5 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የቀድሞው የማን.ዩናይትድ ግብ ጠባቂ እና አሁን የስካይ ስፖርት ተንታኝ የሆነው ጋሪ ኔቪል፣ ማይክል ካሪክ ከካርሎስ ባሌባ ይልቅ ለምን ኦሪሊየን ቹዋሜኒን እንደሚመርጥ በስሜት ሲያስረዳ እንዲህ ብሏል፦
“በቅርቡ ለማይክል ካሪክ እጅግ ቅርብ ከሆነ ሰው ጋር ሳወራ፣ ‘ለምን ካሪክ እንደ ባሌባ ካለ ተጫዋች ይልቅ ቹዋሜኒን አብዝቶ ይፈልጋል?’ ብዬ ጠየቅኩት። ሰውየው ቅንጣት ታክል ሳያመነታ እንዲህ ሲል መለሰልኝ፡ ‘ምክንያቱም ባሌባ ድንቅ ተጫዋች ስላልሆነ አይደለም፤ ይልቁንም ቹዋሜኒ በእግር ኳሱ ዓለም እጅግ ግዙፍ የሚባሉትን ጨዋታዎች እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል አስቀድሞ በሚገባ ስለተረዳው ነው።’”
“ይህን ሀሳቡን በደንብ እንዲያብራራልኝ ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡ ‘የፕሪሚየር ሊጉን እና የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ማንሳት የሚችል ጠንካራ ቡድን ስትገነባ፣ ከከፍተኛ ጥራት በተጨማሪ ሜዳ ላይ ፍፁም እርጋታን የሚያመጡ አማካዮች ያስፈልጉሃል። ቹዋሜኒ የጨዋታውን ፍጥነት መቼ መጨመር እና መቼ ማቀዝቀዝ እንዳለበት፣ የተቃራኒ ቡድንን ጥቃት መቼ ማቋረጥ እና የመስመር ሰንጣቂ ኳሶችን መቼ ማቀበል እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። እነዚህ ልዩ ብቃቶች ደግሞ ከዓመት ዓመት በከፍተኛው የውድድር ደረጃ ላይ ከመጫወት ብቻ የሚገኙ ናቸው።’”
“ያኔ ነው ነገሩ ሁሉ የገባኝ። ካሪክ የተጫዋቹን ተሰጥኦ ብቻ ሳይሆን አስተማማኝነቱንም ጭምር ነው እየገመገመ ያለው። ባሌባ እጅግ ግዙፍ አቅም ያለው እና ወደፊት በአውሮፓ ውስጥ ከሚገኙት ምርጥ አማካዮች አንዱ ሊሆን የሚችል ተጫዋች ነው፤ ቹዋሜኒ ግን ዛሬ ላይ የምትፈልገውን እርግጠኝነት ይሰጥሃል። ትልቁ አላማህ ትልልቆቹን ዋንጫዎች ዛሬውኑ ለማሸነፍ መፎካከር ከሆነ፣ ካሪክ ለምን ራሱን በትልቁ መድረክ ላይ በተግባር ወዳስመሰከረው ተጫዋች እንዳዘነበለ በሚገባ ትረዳለህ።”
“በቅርቡ ለማይክል ካሪክ እጅግ ቅርብ ከሆነ ሰው ጋር ሳወራ፣ ‘ለምን ካሪክ እንደ ባሌባ ካለ ተጫዋች ይልቅ ቹዋሜኒን አብዝቶ ይፈልጋል?’ ብዬ ጠየቅኩት። ሰውየው ቅንጣት ታክል ሳያመነታ እንዲህ ሲል መለሰልኝ፡ ‘ምክንያቱም ባሌባ ድንቅ ተጫዋች ስላልሆነ አይደለም፤ ይልቁንም ቹዋሜኒ በእግር ኳሱ ዓለም እጅግ ግዙፍ የሚባሉትን ጨዋታዎች እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል አስቀድሞ በሚገባ ስለተረዳው ነው።’”
“ይህን ሀሳቡን በደንብ እንዲያብራራልኝ ስጠይቀው እንዲህ አለኝ፡ ‘የፕሪሚየር ሊጉን እና የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ማንሳት የሚችል ጠንካራ ቡድን ስትገነባ፣ ከከፍተኛ ጥራት በተጨማሪ ሜዳ ላይ ፍፁም እርጋታን የሚያመጡ አማካዮች ያስፈልጉሃል። ቹዋሜኒ የጨዋታውን ፍጥነት መቼ መጨመር እና መቼ ማቀዝቀዝ እንዳለበት፣ የተቃራኒ ቡድንን ጥቃት መቼ ማቋረጥ እና የመስመር ሰንጣቂ ኳሶችን መቼ ማቀበል እንዳለበት ጠንቅቆ ያውቃል። እነዚህ ልዩ ብቃቶች ደግሞ ከዓመት ዓመት በከፍተኛው የውድድር ደረጃ ላይ ከመጫወት ብቻ የሚገኙ ናቸው።’”
“ያኔ ነው ነገሩ ሁሉ የገባኝ። ካሪክ የተጫዋቹን ተሰጥኦ ብቻ ሳይሆን አስተማማኝነቱንም ጭምር ነው እየገመገመ ያለው። ባሌባ እጅግ ግዙፍ አቅም ያለው እና ወደፊት በአውሮፓ ውስጥ ከሚገኙት ምርጥ አማካዮች አንዱ ሊሆን የሚችል ተጫዋች ነው፤ ቹዋሜኒ ግን ዛሬ ላይ የምትፈልገውን እርግጠኝነት ይሰጥሃል። ትልቁ አላማህ ትልልቆቹን ዋንጫዎች ዛሬውኑ ለማሸነፍ መፎካከር ከሆነ፣ ካሪክ ለምን ራሱን በትልቁ መድረክ ላይ በተግባር ወዳስመሰከረው ተጫዋች እንዳዘነበለ በሚገባ ትረዳለህ።”
7 hours ago
ለሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ የባህልና ጥበባት አምባሳደር ሞዴል ሩት ይርጋለም ሸኝት ተደረገላት።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለምትወክለው ሞዴል ሩት ይርጋለም የእንኳን ደስ አለሽና የሽኝት መርሃ ግብር አደረገ።
ክብርት ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ለሞዴሏ መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ በማስተዋወቅ በድል እንድትመለስ ተመኝተዋል።
ክብርት ሸዊት በንግግራቸው ሞዴሏ የባህል አምባሳደር ሆና ከተሾመች በኋላ የሀገሪቱን ብዝሃ ባህላዊ ዕሴቶች በቅርበት ለመረዳት በተለያዩ ቦታዎች ጉብኝት ማድረጓን አንስተዋል።
በዚሁ መሠረት በደቡብ ኢትዮጵያ በመገኘት የህዝቡን ባህል፣ በአማራ ክልል ጎንደር በመሄድ የክልሉን ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ባሌ በመገኘት የገዳ ስርዓትንና ድቅ ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን በበቂ ሁኔታ ጎብኝታለች ብለዋል።
ይህ በክልሎች ያደረገችው ቆይታ የሀገሪቱን ባህልና ጥበብ ጠልቃ እንድታውቅ የረዳት ሲሆን፣ ከ130 በላይ የዓለም ሀገራት ሞዴሎች በሚሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያን በብቃት ለማስተዋወቅና ገጽታዋን ከፍ ለማድረግ እንደሚያግዛት ገልፀዋል።
የገጠማትን ማንኛውንም ፈተና ተቋቁማ የሀገሯን ባህልና ጥበብ በዓለም አቀፍ አደባባይ ለማሳየት ቆርጣ የተነሳች ጠንካራ ወጣት በመሆኗ ትልቅ አድናቆትና ምስጋና እንደሚገባትም ክብርት ሸዊት ሻንካ አክለዋል።
ክብርት ሸዊት ለመላው ኢትዮጵያውያን ባስተላለፈው መልዕክት በመጪው ውድድር ላይ በሚፈጠረው የማህበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ (Link) አማካኝነት ሁሉም ድጋፉን እንዲሰጥና ለሞዴሏ ስኬት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ሞዴል ሩት ይርጋለም በበኩሏ ለተደረገላት የሸኝትና መልካም ምኞት መርሀ ግብር ምስጋና አቅርባለች።
ሞዴሏ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለማስጠራት ቆርጣ እንደተነሳች በመግለፅ የገጠማት ችግር ወደሗላ እንደማይመልሳት አንስታለች።
ከዓለም አቀፉ ውድድር በሗላም በሀገሯ ያሉ ባህላዊና ጥበባዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅ እደምሰራ ገልፃለች።
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደር የባህልና ስፖርት ሴክተር አመራሮች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች፣ የሙያ ማህበራት አመራሮችና የሞዴሏ ቤተሰቦች ተገኝተው ለሞዴሏ የሀገር አደራ ተሰጥቷል።
Via የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለምትወክለው ሞዴል ሩት ይርጋለም የእንኳን ደስ አለሽና የሽኝት መርሃ ግብር አደረገ።
ክብርት ሸዊት ሻንካ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ለሞዴሏ መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ በማስተዋወቅ በድል እንድትመለስ ተመኝተዋል።
ክብርት ሸዊት በንግግራቸው ሞዴሏ የባህል አምባሳደር ሆና ከተሾመች በኋላ የሀገሪቱን ብዝሃ ባህላዊ ዕሴቶች በቅርበት ለመረዳት በተለያዩ ቦታዎች ጉብኝት ማድረጓን አንስተዋል።
በዚሁ መሠረት በደቡብ ኢትዮጵያ በመገኘት የህዝቡን ባህል፣ በአማራ ክልል ጎንደር በመሄድ የክልሉን ባህላዊ እሴቶች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ባሌ በመገኘት የገዳ ስርዓትንና ድቅ ተፈጥሮአዊ ሀብቶችን በበቂ ሁኔታ ጎብኝታለች ብለዋል።
ይህ በክልሎች ያደረገችው ቆይታ የሀገሪቱን ባህልና ጥበብ ጠልቃ እንድታውቅ የረዳት ሲሆን፣ ከ130 በላይ የዓለም ሀገራት ሞዴሎች በሚሳተፉበት መድረክ ኢትዮጵያን በብቃት ለማስተዋወቅና ገጽታዋን ከፍ ለማድረግ እንደሚያግዛት ገልፀዋል።
የገጠማትን ማንኛውንም ፈተና ተቋቁማ የሀገሯን ባህልና ጥበብ በዓለም አቀፍ አደባባይ ለማሳየት ቆርጣ የተነሳች ጠንካራ ወጣት በመሆኗ ትልቅ አድናቆትና ምስጋና እንደሚገባትም ክብርት ሸዊት ሻንካ አክለዋል።
ክብርት ሸዊት ለመላው ኢትዮጵያውያን ባስተላለፈው መልዕክት በመጪው ውድድር ላይ በሚፈጠረው የማህበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ (Link) አማካኝነት ሁሉም ድጋፉን እንዲሰጥና ለሞዴሏ ስኬት ከጎኗ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
ሞዴል ሩት ይርጋለም በበኩሏ ለተደረገላት የሸኝትና መልካም ምኞት መርሀ ግብር ምስጋና አቅርባለች።
ሞዴሏ ሀገሯን በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለማስጠራት ቆርጣ እንደተነሳች በመግለፅ የገጠማት ችግር ወደሗላ እንደማይመልሳት አንስታለች።
ከዓለም አቀፉ ውድድር በሗላም በሀገሯ ያሉ ባህላዊና ጥበባዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅ እደምሰራ ገልፃለች።
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልልና የከተማ አስተዳደር የባህልና ስፖርት ሴክተር አመራሮች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች፣ የሙያ ማህበራት አመራሮችና የሞዴሏ ቤተሰቦች ተገኝተው ለሞዴሏ የሀገር አደራ ተሰጥቷል።
Via የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር
23 hours ago
የሲኤንኤን ልዩ ዘገባ በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም እድገት | Bale Mountains | CNN |
#ethiopia #balemountains #unesco #tourismethiopia #cnn #ethiopianairlines #visitethiopia
2 days ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
6 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሀገራዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፡-
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
👉 ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም በከፍተኛ ወታደራዊና የመንግሥት አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትምምን ውስጥ ጠባሳ ፈጥሯል፡፡
👉 የፖለቲካ መተማመን በጣም እንዲቀዘቅዝ አድርጓል፣ በሰዎች መካከል አብረህ እየኖርክ፤ እየሰራህ፤ እየተሰበሰብክ የመተማመን ዝንባሌው በእጅጉ እንዲቀንስ አደርጓል፡፡
👉 አብረህ ስለ ሀገር ከምትመክረው ሰው አደጋ ያጋጥመኛል ብለህ እያሰብክ መምከር በእጅጉ ትምምንን የሚቀንስ ጉዳይ ስለሆነ እንደ አንድ ጠባሳ የሚታይ ክስተት ነው፡፡
👉 ክስተቱ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል አበላሽቶታል፤ ከንግግር ከውይይት ይልቅ በመሳሪያና በጉልበት ግለሰቦችን በማፈንና በመግደል ስልጣን የመጎናጸፍ ልምምድን የሚያስቀጥል ጠባሳ ሆኗል፡፡
👉 ገዳይንም፣ ሟችንም ሁለቱንም ወገኖች በጀግንነት ያወሳ የፖለቲካ ትርክት የታየበት ክስተት ነው፤ ይህንን አሁንም ቆም ብለን ማየት ይገባናል፡፡
👉 ታሪክን እየመረጥን፣ እያንሻፈፍን እና በፈለግነው መንገድ የማቆየት የትርክት ስብራት ጉዳይ አሁን ላለንበት አጠቃላይ ውጥንቅጥ ዋናው መሰረት ነው፡፡
👉 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እስካሁን ከሚስተዋለው ከዚህ ውጥንቅጥ ወጥተን፤ ታሪክን እንዳለ አስቀምጠን ከመልካሙም ከስህተቱም መማር ይገባናል፡፡
