋኖስ ethio fm 107.8
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
አዲስ አበባ - የዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የስፖርት ውድድሮች ተመራጭ ከተማ
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
2 days ago
ቤጂንግ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ እንዲወድሙ ጥሪ አቀረበች
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 days ago
ወደ ዋናው ምክክር - የሀገርን ምሶሶ በጋራ የመጠገን ታሪካዊ ጥሪ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ሂደት በታሪካችን፣ በማንነታችን እና በፖለቲካ አመለካከታችን ዙሪያ ለዘመናት የቆዩትን ስር የሰደዱ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የሚደረግ ከፍተኛ እና ታሪካዊ ጥረት ነው።
ይህ ሂደት በተለይ በኢትዮጵያ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ለዓመታት ሀገርን እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ሲያስከፍል የቆየውን እና ሀገራዊ አንድነታችንን ሲፈታተን የኖረውን "የእኔን ሃሳብ ካልተቀበላችሁ" የሚለውን የጥፋት የዜሮ ድምር አስተሳሰብ እና የጥርጣሬ ድባብ በመስበር፣ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ የበላይነት፣ በጠላትነት ሳይሆን በውይይት፣ እንዲሁም በሴራ ሳይሆን በግልጽነት ላይ የተመሰረተ የሰለጠነ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት የተከፈተ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የፈረሰውን ለመጠገን፣ የላላውን ለማጥበቅ፣ የቆዩ የፖለቲካ ቁስሎችን ለመፈወስና አዲስ የጋራ መጻኢ ዕድልን በጥንካሬ ለመንደፍ የቀረበ ወርቃማ እና ወደር የሌለው ሀገራዊ ዕድል ነው።
የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ እንዲሁም ልዩ ትኩረት በመስጠት የሴቶችና የወጣቶችን ድምፅ በማካተት ከመላው ሀገራችን በተሰበሰቡት አጀንዳዎች ላይ ከመጪዉ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዋናዉ ምክክር ለመጀመር ተዘጋጅቷል።
ይህ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአግባቡ ያሳተፈ ብሄራዊ መድረክ የምክክሩ እውነተኛ ባለቤትና መሪ ራሱ ህዝቡ እንዲሆን የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኙና ዉይይት እንዲደረገባቸዉ ያስችላል።
በጥንቃቄ የተለዩት አጀንዳዎች የምክክሩን ዕድሜ፣ አቅጣጫ እና የመጨረሻ ውጤት የሚወስኑ ስለሆነ ዋነኛ ትኩረታቸዉ መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦች ላይ ብቻ ማድረግ ምክክሩን ውጤታማ ያደርገዋል።
የምክክሩ መሳካት በዋና ዋና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ህዝቡ በተለያዩ መንግስታዊ እና ህዝባዊ ተቋማት ላይ ያለው እምነት እንዲጠነክር፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እንዲጠቆሙ እና ከዚህ ቀደም የነበሩ ቁስላችንን በራሳችን ውስጣዊ አቅምና መድኃኒት በመፈወስ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጽናት ለመግታት ያስችላል።
በጠረጴዛ ዙሪያ መቀራረብ እና መወያየት የሀገርን ሉዓላዊነት የማጽናት እና መረጋጋትን የማጠናከር የህልውና ጉዳይ ነው።
በዚህ ታላቅ የሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የህብረተሰቡ አይንና ጆሮ የሆኑት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሃይማኖት እና የጦር ልሂቃን ያላቸውን ከፍተኛ ተሰሚነት፣ ተፅዕኖና እውቀት ተጠቅመው ህዝቡን በማንቃት ሂደቱን በቅንነት እና በዕውቀት የመምራትና የማገዝ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው።
በአሁኑ ወቅት ኮሚሽኑ በሩን ክፍት አድርጎ ሐሳብን ሲቀበል ቆይቶ ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ የደረሰ በመሆኑ፣ ብሔራዊ ምክክሩ የፖለቲካ ምርጫ ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን ሁላችንም ልንገነዘብ ይገባል።
