19 hours ago
AU Election Observation Mission Praises Transparency in Ethiopia’s 7th General Election
#ethiopia #elections2026 #au #observation #ebcdotstream #uhurukenyatta
21 hours ago
Discover the enchanting charm of Hanoi with our exclusive 7-Nights/8-Days tour package starting at just USD 2639! Experience the perfect blend of rich traditions and stunning architecture in the historic Old Quarter. Don’t miss your chance to explore the heart of
Vietnam. Book your adventure today and let the magic of Hanoi inspire your soul!
https://www.ethiopianholid... #flyethiopian #ethiopianholidays
Vietnam. Book your adventure today and let the magic of Hanoi inspire your soul!
https://www.ethiopianholid... #flyethiopian #ethiopianholidays
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
Sponsored by
Surafel
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
2 days ago
We are pleased to announce the resumption of our services to Kuwait, effective June 16, 2026. #flyethiopian #kuwait
3 days ago
የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው
#ethiopia | ''የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-
• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤
በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡
ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።''
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
#pmabiyahmed #ethiopianelection #democracy #ethiopianpeople #abiyahmed #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ''የኢትዮጵያ ሕዝብ አስደናቂም ተአምረኛም ሕዝብ ነው። ከፈጣሪ በቀር ሕዝባችንን አሟልቶ ሊያውቅና ሊገመግም የሚችል ማን ነው? የዳበረ ባህል፣ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል። በዛሬው ታሪካዊ ዕለት፡-
• የሌሊቱ ብርድና ጨለማ ያላስፈራቸው፣
• የቀትሩ ፀሐይና ድንገተኛ ዝናብ ያልበገራቸው
• ሠርግ፣ ኀዘን፣ ወሊድና ሌሎች ማኅበራዊ ሁነቶች ያላገዳቸው፣
• ረጃጅም ሰልፎች ያላታከታቸው፣
• የአካል ጉዳት ድምጽ ለመስጠት ያልገደባቸው፣
• ሕመም እና እርጅና የሀገር ተስፋን ከማየት ያላገዳቸው፣
• የነገ ሀገር ተረካቢ ጨቅላ ልጃቸውን ማዘል ያላደከማቸው፣
• ከምንም በላይ የጠላት ጩኸትና ማስፈራሪያ ያላስቆማቸው ዜጎች፤
በብዙ ውጣ ውረዶች መካከል (against all odds) ያሳያችሁት ጽናት ለዴሞክራሲና ለሀገር ሕልውና የተከፈለ ነውና ከልብ የመነጨ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡
ይሄንን ሕዝብ ማገልገል መታደል ነውና ተመራጮች ያከበራችሁን አክብራችሁ ለዴሞክራሲ ሥርዓት ዋጋ የከፈለውን ይሄንን ሕዝብ በንጽሕና ለማገልገል ያብቃችሁ።''
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
#pmabiyahmed #ethiopianelection #democracy #ethiopianpeople #abiyahmed #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
ዛሬ የዌብሳይት ዲዛይነሮች ቀን ነው። ዓለማችን ወደ ዲጅታል እየተቀየረች ባለችበት በዚህ ወቅት ድርጅታችሁ እና ቢዝነሳናችሁ መዘመን ግድ ነው።
ሱራፌል ተፈሪ ይባል በጣም ጎበዝ የሆነ የዌብሳይት ዲዛይነር ነው። የፋስት መረጃን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ድረ ገጽ ዲዛይን የሰራው ይህ ጎበዝ ወጣት ነው። "Yene IT solution" የተሰኘ ተቋሙ ምርጥ ምርጥ ድረ ገጾችን ከAI ጋር አስተሳስሮ ይሰራል።
ሱራፌልን ለማግኘት
+25193333-2325
itsolutionyenevibe.com
ሱራፌል ተፈሪ ይባል በጣም ጎበዝ የሆነ የዌብሳይት ዲዛይነር ነው። የፋስት መረጃን ጨምሮ በርካታ ሚዲያዎችን ድረ ገጽ ዲዛይን የሰራው ይህ ጎበዝ ወጣት ነው። "Yene IT solution" የተሰኘ ተቋሙ ምርጥ ምርጥ ድረ ገጾችን ከAI ጋር አስተሳስሮ ይሰራል።
ሱራፌልን ለማግኘት
+25193333-2325
itsolutionyenevibe.com
4 days ago
4 days ago
ዩቱዩብ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በሚሰሩ ቪዲዮዎች ላይ ዘመቻ ከፈተ!
የዓለም ትልቁ የቪዲዮ ማጋሪያ ፕላትፎርም የሆነው ዩቱዩብ (YouTube)፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም በArtificial Intelligence (AI) አማካኝነት በብዛት የሚመረቱ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ በርካታ ቻናሎችን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ መጀመሩ ተሰማ።
እንደ አዳዲስ መረጃዎች ዘገባ፣ ከመድረኩ የተሰረዙት እነዚህ ቻናሎች ከመዘጋታቸው በፊት በአጠቃላይ ከ4.7 ቢሊዮን በላይ እይታዎችን (Views) ማሰባሰብ ችለው ነበር።
🛑 ዋናው ምክንያት ምንድን ነው?
እነዚህ ቻናሎች ያለምንም የሰው ልጅ ተሳትፎ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሞች ብቻ በጅምላ የሚሰሩ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ነበሩ። ዩቱዩብ ይህንን ጠንከር ያለ እርምጃ የወሰደው ተጠቃሚዎችን የሚያሳስቱና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል፣ ጥራታቸውን ያልጠበቁና ሰዎችን የሚያሰለቹ ይዘቶችን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያውን ታማኝነት እና ትክክለኛነት ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታውቋል።
በአሁኑ ጊዜ የAI መተግበሪያዎች እጅግ በጣም ፈጣን እና ቀላል በሆነ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ቪዲዮዎችን በደቂቃዎች ውስጥ ለመፍጠር ያስችላሉ። ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ዩቱዩብ ላሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት አዲስ ፈጠራን ከመደገፍ እና የሰዎችን እምነት በአግባቡ ከማስጠበቅ አንፃር ትልቅ የባላንስ ፈተና ሆኖባቸዋል።
የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው? 🤔
በAI የሚመረቱ ይዘቶች በኢንተርኔት ላይ አዳዲስ ፈጠራዎችን እያገዙ ነው ወይስ ድሩን በጥራት አልባ ቪዲዮዎች እያጨናነቁት? ሃሳብዎን ያካፍሉን!
Seledadotio
Seledadotio
የዓለም ትልቁ የቪዲዮ ማጋሪያ ፕላትፎርም የሆነው ዩቱዩብ (YouTube)፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም በArtificial Intelligence (AI) አማካኝነት በብዛት የሚመረቱ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ በርካታ ቻናሎችን ሙሉ በሙሉ መሰረዝ መጀመሩ ተሰማ።
እንደ አዳዲስ መረጃዎች ዘገባ፣ ከመድረኩ የተሰረዙት እነዚህ ቻናሎች ከመዘጋታቸው በፊት በአጠቃላይ ከ4.7 ቢሊዮን በላይ እይታዎችን (Views) ማሰባሰብ ችለው ነበር።
🛑 ዋናው ምክንያት ምንድን ነው?
እነዚህ ቻናሎች ያለምንም የሰው ልጅ ተሳትፎ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሞች ብቻ በጅምላ የሚሰሩ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ነበሩ። ዩቱዩብ ይህንን ጠንከር ያለ እርምጃ የወሰደው ተጠቃሚዎችን የሚያሳስቱና ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመከላከል፣ ጥራታቸውን ያልጠበቁና ሰዎችን የሚያሰለቹ ይዘቶችን ለመቀነስ እንዲሁም የማህበራዊ ሚዲያውን ታማኝነት እና ትክክለኛነት ለመጠበቅ በማሰብ እንደሆነ ታውቋል።
በአሁኑ ጊዜ የAI መተግበሪያዎች እጅግ በጣም ፈጣን እና ቀላል በሆነ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ቪዲዮዎችን በደቂቃዎች ውስጥ ለመፍጠር ያስችላሉ። ይህ ሁኔታ ደግሞ እንደ ዩቱዩብ ላሉ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ተቋማት አዲስ ፈጠራን ከመደገፍ እና የሰዎችን እምነት በአግባቡ ከማስጠበቅ አንፃር ትልቅ የባላንስ ፈተና ሆኖባቸዋል።
የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው? 🤔
በAI የሚመረቱ ይዘቶች በኢንተርኔት ላይ አዳዲስ ፈጠራዎችን እያገዙ ነው ወይስ ድሩን በጥራት አልባ ቪዲዮዎች እያጨናነቁት? ሃሳብዎን ያካፍሉን!
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
8 days ago
አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
8 days ago
ተለያይቻለሁ !!!
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
8 days ago
Ethiopian Airlines domestic destination is further expanding! Today, we proudly inaugurated Negele Borena Geda Airport and commenced a new passenger service in a grand ceremony attended by the Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia His Excellency Dr. Abiy Ahmed, the President of the Oromia Regional State His Excellency Shimelis Abdisa, Ethiopian Airlines Group CEO Mr. Mesfin Tasew, high level government officials, the airlines’ executives, local community representatives, and various stakeholders.
