5 hours ago
ሞሃመድን ከእንግሊዝ ይልቅ ቱርክ ተቀብላዋለች
#ethiopia | የግብጹ ኮከብ ሞሃመድ ሳላህ በሊቨርፑል የነበረውን ዘጠኝ ዓመታት የቆየ የጨዋታ ጊዜ በማጠናቀቅ የቱርኩን ክለብ ትራብዞንስፖር በይፋ ተቀላቅሏል።
የ34 ዓመቱ አጥቂ ከቱርኩ ክለብ ጋር ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ውል የተፈራረመ ሲሆን በዓመት 17 ሚሊዮን ዩሮ ደመወዝ የሚያገኝ ይሆናል።
በተጨማሪም በስሙ ከሚሸጡ ልዩ ልዩ ምርቶች የ20 በመቶ የገቢ ድርሻ የሚያገኝበት አሰራር የተመቻቸለት ሲሆን ይህም ሳላህን የክለቡና የቱርክ ሱፐር ሊግ ዋና ገጽታ ለማድረግ የተወጠነ የንግድ ስምምነት ነው።
በስታዲየም ተገኝተው ደመቅ ያለ አቀባበል ላደረጉለት በሺዎች ለሚቆጠሩ የትራብዞንስፖር ደጋፊዎች ንግግር ያደረገው ሳላህ በህይወቱ ገጥሞት የማያውቅ ድንቅ ፍቅርና አቀባበል እንደተደረገለት በመግለጽ ደጋፊዎቹን አመስግኗል።
በሊቨርፑል በነበረው ቆይታ በ442 ጨዋታዎች 257 ግቦችን በማስቆጠር ሁለት የፕሪሚየር ሊግ እና አንድ የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ያሸነፈው ሞ፣ አሁንም ከአዲሱ ክለቡ ጋር ዋንጫዎችን በማንሳት አዲስ የስኬት ምዕራፍ ለመጻፍ እንደሚጫወት ገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የግብጹ ኮከብ ሞሃመድ ሳላህ በሊቨርፑል የነበረውን ዘጠኝ ዓመታት የቆየ የጨዋታ ጊዜ በማጠናቀቅ የቱርኩን ክለብ ትራብዞንስፖር በይፋ ተቀላቅሏል።
የ34 ዓመቱ አጥቂ ከቱርኩ ክለብ ጋር ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ውል የተፈራረመ ሲሆን በዓመት 17 ሚሊዮን ዩሮ ደመወዝ የሚያገኝ ይሆናል።
በተጨማሪም በስሙ ከሚሸጡ ልዩ ልዩ ምርቶች የ20 በመቶ የገቢ ድርሻ የሚያገኝበት አሰራር የተመቻቸለት ሲሆን ይህም ሳላህን የክለቡና የቱርክ ሱፐር ሊግ ዋና ገጽታ ለማድረግ የተወጠነ የንግድ ስምምነት ነው።
በስታዲየም ተገኝተው ደመቅ ያለ አቀባበል ላደረጉለት በሺዎች ለሚቆጠሩ የትራብዞንስፖር ደጋፊዎች ንግግር ያደረገው ሳላህ በህይወቱ ገጥሞት የማያውቅ ድንቅ ፍቅርና አቀባበል እንደተደረገለት በመግለጽ ደጋፊዎቹን አመስግኗል።
በሊቨርፑል በነበረው ቆይታ በ442 ጨዋታዎች 257 ግቦችን በማስቆጠር ሁለት የፕሪሚየር ሊግ እና አንድ የቻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ያሸነፈው ሞ፣ አሁንም ከአዲሱ ክለቡ ጋር ዋንጫዎችን በማንሳት አዲስ የስኬት ምዕራፍ ለመጻፍ እንደሚጫወት ገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
7 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኦሮሚያ ክልል ጅማ ከተማ በመገንባት ላይ ባለው "በዳ ቡና" (የቡና ከፍታ) የተሰኘ የፓርክ ፕሮጀክት ምክንያት፣ አስተዳደሩ ህያዋንን ከመኖሪያቸው ከማፈናቀል አልፎ ታሪካዊ እና ሀይማኖታዊ ክብር ያላቸውን የመቃብር ስፍራዎች ለማፍረስ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተከትሎ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ እና ውጥረት መንገሱ ተጋለጠ።
የአካባቢው ምንጮች ባወጡት መረጃ መሰረት፣ የጅማ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊውን የአባ ጅፋር ቤተ-መንግስት የሚያጠቃልል ሰፊ የፓርክ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል። ይህንን የፓርክ ግንባታ ተከትሎ በቤተ-መንግስቱ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀድመው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ፕሮጀክቱ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና ራሳቸው አባ ጅፋር ያረፉበትን ታላቁን የመቃብር ስፍራ (ቀብሪ ጀመዓ) እንዲሁም ታሪካዊውን "የ40ዎቹ መስጊድ" አጠቃልሏል በሚል ስፍራውን በማፍረስ አስከሬን ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከቀናት በፊት የከተማው አስተዳደር መቃብሮቹን ለማፍረስ ከባድ ማሽኖችን ይዞ ወደ ስፍራው ያመራ ቢሆንም፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በከፍተኛ ተቃውሞ ወጥቶ ከማሽኖቹ ፊት በመቆም ድርጊቱን ለጊዜው ሊያስቆመው መቻሉ ታውቋል።
ሆኖም የጅማ ከተማ ካቢኔ አመራሮች፣ ይህ ታሪካዊ የመቃብር ስፍራ እንዲፈርስ እና አስከሬን እንዲወጣ የተሰጠው ትዕዛዝ በቀጥታ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመጣ በመሆኑ፣ ትዕዛዙን ወደ ኋላ መመለስም ሆነ ማፍረሱን ማቆም እንደማይችሉ መናገራቸውን ነዋሪዎች አጋልጠዋል። የአስተዳደሩ ዕቅድ የመቃብር ስፍራውን በማፍረስ የሟቾችን አጥንት ሰብስቦ፣ እስላማዊ ህግጋትን በሚጻረር መልኩ በአንድ የጋራ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ለመቅበር መሆኑ ማህበረሰቡን ክፉኛ አስቆጥቷል።
ይህ የመንግስት እርምጃ የእስልምና ሀይማኖት ህግን፣ የአካባቢውን ታላቅ ባህል፣ ሞራላዊ እሴት (ሰፉ) እና የጅማን ህዝብ ክብር በእጅጉ የሚነካ እና የሚያዋርድ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን የሚገልጹት ነዋሪዎቹ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ)፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች (ኡለማዎች) አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡበት፣ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ለህዝቡ ድምጽ በመሆን ይህን ህገ-ወጥ እና አሳዛኝ ድርጊት እንዲያስቆሙላቸው አጥብቀው ተማጽነዋል።
የአካባቢው ምንጮች ባወጡት መረጃ መሰረት፣ የጅማ ከተማ አስተዳደር ታሪካዊውን የአባ ጅፋር ቤተ-መንግስት የሚያጠቃልል ሰፊ የፓርክ ግንባታ እያከናወነ ይገኛል። ይህንን የፓርክ ግንባታ ተከትሎ በቤተ-መንግስቱ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀድመው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ ፕሮጀክቱ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና ራሳቸው አባ ጅፋር ያረፉበትን ታላቁን የመቃብር ስፍራ (ቀብሪ ጀመዓ) እንዲሁም ታሪካዊውን "የ40ዎቹ መስጊድ" አጠቃልሏል በሚል ስፍራውን በማፍረስ አስከሬን ለማውጣት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገልጿል።
ከቀናት በፊት የከተማው አስተዳደር መቃብሮቹን ለማፍረስ ከባድ ማሽኖችን ይዞ ወደ ስፍራው ያመራ ቢሆንም፣ የአካባቢው ማህበረሰብ በከፍተኛ ተቃውሞ ወጥቶ ከማሽኖቹ ፊት በመቆም ድርጊቱን ለጊዜው ሊያስቆመው መቻሉ ታውቋል።
ሆኖም የጅማ ከተማ ካቢኔ አመራሮች፣ ይህ ታሪካዊ የመቃብር ስፍራ እንዲፈርስ እና አስከሬን እንዲወጣ የተሰጠው ትዕዛዝ በቀጥታ ከኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የመጣ በመሆኑ፣ ትዕዛዙን ወደ ኋላ መመለስም ሆነ ማፍረሱን ማቆም እንደማይችሉ መናገራቸውን ነዋሪዎች አጋልጠዋል። የአስተዳደሩ ዕቅድ የመቃብር ስፍራውን በማፍረስ የሟቾችን አጥንት ሰብስቦ፣ እስላማዊ ህግጋትን በሚጻረር መልኩ በአንድ የጋራ ጉድጓድ ውስጥ በጅምላ ለመቅበር መሆኑ ማህበረሰቡን ክፉኛ አስቆጥቷል።
ይህ የመንግስት እርምጃ የእስልምና ሀይማኖት ህግን፣ የአካባቢውን ታላቅ ባህል፣ ሞራላዊ እሴት (ሰፉ) እና የጅማን ህዝብ ክብር በእጅጉ የሚነካ እና የሚያዋርድ ታሪካዊ ስህተት መሆኑን የሚገልጹት ነዋሪዎቹ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ)፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች (ኡለማዎች) አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡበት፣ እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ለህዝቡ ድምጽ በመሆን ይህን ህገ-ወጥ እና አሳዛኝ ድርጊት እንዲያስቆሙላቸው አጥብቀው ተማጽነዋል።
7 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ውጥረት በነገሰበት በአሁኑ ወቅት፣ የቀይ ባህር ቀጠና ሀገራት የራሳቸውን የጋራ ደህንነት እና ሰፋ ያለ የትብብር ማዕቀፍ መዘርጋት ከምንጊዜውም በላይ አጣዳፊ መሆኑን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ ይህንን ያስታወቁት ኤርትራ ከጥቂት ዓመታት በፊት በቀይ ባህር እና አደን ባህረ ሰላጤ ዳርቻ ሀገራት ምክር ቤት አቅርባው የነበረውን ባለ 12 ነጥብ የደህንነት እና የትብብር ሰነድ ዳግም በትዊተር (ኤክስ) ገጻቸው ይፋ ባደረጉበት ወቅት ነው።
ከዚህ የጸጥታ ማዕቀፍ ጀርባ ያለው ዋነኛ የፖለቲካ እና የኦፕሬሽን ስሌት፣ የቀጠናው ሀገራት በጉዳያቸው ላይ ሙሉ ባለቤትነት እና ወሳኝነት እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ሰነዱ ያብራራል። በተለይም ቀጠናውን ከዓለም አቀፍ ኃያላን ሀገራት የፉክክር እና የፖላራይዜሽን አውድማነት ማዳን፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አቅምን በመገንባት በዋና ባለድርሻ አካላት መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ የኤርትራ ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት መሆኑ ተጠቁሟል። ይህ ማዕቀፍ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቀጠናው የጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታ አንጻር፣ በየጊዜው በሚደረጉ ጥልቅ ውይይቶች ሊዳብር የሚችል መሰረታዊ ግብዓት መሆኑንም ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት ሰነድ በዋናነት በቀይ ባህር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉትን እውነታዎች ከሁሉም አቅጣጫዎች አድልዎ በሌለው መንገድ መገምገም እና ግቦችን በግልጽ ማስቀመጥ ላይ ያተኩራል። ከዚህም ባሻገር በቀይ ባህር ሰላም እና ደህንነት ላይ የተጋረጡ ስጋቶችን በዝርዝር በመለየት እና በመፈረጅ፣ እነዚህን ስጋቶች ለመቆጣጠር እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ተግባራዊ ስትራቴጂዎችን ከገንቢ የትብብር ፖሊሲዎች ጋር በማስተሳሰር መንደፍ እንደሚያስፈልግ ሰነዱ ያብራራል። እነዚህን ስትራቴጂዎች ወደ መሬት ለማውረድም ዝርዝር እቅዶችን፣ የአፈጻጸም ዘዴዎችን፣ መዋቅሮችን እና አስፈላጊ ግብዓቶችን ማሰባሰብ ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
የዚህ ስትራቴጂካዊ ሰነድ እጅግ አሳሳቢ እና ትልቁን ፖለቲካዊ አንድምታ የያዘው ክፍል፣ የባህር ዳርቻ ሀገራት የሉዓላዊነት እና ራስን በራስ የመከላከል መብትን የሚመለከተው ነው። ማንኛውም የሚዋቀር የቀጠናው የደህንነት ማዕቀፍ በሉዓላዊነት መከበር እና በዓለም አቀፍ ህግ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ሰነዱ ያስገድዳል። በተለይም ሁሉም የባህር ዳርቻ ሀገራት የራሳቸውን የባህር ኃይል እና የመከላከያ አቅም በራሳቸው መገንባት እንዳለባቸው እና ይህንንም የጸጥታ ኃላፊነት ለሌሎች የውጭ ኃይሎች በውክልና መስጠት እንደሌለባቸው ኤርትራ በጥብቅ አሳስባለች።
በተናጠል አቅም ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ሀገራቱ በጋራ ጥረት እና ቅንጅት መፍታት እንደሚገባቸው ሰነዱ ያስቀምጣል። ሆኖም ከቀጠናው የጋራ አቅም በላይ ለሆኑ ልዩ ተልዕኮዎች የውጭ ኃይሎችን ማሳተፍ የሚቻለው፣ ሁሉም የሚመለከታቸው የቀጠናው ሀገራት በመግባባት ላይ በተመሰረተ ማዕቀፍ ሲስማሙ ብቻ መሆኑን ሰነዱ ይደነግጋል። በመጨረሻም እነዚህን ውስብስብ ጉዳዮች በሙያዊ መንገድ የሚከታተሉ እና የሚፈቱ ብቁ ኮሚቴዎች መቋቋም እንዳለባቸው በማስገንዘብ ሰነዱ ይቋጫል።
ከዚህ የጸጥታ ማዕቀፍ ጀርባ ያለው ዋነኛ የፖለቲካ እና የኦፕሬሽን ስሌት፣ የቀጠናው ሀገራት በጉዳያቸው ላይ ሙሉ ባለቤትነት እና ወሳኝነት እንዲኖራቸው ማድረግ መሆኑን ሰነዱ ያብራራል። በተለይም ቀጠናውን ከዓለም አቀፍ ኃያላን ሀገራት የፉክክር እና የፖላራይዜሽን አውድማነት ማዳን፣ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አቅምን በመገንባት በዋና ባለድርሻ አካላት መካከል ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ የኤርትራ ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት መሆኑ ተጠቁሟል። ይህ ማዕቀፍ አሁን ካለው ተለዋዋጭ የቀጠናው የጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታ አንጻር፣ በየጊዜው በሚደረጉ ጥልቅ ውይይቶች ሊዳብር የሚችል መሰረታዊ ግብዓት መሆኑንም ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ ይፋ ያደረጉት ሰነድ በዋናነት በቀይ ባህር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያሉትን እውነታዎች ከሁሉም አቅጣጫዎች አድልዎ በሌለው መንገድ መገምገም እና ግቦችን በግልጽ ማስቀመጥ ላይ ያተኩራል። ከዚህም ባሻገር በቀይ ባህር ሰላም እና ደህንነት ላይ የተጋረጡ ስጋቶችን በዝርዝር በመለየት እና በመፈረጅ፣ እነዚህን ስጋቶች ለመቆጣጠር እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ተግባራዊ ስትራቴጂዎችን ከገንቢ የትብብር ፖሊሲዎች ጋር በማስተሳሰር መንደፍ እንደሚያስፈልግ ሰነዱ ያብራራል። እነዚህን ስትራቴጂዎች ወደ መሬት ለማውረድም ዝርዝር እቅዶችን፣ የአፈጻጸም ዘዴዎችን፣ መዋቅሮችን እና አስፈላጊ ግብዓቶችን ማሰባሰብ ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
የዚህ ስትራቴጂካዊ ሰነድ እጅግ አሳሳቢ እና ትልቁን ፖለቲካዊ አንድምታ የያዘው ክፍል፣ የባህር ዳርቻ ሀገራት የሉዓላዊነት እና ራስን በራስ የመከላከል መብትን የሚመለከተው ነው። ማንኛውም የሚዋቀር የቀጠናው የደህንነት ማዕቀፍ በሉዓላዊነት መከበር እና በዓለም አቀፍ ህግ ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ሰነዱ ያስገድዳል። በተለይም ሁሉም የባህር ዳርቻ ሀገራት የራሳቸውን የባህር ኃይል እና የመከላከያ አቅም በራሳቸው መገንባት እንዳለባቸው እና ይህንንም የጸጥታ ኃላፊነት ለሌሎች የውጭ ኃይሎች በውክልና መስጠት እንደሌለባቸው ኤርትራ በጥብቅ አሳስባለች።
በተናጠል አቅም ሊፈቱ የማይችሉ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ሀገራቱ በጋራ ጥረት እና ቅንጅት መፍታት እንደሚገባቸው ሰነዱ ያስቀምጣል። ሆኖም ከቀጠናው የጋራ አቅም በላይ ለሆኑ ልዩ ተልዕኮዎች የውጭ ኃይሎችን ማሳተፍ የሚቻለው፣ ሁሉም የሚመለከታቸው የቀጠናው ሀገራት በመግባባት ላይ በተመሰረተ ማዕቀፍ ሲስማሙ ብቻ መሆኑን ሰነዱ ይደነግጋል። በመጨረሻም እነዚህን ውስብስብ ጉዳዮች በሙያዊ መንገድ የሚከታተሉ እና የሚፈቱ ብቁ ኮሚቴዎች መቋቋም እንዳለባቸው በማስገንዘብ ሰነዱ ይቋጫል።
7 hours ago
የከባድ መሳሪያ ተኩስ‼️
በራያ ግንባር የሚንቀሳቀሰውና ከሰሞኑ ከባድ መሳሪያዎችን እና ተጨማሪ ታጣቂዎችን ሲያጠጋ የነበረው የህወሃት አርሚ 33 እና 44 ዓዲጉደም ➡️ ደቡብ ወጀራት ➡️ኮንካ ➡️ጎነቕ ➡️ቶንሳ ➡️ንፋሮ መጋለ መስመር በዓዲቀይሕ ወደ ገራርሳ እና ቶንሳ አሁን ዛሬ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ላይ በትግራይ ሰላም ሰራዊት ላይ የከባድ መሳሪያ ተኩስ መጀመሩን ምንጮቻችን ገልፀዋል።
እራሱን 'የትግራይ ሰላም ሰራዊት' በሚል የተደራጀው ታጣቂ ሀይል ወደ መቀሌ ለመግባት ዝግጁ መሆኑን ከሳምንት በፊት አሳውቆ ነበር።
Seledadotio
Seledadotio