👉 አሁን እዚህ እንደ ዋዛ በብሄርተኝነት ስሜት በአውራጃዊነት ስሜት ታሪክን አንሻፍፈን ብንጽፍ፣ ብንናገር ነገ ልጆቻችንን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማሰብ አለመቻል ደግሞ ያሳዝነኛል፡፡
👉 ይሄ ጉዳይ እንዳለ ታሪኩን አስቀምጠህ ከተቀመጠው ታሪክ ተነስተህ በሚኖረው ትንተና የፈለግከውን ነገር ወደ ቀኝ ወደ ግራ ወስደህ መማር ትችላለህ፡፡
👉 ታሪክን ማዛባት ግን እምብዛም ጠቃሚ አይደለም፤ ዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገም ዋጋ ያስከፍላል፣ ትውልድ ዋጋ ይከፍልበታል፡፡
👉 እኛ በህይወት እያለን የምናውቀውን ጉዳይ በተንሸዋረረ የታሪክ አረዳድ የምናስቀምጥ ከሆነ እኛ በማንኖርበት ሰዓት የሚኖረው ትወልድ እንዴት እንደሚወስደው አሁን ባለው የኢትዮጵያ ታሪክ መመልከት ይቻላል፡፡
👉 አሁን ያለው የኢትዮጵያ ታሪክ የዚህ የተንሸዋረረ የፖለቲካ ትርክት ውጤት ነው፡፡
👉 ታሪክን እንዳለ ማስቀመጥ ሳይሆን አዛብተን በማስቀመጣችን ምክንያት የሚፈጠር ችግር ነው፤ ከዚያም ሻገር ሲል የፖለቲካ ሴራ ተንታኞች መጠቀሚያም ሆኗል፡፡
👉 ያ ክስተት በተፈጠረበት ወቅት አሚኮን ጠርተን ለሕዝቡ መግለጫ የሰጠነው እዚሁ አዲስ አበባ መሆኑን ታውቃለህ፥ በኋላ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባህር ዳር ሆነው መግለጫ ሰጡ በሚል የሴራ ተንታኔ ተቀይሯል፡፡
👉 እንደዚህ ያለ ከእውነት የተፋታ፤ ለዛሬም ለነገም የማይበጅ፤ የሚሸነገል የሚዋሽ ነገር ጥፋት ብቻ ነው የሚያመጣው፡፡
👉 ክስተቱ እንደ ጥቁር ጠባሳ የሚወሰድ መጥፎ ክስተት ነው፡፡
በአቤል ነዋይ
9 days ago
#ቤተልሔም_ሸረፈዲን - " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ ያላት "
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
9 days ago
ካሜራ አንግተው በሜዳ የሚውሉት የሀገር ፕሬዚዳንት
#ethiopia | የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፔትር ፓቬል ለየት ያለ የዕረፍት ጊዜ የማሳለፋቸው ነገር የብዙዎችን ቀልብ ስበው ከረሙ።
ፕሬዚዳንቱ የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት በተለመዱት ብዙ ጠባቂዎች በተሰበሰቡበት ስፍራዎች ወይም በቅጡ በተዘጋጁ የመዝናኛ ቦታዎች ሳይሆን በሃንጋሪ ግራንድ ፕሪ የፎርሙላ 1 ውድድር ላይ በይፋዊ የፎቶግራፍ ጋዜጠኝነት ስራ ላይ በመሰማራት ነው።
ለሞተር ስፖርት ውድድሮች ካላቸው ጥልቅ ፍቅርና ዝንባሌ የተነሳ ፕሬዚዳንት ፓቬል ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ሕጋዊ የሜዲያ ፈቃድ በማውጣት በውድድሩ ስፍራ እንደ ማንኛውም ሙያተኛ ካሜራቸውን አንግበው ሲሰሩ ይታያሉ።
ከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን ማዕረግ ቢኖራቸውም የሚወዱትን ስፖርት በቅርበት ለመከታተልና የፎቶግራፍ ጥበብ ፍላጎታቸውን ለማርካት ያሳዩት ትህትና በብዙዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፎላቸዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፔትር ፓቬል ለየት ያለ የዕረፍት ጊዜ የማሳለፋቸው ነገር የብዙዎችን ቀልብ ስበው ከረሙ።
ፕሬዚዳንቱ የእረፍት ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት በተለመዱት ብዙ ጠባቂዎች በተሰበሰቡበት ስፍራዎች ወይም በቅጡ በተዘጋጁ የመዝናኛ ቦታዎች ሳይሆን በሃንጋሪ ግራንድ ፕሪ የፎርሙላ 1 ውድድር ላይ በይፋዊ የፎቶግራፍ ጋዜጠኝነት ስራ ላይ በመሰማራት ነው።
ለሞተር ስፖርት ውድድሮች ካላቸው ጥልቅ ፍቅርና ዝንባሌ የተነሳ ፕሬዚዳንት ፓቬል ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ ሕጋዊ የሜዲያ ፈቃድ በማውጣት በውድድሩ ስፍራ እንደ ማንኛውም ሙያተኛ ካሜራቸውን አንግበው ሲሰሩ ይታያሉ።
ከፍተኛ የመንግሥት የሥልጣን ማዕረግ ቢኖራቸውም የሚወዱትን ስፖርት በቅርበት ለመከታተልና የፎቶግራፍ ጥበብ ፍላጎታቸውን ለማርካት ያሳዩት ትህትና በብዙዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፎላቸዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
10 days ago
በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተሳተፉ ያሉ ተመካካሪዎች ምን አሉ?
******************
✅ሰፊ እና ያልተገደበ አካታችነት፦ ውይይቱ የታጠቁ የፖለቲካ ኃይሎችን፣ ባለሥልጣናትን፣ ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ የሃይማኖት አባቶችን እና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያሳተፈ ከመሆኑም በላይ ሁሉም በእኩል ደረጃ የሚወያዩበት መድረክ ነው።
✅ከታች ወደ ላይ (Bottom-Up) የመጣ የአጀንዳ ቀረጻ፦ ውይይት እየተደረገባቸው ያሉት ስምንት አጀንዳዎች የግለሰቦች ሳይሆኑ ከመሰረታዊው ኅብረተሰብ የተሰበሰቡ እና ተጨምቀው የቀረቡ ናቸው፤ እንዲሁም ውይይቱ ፍሬያማ እንዲሆን እስከ አስር አባላት ባሏቸው ትንንሽ ቡድኖች ተከፋፍሎ እየተካሄደ ነው።
✅ የስሜት ተጋሪነት (በሌላው ጫማ ውስጥ ሆኖ ማሰብ)፦ ተሳታፊዎች ከራሳቸው ሰፈር እና አካባቢ ወጥተው የሰሜኑን በደቡብ፣ የደቡቡን በምሥራቅ ችግር ለመረዳት እና የሌላውን ስጋት፣ ፍላጎት እና ባህል በራሳቸው ጫማ ውስጥ ሆነው ለመመልከት ዝንባሌ እያሳዩ ነው።
✅ሀገር በቀል ዕውቀትን እና ውይይትን እንደ ሥልጣኔ መጠቀም፦ እንደ ከዚህ ቀደም ከሩቅ ሆኖ ከመወጋገዝ ይልቅ በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ የሌላውን ስጋት መረዳት ያስፈልጋል፤ ለዘመናት ለነበሩ ቁርሾዎች ነባር ሀገር በቀል ዕውቀቶችን መፍትሔ አድርጎ መጠቀም ለችግሮቻችን ፍቱን መድኃኒት ነው።
✅ከግል እና ከቡድን ፍላጎት ይልቅ ሀገርን ማስቀደም፦ ተሳታፊዎች የነበሯቸውን የፖለቲካ፣ የሃይማኖት እና የግል ጥቅሞች ወደ ጎን በመተው ለቀጣዩ ትውልድ የሚጠቅም መልካም ታሪክ ለማስቀመጥ እና ሀገርን ለማስቀደም እየተወያዩ ነው።
✅ሙሉ የሃሳብ ነፃነት እና የውጫዊ ተጽዕኖ አለመኖር፦ ውይይቱ ያለ ምንም ስጋት፣ ፍርሃት እና ውጫዊ ግፊት የሚካሄድ ነው፤ ተመካካሪዎች የወከሏቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ድምጽ በነፃነት የሚያሰሙበት መድረክም ነው።
✅ከተቀመጡ አጀንዳዎች በላይ የሆኑ መፍትሔዎችን ማመንጨት፦ ከተሰጡት ስምንት አጀንዳዎች ውጭ ተሳታፊዎች ትልልቅ ሀገራዊ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመንጨት በመቻላቸው፣ ሂደቱ ለአፍሪካ እና ለቀሪው ዓለም ተምሳሌት የሚሆን ልምድ እየፈጠረ ነው።
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #ebc
******************
✅ሰፊ እና ያልተገደበ አካታችነት፦ ውይይቱ የታጠቁ የፖለቲካ ኃይሎችን፣ ባለሥልጣናትን፣ ሴቶችን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ የሃይማኖት አባቶችን እና የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያሳተፈ ከመሆኑም በላይ ሁሉም በእኩል ደረጃ የሚወያዩበት መድረክ ነው።
✅ከታች ወደ ላይ (Bottom-Up) የመጣ የአጀንዳ ቀረጻ፦ ውይይት እየተደረገባቸው ያሉት ስምንት አጀንዳዎች የግለሰቦች ሳይሆኑ ከመሰረታዊው ኅብረተሰብ የተሰበሰቡ እና ተጨምቀው የቀረቡ ናቸው፤ እንዲሁም ውይይቱ ፍሬያማ እንዲሆን እስከ አስር አባላት ባሏቸው ትንንሽ ቡድኖች ተከፋፍሎ እየተካሄደ ነው።
✅ የስሜት ተጋሪነት (በሌላው ጫማ ውስጥ ሆኖ ማሰብ)፦ ተሳታፊዎች ከራሳቸው ሰፈር እና አካባቢ ወጥተው የሰሜኑን በደቡብ፣ የደቡቡን በምሥራቅ ችግር ለመረዳት እና የሌላውን ስጋት፣ ፍላጎት እና ባህል በራሳቸው ጫማ ውስጥ ሆነው ለመመልከት ዝንባሌ እያሳዩ ነው።
✅ሀገር በቀል ዕውቀትን እና ውይይትን እንደ ሥልጣኔ መጠቀም፦ እንደ ከዚህ ቀደም ከሩቅ ሆኖ ከመወጋገዝ ይልቅ በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ የሌላውን ስጋት መረዳት ያስፈልጋል፤ ለዘመናት ለነበሩ ቁርሾዎች ነባር ሀገር በቀል ዕውቀቶችን መፍትሔ አድርጎ መጠቀም ለችግሮቻችን ፍቱን መድኃኒት ነው።
✅ከግል እና ከቡድን ፍላጎት ይልቅ ሀገርን ማስቀደም፦ ተሳታፊዎች የነበሯቸውን የፖለቲካ፣ የሃይማኖት እና የግል ጥቅሞች ወደ ጎን በመተው ለቀጣዩ ትውልድ የሚጠቅም መልካም ታሪክ ለማስቀመጥ እና ሀገርን ለማስቀደም እየተወያዩ ነው።
✅ሙሉ የሃሳብ ነፃነት እና የውጫዊ ተጽዕኖ አለመኖር፦ ውይይቱ ያለ ምንም ስጋት፣ ፍርሃት እና ውጫዊ ግፊት የሚካሄድ ነው፤ ተመካካሪዎች የወከሏቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ድምጽ በነፃነት የሚያሰሙበት መድረክም ነው።
✅ከተቀመጡ አጀንዳዎች በላይ የሆኑ መፍትሔዎችን ማመንጨት፦ ከተሰጡት ስምንት አጀንዳዎች ውጭ ተሳታፊዎች ትልልቅ ሀገራዊ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመንጨት በመቻላቸው፣ ሂደቱ ለአፍሪካ እና ለቀሪው ዓለም ተምሳሌት የሚሆን ልምድ እየፈጠረ ነው።
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #ebc
19 days ago
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አዲስ የቱሪዝም ካርታ በጥበብ እየሳለች ነው
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ባህል) የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 ዓ.ም የ"አምባሳደር አሸንዳ" ማዕረግ ተሸላሚ የነበረችውን ወጣት ዜማ እምብዛን ከክብር ማዕረጓ ማንሳቱን ያስታወቀበት ይፋዊ መግለጫ፣ በባህል ልማት ስም የሚንቀሳቀሱ የመንግሥት ተቋማትን ሚና እና የአስተሳሰብ አድማስ በድጋሚ በትዝብት መድረክ ላይ የሚጥል ሆኗል። ቢሮው ውሳኔውን ያስተላለፈው ወጣቷ «አሸንዳ ኢትዮጵያ» በሚል መጠሪያ ባህሉን ለማስተዋወቅ መሞከሯን እንደ ትልቅ ወንጀልና የሕዝብን እሴት የመጣስ ተግባር ቆጥሮት ነው። ይህ እርምጃ ባህላዊ ቅርሶችን ከማሳደግና ዓለም አቀፋዊ አድማሳቸውን ከማስፋት ይልቅ፣ ጥበብንና ባህልን በፖለቲካዊ ቅጥሮች ውስጥ የመሸበብ አደገኛ ዝንባሌ ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል።
አሸንዳ ዕድሜ ጠገብ የሆነ፣ የማንነት፣ የነጻነትና የሴቶች ክብር መገለጫ የሆነ እምቅ የሕዝብ ቅርስ ነው። እንዲህ ዓይነቱን ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ የማስተዋወቅ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም፣ ዋና ዓላማው ቅርሱ ከክልላዊ ወሰን አልፎ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝ፣ አልፎ ተርፎም በዩኔስኮ (UNESCO) የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ እንዲመዘገብ መሥራት መሆን ነበረበት። ሆኖም ግን፣ወጣቷ አምባሳደር የቅርሱን አድማስ ለማስፋት እና ከሌሎች ወገኖች ጋር ድልድይ ለመፍጠር «ኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በማካተቷ ብቻ ማዕረጓን መንጠቅ፣ ከተቋማዊ ራዕይ ማነስ እና ባህልን የፖለቲካ ፍጆታ ከማድረግ የሚመነጭ እጅግ ጠባብ አካሄድ ነው።