የተበታተነ ሀሳብና ልዩነት ሀገርን ስለማያቆም እና ለጋራ መረጋጋት ስለማይበጅ፣ ሁላችንም እንደየድርሻችን ለብሔራዊ ጥቅማችን በጋራ ልንቆም እና ታሪክ ልንሰራ ይገባል።
በአንድነት መምከር፣ በልዩነት መከባበር፣ ለጋራ ውጤት በቅንነት መስራት እና ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም የዘመኑ ታሪካዊ ጥሪ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ እውነተኛ ምክክር፣ ይቅርታ እና መግባባት ትጸና ዘንድ ሁላችንም ለስኬታማነቱ በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሐምሌ8 #ኢትዮጵያ #nationaldialogueethiopia
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ሂደት በታሪካችን፣ በማንነታችን እና በፖለቲካ አመለካከታችን ዙሪያ ለዘመናት የቆዩትን ስር የሰደዱ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የሚደረግ ከፍተኛ እና ታሪካዊ ጥረት ነው።
ይህ ሂደት በተለይ በኢትዮጵያ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ለዓመታት ሀገርን እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ሲያስከፍል የቆየውን እና ሀገራዊ አንድነታችንን ሲፈታተን የኖረውን "የእኔን ሃሳብ ካልተቀበላችሁ" የሚለውን የጥፋት የዜሮ ድምር አስተሳሰብ እና የጥርጣሬ ድባብ በመስበር፣ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ የበላይነት፣ በጠላትነት ሳይሆን በውይይት፣ እንዲሁም በሴራ ሳይሆን በግልጽነት ላይ የተመሰረተ የሰለጠነ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት የተከፈተ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የፈረሰውን ለመጠገን፣ የላላውን ለማጥበቅ፣ የቆዩ የፖለቲካ ቁስሎችን ለመፈወስና አዲስ የጋራ መጻኢ ዕድልን በጥንካሬ ለመንደፍ የቀረበ ወርቃማ እና ወደር የሌለው ሀገራዊ ዕድል ነው።
የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ እንዲሁም ልዩ ትኩረት በመስጠት የሴቶችና የወጣቶችን ድምፅ በማካተት ከመላው ሀገራችን በተሰበሰቡት አጀንዳዎች ላይ ከመጪዉ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዋናዉ ምክክር ለመጀመር ተዘጋጅቷል።
ይህ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአግባቡ ያሳተፈ ብሄራዊ መድረክ የምክክሩ እውነተኛ ባለቤትና መሪ ራሱ ህዝቡ እንዲሆን የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኙና ዉይይት እንዲደረገባቸዉ ያስችላል።
በጥንቃቄ የተለዩት አጀንዳዎች የምክክሩን ዕድሜ፣ አቅጣጫ እና የመጨረሻ ውጤት የሚወስኑ ስለሆነ ዋነኛ ትኩረታቸዉ መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦች ላይ ብቻ ማድረግ ምክክሩን ውጤታማ ያደርገዋል።
የምክክሩ መሳካት በዋና ዋና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ህዝቡ በተለያዩ መንግስታዊ እና ህዝባዊ ተቋማት ላይ ያለው እምነት እንዲጠነክር፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እንዲጠቆሙ እና ከዚህ ቀደም የነበሩ ቁስላችንን በራሳችን ውስጣዊ አቅምና መድኃኒት በመፈወስ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጽናት ለመግታት ያስችላል።
በጠረጴዛ ዙሪያ መቀራረብ እና መወያየት የሀገርን ሉዓላዊነት የማጽናት እና መረጋጋትን የማጠናከር የህልውና ጉዳይ ነው።
በዚህ ታላቅ የሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የህብረተሰቡ አይንና ጆሮ የሆኑት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሃይማኖት እና የጦር ልሂቃን ያላቸውን ከፍተኛ ተሰሚነት፣ ተፅዕኖና እውቀት ተጠቅመው ህዝቡን በማንቃት ሂደቱን በቅንነት እና በዕውቀት የመምራትና የማገዝ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው።