በራያ ግንባር የሚንቀሳቀሰውና ከሰሞኑ ከባድ መሳሪያዎችን እና ተጨማሪ ታጣቂዎችን ሲያጠጋ የነበረው የህወሃት አርሚ 33 እና 44 ዓዲጉደም ➡️ ደቡብ ወጀራት ➡️ኮንካ ➡️ጎነቕ ➡️ቶንሳ ➡️ንፋሮ መጋለ መስመር በዓዲቀይሕ ወደ ገራርሳ እና ቶንሳ አሁን ዛሬ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ላይ በትግራይ ሰላም ሰራዊት ላይ የከባድ መሳሪያ ተኩስ መጀመሩን ምንጮቻችን ገልፀዋል።
እራሱን 'የትግራይ ሰላም ሰራዊት' በሚል የተደራጀው ታጣቂ ሀይል ወደ መቀሌ ለመግባት ዝግጁ መሆኑን ከሳምንት በፊት አሳውቆ ነበር።
Seledadotio
Seledadotio
7 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የእንግሊዙ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮን ማንችስተር ሲቲ፣ ስፔናዊውን ድንቅ አማካይ ሮድሪን ለማስፈረም ከስፔኑ ታላቅ ክለብ ባርሴሎና የቀረበለትን የ38.5 ሚሊዮን ፓውንድ የመነሻ ጥያቄ ውድቅ አደረገ! ሲቲ ተጫዋቹን ለመሸጥ በሩን ክፍት ቢያደርግም፣ ለዝውውሩ ግን ቢያንስ ከ60 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ካልቀረበለት እንደማይደራደር አሳውቋል።
የ30 ዓመቱ ኮከብ በኢትሃድ ስታዲየም ያለው ኮንትራት በመጨረሻው ዓመት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ እስካሁን አዲስ ውል ባለመፈረሙ ምክንያት "የፊታችን ክረምት ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆን?" የሚለው ጉዳይ የዝውውር ገበያውን እያሟሟቀው ይገኛል።
መጀመሪያ ላይ የአውሮፓው ነገስታት ሪያል ማድሪድን ይቀላቀላል ተብሎ በስፋት ቢታሰብም፣ አሁን ግን የላሊጋው ተቀናቃኝ ባርሴሎና በዝውውር ፉክክሩ ፊት አውራሪ ሆኖ ብቅ ብሏል። ቢቢሲ ስፖርት ከታማኝ ምንጮች እንዳረጋገጠው ከሆነ፣ የካታሎኑ ክለብ ከተጫዋቹ ጋር ድርድር ለመጀመር ይሁንታ አግኝቶ አርብ ዕለት ይፋዊ የመነሻ ጥያቄውን ለሲቲ አቅርቧል። ባርሴሎና ከተጫዋቹ ወኪሎች ጋር ንግግሩን አጠናክሮ መቀጠሉንም አሳውቋል።
በሌላ በኩል ሮድሪን ለማስፈረም ከሪያል ማድሪድ ጋር የነበረው ድርድር ሙሉ በሙሉ መቋረጡ ተረጋግጧል። የስፔኑ ሬዲዮ 'ካዴና ሰር' የሮድሪን ወኪል ፓብሎ ባርኬሮን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ስፔን የዓለም ዋንጫን ካነሳች በኋላ ሪያል ማድሪድ ለተጫዋቹ "እምቢ ለማለት የሚያስቸግር" እጅግ ማራኪ ጥያቄ አቅርቦለት ነበር።
ከፕሬዝዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ እስከ ዋና ስራ አስፈፃሚው ሆሴ አንጄል ሳንቼዝ ድረስ ዝውውሩን እውን ለማድረግ ሌት ተቀን ቢሰሩም፣ እና ድርድሩም በከፍተኛ መከባበር ቢካሄድም፤ ሮድሪ ሌላ አማራጭን በመቀበል የራሱን የግል ውሳኔ አሳልፏል። ማድሪድም ይህንን የተጫዋቹን ውሳኔ አርብ ዕለት ሲሰማ፣ ውዥንብርን ላለመፍጠር ሲል ተጫዋቹን በማመስገን በሰለጠነ መንገድ ከዝውውር ፉክክሩ ራሱን አግልሏል።
የ2024ቱ የባሎንዶር አሸናፊ የሆነው ሮድሪ፣ በ2024-25 የውድድር ዘመን በገጠመው ከባድ የጉልበት ጉዳት እና ባለፈው የውድድር ዘመን ባስተናገደው የቋንጃ ጉዳት ምክንያት አብዛኛውን ጊዜ ከሜዳ ርቆ አሳልፏል። ይሁን እንጂ በክረምቱ የዓለም ዋንጫ አስደናቂ ብቃቱን ዳግም በማሳየት ስፔንን ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮን እንድትሆን ከመምራቱም በላይ፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።
ባለፈው ወር በጀርባው ላይ በተደረገለት ቀዶ ጥገና ምክንያት አሁን ላይ ከሜዳ የራቀ ቢሆንም፣ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ማንችስተር ከሚገኙት የቡድን አጋሮቹ ጋር ለልምምድ ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።
የነሀሴ ወር የዝውውር መስኮት ሁለተኛ ሳምንት ላይ እንደመገኘታችን፣ ማንችስተር ሲቲ የሮድሪን ጉዳይ በፍጥነት እልባት በመስጠት ጠንካራ ተተኪ ለማስፈረም ቆርጦ ተነስቷል። ሲቲዎች የ18 ዓመቱን ሞሮኳዊ የሊል አማካይ አዩብ ቡአዲን ወደ ኢትሃድ ለማምጣት ድርድር ላይ ቢሆኑም፣ የፈረንሳዩ ክለብ የጠየቀው 86 ሚሊዮን ፓውንድ ግን ለዝውውሩ ትልቅ እንቅፋት ሆኖባቸዋል።
የሮድሪ ቀጣይ ማረፊያ ካምፕ ኑ ይሆን? የዝውውር መስኮቱ የሚዘጋበት ቀን እየተቃረበ ሲመጣ፣ የዚህ ኮከብ ተጫዋች ፊርማ እጣ ፈንታ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
የ30 ዓመቱ ኮከብ በኢትሃድ ስታዲየም ያለው ኮንትራት በመጨረሻው ዓመት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ እስካሁን አዲስ ውል ባለመፈረሙ ምክንያት "የፊታችን ክረምት ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆን?" የሚለው ጉዳይ የዝውውር ገበያውን እያሟሟቀው ይገኛል።
መጀመሪያ ላይ የአውሮፓው ነገስታት ሪያል ማድሪድን ይቀላቀላል ተብሎ በስፋት ቢታሰብም፣ አሁን ግን የላሊጋው ተቀናቃኝ ባርሴሎና በዝውውር ፉክክሩ ፊት አውራሪ ሆኖ ብቅ ብሏል። ቢቢሲ ስፖርት ከታማኝ ምንጮች እንዳረጋገጠው ከሆነ፣ የካታሎኑ ክለብ ከተጫዋቹ ጋር ድርድር ለመጀመር ይሁንታ አግኝቶ አርብ ዕለት ይፋዊ የመነሻ ጥያቄውን ለሲቲ አቅርቧል። ባርሴሎና ከተጫዋቹ ወኪሎች ጋር ንግግሩን አጠናክሮ መቀጠሉንም አሳውቋል።
በሌላ በኩል ሮድሪን ለማስፈረም ከሪያል ማድሪድ ጋር የነበረው ድርድር ሙሉ በሙሉ መቋረጡ ተረጋግጧል። የስፔኑ ሬዲዮ 'ካዴና ሰር' የሮድሪን ወኪል ፓብሎ ባርኬሮን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ስፔን የዓለም ዋንጫን ካነሳች በኋላ ሪያል ማድሪድ ለተጫዋቹ "እምቢ ለማለት የሚያስቸግር" እጅግ ማራኪ ጥያቄ አቅርቦለት ነበር።
ከፕሬዝዳንት ፍሎሬንቲኖ ፔሬዝ እስከ ዋና ስራ አስፈፃሚው ሆሴ አንጄል ሳንቼዝ ድረስ ዝውውሩን እውን ለማድረግ ሌት ተቀን ቢሰሩም፣ እና ድርድሩም በከፍተኛ መከባበር ቢካሄድም፤ ሮድሪ ሌላ አማራጭን በመቀበል የራሱን የግል ውሳኔ አሳልፏል። ማድሪድም ይህንን የተጫዋቹን ውሳኔ አርብ ዕለት ሲሰማ፣ ውዥንብርን ላለመፍጠር ሲል ተጫዋቹን በማመስገን በሰለጠነ መንገድ ከዝውውር ፉክክሩ ራሱን አግልሏል።
የ2024ቱ የባሎንዶር አሸናፊ የሆነው ሮድሪ፣ በ2024-25 የውድድር ዘመን በገጠመው ከባድ የጉልበት ጉዳት እና ባለፈው የውድድር ዘመን ባስተናገደው የቋንጃ ጉዳት ምክንያት አብዛኛውን ጊዜ ከሜዳ ርቆ አሳልፏል። ይሁን እንጂ በክረምቱ የዓለም ዋንጫ አስደናቂ ብቃቱን ዳግም በማሳየት ስፔንን ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮን እንድትሆን ከመምራቱም በላይ፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል።
ባለፈው ወር በጀርባው ላይ በተደረገለት ቀዶ ጥገና ምክንያት አሁን ላይ ከሜዳ የራቀ ቢሆንም፣ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ማንችስተር ከሚገኙት የቡድን አጋሮቹ ጋር ለልምምድ ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።
የነሀሴ ወር የዝውውር መስኮት ሁለተኛ ሳምንት ላይ እንደመገኘታችን፣ ማንችስተር ሲቲ የሮድሪን ጉዳይ በፍጥነት እልባት በመስጠት ጠንካራ ተተኪ ለማስፈረም ቆርጦ ተነስቷል። ሲቲዎች የ18 ዓመቱን ሞሮኳዊ የሊል አማካይ አዩብ ቡአዲን ወደ ኢትሃድ ለማምጣት ድርድር ላይ ቢሆኑም፣ የፈረንሳዩ ክለብ የጠየቀው 86 ሚሊዮን ፓውንድ ግን ለዝውውሩ ትልቅ እንቅፋት ሆኖባቸዋል።
የሮድሪ ቀጣይ ማረፊያ ካምፕ ኑ ይሆን? የዝውውር መስኮቱ የሚዘጋበት ቀን እየተቃረበ ሲመጣ፣ የዚህ ኮከብ ተጫዋች ፊርማ እጣ ፈንታ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
8 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' የተሰኘው ስብስብ በቅርቡ ሶስት ሰላማዊ የፖለቲካ ታጋዮች መታሰራቸውን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ ድርጊቱ በሀገሪቱ የፖለቲካ ምህዳር ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ጫና እንደሚያሳድር ገልጾ፣ መንግስት የታሰሩትን ግለሰቦች ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ አሳሰበ። ስብስቡ በዚሁ ወቅታዊ መግለጫው "የሠላማዊ ትግል በሮችን በሙሉ ዘግቶ የጦርነት በሮች እንዲከፈቱ ሳይታክት የሚሠራ አለ ወይ?" ሲል ጠንከር ያለ ጥያቄ አቅርቧል።
ስብስቡ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለው የሚያምኑት አቶ አበበ አካሉ፣ አቶ ይስኃቅ ወልዳይ እና ጠበቃ አበራ ንጉሥ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ለእስር መዳረጋቸው በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሯል። ይህንን ክስተትም እጅግ አስደንጋጭ ሆኖ እንዳገኘው አስታውቋል።
አሁን ስራ ላይ ባለው ህገ መንግስት አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ማንኛውም ሰው ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን በነጻነት የመግለጽ፣ በምንም አይነት የማሰራጫ ዘዴ መረጃን የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት መብቱ የተረጋገጠ መሆኑን መግለጫው አስታውሷል። ይሁን እንጂ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ፣ ከህገ መንግስቱ ባፈነገጠ መልኩ ከውዳሴ በስተቀር ምንም አይነት የተቃውሞ እና የትችት ድምጾች እንዳይሰሙ ማሳደድ ያልተጻፈ ህግና መርህ መሆኑን ስብስቡ በመግለጫው አትቷል።
ይህ አካሄድ "ሰላማዊ ትግል ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ ሌሎች አማራጮች እንዲናኙ የሚሰራ ግራ ሃይል ተፈጥሯል ወይ?" የሚል ጥርጣሬ እንዳሳደረበት 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' በግልጽ አስቀምጧል። በመሆኑም መንግስት በጠባብ ቀዳዳ የምትታየውን የፖለቲካ ምህዳር ጭራሹኑ ከማጥፋት ክፉኛ ሊጠነቀቅ ይገባል በማለት፣ በእስር ላይ የሚገኙት የሰላማዊ ፖለቲካ ታጋዮች የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥሪውን አስተላልፏል።
ስብስቡ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ለውጥ ማምጣት ይቻላል ብለው የሚያምኑት አቶ አበበ አካሉ፣ አቶ ይስኃቅ ወልዳይ እና ጠበቃ አበራ ንጉሥ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ለእስር መዳረጋቸው በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሯል። ይህንን ክስተትም እጅግ አስደንጋጭ ሆኖ እንዳገኘው አስታውቋል።
አሁን ስራ ላይ ባለው ህገ መንግስት አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ማንኛውም ሰው ያለ ማንም ጣልቃ ገብነት ሀሳቡን በነጻነት የመግለጽ፣ በምንም አይነት የማሰራጫ ዘዴ መረጃን የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት መብቱ የተረጋገጠ መሆኑን መግለጫው አስታውሷል። ይሁን እንጂ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ፣ ከህገ መንግስቱ ባፈነገጠ መልኩ ከውዳሴ በስተቀር ምንም አይነት የተቃውሞ እና የትችት ድምጾች እንዳይሰሙ ማሳደድ ያልተጻፈ ህግና መርህ መሆኑን ስብስቡ በመግለጫው አትቷል።
ይህ አካሄድ "ሰላማዊ ትግል ሙሉ በሙሉ ተዘግቶ ሌሎች አማራጮች እንዲናኙ የሚሰራ ግራ ሃይል ተፈጥሯል ወይ?" የሚል ጥርጣሬ እንዳሳደረበት 'ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት' በግልጽ አስቀምጧል። በመሆኑም መንግስት በጠባብ ቀዳዳ የምትታየውን የፖለቲካ ምህዳር ጭራሹኑ ከማጥፋት ክፉኛ ሊጠነቀቅ ይገባል በማለት፣ በእስር ላይ የሚገኙት የሰላማዊ ፖለቲካ ታጋዮች የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጥሪውን አስተላልፏል።
Sponsored by
Surafel
8 hours ago
በበጀት አመት ከ118 ቢሊዮን ብር በላይ ማግኘት ተችሏል
#eghiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት አመት 118 ነጥብ 91 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለፀ።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በሰጡት መግለጫ ገቢው ከኢነርጂ ሽያጭ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ከኢነርጂ ሽያጭ 75 ነጥብ 17 ቢሊየን ብር ለማግኘት ታቅዶ የውጭ ሀገር ሽያጭን ጨምሮ 76 ነጥብ 53 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 37 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 39 ነጥብ 23 ቢሊየን ብር መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
የማያገለግሉ ንብረቶችን በመሸጥ 275 ሚሊየን ብር የተገኘ ሲሆን ከልዩ ልዩ ገቢዎች ደግሞ 2 ነጥብ 68 ቢሊየን ብር መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የገቢ አፈጻጸሙ 103 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ88 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ማሳየቱን አመልክተዋል፡፡
የዲጂታል ክፍያ አማራጭ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቶ በአሁን ወቅት 95 ነጥብ 3 በመቶ መደረሱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ገንብቶ ወደ ስራ በማስገባትና ስራ በማስጀመር 14 ነጥብ 25 ሚሊየን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #የኢትዮጵያ #ኤሌክትሪክአገልግሎት #ኤነርጂ #ገበያ #ትርፍ
#eghiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠናቀቀው የ2018 በጀት አመት 118 ነጥብ 91 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለፀ።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በሰጡት መግለጫ ገቢው ከኢነርጂ ሽያጭ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ከኢነርጂ ሽያጭ 75 ነጥብ 17 ቢሊየን ብር ለማግኘት ታቅዶ የውጭ ሀገር ሽያጭን ጨምሮ 76 ነጥብ 53 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 37 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 39 ነጥብ 23 ቢሊየን ብር መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
የማያገለግሉ ንብረቶችን በመሸጥ 275 ሚሊየን ብር የተገኘ ሲሆን ከልዩ ልዩ ገቢዎች ደግሞ 2 ነጥብ 68 ቢሊየን ብር መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የገቢ አፈጻጸሙ 103 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ88 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ማሳየቱን አመልክተዋል፡፡
የዲጂታል ክፍያ አማራጭ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቶ በአሁን ወቅት 95 ነጥብ 3 በመቶ መደረሱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ገንብቶ ወደ ስራ በማስገባትና ስራ በማስጀመር 14 ነጥብ 25 ሚሊየን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #የኢትዮጵያ #ኤሌክትሪክአገልግሎት #ኤነርጂ #ገበያ #ትርፍ
9 hours ago
ከ120 አመት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ውሃ የተቋረጠባት ሀገር ለዜጎቿ ውሃ በፈረቃ ጀመረች!