የባህልና ቱሪዝም ቢሮው በመግለጫው ላይ ወጣቷን «የሕዝቡን ባህላዊ እሴቶች የማይወክል ተግባር ፈጽማለች» ሲል ቢከስም... በተግባር ግን ራሱ ቢሮው የትኛውን ባህላዊ እሴት እየጠበቀ እንደሆነ ግልጽ አይደለም። ባህል የሰዎች መገናኛ፣ የፍቅርና የሰላም መድረክ እንጂ ሰዎችን ማግለያና መቅጫ መሣሪያ አይደለም። ወጣት ዜማ እምብዛ ለአሸንዳ በዓል ሰፊ ዕውቅና ለመስጠት ያሳየችውን ተነሳሽነት በበጎነት ከመደገፍና ይበልጥ ውጤታማ እንድትሆን ከመምራት ይልቅ፣ እንደ ፖለቲካ ወንጀለኛ ቆጥሮ በይፋ ማዋረድና ማዕረግ መንሳት፣ በክልሉ ጥበብና ባህል ላይ የተጣለ ትልቅ ጥላሸት ነው።
ይህ ክስተት የሚያሳየው ትልቁ እውነት፣ የታሪክና የባህል ተቋማት ከዘመኑ የፖለቲካ ውጥረት እና ከልሂቃኑ መከፋፈል ራሳቸውን ማላቀቅ አለመቻላቸውን ነው። የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ይህንን መሰል የተሳሳተ ውሳኔ በማሳለፍ... አሸንዳን ለዓለም ከማስተዋወቅ ይልቅ በጠበበ የፖለቲካ አጥር ውስጥ መልሶ አግቷታል። ተቋማት የሕዝብን ውብ ባህል ወደ ኋላ ከመጎተት እና በወጣቶች የፈጠራ አቅም ላይ ሳንሱር ከመጣል ተቆጥበው፣ ጥበብ ያለ አንዳች የድንበር ገደብ እንድታብብ የነጻነት አየር ሊፈጥሩላት ይገባል የሚለው የብዙኃኑ ጥያቄና የዚህ ክስተት ዋነኛ ማሳያ ነው።
አሸንዳ ዕድሜ ጠገብ የሆነ፣ የማንነት፣ የነጻነትና የሴቶች ክብር መገለጫ የሆነ እምቅ የሕዝብ ቅርስ ነው። እንዲህ ዓይነቱን ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ የማስተዋወቅ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም፣ ዋና ዓላማው ቅርሱ ከክልላዊ ወሰን አልፎ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኝ፣ አልፎ ተርፎም በዩኔስኮ (UNESCO) የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ እንዲመዘገብ መሥራት መሆን ነበረበት። ሆኖም ግን፣ወጣቷ አምባሳደር የቅርሱን አድማስ ለማስፋት እና ከሌሎች ወገኖች ጋር ድልድይ ለመፍጠር «ኢትዮጵያ» የሚለውን ስም በማካተቷ ብቻ ማዕረጓን መንጠቅ፣ ከተቋማዊ ራዕይ ማነስ እና ባህልን የፖለቲካ ፍጆታ ከማድረግ የሚመነጭ እጅግ ጠባብ አካሄድ ነው።
የባህልና ቱሪዝም ቢሮው በመግለጫው ላይ ወጣቷን «የሕዝቡን ባህላዊ እሴቶች የማይወክል ተግባር ፈጽማለች» ሲል ቢከስም... በተግባር ግን ራሱ ቢሮው የትኛውን ባህላዊ እሴት እየጠበቀ እንደሆነ ግልጽ አይደለም። ባህል የሰዎች መገናኛ፣ የፍቅርና የሰላም መድረክ እንጂ ሰዎችን ማግለያና መቅጫ መሣሪያ አይደለም። ወጣት ዜማ እምብዛ ለአሸንዳ በዓል ሰፊ ዕውቅና ለመስጠት ያሳየችውን ተነሳሽነት በበጎነት ከመደገፍና ይበልጥ ውጤታማ እንድትሆን ከመምራት ይልቅ፣ እንደ ፖለቲካ ወንጀለኛ ቆጥሮ በይፋ ማዋረድና ማዕረግ መንሳት፣ በክልሉ ጥበብና ባህል ላይ የተጣለ ትልቅ ጥላሸት ነው።
ይህ ክስተት የሚያሳየው ትልቁ እውነት፣ የታሪክና የባህል ተቋማት ከዘመኑ የፖለቲካ ውጥረት እና ከልሂቃኑ መከፋፈል ራሳቸውን ማላቀቅ አለመቻላቸውን ነው። የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ይህንን መሰል የተሳሳተ ውሳኔ በማሳለፍ... አሸንዳን ለዓለም ከማስተዋወቅ ይልቅ በጠበበ የፖለቲካ አጥር ውስጥ መልሶ አግቷታል። ተቋማት የሕዝብን ውብ ባህል ወደ ኋላ ከመጎተት እና በወጣቶች የፈጠራ አቅም ላይ ሳንሱር ከመጣል ተቆጥበው፣ ጥበብ ያለ አንዳች የድንበር ገደብ እንድታብብ የነጻነት አየር ሊፈጥሩላት ይገባል የሚለው የብዙኃኑ ጥያቄና የዚህ ክስተት ዋነኛ ማሳያ ነው።
Sponsored by
Surafel
21 days ago
አምባሳደሩ ጀኔራሉን እንዳያገኙ ተከለከሉ ‼️
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በትናንትናው የመቀሌ ጉዟቸው ለውይይት ቀጥረዋቸው የነበሩትን አመራሮች ሳያገኙ መመለሳቸውን ተሰምቷል፡፡
አምባሳደሩ በህወሓት እና በፌደራል መንግሥት የተፈጠረውን ውጥርት ለማርገብ፣ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በቻርተር አውሮፕላን ልዑካቸውን አስክትለው ወደ መቀሌ ተጉዘዋል፡፡
ማሲንጋ ወደ መቀሌ ያቀኑትን፣ በዋናነት የህወሓቱን ሊቀመንብረ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን እና ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደን ለማነጋገር ነበር ተብሏል፡፡
ማሲንጋ የተወያዩት ከህወሓቱ ምክትል ሊቀመንብር አማኑኤል አሰፋ እና አምባሳደር አዲስአለም ባሌማ ጋር ነው፡፡
ማሲንጋ መቀሌ ከደረሱ በኋላ የተቀበሏቸውና ለውይይት የተቀመጡት ከእነዚሁ ሁለት አመራሮች ጋር ነው፡፡
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሰው ሥልጣን የተቆጣጠሩት፣ የህወሓቱ ሊቀመንብር ደብረጽዮን “መቀሌ ውስጥ የሉም” በሚል ምክንያት ከአምባሳደሩ ጋር አልተገናኙም ተብሏል፡፡
የአሜሪካ ልዑክ የመቀሌ ጉዞ በኃይል ሥልጣናቸውን የተቀሙትን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰን ማግኘት አልቻሉም ተብሏል፡፡
ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ ከአደባባይ እይታ የጠፉት ጀነራል ታደሰ አምባሳደሩን እንዳያገኙ በህወሓት የጸጥታ አመራሮች “የደህንነት ስጋት” በሚል እንደከለከላቸው ተሰምቷል፡፡
አምባሳደሩ ጀነራል ታደሰ ወረደን እንዳያገኙ መከልከ የቀድሞ አለቃቸው ጌታቸው ረዳ በፌስቡክ ገጻቸው ጽፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ በትናንትናው የመቀሌ ጉዟቸው ለውይይት ቀጥረዋቸው የነበሩትን አመራሮች ሳያገኙ መመለሳቸውን ተሰምቷል፡፡
አምባሳደሩ በህወሓት እና በፌደራል መንግሥት የተፈጠረውን ውጥርት ለማርገብ፣ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በቻርተር አውሮፕላን ልዑካቸውን አስክትለው ወደ መቀሌ ተጉዘዋል፡፡
ማሲንጋ ወደ መቀሌ ያቀኑትን፣ በዋናነት የህወሓቱን ሊቀመንብረ ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን እና ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደን ለማነጋገር ነበር ተብሏል፡፡
ማሲንጋ የተወያዩት ከህወሓቱ ምክትል ሊቀመንብር አማኑኤል አሰፋ እና አምባሳደር አዲስአለም ባሌማ ጋር ነው፡፡
ማሲንጋ መቀሌ ከደረሱ በኋላ የተቀበሏቸውና ለውይይት የተቀመጡት ከእነዚሁ ሁለት አመራሮች ጋር ነው፡፡
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሰው ሥልጣን የተቆጣጠሩት፣ የህወሓቱ ሊቀመንብር ደብረጽዮን “መቀሌ ውስጥ የሉም” በሚል ምክንያት ከአምባሳደሩ ጋር አልተገናኙም ተብሏል፡፡
የአሜሪካ ልዑክ የመቀሌ ጉዞ በኃይል ሥልጣናቸውን የተቀሙትን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕረዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰን ማግኘት አልቻሉም ተብሏል፡፡
ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ ከአደባባይ እይታ የጠፉት ጀነራል ታደሰ አምባሳደሩን እንዳያገኙ በህወሓት የጸጥታ አመራሮች “የደህንነት ስጋት” በሚል እንደከለከላቸው ተሰምቷል፡፡
አምባሳደሩ ጀነራል ታደሰ ወረደን እንዳያገኙ መከልከ የቀድሞ አለቃቸው ጌታቸው ረዳ በፌስቡክ ገጻቸው ጽፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
22 days ago
ወልቂጤ : የመሐመድ ናስር ታሎር (MNT) የታዳጊዎች እግር ኳስ አካዳሚ
#ethiopia | ወልቂጤ — በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የሚገኘው የ"መሐመድ ናስር ታሎር" (MNT) የታዳጊዎች እግር ኳስ አካዳሚ የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ረገድ ተስፋ ሰጪና ለሌሎችም ተሞክሮ የሚሆን አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰይፈ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ የሚገኙ የስፖርት ሥልጠና ፕሮጀክቶችን በአካል ተገኝተው ጎብኝተዋል።
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ንቅናቄና የተተኪዎች ሥልጠና*
የቢሮ ምክትል ኃላፊው አቶ ሰይፈ ዓለሙ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በክረምት ወቅት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም የቴክኒክ ቡድን ተቋቁሞ በሁሉም ዞኖች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ የታጀቡ ሥራዎችን የማስጀመር ተግባር እየተከናወነ ይገኛል።
በክረምት ወቅት ታዳጊዎች አልባሌ ቦታ እንዳይውሉ በማድረግ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲያሳልፉ ማድረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት ኃላፊው፤ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናው የተጠበቀ አምራች ዜጋ ለመፍጠር በሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ሰፊ የንቅናቄ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የሰርከስ ሰልጣኞችን እየመለመለ እንደሚገኝና በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን የሰርከስ ቡድን በአንድ የስልጠና ማዕከል ሰብስቦ ሥራ ለማስጀመር ማቀዱን አስታውቀዋል።
በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ምልከታ ቡድኑ እጅግ መደሰቱን የገለጹት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም በእግር ኳስ በየዕድሜ ክልሉ የሚሰጠው ሥልጠና ጠንካራና የአሰልጣኞችን ቁርጠኝነት በተጨባጭ ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማው የሚገኘው የMNT እግር ኳስ አካዳሚ በተተኪ ታዳጊዎች ላይ እየሠራ ያለው ሥራ ለሀገርና ለክልሉ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፣ በዞኑ የሚገኙ ባለሀብቶች ይህንን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የማኅበረሰብ ድጋፍ**
የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አደም ሽኩር በበኩላቸው፤ በዘንድሮው ክረምት ወጣቶችን በማስተባበር ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
ወጣቶችና ታዳጊዎች በአካባቢ ጽዳት፣ በችግኝ ተከላ፣ በኪነ-ጥበብ እና በስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሳተፉ እየተደረገ ከመሆኑም በላይ፤ አቅመ-ደካሞችን የመደገፍና አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ደብተር የማሰባሰብ ሥራዎች በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ስለ መሐመድ ናስር ታሎር (MNT) አካዳሚ
የአካዳሚው አሰልጣኝና ሥራ አስኪያጅ አብድልህኒ ተሰማ እንደገለጹት፤ አካዳሚው በአሜሪካ ሀገር በሚኖረውና የከተማው ተወላጅ በሆነው በአቶ መሐመድ ናስር የተመሠረተ ነው።
ከተመሠረተ አምስት ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ አካዳሚ፦
* ከ6 እስከ 18 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ታዳጊዎችን ያቅፋል።
* በአሁኑ ወቅት ከ400 በላይ ታዳጊ ስፖርተኞችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የጉራጌ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን
#ethiopia | ወልቂጤ — በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የሚገኘው የ"መሐመድ ናስር ታሎር" (MNT) የታዳጊዎች እግር ኳስ አካዳሚ የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ረገድ ተስፋ ሰጪና ለሌሎችም ተሞክሮ የሚሆን አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ።
የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሰይፈ ዓለሙን ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በወልቂጤ ከተማ የሚገኙ የስፖርት ሥልጠና ፕሮጀክቶችን በአካል ተገኝተው ጎብኝተዋል።
የክረምት ወቅት ስፖርታዊ ንቅናቄና የተተኪዎች ሥልጠና*
የቢሮ ምክትል ኃላፊው አቶ ሰይፈ ዓለሙ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት፤ በክልሉ በክረምት ወቅት ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ያሉበትን ሁኔታ ለመገምገም የቴክኒክ ቡድን ተቋቁሞ በሁሉም ዞኖች በአካል ብቃት እንቅስቃሴ የታጀቡ ሥራዎችን የማስጀመር ተግባር እየተከናወነ ይገኛል።
በክረምት ወቅት ታዳጊዎች አልባሌ ቦታ እንዳይውሉ በማድረግ በበጎ ፈቃድ አገልግሎትና በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እንዲያሳልፉ ማድረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት ኃላፊው፤ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ጤናው የተጠበቀ አምራች ዜጋ ለመፍጠር በሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ሰፊ የንቅናቄ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የሰርከስ ሰልጣኞችን እየመለመለ እንደሚገኝና በ2019 በጀት ዓመት የክልሉን የሰርከስ ቡድን በአንድ የስልጠና ማዕከል ሰብስቦ ሥራ ለማስጀመር ማቀዱን አስታውቀዋል።
በወልቂጤ ከተማ በተደረገው ምልከታ ቡድኑ እጅግ መደሰቱን የገለጹት አቶ ሰይፈ፤ በተለይም በእግር ኳስ በየዕድሜ ክልሉ የሚሰጠው ሥልጠና ጠንካራና የአሰልጣኞችን ቁርጠኝነት በተጨባጭ ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።
በከተማው የሚገኘው የMNT እግር ኳስ አካዳሚ በተተኪ ታዳጊዎች ላይ እየሠራ ያለው ሥራ ለሀገርና ለክልሉ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን ጠቁመው፣ በዞኑ የሚገኙ ባለሀብቶች ይህንን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎትና የማኅበረሰብ ድጋፍ**
የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ምክትልና የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አደም ሽኩር በበኩላቸው፤ በዘንድሮው ክረምት ወጣቶችን በማስተባበር ማኅበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ልዩ ልዩ የበጎ ፈቃድ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
ወጣቶችና ታዳጊዎች በአካባቢ ጽዳት፣ በችግኝ ተከላ፣ በኪነ-ጥበብ እና በስፖርታዊ ውድድሮች እንዲሳተፉ እየተደረገ ከመሆኑም በላይ፤ አቅመ-ደካሞችን የመደገፍና አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ደብተር የማሰባሰብ ሥራዎች በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ስለ መሐመድ ናስር ታሎር (MNT) አካዳሚ
የአካዳሚው አሰልጣኝና ሥራ አስኪያጅ አብድልህኒ ተሰማ እንደገለጹት፤ አካዳሚው በአሜሪካ ሀገር በሚኖረውና የከተማው ተወላጅ በሆነው በአቶ መሐመድ ናስር የተመሠረተ ነው።
ከተመሠረተ አምስት ዓመታትን ያስቆጠረው ይህ አካዳሚ፦
* ከ6 እስከ 18 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ታዳጊዎችን ያቅፋል።
* በአሁኑ ወቅት ከ400 በላይ ታዳጊ ስፖርተኞችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል።
የጉራጌ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን
29 days ago
''የውቦች ንግስት''
በምህረት
#Ethiopia | ምህረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች።
ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሐገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
በምህረት
#Ethiopia | ምህረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች።
ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሐገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ 2026 ሩት ይርጋለም ወደ ሮቤ ከተማ አቀናች
#ethiopia | ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ 2026 እና የባህልና ጥበባት አምባሳደር ሩት ይርጋለም የባህል፣ የጥበብና የታሪክ ጉብኝቷን በመቀጠል ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ ተገኝታለች።
ሩት ይርጋለም ከዚህ ቀደም በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ያደረገችውን ጉብኝት ካጠናቀቀች በኋላ ወደ ባሌ ዞን በማቅናት የአካባቢውን ባህላዊ እሴቶች፣ የጥበብ ቅርሶች እና ታሪካዊ መስህቦች ለመጎብኘት ፕሮግራም ጀምራለች።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ጉብኝቱ አምባሳደሯ ስለ ኢትዮጵያ ባህል፣ ጥበብና ታሪክ ተጨባጭ ግንዛቤ እንድታገኝ እንዲሁም የሀገሪቱን ባህላዊ እሴቶች በዓለም አቀፍ መድረኮች በተሻለ ሁኔታ እንድታስተዋውቅ ያግዛል።
አምባሳደር ሩት ይርጋለም በዋቆ ጉቱ አየር ማረፊያ ስትደርስ በሀዳ ሲንቄዎች፣ በባሌ ዞን ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት አመራሮች እና በዞኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል።
#ethiopia | ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ 2026 እና የባህልና ጥበባት አምባሳደር ሩት ይርጋለም የባህል፣ የጥበብና የታሪክ ጉብኝቷን በመቀጠል ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ ተገኝታለች።
ሩት ይርጋለም ከዚህ ቀደም በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ያደረገችውን ጉብኝት ካጠናቀቀች በኋላ ወደ ባሌ ዞን በማቅናት የአካባቢውን ባህላዊ እሴቶች፣ የጥበብ ቅርሶች እና ታሪካዊ መስህቦች ለመጎብኘት ፕሮግራም ጀምራለች።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ጉብኝቱ አምባሳደሯ ስለ ኢትዮጵያ ባህል፣ ጥበብና ታሪክ ተጨባጭ ግንዛቤ እንድታገኝ እንዲሁም የሀገሪቱን ባህላዊ እሴቶች በዓለም አቀፍ መድረኮች በተሻለ ሁኔታ እንድታስተዋውቅ ያግዛል።
አምባሳደር ሩት ይርጋለም በዋቆ ጉቱ አየር ማረፊያ ስትደርስ በሀዳ ሲንቄዎች፣ በባሌ ዞን ባህልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት አመራሮች እና በዞኑ ከፍተኛ ኃላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል።
1 month ago
የመደመር አንቀጽ
“እሳት አመድን ወለደ" የሚለው ሀገርኛ ብሂል፤ ነባሩ ትውልድ አዲሱን ትውልድ ለመውቀስ የሚጠቀምበት የተለመደ አገላለጽ ነው።
በትውልድ መካከል ካለው ልዩነት የተነሳ፤ ነባሩ ትውልድ የአዲሱን ትውልድ ባሕርይና ዐሻራ ለመቀበል የሚቸገርበት ሁኔታ ውስጥ ሲገባ፤ ወይም ከአዲሱ ትውልድ ጋር በቀላሉ መላመድ ሲቸገር፤ አዲሱን ትውልድ መተቸቱ የሚጠበቅ ነው።
በአዲሱም ትውልድ ዘንድ በአንድ በኩል የቀደመውን ትውልድ ሥራዎችና ዐሻራዎች የማናናቅና ኋላ ቀር አድርጎ የመውሰድ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የቀደመውን ትውልድ ሥራዎች አግንኖና የማይለወጡ አድርጎ የማየት ወይም ያልኖረውን ያለፈ ሕይወት የመናፈቅ፤ ዝንባሌዎች ይስተዋላሉ።
የትውልድ ዐሻራዎችን፣ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በልካቸው ተመልክቶ፤ ከእያንዳንዱ ትውልድ ተገቢውን ትምህርት መቅሰም፤ አስፈላጊና ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው።
ይኸንን ለማድረግ ዋናው ፈታኝ ጉዳይ ደግሞ፤ ነገረ ትውልድ ከታሪክ አጠናንና አረዳድ ጋር የተቆራኘ መሆኑ ነው።
የታሪክ ጥራት የሚወሰነው ደግሞ ከሠሪው ማንነት ይልቅ፤ በተራኪው ሙያዊ ብቃትና የተረክ አመክንዮ ላይ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ 28
Ethiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #ትውልድ
“እሳት አመድን ወለደ" የሚለው ሀገርኛ ብሂል፤ ነባሩ ትውልድ አዲሱን ትውልድ ለመውቀስ የሚጠቀምበት የተለመደ አገላለጽ ነው።
በትውልድ መካከል ካለው ልዩነት የተነሳ፤ ነባሩ ትውልድ የአዲሱን ትውልድ ባሕርይና ዐሻራ ለመቀበል የሚቸገርበት ሁኔታ ውስጥ ሲገባ፤ ወይም ከአዲሱ ትውልድ ጋር በቀላሉ መላመድ ሲቸገር፤ አዲሱን ትውልድ መተቸቱ የሚጠበቅ ነው።
በአዲሱም ትውልድ ዘንድ በአንድ በኩል የቀደመውን ትውልድ ሥራዎችና ዐሻራዎች የማናናቅና ኋላ ቀር አድርጎ የመውሰድ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የቀደመውን ትውልድ ሥራዎች አግንኖና የማይለወጡ አድርጎ የማየት ወይም ያልኖረውን ያለፈ ሕይወት የመናፈቅ፤ ዝንባሌዎች ይስተዋላሉ።
የትውልድ ዐሻራዎችን፣ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በልካቸው ተመልክቶ፤ ከእያንዳንዱ ትውልድ ተገቢውን ትምህርት መቅሰም፤ አስፈላጊና ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው።
ይኸንን ለማድረግ ዋናው ፈታኝ ጉዳይ ደግሞ፤ ነገረ ትውልድ ከታሪክ አጠናንና አረዳድ ጋር የተቆራኘ መሆኑ ነው።
የታሪክ ጥራት የሚወሰነው ደግሞ ከሠሪው ማንነት ይልቅ፤ በተራኪው ሙያዊ ብቃትና የተረክ አመክንዮ ላይ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ 28
Ethiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #ትውልድ
Sponsored by
Surafel
1 month ago
“ኢትዮጵያ አንድ ቪዛ ብቻ ወስደው መላውን ዓለም የሚያዩባት ድንቅ ሀገር ናት” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
❣️ ኑሮቤ ሆቴል – የምቾትና የጥራት አዲሱ መዳረሻ
#ethiopia | በባሌ ሮቤ ከተማ ልዩ የመስተንግዶ ልምድ የሚያገኙበት ኑሮቤ ሆቴል በዘመናዊ አገልግሎቶቹ እንግዶቹን በክብር ለመቀበል ዝግጁ ነው።
✨ የምናቀርብልዎት
✅ ዘመናዊና ምቹ የመኝታ ክፍሎች
✅ የተሟላ የባርና ሬስቶራንት አገልግሎት
✅ ዘመናዊ የስብሰባ፣ የሴሚናርና የስልጠና አዳራሾች
✅ ልምድ ባላቸው ሼፎች የሚዘጋጁ ጣፋጭ ምግቦች
✅ ሰፊና አስተማማኝ የመኪና ማቆሚያ
✅ ፈጣንና ተገቢ የእንግዳ አገልግሎት
ከዋቆ ጉቱ አየር ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘው ኑሮቤ ሆቴል፣ ወደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና ሌሎች የተፈጥሮ መስህቦች ለሚጓዙ እንግዶች ተመራጭ ማረፊያ ነው።
📍 አድራሻ፦ ባሌ ሮቤ፣ ቦሌ ቶኩማ ቀበሌ
📞 ስልክ፦ +251 911 819 959
🌟 ኑሮቤ ሆቴል
“ምቾት፣ ጥራት እና እንግዳ ተቀባይነት በአንድ ስፍራ”