በአሁኑ ወቅት ኮሚሽኑ በሩን ክፍት አድርጎ ሐሳብን ሲቀበል ቆይቶ ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ የደረሰ በመሆኑ፣ ብሔራዊ ምክክሩ የፖለቲካ ምርጫ ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን ሁላችንም ልንገነዘብ ይገባል።
የተበታተነ ሀሳብና ልዩነት ሀገርን ስለማያቆም እና ለጋራ መረጋጋት ስለማይበጅ፣ ሁላችንም እንደየድርሻችን ለብሔራዊ ጥቅማችን በጋራ ልንቆም እና ታሪክ ልንሰራ ይገባል።
በአንድነት መምከር፣ በልዩነት መከባበር፣ ለጋራ ውጤት በቅንነት መስራት እና ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም የዘመኑ ታሪካዊ ጥሪ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ እውነተኛ ምክክር፣ ይቅርታ እና መግባባት ትጸና ዘንድ ሁላችንም ለስኬታማነቱ በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሐምሌ8 #ኢትዮጵያ #nationaldialogueethiopia
Sponsored by
Surafel
2 days ago
አሁን - የአሜሪካዊው ራፐር ፊውቸር እና የደቡብ አፍሪካዊቷ ዘፋኝ እና የዘፈን ደራሲ ታይላ ትዕይንት - በ2026 የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ በኢንግልዉድ በሚገኘው ሎስ አንጀለስ ስታዲየም ያቀረቡት የሙዚቃ ዝግጅት።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን የሚደገፈው የየመን ሁቲ ታጣቂ ቡድን በቀይ ባህር በሚተላለፉ የእስራኤል መርከቦች ላይ ያወጀውን "ሙሉ እገዳ" ተከትሎ አካባቢው ወደ አጠቃላይ የጦርነት ቀጣና ሊለወጥ እንደሚችል ዓለም አቀፍ የደህንነት ባለሙያዎች አሳሰቡ። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሁቲዎችን ማስፈራሪያ "ተቀባይነት የሌለው እና አደገኛ" ሲል አውግዞታል፤ እንዲሁም አሜሪካ ከቀጠናው አጋሮቿ ጋር በመሆን የባህር ላይ ጉዞ ደህንነትን ለማረጋገጥ እንደምትሰራ አስታውቋል።
በየመን የቀድሞው የእንግሊዝ አምባሳደር እና የመከላከያ ዴሞክራሲ ፋውንዴሽን ከፍተኛ ተመራማሪ ኤድመንድ ፊቶን-ብራውን፣ ሁቲዎች ይህንን ማስፈራሪያ ወደ ተግባር ከለወጡና የባህር ላይ ጥቃታቸውን አጠናክረው ከቀጠሉ "የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ቁጣ ከመቀስቀሱም በላይ፣ እስራኤል እና አሜሪካ በሰነዓ እና ሆዴዳ ላይ ከባድ የአየር ጥቃት እንዲፈጽሙ ይገፋፋቸዋል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በዚሁ ቀጠናዊ ውጥረት ውስጥ ወደብ አልባዋ እና 130 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ቁልፍ የጸጥታ አጋር በመሆን እያገለገለች መሆኑ ተጠቁሟል። በአዲስ አበባ የሚገኘው "ሆርን ሪቪው" የምርምር ተቋም ስራ አስፈጻሚ ብሌን ምህረት ዲሪባ ለፎክስ ኒውስ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ከኢራን አንስቶ እስከ ሱዳን ለተዘረጋው "የእስላማዊ ጽንፈኝነት መስፋፋት አውራ ጎዳና" ላይ እንደ ትልቅ እንቅፋት ሆና ቆማለች።
ሆኖም ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት ጠብቃ እያለ፣ ከኢራንም ጋር ያላት ግንኙነት በባለሙያዎች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል። አምባሳደር ፊቶን-ብራውን እንዳሉት "ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ጨዋታ ውስጥ ናት፤ ኢራን በትግራይ ጦርነት ወቅት ለኢትዮጵያ መንግስት የድሮን እና ወታደራዊ ድጋፍ አድርጋለች፤ አሁንም የውስጥ አማጺያንን ለመዋጋት ኢትዮጵያ ከኢራን የፖሊስ፣ የደህንነት እና የወታደራዊ ድጋፍ ለማግኘት ስምምነት አላት" ሲሉ ተችተዋል።
በአንጻሩ ተመራማሪዋ ብሌን ምህረት፣ኢትዮጵያ እና ኢራን ግንኙነት "ፍቅር ሳይሆን ስትራቴጂካዊ ጥንቃቄ" መሆኑን ገልጸው፣ ኢትዮጵያ በአስቸጋሪው የቀጠናው ፖለቲካ ውስጥ እራሷን ለማዳን ስትል "ተለዋዋጭ የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ" እየተከተለች መሆኑን አስረድተዋል። ተመራማሪዋ አክለውም፣ ኢትዮጵያ አሁንም ዋነኛ እና ቀዳሚ አጋሯ አሜሪካ መሆኗን አስምረውበታል።