#ethiopia | በፖርቶ ሪኮ ከ120 አመት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ለ48 ሰአታት ያህል የቧንቧ ውሃ መቋረጡ ተነገረ።
በአካባቢው ያለው አሮጌና ለዘመናት በቂ እድሳት ያልተደረገለት የውሃ መስመር መሰረተ ልማት ችግሩን የበለጠ አባብሶታል።
በግዛቲቷ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ለ48 ሰዓታት ያህል ከቧንቧ ውሃ ርቀዋል ተብሏል።
በዋና ከተማዋ ሳን ሁዋን እና በዙሪያዋ ባሉ ዋና ዋና ከተሞች የሚኖሩ ከ180,000 በላይ ዜጎች ለ48 ሰዓታት ያህል ውሃ በፈረቃ እንዲያነኙ ተደርጓል።
የአካባቢው ባለስልጣናት እና የአየር ንብረት ባለሙያዎች እንዳሉት አሁን እየተመዘገበ ያለው ከባድ የሙቀት መጠን የሚቀጥል ከሆነ ነዋሪዎች ያለ ቧንቧ ውሃ የሚቆዩበት ጊዜ እስከ 72 ሰዓታት ሊራዘም ይችላል ብለዋል።
የግዛቲቱ ዋና ገዢ ጄኒፈር ጎንዛሌዝ እንደገለጹት ሁኔታው ከአቅማችን በላይ እየሆነ ነው ሲሉ የአየር ንብረት መዛባቱ ሁኔታውን እንዳባባሰው ገልጸዋል።
የአደጋ ጊዜ አገልግሎቶች ለሆስፒታሎችና ለወጣቶች/አረጋውያን መኖሪያዎች በቦቲ ውሃ በማደል ቅድሚያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #puertorico #water #shutoffs
#ethiopia | በፖርቶ ሪኮ ከ120 አመት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ለ48 ሰአታት ያህል የቧንቧ ውሃ መቋረጡ ተነገረ።
በአካባቢው ያለው አሮጌና ለዘመናት በቂ እድሳት ያልተደረገለት የውሃ መስመር መሰረተ ልማት ችግሩን የበለጠ አባብሶታል።
በግዛቲቷ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ለ48 ሰዓታት ያህል ከቧንቧ ውሃ ርቀዋል ተብሏል።
በዋና ከተማዋ ሳን ሁዋን እና በዙሪያዋ ባሉ ዋና ዋና ከተሞች የሚኖሩ ከ180,000 በላይ ዜጎች ለ48 ሰዓታት ያህል ውሃ በፈረቃ እንዲያነኙ ተደርጓል።
የአካባቢው ባለስልጣናት እና የአየር ንብረት ባለሙያዎች እንዳሉት አሁን እየተመዘገበ ያለው ከባድ የሙቀት መጠን የሚቀጥል ከሆነ ነዋሪዎች ያለ ቧንቧ ውሃ የሚቆዩበት ጊዜ እስከ 72 ሰዓታት ሊራዘም ይችላል ብለዋል።
የግዛቲቱ ዋና ገዢ ጄኒፈር ጎንዛሌዝ እንደገለጹት ሁኔታው ከአቅማችን በላይ እየሆነ ነው ሲሉ የአየር ንብረት መዛባቱ ሁኔታውን እንዳባባሰው ገልጸዋል።
የአደጋ ጊዜ አገልግሎቶች ለሆስፒታሎችና ለወጣቶች/አረጋውያን መኖሪያዎች በቦቲ ውሃ በማደል ቅድሚያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #puertorico #water #shutoffs
10 hours ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን እና አየር ኃይሉም ይህን ለማስጠበቅ አቅሙን እየገነባ እንደሚገኝ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን እጅግ ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ። የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው እንዳሉት፣ ተቋሙ ይህንን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚመጥን ጠንካራ አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚዘልቅ ነው። አየር ኃይሉም ለዚህ አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም የሚመጥን የላቀ የመከላከል አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል።
ምክትል አዛዡ አክለውም ባላጋራ ኃይሎች የቱንም ያህል ፍላጎትና ዛቻ ቢኖራቸውም፣ የአየር ኃይሉ የመከላከል አቅም በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ ስለሚረዱት ጥቃት ከመሰንዘር መቆጠባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ የአየር ኃይሉ ከአፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት፤ በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በእውቀት እና ራስን ችሎ በመሥራት በኩል ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ድርሻ እንደምትይዝ አስረድተዋል።
እንደ ምክትል አዛዡ ገለጻ፣ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቋሙን ለመጎብኘት የሚመጡ የልዑካን ቡድኖች በአየር ኃይሉ ውስጥ ያለውን ዘመናዊ አሠራር ሲመለከቱ ከጠበቁት በላይ ይሆንባቸዋል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር “በጋራ እንሥራ” የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከሦስት በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችሉ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን እጅግ ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ። የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው እንዳሉት፣ ተቋሙ ይህንን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚመጥን ጠንካራ አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚዘልቅ ነው። አየር ኃይሉም ለዚህ አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም የሚመጥን የላቀ የመከላከል አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል።
ምክትል አዛዡ አክለውም ባላጋራ ኃይሎች የቱንም ያህል ፍላጎትና ዛቻ ቢኖራቸውም፣ የአየር ኃይሉ የመከላከል አቅም በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ ስለሚረዱት ጥቃት ከመሰንዘር መቆጠባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ የአየር ኃይሉ ከአፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት፤ በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በእውቀት እና ራስን ችሎ በመሥራት በኩል ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ድርሻ እንደምትይዝ አስረድተዋል።
እንደ ምክትል አዛዡ ገለጻ፣ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቋሙን ለመጎብኘት የሚመጡ የልዑካን ቡድኖች በአየር ኃይሉ ውስጥ ያለውን ዘመናዊ አሠራር ሲመለከቱ ከጠበቁት በላይ ይሆንባቸዋል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር “በጋራ እንሥራ” የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከሦስት በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችሉ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 hours ago
ተወዳጇ አርቲስት ቬሮኒካ አዳነህ በነፃ ለSUSU HUMAN HAIR አምባሳደር ሆነች!!!
በህይወቴ ብዙ ፈተናዎችን እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ። ነገር ግን ከልጅነቴ ጀምሮ ያሰብኩትን ነገር ከማሳካት የሚያስቆመኝ ምንም አይነት ችግር ሆነ ፈተና አልነበረም።
በስደት ሀገር እንደማንኛውም ስደተኛ ሰው ቤት ተቀጥሬ እሰራ ነበር። ከዛ በመውጣት የራሴን ስራ ለመስራት ሞከርኩ። በትንሽዬ የሴቶች የውበት ሳሎን በመጀመር፣ በሊባኖስ ዋና ከተማ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ እስከመሆን ደረስኩ። ህይወቴ እየተለወጠ፣ እያደግኩ እና እየተሳካልኝ ሲመጣ በማህበራዊ ሚዲያ (በቲክቶክ) ብቅ አልኩ በሀቢባ ቤት LIVE በመግባት እውቅናንም ማግኘት ጀመርኩ ሀቢባ ታዋቂ ለመሆኔ ምክንያት ሆነችኝ። ያኔም ነው ቬሮኒካ አዳነ ያወቀችኝ እንደምወዳት እና አድናቂዋ እንደሆንኩኝ በሷ ሙዚቃ በምሰራቸው ቪድዎች አየች ኮሜንት ለመጀርያ ጊዜ ስትፅፍልኝ የነበረውን ስሜት አልረሳውም። በቬሮኒካም ምክንያት በደንብ ታዋቂ መሆን ጀመርኩ፤
በዚያም ብዙ ወዳጆችን በማፍራት ስሜ በሀገሬ በኢትዮጵያም መታወቅ ጀመረ፤ ተደራሽነቴ እየሰፋ ሄዶ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ያሉ ደንበኞችን ማፈራት ቻልኩ። የመጀመሪያ ልጄንም በዚህ ስራ ላይ እያለሁ ወለድኩ፤ ይህም ይበልጥ ጠንካራ አደረገኝ።
ነገር ግን፣ ምንም በማላውቀው ምክንያት
ሁለት ወር እስራት ገጠመኝ ከዛ በኋላ ከእስር ቤት ወጥቼ ወደ ሀገሬ ገባው በህይወቴ ትልቁን ፈተና የተፈተንኩት ያኔ ነበር ለአስር ዓመታት የለፋሁበትን ህይወት፣ ስራዬን እና ከልጄ ጋር የነበረኝን አንድነት እንደ ቀልድ አጣሁት።
እውነት ለመናገር ያኔ ተስፋዬ ተሟጦ አልቆ ነበር። ነገር ግን ፈጣሪ ሁሌም አለ፤ አይተወኝም። ጠንካራ ሴት ነኝና በህይወቴ እንደ ሀቢባ እና ቬሮኒካ አዳነ ያሉ ጠንካራ ሴቶችን ላከልኝ። ልወድቅ ስል ደገፉኝ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሉ ውድ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የሚወዱኝ ሰዎች ትልቅ ድጋፍ ሆኑኝ።
ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ በኋላ፣ የምወዳት እና የማደንቃት አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ በህይወቴ የማልረሳውን ትልቅ ውለታ ውላልኛለች፤ *«የሁለት ዓመት በነፃ ያለ ምንም ክፍያ የ’ሱሱ ሂውማን ሄር’ (Susu Human Hair) አምባሳደር ነኝ»* ብላ ሰርፕራይዝ አደረገችኝ። ይህ የህይወቴ ትልቁ ሰርፕራይዝ ነበር! ልጄም ወደ ሀገሩ ተመለሰ። በሀቢባ፣ በወዳጆቿ እና በአድናቂዎቼ አማካኝነትም የገንዘብ ድጋፍ ተደረገልኝ።
አሁን የህይወቴ ትልቁ ምዕራፍ ላይ እገኛለሁ። የሂውማን ሄር መሸጫዬን እና የውበት ሳሎኔን እዚሁ ሀገሬ ላይ ልከፍት ነው። ቬሮኒካ አዳነ የ2 ዓመት አምባሳደሬ ሆና በነፃ ትሰራለች፤ ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋርም አብሬ እየሰራሁ እገኛለሁ።
አሁን ማንም ሊያስቆመኝ አይችልም! ፈጣሪ ሳይደግስ አይጣላም ከፍ እንድል ምክንያት ሆነውኛል
ከፈተናዎች ማዶ የተገነባ ስኬት:- የሱመያ ዋሪስ የህይወት ጉዞ
እኔ SUSU HUMAN HAIR ነኝ።
በህይወቴ ብዙ ፈተናዎችን እና ተስፋ የሚያስቆርጡ ውጣ ውረዶችን አሳልፌያለሁ። ነገር ግን ከልጅነቴ ጀምሮ ያሰብኩትን ነገር ከማሳካት የሚያስቆመኝ ምንም አይነት ችግር ሆነ ፈተና አልነበረም።
በስደት ሀገር እንደማንኛውም ስደተኛ ሰው ቤት ተቀጥሬ እሰራ ነበር። ከዛ በመውጣት የራሴን ስራ ለመስራት ሞከርኩ። በትንሽዬ የሴቶች የውበት ሳሎን በመጀመር፣ በሊባኖስ ዋና ከተማ ታዋቂ የሂውማን ሄር (Human Hair) አስመጪ እስከመሆን ደረስኩ። ህይወቴ እየተለወጠ፣ እያደግኩ እና እየተሳካልኝ ሲመጣ በማህበራዊ ሚዲያ (በቲክቶክ) ብቅ አልኩ በሀቢባ ቤት LIVE በመግባት እውቅናንም ማግኘት ጀመርኩ ሀቢባ ታዋቂ ለመሆኔ ምክንያት ሆነችኝ። ያኔም ነው ቬሮኒካ አዳነ ያወቀችኝ እንደምወዳት እና አድናቂዋ እንደሆንኩኝ በሷ ሙዚቃ በምሰራቸው ቪድዎች አየች ኮሜንት ለመጀርያ ጊዜ ስትፅፍልኝ የነበረውን ስሜት አልረሳውም። በቬሮኒካም ምክንያት በደንብ ታዋቂ መሆን ጀመርኩ፤
በዚያም ብዙ ወዳጆችን በማፍራት ስሜ በሀገሬ በኢትዮጵያም መታወቅ ጀመረ፤ ተደራሽነቴ እየሰፋ ሄዶ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ሀገራት ያሉ ደንበኞችን ማፈራት ቻልኩ። የመጀመሪያ ልጄንም በዚህ ስራ ላይ እያለሁ ወለድኩ፤ ይህም ይበልጥ ጠንካራ አደረገኝ።
ነገር ግን፣ ምንም በማላውቀው ምክንያት
ሁለት ወር እስራት ገጠመኝ ከዛ በኋላ ከእስር ቤት ወጥቼ ወደ ሀገሬ ገባው በህይወቴ ትልቁን ፈተና የተፈተንኩት ያኔ ነበር ለአስር ዓመታት የለፋሁበትን ህይወት፣ ስራዬን እና ከልጄ ጋር የነበረኝን አንድነት እንደ ቀልድ አጣሁት።
እውነት ለመናገር ያኔ ተስፋዬ ተሟጦ አልቆ ነበር። ነገር ግን ፈጣሪ ሁሌም አለ፤ አይተወኝም። ጠንካራ ሴት ነኝና በህይወቴ እንደ ሀቢባ እና ቬሮኒካ አዳነ ያሉ ጠንካራ ሴቶችን ላከልኝ። ልወድቅ ስል ደገፉኝ፤ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሉ ውድ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የሚወዱኝ ሰዎች ትልቅ ድጋፍ ሆኑኝ።
ከዚህ ሁሉ ውጣ ውረድ በኋላ፣ የምወዳት እና የማደንቃት አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ በህይወቴ የማልረሳውን ትልቅ ውለታ ውላልኛለች፤ *«የሁለት ዓመት በነፃ ያለ ምንም ክፍያ የ’ሱሱ ሂውማን ሄር’ (Susu Human Hair) አምባሳደር ነኝ»* ብላ ሰርፕራይዝ አደረገችኝ። ይህ የህይወቴ ትልቁ ሰርፕራይዝ ነበር! ልጄም ወደ ሀገሩ ተመለሰ። በሀቢባ፣ በወዳጆቿ እና በአድናቂዎቼ አማካኝነትም የገንዘብ ድጋፍ ተደረገልኝ።
አሁን የህይወቴ ትልቁ ምዕራፍ ላይ እገኛለሁ። የሂውማን ሄር መሸጫዬን እና የውበት ሳሎኔን እዚሁ ሀገሬ ላይ ልከፍት ነው። ቬሮኒካ አዳነ የ2 ዓመት አምባሳደሬ ሆና በነፃ ትሰራለች፤ ከቻይና ሂውማን ሄር ኩባንያ ጋርም አብሬ እየሰራሁ እገኛለሁ።
አሁን ማንም ሊያስቆመኝ አይችልም! ፈጣሪ ሳይደግስ አይጣላም ከፍ እንድል ምክንያት ሆነውኛል
ከፈተናዎች ማዶ የተገነባ ስኬት:- የሱመያ ዋሪስ የህይወት ጉዞ
እኔ SUSU HUMAN HAIR ነኝ።
Sponsored by
Surafel
12 hours ago
በሞትና በህይወት መካከል ናቸው
#ethiopia | የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከካንሰር ህመም ጋር ትግል እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ።
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በደረጃ 4 የፕሮስቴት ካንሰር ጋር እያደረጉት ባለው ህክምና ላይ ባለቤታቸው ዶ/ር ጂል ባይደን ልብ የሚነካ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የቀድሞው ፕሬዚዳንት ከኋይት ሀውስ ከተለዩ በኋላ በ2025 ህመሙ እንደተገኘባቸው ይታወሳል።
በጊዜው ካንሰሩ ከፍተኛ የጉዳት ደረጃ ያለውና አጥንት ላይ የደረሰ እንደሆነ ተገልጾ ነበር።
ጂል ባይደን ከኬሊ ሪፓ ጋር በነበራቸው የፖድካስት ቆይታ ወቅት እንደገለጹት የካንሰሩ ህመም ወደ አጥንታቸው በመሰራጨቱ ሙሉ በሙሉ ማዳን የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።
ካንሰሩ ወደ አጥንት በመሰራጨቱ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ሊድን እንደማይችል የተናገሩት ጂል ባይደን
ጆ ባይደን እስከ ህይወቱ ፍፃሜ ድረስ ከካንሰር ጋር ይኖራል ብለዋል።
አሁን ላይ በየሶስት ወሩ በሚደረጉ የህክምና ክትትሎች እና መድኃኒቶች ህመሙን የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ ይገኛል ሲሉም አክለዋል።
ጂል ባይደን በኋይት ሀውስ በነበሩበት ወቅት የፕሬዚዳንቱን የጤና ሁኔታ ደብቀዋል በሚል ወቀሳ ደርሷቸው ነበር።
ካንሰሩ እድገቱን ለማዘገየት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝና አሁን ባለው ሁኔታ ባይደን በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usapresident #cancer #joebiden #jilebiden
#ethiopia | የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከካንሰር ህመም ጋር ትግል እያደረጉ መሆናቸው ተገለፀ።
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በደረጃ 4 የፕሮስቴት ካንሰር ጋር እያደረጉት ባለው ህክምና ላይ ባለቤታቸው ዶ/ር ጂል ባይደን ልብ የሚነካ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የቀድሞው ፕሬዚዳንት ከኋይት ሀውስ ከተለዩ በኋላ በ2025 ህመሙ እንደተገኘባቸው ይታወሳል።
በጊዜው ካንሰሩ ከፍተኛ የጉዳት ደረጃ ያለውና አጥንት ላይ የደረሰ እንደሆነ ተገልጾ ነበር።
ጂል ባይደን ከኬሊ ሪፓ ጋር በነበራቸው የፖድካስት ቆይታ ወቅት እንደገለጹት የካንሰሩ ህመም ወደ አጥንታቸው በመሰራጨቱ ሙሉ በሙሉ ማዳን የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል።
ካንሰሩ ወደ አጥንት በመሰራጨቱ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ሊድን እንደማይችል የተናገሩት ጂል ባይደን
ጆ ባይደን እስከ ህይወቱ ፍፃሜ ድረስ ከካንሰር ጋር ይኖራል ብለዋል።
አሁን ላይ በየሶስት ወሩ በሚደረጉ የህክምና ክትትሎች እና መድኃኒቶች ህመሙን የመቆጣጠር ስራ እየተሰራ ይገኛል ሲሉም አክለዋል።
ጂል ባይደን በኋይት ሀውስ በነበሩበት ወቅት የፕሬዚዳንቱን የጤና ሁኔታ ደብቀዋል በሚል ወቀሳ ደርሷቸው ነበር።
ካንሰሩ እድገቱን ለማዘገየት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑ እየተደረገ እንደሚገኝና አሁን ባለው ሁኔታ ባይደን በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usapresident #cancer #joebiden #jilebiden
12 hours ago
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 118 ነጥብ 91 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በሰጡት መግለጫ ÷ ገቢው ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ከኢነርጂ ሽያጭ 75 ነጥብ 17 ቢሊየን ብር ለማግኘት ታቅዶ የውጭ ሀገር ሽያጭን ጨምሮ 76 ነጥብ 53 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 37 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 39 ነጥብ 23 ቢሊየን ብር መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
የማያገለግሉ ንብረቶችን በመሸጥ 275 ሚሊየን ብር የተገኘ ሲሆን ÷ ከልዩ ልዩ ገቢዎች ደግሞ 2 ነጥብ 68 ቢሊየን ብር መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የገቢ አፈጻጸሙ 103 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ88 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ማሳየቱን አመልክተዋል፡፡