#ethiopia | በባሌ ሮቤ ከተማ ልዩ የመስተንግዶ ልምድ የሚያገኙበት ኑሮቤ ሆቴል በዘመናዊ አገልግሎቶቹ እንግዶቹን በክብር ለመቀበል ዝግጁ ነው።
✨ የምናቀርብልዎት
✅ ዘመናዊና ምቹ የመኝታ ክፍሎች
✅ የተሟላ የባርና ሬስቶራንት አገልግሎት
✅ ዘመናዊ የስብሰባ፣ የሴሚናርና የስልጠና አዳራሾች
✅ ልምድ ባላቸው ሼፎች የሚዘጋጁ ጣፋጭ ምግቦች
✅ ሰፊና አስተማማኝ የመኪና ማቆሚያ
✅ ፈጣንና ተገቢ የእንግዳ አገልግሎት
ከዋቆ ጉቱ አየር ማረፊያ አቅራቢያ የሚገኘው ኑሮቤ ሆቴል፣ ወደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክና ሌሎች የተፈጥሮ መስህቦች ለሚጓዙ እንግዶች ተመራጭ ማረፊያ ነው።
📍 አድራሻ፦ ባሌ ሮቤ፣ ቦሌ ቶኩማ ቀበሌ
📞 ስልክ፦ +251 911 819 959
🌟 ኑሮቤ ሆቴል
“ምቾት፣ ጥራት እና እንግዳ ተቀባይነት በአንድ ስፍራ”
1 month ago
የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ
#ethiopia | ባሌ፣ ሮቤ - የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገለጹ።
በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል አበይት ርዕስ ሚኒስትሩ “የመዳረሻ ልማት ብሔራዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ንግግር፣ መዳረሻዎች የቱሪዝም መስህቦች ብቻ ሳይሆኑ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የኢንቨስትመንት ማዕከላት፣ የማህበራዊ ለውጥ መድረኮች እና የብሔራዊ ማንነት መገለጫዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞቿ ውስጥ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ መሠረተ ልማትን ለማዘመን እና ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር እየሰራች ሲሆን፣ የመዳረሻ ልማት እነዚህን ግቦች በተግባር የሚያሳካ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሶፍ ኦማር ዋሻዎች፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ ዋንጪ፣ ሐረር፣ ሐዋሳ ሐይቅ፣ ጣና ሐይቅ፣ ገራልታ እና አርባምንጭን ጨምሮ የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ጎብኚዎችን፣ ባለሀብቶችን፣ ተመራማሪዎችን እና ፈጣሪዎችን ከዓለም ዙሪያ ለመሳብ ትልቅ አቅም እንዳላቸውም ተናግረዋል።
ዶ/ር አብርሃም የመዳረሻ ልማት በትራንስፖርት፣ ሎጂስቲክስ፣ ግብርና፣ ሪል እስቴት፣ መስተንግዶ እና አገልግሎት ዘርፎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን እንደሚያነቃቃ ገልጸው፣ በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትስስር እና መሠረተ ልማት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች የቱሪዝም፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሪል እስቴት ዕድሎችን እንደሚያሰፉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች እና የአካባቢ ማህበረሰቦች በመዳረሻ ልማት ዘርፍ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበው፣ የኢትዮጵያ መዳረሻዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የኢንቨስትመንትና የፈጠራ ማዕከላት ማድረግ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
#ethiopia #destinationdevelopment #tourism #investment #economicgrowth #getutemesgen #ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
#ethiopia | ባሌ፣ ሮቤ - የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ የመዳረሻ ልማት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሽግግር፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ማሳደግ ወሳኝ ሚና እንዳለው ገለጹ።
በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል አበይት ርዕስ ሚኒስትሩ “የመዳረሻ ልማት ብሔራዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ንግግር፣ መዳረሻዎች የቱሪዝም መስህቦች ብቻ ሳይሆኑ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የኢንቨስትመንት ማዕከላት፣ የማህበራዊ ለውጥ መድረኮች እና የብሔራዊ ማንነት መገለጫዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
እንደ ዶ/ር አብርሃም ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሞቿ ውስጥ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ፣ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ መሠረተ ልማትን ለማዘመን እና ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር እየሰራች ሲሆን፣ የመዳረሻ ልማት እነዚህን ግቦች በተግባር የሚያሳካ ስትራቴጂ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሶፍ ኦማር ዋሻዎች፣ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ ዋንጪ፣ ሐረር፣ ሐዋሳ ሐይቅ፣ ጣና ሐይቅ፣ ገራልታ እና አርባምንጭን ጨምሮ የኢትዮጵያ መዳረሻዎች ጎብኚዎችን፣ ባለሀብቶችን፣ ተመራማሪዎችን እና ፈጣሪዎችን ከዓለም ዙሪያ ለመሳብ ትልቅ አቅም እንዳላቸውም ተናግረዋል።
ዶ/ር አብርሃም የመዳረሻ ልማት በትራንስፖርት፣ ሎጂስቲክስ፣ ግብርና፣ ሪል እስቴት፣ መስተንግዶ እና አገልግሎት ዘርፎች የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን እንደሚያነቃቃ ገልጸው፣ በተለይም ለወጣቶችና ለሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር አስታውቀዋል።
በተጨማሪም የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በትስስር እና መሠረተ ልማት ላይ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶች የቱሪዝም፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሪል እስቴት ዕድሎችን እንደሚያሰፉ ገልጸዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ ባለሀብቶች እና የአካባቢ ማህበረሰቦች በመዳረሻ ልማት ዘርፍ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበው፣ የኢትዮጵያ መዳረሻዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የኢንቨስትመንትና የፈጠራ ማዕከላት ማድረግ እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
#ethiopia #destinationdevelopment #tourism #investment #economicgrowth #getutemesgen #ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
2 months ago
ኢትዮጵያ በ2030 በኃላፊነት በተመራ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ተቋማዊ ብቃቷን ማጠናከር አለባት ተባለ
ሮቤ፣ ባሌ – ሰኔ 15፣ 2018 ዓ.ም.
#ethiopia | ኢትዮጵያ በ2030 የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባሻገር ጠንካራ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ብቃት እና የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ላይ ማተኮር እንዳለባት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ገለጹ።
ዶ/ር አብዮት ይህን ያሉት በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ቁልፍ ንግግር ነው።
እንደ አማካሪው ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ሽግግር ጉዞዋ ከዜሮ እየተነሳች አይደለችም። ባለፉት ሰባት ዓመታት በቴሌኮም ሪፎርም፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በዲጂታል መታወቂያ፣ በክፍያ ሥርዓቶችና በመንግሥት አገልግሎቶች ዘርፍ ጉልህ እድገቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. የተጀመረው “Digital Ethiopia 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ሁሉም ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ እኩል ዕድል እንዲያገኙ እና የዲጂታል አገልግሎቶች በእምነትና በደህንነት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል።
ዶ/ር አብዮት እንዳሉት፣ የቱሪዝም ዘርፉ ከዲጂታል ለውጥ በፍጥነት ተጠቃሚ ሊሆን ከሚችሉ ዘርፎች አንዱ ሲሆን፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተደገፉ የቱሪዝም መድረኮች፣ የዲጂታል ትኬትና ክፍያ ሥርዓቶች፣ የጎብኚዎች ፍሰት ትንተና እና የተቀናጀ የቱሪዝም መረጃ ሥርዓት ለዘርፉ አዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።
በንግግራቸው የ“MESOB” የተባለውን የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት መድረክ በአርአያነት ያነሱት አማካሪው፣ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን እንደ አንድ የጉዞ ልምድ እንጂ እንደ ተለያዩ ተቋማት እንደማያዩ ገልጸው፣ የቱሪዝም መረጃ፣ የሆቴል አገልግሎቶች፣ የመጓጓዣ አማራጮች፣ የክፍያ ሥርዓቶችና የደህንነት መረጃዎች በአንድ የተቀናጀ ሥርዓት መሰጠት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ለዚህም የቴክኖሎጂ፣ የሂደት እና የሰው ኃይል ሦስት ዋና ምሰሶዎች በአንድነት መሠራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ብሮድባንድ ግንኙነት፣ ዲጂታል መድረኮች፣ የመረጃ አስተዳደር፣ የAI ሥነ-ምግባር መመሪያዎች እና የሰው ኃይል ብቃት በጋራ ሲጠናከሩ ብቻ ዘላቂ ለውጥ እንደሚመጣ አስገንዝበዋል።
አማካሪው ኢትዮጵያ በ“5 Million Ethiopian Coders” መርሃ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በኮዲንግ፣ በዳታ ትንተናና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ክህሎቶች ማሠልጠን መቻሏ ለዘርፉ ጠንካራ የሰው ኃይል መሠረት እየፈጠረች መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ በ2030 የኢትዮጵያ ስኬት የሚለካው በተጠቀመችባቸው የAI መሣሪያዎች ብዛት ሳይሆን በዩኒቨርሲቲዎች የተሻሻሉ ሥርዓተ ትምህርቶች፣ በተቋማት የመረጃ ጥራት፣ በዲጂታል ብቃት፣ በግላዊነት ጥበቃ እና በሕዝብ እምነት ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኮንፈረንሱ በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚያመጣውን ዕድልና ተግዳሮት መወያየት ቀጥሏል።
#ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
ሮቤ፣ ባሌ – ሰኔ 15፣ 2018 ዓ.ም.
#ethiopia | ኢትዮጵያ በ2030 የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባሻገር ጠንካራ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ብቃት እና የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ላይ ማተኮር እንዳለባት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ገለጹ።
ዶ/ር አብዮት ይህን ያሉት በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ቁልፍ ንግግር ነው።
እንደ አማካሪው ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ሽግግር ጉዞዋ ከዜሮ እየተነሳች አይደለችም። ባለፉት ሰባት ዓመታት በቴሌኮም ሪፎርም፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በዲጂታል መታወቂያ፣ በክፍያ ሥርዓቶችና በመንግሥት አገልግሎቶች ዘርፍ ጉልህ እድገቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. የተጀመረው “Digital Ethiopia 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ሁሉም ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ እኩል ዕድል እንዲያገኙ እና የዲጂታል አገልግሎቶች በእምነትና በደህንነት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል።
ዶ/ር አብዮት እንዳሉት፣ የቱሪዝም ዘርፉ ከዲጂታል ለውጥ በፍጥነት ተጠቃሚ ሊሆን ከሚችሉ ዘርፎች አንዱ ሲሆን፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተደገፉ የቱሪዝም መድረኮች፣ የዲጂታል ትኬትና ክፍያ ሥርዓቶች፣ የጎብኚዎች ፍሰት ትንተና እና የተቀናጀ የቱሪዝም መረጃ ሥርዓት ለዘርፉ አዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።
በንግግራቸው የ“MESOB” የተባለውን የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት መድረክ በአርአያነት ያነሱት አማካሪው፣ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን እንደ አንድ የጉዞ ልምድ እንጂ እንደ ተለያዩ ተቋማት እንደማያዩ ገልጸው፣ የቱሪዝም መረጃ፣ የሆቴል አገልግሎቶች፣ የመጓጓዣ አማራጮች፣ የክፍያ ሥርዓቶችና የደህንነት መረጃዎች በአንድ የተቀናጀ ሥርዓት መሰጠት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ለዚህም የቴክኖሎጂ፣ የሂደት እና የሰው ኃይል ሦስት ዋና ምሰሶዎች በአንድነት መሠራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ብሮድባንድ ግንኙነት፣ ዲጂታል መድረኮች፣ የመረጃ አስተዳደር፣ የAI ሥነ-ምግባር መመሪያዎች እና የሰው ኃይል ብቃት በጋራ ሲጠናከሩ ብቻ ዘላቂ ለውጥ እንደሚመጣ አስገንዝበዋል።
አማካሪው ኢትዮጵያ በ“5 Million Ethiopian Coders” መርሃ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በኮዲንግ፣ በዳታ ትንተናና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ክህሎቶች ማሠልጠን መቻሏ ለዘርፉ ጠንካራ የሰው ኃይል መሠረት እየፈጠረች መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ በ2030 የኢትዮጵያ ስኬት የሚለካው በተጠቀመችባቸው የAI መሣሪያዎች ብዛት ሳይሆን በዩኒቨርሲቲዎች የተሻሻሉ ሥርዓተ ትምህርቶች፣ በተቋማት የመረጃ ጥራት፣ በዲጂታል ብቃት፣ በግላዊነት ጥበቃ እና በሕዝብ እምነት ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኮንፈረንሱ በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚያመጣውን ዕድልና ተግዳሮት መወያየት ቀጥሏል።
#ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
2 months ago
2ኛ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በባሌ ተከፈተ
#ethiopia | ባሌ ሮቤ— በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ - የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ትምህርትን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ( AI ) በአዲስ እሳቤ ማላቅ - ( የወደፊት ክህሎቶችን፣ የፈጠራ አቅምንና እና ሥነ ምግባራዊ ሰው - ተኮር አሰራርን ማጎልበት ) ” በሚል መሪ ሃሳብ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ ተናጋሪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራን እና ተሳታፊዎች በተገኙበት ሁለተኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።
የኮንፈረንሱ አስተናጋጅ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና (PhD) የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የምንኖርበት ዘመን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በማሽን ትምህርት (Machine Learning) እና በአውቶሜሽን ምክንያት ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየታየበት ያለና የሆስፒታሊቲውን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ እየቀየረው የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
የኮንፈረንሱ አስተናጋጅ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና (PhD) የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የምንኖርበት ዘመን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በማሽን ትምህርት (Machine Learning) እና በአውቶሜሽን ምክንያት ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየታየበት ያለና የሆስፒታሊቲውን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ እየቀየረው የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና አያይዘውም፣ ቴክኖሎጂው ሰብአዊ እሴቶችን፣ የሰዎችን ግላዊነት፣ ፍትሃዊነትንና ባህልን በጠበቀ መልኩ ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበትና ተማሪዎችንም ለነገው ያልተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች በዲጂታል ክህሎትና በሰብአዊ እሴቶች ማነጽ እንደሚገባ አፅንዖት ሰጥተዋል።
የባሌን ምድር አንድ ፓርክ፣ ብዙ ዓለማት" ሲሉ የገለጹት ዶ/ር ብርሃነመስቀል፣ እንደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ የቱሉ ዲምቱ ጫፍ እና የዲሬ ሸኽ ሁሴን መካነ መቃብር ያሉ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋዎች መገኛ የሆነው ይህ ቀጠና ለዩኒቨርሲቲው ትልቅ ሕያው የመማሪያ ክፍል መሆኑንና የዩኒቨርሲቲውም ስኬት የሚለካው በምርምር ወረቀቶች ብቻ ሳይሆን በማኅበረሰቡ ውስጥ በሚያመጣው እውነተኛ ለውጥ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከዚሁ የኮንፈረንስ መክፈቻ ጎን ለጎን፣ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) የመጡ የባለሙያዎች ቡድን በቅርብ ትብብር ያበለጸገውንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀውን አዲሱን የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ (Website) በይፋ መርቋል።
ይህ አዲስ ዲጂታል መድረክ ዩኒቨርሲቲው በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተደራሽነትና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር የሽርክና ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ምክትል አምባሳደር ክቡር አምባሳደር ሌሊሳ ጫላ እና አቶ ሙሉጌታ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እና መሪነት ፕሬዝዳንቱ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ የባለሙያዎቹ ቡድንና ጥሪ የተደረገላቸው ክብራን እንግዶች መድረክ ላይ በመውጣት ድረ-ገጹን በጋራ እንድሚርቁ አድርገዋል።
በመጨረሻም፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ ለሁለት ቀናት የሚቆየውን ይህንን ሁለተኛውን ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በይፋ የከፈቱ ሲሆን፣ በቆይታውም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች በመጡ ምሁራን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ከቱሪዝም ልማት ጋር ያገናዘቡ በርካታ የምርምር ሥራዎችና ውይይቶች እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።
በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር እና የዕለቱ ቁልፍ ተናጋሪ ክቡር ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የቱሪዝም ስቴት ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር እንደገና አበበ፣ የባሌ ዞን አስተዳደር ዋና አዛዥ ክቡር አቶ አብዱልሀኪም አሊዪ እና የባሌ-ሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ዲኖ አሚን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ከአውሮፓ፣ ከእስያ፣ ከአፍሪካና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተውጣጡ በርካታ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ የዘርፉ የልማት አጋሮች እና ስፖንሰሮች በአካልና በበይነ-መረብ (ኦንላይን) በጋራ እየታደሙ ናቸው።
#maddawalabuuniversity #ai #tourism #hospitality #conference #robe #ethiopianews #education #innovation #mwu
#ethiopia | ባሌ ሮቤ— በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ - የቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ትምህርትን በሰው ሰራሽ አስተውሎት ( AI ) በአዲስ እሳቤ ማላቅ - ( የወደፊት ክህሎቶችን፣ የፈጠራ አቅምንና እና ሥነ ምግባራዊ ሰው - ተኮር አሰራርን ማጎልበት ) ” በሚል መሪ ሃሳብ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ ተናጋሪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራን እና ተሳታፊዎች በተገኙበት ሁለተኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።
የኮንፈረንሱ አስተናጋጅ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና (PhD) የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የምንኖርበት ዘመን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በማሽን ትምህርት (Machine Learning) እና በአውቶሜሽን ምክንያት ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየታየበት ያለና የሆስፒታሊቲውን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ እየቀየረው የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
የኮንፈረንሱ አስተናጋጅ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና (PhD) የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም የምንኖርበት ዘመን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በማሽን ትምህርት (Machine Learning) እና በአውቶሜሽን ምክንያት ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ሽግግር እየታየበት ያለና የሆስፒታሊቲውን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ እየቀየረው የሚገኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃነመስቀል ጠና አያይዘውም፣ ቴክኖሎጂው ሰብአዊ እሴቶችን፣ የሰዎችን ግላዊነት፣ ፍትሃዊነትንና ባህልን በጠበቀ መልኩ ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበትና ተማሪዎችንም ለነገው ያልተፈጠሩ የሥራ ዕድሎች በዲጂታል ክህሎትና በሰብአዊ እሴቶች ማነጽ እንደሚገባ አፅንዖት ሰጥተዋል።
የባሌን ምድር አንድ ፓርክ፣ ብዙ ዓለማት" ሲሉ የገለጹት ዶ/ር ብርሃነመስቀል፣ እንደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ፣ የሶፍ ዑመር ዋሻ፣ የቱሉ ዲምቱ ጫፍ እና የዲሬ ሸኽ ሁሴን መካነ መቃብር ያሉ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋዎች መገኛ የሆነው ይህ ቀጠና ለዩኒቨርሲቲው ትልቅ ሕያው የመማሪያ ክፍል መሆኑንና የዩኒቨርሲቲውም ስኬት የሚለካው በምርምር ወረቀቶች ብቻ ሳይሆን በማኅበረሰቡ ውስጥ በሚያመጣው እውነተኛ ለውጥ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከዚሁ የኮንፈረንስ መክፈቻ ጎን ለጎን፣ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) የመጡ የባለሙያዎች ቡድን በቅርብ ትብብር ያበለጸገውንና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀውን አዲሱን የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ (Website) በይፋ መርቋል።
ይህ አዲስ ዲጂታል መድረክ ዩኒቨርሲቲው በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ተደራሽነትና የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር የሽርክና ውጤት መሆኑ ተገልጿል።
ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ ምክትል አምባሳደር ክቡር አምባሳደር ሌሊሳ ጫላ እና አቶ ሙሉጌታ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እና መሪነት ፕሬዝዳንቱ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ የባለሙያዎቹ ቡድንና ጥሪ የተደረገላቸው ክብራን እንግዶች መድረክ ላይ በመውጣት ድረ-ገጹን በጋራ እንድሚርቁ አድርገዋል።
በመጨረሻም፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ ለሁለት ቀናት የሚቆየውን ይህንን ሁለተኛውን ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ በይፋ የከፈቱ ሲሆን፣ በቆይታውም ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች በመጡ ምሁራን አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን ከቱሪዝም ልማት ጋር ያገናዘቡ በርካታ የምርምር ሥራዎችና ውይይቶች እንደሚቀርቡ ይጠበቃል።
በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እና የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላ፣ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር እና የዕለቱ ቁልፍ ተናጋሪ ክቡር ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ የቱሪዝም ስቴት ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር እንደገና አበበ፣ የባሌ ዞን አስተዳደር ዋና አዛዥ ክቡር አቶ አብዱልሀኪም አሊዪ እና የባሌ-ሮቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ዲኖ አሚን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ከአውሮፓ፣ ከእስያ፣ ከአፍሪካና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተውጣጡ በርካታ ምሁራን፣ ተመራማሪዎች፣ የዘርፉ የልማት አጋሮች እና ስፖንሰሮች በአካልና በበይነ-መረብ (ኦንላይን) በጋራ እየታደሙ ናቸው።
#maddawalabuuniversity #ai #tourism #hospitality #conference #robe #ethiopianews #education #innovation #mwu
2 months ago
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና ቱሪዝም ዙሪያ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ሊያካሂድ ነው
#ethiopia | ሮቤ – በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘው መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሚናን የሚመለከት ሁለተኛውን ዙር ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ከሰኔ 15 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚያካሂድ ዶ/ር ተሰማ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አስታውቋል።
“Reimagining Tourism and Hospitality Education through Artificial Intelligence: Building Future-Ready Skills, Innovation Capacity, and Ethical Human-Centered Practice” በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ኮንፍረንስ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ ቁልፍ ተናጋሪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራን እና ተሳታፊዎችን ያሳትፋል።
እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ኢንዶኔዢያ፣ ሩሲያ፣ ካሜሩን እና ሌሎች ሀገራት ተሳታፊዎች እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ደግሞ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ከመንግስት ተቋማት እና ከቱሪዝም ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች ይሳተፋሉ።
በኮንፍረንሱ ወቅት ዘመናዊ የምረቃ አዳራሽ ምረቃ፣ በውጭ አጋሮች ድጋፍ የተገነባ አዲስ የዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ (Website) ምረቃ እና ሌሎች ተቋማዊ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑም ተጠቁሟል።
ከ430 ኪሎ ሜትር በላይ ከአዲስ አበባ ርቀት ላይ የሚገኘው መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ1999 ዓ.ም. የተመሰረተ ሲሆን በሮቤ፣ ጎባ እና ሻሸመኔ ካምፓሶች በመዋቀር 52 የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 58 የማስተርስ እና 6 የዶክትሬት መርሃ ግብሮችን እያስተማረ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ከ46 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በማስመረቅ ለአገሪቱ ልማት አስተዋፅኦ እያደረገ ሲሆን በትምህርት፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ያለውን ሚና እያጠናከረ መሆኑን ገልጿል።
የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ኮንፍረንሱን በአካል ወይም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮቹ እንዲከታተሉ ለምሁራን፣ ለተማሪዎች እና ለህዝብ ዶ/ር ተሰማ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ ጥሪ አቅርበዋል።
#maddawalabuuniversity #ai #tourism #hospitality #conference #robe #ethiopianews #education #innovation #mwu
#ethiopia | ሮቤ – በኦሮሚያ ክልል ባሌ ዞን ሮቤ ከተማ የሚገኘው መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሚናን የሚመለከት ሁለተኛውን ዙር ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ከሰኔ 15 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚያካሂድ ዶ/ር ተሰማ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አስታውቋል።
“Reimagining Tourism and Hospitality Education through Artificial Intelligence: Building Future-Ready Skills, Innovation Capacity, and Ethical Human-Centered Practice” በሚል መሪ ሃሳብ የሚካሄደው ኮንፍረንስ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የመጡ ቁልፍ ተናጋሪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ምሁራን እና ተሳታፊዎችን ያሳትፋል።
እንግሊዝ፣ ጣሊያን፣ ኢንዶኔዢያ፣ ሩሲያ፣ ካሜሩን እና ሌሎች ሀገራት ተሳታፊዎች እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ ደግሞ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች፣ ከመንግስት ተቋማት እና ከቱሪዝም ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች ይሳተፋሉ።
በኮንፍረንሱ ወቅት ዘመናዊ የምረቃ አዳራሽ ምረቃ፣ በውጭ አጋሮች ድጋፍ የተገነባ አዲስ የዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ (Website) ምረቃ እና ሌሎች ተቋማዊ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑም ተጠቁሟል።
ከ430 ኪሎ ሜትር በላይ ከአዲስ አበባ ርቀት ላይ የሚገኘው መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በ1999 ዓ.ም. የተመሰረተ ሲሆን በሮቤ፣ ጎባ እና ሻሸመኔ ካምፓሶች በመዋቀር 52 የመጀመሪያ ዲግሪ፣ 58 የማስተርስ እና 6 የዶክትሬት መርሃ ግብሮችን እያስተማረ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ከ46 ሺህ በላይ ተማሪዎችን በማስመረቅ ለአገሪቱ ልማት አስተዋፅኦ እያደረገ ሲሆን በትምህርት፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ያለውን ሚና እያጠናከረ መሆኑን ገልጿል።
የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ኮንፍረንሱን በአካል ወይም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮቹ እንዲከታተሉ ለምሁራን፣ ለተማሪዎች እና ለህዝብ ዶ/ር ተሰማ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)
የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ ጥሪ አቅርበዋል።
#maddawalabuuniversity #ai #tourism #hospitality #conference #robe #ethiopianews #education #innovation #mwu
2 months ago
የሰው ፂም የሚመስል የተፈጥሮ ፀጉር ያላት ድመት በኢንተርኔት ዓለም መነጋገሪያ ሆነች!