በየመን የቀድሞው የእንግሊዝ አምባሳደር እና የመከላከያ ዴሞክራሲ ፋውንዴሽን ከፍተኛ ተመራማሪ ኤድመንድ ፊቶን-ብራውን፣ ሁቲዎች ይህንን ማስፈራሪያ ወደ ተግባር ከለወጡና የባህር ላይ ጥቃታቸውን አጠናክረው ከቀጠሉ "የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ቁጣ ከመቀስቀሱም በላይ፣ እስራኤል እና አሜሪካ በሰነዓ እና ሆዴዳ ላይ ከባድ የአየር ጥቃት እንዲፈጽሙ ይገፋፋቸዋል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በዚሁ ቀጠናዊ ውጥረት ውስጥ ወደብ አልባዋ እና 130 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ቁልፍ የጸጥታ አጋር በመሆን እያገለገለች መሆኑ ተጠቁሟል። በአዲስ አበባ የሚገኘው "ሆርን ሪቪው" የምርምር ተቋም ስራ አስፈጻሚ ብሌን ምህረት ዲሪባ ለፎክስ ኒውስ እንደገለጹት ኢትዮጵያ ከኢራን አንስቶ እስከ ሱዳን ለተዘረጋው "የእስላማዊ ጽንፈኝነት መስፋፋት አውራ ጎዳና" ላይ እንደ ትልቅ እንቅፋት ሆና ቆማለች።
ሆኖም ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ጠንካራ አጋርነት ጠብቃ እያለ፣ ከኢራንም ጋር ያላት ግንኙነት በባለሙያዎች ዘንድ አነጋጋሪ ሆኗል። አምባሳደር ፊቶን-ብራውን እንዳሉት "ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ጨዋታ ውስጥ ናት፤ ኢራን በትግራይ ጦርነት ወቅት ለኢትዮጵያ መንግስት የድሮን እና ወታደራዊ ድጋፍ አድርጋለች፤ አሁንም የውስጥ አማጺያንን ለመዋጋት ኢትዮጵያ ከኢራን የፖሊስ፣ የደህንነት እና የወታደራዊ ድጋፍ ለማግኘት ስምምነት አላት" ሲሉ ተችተዋል።
በአንጻሩ ተመራማሪዋ ብሌን ምህረት፣ኢትዮጵያ እና ኢራን ግንኙነት "ፍቅር ሳይሆን ስትራቴጂካዊ ጥንቃቄ" መሆኑን ገልጸው፣ ኢትዮጵያ በአስቸጋሪው የቀጠናው ፖለቲካ ውስጥ እራሷን ለማዳን ስትል "ተለዋዋጭ የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ" እየተከተለች መሆኑን አስረድተዋል። ተመራማሪዋ አክለውም፣ ኢትዮጵያ አሁንም ዋነኛ እና ቀዳሚ አጋሯ አሜሪካ መሆኗን አስምረውበታል።
2 days ago
የፋይዳ ተጨባጭ ስኬት የዲጂታል ኢትዮጵያ ውጤት ማሳያ ነው
********************
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያን የዲጂታል ምህዳር ቀይሯል። በፕሮግራሙ እስከአሁን ከ45.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የባዮሜትሪክስ መረጃቸው ተመዝግቦ የፋይዳ ቁጥር አግኝተዋል። አገልግሎቱ በከተሞች ሳይወሰን እስከ ቀበሌ መዋቅር በመውረድ ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ ተደራሽ ሆኗል።
ፋይዳ ከብሔራዊና ከግል ባንኮች ጋር በአደረገው ትስስር አዲስ አካውንት ለመክፈትና ማንነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ማረጋገጫ መንገድ ሆኖ እያገለገለም ነው። ይህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ፋይናንስ ሥርዓቱ እንዲገቡና የብድር ዕድል እንዲያገኙ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
ከገቢዎች፣ ከትራንስፖርት፣ ከጤና ፣ ከውልና ማስረጃ እና ከተለያዩ ዘርፎች ጋር እንዲተሳሰር በመደረጉ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ እያሳለጠ ይገኛል። ቴክኖሎጂው የሐሰተኛ ሰነድ ዝግጅትንና ማጭበርበርን በመከላከል ረገድ ጉልህ ድርሻ አለው።
አዲሱ የዲጂታል 2030 ዕቅድም 100 በመቶ የጂዲታል ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማለም የስኬት ፍሬዎችን ለሁሉም ዜጋ ለማድረስ በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል።
ፋይዳ ባለፉት ዓመታት ከመታወቂያነት ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ እንደ ዋነኛ መሠረት ተደርጎ እየተሰራበት ይገኛል። ይህ የዲጂታል ለውጥ ጉዞም ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ሕይወት በእጅጉ እያሻሻለ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
{#id:2647#} {#id:5682#} {#id:6339#} #id
********************
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያን የዲጂታል ምህዳር ቀይሯል። በፕሮግራሙ እስከአሁን ከ45.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የባዮሜትሪክስ መረጃቸው ተመዝግቦ የፋይዳ ቁጥር አግኝተዋል። አገልግሎቱ በከተሞች ሳይወሰን እስከ ቀበሌ መዋቅር በመውረድ ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ ተደራሽ ሆኗል።