የዲጂታል ክፍያ አማራጭ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቶ በአሁን ወቅት 95 ነጥብ 3 በመቶ መደረሱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ገንብቶ ወደ ስራ በማስገባትና ስራ በማስጀመር 14 ነጥብ 25 ሚሊየን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በሰጡት መግለጫ ÷ ገቢው ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ፣ ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ እና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች መገኘቱን ተናግረዋል፡፡
በዚህ መሰረትም ከኢነርጂ ሽያጭ 75 ነጥብ 17 ቢሊየን ብር ለማግኘት ታቅዶ የውጭ ሀገር ሽያጭን ጨምሮ 76 ነጥብ 53 ቢሊየን ብር ገቢ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም ከአዲስ ደንበኞች መስተንግዶ 37 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 39 ነጥብ 23 ቢሊየን ብር መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
የማያገለግሉ ንብረቶችን በመሸጥ 275 ሚሊየን ብር የተገኘ ሲሆን ÷ ከልዩ ልዩ ገቢዎች ደግሞ 2 ነጥብ 68 ቢሊየን ብር መገኘቱን አስረድተዋል፡፡
የገቢ አፈጻጸሙ 103 በመቶ መሆኑንና ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ88 ነጥብ 4 በመቶ እድገት ማሳየቱን አመልክተዋል፡፡
የዲጂታል ክፍያ አማራጭ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መጥቶ በአሁን ወቅት 95 ነጥብ 3 በመቶ መደረሱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች ገንብቶ ወደ ስራ በማስገባትና ስራ በማስጀመር 14 ነጥብ 25 ሚሊየን ብር ገቢ ተገኝቷል ብለዋል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች ላይ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት ቀጠሮ ተሰጠ።
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
13 hours ago
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት 118.91 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረውን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን አስመልክቶ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን አብዛኞቹን ዋና ዋና ግቦች በላቀ ደረጃ ማሳካት መቻሉን እና በተለይም በአዳዲስ ደንበኞች ትስስር ረገድ በተቋሙ ታሪክም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ውጤት ማስመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
በበጀት ዓመቱ 800 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 664 ሺህ 505 አባወራዎችን በማገናኘት የ83.1 በመቶ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህም አፈጻጸም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ32.5 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን፣ ተቋሙን በዓይነቱ ከአፍሪካ መሰል የኃይል አቅርቦት ኩባንያዎች የመሪነት ደረጃ ላይ አሰልፎታል።
በተጨማሪም የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን በማጠናከር ከዋናው ግሪድ እና ከኦፍ-ግሪድ የፀሐይ ኃይል አማራጮች 205 አዳዲስ የገጠር ቀበሌዎችንና መንደሮችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ተደራሽ የሆኑ የገጠር አካባቢዎችን ቁጥር ወደ 7 ሺህ 908 አድርሶታል።
በፋይናንስና በገቢ አሰባሰብ ረገድም ተቋሙ አስደናቂ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን፣ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዳዲስ ደንበኞች መስተንግዶና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች 115.86 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 118.91 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የ103 በመቶ አፈጻጸም አሳይቷል።
ይህ የገቢ መጠን ከቀደመው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ88.4 በመቶ ከፍተኛ እድገት ያሳየ ነው። ለዚህ አፈጻጸም መሻሻል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ክፍያ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር 95.3 በመቶ ደርሷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ከስርቆትና ከኃይል ብክነት የመከላከል ሥራዎችን በማጠናከር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ለተቋሙ ገቢ ማድረግ ችሏል።
ተቋሙ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ሰፊ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች ማሻሻያ፣ የትራንስፎርመር ጥገናና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ያከናወነ ቢሆንም፣ አሁንም የመሰረተ ልማት እርጅና፣ የግብዓትና የነዳጅ እጥረት እንዲሁም የመሰረተ ልማቶች ስርቆትና ውድመት ዋና ዋና ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገልጿል።
ሆኖም ተቋሙ የተደቀኑበትን ተግዳሮቶች በመቋቋም የቴክኖሎጂ ትግበራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት የሚጠበቅበትን የላቀ ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
ጌትነት ተመስገን
#ethiopianelectricutility #eeu #ethiopia #energysector #ethiopianeconomy #digitalethiopia2030 #ruralelectrification #offgridenergy #performancereport #africaenergy
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረውን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን አስመልክቶ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን አብዛኞቹን ዋና ዋና ግቦች በላቀ ደረጃ ማሳካት መቻሉን እና በተለይም በአዳዲስ ደንበኞች ትስስር ረገድ በተቋሙ ታሪክም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ውጤት ማስመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
በበጀት ዓመቱ 800 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 664 ሺህ 505 አባወራዎችን በማገናኘት የ83.1 በመቶ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህም አፈጻጸም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ32.5 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን፣ ተቋሙን በዓይነቱ ከአፍሪካ መሰል የኃይል አቅርቦት ኩባንያዎች የመሪነት ደረጃ ላይ አሰልፎታል።
በተጨማሪም የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን በማጠናከር ከዋናው ግሪድ እና ከኦፍ-ግሪድ የፀሐይ ኃይል አማራጮች 205 አዳዲስ የገጠር ቀበሌዎችንና መንደሮችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ተደራሽ የሆኑ የገጠር አካባቢዎችን ቁጥር ወደ 7 ሺህ 908 አድርሶታል።
በፋይናንስና በገቢ አሰባሰብ ረገድም ተቋሙ አስደናቂ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን፣ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዳዲስ ደንበኞች መስተንግዶና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች 115.86 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 118.91 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የ103 በመቶ አፈጻጸም አሳይቷል።
ይህ የገቢ መጠን ከቀደመው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ88.4 በመቶ ከፍተኛ እድገት ያሳየ ነው። ለዚህ አፈጻጸም መሻሻል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ክፍያ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር 95.3 በመቶ ደርሷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ከስርቆትና ከኃይል ብክነት የመከላከል ሥራዎችን በማጠናከር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ለተቋሙ ገቢ ማድረግ ችሏል።
ተቋሙ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ሰፊ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች ማሻሻያ፣ የትራንስፎርመር ጥገናና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ያከናወነ ቢሆንም፣ አሁንም የመሰረተ ልማት እርጅና፣ የግብዓትና የነዳጅ እጥረት እንዲሁም የመሰረተ ልማቶች ስርቆትና ውድመት ዋና ዋና ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገልጿል።
ሆኖም ተቋሙ የተደቀኑበትን ተግዳሮቶች በመቋቋም የቴክኖሎጂ ትግበራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት የሚጠበቅበትን የላቀ ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
ጌትነት ተመስገን
#ethiopianelectricutility #eeu #ethiopia #energysector #ethiopianeconomy #digitalethiopia2030 #ruralelectrification #offgridenergy #performancereport #africaenergy
14 hours ago
ሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እና ኩባንያዎቹ ምን እየሰሩ ነው?
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
👉የብረት ፋብሪካው በከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከአካባቢ ብከላ ነጻ የሆነ የምርት ሂደት መጀመሩ ተነግሯል፡፡
በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ኃ/የተ/ግ/ማ እንደ አገር በአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የተቀመጠውን የኢንደስትሪ ቅጥር ግቢ ሁለት በመቶ ከባቢ በአረንገዴ የመሸፈን ሃላፊነት ተወጥተው ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት አቅራቢያ የማህበረሰብ አቀፍ የአካባቢ ልማት ላይ በጉልህ መሳተፍ እንደቀጠሉ ተገለጠ፡፡
ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ኢንደስትሪዎቹ በሚገኙበት የቢሾፍቱ ከተማ ቅጥር ግቢ እና አካባቢው በሚገኙ የተራቆቱ ስፍራዎቸን በአረንጓዴ የመሸፈን ስራ አጠናክረው የቀጠለ መሆኑ ታውቋል፡፡
በዚህም ዘንድሮው የክረምት ወቅት ከመንግስት ተረክበው መልሶ እንዲያገግም እየተንከባከቡት በሚገኘው ዲባዬ ተራራ በተከታታይ ለ 5ኛ አመት የተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡
ሀሙስ ሐምሌ 30 ቀን በተከናወነው እና የሁለቱ ኩባንያ ሰራተኞች በተሳተፉበት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቢሾፍቱ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ኃላፊ ጣይቱ ያሚ የሁለቱ ድርጅቶች የአረንጓዴ ልማት ተግባር በአካባቢው ለሚገኙ በርካታ ኢንደስትሪዎች አርአያ እና ቀዳሚ ነው ብለዋል፡፡
እንደ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ከኢንደስትሪ ግቢ 2 በመቶ በአረንጓዴ መሸፈን አለበት የሚለውን ህግ በተገቢው ሁለቱም ድርጅቶች መወጣታቸውን አስታውሰው፡፡
በተጨማሪነት በሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር የሚገኙት ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን ከኢንደስትሪ ስፍራዎቻቸው ባለፈ በአዋሳኝ የመንገድ አካባቢዎች እንዲሁም የተራቆቱ ቦታዎችን ወደ ጫካ የመለወጥ ስራን እንዲወጡ በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸውን ቦታዎች በዛፍ የመሸፈን ስራ ለአመታት በከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰሩ እንደቆዩ ነው የተናገሩት፡፡
ከተማ አሰስተዳደሩ በአረንጓዴ ልማት ሆነ ሌሎች ማህበራዊ ሃላፊነት ስራዎች ጥሪ ባደረገ ጊዜ ቀድመው የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወሱት የከተማ አስተዳደሩ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ጣይቱ ይህን መልካም ተግባር ሌሎች በተሞክሮ እንዲወስዱት ነው ያሳሰቡት፡፡
በተከላው ወቅት የግዙፉ ብረት አምራች ስቲሊ አር ኤም አይ ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ሰለሞን ደስታ እንደገለፁት ድርጅታቸው ስቲሊ በመርህ ደረጃ የተያዘውን የማህበራዊ ሃላፊነት የመወጣት ተግባር በህብረተሰብ ድጋፍ ላይ ብቻ ያተኮረ አለመሆኑን አስታውሰው፡፡
በአካባቢ ጠበቃ የሚሰራው ስራ የኩባንያው አይነተኛ መርህ መሆኑን እንደ ተጨማሪ የማህበራዊ ሃላፊነት ስራ ተግባር ለአብነት አንስተዋል፡፡
በዚህም ስቲሊ አር ኤም አይ ማምረት ከጀመረበት ያለፉት ሁለት አስርት አመታት ወደ ስራ ካስገባቸው እንደ ዘመናዊ ትምህርት ቤት እንዲሁም የውሃ አቅርቦት አይነት ጉልህ ማህበራዊ ሃላፊነት ባልተናነሰ በአረንጓዴ ልማት ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡
በግቢያችን በመንግስት ከተቀመጠው የሁለት በመቶ አረንጓዴ ሽፋን አልፈናል ያሉት ኢ/ር ሰለሞን ለምግብነት የሚያገለግሉ ዛፎችን የመትከል ግቡም ውጤታማ እየሆነልን ነው ሲሉ ነው ያከሉት።
ዋና ስራ አስኪያጁ በተጨማሪነት በአካበቢው በሚገኙ ተራራማ ቦታዎች ችግኝ በመትከል እና በቋሚነት ባለሞያ ቀጥሮ በመንከባከብ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘት መቻሉንም እንደ ከፍተኛ ተጠቃሽ ውጤት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ኩባያው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት በማድረግ ዘመናዊ የምርት ሂደትን ያስተዋወቀ መሆኑን ጠቅሰው። ይህም የአካባቢ ጥበቃ አካል ነው ሲሉ በአገር ደረጃ በዘመናዊነት ቀዳሚ የሆነው የብረት ፋብሪካ የስራ ሂደት ጠቅሰዋል፡፡
በተመሳሳይ ከፍተኛ ተኪ የብረት ምርት እና የግንባታ ግብአቶችን በማምረት ላለፉት ሩብ ክፍለ ዘመናት መቆየት የቻለው የአስመን ስራ አስኪያጅ አቶ ኑሩ እሸቱ የአረንጓዴ አሻራ ስራ የኩባንያቸው ባህል መሆኑን ጠቅሰው በቀጣይ ይህ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጠል መሆኑን ነው የገለፁት፡፡
እንደ አስመን ስራ አስኪያጅ ገለፃ የኩባንያውን ሰራተኛና የአካበባቢውን ነዋሪ በማሳተፍ ሲከናወን የቆየው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በተለይ አሁን በፋብሪካዎቹ እና የችግኝ ተከላ በሚከናወንበት አቅራቢያ በሚገኘው በአቡሴራ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ አየር መንገድ ምቹ እና አረንጓዴ ከባቢ በመፍጠር የራሱ ሚና አለው ሲሉ ነው የገለጹት፡፡
የሴንቸሪ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቦርድ ተወካይ አቶ ግርማ አዲስ በበኩላቸው ስቲሊ አር ኤም አይ እና አስመን አረጋውያን የማገዝ፣ ተንከባካቢ የሌላቸው ህጻናትን ከጎናቸው በመሆን አሌንታነት በማረጋገጥ፣ የምገባ ማዕከላትን በማቋቋም፣ በተለያየ ምክንያት እና እንደ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ አይነት አጣዳፊ ሁኔታ ሲያጋጥም ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ በማድረግ የወገን ደራሽ የመሆን ሚናቸውን ከምስረታቸው ጀምሮ እንደተገበሩ ገልፀዋል፡፡
ይህንኑ ተግባር ወደ ፊትም በተቀናጀ መልኩ እንደ ግሩፕ ለማከናወን ፋውንዴሽን መቋቋሙን ነው አክለው የገለጹት፡፡
16 hours ago
🎉🎉 30ኛ ዙር የትዊተር #ንቁ_ተሳታፊ አሸናፊዎች!!
✅ አሁንም የኢትዮ ቴሌኮምን https://x.com/ethiotelecom እና ቴሌብር የትዊተር ገጾች https://x.com/telebirr በመከተል መልእክቶችን ላይክ፣ ኮመንት፣ ሪፖስት እንዲሁም ሼር በማድረግ 10 ጂቢ ወርኃዊ የኢንተርኔት ጥቅል በዕጣ ያሸንፉ!
📥 አሸናፊዎች በትዊተር ገጾቻችን በውስጥ መልእክት (DM) የስልክ ቁጥራችሁን ላኩልን!
#ethiotelecom #telebirr #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
✅ አሁንም የኢትዮ ቴሌኮምን https://x.com/ethiotelecom እና ቴሌብር የትዊተር ገጾች https://x.com/telebirr በመከተል መልእክቶችን ላይክ፣ ኮመንት፣ ሪፖስት እንዲሁም ሼር በማድረግ 10 ጂቢ ወርኃዊ የኢንተርኔት ጥቅል በዕጣ ያሸንፉ!
📥 አሸናፊዎች በትዊተር ገጾቻችን በውስጥ መልእክት (DM) የስልክ ቁጥራችሁን ላኩልን!
#ethiotelecom #telebirr #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
19 hours ago
ከ4መቶ በላይ ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ማድረጉን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ተናገረ
ባለስልጣኑ የፕላስቲክ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡና ምርቱም እንዲቆም የሚያደርገዉ ህግ ወደ ስራ መግባቱን ተከትሎ ቁጥጥር እያደረጉ እገኛለሁ ብሏል።
በዚህም መሠረት በተጠናቀቀው በጀት አመት ከረጢት ስራ ላይ እንዳይውል ለማድረግ በተሰራው ስራ 4መቶ 88 ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ተብሏል።
አሁንም በርካታ የምርት ክምችቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኝ የገልፁት የባለስልጣኑ ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ ባለስልጣኑ በደረሰበት ልክ ክትትል እያደረገ ቢሆንም ህብረተሰቡ ስለፌስታል ያለውን ግንዛቤ መቀየር ካልተቀየሩ ምርቱን በቀላሉ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አምራች ተቋማቱ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ወደ ሌሎች ተኪ ምርቶች እንዲሰማሩ በማድረግ ያላሻሻሉት ላይ እስከማሸግ የደረሰ እርምጃ መውሰድ እንደተቻለም አያይዙዉ ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ከብክለት ጋር በተያያዘ ከ17ሺ 1መቶ በላይ ተቋማት ላይ ባደረገው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ተነግሯል።
ህግ ተላልፈው የተገኙ 3ሺ 3መቶ 18 ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷልም ተብሏል።
ቁምነገር አየለ
ባለስልጣኑ የፕላስቲክ ምርቶች ለገበያ እንዳይቀርቡና ምርቱም እንዲቆም የሚያደርገዉ ህግ ወደ ስራ መግባቱን ተከትሎ ቁጥጥር እያደረጉ እገኛለሁ ብሏል።
በዚህም መሠረት በተጠናቀቀው በጀት አመት ከረጢት ስራ ላይ እንዳይውል ለማድረግ በተሰራው ስራ 4መቶ 88 ፌስታል የሚያመርቱ ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ተደርጓል ተብሏል።
አሁንም በርካታ የምርት ክምችቶች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኝ የገልፁት የባለስልጣኑ ዋና አማካሪ አቶ አዱኛ ወንድሙ ባለስልጣኑ በደረሰበት ልክ ክትትል እያደረገ ቢሆንም ህብረተሰቡ ስለፌስታል ያለውን ግንዛቤ መቀየር ካልተቀየሩ ምርቱን በቀላሉ ማስቆም እንዳልተቻለ ተናግረዋል።
አምራች ተቋማቱ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ወደ ሌሎች ተኪ ምርቶች እንዲሰማሩ በማድረግ ያላሻሻሉት ላይ እስከማሸግ የደረሰ እርምጃ መውሰድ እንደተቻለም አያይዙዉ ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ከብክለት ጋር በተያያዘ ከ17ሺ 1መቶ በላይ ተቋማት ላይ ባደረገው ክትትልና ቁጥጥር መደረጉ ተነግሯል።
ህግ ተላልፈው የተገኙ 3ሺ 3መቶ 18 ተቋማት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዷልም ተብሏል።
ቁምነገር አየለ
Sponsored by
Surafel
20 hours ago
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን🙏
ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች” በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ከኖረች በኋላ ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ዐርፈለች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና፣ ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው ብለው ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡ መላእክት የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ቅዱስ ይህን በረከት አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ይዘው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት።
ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበርና ሲቀብሯት አልተገኘም። እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ከሙታን ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው እርሱ የቀረበት መስሎት “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው። እመቤታችን ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነግራ ግን ቶማስን አፅናናችው፡፡ ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች። ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ አላቸው፡፡ እነርሱም አግኝተን ቀበናት አሉት፡፡
እርሱም “ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ ይህ እንዴት ይሆናል?” ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ “ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ” ብሎት ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ” ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸውና ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡ በዓመቱም ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ። ነሐሴ 16 ጌታችን እመቤታችን አምጥቶ ሐዋርያትን ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ገዳውያን ይህን የጾም ወቅት ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመጸለይ ያሳልፉታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች” በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ከኖረች በኋላ ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ዐርፈለች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና፣ ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው ብለው ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡ መላእክት የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ቅዱስ ይህን በረከት አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ይዘው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት።
ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበርና ሲቀብሯት አልተገኘም። እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ከሙታን ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው እርሱ የቀረበት መስሎት “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው። እመቤታችን ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነግራ ግን ቶማስን አፅናናችው፡፡ ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች። ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ አላቸው፡፡ እነርሱም አግኝተን ቀበናት አሉት፡፡
እርሱም “ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ ይህ እንዴት ይሆናል?” ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ “ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ” ብሎት ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ” ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸውና ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡ በዓመቱም ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ። ነሐሴ 16 ጌታችን እመቤታችን አምጥቶ ሐዋርያትን ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ገዳውያን ይህን የጾም ወቅት ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመጸለይ ያሳልፉታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
20 hours ago
እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ፤አደረሰን🙏
ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች” በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ከኖረች በኋላ ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ዐርፈለች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና፣ ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው ብለው ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡ መላእክት የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ቅዱስ ይህን በረከት አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ይዘው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት።
ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበርና ሲቀብሯት አልተገኘም። እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ከሙታን ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው እርሱ የቀረበት መስሎት “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው። እመቤታችን ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነግራ ግን ቶማስን አፅናናችው፡፡ ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች። ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ አላቸው፡፡ እነርሱም አግኝተን ቀበናት አሉት፡፡
እርሱም “ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ ይህ እንዴት ይሆናል?” ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ “ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ” ብሎት ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ” ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸውና ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡ በዓመቱም ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ። ነሐሴ 16 ጌታችን እመቤታችን አምጥቶ ሐዋርያትን ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ገዳውያን ይህን የጾም ወቅት ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመጸለይ ያሳልፉታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ፍልሰታ የሚለው ቃል የተገኘው ፈለሰ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን በጥሬ ትርጉሙ መለየት፣ ማረግ፣ ወደላይ መውጣት የሚለውን ትርጉም ይይዛል። ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች” በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡ ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋዋ ከሞትና መቃብር መለየትና ማረግን ያመለክታል። ይህ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከተወሰኑት ሰባቱ አጸዋማት ለዓመቱ የመጨረሻው ጾም ነው። እመቤታችን በዚህ ዓለም ለ64 ዓመታት ከኖረች በኋላ ጥር 21 ቀን 49 ዓመተ ምሕረት ዐርፈለች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና፣ ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ኖረዋል፤ እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው ብለው ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡ መላእክት የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ በስምንተኛው ወር በነሐሴ ሐዋርያት ቅዱስ ይህን በረከት አይቶ እኛ ሳናይ ቀረን ብለው ከነሐሴ 1 እስከ 14 ሁለት ሱባዔ ይዘው ከጌታችን ተቀብለው በጸሎትና በምህላ ቀበሯት።
ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወጥቶ ነበርና ሲቀብሯት አልተገኘም። እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ከሙታን ተነሥታ ስታርግ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ አገኛት። በዚህን ጊዜ ትንሣኤዋን ሌሎች ሐዋርያት አይተው እርሱ የቀረበት መስሎት “ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንችን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ” ብሎ ራሱን ከደመና ላይ ሊወረውር ቃጣው። እመቤታችን ከእርሱ በስተቀር ትንሣኤዋን ያየ አለመኖሩን ነግራ ግን ቶማስን አፅናናችው፡፡ ለምስክርነት እንዲሆንም በቀብሯ ጊዜ የነበረውን ሰበኗን ሰጥታው አረገች። ቅዱስ ቶማስም ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ አላቸው፡፡ እነርሱም አግኝተን ቀበናት አሉት፡፡
እርሱም “ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ ይህ እንዴት ይሆናል?” ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ “ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ” ብሎት ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ “አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ” ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸውና ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡ በዓመቱም ቶማስ ትንሣኤሽን አይቷልና እኛም በረከት አይቅርብን ብለው ከነሐሴ አንድ ጀምረው ሱባዔ ገቡ። ነሐሴ 16 ጌታችን እመቤታችን አምጥቶ ሐዋርያትን ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ገዳውያን ይህን የጾም ወቅት ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በመጸለይ ያሳልፉታል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
20 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በደቡብ ሱዳን መዲና ጁባ በሚገኝ አንድ ጠባብ የወርቅ ገበያ ውስጥ፣ በኮንትሮባንድ ከሱዳን የሚገባው ወርቅ ህጋዊ ሽፋን ተሰጥቶት ወደ ዱባይ እንዴት እንደሚላክ ለግል ደህንነታቸው ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ (F.A. በሚል ምህጻረ ቃል የተገለጹ) አንድ ነጋዴ አጋልጠዋል።
ነጋዴው ለሱዳን ትሪቢዩን እንደገለጹት፣ በየብስ ድንበር በኩል የሚደረገው የሱዳን ወርቅ ዝውውር አሁንም አልቆመም። ከዳርፉር እና ከደቡብ ኮርዶፋን ማዕድን ማውጫዎች የሚነሱ የጭነት መኪናዎች እና ሞተር ብስክሌቶች ቁጥጥር በማይደረግባቸው የድንበር መስመሮች በኩል ወርቁን ያለማቋረጥ ያጓጉዛሉ።
ወርቁ ወደ ጁባ የሚገባው ባልተጣራ እና ጥሬ በሆነ መልኩ መሆኑን ያስረዱት ነጋዴው፤ ደላሎች እና የሀገር ውስጥ ነጋዴዎች ማዕድኑን በሱዳን ማዕከላዊ ባንክ ከሚሰጠው መደበኛ የምንዛሬ ተመን እጅግ በተሻለ ዋጋ በአሜሪካ ዶላር በጥሬ ገንዘብ እንደሚገዙት አብራርተዋል።
ይህንን ወርቅ ህጋዊ ለማድረግ፣ ነጋዴዎቹ ማዕድኑን ዳግም በማቅለጥ እና በመቀላቀል አዲስ ቅርጽ ይሰጡታል። በመቀጠልም ወርቁ በደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያ ወይም ምዕራብ ባህር ኤል ጋዛል ግዛቶች እንደተመረተ የሚያስመስል የሀሰት ሰነድ ይዘጋጅለታል። ይህ የሀሰት ሰነድ ወርቁ ያለምንም ህጋዊ እንቅፋት በጁባ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል በአየር ጭነት ወደ አረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) እና ዓለም አቀፍ ማጣሪያዎች እንዲላክ ያስችለዋል።
ይህ የምስክርነት ቃል በሱዳን የወርቅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የታየውን መዋቅራዊ ለውጥ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይህንን የተወሳሰበ ሂደት "የእሴት ሰንሰለት ዳግም ምህንድስና እና የመነሻ ሀገር ማጭበርበር" ሲሉ ይጠሩታል። በዚህም ህገ-ወጥ አውታረ መረቦች ጎረቤት ሀገራትን (በተለይም ደቡብ ሱዳንን) እንደ መሸጋገሪያ በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማዕቀቦችን በማለፍ የማዕድኑን ህጋዊ ማንነት ይቀይራሉ።
በ2017 የጀበል አሜር የወርቅ ማዕድን ማውጫን በኃይል የተቆጣጠሩት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) አዛዥ ሞሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ)፣ ከማዕድኑ የሚገኘውን ትርፍ ከRSF ጋር ግንኙነት ላላቸው 50 ገደማ ኩባንያዎች እንዲገባ ማድረጋቸው ይታወሳል። በ2019 ሄሜቲ የሱዳንን ኢኮኖሚ ለማረጋጋት በሚል ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ድጋፍ አቅርበው ነበር።