ምንም ዓይነት ሰው ሰራሽ ቅብ፣ የፀጉር ማስተካከል ወይም የፎቶ ማጭበርበር ሳይደረግባት፣ በትክክል የሰውን ወፍራም ጥቁር ፂም የሚመስል የተፈጥሮ ፀጉር ይዛ የተወለደች ድመት በመላው ዓለም በሚገኙ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ መደነቅን ፈጥራለች። ይህ በድመቷ አገጭ ላይ የሚታየው "ፂም" ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊ ሲሆን፣ ድመቷ እያደገች ስትሄድ በጄኔቲክስ ምክንያት የተፈጠረ ልዩ የቆዳ ቀለም መዋቅር ውጤት ነው።
ድመቶች በጄኔቲክስ ስብጥር ምክንያት እንደ ፂም፣ ቅንድብ፣ ልብ ቅርጽ፣ ጭምብል እና የሰውን የፊት ገጽታ የሚመስሉ አስደናቂ የተፈጥሮ ምልክቶችን በፀጉራቸው ላይ ይዘው ሊወለዱ ይችላሉ። የዚህች ድመት ፂም ግን እጅግ ማራኪ እና የተለየ ያደረገው፣ ልክ እንደ ሰው ልጅ ፂም ግራና ቀኙ እኩል ተስተካክሎ እና በትክክል መሆን ባለበት ቦታ ላይ ተፈጥሮ ያቀለመችው በመሆኑ ነው።
የዚህ ዓይነቱ ድመት ፎቶዎች በኢንተርኔት ላይ በፍጥነት ታዋቂ የሚሆኑት ፓሬዶሊያ (Pareidolia) በሚባለው የስነ-ልቦናዊ ክስተት ምክንያት ነው። የሰው ልጅ አእምሮ በማንኛውም ነገር ላይ የሰውን መልክ ወይም የታወቁ ቅርጾችን ፈጥኖ የመለየት ተፈጥሯዊ ዝንባሌ ስላለው፣ ድመቷን ስንመለከት አእምሯችን ወዲያውኑ ከሰው ፂም ጋር በማገናኘት ነገሩን እጅግ አስቂኝ እና የማይረሳ ያደርገዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ምንም ዓይነት ሰው ሰራሽ ቅብ፣ የፀጉር ማስተካከል ወይም የፎቶ ማጭበርበር ሳይደረግባት፣ በትክክል የሰውን ወፍራም ጥቁር ፂም የሚመስል የተፈጥሮ ፀጉር ይዛ የተወለደች ድመት በመላው ዓለም በሚገኙ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ መደነቅን ፈጥራለች። ይህ በድመቷ አገጭ ላይ የሚታየው "ፂም" ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊ ሲሆን፣ ድመቷ እያደገች ስትሄድ በጄኔቲክስ ምክንያት የተፈጠረ ልዩ የቆዳ ቀለም መዋቅር ውጤት ነው።
ድመቶች በጄኔቲክስ ስብጥር ምክንያት እንደ ፂም፣ ቅንድብ፣ ልብ ቅርጽ፣ ጭምብል እና የሰውን የፊት ገጽታ የሚመስሉ አስደናቂ የተፈጥሮ ምልክቶችን በፀጉራቸው ላይ ይዘው ሊወለዱ ይችላሉ። የዚህች ድመት ፂም ግን እጅግ ማራኪ እና የተለየ ያደረገው፣ ልክ እንደ ሰው ልጅ ፂም ግራና ቀኙ እኩል ተስተካክሎ እና በትክክል መሆን ባለበት ቦታ ላይ ተፈጥሮ ያቀለመችው በመሆኑ ነው።
የዚህ ዓይነቱ ድመት ፎቶዎች በኢንተርኔት ላይ በፍጥነት ታዋቂ የሚሆኑት ፓሬዶሊያ (Pareidolia) በሚባለው የስነ-ልቦናዊ ክስተት ምክንያት ነው። የሰው ልጅ አእምሮ በማንኛውም ነገር ላይ የሰውን መልክ ወይም የታወቁ ቅርጾችን ፈጥኖ የመለየት ተፈጥሯዊ ዝንባሌ ስላለው፣ ድመቷን ስንመለከት አእምሯችን ወዲያውኑ ከሰው ፂም ጋር በማገናኘት ነገሩን እጅግ አስቂኝ እና የማይረሳ ያደርገዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የመደመር አንቀጽ
አክራሪነት የሰማይን ዳርቻ ፍለጋ የሚደረግ ከንቱ ግሥጋሴ ነው። ሰማይን ስንመለከተው ከተራራው ወይም ከሩቅ ከሚታየው አንድ የተፈጥሮ ወይም ሰው ሠራሽ ነገር ጀርባ የተሸሸገ ጥግ ያለው ይመስለናል።
ነገር ግን ከአድማስ ጥጉ ለመድረስ እስከ ተራራው ጫፍ ብንጓዝም፤ ከሩቅ የሚታይ ሌላ የሰማዩ ዳር የሚመስል አዲስ አድማስ እናገኛለን። ከቀጣዩ አድማስ ጥግ ደርሰን ብንመለከትም ሰማይ ከምድር የተሰፋበት የሚመስል ሌላ ነገር ከሩቅ ይጠብቀናል፡፡
በዘመናዊቱ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ጉዞ ውስጥ፤ አክራሪነት ዓይነተኛ ኃይል ሆኖ ትውልዶችን የመፍጠርና የመቅረጽ ከፍተኛ ሚናው ቀጥሏል። አክራሪነት የአንድ ሐሳብ የመጨረሻ ጥግን መፈለግ ነው። አንዱ ዳር ሲደርሱ ሐሳብን እየለጠጡ ሌላ ጫፍ የመፈለግ።
የማያባራ የአንድ ጽንፍ ፍለጋ ጉዞ። ይህም አንድን ጥግ የመፈለግ ወይም ውል የሌለው ልዩነትን የመለጠጥ የማያባራ ጉዞ፤ በትብብርና በፉክክር መካከል ሚዛን የመሳት ውጤት ነው።
በአንድ በኩል ከእኔ ጋር ብቻ ተሰለፉ የሚል አላስፈላጊ ልሙጥ የሆነ ትብብር ፍለጋ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ እኔ ወይ አንተ ብቻ ትክክል ነን፤ የሚል የተወጠረ ፉክክርመልክ አለው፡፡ አክራሪነት “እኔን ምሰል” የሚል ጠቅላይነት እና “አትመስለኝም” የሚል አግላይነት ያቀፉት፤ ከራሱ የተጣላ የአስተሳሰብ ዝንባሌ ነው፡፡
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 53
አክራሪነት የሰማይን ዳርቻ ፍለጋ የሚደረግ ከንቱ ግሥጋሴ ነው። ሰማይን ስንመለከተው ከተራራው ወይም ከሩቅ ከሚታየው አንድ የተፈጥሮ ወይም ሰው ሠራሽ ነገር ጀርባ የተሸሸገ ጥግ ያለው ይመስለናል።
ነገር ግን ከአድማስ ጥጉ ለመድረስ እስከ ተራራው ጫፍ ብንጓዝም፤ ከሩቅ የሚታይ ሌላ የሰማዩ ዳር የሚመስል አዲስ አድማስ እናገኛለን። ከቀጣዩ አድማስ ጥግ ደርሰን ብንመለከትም ሰማይ ከምድር የተሰፋበት የሚመስል ሌላ ነገር ከሩቅ ይጠብቀናል፡፡
በዘመናዊቱ ኢትዮጵያ ሀገራዊ ጉዞ ውስጥ፤ አክራሪነት ዓይነተኛ ኃይል ሆኖ ትውልዶችን የመፍጠርና የመቅረጽ ከፍተኛ ሚናው ቀጥሏል። አክራሪነት የአንድ ሐሳብ የመጨረሻ ጥግን መፈለግ ነው። አንዱ ዳር ሲደርሱ ሐሳብን እየለጠጡ ሌላ ጫፍ የመፈለግ።
የማያባራ የአንድ ጽንፍ ፍለጋ ጉዞ። ይህም አንድን ጥግ የመፈለግ ወይም ውል የሌለው ልዩነትን የመለጠጥ የማያባራ ጉዞ፤ በትብብርና በፉክክር መካከል ሚዛን የመሳት ውጤት ነው።
በአንድ በኩል ከእኔ ጋር ብቻ ተሰለፉ የሚል አላስፈላጊ ልሙጥ የሆነ ትብብር ፍለጋ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ እኔ ወይ አንተ ብቻ ትክክል ነን፤ የሚል የተወጠረ ፉክክርመልክ አለው፡፡ አክራሪነት “እኔን ምሰል” የሚል ጠቅላይነት እና “አትመስለኝም” የሚል አግላይነት ያቀፉት፤ ከራሱ የተጣላ የአስተሳሰብ ዝንባሌ ነው፡፡
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 53
2 months ago
ከተግባር ከፍታ ወደ ብሔራዊ ጽናት - የኢትዮጵያ የሜጋ ፕሮጀክቶች የስኬት ዐሻራ
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
2 months ago
የመደመር አንቀጽ
“እሳት አመድን ወለደ" የሚለው ሀገርኛ ብሂል፤ ነባሩ ትውልድ አዲሱን ትውልድ ለመውቀስ የሚጠቀምበት የተለመደ አገላለጽ ነው። በትውልድ መካከል ካለው ልዩነት የተነሳ፤ ነባሩ ትውልድ የአዲሱን ትውልድ ባሕርይና ዐሻራ ለመቀበል የሚቸገርበት ሁኔታ ውስጥ ሲገባ፤ ወይም ከአዲሱ ትውልድ ጋር በቀላሉ መላመድ ሲቸገር፤ አዲሱን ትውልድ መተቸቱ የሚጠበቅ ነው።
በአዲሱም ትውልድ ዘንድ በአንድ በኩል የቀደመውን ትውልድ ሥራዎችና ዐሻራዎች የማናናቅና ኋላ ቀር አድርጎ የመውሰድ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የቀደመውን ትውልድ ሥራዎች አግንኖና የማይለወጡ አድርጎ የማየት ወይም ያልኖረውን ያለፈ ሕይወት የመናፈቅ፤ ዝንባሌዎች ይስተዋላሉ።
የትውልድ ዐሻራዎችን፣ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በልካቸው ተመልክቶ፤ ከእያንዳንዱ ትውልድ ተገቢውን ትምህርት መቅሰም፤ አስፈላጊና ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው። ይኸንን ለማድረግ ዋናው ፈታኝ ጉዳይ ደግሞ፤ ነገረ ትውልድ ከታሪክ አጠናንና አረዳድ ጋር የተቆራኘ መሆኑ ነው። የታሪክ ጥራት የሚወሰነው ደግሞ ከሠሪው ማንነት ይልቅ፤ በተራኪው ሙያዊ ብቃትና የተረክ አመክንዮ ላይ ነው፡፡
የመደመር ትውልድ
ገጽ 28
eEthiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #ትውልድ
“እሳት አመድን ወለደ" የሚለው ሀገርኛ ብሂል፤ ነባሩ ትውልድ አዲሱን ትውልድ ለመውቀስ የሚጠቀምበት የተለመደ አገላለጽ ነው። በትውልድ መካከል ካለው ልዩነት የተነሳ፤ ነባሩ ትውልድ የአዲሱን ትውልድ ባሕርይና ዐሻራ ለመቀበል የሚቸገርበት ሁኔታ ውስጥ ሲገባ፤ ወይም ከአዲሱ ትውልድ ጋር በቀላሉ መላመድ ሲቸገር፤ አዲሱን ትውልድ መተቸቱ የሚጠበቅ ነው።
በአዲሱም ትውልድ ዘንድ በአንድ በኩል የቀደመውን ትውልድ ሥራዎችና ዐሻራዎች የማናናቅና ኋላ ቀር አድርጎ የመውሰድ፤ በሌላ በኩል ደግሞ የቀደመውን ትውልድ ሥራዎች አግንኖና የማይለወጡ አድርጎ የማየት ወይም ያልኖረውን ያለፈ ሕይወት የመናፈቅ፤ ዝንባሌዎች ይስተዋላሉ።
የትውልድ ዐሻራዎችን፣ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን በልካቸው ተመልክቶ፤ ከእያንዳንዱ ትውልድ ተገቢውን ትምህርት መቅሰም፤ አስፈላጊና ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው። ይኸንን ለማድረግ ዋናው ፈታኝ ጉዳይ ደግሞ፤ ነገረ ትውልድ ከታሪክ አጠናንና አረዳድ ጋር የተቆራኘ መሆኑ ነው። የታሪክ ጥራት የሚወሰነው ደግሞ ከሠሪው ማንነት ይልቅ፤ በተራኪው ሙያዊ ብቃትና የተረክ አመክንዮ ላይ ነው፡፡
የመደመር ትውልድ
ገጽ 28
eEthiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #ትውልድ
2 months ago
ምሕረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች። ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
2 months ago
ብሪክስ 50% የሚሆነውን የዓለም ዕድገት መሸፈኑ ጅማሮ ነው - ባለሙያ
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ሁሉም ነገር ሲፈራርስ!