The ceremony unveiled a new airport and marked the beginning of a new thrice weekly service to Negele Borena, growing the airlines’ domestic destination to 24. #ethiopianairlines
The ceremony unveiled a new airport and marked the beginning of a new thrice weekly service to Negele Borena, growing the airlines’ domestic destination to 24. #ethiopianairlines
8 days ago
✨ Makeup by TIYO ✨
WHERE BEAUTY MEETS ELEGANCE
ተፈጥሯዊ ውበትዎን ሳይቀይር፣ ይበልጥ በሚያምርና ረቂቅ አቀራረብ ፕሮፌሽናል የሜካፕ አገልግሎት እንሰጣለን።
Our Services | አገልግሎቶቻችን
💍 የሙሽራ ሜካፕ (Bridal Makeup)
✨ ቀላልና ማራኪ ሜካፕ (Soft Glam Makeup)
🎨 ክሬኤቲቭ ሜካፕ (Creative Makeup)
Booking Open For | ቀጠሮ እንቀበላለን
💒 ሰርግ እና መልስ
🎓 ምርቃት
🎂 ልደት እና ልዩ ዝግጅቶች
📸 Photoshoots & Events
🌿 Enhancing beauty, naturally
“የተፈጥሮ ውበትን ይበልጥ እናጎላለን”
👩🎨 Tiyobistiya Ayele
Professional Makeup Artist
📞 Book Now: +251973796149
📧 tiyobistiyaayele21gmail.com
📸 Instagram: makeupbytiyo
WHERE BEAUTY MEETS ELEGANCE
ተፈጥሯዊ ውበትዎን ሳይቀይር፣ ይበልጥ በሚያምርና ረቂቅ አቀራረብ ፕሮፌሽናል የሜካፕ አገልግሎት እንሰጣለን።
Our Services | አገልግሎቶቻችን
💍 የሙሽራ ሜካፕ (Bridal Makeup)
✨ ቀላልና ማራኪ ሜካፕ (Soft Glam Makeup)
🎨 ክሬኤቲቭ ሜካፕ (Creative Makeup)
Booking Open For | ቀጠሮ እንቀበላለን
💒 ሰርግ እና መልስ
🎓 ምርቃት
🎂 ልደት እና ልዩ ዝግጅቶች
📸 Photoshoots & Events
🌿 Enhancing beauty, naturally
“የተፈጥሮ ውበትን ይበልጥ እናጎላለን”
👩🎨 Tiyobistiya Ayele
Professional Makeup Artist
📞 Book Now: +251973796149
📧 tiyobistiyaayele21gmail.com
📸 Instagram: makeupbytiyo
8 days ago
Sponsored by
Surafel
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን የጦር ኃይሎች ከፍተኛ ቃል አቀባይ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በሀገሪቱ ላይ የሚያካሂዱትን የአየር ድብደባ ዳግም የሚጀምሩ ከሆነ፣ ኢራን "እጅግ የከፋ" እና "በጣም ጠንካራ" የሆነ የአጸፋ እርምጃ እንደምትወስድ አስጠንቅቀዋል።
አቦልፋዝል ሸካርቺ የተባሉት የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ በከፊል የመንግስት የዜና ወኪል በሆነው ፋርስ (Fars) በኩል በሰጡት መግለጫ፣ "ቀጠናው ወደ ሌላ ዙር ጦርነት የሚገባ ከሆነ፣ የኢራን ምላሽ ከቀጠናው ድንበሮችም የተሻገረ፣ እንዲሁም እጅግ የከፋ እና በጣም ጠንካራ ይሆናል" በማለት የሀገሪቱን አቋም አብራርተዋል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ይኸው የዜና ወኪል ባወጣው ዘገባ፣ የአሜሪካ እና የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች በሆርሙዝ ስትሬት (Strait of Hormuz) አቅራቢያ ከምትገኘው የላራክ ደሴት (Larak Island) በስተደቡብ በሚንቀሳቀሱ የኢራን ጀልባዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን እና በዚህም "በርካታ የኢራን ዜጎች" ህይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቆ ነበር።
እነዚህ የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች የተሰነዘሩት፣ በየካቲት ወር መጨረሻ አካባቢ በአሜሪካ እና በእስራኤል አነሳሽነት በኢራን ላይ የተከፈተውን እና ተከታትሎም የኢራንን የአጸፋ እርምጃ ያስተናገደውን ጦርነት በዘላቂነት ለማስቆም፣ በፓኪስታን አደራዳሪነት የሰላም ጥረቶች እየተካሄዱ ባሉበት ወቅት መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጨምሮታል።
አቦልፋዝል ሸካርቺ የተባሉት የጦር ኃይሉ ቃል አቀባይ በከፊል የመንግስት የዜና ወኪል በሆነው ፋርስ (Fars) በኩል በሰጡት መግለጫ፣ "ቀጠናው ወደ ሌላ ዙር ጦርነት የሚገባ ከሆነ፣ የኢራን ምላሽ ከቀጠናው ድንበሮችም የተሻገረ፣ እንዲሁም እጅግ የከፋ እና በጣም ጠንካራ ይሆናል" በማለት የሀገሪቱን አቋም አብራርተዋል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ይኸው የዜና ወኪል ባወጣው ዘገባ፣ የአሜሪካ እና የእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች በሆርሙዝ ስትሬት (Strait of Hormuz) አቅራቢያ ከምትገኘው የላራክ ደሴት (Larak Island) በስተደቡብ በሚንቀሳቀሱ የኢራን ጀልባዎች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን እና በዚህም "በርካታ የኢራን ዜጎች" ህይወታቸውን ማጣታቸውን አስታውቆ ነበር።
እነዚህ የቅርብ ጊዜ ጥቃቶች የተሰነዘሩት፣ በየካቲት ወር መጨረሻ አካባቢ በአሜሪካ እና በእስራኤል አነሳሽነት በኢራን ላይ የተከፈተውን እና ተከታትሎም የኢራንን የአጸፋ እርምጃ ያስተናገደውን ጦርነት በዘላቂነት ለማስቆም፣ በፓኪስታን አደራዳሪነት የሰላም ጥረቶች እየተካሄዱ ባሉበት ወቅት መሆኑ የጉዳዩን አሳሳቢነት ጨምሮታል።
9 days ago
9 days ago
በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘው ዘመናዊው የላፍቶ ሆስፒታል ተመረቀ
#fastmereja በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እጅግ ዘመናዊው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ግንባታው በ5.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውና 17 ዘመናዊ ሕንጻዎችን ያቀፈው ይህ ግዙፍ የሕክምና ማዕከል፣ 500 አልጋዎችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን በተለይም የካንሰር እና የልብ ሕክምናዎችን በላቀ ደረጃ በመስጠት ዜጎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ አገር የሚያደርጉትን ጉዞና የውጭ ምንዛሬ ወጪን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፣ ይህ የሕክምና ማዕከል በምሥራቅ አፍሪካ ብቸኛና ልዩ የሚያደርጉትን በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የሚደገፉና የ2026 ምርት የሆኑ የረቀቁ የሕክምና መሣሪያዎችን በውስጡ አካትቷል። ከእነዚህም መካከል በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የPET-SCAN የቅድመና ድህረ ካንሰር ምርመራ ማሽን፣ የሂሊየም ትነትን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀረው የMRI- 3 Tesla መሣሪያ፣ ልብ አንድ ጊዜ መትታ ሳትጨርስ ሙሉ ምርመራ የሚያከናውነው ፈጣን የCT Scan (640 Slice) ቴክኖሎጂ፣ እና የልብና የአንጎል ደም ሥር ችግሮችን በአጭር ጊዜ ለይቶ የሚያክመው የካዝ ላብ (Cath Lab) ይገኙበታል።
በተጨማሪም የጡት ካንሰርን በቅድሚያ ለመመርመርና የናሙና ምርመራ ለመውሰድ የሚያስችለው 3D ማሞግራፊ፣ ሙሉ በሙሉ ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ የሆነውና የሰውን ስህተት የሚያስቀረው የመጀመሪያው የሮቦቲክ ላቦራቶሪ (TLA) ሥርዓት፣ እንዲሁም ዘመናዊ የአልትራሳውንድ እና የዲጂታል ኤክስሬይ ማሽኖች በሆስፒታሉ ውስጥ ተሟልተዋል። ማዕከሉ በሰዓት 80 ሜትር ኩብ ኦክስጂን የማምረት አቅም ያለው የሜዲካል ጋዝ ማምረቻ ፕላንት፣ የራሱ የውኃ ጉድጓድ፣ የፍሳሽ ማጣሪያ ፕላንት እና 18 ዘመናዊ የአስከሬን ማቀዝቀዣዎች ያሉት ሲሆን፣ በሆስፒታሎች የሚያጋጥመውን የኢንፌክሽን ችግር ለመከላከል ሲባልም ግድግዳዎቹና ወለሎቹ ባክቴሪያን ሙሉ በሙሉ በሚከላከል (Anti-bacterial) ቁስ መገንባታቸው ተረጋግጧል። ለፕሮጀክቱ መሳካት ሌት ተቀን ለደገፉ አመራሮችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#fastmereja በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እጅግ ዘመናዊው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ግንባታው በ5.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውና 17 ዘመናዊ ሕንጻዎችን ያቀፈው ይህ ግዙፍ የሕክምና ማዕከል፣ 500 አልጋዎችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን በተለይም የካንሰር እና የልብ ሕክምናዎችን በላቀ ደረጃ በመስጠት ዜጎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ አገር የሚያደርጉትን ጉዞና የውጭ ምንዛሬ ወጪን ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፣ ይህ የሕክምና ማዕከል በምሥራቅ አፍሪካ ብቸኛና ልዩ የሚያደርጉትን በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) የሚደገፉና የ2026 ምርት የሆኑ የረቀቁ የሕክምና መሣሪያዎችን በውስጡ አካትቷል። ከእነዚህም መካከል በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የPET-SCAN የቅድመና ድህረ ካንሰር ምርመራ ማሽን፣ የሂሊየም ትነትን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀረው የMRI- 3 Tesla መሣሪያ፣ ልብ አንድ ጊዜ መትታ ሳትጨርስ ሙሉ ምርመራ የሚያከናውነው ፈጣን የCT Scan (640 Slice) ቴክኖሎጂ፣ እና የልብና የአንጎል ደም ሥር ችግሮችን በአጭር ጊዜ ለይቶ የሚያክመው የካዝ ላብ (Cath Lab) ይገኙበታል።
በተጨማሪም የጡት ካንሰርን በቅድሚያ ለመመርመርና የናሙና ምርመራ ለመውሰድ የሚያስችለው 3D ማሞግራፊ፣ ሙሉ በሙሉ ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ የሆነውና የሰውን ስህተት የሚያስቀረው የመጀመሪያው የሮቦቲክ ላቦራቶሪ (TLA) ሥርዓት፣ እንዲሁም ዘመናዊ የአልትራሳውንድ እና የዲጂታል ኤክስሬይ ማሽኖች በሆስፒታሉ ውስጥ ተሟልተዋል። ማዕከሉ በሰዓት 80 ሜትር ኩብ ኦክስጂን የማምረት አቅም ያለው የሜዲካል ጋዝ ማምረቻ ፕላንት፣ የራሱ የውኃ ጉድጓድ፣ የፍሳሽ ማጣሪያ ፕላንት እና 18 ዘመናዊ የአስከሬን ማቀዝቀዣዎች ያሉት ሲሆን፣ በሆስፒታሎች የሚያጋጥመውን የኢንፌክሽን ችግር ለመከላከል ሲባልም ግድግዳዎቹና ወለሎቹ ባክቴሪያን ሙሉ በሙሉ በሚከላከል (Anti-bacterial) ቁስ መገንባታቸው ተረጋግጧል። ለፕሮጀክቱ መሳካት ሌት ተቀን ለደገፉ አመራሮችና ለአካባቢው ማኅበረሰብ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
9 days ago
ጥቂት ስለ ግጥምና ገጣምያን!
ደረጀ በላይነህ
ገጣሚና ሐያሲ
#ethiopia | ግጥም እንደ ቋንቋ ጥንታዊና ሁለንታዊና መግባቢያ ስለሆነ፣ጥንታውያኑ ተጠቅመውበታል፤ዘመናውያኑ ደግሞ ኮትኩተውታል ይላሉ-ፕሮፌሰር ሎረነስ ፐሪኔ።
ግጥም ከሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ተወዳጅና አክሊል የሚባለውም እንደ ጥንቅሽ እየተላጠ ተበልቶ ትዝታው ስለማይጠፋ፣የዋሽንቱ ዜማ ከልብ ስለማይገሠሥ ነው።
ዜማዊነቱ ለአይረሴነቱ ሰበብ ሲሆን፣ እምቅነቱ፣ምናባዊነቱ፣ተውኔታዊነት፣ቁጥብነት ወዘተ መለያ ባህርያቱ ናቸው።
ሌላው ብርቅ ከሚያሰኙት አንዱ ደግሞ አተያዩና ፍካሬው ነው። እንደ አልማዝ የተለያዩ ነጸብራቆች ስላሉት የዚያ ብርቅርቅታና ቀለም የገጣሚውን ምናብ ይለካዋል።
ግጥም ይፈላሰፋል፤ግን ፍልስፍና አይደለም። ገጠመኝን አሳምሮ፣በምናብ ወልውሎ ያመጣል እንጂ!