መረጃውን ያጋለጡት ነጋዴ አክለውም፣ ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ ከጁባ ወደ አረብ ኤምሬትስ በተደረጉ ሁለት በረራዎች 115 ኪሎ ግራም የሚመዝን የሱዳን የኮንትሮባንድ ወርቅ መጓጓዙን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ሱዳን ትሪቢዩን ይህንን የተወሰነ መረጃ በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ እንዳልቻለ በዘገባው አስፍሯል።
ነጋዴው ለሱዳን ትሪቢዩን እንደገለጹት፣ በየብስ ድንበር በኩል የሚደረገው የሱዳን ወርቅ ዝውውር አሁንም አልቆመም። ከዳርፉር እና ከደቡብ ኮርዶፋን ማዕድን ማውጫዎች የሚነሱ የጭነት መኪናዎች እና ሞተር ብስክሌቶች ቁጥጥር በማይደረግባቸው የድንበር መስመሮች በኩል ወርቁን ያለማቋረጥ ያጓጉዛሉ።
ወርቁ ወደ ጁባ የሚገባው ባልተጣራ እና ጥሬ በሆነ መልኩ መሆኑን ያስረዱት ነጋዴው፤ ደላሎች እና የሀገር ውስጥ ነጋዴዎች ማዕድኑን በሱዳን ማዕከላዊ ባንክ ከሚሰጠው መደበኛ የምንዛሬ ተመን እጅግ በተሻለ ዋጋ በአሜሪካ ዶላር በጥሬ ገንዘብ እንደሚገዙት አብራርተዋል።
ይህንን ወርቅ ህጋዊ ለማድረግ፣ ነጋዴዎቹ ማዕድኑን ዳግም በማቅለጥ እና በመቀላቀል አዲስ ቅርጽ ይሰጡታል። በመቀጠልም ወርቁ በደቡብ ሱዳን ኢኳቶሪያ ወይም ምዕራብ ባህር ኤል ጋዛል ግዛቶች እንደተመረተ የሚያስመስል የሀሰት ሰነድ ይዘጋጅለታል። ይህ የሀሰት ሰነድ ወርቁ ያለምንም ህጋዊ እንቅፋት በጁባ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል በአየር ጭነት ወደ አረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) እና ዓለም አቀፍ ማጣሪያዎች እንዲላክ ያስችለዋል።
ይህ የምስክርነት ቃል በሱዳን የወርቅ አቅርቦት ሰንሰለት ላይ የታየውን መዋቅራዊ ለውጥ ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይህንን የተወሳሰበ ሂደት "የእሴት ሰንሰለት ዳግም ምህንድስና እና የመነሻ ሀገር ማጭበርበር" ሲሉ ይጠሩታል። በዚህም ህገ-ወጥ አውታረ መረቦች ጎረቤት ሀገራትን (በተለይም ደቡብ ሱዳንን) እንደ መሸጋገሪያ በመጠቀም ዓለም አቀፍ ማዕቀቦችን በማለፍ የማዕድኑን ህጋዊ ማንነት ይቀይራሉ።
በ2017 የጀበል አሜር የወርቅ ማዕድን ማውጫን በኃይል የተቆጣጠሩት የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) አዛዥ ሞሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ)፣ ከማዕድኑ የሚገኘውን ትርፍ ከRSF ጋር ግንኙነት ላላቸው 50 ገደማ ኩባንያዎች እንዲገባ ማድረጋቸው ይታወሳል። በ2019 ሄሜቲ የሱዳንን ኢኮኖሚ ለማረጋጋት በሚል ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ድጋፍ አቅርበው ነበር።
መረጃውን ያጋለጡት ነጋዴ አክለውም፣ ባለፈው መጋቢት ወር ብቻ ከጁባ ወደ አረብ ኤምሬትስ በተደረጉ ሁለት በረራዎች 115 ኪሎ ግራም የሚመዝን የሱዳን የኮንትሮባንድ ወርቅ መጓጓዙን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ሱዳን ትሪቢዩን ይህንን የተወሰነ መረጃ በገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ እንዳልቻለ በዘገባው አስፍሯል።
20 hours ago
መጥፎውን አዙሪት እንስበር፡ በሌብነት ላይ የሚደረግ የጋራ ትግል
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ሀገር የምታድገው፣ የምትበለፅገው እና የዜጎቿን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የምትችለው በንፁህ እጆች እና በቅን ልቦች ስትመራ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና እና የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ እንደ ትልቅ ካንሰር እና ማነቆ የተጋረጠው አሳሳቢ ፈተና ሌብነት እና የሙስና ተግባር ነው። ይህ እኩይ ድርጊት በግለሰቦች፣ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች እና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ እንደ ምስጥ በመሰግሰግ የሀገርን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመመዝበር ላይ ይገኛል።
ሙስና እና ሌብነት የሀገርን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ከማድማት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ እና የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲስፋፋ ያደርጋል። በመሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት ፈጥሮ የዋጋ ንረት እንዲባባስ በማድረግ ኅብረተሰቡን ለከፋ ችግር እያጋለጠው ይገኛል። ይህን የጥፋት ተግባር ከሥረ መሠረቱ ነቅሎ ማውጣት አሁን ላይ የሀገር ህልውና፣ ሰላም እና ደህንነት ጉዳይ ሆኗል።
ይህንኑ አሳሳቢ ሀገራዊ ፈተና አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የችግሩን ሥር-ሰደድነት ሲያብራሩ፤ "የተንዛዛ አሰራር ጉቦ ሰጭ ይፈጥራል። ጉቦ ሰጭ ጉቦ ተቀባይ ይፈጥራል። ጉቦ ተቀባይ የተንዛዛ አሰራር ይፈጥራል። ይህ መጥፎ አዙሪት ነው፤ በቀላሉ አንወጣውም። ጉቦኞች እና ሌቦች ባሉበት ሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት ማምጣት ቀርቶ አብሮ መኖርም አስቸጋሪ ይሆናል፤ ካልተረባረብን ያጠፋናል" በማለት አስገንዝበዋል።
ይህን በሽታ ለማከም መንግሥት አሁን ላይ በማያዳግም ሁኔታ ሰፊ የማጽዳት ዘመቻ እና የሕግ ማስከበር እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ በነበሩ አካላት፣ እንዲሁም በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር መዋቅር ውስጥ በተሰገሰጉ ሌቦች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው።
በተለይም በነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ፣ በማዕድን ዘርፍ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ በፋይናንስ ተቋማት እና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም ከአፈር ማዳበሪያ ግዢ እና ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ላይ ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የሕዝብን ሀብት በመመዝበር በተገኙ አመራሮች፣ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና የውጭ ዜጎች ጭምር ላይ የማያዳግም የሕግ ተጠያቂነት እየሰፈነ መሆኑ፤ ሕገ-ወጥ የንግድ ድርጅቶች እና መጋዘኖች እየታሸጉ፣ የተጭበረበሩ የባንክ ሒሳቦች እየታገዱ መሆኑ እንዲሁም አሻጥሩን ከመሰረቱ ለማጋለጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ይበል የሚያሰኝ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ተግባር ነው።
ይሁን እንጂ ሌብነትን የማጥፋቱ እና ግልጽነት ያለው ዘመናዊ አሠራርን የመዘርጋቱ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም። መንግሥት የጀመረው ይህ ጠንካራ የሕግ ማስከበር እርምጃ ግቡን እንዲመታ እና ሀገርን ከሕገ-ወጥነት ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ እና የማይተካ ሚና አለው።
ስለሆነም እያንዳንዱ ዜጋ ሕጋዊ መብቱን ለማስከበርም ሆነ አገልግሎት ለማግኘት ጉቦ ከመስጠት መቆጠብ፣ ሌቦችን እና አሻጥር ፈጻሚዎችን ያለ አንዳች ይሉኝታ እና ፍርሃት ማጋለጥ እንዲሁም ከሕገ-ወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በጽናት ሊቆም ይገባል።
በተጨማሪም በጅምላ ከመወነጃጀል ወጥተን፣ ሌባውን ለይተን ሌባ በማለት፣ በተቃራኒው በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግለውን ሠራተኛ ደግሞ በማክበርና በማበረታታት ሀገራዊ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል።
ካልተረባረብን አብሮ መኖርን ጭምር አደጋ ላይ የሚጥለውን ይህን የሙስና እና የሌብነት ደዌ፣ በጋራ ትግላችን፣ በቁርጠኝነታችን እና በማይናወጥ ጽናታችን ማሸነፍ ግድ ይለናል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ሀገር የምታድገው፣ የምትበለፅገው እና የዜጎቿን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የምትችለው በንፁህ እጆች እና በቅን ልቦች ስትመራ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና እና የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ እንደ ትልቅ ካንሰር እና ማነቆ የተጋረጠው አሳሳቢ ፈተና ሌብነት እና የሙስና ተግባር ነው። ይህ እኩይ ድርጊት በግለሰቦች፣ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች እና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ እንደ ምስጥ በመሰግሰግ የሀገርን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመመዝበር ላይ ይገኛል።
ሙስና እና ሌብነት የሀገርን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ከማድማት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ እና የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲስፋፋ ያደርጋል። በመሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት ፈጥሮ የዋጋ ንረት እንዲባባስ በማድረግ ኅብረተሰቡን ለከፋ ችግር እያጋለጠው ይገኛል። ይህን የጥፋት ተግባር ከሥረ መሠረቱ ነቅሎ ማውጣት አሁን ላይ የሀገር ህልውና፣ ሰላም እና ደህንነት ጉዳይ ሆኗል።
ይህንኑ አሳሳቢ ሀገራዊ ፈተና አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የችግሩን ሥር-ሰደድነት ሲያብራሩ፤ "የተንዛዛ አሰራር ጉቦ ሰጭ ይፈጥራል። ጉቦ ሰጭ ጉቦ ተቀባይ ይፈጥራል። ጉቦ ተቀባይ የተንዛዛ አሰራር ይፈጥራል። ይህ መጥፎ አዙሪት ነው፤ በቀላሉ አንወጣውም። ጉቦኞች እና ሌቦች ባሉበት ሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት ማምጣት ቀርቶ አብሮ መኖርም አስቸጋሪ ይሆናል፤ ካልተረባረብን ያጠፋናል" በማለት አስገንዝበዋል።
ይህን በሽታ ለማከም መንግሥት አሁን ላይ በማያዳግም ሁኔታ ሰፊ የማጽዳት ዘመቻ እና የሕግ ማስከበር እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ በነበሩ አካላት፣ እንዲሁም በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር መዋቅር ውስጥ በተሰገሰጉ ሌቦች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው።
በተለይም በነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ፣ በማዕድን ዘርፍ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ በፋይናንስ ተቋማት እና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም ከአፈር ማዳበሪያ ግዢ እና ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ላይ ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የሕዝብን ሀብት በመመዝበር በተገኙ አመራሮች፣ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና የውጭ ዜጎች ጭምር ላይ የማያዳግም የሕግ ተጠያቂነት እየሰፈነ መሆኑ፤ ሕገ-ወጥ የንግድ ድርጅቶች እና መጋዘኖች እየታሸጉ፣ የተጭበረበሩ የባንክ ሒሳቦች እየታገዱ መሆኑ እንዲሁም አሻጥሩን ከመሰረቱ ለማጋለጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ይበል የሚያሰኝ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ተግባር ነው።
ይሁን እንጂ ሌብነትን የማጥፋቱ እና ግልጽነት ያለው ዘመናዊ አሠራርን የመዘርጋቱ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም። መንግሥት የጀመረው ይህ ጠንካራ የሕግ ማስከበር እርምጃ ግቡን እንዲመታ እና ሀገርን ከሕገ-ወጥነት ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ እና የማይተካ ሚና አለው።
ስለሆነም እያንዳንዱ ዜጋ ሕጋዊ መብቱን ለማስከበርም ሆነ አገልግሎት ለማግኘት ጉቦ ከመስጠት መቆጠብ፣ ሌቦችን እና አሻጥር ፈጻሚዎችን ያለ አንዳች ይሉኝታ እና ፍርሃት ማጋለጥ እንዲሁም ከሕገ-ወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በጽናት ሊቆም ይገባል።
በተጨማሪም በጅምላ ከመወነጃጀል ወጥተን፣ ሌባውን ለይተን ሌባ በማለት፣ በተቃራኒው በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግለውን ሠራተኛ ደግሞ በማክበርና በማበረታታት ሀገራዊ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል።
ካልተረባረብን አብሮ መኖርን ጭምር አደጋ ላይ የሚጥለውን ይህን የሙስና እና የሌብነት ደዌ፣ በጋራ ትግላችን፣ በቁርጠኝነታችን እና በማይናወጥ ጽናታችን ማሸነፍ ግድ ይለናል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
21 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቺካጎ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር የሆኑት ሮበርት ፔፕ ለአልጀዚራ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር በገጠመችው ጦርነት "በታሪክ ውስጥ እጅግ አስከፊ በሆነ የመባባስ አዙሪት (Escalation trap)" ውስጥ መውደቋን አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ በኢራን ላይ እየፈጸመችው ያለው የአየር እና የባህር ላይ ጥቃት በታክቲክ ደረጃ ስኬቶችን ማምጣት ቢችልም፣ "ምንም ዓይነት ስትራቴጂካዊ ዓላማዎችን ማሳካት ግን አልቻለም" ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ይልቅ ኢራን አሁን ይበልጥ ጠንክራ መውጣቷን አብራርተዋል።
እንደ ሮበርት ፔፕ ትንታኔ፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሁኑ ወቅት ከባድ አጣብቂኝ ውስጥ ይገኛሉ። የኢራንን እያደገ የመጣ ተጽዕኖ አምኖ መቀበል አሊያም ደግሞ ጦርነቱን ይበልጥ ማባባስ የሚሉ ሁለት ምርጫዎች ፊት ለፊት የቆሙ ሲሆን፣ "ከዚህ ውጪ ሶስተኛ አማራጭ የለም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአየር እና የባህር ኃይል ጥቃቶች ያላቸውን ውሱንነት አሁን ላይ በሚገባ እየተረዱት መምጣታቸውን የጠቆሙት ፕሮፌሰሩ፣ በመጪው የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ዋዜማ ፖለቲካዊ ትርጉም ያለው ተምሳሌታዊ ድል ለማስመዝገብ ሲሉ ወታደሮቻቸውን ወደ ምድር ጦር ዘመቻሊያስገቡ እንደሚችሉ ስጋታቸውን አስጠንቅቀዋል።
አሜሪካ በኢራን ላይ እየፈጸመችው ያለው የአየር እና የባህር ላይ ጥቃት በታክቲክ ደረጃ ስኬቶችን ማምጣት ቢችልም፣ "ምንም ዓይነት ስትራቴጂካዊ ዓላማዎችን ማሳካት ግን አልቻለም" ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ ይልቅ ኢራን አሁን ይበልጥ ጠንክራ መውጣቷን አብራርተዋል።
እንደ ሮበርት ፔፕ ትንታኔ፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሁኑ ወቅት ከባድ አጣብቂኝ ውስጥ ይገኛሉ። የኢራንን እያደገ የመጣ ተጽዕኖ አምኖ መቀበል አሊያም ደግሞ ጦርነቱን ይበልጥ ማባባስ የሚሉ ሁለት ምርጫዎች ፊት ለፊት የቆሙ ሲሆን፣ "ከዚህ ውጪ ሶስተኛ አማራጭ የለም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአየር እና የባህር ኃይል ጥቃቶች ያላቸውን ውሱንነት አሁን ላይ በሚገባ እየተረዱት መምጣታቸውን የጠቆሙት ፕሮፌሰሩ፣ በመጪው የአጋማሽ ዘመን ምርጫ ዋዜማ ፖለቲካዊ ትርጉም ያለው ተምሳሌታዊ ድል ለማስመዝገብ ሲሉ ወታደሮቻቸውን ወደ ምድር ጦር ዘመቻሊያስገቡ እንደሚችሉ ስጋታቸውን አስጠንቅቀዋል።
Sponsored by
Surafel
22 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዛሬ 15 ዓመት ገደማ በፈረንጆቹ ግንቦት 2011፣ በአሜሪካ ዋሽንግተን ግዛት የምትገኝ አንዲት ትንሽ ከተማ በአሰቃቂ ድርጊት ተናወጠች። ከትውልድ አገሯ ኢትዮጵያ የተሻለ ሕይወትና ፍቅር ፍለጋ የመጣችው የ13 ዓመቷ ታዳጊ ሃና አለሙ (Hana Williams)፣ ማንም ሰብዓዊ ፍጡር ሊሸከመው የማይችለውን ስቃይና ፍጹም ጭካኔ በአሳዳጊ ወላጆቿ እጅ ካስተናገደች በኋላ፣ በአንድ ቀዝቃዛ ምሽት በጭቃ ላይ ወድቃ ሕይወቷ አለፈ።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
ሃና ከዚህ ዓለም ብትለይም፣ የእሷን አሳዛኝ ታሪክ የሚሰማ ማንኛውም ሰው ልብ ዛሬም ድረስ በሐዘንና በቁጭት ይደማል። ዛሬም ድረስ ብዙዎችን ምሽት ላይ እንቅልፍ የሚነሳው ይህ ታሪክ፣ በቅርቡ በአዲስ አሁናዊ ዜና ወደ አደባባይ መጥቷል።
በዚህ ጉዳይ ላይ የወጣው የመጨረሻውና አሁናዊው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ያቺን ንጽሕት ሕፃን በረሃብና በብርድ አሰቃይተው የገደሏት ጨካኞቹ አሳዳጊ ወላጆቿ — ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ—ከተፈረደባቸው የረጅም ዓመታት እስራት ለማምለጥ የሙጥኝ ያሉበት የመጨረሻው የይግባኝ ተስፋቸው ሙሉ በሙሉ ተዘግቷል።
ፍርድ ቤቱ በቅርቡ በሰጠው ውሳኔ፣ ወንጀለኞቹ "በፍርድ ሂደቱ ላይ ስህተት ተፈጽሟል፣ በድጋሚ ይታይልን" በማለት ያቀረቡትን አቤቱታ ውድቅ አድርጎታል። የዋሽንግተን ግዛት ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ባወጣው ባለ ብዙ ገጽ ዝርዝር ውሳኔ፣ የተሰጣቸው የ37 እና የ28 ዓመታት የእስራት ፍርድ ፍጹም ፍትሐዊ መሆኑንና በአንዲት አቅመ-ቢስ ሕፃን ላይ የፈጸሙት ግፍ ይቅር የማይባል መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል። ይህም ማለት ሁለቱም ጨካኝ ወላጆች ዕድሜያቸውን በሙሉ በጠበቀ ጥበቃ ሥር ባሉ የሴቶችና የወንዶች ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አሳልፈው ይጨርሳሉ።
ምንም እንኳ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ወንጀለኞቹ ከእስር ቤት አምልጠው በነፃነት አየር እንዳይተነፍሱ ቢያደርግም፣ በጉዲፈቻ ስም ተሰርቆ የጠፋውን የሃናን የልጅነት ጊዜና የተቀጠፈውን ውድ ሕይወቷን መመለስ አይችልም። ዛሬም ድረስ በአሜሪካና በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ ትልቅ ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የሃና ታሪክ፣ የሕፃናትን መብት ለማስከበርና መሰል ግፎችን ለመከላከል የሚደረገውን ትግል በሐዘን ማስታወሻነት እየመራ ይገኛል።
ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ምድራዊ ፍቅር የተነፈገችው ሃና አለሙ፣ ዛሬ ካለችበት ዓለም ሆና ወንጀለኞቿ ከእስር ቤት የብረት ዘንጎች በስተጀርባ ሆነው ዋጋቸውን ሲከፍሉ እያየች ይሆን? ብዙዎች አሁንም የሚመኙት አንድ ነገር ብቻ ነው — ይህች ንጽሕት ነፍስ በምድር ላይ ያጣችውን ሰላምና እቅፍ በሰማይ አግኝታ ለዘላለም እንድታርፍ። ክሪሚናል ማተር የተሰኘው የሰብ አዊ መብት ተሟጋች ዛሬ ባወጣው ጽሑፍ "የ13 ዓመቷ የሃና ግሬስ-ሮዝ ዊሊያምስ ታሪክ እውነቱን ለመናገር ሌሊት እንቅልፍ የሚነሳኝ እና ዕረፍት የሚያሳጣኝ ታሪክ ነው። የተሻለ ሕይወት ታገኛለች በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ በጉዲፈቻ ወደ አሜሪካዋ ዋሽንግተን ግዛት ብትወሰድም፣ የገጠማት ግን ሊታሰብ የማይችል ዘግናኝ ጭካኔ ነበር። አሳዳጊ ወላጆቿ የሆኑት ካሪ እና ላሪ ዊሊያምስ ባደረሱባት በደል እና እንግልት፣ እ.ኤ.አ. በ2011 በከፍተኛ ቅዝቃዜ (Hypothermia) ምክንያት ለሞት እንድትዳረግ በማድረጋቸው ጥፋተኛ ተብለው ተፈርዶባቸዋል።
ሊጠብቋት እና ሊንከባከቧት ኃላፊነት በወሰዱ ሰዎች፣ እንዲህ ባለች ምስኪን ልጅ ላይ እንዴት ይህን ያህል ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ሊፈጸም እንደቻለ ለማሰብ እና ለመቀበል ይከብደኛል። በዚህች ምድር ላይ የተነፈገችውን ሰላም በመጨረሻው ዓለም እንዳገኘችው ተስፋ አደርጋለሁ።" ብሏል።
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የሀገሪቱን የትውልድ ዜግነት መብት ለመገደብ ያለመ አዲስ ነገር ግን ጠበብ ያለ ማዕቀፍ ያላቸውን ሁለት አስፈጻሚ ትዕዛዞች ሐሙስ ዕለት ፈርመዋል። ይህ አዲስ እርምጃ፣ ፕሬዝዳንቱ ቀደም ሲል ያወጡት ተመሳሳይ ትዕዛዝ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ውድቅ መደረጉን ተከትሎ፣ የአሜሪካን ህገ-መንግስት ድንጋጌ ዳግም ለመሞገት የተደረገ ሙከራ ነው።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
በትራምፕ የሪፐብሊካን አስተዳደር የጸረ-ስደተኞች ፖሊሲ ውስጥ የትውልድ ዜግነትን መገደብ ቀዳሚው አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል። በተለይም ነፍሰጡር የውጭ ዜጎች ልጆቻቸውን በአሜሪካ ምድር በመውለድ ዜግነት ለማግኘት የሚያደርጉትን ጉዞ ወይም ዋይት ሀውስ "የወሊድ ቱሪዝም" በማለት የሚጠራውን አሰራር ዋነኛ ኢላማው አድርጓል።
ባለፈው ሰኔ 30 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የትራምፕን የመጀመሪያ ትዕዛዝ "ከህገ-መንግስቱ ጋር የሚጻረር ነው" በማለት ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፣ ፕሬዝዳንቱ ኮንግረሱ ህግ እንዲያወጣ ጥሪ አቅርበው ነበር። ሆኖም ሐሙስ ዕለት ፖሊሲን የሚያወጡ ነገር ግን የህግ አስገዳጅነት የሌላቸውን አስፈጻሚ ትዕዛዞችን መፈረምን መርጠዋል። የትራምፕ አስተዳደር እንደሚለው፣ እነዚህ አዳዲስ መመሪያዎች ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካስቀመጣቸው ገደቦች ውጪ የሆኑ ናቸው። ይህም የወሊድ ቱሪዝምን ጨምሮ የትውልድ ዜግነት መብት የማይገባቸውን ሰዎች ምድብ ለማስፋት ያስችለዋል ብሏል። በትራምፕ ትዕዛዝ መሰረት፣ እነዚህ ምድቦች "ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካወጀው የትውልድ ዜግነት ደንብ ስር አይወድቁም።"
በዋይት ሀውስ የፕሬዝዳንቱ ረዳት የሆኑት ስቴፈን ሚለር በትዕዛዙ የፊርማ ስነ-ስርዓት ላይ፣ "ይህ ትዕዛዝ ከተፈረመበት ጊዜ ጀምሮ የወሊድ ቱሪዝም ልምምድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። ይህ ማለት ማንም ሰው ለዚህ አታላይ ዓላማ ቪዛ ማግኘት አይፈቀድለትም" ሲሉ ተናግረዋል።
አዳዲሶቹ ትዕዛዞች ከወሊድ ቱሪዝም ባሻገር፣ በአሜሪካ ለሚገኙ የውጭ መንግስታት ሰራተኞች እና እንደ 'ጠላት' (Alien Enemies) ለተፈረጁ የውጭ ዜጎች የሚወለዱ ልጆችን የዜግነት መብት ይገድባሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኮንግረሱ አዲስ ህግ ካጸደቀ፣ በአሜሪካ ግዛቶች (Territories) ውስጥ የሚወለዱ ሰዎች አውቶማቲክ ዜግነት እንዳያገኙ ሊያደርግ እንደሚችል ተጠቁሟል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የ6 ለ 3 የድምጽ ውሳኔ አጥብቀው ተችተዋል። "በትውልድ ዜግነት ላይ ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ አጋጥሞናል... በጣም ተቀራራቢ ድምጽ ቢሆንም፣ እጅግ አሳዛኝ ውሳኔ ነው" ብለዋል። አክለውም፣ "ሰዎች ዜግነትን ማግኛ መንገድ አድርገው ንግድ እየገነቡበት ነው። አሰራሩ እንደዚህ መሆን አልነበረበትም፤ ይህ አሳፋሪ ነው። ዜግነትን በገንዘብ እየገዙ ነው፣ እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን አንፈቅድም" ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ህገ-መንግስት 14ኛው ማሻሻያ ከውጭ ዲፕሎማቶች ወይም ወራሪ የጠላት ኃይል አባላት ልጆች ውጪ፣ በአሜሪካ ምድር ለሚወለዱ ህጻናት በሙሉ የዜግነት መብትን እንደሚያረጋግጥ በህግ ሲተረጎም ቆይቷል። ትራምፕ ግን ይህ ህግ የወጣው ከእርስ በርስ ጦርነቱ በኋላ ለባሮች ልጆች ዜግነት ለመስጠት መሆኑን በመጥቀስ፣ የአሁኑ አሰራር የህጉን መንፈስ የሳተ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ዋና ዳኛ ጆን ሮበርትስ በውሳኔያቸው ላይ፣ የ14ኛው ማሻሻያ አርቃቂዎች ይህንን ቃል ኪዳን በሀገሪቱ ውስጥ ለተወለደ እያንዳንዱ ነጻ ሰው እንዳሰፉት አስታውሰው፣ "ዜግነት በዚያን ጊዜም ሆነ አሁን መብቶችን የማግኘት እና በፖለቲካዊ ማህበረሰባችን ውስጥ በነጻነት የመሳተፍ መብት ነው። ይህንን ቃል ኪዳን ዛሬም እንጠብቃለን" በማለት የህገ-መንግስቱን ሰፊ ትርጉም አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በ2020 የትራምፕ የመጀመሪያ የስልጣን ዘመን አዲስ የተወለደ ልጅ የአሜሪካ ዜግነት እንዲያገኝ በሚል ዓላማ የቱሪስት እና የንግድ ቪዛዎችን መጠቀምን የሚከለክል የፌዴራል ደንብ ወጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የወሊድ ቱሪዝምን ሙሉ በሙሉ የሚከለክል ግልጽ ህግ በአሜሪካ የለም። ይህን መሰል ማጭበርበር ላይ የሚሳተፉ ሰዎች በህግ ሊጠየቁ ቢችሉም፣ የትራምፕ አዳዲስ አስፈጻሚ ትዕዛዞች በፍርድ ቤቶች በኩል ጠንካራ የህግ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው በሰፊው ይጠበቃል።
1 day ago
ምክክር ለዘላቂ ሠላም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከጥንታዊ ነጻ ሀገረ መንግሥታት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በበርካታ ባህሎች፣ ቋንቋዎችና እሴቶች የተዋቀረች ኅብረብሔራዊት ሀገር ናት፡፡
ከ130 ሚሊየን በላይ ሕዝብ መኖሪያ የሆነችው ሀገራችን ህልውናዋን አጽንታ ዘመናትን መሻገር የቻለችው በልጆቿ የተባበረ ክንድ ስለመሆኑ ታሪክ ህያው ምስክር ነው።
በእነዚያ ጊዜያት ውስጥ ሰላሟንና ልማቷን ሲፈታተኑ የዘለቁ ቅራኔዎችን በሰላማዊ ውይይት በመፍታት ነገዋን የተሻለ ለማድረግ በሀገራዊ ምክክር ሂደት ላይ ትገኛለች፡፡
ዜጎቿ ዘላቂ ሰላምን የሚያረጋግጥ የጋራ መግባባት ላይ የሚያደርስ መፍትሄ እንዲያበጁ በገለልተኛ የምክክር ኮሚሽን የሚመራ አሳታፊና አካታች ሀገራዊ መድረክ አበጅታለች፡፡
ይህ አሳታፊነት ምክከሩ በሀገሪቱ ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታዩ እጅግ ሰፊና ለውጥ አምጪ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚያመላክት ነው፡፡
ለብዙ ዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ አለመግባባቶች ዛሬም ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ለሚቀሰቀሱ ግጭቶችና የሰላም እጦት በምክንያትነት ሲቀርቡ ይስተዋላል፡፡
ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ የውይይት እሴቶችን ማዕከል በማድረግ እየተካሄደ የሚገኘው ሀገራዊ ምክክር እነዚህን የቆዩ ቁርሾዎች በዘላቂነት ለመፍታት ያስችላል፡፡
የጋራ ሀገራዊ ራዕይ እውን የሚሆንበት ይህ መድረክ ከጊዜያዊ ፖለቲካዊ ጥቅም በላይ የሀገሪቱን የዘላቂ ሰላም ጉዞ የሚያሳልጥ ታሪካዊ እድል ነው፡፡
የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድምፅ እኩል የሚሰማበት ይህ ሀገራዊ ምክክር የአሸናፊና ተሸናፊ ትርክትን በጋራ መግባባት ላይ በተመሠረተ ባህል የሚተካ ወሳኝ መድረክ ነው።
አንዲት ሀገር ለትናንት ቅራኔዎች ሕዝብን ባሳተፈ መንገድ እውነተኛ መፍትሄ ሳትሰጥ ሰላማዊ ነገን መገንባት አትችልም።
በዚህ መንፈስ በእኩልነት ላይ በተመሰረተ፣ ግልጽ፣ ነጻ እና አሳታፊ ሂደት እየተካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር፥ ሀገሪቱን ወደ ብልጽግና የሚያሸጋግር ድልድይ እንዲሁም ከውርስ ህመሟ የሚፈውስ ፍቱን መድሃኒት ነው፡፡
ግጭትና የሕዝቦች መለያየት የሀገርን ሀብት የሚያወድሙና ልማትን የሚያደናቅፉ በመሆናቸው፤ የሀገርን ጥቅም ባስቀደመ የጋራ መግባባት የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታን በመፍጠር ብሔራዊ ምክክሩ ለጠንካራ ኢኮኖሚ ዕድገት መሠረት ይጥላል።
የዜጎችን የጋራ መግባባት ጽኑ መሰረት አድርጋ የምትገነባው ሰላማዊት ኢትዮጵያ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና ሌሎች የመሠረተ ልማት ዘርፎች ያላትን አቅም ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የዜጎቿን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች፡፡
ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል እንዲሁም የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ እንደመሆኗ፤ አለመግባባትን በውይይት ለመፍታት የጀመረችው ጉዞ አፍሪካውያን ችግሮችን በራሳቸው ለመፍታት ለሚያደርጉት ጥረት መልካም አርአያ ነው።
የተዋሃደችና ደህንነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን በማረጋጋት የቀጣናውን የኢኮኖሚ ትስስር፣ ንግድና የጋራ ደህንነት ማረጋገጥ ይቻላታል፡፡
ምክክሩ የአንድ ጊዜ ሁነት ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ሀገራዊ ተቆርቋሪነት የሚጠይቅ የታሰበበት ረጅም ጉዞ ነው።
አለመግባባቶች የማህበረሰብ ተፈጥሯዊ አካል ቢሆኑም ጠንካራ ሀገር የሚገነባው ግን እነዚህን ልዩነቶች ባስተናገዱበት ጤናማ መንገድ እንደሆነ ይታመናል፡፡
ኢትዮጵያ ከግጭት ይልቅ ውይይትን በማስቀደም እያከናወነች የምትገኘው ሀገራዊ ምክክር አንድነት፣ የተቋማት ጥንካሬና ዘላቂ ሰላም የሚጸናበት አዲስ ምዕራፍ ነው፡፡
ከምንጊዜውም በላይ ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በመጠቀም ለወደፊቱ ትውልድ ምቹ ሀገር ለመገንባት ጊዜው አሁን ነው።
በምሕረት ደምሴ
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው 'ማሪን ዋን' የተሰኘው ሄሊኮፕተር፣ በዋሽንግተን ዲሲ የአየር ክልል ውስጥ ከኤንቮይ ኤር የመንገደኞች አውሮፕላን ጋር ከመጋጨት ለጥቂት ማምለጡን ተከትሎ የአሜሪካ አቪዬሽን ባለስልጣናት ጥብቅ ምርመራ ጀመሩ።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደ ሎስ አንጀለስ የሚያደርጉትን በረራ ለመጀመር ማክሰኞ ዕለት ከዋይት ሀውስ ወደ ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ በሄሊኮፕተራቸው እያመሩ ሳለ አደጋው ሊከሰት መቃረቡን ዘ ዋል ስትሪት ጆርናል ዛሬ በዘገባው አጋልጧል። የደህንነት ፕሮቶኮሎች እንደሚያስገድዱት፣ የፕሬዝዳንቱ ሄሊኮፕተር በአየር ላይ በሚሆንበት ወቅት በአቅራቢያው በሚገኘው የሮናልድ ሪገን ዋሽንግተን ብሔራዊ አውሮፕላን ማረፊያ የንግድ በረራዎች መቋረጥ የነበረባቸው ቢሆንም፣ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ይህንን የደህንነት አሰራር ባለማክበራቸው ሁለቱ አውሮፕላኖች እጅግ አደገኛ ወደሆነ ቅርበት ሊመጡ ችለዋል።
ለፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (FAA) የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶች ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጹት፣ ሄሊኮፕተሩ እና የመንገደኞች አውሮፕላኑ በጎን 1.3 ኪሎ ሜትር (0.8 ማይል) እንዲሁም ከላይ እና ታች በ213 ሜትር (700 ጫማ) ርቀት ላይ ብቻ ተገናኝተው ነበር። ይሁን እንጂ ሁለቱም በሰላም ማረፋቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ አውሮፕላኖቹ ርቀታቸውን እስኪጠብቁ ድረስ የቅርብ ግንኙነት ማድረጋቸውን አስተዳደሩ አስታውቋል። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይም በበኩላቸው "ፕሬዝዳንቱ በምንም ዓይነት አደጋ ውስጥ አልነበሩም" ሲሉ አረጋግጠዋል። አሁን ላይ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር እና የብሔራዊ ትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ በጉዳዩ ላይ የጋራ ምርመራ እያካሄዱ ይገኛሉ።
ይህ አሳሳቢ የደህንነት ጥሰት የተፈጠረው፣ በጥር 2025 የአሜሪካ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን እና የአሜሪካ ጦር 'ብላክ ሆክ' ሄሊኮፕተር ተጋጭተው 67 ሰዎች (በአውሮፕላኑ የነበሩ 64 መንገደኞች እና 3 የሄሊኮፕተር አብራሪዎች) ህይወታቸውን ካጡበት አሰቃቂ አደጋ በኋላ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
በወቅቱ ወደ ፖቶማክ ወንዝ በተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ ህይወታቸውን ካጡት መካከል፣ ከካንሳስ የአሜሪካ ፊገር ስኬቲንግ ሻምፒዮና ሲመለሱ የነበሩ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ቤተሰቦቻቸው ይገኙበታል። ከእነዚህም ውስጥ በ1998 ወደ አሜሪካ በማምራት በአሰልጣኝነት ሲሰሩ የነበሩት የ1994ቱ የዓለም ሻምፒዮን ሩሲያውያን ኦሎምፒያኖች ቫዲም ናኡሞቭ እና ዬቭጄኒያ ሺሽኮቫ ይገኙበታል። ያንን የጥር ወር አደጋ ተከትሎ፣ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሮናልድ ሪገን አውሮፕላን ማረፊያ ዙሪያ የሄሊኮፕተር በረራዎችን በቋሚነት የገደበ ሲሆን፣ ማሪን ዋን በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የንግድ በረራዎች ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጡ ጥብቅ አሰራር ተግባራዊ አድርጎ እንደነበር ይታወሳል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደ ሎስ አንጀለስ የሚያደርጉትን በረራ ለመጀመር ማክሰኞ ዕለት ከዋይት ሀውስ ወደ ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ በሄሊኮፕተራቸው እያመሩ ሳለ አደጋው ሊከሰት መቃረቡን ዘ ዋል ስትሪት ጆርናል ዛሬ በዘገባው አጋልጧል። የደህንነት ፕሮቶኮሎች እንደሚያስገድዱት፣ የፕሬዝዳንቱ ሄሊኮፕተር በአየር ላይ በሚሆንበት ወቅት በአቅራቢያው በሚገኘው የሮናልድ ሪገን ዋሽንግተን ብሔራዊ አውሮፕላን ማረፊያ የንግድ በረራዎች መቋረጥ የነበረባቸው ቢሆንም፣ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ይህንን የደህንነት አሰራር ባለማክበራቸው ሁለቱ አውሮፕላኖች እጅግ አደገኛ ወደሆነ ቅርበት ሊመጡ ችለዋል።
ለፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (FAA) የመጀመሪያ ደረጃ ግኝቶች ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለኒው ዮርክ ታይምስ እንደገለጹት፣ ሄሊኮፕተሩ እና የመንገደኞች አውሮፕላኑ በጎን 1.3 ኪሎ ሜትር (0.8 ማይል) እንዲሁም ከላይ እና ታች በ213 ሜትር (700 ጫማ) ርቀት ላይ ብቻ ተገናኝተው ነበር። ይሁን እንጂ ሁለቱም በሰላም ማረፋቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎቹ አውሮፕላኖቹ ርቀታቸውን እስኪጠብቁ ድረስ የቅርብ ግንኙነት ማድረጋቸውን አስተዳደሩ አስታውቋል። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይም በበኩላቸው "ፕሬዝዳንቱ በምንም ዓይነት አደጋ ውስጥ አልነበሩም" ሲሉ አረጋግጠዋል። አሁን ላይ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር እና የብሔራዊ ትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ በጉዳዩ ላይ የጋራ ምርመራ እያካሄዱ ይገኛሉ።
ይህ አሳሳቢ የደህንነት ጥሰት የተፈጠረው፣ በጥር 2025 የአሜሪካ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን እና የአሜሪካ ጦር 'ብላክ ሆክ' ሄሊኮፕተር ተጋጭተው 67 ሰዎች (በአውሮፕላኑ የነበሩ 64 መንገደኞች እና 3 የሄሊኮፕተር አብራሪዎች) ህይወታቸውን ካጡበት አሰቃቂ አደጋ በኋላ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
በወቅቱ ወደ ፖቶማክ ወንዝ በተከሰከሰው አውሮፕላን ውስጥ ህይወታቸውን ካጡት መካከል፣ ከካንሳስ የአሜሪካ ፊገር ስኬቲንግ ሻምፒዮና ሲመለሱ የነበሩ አትሌቶች፣ አሰልጣኞች እና ቤተሰቦቻቸው ይገኙበታል። ከእነዚህም ውስጥ በ1998 ወደ አሜሪካ በማምራት በአሰልጣኝነት ሲሰሩ የነበሩት የ1994ቱ የዓለም ሻምፒዮን ሩሲያውያን ኦሎምፒያኖች ቫዲም ናኡሞቭ እና ዬቭጄኒያ ሺሽኮቫ ይገኙበታል። ያንን የጥር ወር አደጋ ተከትሎ፣ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር በሮናልድ ሪገን አውሮፕላን ማረፊያ ዙሪያ የሄሊኮፕተር በረራዎችን በቋሚነት የገደበ ሲሆን፣ ማሪን ዋን በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የንግድ በረራዎች ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጡ ጥብቅ አሰራር ተግባራዊ አድርጎ እንደነበር ይታወሳል።
1 day ago
አዲሱ ተርሚናል የአማራ ክልልን ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት በማበልፀግ ቁልፍ ሚና ይጫወታል፦ አቶ መስፍን ጣሰው
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
*******************
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ4.1 ቢሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ የመንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፣ ባህር ዳር ከቀድሞው የጎጃም ክፍለ ሀገር እስከ አሁኑ የአማራ ክልል ዋና ከተማነቷ ላሳየችው ዕድገት ከ60 ዓመታት በፊት ወደ ከተማዋ በረራ የጀመረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የላቀ ሚና ተጫውቷል።
ይህ በ8 ሺህ 300 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው እና ጠቅላላ የወለል ስፋቱ 11 ሺህ 170 ካሬ ሜትር የሆነው አዲሱ ተርሚናል፣ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቀጥሎ ትልቁ የሀገር ውስጥ ተርሚናል መሆኑን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
ተርሚናሉ በአንድ ጊዜ እስከ 700 መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ሲሆን፣ ሰፊ የቪአይፒ ሳሎኖችን፣ የክቡር መንገደኞች ላውንጆችን እና ምግብ ቤቶችን ጭምር ያካተተ መሆኑንም አክለዋል።
በተደረገለት የኤፕሮን ማስፋፊያ አሁን ላይ በአንድ ጊዜ እንደ ቦይንግ 777 ያሉ 4 ትላልቅ እና እንደ ቦይንግ 737 ያሉ 6 መለስተኛ አውሮፕላኖችን ማቆም የሚያስችል አቅም ያለው ተርሚናሉ፣ ወደፊት በትንሽ ማስተካከያ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ መንገደኞችን በተጓዳኝ ማስተናገድ ይችላል ብለዋል።
አየር መንገዱ ወደ ባህር ዳር በቀን እስከ 14 የበረራ ምልልሶችን እንደሚያደርግ ጠቅሰው፤ የተርሚናሉ መገንባት በክልሉ ቱሪዝም፣ ንግድና ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ ከማድረግ ባሻገር ከተማዋ የኮንፈረንስች ማዕከል እንድትሆን ያግዛል ብለዋል።
አየር መንገዱ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አራት አዳዲስ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ገንብቶ አገልግሎት ላይ ማዋሉን እና አምስተኛው በመቱ በሚመጡት ሁለት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸው፤ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ እየተፋጠነ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለፕሮጀክቱ ስኬት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) እና ለኢፌዴሪ መንግሥት እንዲሁም ለቻይናው ሳኢኖ ሃይድሮ፣ ለአማካሪው ዳር አልሀንዳሳ፣ ለአየር መንገዱ መሀንዲሶች፣ ለአማራ ክልል እና ለባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #aviation #ethiopianairlines #bahirdar #airport #ebc
1 day ago
ሃምሣ ዓመታትን የዘለቀ የተቃርኖ እና የደባ ጉዞ
*********************
የከሰረው የህወሓት ቡድን ከተፈጠረበት ዘመን አንሥቶ እስካሁን ድረስ የሚናገረው ሌላ፣ የሚያደርገው ሌላ የሆነ የተቃርኖ ፖለቲካ ቁንጮ ነው።
ብዙ ጊዜ በጽሑፍ ማንነቱን ሲገልጽ የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስብስብ በእውነተኛ ትርጉሙ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የሀገር መሪ ሆኖ አያውቅም። ይልቁንም ላለፉት አምስት ዐሥርት ዓመታት፣ ክልልንም ሆነ ሀገርን ጨምድዶ በመያዝ እንደ አንድ የሽፍታ ቡድን የሚያስብ፣ በጥቂት ቤተሰቦች የጥቅም ትሥሥር የሚዘወር ማፍያዊ ስብስብ ነው።
ድሮም ሆነ አሁን ለፍላጎቱ ያልተገዙትን የሚጨቁን፣ ትብብርን የሚጠላ፣ የሚያጠፋ፣ የሚበትን እና የሚገድል፤ የጥላቻ ቁንጮ የሆነ፣ ፀረ አንድነት እና ፀረ ኅብረ ብሔራዊነት የተጠናወተው ቡድን ነው። ይህ ቡድን በ1968 ዓ.ም ባወጣው ማኒፌስቶው እውነተኛ ፀረ ሕዝብ ማንነቱን አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ታሪክ ዋልታ የሆነውን፣ የጠንካራ ኢትዮጵያዊነት መሠረት የሆነውን የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያ ነጥሎ ለማኖር ለዘመናት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። “የትግራይ ሪፐብሊክ”፣ የቅኝ ገዥ እና ተገዥ የመሳሰሉ የተለያዩ ከፋፋይ የሐሰት ትርክቶችን በስፋት ሲገነባ የኖረ ቡድን ነው።
ዓላማውን ለማሳካትም ኢትዮጵያውያን ወንድም እኅቶቹን “ቅኝ ገዢ” ብሎ በመፈረጅ እና ታሪክን ለሴራው በሚመች መልኩ በማጣመም የጥላቻ መርዝን ሲዘራ ኖሯል።
አፈና፣ ደም አፋሳሽነት እና የሤራ ፖለቲካ የተጠናወተው የከሰረው የህወሓት ቡድን ፀረ አንድነት ብቻ ሳይሆን የገዛ ወንድሞቹን የሚበላ፣ ለራሱ ወዳጆችም የማይመለስ ርኅራኄ አልባ ቡድን ነው።
በ1969 ዓ.ም በድርጅቱ ውስጥ የተነሳውን ህንፍሽፍሽ መሠረት አድርጎ የገዛ ታጋዮቹን በጅምላ ረሽኗል። በሌላ ጊዜ ደግሞ የተለየ ሐሳብ ያነሱትን መሥራቾችን ሳይቀር “ጋንግሪን” በማለት አስወግዷል።
ይህ ቡድን ዜጎችን በማጎሪያ ካምፖቹ ውስጥ በማጎር አሰቃይቷል፣ በሰው ልጆች ላይ ሊፈጸሙ የማይገባቸውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ወንጀሎችን ሲፈጽም ኖሯል።
ሌላው ታሪካዊ ክህደት በግገሓት ላይ የተፈጸመው ወንጀል ሲሆን፣ ይህም ሁለቱ ድርጅቶች አብረን እንታገል ብለው ተስማምተው አብረው ካደሩ በኋላ፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን በሌሊት የግገሓት መሪዎችን በጥይት ደብድቦ የፈጁበት ታሪክ ነው።
ይህ ስብስብ ሀገር በመካድ በሕዝብ ስም እየነገደ የራሱን ቢዝነስ ኢምፓየር መገንባትን ዋነኛ ግቡ ያደረገ ቡድን ነው። አንጋፋው የቡድኑ መሥራች አቶ ገብሩ አስራት ዛሬ በጸጸት እንደሚመሰክሩት፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን የኤርትራን ጉዳይ “የቅኝ ግዛት ነፃነት ጥያቄ ነው” በሚል የተሳሳተ ትርክት ተሟግቶ ኢትዮጵያን ያለ ባሕር በር አስቀርቷል።
ዛሬም ቢሆን ለትግራይ ሕዝብ አንዳች ነገር የማይፈይደው ይህ የከሰረ ቡድን፣ ሕዝቡን ከግጭት ወደ ትርምስ እያሸጋገረ፣ ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር እያጋጨ የትግራይን ወጣት እያስጨረሰው ይገኛል። ሕዝቡን መላልሶ ለማያልቅ ስጋት፣ ውጥረት እና ችግር እየዳረገው ነው።
አሁን ግን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው ይህ የጥላቻ እና የክፋት ጉዞ ማብቂያው ደርሷል! የትግራይ ሕዝብ የቡድኑን ማፊያዊ ባሕርይ ጠንቅቆ ተረድቶ "በቃኝ!" ብሏል።
ቡድኑ የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን እና "እኔ ነኝ የማውቅልህ" ለማለት ቢሞክርም፣ የዚህ አውዳሚ ኃይል መጨረሻው እጅግ ቀርቧል። አሁን ሕዝቡ ይህን የጥፋት ቡድን ከራሱ ነጥሎ የሚጥልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ዛሬ ለትግራይ ሕዝብ አዲስ ዘመን ሊበሰር ዋዜማው ላይ ነን። የትግራይ ወጣት ተስፋው የሚቀየርበት፣ ከጥላቻ ፖለቲካ ተላቅቆ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የኢትዮጵያን የጋራ ብልጽግና የሚያረጋግጥበት ብሩህ ዘመን እጅግ ቅርብ ነው!
#ethiopia #tigray #peace
*********************
የከሰረው የህወሓት ቡድን ከተፈጠረበት ዘመን አንሥቶ እስካሁን ድረስ የሚናገረው ሌላ፣ የሚያደርገው ሌላ የሆነ የተቃርኖ ፖለቲካ ቁንጮ ነው።
ብዙ ጊዜ በጽሑፍ ማንነቱን ሲገልጽ የነበረ ቢሆንም፣ ይህ ስብስብ በእውነተኛ ትርጉሙ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም የሀገር መሪ ሆኖ አያውቅም። ይልቁንም ላለፉት አምስት ዐሥርት ዓመታት፣ ክልልንም ሆነ ሀገርን ጨምድዶ በመያዝ እንደ አንድ የሽፍታ ቡድን የሚያስብ፣ በጥቂት ቤተሰቦች የጥቅም ትሥሥር የሚዘወር ማፍያዊ ስብስብ ነው።
ድሮም ሆነ አሁን ለፍላጎቱ ያልተገዙትን የሚጨቁን፣ ትብብርን የሚጠላ፣ የሚያጠፋ፣ የሚበትን እና የሚገድል፤ የጥላቻ ቁንጮ የሆነ፣ ፀረ አንድነት እና ፀረ ኅብረ ብሔራዊነት የተጠናወተው ቡድን ነው። ይህ ቡድን በ1968 ዓ.ም ባወጣው ማኒፌስቶው እውነተኛ ፀረ ሕዝብ ማንነቱን አሳይቷል።
የኢትዮጵያ ታሪክ ዋልታ የሆነውን፣ የጠንካራ ኢትዮጵያዊነት መሠረት የሆነውን የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያ ነጥሎ ለማኖር ለዘመናት ያልፈነቀለው ድንጋይ አልነበረም። “የትግራይ ሪፐብሊክ”፣ የቅኝ ገዥ እና ተገዥ የመሳሰሉ የተለያዩ ከፋፋይ የሐሰት ትርክቶችን በስፋት ሲገነባ የኖረ ቡድን ነው።
ዓላማውን ለማሳካትም ኢትዮጵያውያን ወንድም እኅቶቹን “ቅኝ ገዢ” ብሎ በመፈረጅ እና ታሪክን ለሴራው በሚመች መልኩ በማጣመም የጥላቻ መርዝን ሲዘራ ኖሯል።
አፈና፣ ደም አፋሳሽነት እና የሤራ ፖለቲካ የተጠናወተው የከሰረው የህወሓት ቡድን ፀረ አንድነት ብቻ ሳይሆን የገዛ ወንድሞቹን የሚበላ፣ ለራሱ ወዳጆችም የማይመለስ ርኅራኄ አልባ ቡድን ነው።
በ1969 ዓ.ም በድርጅቱ ውስጥ የተነሳውን ህንፍሽፍሽ መሠረት አድርጎ የገዛ ታጋዮቹን በጅምላ ረሽኗል። በሌላ ጊዜ ደግሞ የተለየ ሐሳብ ያነሱትን መሥራቾችን ሳይቀር “ጋንግሪን” በማለት አስወግዷል።
ይህ ቡድን ዜጎችን በማጎሪያ ካምፖቹ ውስጥ በማጎር አሰቃይቷል፣ በሰው ልጆች ላይ ሊፈጸሙ የማይገባቸውን አሰቃቂ ሰብዓዊ ወንጀሎችን ሲፈጽም ኖሯል።
ሌላው ታሪካዊ ክህደት በግገሓት ላይ የተፈጸመው ወንጀል ሲሆን፣ ይህም ሁለቱ ድርጅቶች አብረን እንታገል ብለው ተስማምተው አብረው ካደሩ በኋላ፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን በሌሊት የግገሓት መሪዎችን በጥይት ደብድቦ የፈጁበት ታሪክ ነው።
ይህ ስብስብ ሀገር በመካድ በሕዝብ ስም እየነገደ የራሱን ቢዝነስ ኢምፓየር መገንባትን ዋነኛ ግቡ ያደረገ ቡድን ነው። አንጋፋው የቡድኑ መሥራች አቶ ገብሩ አስራት ዛሬ በጸጸት እንደሚመሰክሩት፣ የከሰረው የህወሓት ቡድን የኤርትራን ጉዳይ “የቅኝ ግዛት ነፃነት ጥያቄ ነው” በሚል የተሳሳተ ትርክት ተሟግቶ ኢትዮጵያን ያለ ባሕር በር አስቀርቷል።
ዛሬም ቢሆን ለትግራይ ሕዝብ አንዳች ነገር የማይፈይደው ይህ የከሰረ ቡድን፣ ሕዝቡን ከግጭት ወደ ትርምስ እያሸጋገረ፣ ከአጎራባች ሕዝቦች ጋር እያጋጨ የትግራይን ወጣት እያስጨረሰው ይገኛል። ሕዝቡን መላልሶ ለማያልቅ ስጋት፣ ውጥረት እና ችግር እየዳረገው ነው።
አሁን ግን፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀው ይህ የጥላቻ እና የክፋት ጉዞ ማብቂያው ደርሷል! የትግራይ ሕዝብ የቡድኑን ማፊያዊ ባሕርይ ጠንቅቆ ተረድቶ "በቃኝ!" ብሏል።
ቡድኑ የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን እና "እኔ ነኝ የማውቅልህ" ለማለት ቢሞክርም፣ የዚህ አውዳሚ ኃይል መጨረሻው እጅግ ቀርቧል። አሁን ሕዝቡ ይህን የጥፋት ቡድን ከራሱ ነጥሎ የሚጥልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል።
ዛሬ ለትግራይ ሕዝብ አዲስ ዘመን ሊበሰር ዋዜማው ላይ ነን። የትግራይ ወጣት ተስፋው የሚቀየርበት፣ ከጥላቻ ፖለቲካ ተላቅቆ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ የኢትዮጵያን የጋራ ብልጽግና የሚያረጋግጥበት ብሩህ ዘመን እጅግ ቅርብ ነው!
#ethiopia #tigray #peace
Sponsored by
Surafel
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው" ሲሉ የኩምሩክ ግዛት አስተዳዳሪ ተናገሩ፡፡ የኩምሩክ ገዥ አብደል አቲ መሀመድ አልፋቂ የአካባቢው ነዋሪዎች ቀስ በቀስ መመለስ እንደጀመሩ አስታወቁ፡፡ ይህም በሰሜናዊ ኩምሩክ ውስጥ በሚገኙት ሁለት አስተዳደሮች ውስጥ መረጋጋት እየተፈጠረ መሆኑን እንደሚያሳይ ገልፀዋል፡፡
አልፋቂ ከሱዳን ሆራይዘን ጋር በተለይ ባደረጉት ቃለምልልስ አካባቢው በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወይንም RSF እጅ በነበረበት ወቅት የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አጠቃላይ ግምገማ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ወሳኝ የሆኑ የህዝብ አገልግሎት መስጫዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡ በከተማው ውስጥ የተበተኑ ያልፈነዱ ቦምቦች፣ አደገኛ እቃዎችና ሌሎች የጦርነት ቅሪቶች በብዛት መኖራቸውን ጠቅሰውም እነዚህን የማፅዳት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡
በከተማው የተቀበሩ ፈንጂዎች ለማህበረሰቡ ትልቅ ስጋት መሆናቸውን ያስታወቁት ገዥው የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ ለመመለስ የሚቻለው ይህ የማፅዳት ስራው በቴክኒክ ኮሚቴዎች ከተረጋገጠ በኋላ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ የጤናና የውሀ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የጠቀሱት ገዢው በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህም ሆኖ RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው›› በማለት መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
አልፋቂ ከሱዳን ሆራይዘን ጋር በተለይ ባደረጉት ቃለምልልስ አካባቢው በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ወይንም RSF እጅ በነበረበት ወቅት የደረሰውን ጉዳት ለማወቅ አጠቃላይ ግምገማ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ጨምረውም ወሳኝ የሆኑ የህዝብ አገልግሎት መስጫዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልፀዋል፡፡ በከተማው ውስጥ የተበተኑ ያልፈነዱ ቦምቦች፣ አደገኛ እቃዎችና ሌሎች የጦርነት ቅሪቶች በብዛት መኖራቸውን ጠቅሰውም እነዚህን የማፅዳት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም አስረድተዋል፡፡
በከተማው የተቀበሩ ፈንጂዎች ለማህበረሰቡ ትልቅ ስጋት መሆናቸውን ያስታወቁት ገዥው የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ ለመመለስ የሚቻለው ይህ የማፅዳት ስራው በቴክኒክ ኮሚቴዎች ከተረጋገጠ በኋላ እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡ የጤናና የውሀ መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የጠቀሱት ገዢው በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህም ሆኖ RSF አሁንም ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ካምፕ አለው›› በማለት መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የሆኑትን አቶ አዘዘው ጫኔን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። ዜናው የሀገሪቱን የፋይናንስ እና የጸጥታ ተቋማት በእጅጉ ያስገረመ ሲሆን፣ ምክትል ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት "ህገ-ወጥ ንግድን እና የኮንትሮባንድ ዝውውርን ይቆጣጠራሉ" ተብሎ በተሰጣቸው ከፍተኛ የኃላፊነት ወንበር ላይ ተቀምጠው፣ በተቃራኒው መንግስትን ለከፍተኛ ኪሳራ የዳረገ የተደራጀ ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ነው።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
አቶ አዘዘው ጫኔ የጉምሩክ ኮሚሽን የህግ ተገዥነት ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ሀገርን ከኢኮኖሚ አሻጥር ከመጠበቅ ይልቅ አሻጥሩን በዋናነት ሲመሩት እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ዘ-ሐበሻ የተመለከተው በምክትል ኮሚሽነሩ ላይ ከቀረቡት ዋና ዋና የጥርጣሬ ክሶች መካከል በገቢዎች እና ጉምሩክ አስተዳደር ውስጥ የዘረጉትን ሰፊ መረብ በመጠቀም፣ ትክክለኛ የግብር ምዘናዎችን በማዛባት እና መንግስት ማግኘት የነበረበትን ከፍተኛ ገቢ በማሳጣት የግብር ምዘና ማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው በዋናነት ይጠቀሳል። ከዚህም በተጨማሪ የሐሰት የክፍያ ደረሰኞችን እና ህገ-ወጥ ሰነዶችን ወደ ተቋሙ ስርዓት በማስገባት እና በማስተናገድ የሰነድ ማጭበርበር እንደፈጸሙ ተገልጿል።
በተያያዘም የመንግሥትን ገቢ ለመቀነስ፣ የፈጸሙትን ወንጀል ዱካ ለማጥፋት እና ምርመራን ለማደናቀፍ ሲባል የተቋሙን ቁልፍ የኮምፒውተር መረጃዎች ሆን ብሎ በመደምሰስ የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎችን በማጥፋት ክስ ቀርቦባቸዋል። ከዚህ ሁሉ ባለፈ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ ተግባራዊ እያደረገች ያለውን የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማስተጓጎል በማሰብ፣ ከኮንትሮባንድ አዘዋዋሪዎች እና ከሌሎች ህገ-ወጥ የጥቅም መረቦች ጋር በቀጥታ በመመሳጠር የተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር መፈጸማቸው በምርመራ መመላከቱን ፖሊስ አብራርቷል።
ይህ ክስተት የህግ የበላይነትን እና የተቋማት ታማኝነትን በተመለከተ ትልቅ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው። የህግ ተገዥነትን እንዲያስከብሩ የተሾሙ ከፍተኛ ባለስልጣን፣ የመንግስትን የኤሌክትሮኒክስ መረጃዎች እስከማጥፋት እና ከኮንትሮባንዲስቶች ጋር እስከመመሳጠር መድረሳቸው በጉምሩክ ኮሚሽኑ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ላይ ትልቅ የደህንነት ክፍተት መኖሩን ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
በተለይም መንግስት የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የውጭ ምንዛሬ እና የገበያ መረጋጋትን ለማምጣት በሚጥርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ ቁልፍ የተቋሙ አመራሮች ራሳቸው ስርዓቱን ለማፍረስ በሚደረግ አሻጥር ውስጥ መገኘታቸው፣ የጸረ-ሙስና ዘመቻው ከመቼውም ጊዜ በላይ ከራሱ ከመንግስት መዋቅር መጀመር እንዳለበት የሚያመላክት ነው። ፌዴራል ፖሊስ በጉዳዩ ላይ የጀመረውን ጥልቅ ምርመራ አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
Comments