#ethiopia ሁሉም ነገር እየፈራረሰ ሲመስል፣ የወደፊት ሕይወቴም አብሮ ከሽፏል ብሎ መደምደም ቀላል ነው። ነገር ግን የከሸፈ ሙከራ፣ የከሸፈ ፕሮጀክት፣ የፈረሰ ግንኙነት ወይም የከሸፈ እቅድ ማለት ወዲያውኑ የከሸፈ ሕይወት ይሰጠናል ማለት አይደለም።
የአለምን ታሪክ መለስ ብለን ብንመለከት የማይሰሩና የተበላሹ በርካታ አማራጮችን አሟጠው ከሞከሩ በኋላ አለቀ ሲሉ እንደገና ተነስተው ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን እናገኛለን፡፡
እነዚህ ሰዎች . . .
1. ማንነታቸውንና ውጤታቸውን አያነካኩም
አንድ ነገራቸው ወደቀ ማለት እነሱ ውዳቂ እንዳልሆኑ ያምናሉ፡፡ ስለዚህ ማንነታቸውን በስኬታማነታቸው አይመዝኑትም፡፡
2. ውድቀትን ወደ ትምህርት ይቀይሩታል
ውድቀት ዋጋ የሚኖረው አንድ ነገር ሲያስተምራቸው ብቻ እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ ልምምዳቸው ይማራሉ፡፡
3. ራሳቸውንና እቅዶቻቸውን ሰብሰብ ያደርጋሉ
ነገሮች ሲበላሹ፣ በአንድ ጊዜ ሁሉንም የወደፊት ሕይወታቸውን መስመር ለማስያዝ መሞከር አደገኛ እንደሆነ ስለሚያውቁ በቅርብ ርቀት ላይ ባለው ነገር ላይ ያተኩራሉ፡፡
4. በስሜት ከማሰብ ይጠነቀቃሉ
ሰዎች ሲደክሙ ወይም ተስፋ ሲቆርጡ፣ ስሜታቸውን እንደ እውነት የመውሰድ ዝንባሌ እንዳላቸው ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ስሜታቸውን በመግራት በምክንያታዊነት ያስባሉ፡፡
5. መቆጣጠር በሚችሉት ነገር ላይ ብቻ ያተኩራሉ
ብዙ ውድቀቶች ሰዎችን የሚያደናግጧቸው ከአቅማቸው በላይ በሆኑ ነገሮች ላይ ሙሉ በሙሉ ስሚያተኩሩ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ከእነሱ የቁጥር ቀጠና ውጪ የሆነውን በጸሎት ለፈጣሪ በመተው እነሱ ማድረግ የሚችሉት ላይ ያተኩራ፡፡
እኛም የእነሱን ምሳሌ እንከተል!
Dr eyob mamo
#ethiopia ሁሉም ነገር እየፈራረሰ ሲመስል፣ የወደፊት ሕይወቴም አብሮ ከሽፏል ብሎ መደምደም ቀላል ነው። ነገር ግን የከሸፈ ሙከራ፣ የከሸፈ ፕሮጀክት፣ የፈረሰ ግንኙነት ወይም የከሸፈ እቅድ ማለት ወዲያውኑ የከሸፈ ሕይወት ይሰጠናል ማለት አይደለም።
የአለምን ታሪክ መለስ ብለን ብንመለከት የማይሰሩና የተበላሹ በርካታ አማራጮችን አሟጠው ከሞከሩ በኋላ አለቀ ሲሉ እንደገና ተነስተው ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን እናገኛለን፡፡
እነዚህ ሰዎች . . .
1. ማንነታቸውንና ውጤታቸውን አያነካኩም
አንድ ነገራቸው ወደቀ ማለት እነሱ ውዳቂ እንዳልሆኑ ያምናሉ፡፡ ስለዚህ ማንነታቸውን በስኬታማነታቸው አይመዝኑትም፡፡
2. ውድቀትን ወደ ትምህርት ይቀይሩታል
ውድቀት ዋጋ የሚኖረው አንድ ነገር ሲያስተምራቸው ብቻ እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ ልምምዳቸው ይማራሉ፡፡
3. ራሳቸውንና እቅዶቻቸውን ሰብሰብ ያደርጋሉ
ነገሮች ሲበላሹ፣ በአንድ ጊዜ ሁሉንም የወደፊት ሕይወታቸውን መስመር ለማስያዝ መሞከር አደገኛ እንደሆነ ስለሚያውቁ በቅርብ ርቀት ላይ ባለው ነገር ላይ ያተኩራሉ፡፡
4. በስሜት ከማሰብ ይጠነቀቃሉ
ሰዎች ሲደክሙ ወይም ተስፋ ሲቆርጡ፣ ስሜታቸውን እንደ እውነት የመውሰድ ዝንባሌ እንዳላቸው ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ስሜታቸውን በመግራት በምክንያታዊነት ያስባሉ፡፡
5. መቆጣጠር በሚችሉት ነገር ላይ ብቻ ያተኩራሉ
ብዙ ውድቀቶች ሰዎችን የሚያደናግጧቸው ከአቅማቸው በላይ በሆኑ ነገሮች ላይ ሙሉ በሙሉ ስሚያተኩሩ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ከእነሱ የቁጥር ቀጠና ውጪ የሆነውን በጸሎት ለፈጣሪ በመተው እነሱ ማድረግ የሚችሉት ላይ ያተኩራ፡፡
እኛም የእነሱን ምሳሌ እንከተል!
Dr eyob mamo
2 months ago
የተገለጠው እውነታ
በ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
በምሥራቃዊው ኢትዮጵያ ይልቁንም በሐረር፣ አርሲና ባሌ አካባቢዎች ላይ ትኩረት አድርጎና አቅዶ ክርስቲያኖችን የሚገድል፣ የሚያፈናቅል እና የሚያሳድድ የአክራሪ ክንፍ መኖሩ ተደጋግሞ ሲነገር ኖሯል። ይህ አካል ደርግ ወድቆ ኢህአዴግ ከተተካበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛዋንም የለውጥ፣ የምርጫ እና የመሳሰሉትን የጫና ወቅቶች ጠብቆ አደጋ ያላደረሰበት ጊዜ የለም።
ከተቻለ የመንግሥት መዋቅርን በመጠቀምና በየዘመኑ ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም እና ለሚገድላቸው አካላት ከወቅቱ ፖለቲካ አንጻር የሚስማማ ታርጋ በመስጠት የሚቻለውን ያህል ይገድላል፣ ያፈናቅላል፣ ያሳድዳል።
ይህ የተገለጠ እውነት ነው። ተደጋግሞም ተነግሯል፣ ተገልጿል። ሆኖም እንደዚህ ዘመን እንደ ልቡ ክርስቲያኖችን የሚያጸዳበት ስለመኖሩ ግን አላውቅም። በእኔ እምነት ኢህአዴግ ከመጣበት ጀምሮ የተፈጸሙት ተደምረው በዚህ ዓመት ብቻ የፈጸመውን የመግደልና የማሳደድ ተግባር የሚያክሉ አይመስለኝም። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም መንግሥታዊ ተቋም ሐዘኔታ ሲያሳዩ፣ አንድም አካል ተጠያቂ ሲደረግ ዓይተንም ሰምተንም አናውቅም።
ይህም የተገለጠ እውነት ነው።
ምንም ቢሆን፣ ማንም ቢሆኑ ይህ ሁሉ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች ደግሞም ዜጎች ነበሩ። በደቡብ አፍሪካ ላለው ከሀገራችን ውጡ የሚል ዐመጽ ዜጎቹን ለመከላከል መንግሥት በኢንባሲው በኩል እየሠራ እንደሆነ የሚገልጽ ዜና ከሰማንና ለዚህኛው መንግሥት በዝምታ የሚያልፍ ከሆነ ድርጊቱን የሚፈጽመው እርሱም ጭምር ነው የሚለውን ወቀሳ እውነት ነው ብሎ በአዎንታ እንደተቀበለው ለመረዳት ግዴታችን ጭምር ይሆናል። ይህ በእውነት ከልብ ያሳዝናል።
አንድ የተረጋገጠና የትገለጠ እውነት ደግሞ አለ። የሰው ደም በከንቱ ፈስሶ አይቀርም። እግዚአብሔር የሚባል ተበቃይ አምላክ አለና። ለንስሐ ጊዜ ቢሰጥም "በቀል የእኔ ነው" ያለውና "ከኦሪትና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምታልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል" ያለው አምላክ ቃሉ የታመነ ነውና አይቀርም። እርሱ ሁላችንንም ይቅር ይበለን፣ የመከራውንም ወቅት አሳልፎ ለሰላምና ለፍቅር ያብቃን።
በ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
በምሥራቃዊው ኢትዮጵያ ይልቁንም በሐረር፣ አርሲና ባሌ አካባቢዎች ላይ ትኩረት አድርጎና አቅዶ ክርስቲያኖችን የሚገድል፣ የሚያፈናቅል እና የሚያሳድድ የአክራሪ ክንፍ መኖሩ ተደጋግሞ ሲነገር ኖሯል። ይህ አካል ደርግ ወድቆ ኢህአዴግ ከተተካበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛዋንም የለውጥ፣ የምርጫ እና የመሳሰሉትን የጫና ወቅቶች ጠብቆ አደጋ ያላደረሰበት ጊዜ የለም።
ከተቻለ የመንግሥት መዋቅርን በመጠቀምና በየዘመኑ ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም እና ለሚገድላቸው አካላት ከወቅቱ ፖለቲካ አንጻር የሚስማማ ታርጋ በመስጠት የሚቻለውን ያህል ይገድላል፣ ያፈናቅላል፣ ያሳድዳል።
ይህ የተገለጠ እውነት ነው። ተደጋግሞም ተነግሯል፣ ተገልጿል። ሆኖም እንደዚህ ዘመን እንደ ልቡ ክርስቲያኖችን የሚያጸዳበት ስለመኖሩ ግን አላውቅም። በእኔ እምነት ኢህአዴግ ከመጣበት ጀምሮ የተፈጸሙት ተደምረው በዚህ ዓመት ብቻ የፈጸመውን የመግደልና የማሳደድ ተግባር የሚያክሉ አይመስለኝም። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም መንግሥታዊ ተቋም ሐዘኔታ ሲያሳዩ፣ አንድም አካል ተጠያቂ ሲደረግ ዓይተንም ሰምተንም አናውቅም።
ይህም የተገለጠ እውነት ነው።
ምንም ቢሆን፣ ማንም ቢሆኑ ይህ ሁሉ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች ደግሞም ዜጎች ነበሩ። በደቡብ አፍሪካ ላለው ከሀገራችን ውጡ የሚል ዐመጽ ዜጎቹን ለመከላከል መንግሥት በኢንባሲው በኩል እየሠራ እንደሆነ የሚገልጽ ዜና ከሰማንና ለዚህኛው መንግሥት በዝምታ የሚያልፍ ከሆነ ድርጊቱን የሚፈጽመው እርሱም ጭምር ነው የሚለውን ወቀሳ እውነት ነው ብሎ በአዎንታ እንደተቀበለው ለመረዳት ግዴታችን ጭምር ይሆናል። ይህ በእውነት ከልብ ያሳዝናል።
አንድ የተረጋገጠና የትገለጠ እውነት ደግሞ አለ። የሰው ደም በከንቱ ፈስሶ አይቀርም። እግዚአብሔር የሚባል ተበቃይ አምላክ አለና። ለንስሐ ጊዜ ቢሰጥም "በቀል የእኔ ነው" ያለውና "ከኦሪትና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምታልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል" ያለው አምላክ ቃሉ የታመነ ነውና አይቀርም። እርሱ ሁላችንንም ይቅር ይበለን፣ የመከራውንም ወቅት አሳልፎ ለሰላምና ለፍቅር ያብቃን።
Sponsored by
Surafel
Comments