Its primary concern is not with beauty,not philosophical truth,not eith percuation,but with experience. ይላሉ።
ፊትን በመስታወት እንደማየት ይመስላል፤ ጥሬ ምስል አይደለም። ብዙ ቀለም በርካታ ቅርጾች አሉት። ምናልባትም በተሰባበረ መስተዋት እንደማየት ሊሆን ይችላል።.
በቅርጹም ወይ ተራኪ፣ተውኔታዊ፣አሊያም ሌሪክ ይሆንና እንደገና በየፈርጁ ይሸነሸናል።...በተለይ ስሜት ንክር፣ሙዚቃዊ የሆነው ሌሪክ የስሜት ዳንሶች ይዞ በሙሾ ሊያላዝን፣በፍቅር እስክስታ ሊመታ፣በትዝታ ቆርፍዶ እንባው በረዶ ሊሆን ይችላል።...እንጉርጉሮ ቢሆን፣ ጸሎትና ምሕላ፣ሽለላና ቀረርቶም እንደዚሁ።
ቃላት ለግጥም አንዱ መታበያው፣የቁመናው ጌጥ፣የመጋረጃው ዘርፍ ነው።...በተለይ ዘይቤያዊ ቃላት ደመና ላይ ሰቅለው ቼ! በለው የሚሉበት የከፍታው ጉልላት ነው።
ቃላቱንም እማሬያዊና ፍካሬያዊ ብለን ብንለያቸው፣በአብዛኛው ከዘወትራዊው ይልቅ በተምሳሌታዊና አምሳያዊ ትዕምርቶች በወደድነው ሥፍራ ብንዶላቸው ጣማቸው ይጨምራል።
ወይም ስሜት የነሸጠውን ያየንበት ትዝብት ውል ሲልብን፣እንደ መንግሥቱ ለማ፦
በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ እንደክዋክብት
"ሳማት ሳማት"አሉት"ዕቀፍ ዕቀፋት"
አላወላወለም፤ወጣቱ ታዘዘ፤
ወገቧን አንገቷን፤በእጅና እጁ ያዘ፤
ከንፈሩ በረአድ ወዳፏ ተጠጋ።
-ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ የበረዶ አለንጋ፤
ጆሮግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ።
በጠራው ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን ፤ዋ ተማሪነት፣
ዋ ትዕዛዝ መፈጸም፣ዋ ምክር መስማት።
እንግዲህ ተራኪው ግጥም እንዲህ ያለ መልዕክት፣ሲያስላልፍ ሥዕሉ ደምቋል። ጣቶቿ አለንጋ፤ጡቶቿ ሹል፣ሲል የልጅቷ ዕድሜ ከውስጥ ፤ቁመናው ከላይ ይታዩናል። ከዚህም አልፎ ደግሞ የምንበረብረው ሳጥን አለ። ከንፈሩ ለምን ቀዘቀዘ?...ፈርቷል። የፈራው ለምንድነው?...ልጅቷ እንዳትቆጣ!...ያኔ በዘመኑ ዐውድ ልጃገረ በእጅ መንካት ሽጉጥ ያስመዝዛል። ግን ተማሪ ጓደኞቹ አሳሳቱትና ጥፊ ቀመሰ።ቅምሻ ብቻ አይደለም ተናጋ። ሲናጋ ድምፅ አለው።
እዚህ ጋ ምሰላ ይመጣል- ድምፅ፣እላይ አጎጠጎጤ- ምስል፤ዐይኖችዋ መጉላት-ዕይታ።
ግጥም እንዲህና እንዲያ ነው። ሙዚቃው ያግባባል፤ሐሳቡ ሆድ ይገባል።
ግጥም የየዘመኑን ዳና ያስቀራል ስንል፥ ፖለቲካው፣ሥነ ልቦናው፣ፍልስፍናው ባሕሉ ወዘተ ቀለሙ ውስጥ ታትሞ ይኖራል። የረሃብ ይሆን ጥጋብ፤የጸብ ይሁን ፍቅር የትውልዱን ትዝብት፣ የነውጡን ንፋስ ፈትል ሰማይ ላይ ረጭቶ፣ የትካዜው ፉጨት፣የሳቁን ዜማ፣የትዝታውን ጥላ፤ ሻካራና እሾሁን፣ ሕመምና ጥዝጣዜውን፣ሳቅና ፍካቱን፣...
የአማርኛ ግጥሞች ዕድሜ ብዙ ሩቅ አይደለም።በዚያ ላይ አዳዲስ ፈርጆችን ይዞ አላስደነቀም። ከፖለቲካው ሥርዐትና ርዕዮት ጋር የቀየረው ቅርጽ የለም።ርዕዮቶችን በአንቀልባ እያዘሉ ከማውረድ የተለየ ሚናም አልነበረው። እንደ ፈረንጆቹ፣ወይም እንደላቲኖቹ፣ካልሆነም እንደመካከለኛ ምሥራቋ እሰራኤል የቤት ዐመታት ላይ የመጣው ለውጥ አልተመዘገበም።
ዘውጉን ሳይለቅ የቁመና ለውጥ ያመጣው ባለፉት አርባ ዐመታት ይመስለኛል። ያም ከፖለቲካዊና አገዛዛዊ ሸምቀቆ ጋር ተያይዞ የመጣ መጉበጥ ይመስላል።
አጫጭር ግጥሞች መብዛታቸውም፣የመታከት፣ብዙ ለመተንተን ሰሚ በማጣት የተፈጠረ መሰልቸት ይመስላል፤ዝም ብሎ ለመተንፈስ ብቻ። ቢጨንቀውና ሰሚ ቢያጣ መሬት ቆፍሮ ለመሬት እንዳወራው ሰው ዓይነት።
በዚሁ ተመሳሳይ ዘመን ሌላም ነገር ታይቷል። በግጥሙ መዝጊያ ላይ አንድ መገረሚያ ማምጣት። ትንሽ ቆይቶም፣
የአዳራሽ ግጥሞች በሙዚቃ እየታጀቡ መቅረብ መጀመራቸው ዘለግ ያሉና መድረክ ላይ የሚያቆዩትን አመጣ። እነዚህ የተንዛዙ ግጥሞችን ወደ ኅትመት ሰፈር ሲመጡ ዘልዛላ ሆኑ።
የመጀመሪያ መጻሕፍታቸው ያማሩላቸው ገጣምያን ሳይቀሩ ግጥሞቻቸው ለዛቸውንና እምቅነታቸውን ነጠቋቸው።
ከዚህ ዘመን ገጣምያን አንዷ ሜሮን ጌትነት ነበረች። ሜሮን ነገሮችን የምታይበትና የምትፈትልበት መንገድ ግሩም ነው። "ዙረት" በሚለው የግጥም መጽሐፏ አንገት በሚያስነቀንቁ፣ልብ በሚንጡ ግጥሞቿ አስመሰከረች።
መድረኮች ላይ ስትወጣ ግን፣እንደነምሥራቅ፣እንደነ ዶክተር በድሉ፣አረዘመቻቸው። ከነርዝመቱ ለዛውን ጠብቆ የሚሄደው አሳየኸኝ ረጋሳ ይመስለኛል። ትዕግሥት ማሞም አንዳች የማይረግብ ገሞራ አላት።
በግጥም ኅትመት ዓለም ብዙዎቹ የመጀመሪያ መጽሐፋቸውና ቀጣዮቹ እኩል አይደምቁም። ስስነትና እርግበት ይታይባቸዋል። በዚህ ፈተና ያልወደቀው ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ ነው፤የእነ ደበበ ሰይፉን ደጅ እያንኳኳ ይመስላል።እነ አበረ አያሌው ገና አልተፈተኑም። ትዕግሥት ዓለምነህም ወደፊት በመጀመሪያ ግጥሟ ልክ ከመጣች፣ተዐምር ነው።ቋንቋ፣አተያይዋና Allusion አጠቃቀሟ ድንቅ ነው።
ወደ ሜሮን አዲሱ መጽሐፍ ልምጣ ። ስሜት የሚያሞቁት ከበሮ ድብደባዎች፣በቀጭን የሚመጡት ሳቆቿ ፣አንገት የሚያወዛውዙት ግርምቶች፣በአጫጭር ግጥሞቿ የምታደርጋቸው ተዐምራት የቀነሱ ይመስላል።
ቆንጆ ግጥሞች አሏት?...አዎ። ግን እንደድሮ አይደሉም። አዳዲስ ውበቶችና የቃላት ውበት ጨምራለች።
ግጥሞቿ፣ይስበኩን አይባልም። poetry does not teach:but it inspires.ይላሉ የዘርፉ ሰዎች።...ለነገሩ በዚህ የሚያምኑት ሊቃውንት በርካታ ናቸው።
እስቲ ከሜሮን ልምዘዝ፦
መተላለፍ 2
ሐቀኛ ነጋዴ በአመድ ገበያ ላይ ዱቄት ይዟል ማልዶ፣
የታይታ ሀብታም ሰው በሥጋ ወረፋ ይሰለፋል ማዶ።
ዘመን ሰውነትን ሸቀጥ አርጎ አውጥቶ ዐየን እንደዋዛ፣
የወረቀት ገንዘብ ወርቅ ሕልም እየገዛ።
ይህ ግጥሟ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን የቤት መምቻው ድምፅ ደማቅ ነው። ይህን ያደረጉት አናባቢዎቿ ናቸው። ሐሳቡም ግዙፍና የነፋሱን ዘመን በእፍኝ የሰፈረ ነው። ወርቅ ሕልም ፣በወረቀት እየሸጠ፤ዕንቁ በእሪያዎች ፊት እየተጣለ።
ልበ...
የአንተም ልብ ድንጋይ...
የእኔም ልብ ድንጋይ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ)
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።
ግጥም ሙዚቃ፣ ሥዕልም የተካተቱበት የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ሰለሆነ፣ነፍስ ያፍነከንካል ፤ትርዒት ያሳያል።
ጋሽ ጸጋዬ በዘይቤዎቹ መዐዛ፣ በምሰላዎቹ ምትሐት ቀልብ ሲስብ፣ ገብረክርስቶስ በሜሎዲዎቹ ብብት ይኮረኩራል። ደበበ ሐሳብ እንደሽንኩርት እየላጠ ያስደምማል። ሁሉም በየራሳቸው ድንኳን የሚሰጡን ጣ'ም አለ።
ላምቦርን("ዶ/ር)ስለዚህ ሲጽፉ፦ Since every one likes pictures and most find pleasure in music,the common indifference to poetry must be due to a failure to realize that poetry is really both.
ደረጀ በላይነህ
ገጣሚና ሐያሲ
#ethiopia | ግጥም እንደ ቋንቋ ጥንታዊና ሁለንታዊና መግባቢያ ስለሆነ፣ጥንታውያኑ ተጠቅመውበታል፤ዘመናውያኑ ደግሞ ኮትኩተውታል ይላሉ-ፕሮፌሰር ሎረነስ ፐሪኔ።
ግጥም ከሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ተወዳጅና አክሊል የሚባለውም እንደ ጥንቅሽ እየተላጠ ተበልቶ ትዝታው ስለማይጠፋ፣የዋሽንቱ ዜማ ከልብ ስለማይገሠሥ ነው።
ዜማዊነቱ ለአይረሴነቱ ሰበብ ሲሆን፣ እምቅነቱ፣ምናባዊነቱ፣ተውኔታዊነት፣ቁጥብነት ወዘተ መለያ ባህርያቱ ናቸው።
ሌላው ብርቅ ከሚያሰኙት አንዱ ደግሞ አተያዩና ፍካሬው ነው። እንደ አልማዝ የተለያዩ ነጸብራቆች ስላሉት የዚያ ብርቅርቅታና ቀለም የገጣሚውን ምናብ ይለካዋል።
ግጥም ይፈላሰፋል፤ግን ፍልስፍና አይደለም። ገጠመኝን አሳምሮ፣በምናብ ወልውሎ ያመጣል እንጂ!
Its primary concern is not with beauty,not philosophical truth,not eith percuation,but with experience. ይላሉ።
ፊትን በመስታወት እንደማየት ይመስላል፤ ጥሬ ምስል አይደለም። ብዙ ቀለም በርካታ ቅርጾች አሉት። ምናልባትም በተሰባበረ መስተዋት እንደማየት ሊሆን ይችላል።.
በቅርጹም ወይ ተራኪ፣ተውኔታዊ፣አሊያም ሌሪክ ይሆንና እንደገና በየፈርጁ ይሸነሸናል።...በተለይ ስሜት ንክር፣ሙዚቃዊ የሆነው ሌሪክ የስሜት ዳንሶች ይዞ በሙሾ ሊያላዝን፣በፍቅር እስክስታ ሊመታ፣በትዝታ ቆርፍዶ እንባው በረዶ ሊሆን ይችላል።...እንጉርጉሮ ቢሆን፣ ጸሎትና ምሕላ፣ሽለላና ቀረርቶም እንደዚሁ።
ቃላት ለግጥም አንዱ መታበያው፣የቁመናው ጌጥ፣የመጋረጃው ዘርፍ ነው።...በተለይ ዘይቤያዊ ቃላት ደመና ላይ ሰቅለው ቼ! በለው የሚሉበት የከፍታው ጉልላት ነው።
ቃላቱንም እማሬያዊና ፍካሬያዊ ብለን ብንለያቸው፣በአብዛኛው ከዘወትራዊው ይልቅ በተምሳሌታዊና አምሳያዊ ትዕምርቶች በወደድነው ሥፍራ ብንዶላቸው ጣማቸው ይጨምራል።
ወይም ስሜት የነሸጠውን ያየንበት ትዝብት ውል ሲልብን፣እንደ መንግሥቱ ለማ፦
በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ እንደክዋክብት
"ሳማት ሳማት"አሉት"ዕቀፍ ዕቀፋት"
አላወላወለም፤ወጣቱ ታዘዘ፤
ወገቧን አንገቷን፤በእጅና እጁ ያዘ፤
ከንፈሩ በረአድ ወዳፏ ተጠጋ።
-ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ የበረዶ አለንጋ፤
ጆሮግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ።
በጠራው ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን ፤ዋ ተማሪነት፣
ዋ ትዕዛዝ መፈጸም፣ዋ ምክር መስማት።
እንግዲህ ተራኪው ግጥም እንዲህ ያለ መልዕክት፣ሲያስላልፍ ሥዕሉ ደምቋል። ጣቶቿ አለንጋ፤ጡቶቿ ሹል፣ሲል የልጅቷ ዕድሜ ከውስጥ ፤ቁመናው ከላይ ይታዩናል። ከዚህም አልፎ ደግሞ የምንበረብረው ሳጥን አለ። ከንፈሩ ለምን ቀዘቀዘ?...ፈርቷል። የፈራው ለምንድነው?...ልጅቷ እንዳትቆጣ!...ያኔ በዘመኑ ዐውድ ልጃገረ በእጅ መንካት ሽጉጥ ያስመዝዛል። ግን ተማሪ ጓደኞቹ አሳሳቱትና ጥፊ ቀመሰ።ቅምሻ ብቻ አይደለም ተናጋ። ሲናጋ ድምፅ አለው።
እዚህ ጋ ምሰላ ይመጣል- ድምፅ፣እላይ አጎጠጎጤ- ምስል፤ዐይኖችዋ መጉላት-ዕይታ።
ግጥም እንዲህና እንዲያ ነው። ሙዚቃው ያግባባል፤ሐሳቡ ሆድ ይገባል።
ግጥም የየዘመኑን ዳና ያስቀራል ስንል፥ ፖለቲካው፣ሥነ ልቦናው፣ፍልስፍናው ባሕሉ ወዘተ ቀለሙ ውስጥ ታትሞ ይኖራል። የረሃብ ይሆን ጥጋብ፤የጸብ ይሁን ፍቅር የትውልዱን ትዝብት፣ የነውጡን ንፋስ ፈትል ሰማይ ላይ ረጭቶ፣ የትካዜው ፉጨት፣የሳቁን ዜማ፣የትዝታውን ጥላ፤ ሻካራና እሾሁን፣ ሕመምና ጥዝጣዜውን፣ሳቅና ፍካቱን፣...
የአማርኛ ግጥሞች ዕድሜ ብዙ ሩቅ አይደለም።በዚያ ላይ አዳዲስ ፈርጆችን ይዞ አላስደነቀም። ከፖለቲካው ሥርዐትና ርዕዮት ጋር የቀየረው ቅርጽ የለም።ርዕዮቶችን በአንቀልባ እያዘሉ ከማውረድ የተለየ ሚናም አልነበረው። እንደ ፈረንጆቹ፣ወይም እንደላቲኖቹ፣ካልሆነም እንደመካከለኛ ምሥራቋ እሰራኤል የቤት ዐመታት ላይ የመጣው ለውጥ አልተመዘገበም።
ዘውጉን ሳይለቅ የቁመና ለውጥ ያመጣው ባለፉት አርባ ዐመታት ይመስለኛል። ያም ከፖለቲካዊና አገዛዛዊ ሸምቀቆ ጋር ተያይዞ የመጣ መጉበጥ ይመስላል።
አጫጭር ግጥሞች መብዛታቸውም፣የመታከት፣ብዙ ለመተንተን ሰሚ በማጣት የተፈጠረ መሰልቸት ይመስላል፤ዝም ብሎ ለመተንፈስ ብቻ። ቢጨንቀውና ሰሚ ቢያጣ መሬት ቆፍሮ ለመሬት እንዳወራው ሰው ዓይነት።
በዚሁ ተመሳሳይ ዘመን ሌላም ነገር ታይቷል። በግጥሙ መዝጊያ ላይ አንድ መገረሚያ ማምጣት። ትንሽ ቆይቶም፣
የአዳራሽ ግጥሞች በሙዚቃ እየታጀቡ መቅረብ መጀመራቸው ዘለግ ያሉና መድረክ ላይ የሚያቆዩትን አመጣ። እነዚህ የተንዛዙ ግጥሞችን ወደ ኅትመት ሰፈር ሲመጡ ዘልዛላ ሆኑ።
የመጀመሪያ መጻሕፍታቸው ያማሩላቸው ገጣምያን ሳይቀሩ ግጥሞቻቸው ለዛቸውንና እምቅነታቸውን ነጠቋቸው።
ከዚህ ዘመን ገጣምያን አንዷ ሜሮን ጌትነት ነበረች። ሜሮን ነገሮችን የምታይበትና የምትፈትልበት መንገድ ግሩም ነው። "ዙረት" በሚለው የግጥም መጽሐፏ አንገት በሚያስነቀንቁ፣ልብ በሚንጡ ግጥሞቿ አስመሰከረች።
መድረኮች ላይ ስትወጣ ግን፣እንደነምሥራቅ፣እንደነ ዶክተር በድሉ፣አረዘመቻቸው። ከነርዝመቱ ለዛውን ጠብቆ የሚሄደው አሳየኸኝ ረጋሳ ይመስለኛል። ትዕግሥት ማሞም አንዳች የማይረግብ ገሞራ አላት።
በግጥም ኅትመት ዓለም ብዙዎቹ የመጀመሪያ መጽሐፋቸውና ቀጣዮቹ እኩል አይደምቁም። ስስነትና እርግበት ይታይባቸዋል። በዚህ ፈተና ያልወደቀው ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ ነው፤የእነ ደበበ ሰይፉን ደጅ እያንኳኳ ይመስላል።እነ አበረ አያሌው ገና አልተፈተኑም። ትዕግሥት ዓለምነህም ወደፊት በመጀመሪያ ግጥሟ ልክ ከመጣች፣ተዐምር ነው።ቋንቋ፣አተያይዋና Allusion አጠቃቀሟ ድንቅ ነው።
ወደ ሜሮን አዲሱ መጽሐፍ ልምጣ ። ስሜት የሚያሞቁት ከበሮ ድብደባዎች፣በቀጭን የሚመጡት ሳቆቿ ፣አንገት የሚያወዛውዙት ግርምቶች፣በአጫጭር ግጥሞቿ የምታደርጋቸው ተዐምራት የቀነሱ ይመስላል።
ቆንጆ ግጥሞች አሏት?...አዎ። ግን እንደድሮ አይደሉም። አዳዲስ ውበቶችና የቃላት ውበት ጨምራለች።
ግጥሞቿ፣ይስበኩን አይባልም። poetry does not teach:but it inspires.ይላሉ የዘርፉ ሰዎች።...ለነገሩ በዚህ የሚያምኑት ሊቃውንት በርካታ ናቸው።
እስቲ ከሜሮን ልምዘዝ፦
መተላለፍ 2
ሐቀኛ ነጋዴ በአመድ ገበያ ላይ ዱቄት ይዟል ማልዶ፣
የታይታ ሀብታም ሰው በሥጋ ወረፋ ይሰለፋል ማዶ።
ዘመን ሰውነትን ሸቀጥ አርጎ አውጥቶ ዐየን እንደዋዛ፣
የወረቀት ገንዘብ ወርቅ ሕልም እየገዛ።
ይህ ግጥሟ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን የቤት መምቻው ድምፅ ደማቅ ነው። ይህን ያደረጉት አናባቢዎቿ ናቸው። ሐሳቡም ግዙፍና የነፋሱን ዘመን በእፍኝ የሰፈረ ነው። ወርቅ ሕልም ፣በወረቀት እየሸጠ፤ዕንቁ በእሪያዎች ፊት እየተጣለ።
ልበ...
የአንተም ልብ ድንጋይ...
የእኔም ልብ ድንጋይ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ)
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።
ግጥም ሙዚቃ፣ ሥዕልም የተካተቱበት የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ሰለሆነ፣ነፍስ ያፍነከንካል ፤ትርዒት ያሳያል።
ጋሽ ጸጋዬ በዘይቤዎቹ መዐዛ፣ በምሰላዎቹ ምትሐት ቀልብ ሲስብ፣ ገብረክርስቶስ በሜሎዲዎቹ ብብት ይኮረኩራል። ደበበ ሐሳብ እንደሽንኩርት እየላጠ ያስደምማል። ሁሉም በየራሳቸው ድንኳን የሚሰጡን ጣ'ም አለ።
ላምቦርን("ዶ/ር)ስለዚህ ሲጽፉ፦ Since every one likes pictures and most find pleasure in music,the common indifference to poetry must be due to a failure to realize that poetry is really both.
9 days ago
በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን የሚያሳድገው "ArifSchool" በይፋ ተዋወቀ!
#fastmereja : የሀገሪቱን የትምህርት ዘርፍ የእሴት ሰንሰለት በቴክኖሎጂ ለማቀናጀትና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ብሄራዊ ስትራቴጂን ግቦች ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀው "ArifSchool" የተሰኘ የተቀናጀ የዲጂታል ትምህርት ስነ-ምህዳር በዛሬዉ እለት ይፋ ተደርጓል።
በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጥምረት በአራት ግንባር ቀደም የቴክኖሎጂና የትምህርት ተቋማት ማለትም በአሪፍፔይ (Arifpay)፣ ኤአይቲ (AIT)፣ ገበያ (Gebeya - Dala Studios) እና ኤጁኬሽን ማተርስ (EducationMatters) መካከል የተመሰረተ ነው።
ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ የትምህርት ቤት አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ግብይትን፣ በሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) የታገዙ የመማሪያ መሳሪያዎችን እና የስነ-ምህዳር ምክር አገልግሎትን በአንድ ጥላ ስር የሚያገናኝ ስለመሆኑ ተገልጿል።
በማስተዋወቂያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ እያንዳንዱ ተቋም በዘርፉ ያለውን ልምድና ቴክኖሎጂ አቀናጅቶ ያቀረበ ሲሆን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን፣ የወላጆችን መዋጮ እና የሰራተኞችን ደሞዝ በዲጂታል መንገድ በማዘመን የትምህርት ቤቶችን የፋይናንስ አስተዳደር ሸክም እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሀገሪቱን የዲጂታል ክፍያ በ2030 ሰባት እጥፍ ለማሳደግ ከተቀመጠው ብሄራዊ ግብ ጋር የተናበበ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ብሄራዊ የትምህርት ደረጃን የጠበቀ የትምህርት ቤት ማኔጅመንት እና የኢ‐ለርኒንግ መድረክን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ይህም የተማሪዎችን ክትትል፣ የክፍል መርሃ-ግብር፣ ምዘና እና ምናባዊ ክፍሎች (Virtual Classrooms) በስርዓት ለመምራት ያስችላል፣ተማሪዎችና መምህራን የራሳቸውን የፈጠራ ስራዎች፣ የታሪክ መጽሃፍት፣ የዝግጅት ማቅረቢያዎች እና ድረ-ገጾች እንዲያዘጋጁ የሚያስችሉ የጄነሬቲቭ ኤአይ (Generative Al) ቴክኖሎጂዎችን የሚያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪ የቴክኖሎጂውን ዘላቂነት ለማረጋገጥ የአቅም ግንባታ፣ የስልጠና ድጋፍ፣ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እና የለውጥ አመራር (Change Management) ስራዎችን እንደሚያከናውን ታውቋል።
ይህ ዘመናዊ መፍትሄ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር የሚከናወን ሲሆን፤ በገጠርም ሆነ በከተማ ለሚገኙ የመንግስት፣ የግል እና የህዝብ ትምህርት ቤቶች እኩል ተደራሽ እንዲሆን ተደርጎ መቅረጹ ተገልጿል።
በዛሬዉ እለት ይፋ በተደረገዉ አዲስ ቴክኖሎጂ አራቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን ስምምነት ተፈራርመዋል።
#fastmereja : የሀገሪቱን የትምህርት ዘርፍ የእሴት ሰንሰለት በቴክኖሎጂ ለማቀናጀትና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ብሄራዊ ስትራቴጂን ግቦች ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀው "ArifSchool" የተሰኘ የተቀናጀ የዲጂታል ትምህርት ስነ-ምህዳር በዛሬዉ እለት ይፋ ተደርጓል።
በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጥምረት በአራት ግንባር ቀደም የቴክኖሎጂና የትምህርት ተቋማት ማለትም በአሪፍፔይ (Arifpay)፣ ኤአይቲ (AIT)፣ ገበያ (Gebeya - Dala Studios) እና ኤጁኬሽን ማተርስ (EducationMatters) መካከል የተመሰረተ ነው።
ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ የትምህርት ቤት አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ግብይትን፣ በሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) የታገዙ የመማሪያ መሳሪያዎችን እና የስነ-ምህዳር ምክር አገልግሎትን በአንድ ጥላ ስር የሚያገናኝ ስለመሆኑ ተገልጿል።
በማስተዋወቂያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ እያንዳንዱ ተቋም በዘርፉ ያለውን ልምድና ቴክኖሎጂ አቀናጅቶ ያቀረበ ሲሆን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን፣ የወላጆችን መዋጮ እና የሰራተኞችን ደሞዝ በዲጂታል መንገድ በማዘመን የትምህርት ቤቶችን የፋይናንስ አስተዳደር ሸክም እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሀገሪቱን የዲጂታል ክፍያ በ2030 ሰባት እጥፍ ለማሳደግ ከተቀመጠው ብሄራዊ ግብ ጋር የተናበበ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ብሄራዊ የትምህርት ደረጃን የጠበቀ የትምህርት ቤት ማኔጅመንት እና የኢ‐ለርኒንግ መድረክን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ይህም የተማሪዎችን ክትትል፣ የክፍል መርሃ-ግብር፣ ምዘና እና ምናባዊ ክፍሎች (Virtual Classrooms) በስርዓት ለመምራት ያስችላል፣ተማሪዎችና መምህራን የራሳቸውን የፈጠራ ስራዎች፣ የታሪክ መጽሃፍት፣ የዝግጅት ማቅረቢያዎች እና ድረ-ገጾች እንዲያዘጋጁ የሚያስችሉ የጄነሬቲቭ ኤአይ (Generative Al) ቴክኖሎጂዎችን የሚያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪ የቴክኖሎጂውን ዘላቂነት ለማረጋገጥ የአቅም ግንባታ፣ የስልጠና ድጋፍ፣ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እና የለውጥ አመራር (Change Management) ስራዎችን እንደሚያከናውን ታውቋል።
ይህ ዘመናዊ መፍትሄ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር የሚከናወን ሲሆን፤ በገጠርም ሆነ በከተማ ለሚገኙ የመንግስት፣ የግል እና የህዝብ ትምህርት ቤቶች እኩል ተደራሽ እንዲሆን ተደርጎ መቅረጹ ተገልጿል።
በዛሬዉ እለት ይፋ በተደረገዉ አዲስ ቴክኖሎጂ አራቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን ስምምነት ተፈራርመዋል።
9 days ago
Ethiopian Airlines is proud to be part of one of the leading global trade fairs in the travel, tourism, and hospitality industry, ITB China. From highlighting our rich cultural heritage and exceptional tourism attractions to building meaningful connections with global partners, it was truly an inspiring experience.
#flyethiopian #itbchina #visitethiopia #landoforigins
#flyethiopian #itbchina #visitethiopia #landoforigins
9 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዘመናት ባልቀየሩት ድንቅ ተፈጥሮና ጥንታዊ ማንነት ውስጥ የሚኖር ታላቅና ኩሩ ህዝብ አለ።
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
Sponsored by
Surafel
9 days ago
አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል።
#ethiopia | አፍሪካውያን በራሳቸው ጥረትና አቅም እየገነቧት ያለችውን አህጉር ለዓለም ለማስተዋወቅና ስኬቶቻቸውን ወደ አደባባይ ለማውጣት ያለመ #notwaiting (አልጠብቅም) ዘመቻ ተጀመረ።
ይህ አህጉር አቀፍ ዘመቻ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25, 2026) በአፍሪካ ቀን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ፣ ጆሃንስበርግ፣ ናይሮቢ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተሞች በጋራ ይፋ የተደረገው ይህ ዘመቻ፤ «ኦፖርቹኒቲ አፍሪካ» (Opportunity Africa) በተሰኘ ተቋም የሚመራ ነው።
በአህጉሪቱና በዲያስፖራው የሚገኙ አፍሪካውያን በአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ እያመጡት ያለውን በጎ ተጽዕኖ፣ አዳዲስ ዕይታዎችና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የዘመቻው ዋነኛ መርህ አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል በሚል እምነት ላይ የተመሠረተ ነው።
በአሁኑ ወቅት በርካታ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋማትን እየገነቡና ማኅበረሰባቸውን እየለወጡ ቢሆንም፣ እነዚህ የስኬት ታሪኮች አሁንም ድረስ በችግር፣ በረሃብና በውስንነቶች ላይ ብቻ በሚያተኩሩ አሉታዊ ትረካዎች (narratives) እየተሸፈኑ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዚህ እንቅስቃሴ ዓላማ አፍሪካን በተመለከተ የሚነገሩ ትረካዎችን ሚዛን ለመጠበቅና ፍሬያማ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን፣ ግንባታዎችንና እድገቶችን በጋራ ድምፅ ከፍ አድርጎ ለማሳየት ነው።
ይህ እንቅስቃሴ የጥቂት ስኬታማ ሰዎች ታሪክ ሳይሆን፣ መላው አህጉሪቱ እያሳየችው ያለውን የእድገት ጉዞና አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
አዘጋጆቹ መላው የአፍሪካ ሕዝብና ትውልደ አፍሪካውያን በፈጠራ ሥራዎቻቸው፣ ስኬቶቻቸውና አዳዲስ ሐሳቦቻቸው ላይ ያተኮሩ ታሪኮችን በ#notwaiting የሃሽታግ ምልክት በመጠቀም በማኅበራዊ ሚዲያዎች እንዲያጋሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ፍላጎት ያላቸው ወገኖች www.notwaiting.africa በተሰኘው ድረ-ገጽ ላይ በመግባት የዘመቻውን ማኒፌስቶ መፈረም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ ዘመቻ ዛሬ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ በየወሩ በ25ኛው ቀን እየታደሰ የሚቀጥልና አፍሪካውያን በአንድነት በመሆን የኢንተርኔት ዓለምን በስኬት፣ በፈጠራና በዕድሎች ታሪክ የሚያጥለቀልቁበት ተከታታይ መድረክ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | አፍሪካውያን በራሳቸው ጥረትና አቅም እየገነቧት ያለችውን አህጉር ለዓለም ለማስተዋወቅና ስኬቶቻቸውን ወደ አደባባይ ለማውጣት ያለመ #notwaiting (አልጠብቅም) ዘመቻ ተጀመረ።
ይህ አህጉር አቀፍ ዘመቻ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም (May 25, 2026) በአፍሪካ ቀን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
በአዲስ አበባ፣ ጆሃንስበርግ፣ ናይሮቢ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተሞች በጋራ ይፋ የተደረገው ይህ ዘመቻ፤ «ኦፖርቹኒቲ አፍሪካ» (Opportunity Africa) በተሰኘ ተቋም የሚመራ ነው።
በአህጉሪቱና በዲያስፖራው የሚገኙ አፍሪካውያን በአፍሪካ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ እያመጡት ያለውን በጎ ተጽዕኖ፣ አዳዲስ ዕይታዎችና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የዘመቻው ዋነኛ መርህ አፍሪካውያን ስለ ራሳቸው ያላቸውን አመለካከት ሲቀይሩ፣ ቀሪው ዓለምም ስለ አፍሪካ ያለውን ዕይታ ይቀይራል በሚል እምነት ላይ የተመሠረተ ነው።
በአሁኑ ወቅት በርካታ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎችና የፈጠራ ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋማትን እየገነቡና ማኅበረሰባቸውን እየለወጡ ቢሆንም፣ እነዚህ የስኬት ታሪኮች አሁንም ድረስ በችግር፣ በረሃብና በውስንነቶች ላይ ብቻ በሚያተኩሩ አሉታዊ ትረካዎች (narratives) እየተሸፈኑ መሆኑ ተጠቅሷል።
የዚህ እንቅስቃሴ ዓላማ አፍሪካን በተመለከተ የሚነገሩ ትረካዎችን ሚዛን ለመጠበቅና ፍሬያማ የሆኑ የፈጠራ ስራዎችን፣ ግንባታዎችንና እድገቶችን በጋራ ድምፅ ከፍ አድርጎ ለማሳየት ነው።
ይህ እንቅስቃሴ የጥቂት ስኬታማ ሰዎች ታሪክ ሳይሆን፣ መላው አህጉሪቱ እያሳየችው ያለውን የእድገት ጉዞና አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
አዘጋጆቹ መላው የአፍሪካ ሕዝብና ትውልደ አፍሪካውያን በፈጠራ ሥራዎቻቸው፣ ስኬቶቻቸውና አዳዲስ ሐሳቦቻቸው ላይ ያተኮሩ ታሪኮችን በ#notwaiting የሃሽታግ ምልክት በመጠቀም በማኅበራዊ ሚዲያዎች እንዲያጋሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተጨማሪም ፍላጎት ያላቸው ወገኖች www.notwaiting.africa በተሰኘው ድረ-ገጽ ላይ በመግባት የዘመቻውን ማኒፌስቶ መፈረም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ ዘመቻ ዛሬ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ በየወሩ በ25ኛው ቀን እየታደሰ የሚቀጥልና አፍሪካውያን በአንድነት በመሆን የኢንተርኔት ዓለምን በስኬት፣ በፈጠራና በዕድሎች ታሪክ የሚያጥለቀልቁበት ተከታታይ መድረክ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
10 days ago
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
ግሎባል ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለሙያዎች አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ይህ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ በአካል በመቅረብ ማመልከትና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Email: globalgeneralcon2030gmail.Com
Tel: +251 114 623758 Mob: +251 +251 91 134 0270
Location: Bole next to Garad Mall, Semay Tower 4th Floor Addis Ababa, Ethiopia
ግሎባል ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለሙያዎች አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ይህ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ በአካል በመቅረብ ማመልከትና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Email: globalgeneralcon2030gmail.Com
Tel: +251 114 623758 Mob: +251 +251 91 134 0270
Location: Bole next to Garad Mall, Semay Tower 4th Floor Addis Ababa, Ethiopia
11 days ago
አብረን ከርመን አብረን ሳንሆን ቀረን!
ፋናን እንደተቀላቀልኩ አንድ ሳምንት የተሻገረኝ አይመስለኝም። በወቅቱ 7ኛ ፎቅ ላይ ከነበረው የጋዜጠኞች መሥሪያ (Workstation) እና መሰባሰቢያ ቦታ ተቀምጦ የነበረ አንድ ባለ ጆሮ-ገብ ድምፅ ከወትሮ በተለየ ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ ተቀመጠበት እንድጠጋው በእጁ አመለከተኝ። እዚያ ተቋም ስንገናኝ ለሁለተኛ ጊዜ ቢሆንም፣ ሰላምታውና አቀባበሉ ለከረመ ወዳጅ ይመስል ነበር።
የግራ እጁን ሁለት ጣቶች አገጩ ላይ ጭኖ፣ በቀኝ እጁ ከደረቱ ትይዩ ካስቀመጠው ወፍራም የግል ኮምፒውተር (PC) “መለስተኛ ሳጥን ብንለው😂” ውስጥ ፋይል መበርበር ጀመረ። “ይሄ ልጅ ከተዋወቅን ገና ሁለተኛ ሰላምታ ስሰጠው ነው፤ ምን ይዞብኝ ይሆን?” ብዬ ሳስብ፣ ከመቅጽበት የሆነ ፎቶ አወጣና፣ “ይሄ ልጅ አንተ ነህ አይደል?” አለኝ።
ፎቶውን ሳይ እራሴን ለመካድ ዳዳኝ። ለካስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለን፣ እነሱ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርታዊ ጉዞ ወደ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በመጡ ጊዜ፣ የJOCOSA ፕሬዝዳንት ስለነበርኩ አቀባበልና ግብዣ (የውሃ😂) አድርጌላቸው ነበር። በዚያ ጊዜ ያስቀረነውን ፎቶ ነው መዞ ያሳየኝ። እኔ ግን በፍጹም አላስታወስኩትም ነበር። የተማሪነት ጊዜው አዳነ ከጋዜጠኛው አዳነ ጋር የተራራቁ ናቸው።
ከአዴ ጋር የጓደኝነት ውላችን ከዚያች ቀን የጀመረ ይመስለኛል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ደስ የሚል ቤተሰባዊ ጓደኝነት ፈጥረን ኖረናል። በእኔ ወሳኝ ደስታና ሐዘን ውስጥ እሱ አለ፤ እኔም በተመሳሳይ።
እኔ ባለቤቴን ሳጭ፣ ሽምግልና ከሄዱት ውስጥ አዴ አንዱ ነው። ሳገባም ሚዜዬ ነበር። በተቃራኒው፣ እሱ “እጮኛውን ታገቢኛለሽ?” ሲል ከተገኙት ጥቂት ወዳጆቹ መካከል እኔ ነበርኩ። ሽምግልና ከሄዱት ታላላቅ ሰዎች መካከልም ተገኝቻለሁ።ይሄን ጋብቻ በህግ ለማፅናት ቀበሌ ተገኝተው የጋብቻ ውል(80) ሲፈራረሙም አንዱ እማኝ ነበርኩ።
ይህን ሂደት በታላቅ ሥርዓት ለመቋጨትና ለሰርጉ ሲሰናዳም፣ ሚዜው ሆኜ ከአጠገቡ ለመቆም እኔ ብቻ ሳልሆን፣ ውድ ባለቤቴም የእሱ ባለቤት ሚዜ ሆና የማይረሳውን ቀን በጋራ ለማሳለፍ አቅደን፣ ልብስ ተለክተን፣ መኪና ተከራይተን ዝግጁ ብንሆንም፣ ሰርጉ ሳምንት ሲቀረው በሥራ ምክንያት ከአገር መውጣት ግዴታ ሆነብኝ።
ከዓመታት በፊት ማግባቱን ሲወስንና ሲያሳውቀኝ፣ ቀን ቆጥረን የጋብቻ እቅድ አውጥተን፣ እንደ ወንድም ቀኑን በጋራ ናፍቀን እንደከረምን ሰዎች፣ በዚህ ውብ ቀን አጠገቡ አለመቆም የሚፈጥረው ስሜት ከባድ ቢሆንም፣ መልካም ምኞትን ከማስፈር ውጪ ሌላ አማራጭ የለም።
አዴ እና B2 መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ ከውዷ ባለቤቴ ጋር እንመኝላችኋለን።
Haikemikael_Debisa
ፋናን እንደተቀላቀልኩ አንድ ሳምንት የተሻገረኝ አይመስለኝም። በወቅቱ 7ኛ ፎቅ ላይ ከነበረው የጋዜጠኞች መሥሪያ (Workstation) እና መሰባሰቢያ ቦታ ተቀምጦ የነበረ አንድ ባለ ጆሮ-ገብ ድምፅ ከወትሮ በተለየ ስሜት ውስጥ ሆኖ ወደ ተቀመጠበት እንድጠጋው በእጁ አመለከተኝ። እዚያ ተቋም ስንገናኝ ለሁለተኛ ጊዜ ቢሆንም፣ ሰላምታውና አቀባበሉ ለከረመ ወዳጅ ይመስል ነበር።
የግራ እጁን ሁለት ጣቶች አገጩ ላይ ጭኖ፣ በቀኝ እጁ ከደረቱ ትይዩ ካስቀመጠው ወፍራም የግል ኮምፒውተር (PC) “መለስተኛ ሳጥን ብንለው😂” ውስጥ ፋይል መበርበር ጀመረ። “ይሄ ልጅ ከተዋወቅን ገና ሁለተኛ ሰላምታ ስሰጠው ነው፤ ምን ይዞብኝ ይሆን?” ብዬ ሳስብ፣ ከመቅጽበት የሆነ ፎቶ አወጣና፣ “ይሄ ልጅ አንተ ነህ አይደል?” አለኝ።
ፎቶውን ሳይ እራሴን ለመካድ ዳዳኝ። ለካስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያለን፣ እነሱ ከአ/አ ዩኒቨርሲቲ ለትምህርታዊ ጉዞ ወደ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በመጡ ጊዜ፣ የJOCOSA ፕሬዝዳንት ስለነበርኩ አቀባበልና ግብዣ (የውሃ😂) አድርጌላቸው ነበር። በዚያ ጊዜ ያስቀረነውን ፎቶ ነው መዞ ያሳየኝ። እኔ ግን በፍጹም አላስታወስኩትም ነበር። የተማሪነት ጊዜው አዳነ ከጋዜጠኛው አዳነ ጋር የተራራቁ ናቸው።
ከአዴ ጋር የጓደኝነት ውላችን ከዚያች ቀን የጀመረ ይመስለኛል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ደስ የሚል ቤተሰባዊ ጓደኝነት ፈጥረን ኖረናል። በእኔ ወሳኝ ደስታና ሐዘን ውስጥ እሱ አለ፤ እኔም በተመሳሳይ።
እኔ ባለቤቴን ሳጭ፣ ሽምግልና ከሄዱት ውስጥ አዴ አንዱ ነው። ሳገባም ሚዜዬ ነበር። በተቃራኒው፣ እሱ “እጮኛውን ታገቢኛለሽ?” ሲል ከተገኙት ጥቂት ወዳጆቹ መካከል እኔ ነበርኩ። ሽምግልና ከሄዱት ታላላቅ ሰዎች መካከልም ተገኝቻለሁ።ይሄን ጋብቻ በህግ ለማፅናት ቀበሌ ተገኝተው የጋብቻ ውል(80) ሲፈራረሙም አንዱ እማኝ ነበርኩ።
ይህን ሂደት በታላቅ ሥርዓት ለመቋጨትና ለሰርጉ ሲሰናዳም፣ ሚዜው ሆኜ ከአጠገቡ ለመቆም እኔ ብቻ ሳልሆን፣ ውድ ባለቤቴም የእሱ ባለቤት ሚዜ ሆና የማይረሳውን ቀን በጋራ ለማሳለፍ አቅደን፣ ልብስ ተለክተን፣ መኪና ተከራይተን ዝግጁ ብንሆንም፣ ሰርጉ ሳምንት ሲቀረው በሥራ ምክንያት ከአገር መውጣት ግዴታ ሆነብኝ።
ከዓመታት በፊት ማግባቱን ሲወስንና ሲያሳውቀኝ፣ ቀን ቆጥረን የጋብቻ እቅድ አውጥተን፣ እንደ ወንድም ቀኑን በጋራ ናፍቀን እንደከረምን ሰዎች፣ በዚህ ውብ ቀን አጠገቡ አለመቆም የሚፈጥረው ስሜት ከባድ ቢሆንም፣ መልካም ምኞትን ከማስፈር ውጪ ሌላ አማራጭ የለም።
አዴ እና B2 መልካም ጋብቻ እንዲሆንላችሁ ከውዷ ባለቤቴ ጋር እንመኝላችኋለን።
Haikemikael_Debisa
11 days ago
የወህኒ አምባ ታሪካዊ ተውኔት በልዩ ስነ ስርዓት ተመረቀ
#ethiopia | የወህኒ አምባ የተሰኘው አዲስ ታሪካዊ ትያትር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት አዳራሽ ለተመልካች መብቃት ጀምሯል።
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተፅፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ አዘጋጅነት ለክብር መድረክ የበቃው ይህ ተውኔት በምረቃው ዕለት እጅግ ማራኪ እና የተዋጣለት አቀራረብ ለተመልካቾች አሳይቷል።
ይህ ታሪካዊ የጥበብ ስራ ከዝግጅት ጥበቡ ጀምሮ ከማጀቢያ ፊልም (AI ቅንጭብጭቦች) ጋር የተዋሃደበት መንገድ፣ የታሪኩ ጥልቅነት፣ የተዋናዮቹ የትወና ድንቅ ብቃት እንዲሁም የኬሮግራፈር (ዳንስ ውህደቱ) እንዲሁም የመድረክ እነጻ እጅግ የሚደነቅ እንደነበር ተመልካቾች ገልጸዋል።
የተውኔቱ ደራሲ ጸሐፊ ተውኔት መልካሙ ዘሪሁን የትያትሩ አጽመ ታሪክና መቼቱ እንደገለጹት፣ ከ300 እስከ 400 ዓመታት ወደ ኋላ በመመለስ በወቅቱ የነበረውን የአለባበስ፣ የምግብ እና የጸጉር አሰራር ዘይቤ በዝርዝር አጥንቶ በመድረክ ላይ ህያው ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በርካታ የኢትዮጵያ ነገስታት ሀገር ለመምራት ሲዘጋጁ ይማሩበት በነበረው ወህኒ አምባ ታሪካዊ ስፍራ ላይ የሚያጠነጥን ነው።
ይህ ታሪካዊ ቦታ ነገስታት የቅስና፣ የድቁና፣ የአካል ብቃት፣ የጦርነት እንዲሁም የህክምና እውቀቶችን የሚቀስሙበት የትምህርት ማዕከል እንጂ የስቃይ ማሰሪያ እንዳልነበረ ታሪኩ በግልጽ ያሳያል።
ይህንን ታላቅ ስራ ወደ መድረክ ለማምጣት ከሰባት ወራት በላይ የፈጀ ሰፊ የታሪክ ምርምርና ዝግጅት ተደርጓል።
አዲሱ ትውልድ የሀገሩን ቀደምት ታሪክ እና አባቶች አገርን ያቆዩበትን ጥበብ ከዚህ የጥበብ ስራ በስፋት እንደሚማርበት ታምኖበታል።
ከዚህ ቀደም ንጉሥ አርማህ እና ህንደኬ የተሰኙ ተወዳጅ ታሪካዊ ተውኔቶችን ለተመልካች ያቀረቡት አዘጋጆች፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ መልክ የተከፈቱት የባህልና ትያትር አዳራሾች መኖራቸው የትያትር ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም መላው ህዝብና የጥበብ አፍቃሪ ይህን አዲስ ቲያትር በመመልከት በታሪኩ እንዲማር፣ እንዲደሰትና እንዲኮራ ጥሪ ቀርቧል።
በዚህ የኪነ ጥበብ ስራ ላይ የረዳት አዘጋጅነት ሚናውን ተስፋዬ ሲማ ሲረከቡ፣ ኤልያስ ደጀኔ፣ ትዕግሥት ዋሲይሁን፣ ራሄል ኤርሚያስ፣ መዓዛ ገብረህይወት፣ ዘቢባ ሀይል፣ ፋሲል ግርማ፣ ያሬድ ኤጉ፣ ኢንስፔክተር መኮንን ምጉሴ፣ ፋአድ መሀመድ፣ ሳሙሶን ግርማ፣ አያሌው ገብረህይወት፣ ፍቃዱ ሳህሌ፣ አሉላ ወንድሙ፣ ከድር ዮናስ፣ ሳሙኤል መስፍን፣ ተፈሪ ደጀኑ፣ መቼልይሽ ታከለ፣ ተመስገን መርሶ እና ሰሎሞን ሞገስን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ተዋንያን የየራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ገጸ ባህሪያቱን ህያው አድርገው አቅርበውታል።
#ወህኒአምባ #ታሪካዊቲያትር #ኪነጥበብ #የኢትዮጵያታሪክ #የባህልናቲያትር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የወህኒ አምባ የተሰኘው አዲስ ታሪካዊ ትያትር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት አዳራሽ ለተመልካች መብቃት ጀምሯል።
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተፅፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ አዘጋጅነት ለክብር መድረክ የበቃው ይህ ተውኔት በምረቃው ዕለት እጅግ ማራኪ እና የተዋጣለት አቀራረብ ለተመልካቾች አሳይቷል።
ይህ ታሪካዊ የጥበብ ስራ ከዝግጅት ጥበቡ ጀምሮ ከማጀቢያ ፊልም (AI ቅንጭብጭቦች) ጋር የተዋሃደበት መንገድ፣ የታሪኩ ጥልቅነት፣ የተዋናዮቹ የትወና ድንቅ ብቃት እንዲሁም የኬሮግራፈር (ዳንስ ውህደቱ) እንዲሁም የመድረክ እነጻ እጅግ የሚደነቅ እንደነበር ተመልካቾች ገልጸዋል።
የተውኔቱ ደራሲ ጸሐፊ ተውኔት መልካሙ ዘሪሁን የትያትሩ አጽመ ታሪክና መቼቱ እንደገለጹት፣ ከ300 እስከ 400 ዓመታት ወደ ኋላ በመመለስ በወቅቱ የነበረውን የአለባበስ፣ የምግብ እና የጸጉር አሰራር ዘይቤ በዝርዝር አጥንቶ በመድረክ ላይ ህያው ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በርካታ የኢትዮጵያ ነገስታት ሀገር ለመምራት ሲዘጋጁ ይማሩበት በነበረው ወህኒ አምባ ታሪካዊ ስፍራ ላይ የሚያጠነጥን ነው።
ይህ ታሪካዊ ቦታ ነገስታት የቅስና፣ የድቁና፣ የአካል ብቃት፣ የጦርነት እንዲሁም የህክምና እውቀቶችን የሚቀስሙበት የትምህርት ማዕከል እንጂ የስቃይ ማሰሪያ እንዳልነበረ ታሪኩ በግልጽ ያሳያል።
ይህንን ታላቅ ስራ ወደ መድረክ ለማምጣት ከሰባት ወራት በላይ የፈጀ ሰፊ የታሪክ ምርምርና ዝግጅት ተደርጓል።
አዲሱ ትውልድ የሀገሩን ቀደምት ታሪክ እና አባቶች አገርን ያቆዩበትን ጥበብ ከዚህ የጥበብ ስራ በስፋት እንደሚማርበት ታምኖበታል።
ከዚህ ቀደም ንጉሥ አርማህ እና ህንደኬ የተሰኙ ተወዳጅ ታሪካዊ ተውኔቶችን ለተመልካች ያቀረቡት አዘጋጆች፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ መልክ የተከፈቱት የባህልና ትያትር አዳራሾች መኖራቸው የትያትር ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም መላው ህዝብና የጥበብ አፍቃሪ ይህን አዲስ ቲያትር በመመልከት በታሪኩ እንዲማር፣ እንዲደሰትና እንዲኮራ ጥሪ ቀርቧል።
በዚህ የኪነ ጥበብ ስራ ላይ የረዳት አዘጋጅነት ሚናውን ተስፋዬ ሲማ ሲረከቡ፣ ኤልያስ ደጀኔ፣ ትዕግሥት ዋሲይሁን፣ ራሄል ኤርሚያስ፣ መዓዛ ገብረህይወት፣ ዘቢባ ሀይል፣ ፋሲል ግርማ፣ ያሬድ ኤጉ፣ ኢንስፔክተር መኮንን ምጉሴ፣ ፋአድ መሀመድ፣ ሳሙሶን ግርማ፣ አያሌው ገብረህይወት፣ ፍቃዱ ሳህሌ፣ አሉላ ወንድሙ፣ ከድር ዮናስ፣ ሳሙኤል መስፍን፣ ተፈሪ ደጀኑ፣ መቼልይሽ ታከለ፣ ተመስገን መርሶ እና ሰሎሞን ሞገስን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ተዋንያን የየራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ገጸ ባህሪያቱን ህያው አድርገው አቅርበውታል።
#ወህኒአምባ #ታሪካዊቲያትር #ኪነጥበብ #የኢትዮጵያታሪክ #የባህልናቲያትር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
11 days ago
የወህኒ አምባ ታሪካዊ ተውኔት በልዩ ስነ ስርዓት ተመረቀ
#ethiopia | የወህኒ አምባ የተሰኘው አዲስ ታሪካዊ ትያትር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት አዳራሽ ለተመልካች መብቃት ጀምሯል።
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተፅፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ አዘጋጅነት ለክብር መድረክ የበቃው ይህ ተውኔት በምረቃው ዕለት እጅግ ማራኪ እና የተዋጣለት አቀራረብ ለተመልካቾች አሳይቷል።
ይህ ታሪካዊ የጥበብ ስራ ከዝግጅት ጥበቡ ጀምሮ ከማጀቢያ ፊልም (AI ቅንጭብጭቦች) ጋር የተዋሃደበት መንገድ፣ የታሪኩ ጥልቅነት፣ የተዋናዮቹ የትወና ድንቅ ብቃት እንዲሁም የኬሮግራፈር (ዳንስ ውህደቱ) እንዲሁም የመድረክ እነጻ እጅግ የሚደነቅ እንደነበር ተመልካቾች ገልጸዋል።
የተውኔቱ ደራሲ ጸሐፊ ተውኔት መልካሙ ዘሪሁን የትያትሩ አጽመ ታሪክና መቼቱ እንደገለጹት፣ ከ300 እስከ 400 ዓመታት ወደ ኋላ በመመለስ በወቅቱ የነበረውን የአለባበስ፣ የምግብ እና የጸጉር አሰራር ዘይቤ በዝርዝር አጥንቶ በመድረክ ላይ ህያው ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በርካታ የኢትዮጵያ ነገስታት ሀገር ለመምራት ሲዘጋጁ ይማሩበት በነበረው ወህኒ አምባ ታሪካዊ ስፍራ ላይ የሚያጠነጥን ነው።
ይህ ታሪካዊ ቦታ ነገስታት የቅስና፣ የድቁና፣ የአካል ብቃት፣ የጦርነት እንዲሁም የህክምና እውቀቶችን የሚቀስሙበት የትምህርት ማዕከል እንጂ የስቃይ ማሰሪያ እንዳልነበረ ታሪኩ በግልጽ ያሳያል።
ይህንን ታላቅ ስራ ወደ መድረክ ለማምጣት ከሰባት ወራት በላይ የፈጀ ሰፊ የታሪክ ምርምርና ዝግጅት ተደርጓል።
አዲሱ ትውልድ የሀገሩን ቀደምት ታሪክ እና አባቶች አገርን ያቆዩበትን ጥበብ ከዚህ የጥበብ ስራ በስፋት እንደሚማርበት ታምኖበታል።
ከዚህ ቀደም ንጉሥ አርማህ እና ህንደኬ የተሰኙ ተወዳጅ ታሪካዊ ተውኔቶችን ለተመልካች ያቀረቡት አዘጋጆች፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ መልክ የተከፈቱት የባህልና ትያትር አዳራሾች መኖራቸው የትያትር ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም መላው ህዝብና የጥበብ አፍቃሪ ይህን አዲስ ቲያትር በመመልከት በታሪኩ እንዲማር፣ እንዲደሰትና እንዲኮራ ጥሪ ቀርቧል።
በዚህ የኪነ ጥበብ ስራ ላይ የረዳት አዘጋጅነት ሚናውን ተስፋዬ ሲማ ሲረከቡ፣ ኤልያስ ደጀኔ፣ ትዕግሥት ዋሲይሁን፣ ራሄል ኤርሚያስ፣ መዓዛ ገብረህይወት፣ ዘቢባ ሀይል፣ ፋሲል ግርማ፣ ያሬድ ኤጉ፣ ኢንስፔክተር መኮንን ምጉሴ፣ ፋአድ መሀመድ፣ ሳሙሶን ግርማ፣ አያሌው ገብረህይወት፣ ፍቃዱ ሳህሌ፣ አሉላ ወንድሙ፣ ከድር ዮናስ፣ ሳሙኤል መስፍን፣ ተፈሪ ደጀኑ፣ መቼልይሽ ታከለ፣ ተመስገን መርሶ እና ሰሎሞን ሞገስን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ተዋንያን የየራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ገጸ ባህሪያቱን ህያው አድርገው አቅርበውታል።
#ወህኒአምባ #ታሪካዊቲያትር #ኪነጥበብ #የኢትዮጵያታሪክ #የባህልናቲያትር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የወህኒ አምባ የተሰኘው አዲስ ታሪካዊ ትያትር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትር ቤት አዳራሽ ለተመልካች መብቃት ጀምሯል።
በደራሲ መልካሙ ዘሪሁን ተፅፎ በዳግማዊ አመለወርቅ ፈይሳ አዘጋጅነት ለክብር መድረክ የበቃው ይህ ተውኔት በምረቃው ዕለት እጅግ ማራኪ እና የተዋጣለት አቀራረብ ለተመልካቾች አሳይቷል።
ይህ ታሪካዊ የጥበብ ስራ ከዝግጅት ጥበቡ ጀምሮ ከማጀቢያ ፊልም (AI ቅንጭብጭቦች) ጋር የተዋሃደበት መንገድ፣ የታሪኩ ጥልቅነት፣ የተዋናዮቹ የትወና ድንቅ ብቃት እንዲሁም የኬሮግራፈር (ዳንስ ውህደቱ) እንዲሁም የመድረክ እነጻ እጅግ የሚደነቅ እንደነበር ተመልካቾች ገልጸዋል።
የተውኔቱ ደራሲ ጸሐፊ ተውኔት መልካሙ ዘሪሁን የትያትሩ አጽመ ታሪክና መቼቱ እንደገለጹት፣ ከ300 እስከ 400 ዓመታት ወደ ኋላ በመመለስ በወቅቱ የነበረውን የአለባበስ፣ የምግብ እና የጸጉር አሰራር ዘይቤ በዝርዝር አጥንቶ በመድረክ ላይ ህያው ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል።
ጎንደር ውስጥ በሚገኘውና በርካታ የኢትዮጵያ ነገስታት ሀገር ለመምራት ሲዘጋጁ ይማሩበት በነበረው ወህኒ አምባ ታሪካዊ ስፍራ ላይ የሚያጠነጥን ነው።
ይህ ታሪካዊ ቦታ ነገስታት የቅስና፣ የድቁና፣ የአካል ብቃት፣ የጦርነት እንዲሁም የህክምና እውቀቶችን የሚቀስሙበት የትምህርት ማዕከል እንጂ የስቃይ ማሰሪያ እንዳልነበረ ታሪኩ በግልጽ ያሳያል።
ይህንን ታላቅ ስራ ወደ መድረክ ለማምጣት ከሰባት ወራት በላይ የፈጀ ሰፊ የታሪክ ምርምርና ዝግጅት ተደርጓል።
አዲሱ ትውልድ የሀገሩን ቀደምት ታሪክ እና አባቶች አገርን ያቆዩበትን ጥበብ ከዚህ የጥበብ ስራ በስፋት እንደሚማርበት ታምኖበታል።
ከዚህ ቀደም ንጉሥ አርማህ እና ህንደኬ የተሰኙ ተወዳጅ ታሪካዊ ተውኔቶችን ለተመልካች ያቀረቡት አዘጋጆች፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ መልክ የተከፈቱት የባህልና ትያትር አዳራሾች መኖራቸው የትያትር ኢንዱስትሪውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነቃቃው መሆኑን ጠቁመዋል።
በመጨረሻም መላው ህዝብና የጥበብ አፍቃሪ ይህን አዲስ ቲያትር በመመልከት በታሪኩ እንዲማር፣ እንዲደሰትና እንዲኮራ ጥሪ ቀርቧል።
በዚህ የኪነ ጥበብ ስራ ላይ የረዳት አዘጋጅነት ሚናውን ተስፋዬ ሲማ ሲረከቡ፣ ኤልያስ ደጀኔ፣ ትዕግሥት ዋሲይሁን፣ ራሄል ኤርሚያስ፣ መዓዛ ገብረህይወት፣ ዘቢባ ሀይል፣ ፋሲል ግርማ፣ ያሬድ ኤጉ፣ ኢንስፔክተር መኮንን ምጉሴ፣ ፋአድ መሀመድ፣ ሳሙሶን ግርማ፣ አያሌው ገብረህይወት፣ ፍቃዱ ሳህሌ፣ አሉላ ወንድሙ፣ ከድር ዮናስ፣ ሳሙኤል መስፍን፣ ተፈሪ ደጀኑ፣ መቼልይሽ ታከለ፣ ተመስገን መርሶ እና ሰሎሞን ሞገስን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ተዋንያን የየራሳቸውን ድርሻ በመወጣት ገጸ ባህሪያቱን ህያው አድርገው አቅርበውታል።
#ወህኒአምባ #ታሪካዊቲያትር #ኪነጥበብ #የኢትዮጵያታሪክ #የባህልናቲያትር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
12 days ago
የፌስቡክ ባለቤት ሜታ
8 ሺህ ሰራተኞችን አባረረ
ሜታ ኩባንያውን ይበልጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ለማስቻል በያዘው ትልቅ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰራተኞችን ማባረሩ ተዘግቧል። የኩባንያውን አጠቃላይ አለም አቀፍ የስራ ኃይል 10% ያህል የሚነካው ይህ የስራ ስንብት የመጣው፣ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማርክ ዙከርበርግ በ-AI ቴክኖሎጂ ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለማድረግ በመወሰኑ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ከነበሩበት የስራ መደብ በማንሳት ከ-AI ጋር በተያያዙ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲመደቡ አድርጓል። ይህ ድንገተኛ ለውጥ በሰራተኞች መካከል ስለ ስራ ዋስትና፣ በስራ ቦታ ላይ ስላለው የመረጃ አጠቃቀምና በኩባንያው ውስጥ እያደገ ስለመጣው የ-AI ሚና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።
Addis_News
Addis_Newsየፌስቡክ ባለቤት ሜታ
8 ሺህ ሰራተኞችን አባረረ
ሜታ ኩባንያውን ይበልጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ለማስቻል በያዘው ትልቅ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰራተኞችን ማባረሩ ተዘግቧል። የኩባንያውን አጠቃላይ አለም አቀፍ የስራ ኃይል 10% ያህል የሚነካው ይህ የስራ ስንብት የመጣው፣ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማርክ ዙከርበርግ በ-AI ቴክኖሎጂ ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለማድረግ በመወሰኑ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ከነበሩበት የስራ መደብ በማንሳት ከ-AI ጋር በተያያዙ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲመደቡ አድርጓል። ይህ ድንገተኛ ለውጥ በሰራተኞች መካከል ስለ ስራ ዋስትና፣ በስራ ቦታ ላይ ስላለው የመረጃ አጠቃቀምና በኩባንያው ውስጥ እያደገ ስለመጣው የ-AI ሚና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
8 ሺህ ሰራተኞችን አባረረ
ሜታ ኩባንያውን ይበልጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ለማስቻል በያዘው ትልቅ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰራተኞችን ማባረሩ ተዘግቧል። የኩባንያውን አጠቃላይ አለም አቀፍ የስራ ኃይል 10% ያህል የሚነካው ይህ የስራ ስንብት የመጣው፣ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማርክ ዙከርበርግ በ-AI ቴክኖሎጂ ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለማድረግ በመወሰኑ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ከነበሩበት የስራ መደብ በማንሳት ከ-AI ጋር በተያያዙ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲመደቡ አድርጓል። ይህ ድንገተኛ ለውጥ በሰራተኞች መካከል ስለ ስራ ዋስትና፣ በስራ ቦታ ላይ ስላለው የመረጃ አጠቃቀምና በኩባንያው ውስጥ እያደገ ስለመጣው የ-AI ሚና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።
Addis_News
Addis_Newsየፌስቡክ ባለቤት ሜታ
8 ሺህ ሰራተኞችን አባረረ
ሜታ ኩባንያውን ይበልጥ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ላይ ትኩረት እንዲያደርግ ለማስቻል በያዘው ትልቅ መዋቅራዊ ለውጥ ወደ 8,000 የሚጠጉ ሰራተኞችን ማባረሩ ተዘግቧል። የኩባንያውን አጠቃላይ አለም አቀፍ የስራ ኃይል 10% ያህል የሚነካው ይህ የስራ ስንብት የመጣው፣ ዋና ስራ አስፈፃሚው ማርክ ዙከርበርግ በ-AI ቴክኖሎጂ ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ለማድረግ በመወሰኑ መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚህም በተጨማሪ ኩባንያው በሺዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ከነበሩበት የስራ መደብ በማንሳት ከ-AI ጋር በተያያዙ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲመደቡ አድርጓል። ይህ ድንገተኛ ለውጥ በሰራተኞች መካከል ስለ ስራ ዋስትና፣ በስራ ቦታ ላይ ስላለው የመረጃ አጠቃቀምና በኩባንያው ውስጥ እያደገ ስለመጣው የ-AI ሚና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
12 days ago
Truly a night to remember. More of the Gala Dinner that concluded Ethiopian Airlines’ series of celebrations commemorating the airline’s 80th anniversary since commencing service. #flyethiopian #80yearsofexcellence