ፋይዳ ከብሔራዊና ከግል ባንኮች ጋር በአደረገው ትስስር አዲስ አካውንት ለመክፈትና ማንነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ማረጋገጫ መንገድ ሆኖ እያገለገለም ነው። ይህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ፋይናንስ ሥርዓቱ እንዲገቡና የብድር ዕድል እንዲያገኙ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
ከገቢዎች፣ ከትራንስፖርት፣ ከጤና ፣ ከውልና ማስረጃ እና ከተለያዩ ዘርፎች ጋር እንዲተሳሰር በመደረጉ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ እያሳለጠ ይገኛል። ቴክኖሎጂው የሐሰተኛ ሰነድ ዝግጅትንና ማጭበርበርን በመከላከል ረገድ ጉልህ ድርሻ አለው።
አዲሱ የዲጂታል 2030 ዕቅድም 100 በመቶ የጂዲታል ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማለም የስኬት ፍሬዎችን ለሁሉም ዜጋ ለማድረስ በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል።
ፋይዳ ባለፉት ዓመታት ከመታወቂያነት ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ እንደ ዋነኛ መሠረት ተደርጎ እየተሰራበት ይገኛል። ይህ የዲጂታል ለውጥ ጉዞም ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ሕይወት በእጅጉ እያሻሻለ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
{#id:2647#} {#id:5682#} {#id:6339#} #id
2 days ago
ኢሎን ማስክ የስፔስ ኤክስ አክሲዮን ማደጉን ተከትሎ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ሆነ
አርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስፔስ ኤክስ (SpaceX) አክሲዮኖች በናስዳቅ የገበያ ማዕከል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ክፍት በሆኑበት ዕለት የ11 በመቶ ዕድገት በማሳየት 150 ዶላር ደርሰዋል።
ይህ በታሪክ ትልቁ የሆነው የአክሲዮን ሽያጭ (IPO) የኩባንያውን አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 2 ትሪሊዮን ዶላር ያደረሰው ሲሆን፣ ባለቤቱን ኢሎን ማስክን የዓለማችን የመጀመሪያው ባለ ትሪሊዮን ዶላር (Trillionaire) ሀብታም አድርጎታል።
ከ75 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ይህ ሽያጭ፣ ኩባንያውን ከቴስላ እና ሜታ በላይ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ2002 የተመሠረተው ስፔስ ኤክስ፣ አሁን ላይ የሳተላይት አገልግሎትን፣ የኤአይ (xAI) ኩባንያን እና የኤክስ (X) ማህበራዊ ሚዲያን ያካተተ ግዙፍ ጥምረት ሆኗል።
ማስክ በሰጠው መግለጫ የኩባንያው ቀጣይ ግብ የሰውን ልጅ ወደ ጨረቃና ማርስ ማድረስ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
አርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስፔስ ኤክስ (SpaceX) አክሲዮኖች በናስዳቅ የገበያ ማዕከል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ክፍት በሆኑበት ዕለት የ11 በመቶ ዕድገት በማሳየት 150 ዶላር ደርሰዋል።
ይህ በታሪክ ትልቁ የሆነው የአክሲዮን ሽያጭ (IPO) የኩባንያውን አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 2 ትሪሊዮን ዶላር ያደረሰው ሲሆን፣ ባለቤቱን ኢሎን ማስክን የዓለማችን የመጀመሪያው ባለ ትሪሊዮን ዶላር (Trillionaire) ሀብታም አድርጎታል።
ከ75 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ይህ ሽያጭ፣ ኩባንያውን ከቴስላ እና ሜታ በላይ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ2002 የተመሠረተው ስፔስ ኤክስ፣ አሁን ላይ የሳተላይት አገልግሎትን፣ የኤአይ (xAI) ኩባንያን እና የኤክስ (X) ማህበራዊ ሚዲያን ያካተተ ግዙፍ ጥምረት ሆኗል።
ማስክ በሰጠው መግለጫ የኩባንያው ቀጣይ ግብ የሰውን ልጅ ወደ ጨረቃና ማርስ ማድረስ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments