የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን እና አየር ኃይሉም ይህን ለማስጠበቅ አቅሙን እየገነባ እንደሚገኝ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን እጅግ ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ። የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው እንዳሉት፣ ተቋሙ ይህንን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚመጥን ጠንካራ አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚዘልቅ ነው። አየር ኃይሉም ለዚህ አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም የሚመጥን የላቀ የመከላከል አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል።
ምክትል አዛዡ አክለውም ባላጋራ ኃይሎች የቱንም ያህል ፍላጎትና ዛቻ ቢኖራቸውም፣ የአየር ኃይሉ የመከላከል አቅም በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ ስለሚረዱት ጥቃት ከመሰንዘር መቆጠባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ የአየር ኃይሉ ከአፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት፤ በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በእውቀት እና ራስን ችሎ በመሥራት በኩል ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ድርሻ እንደምትይዝ አስረድተዋል።
እንደ ምክትል አዛዡ ገለጻ፣ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቋሙን ለመጎብኘት የሚመጡ የልዑካን ቡድኖች በአየር ኃይሉ ውስጥ ያለውን ዘመናዊ አሠራር ሲመለከቱ ከጠበቁት በላይ ይሆንባቸዋል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር “በጋራ እንሥራ” የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከሦስት በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችሉ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም በታላቁ ሕዳሴ ግድብ ላይ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን እጅግ ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚደርስ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስታወቀ። የአየር ኃይሉ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው እንዳሉት፣ ተቋሙ ይህንን አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚመጥን ጠንካራ አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን በትጋት እየሠራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት ጌታቸው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም ሰፊና እስከ ሕንድ ውቅያኖስ የሚዘልቅ ነው። አየር ኃይሉም ለዚህ አገራዊና ቀጣናዊ ጥቅም የሚመጥን የላቀ የመከላከል አቅም ለመገንባት ሌት ተቀን እየሠራ ይገኛል።
ምክትል አዛዡ አክለውም ባላጋራ ኃይሎች የቱንም ያህል ፍላጎትና ዛቻ ቢኖራቸውም፣ የአየር ኃይሉ የመከላከል አቅም በየቀኑ እየጨመረ መምጣቱን በሚገባ ስለሚረዱት ጥቃት ከመሰንዘር መቆጠባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል፣ የአየር ኃይሉ ከአፍሪካ አገራት ጋር ሲነፃፀር አሁን ላይ ያለበት ደረጃ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ብርጋዴር ጄኔራል መሠረት፤ በተለይም በቴክኖሎጂ፣ በእውቀት እና ራስን ችሎ በመሥራት በኩል ኢትዮጵያ ከፍተኛውን ድርሻ እንደምትይዝ አስረድተዋል።
እንደ ምክትል አዛዡ ገለጻ፣ ከበርካታ የአፍሪካ አገራት ተቋሙን ለመጎብኘት የሚመጡ የልዑካን ቡድኖች በአየር ኃይሉ ውስጥ ያለውን ዘመናዊ አሠራር ሲመለከቱ ከጠበቁት በላይ ይሆንባቸዋል። በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ አየር ኃይል ጋር “በጋራ እንሥራ” የሚሉ ጥያቄዎችን በስፋት የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከሦስት በላይ ከሚሆኑ የአፍሪካ አገራት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችሉ የትብብር ስምምነቶች መፈረማቸውን ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago