20 hours ago
የሙቀት ማዕበል በሰሜን ኮሪያ፡ መንግሥት ዜጎች የውሻ ሥጋ ሾርባ እንዲመገቡ መከረ
በሰሜን ኮሪያ ታሪካዊ የሙቀት ማዕበል በመከሰቱ መንግሥት ዜጎች አካላቸውን ለማቀዝቀዝ የውሻ ሥጋ ሾርባ እንዲመገቡ መከረ።
በሀገሪቱ የሙቀት መጠን ከዚህ ቀደም ተመዝግቦ የማያውቅ 36.7 ዲግሪ ሴልሺየስ የደረሰ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ የአየር ሁኔታ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል። 'ሳምቦክ' በተሰኘው በዚህ የከፋ የሙቀት ወቅት የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን እንደ የውሻ ሥጋ ሾርባ፣ የዓሣ ገንፎ፣ ሀብሐብ እና ዱባ ያሉ ምግቦች የሰውነትን ጥንካሬ ለመጠበቅና ሙቀቱን ለመቋቋም ይረዳሉ ብለዋል።
የኮሪያ ማዕከላዊ ዜና ኤጀንሲ (KCNA) እንደገለጸው፣ በዋና ከተማዋ ፒዮንግያንግ የሚገኙ ምግብ ቤቶች እነዚህን ባህላዊ ምግቦች ለሚፈልጉ ደንበኞች አስተናጋጅነት እየሰጡ ይገኛሉ።
ጎረቤት ደቡብ ኮሪያ ከሙቀት ማዕበሉ ጋር በተያያዘ ከ20 በላይ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ብታረጋግጥም፣ ሰሜን ኮሪያ እስካሁን የሞት መረጃ አላወጣችም።
Seledadotio
Seledadotio
በሰሜን ኮሪያ ታሪካዊ የሙቀት ማዕበል በመከሰቱ መንግሥት ዜጎች አካላቸውን ለማቀዝቀዝ የውሻ ሥጋ ሾርባ እንዲመገቡ መከረ።
በሀገሪቱ የሙቀት መጠን ከዚህ ቀደም ተመዝግቦ የማያውቅ 36.7 ዲግሪ ሴልሺየስ የደረሰ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ የአየር ሁኔታ ታሪክ ከፍተኛው ሆኖ ተመዝግቧል። 'ሳምቦክ' በተሰኘው በዚህ የከፋ የሙቀት ወቅት የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን እንደ የውሻ ሥጋ ሾርባ፣ የዓሣ ገንፎ፣ ሀብሐብ እና ዱባ ያሉ ምግቦች የሰውነትን ጥንካሬ ለመጠበቅና ሙቀቱን ለመቋቋም ይረዳሉ ብለዋል።
የኮሪያ ማዕከላዊ ዜና ኤጀንሲ (KCNA) እንደገለጸው፣ በዋና ከተማዋ ፒዮንግያንግ የሚገኙ ምግብ ቤቶች እነዚህን ባህላዊ ምግቦች ለሚፈልጉ ደንበኞች አስተናጋጅነት እየሰጡ ይገኛሉ።
ጎረቤት ደቡብ ኮሪያ ከሙቀት ማዕበሉ ጋር በተያያዘ ከ20 በላይ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ብታረጋግጥም፣ ሰሜን ኮሪያ እስካሁን የሞት መረጃ አላወጣችም።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዩኤን ዋች ‹‹የኤርትራ በሰብአዊ ምክር ቤት መመረጥ አስከፊ ቀልድ ነው›› አለ፡፡ መቀመጫውን በጄኔቭ ያደረገውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን አሰራር የሚከታተለው ‹ዩኤን ዋች›› ዛሬ ባወጣው መግለጫ ኤርትራ በተመድ ሰብአዊ መብት ምክር ቤት ውስጥ የማህበራዊ መድረክ ሊቀመንበር ሆና መመረጧን አጥብቆ እንደሚቃወም ገለፀ፡፡ ውሳኔውንም ‹‹በአለም ላይ ካሉ ጨቋኝ መንግስታት አንዱን የሰብአዊ መብትን ለማሳደግ በሚጥር አካል ውስጥ ሀላፊነት መስጠር አስከፊ ቀልድ ነው›› ብሎታል፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ሂሌል ኑየር ሲናገሩ ‹‹ኤርትራ በወታደራዊ ሀይል የምትተዳደር የአንድ ፓርቲ አምባገነን አገር ስትሆን በፍሪደም ሀውስ ከ100 ነጥብ ውስጥ 3 ያገኘች ናት፡፡ ይህ ማለት የሰብአዊ መብት ሪከርዷ እጅግ የከፋ ነው›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹የኤርትራ መንግስት እ.ኤ.አ ከ1993 አገሪቱ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ አንስቶ ምንም አይነት ብሄራዊ ምርጫ አላካሄደም፡፡
እንደባርነት የሚቆጠር የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎትን ያስፈፅማል፡፡ የሚተቹትንና ጋዜጠኞችን ለአስርት አመታት ያለምንም ክስ ያስራል፡፡ የፖለቲካ እስረኞችንና የሀይማኖት አባቶችን ያሰቃያል፡፡ ይህ የአፍሪካ ሰሜን ኮሪያ ተብሎ የሚጠራው መንግስት ከሰብአዊ መብቶች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ የኤርትራን መንግስት እዚህ ወንበር ላይ ማስቀመጥ እጅግ መጥፎ ቀልድ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የራሱን ደንቦች ማክበር እያቃተው ለመሆኑ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቀሱት ዳይሬክተሩ አስከትለውም ‹‹በሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ ውስጥ የተወከሉትን ሁለንተናዊ መብቶች እንደሚከላከሉ የሚናገሩ መንግስታት በተለይም እንደፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድስ፣ ጣሊያን፣ ስፔን፣ ብራዚልና ስዊዘርላንድ የመሳሰሉ የምክር ቤቱ አባላት ይህንን የኤርትራን ሹመት አውግዘው መግለጫ እንዲያወጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ይህ አፀያፊ ሹመት እንዲቀለበስ በማድረግም የኤርትራ መንግስት በሰብአዊ መብት ረገድ ምንም እውቅና እንዳይሰጠው ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል፡፡ በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህ ሹመት አምባገነንነትን የሚሸልምና የሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ የተነሳለትን አላማ የሚክድ ነው፡፡ አለም ይህንን እየተመለከተ ነው፡፡ ዝም የሚሉ ዲሞክራሲዎች ለዚህ አሳፋሪ ውሳኔ ሀላፊነቱን ይወስዳሉ›› በማለት መግለፃቸውን ከመግለጫው ላይ ተመልክተናል፡፡
እንደባርነት የሚቆጠር የግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎትን ያስፈፅማል፡፡ የሚተቹትንና ጋዜጠኞችን ለአስርት አመታት ያለምንም ክስ ያስራል፡፡ የፖለቲካ እስረኞችንና የሀይማኖት አባቶችን ያሰቃያል፡፡ ይህ የአፍሪካ ሰሜን ኮሪያ ተብሎ የሚጠራው መንግስት ከሰብአዊ መብቶች ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፡፡ የኤርትራን መንግስት እዚህ ወንበር ላይ ማስቀመጥ እጅግ መጥፎ ቀልድ ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡ የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የራሱን ደንቦች ማክበር እያቃተው ለመሆኑ ይህ ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቀሱት ዳይሬክተሩ አስከትለውም ‹‹በሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ ውስጥ የተወከሉትን ሁለንተናዊ መብቶች እንደሚከላከሉ የሚናገሩ መንግስታት በተለይም እንደፈረንሳይ፣ እንግሊዝ፣ ኔዘርላንድስ፣ ጣሊያን፣ ስፔን፣ ብራዚልና ስዊዘርላንድ የመሳሰሉ የምክር ቤቱ አባላት ይህንን የኤርትራን ሹመት አውግዘው መግለጫ እንዲያወጡ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ይህ አፀያፊ ሹመት እንዲቀለበስ በማድረግም የኤርትራ መንግስት በሰብአዊ መብት ረገድ ምንም እውቅና እንዳይሰጠው ማድረግ ያስፈልጋል›› ብለዋል፡፡ በማጠቃለያቸውም ‹‹ይህ ሹመት አምባገነንነትን የሚሸልምና የሰብአዊ መብት ምክር ቤቱ የተነሳለትን አላማ የሚክድ ነው፡፡ አለም ይህንን እየተመለከተ ነው፡፡ ዝም የሚሉ ዲሞክራሲዎች ለዚህ አሳፋሪ ውሳኔ ሀላፊነቱን ይወስዳሉ›› በማለት መግለፃቸውን ከመግለጫው ላይ ተመልክተናል፡፡
3 days ago
ሰሜን ኮሪያ ወደ ጃፓን ባሕር ባሊስቲክ ሚሳይል አስወነጨፈ
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ከምሥራቅ ጠረፏ ከዎንሳን (Wonsan) አካባቢ ወደ ጃፓን ባሕር (በደቡብ ኮሪያ “ምሥራቅ ባሕር” ተብሎ የሚጠራው) አጭር ርቀት የሚጓዝ ተጠርጣሪ ባሊስቲክ ሚሳይል ማስወንጨፏን የደቡብ ኮሪያ ጦር እና የጃፓን ባሕር ዳርቻ ጥበቃ አስታውቀዋል።
በጃፓን ባለሥልጣናት መረጃ መሠረት ሚሳይሉ በጃፓን ግዛት ወይም በኢኮኖሚያዊ የባሕር ቀጠናዋ (EEZ) ውስጥ አላረፈም፤ እስካሁንም የደረሰ ጉዳት ወይም ሰው ጉዳት አልተዘገበም።
የደቡብ ኮሪያ፣ የአሜሪካ እና የጃፓን ወታደራዊ ኃይሎች የሚሳይሉን አይነትና የበረራ መረጃ በጋራ እየመረመሩ ነው።
ይህ የሚሳይል ሙከራ በአሜሪካና በደቡብ ኮሪያ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶች ሊጀመሩ ጥቂት ቀናት ሲቀሩ የተፈጸመ ሲሆን፣ ፒዮንግያንግ እነዚህን ልምምዶች ለወረራ ዝግጅት አድርጋ እንደምትመለከታቸው ትገልጻለች።
ከቀናት በፊትም ሰሜን ኮሪያ በጃፓን የመከላከያ አቅም መስፋፋት ምክንያት “ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች” ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር።
የደቡብ ኮሪያ እና የጃፓን መንግሥታት የሚሳይሉን ሙከራ በማውገዝ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔዎችን የሚጥስ ነው ብለዋል፤ በቀጣይ ተጨማሪ የሚሳይል ሙከራዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም በከፍተኛ ንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | ሰሜን ኮሪያ ዛሬ ከምሥራቅ ጠረፏ ከዎንሳን (Wonsan) አካባቢ ወደ ጃፓን ባሕር (በደቡብ ኮሪያ “ምሥራቅ ባሕር” ተብሎ የሚጠራው) አጭር ርቀት የሚጓዝ ተጠርጣሪ ባሊስቲክ ሚሳይል ማስወንጨፏን የደቡብ ኮሪያ ጦር እና የጃፓን ባሕር ዳርቻ ጥበቃ አስታውቀዋል።
በጃፓን ባለሥልጣናት መረጃ መሠረት ሚሳይሉ በጃፓን ግዛት ወይም በኢኮኖሚያዊ የባሕር ቀጠናዋ (EEZ) ውስጥ አላረፈም፤ እስካሁንም የደረሰ ጉዳት ወይም ሰው ጉዳት አልተዘገበም።
የደቡብ ኮሪያ፣ የአሜሪካ እና የጃፓን ወታደራዊ ኃይሎች የሚሳይሉን አይነትና የበረራ መረጃ በጋራ እየመረመሩ ነው።
ይህ የሚሳይል ሙከራ በአሜሪካና በደቡብ ኮሪያ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶች ሊጀመሩ ጥቂት ቀናት ሲቀሩ የተፈጸመ ሲሆን፣ ፒዮንግያንግ እነዚህን ልምምዶች ለወረራ ዝግጅት አድርጋ እንደምትመለከታቸው ትገልጻለች።
ከቀናት በፊትም ሰሜን ኮሪያ በጃፓን የመከላከያ አቅም መስፋፋት ምክንያት “ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች” ልትወስድ እንደምትችል አስጠንቅቃ ነበር።
የደቡብ ኮሪያ እና የጃፓን መንግሥታት የሚሳይሉን ሙከራ በማውገዝ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክር ቤት ውሳኔዎችን የሚጥስ ነው ብለዋል፤ በቀጣይ ተጨማሪ የሚሳይል ሙከራዎች ሊኖሩ እንደሚችሉም በከፍተኛ ንቃት እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
12 days ago
🚨በየ5 ደቂቃው ምስል የሚያነሳውና ሰላይ የሆነው የስማርት ፎን ምስጢር ይፋ ሆነ‼️ከሰሜን ኮሪያ በምስጢር ተሰርቆ የወጣ አንድ የስማርት ፎን ስልክ፣ የመንግስቱ አገዛዝ የዜጎቹን እያንዳንዱን እንቅስቃሴ ምን ያህል በአስፈሪ ሁኔታ እንደሚቆጣጠር ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጓል።
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
19 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሰሜን ኮሪያ እና የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሞስኮ ተገናኝተው መወያየታቸውን ተከትሎ፣ ፕዮንግያንግ በዩክሬን ላይ ለምታካሂደው ጦርነት ለሞስኮ ያላትን ሙሉና ፅኑ ድጋፍ በድጋሚ ማረጋገጧን የሀገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ይህ ስብሰባ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቅርቡ ክሬምሊንን ሊጎበኙ ይችላሉ የሚለውን ግምት ከፍ አድርጎታል።
በዲፕሎማሲው መስክ የተገለሉት ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ፣ እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ ወረራ ከሰነዘረችበት ጊዜ ጀምሮ በመካከላቸው ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር በከፍተኛ ፍጥነት እያሰፉት ይገኛሉ። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚያስረዱት፣ ፕዮንግያንግ የጦር ግንባር በሆነችው የሩሲያ ኩርስክ (Kursk) ግዛት ውስጥ የጦር ሰራዊት ያሰማራች ሲሆን፣ ለሞስኮም የተለያዩ የጦር መሣሪያ ሥርዓቶችን አቅርባለች። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ያደረገችው ከሩሲያ የምታገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ፣ የምግብ፣ የኃይል አቅርቦት እና የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋስትና ለማረጋገጥ ነው።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቾይ ሶን ሁዪ ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሞስኮ ካደረጉት ስብሰባ በኋላ፣ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት በረጅም ጊዜ እና በዘርፈ ብዙ መስኮች ይበልጥ ለማፋጠን ያላቸውን "የማይናወጥ የፖለቲካ ፍላጎት" በድጋሚ ማረጋገጣቸውን የፕዮንግያንግ መንግሥት ሚዲያ ዘግቧል። በሌላ በኩል ሩሲያ፣ ሰሜን ኮሪያ ሉዓላዊነቷን እና ደኅንነቷን ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት ሙሉ ድጋፏን መግለጿ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
በዲፕሎማሲው መስክ የተገለሉት ሰሜን ኮሪያ እና ሩሲያ፣ እ.ኤ.አ. በ2022 መጀመሪያ ላይ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ሙሉ በሙሉ ወታደራዊ ወረራ ከሰነዘረችበት ጊዜ ጀምሮ በመካከላቸው ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር በከፍተኛ ፍጥነት እያሰፉት ይገኛሉ። የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚያስረዱት፣ ፕዮንግያንግ የጦር ግንባር በሆነችው የሩሲያ ኩርስክ (Kursk) ግዛት ውስጥ የጦር ሰራዊት ያሰማራች ሲሆን፣ ለሞስኮም የተለያዩ የጦር መሣሪያ ሥርዓቶችን አቅርባለች። ሰሜን ኮሪያ ይህንን ያደረገችው ከሩሲያ የምታገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ፣ የምግብ፣ የኃይል አቅርቦት እና የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ሽግግር ዋስትና ለማረጋገጥ ነው።
የሰሜን ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቾይ ሶን ሁዪ ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭ ጋር በሞስኮ ካደረጉት ስብሰባ በኋላ፣ የሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት በረጅም ጊዜ እና በዘርፈ ብዙ መስኮች ይበልጥ ለማፋጠን ያላቸውን "የማይናወጥ የፖለቲካ ፍላጎት" በድጋሚ ማረጋገጣቸውን የፕዮንግያንግ መንግሥት ሚዲያ ዘግቧል። በሌላ በኩል ሩሲያ፣ ሰሜን ኮሪያ ሉዓላዊነቷን እና ደኅንነቷን ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት ሙሉ ድጋፏን መግለጿ በሪፖርቱ ተመልክቷል።
Sponsored by
Surafel
20 days ago
አሜሪካ ወደ በርካታ የአፍሪካ ሀገራት የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈች
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዓለም ሀገራትን የፀጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ በሚያወጣው መመሪያ፣ በርካታ የአፍሪካ ሀገራትን በከፍተኛው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዝርዝር ውስጥ አስፍሯል።
ዋሽንግተን የራሷ ዜጎች ወደነዚህ ሀገራት ፍጹም ጉዞ እንዳያደርጉ ያሳሰበችው በእነዚህ ቀጠናዎች ባለው እጅግ አሳሳቢ የፀጥታ ችግር፣ የሽብርተኝነት ስጋት፣ የእርስ በርስ ግጭቶች፣ የታጠቁ አማፂያን ጥቃት እና ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጠው የቆንስላ ወይም የድንገተኛ ጊዜ ድጋፍ እጅግ ውስን በመሆኑ ነው።
በዚህ የዩናይትድ ስቴትስ የ«አትሂዱ» ጥብቅ መመሪያ ውስጥ ከተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ቡርኪና ፋሶ፣ ሊቢያ፣ ማሊ፣ ኒጀር፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳንና ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ እንደ ቻድ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ያሉ ሀገራት ደግሞ በተለይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሚያገናኟቸው ድንበሮችና የተወሰኑ ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ግዛቶቻቸው ላይ ተመሳሳይ የደረጃ 4 እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በሌላ በኩል ዩጋንዳ በደረጃ 3 (Reconsider Travel ወይም ጉዞን መልሶ ማሰብ) ስር የምትገኝ ሲሆን፣ ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመጓዛቸው በፊት በወንጀል እና በሽብርተኝነት ስጋቶች ዙሪያ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ተመክሯል።
ይህ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በየጊዜው የሚሻሻለው የደረጃ 4 የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከአፍሪካ ውጭ እንደ ሩሲያ፣ ዩክሬን፣ አፍጋኒስታን፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን፣ ሶሪያ፣ ቬንዙዌላ፣ ኢራን እና ጋዛን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦርነትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ያሉ የዓለማችን አካባቢዎችንም ያጠቃልላል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
ብሔራዊ ጥቅሞቻችን.....
በየትኛውም ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ለድርድር የማይቀርብ ቀይ መስመር ነው፡፡ አንዲት ሀገር እንደ ሀገር ለመቀጠል፣ ደህንነቷን ለማስጠበቅና የሕዝቧን ሰላም ለማረጋገጥ በፍጹም ለድርድር የማታቀርባቸው እና ለማንኛውም ኃይል በማንኛውም ሁኔታ አሳልፋ የማትሰጣቸው ወሳኝ ጉዳዮች አሉ።
እነዚህ ጉዳዮች በዋናነት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት፣ የህዝብ ደህንነትና ህልውና፣ ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች፣ ብሔራዊ ክብርና ታሪክ ዋና ዋናዎቹ ተብለው ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሀገርን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክልል ወሰን ሳይደፈር ማስከበር፤ ሀገር እንዳትከፋፈል እና አንድነቷ እንዳይናጋ ማድረግ፤ የውጭ ኃይሎች በሀገር የውስጥ ፖለቲካ እና ውሳኔ ላይ ጣልቃ እንዳይገቡ መከላከልን ያካትታል፡፡
ደህንነት እና ህልውና ሕዝብን ከማንኛውም የውጭ ወረራ፣ ሽብርተኝነት እና የደህንነት ስጋት መጠበቅ፤ የሕዝብን መሰረታዊ የህልውና ፍላጎቶች (ምግብ፣ ውሃ፣ መድሃኒት) የማግኘት መብት ማረጋገጥ እና ሌሎች ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡
ስልታዊ እና የተፈጥሮ ሀብቶች ማለት ደግሞ ለሀገር ህልውና ወሳኝ የሆኑ እንደ ወንዞች፣ ማዕድናት እና ስልታዊ መሬቶች ላይ ሙሉ ቁጥጥር እና የባለቤትነት መብትን ማረጋገጥ፣ በራስ ሀብት ላይ የማዘዝ እና ሀገራዊ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን ያለ ውጭ ጫና የመቅረጽ መብቶች ናቸው፡፡
የሕዝብ ማንነት እና ባህል የሚንጸባረቅባቸው ብሔራዊ ክብር እና ታሪክ ለብሔራዊ ጥቅም መጠበቅ ወሳኝ ናቸው፡፡ የሀገርን ታሪክ፣ ቅርሶች፣ እሴቶች እና ብሔራዊ ክብር አሳልፎ ካለመስጠት ጋር ስለሚተሳሰሩ፡፡ ሀገራዊ መዳረሻን እና የወደፊት እጣ ፈንታን በራስ ሉዓላዊ ውሳኔ ብቻ የማጽናት ስራ ደግሞ ዋነኛው የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ነው፡፡
በዚሁ ቅኝት ሀገራት እንደየፍላጎታቸው ለድርድር የማያቀርቧቸው ብሔራዊ ጥቅሞች አሉ፡፡ የአንድ ሀገር ህልውና፣ ደህንነት እና ሉዓላዊነት ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተፅዕኖ የሚያሳርፉ ወሳኝ ጉዳዮች ስለሆኑ።
የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነትን በተመለከተ ቻይናን እንደ ምሳሌ እናንሳ፡፡ ቻይና ታይዋንን እና የደቡብ ቻይና ባህርን በተመለከተ ያላት አቋም ጽኑ ነው። ቻይና ታይዋንን የራሷ አካል አድርጋ ስለምትቆጥር፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ከማንኛውም ሀይል ጋር ለመደራደር ፈቃደኛ አይደለችም። በማንኛውም ዲፕሎማሲያዊ መድረክ ላይ ታይዋንን ነጻ ሀገር አድርጎ የመቀበል ሃሳብ በፍጹም የላትም፤ በዚህ ጉዳይም አትደራደርም።
በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በወሳኝ የተፈጥሮ ሀብቶቿ እና የውኃ ደህንነቷ ላይ ብሔራዊ ጥቅሞቼ ብላ ቀይ መስመር አስምራለች፡፡ እነዚህ ሀብቶች ለሀገር ህልውና እና ኢኮኖሚ መሰረት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመገንባት፣ ውኃ የመሙላት እና የመጠቀም መብቷን እንዲሁም ፍትሃዊ የውሃ አጠቃቀም መርህን ለድርድር የማይቀርቡ ብሔራዊ ቀይ መስመሬ ብላ አስቀምጣለች፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። የቀይ ባህር መስመር ለዓለም ንግድ ወሳኝ በመሆኑ፣ አካባቢው ካሉ ሀገራት እና በዓለም አቀፍ ኃይሎች ዘንድ የባህር መስመሩን ደህንነት ማስጠበቅ ለድርድር የማይቀርብ ስልታዊ ጥቅም ነው። ኢትዮጵያም ለዚሁ ብላ ነው የባህር በርን ብሔራዊ አጀንዳዋ እያደረገች ያለችው፡፡
ቀይ ባህርን በተመለከተ ግብፅና ኤርትራ “የቀይ ባህር ደኅንነትና አስተዳደር የሚመለከተው ከባህሩ ጋር የሚዋሰኑ (የባህር ዳርቻ ያላቸውን) ሀገራት ብቻ ነው” የሚል ጽኑ አቋም ማራመድ ጀምረዋል፡፡ ይህ ኢትዮጵያን የማግለል ስትራቴጂ ነው፡፡ ይህ የሁለቱ ሀገራት አቋም የኢትዮጵያን የባህር በር ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ የባለቤትነትና የመጠቀም መብት ለመንፈግ ያለመ ነው፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ኢትዮጵያን ከቀጣናው ለማግለል እና ከበባ ውስጥ ለማቆየት የሚደረግ ጥረት ነው፡፡ ይህንንም አቋም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ሊያወግዘው እና ለብሔራዊ ጥቅሙ በጋራ መቆም ያለበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
የግብፅ ልሂቃን በብዙ ጉዳዮች ላይ ሞቅ ያለ ክርክር ቢያደርጉም በናይል ጉዳይ የተለየ አቋም የላቸውም፡፡ የህልውና ጉዳይ ሆኖ እንደ አስተሳሰብ ተገንብቷል። የተለየ የሚያስብ እንኳን ቢኖር የተወገዘ፤ የተረገመ፤ እንደ ብሔራዊ ጠላት የሚታይ ይሆናል፡፡ ዓባይ እንደ ተራ የፓርቲ መሳሪያ ሳይሆን እንደ ህልውና ጉዳይ ተደርጎ ይወሰዳል። ይህ ወጥነት የግብፅን ስትራቴጂካዊ አቋም አጠናክሯል፡፡
ህንዳውያን በሉዓላዊነት፣ በግዛት አንድነት፣ የኑክሌር መከላከያ ያለልዩነት ይስማማሉ፡፡ ቀይ መስመራቸውም ነው፡፡
እንደነ ሳዑዲ አረቢያ እና ኳታር ያሉ ሀገራት ደግሞ በነዳጅ ሀብታቸው ላይ ያላቸውን ሙሉ የማዘዝ መብት ለውጭ አካል አሳልፈው አይሰጡም።
አሜሪካ በምርጫ ስርዓቷ እና በዴሞክራሲያዊ ተቋሞቿ ላይ የማንኛውንም የውጭ ሀገር ጣልቃ ገብነትን እንደ ብሔራዊ ደህንነት አደጋ ትቆጥራለች። እነዚህ ጉዳዮች ተዛብተዋል ብላ ካመነች በሌሎች ሀገራት ሥርዓት ውስጥም ጣልቃ ለመግባት እንደ ቅድመ ሁኔታ ታስቀምጣቸዋለች፡፡ ቀይ መስመሮቼ ናቸውም ብላ ታምናለች፡፡
ስልታዊ የባህር በር እና የንግድ መስመሮች ላይ የሩሲያን ደግሞ እንመልከት፡፡ ሀገሪቷ ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ ለመውጣት እና የኢኮኖሚ ደህንነትን ለመጠበቅ ስልታዊ የባህር በሮችን መቆጣጠር ወይም ማግኘት ወሳኝ ነው ብላ ታምናለች። ለዚህም ነው በጥቁር ባህር እና ወሳኝ የዓለም የባህር የመጓጓዟ መስመሮች ላይ ያላትን ድርሻ ማጣት የማትፈልገው፡፡ ራሺያ ከዩክሬን ጋር ላለችበት ግጭት መነሻም ይኸው ነው፡፡
ሌላኛው የአንድ ሀገር የብሔራዊ ጥቅም ቀይ መስመር ማሳያ የፖለቲካ ስርዓት እና የውስጥ ነጻነት ነው፡፡ ይህም የውጭ ሀይሎች የአንድን ሀገር የውስጥ የፖለቲካ ስርዓት ወይም የአመራር መዋቅር እንዲቀይሩ የሚደረግ ጫናን ሀገራት አይቀበሉም። ለዚህ ሰሜን ኮሪያ ጥሩ ምሳሌ ናት፡፡ የራሷን የፖለቲካ ስርዓት እና የኑክሌር እቅዷን ለማስጠበቅ ያላት ጽናት በመሪዎች መለዋወጥ የማይናወጥ ነው። የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ማዕቀቦች ቢበረቱባትም፣ የሀገሪቱን የፖለቲካ ህልውና አሳልፋ ላለመስጠት የኑክሌር አቅሟን እንደ ዋና ዋስትና አድርጋ ትጠቀማለች። ይህንን አቋሟንም ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የህልውና ስጋት ለመጠበቅ ነው ብላ ታምናለች፡፡
በብሔራዊ ደህንነት እና ራስን ከውጭ ጥቃት መከላከል ላይ የእስራኤል አቋም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ እስራኤል ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥል ማንኛውንም የጎረቤት ሀገራት እንቅስቃሴ ለማስቆም ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ አትልም፡፡ ይህ ህዝቧን ከውጭ ወረራ ወይም የደህንነት ስጋት የመጠበቅ መብት ነው ብላ ስለምታምን እንደ የመጨረሻ ቀይ መስመሯ አስቀምጣዋለች፡፡
ሀገራት እና ዜጎቻቸው እንደየአውዱ ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻቸውን ለድርድር አያቀርቡም፡፡ በኢትዮጵያ እንደ ብሔራዊ ጥቅም የሚታዩ ጉዳዮች ላይ የእኛ የዜጎች አቋም እንዴት ነው? በብሔራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ምሁራኖቻችን፣ የፖለቲካ ተዋንያን፣ ተቋማት፣ ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ያለልዩነት ይህ ቀይ መስመሬ ነው አትንኩብኝ የሚለው ጉዳይ ሊኖረው ይገባል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ከሀገር ፍቅር ስሜት ጋር መታየት አለበት፡፡ በዚሁ መሠረት ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን ቆጥረን ቀይ መስመር ማስመር ይገባናል፡፡
2 months ago
ሺ ጂንፒንግ ሰሜን ኮሪያ ገቡ
#ethiopia | የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሰሜን ኮሪያ የገቡ ሲሆን፥ በፒዮንግያንግ አየር ማረፊያ ሲደርሱም በሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ከፍተኛና ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ይህ በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚካሄደው ታሪካዊ ምክክር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበ ሲሆን፥ በቆይታቸውም ቀጣናዊ ደህንነትንና የሁለትዮሽ ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው አበይት ጉዳዮች ላይ በስፋት ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#china #northkorea #xijinping #kimjongun #geopolitics #asiapacific #breakingnews
#ethiopia | የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሰሜን ኮሪያ የገቡ ሲሆን፥ በፒዮንግያንግ አየር ማረፊያ ሲደርሱም በሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ከፍተኛና ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ይህ በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚካሄደው ታሪካዊ ምክክር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበ ሲሆን፥ በቆይታቸውም ቀጣናዊ ደህንነትንና የሁለትዮሽ ስትራቴጂካዊ ግንኙነትን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው አበይት ጉዳዮች ላይ በስፋት ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#china #northkorea #xijinping #kimjongun #geopolitics #asiapacific #breakingnews
3 months ago
የፕሬዚዳንት ኪም ትዕዛዝ
#ethiopia | ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በደቡባዊ የአገራቸው ድንበር መከላከያው እንዲጠናከር ትዕዛዝ ሰጡ።
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #nbcethiopia #skorea #leader #sk
#ethiopia | ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በደቡባዊ የአገራቸው ድንበር መከላከያው እንዲጠናከር ትዕዛዝ ሰጡ።
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #nbcethiopia #skorea #leader #sk
3 months ago
ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን በደቡባዊ የአገራቸው ድንበር መከላከያው እንዲጠናከር ትዕዛዝ ሰጡ።
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
seledadotio
seledadotio
ከሰሜን ኮሪያ የተለያዩ ዕዞች ከተውጣጡ ወታደራዊ ሀላፊዎች ጋር ስለዝግጁነት መክረዋል ኪም ጆንግ ኡን።
ከዕዝና ብርጌድ አዛዦች ጋር የተወያዩት ኪም በደቡባዊ የሰሜን ኮሪያ ክፍል ያለው ድንበር ላይ ዝግጅት እንዲደረግ ማሳሰባቸው ለደቡብ ኮሪያ ፖለቲከኞች አዲስ ወታደራዊ ስጋት ጋርጦባቸዋል ።
ሊቀሰቀስ የሚችልን ማንኛውንም ጦርነት ለመቀልበስ የጦሩን ትጥቅ ማዘመን፣ቁልፍ ዕዞችን ማጠናከር እና መሰል ዝግጅቶች እንዲደረጉም ጥሪ ቀርቧል።
በደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ትስስር ስጋት የሆነባቸው ኪሞቹ በተለያየ ጊዜ የሚፈፀምብንን ወታደራዊ ትንኮሳ መመከት አለብን የሚል ዕምነት አላቸውም ተብሏል።
በፒዮንግያንግ እና ሴዑል መካከል ያለው ወታደራዊ ውጥረት መልኩን እየለወጠ መምጣቱን የሚጠቁም ትዕዛዝ ሆኖም ተመዝግቧል።
ኪም ጆንግ ኡን አዳዲስ የጦር መሳሪያ ስርዓቶች ወደ ውጊያ አውድ እንዲገቡ ተደጋጋሚ ማሳሰቢያ መስጠታቸውም አይዘነጋም።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዛሬው ዕለት በሞስኮ ቀይ አደባባይ የተለመደውን የታንክ እና የሚሳኤል ማጓጓዣዎችን ትዕይንት የቀነሰ የድል ቀን በዓል አክብረዋል። ሩሲያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ናዚ ጀርመንን ያሸነፈችበትን 81ኛ ዓመት ለማሰብ በተዘጋጀው በዚህ በዓል ላይ ወታደራዊ ትርኢቱ እንዲቀነስ የተደረገው፣ በዩክሬን ባለው "ወቅታዊ የጦርነት ሁኔታ" እና ኪየቭ በምታስወነጭፋቸው የረጅም ርቀት ድሮኖች ስጋት ምክንያት መሆኑ ተነግሯል።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
ለ45 ደቂቃዎች ብቻ በዘለቀው በዚህ ዝግጅት ላይ ከሩሲያ ወታደሮች ጋር በዩክሬን አብረዋቸው ሲዋጉ የነበሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችም ተሳትፈዋል። ሩሲያ ሁልጊዜም ግዙፍ ወታደራዊ አቅሟን የምታሳይበት ይህ በዓል፣ ዘንድሮ ታላላቅ የጦር መሳሪያዎችን በአካል ከማሳየት ይልቅ በግዙፍ ስክሪኖች ላይ በምስል ማሳየትን መርጧል። የውጭ ሀገራት መሪዎች እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ተሳትፎም እጅግ አነስተኛ ሲሆን፣ እንደ ሲኤንኤን ባሉት ሚዲያዎች ተሰጥቶ የነበረው ፈቃድም በድንገት ተነጥቋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ ታጅበው ባደረጉት ንግግር፣ አሁን በዩክሬን እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጋር በማነጻጸር፣ ጦራቸው "በሙሉ የኔቶ ኃይል የሚደገፈውን አጥቂ ኃይል" እየተጋፈጠ መሆኑን ተናግረዋል።
የዘንድሮውን የድል በዓል ለየት የሚያደርገው በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አደራዳሪነት ከሜይ 9 እስከ 11 የሚቆይ የሶስት ቀናት የተኩስ አቁም እና የ1,000 እስረኞች ልውውጥ ስምምነት መደረጉ ነው። ይህንን ተከትሎ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ ለሩሲያ የድል ቀን ሰልፍ መካሄድ በፌዝ መልክ "ፈቃድ" መስጠታቸውን ገልጸው፣ "ከቀይ አደባባይ ይልቅ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱት የዩክሬን እስረኞች ህይወት ይበልጥብናል" ብለዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፣ በበኩላቸው "ሩሲያ በድል ቀኗ ለመኩራት የማንም ፈቃድ አያስፈልጋትም" ሲሉ መልስ ሰጥተዋል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴርም በዓሉን ለማስተጓጎል የሚሞክር ካለ በኪየቭ ማእከል ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት እንደሚፈጽም ዝቶ ነበር።
ከበዓሉ ድምቀት ጀርባ ግን ሩሲያ በዩክሬን የከፈተችው እና "የሶስት ቀናት ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ" ስትል የጀመረችው ጦርነት አራት ዓመታትን አስቆጥሮ እጅግ አድካሚ እና ደም አፋሳሽ ወደሆነ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የተለያዩ ገለልተኛ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከጦርነቱ መጀመርያ እስከ 2025 መገባደጃ ድረስ ወደ 352,000 የሚጠጉ የሩሲያ ወታደሮች ህይወታቸውን አጥተዋል። ምንም እንኳን ሞስኮ አሁንም ዩክሬንን የማሸነፍ አቅሙም ሆነ ጽናቱ እንዳላት ብትገልጽም፣ የሩሲያ ጦር በጦር ሜዳ እያሳየ ያለው ግስጋሴ እጅግ አዝጋሚ (በቀን 70 ሜትር ብቻ) ከመሆኑም በላይ፣ የጦርነቱ ወጪ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን እንደቀጠለ የፖለቲካ እና የጦርነት ጉዳዮች ተንታኞች ያብራራሉ።
3 months ago
"ኪም ጆንግ ኡን ከተገደሉ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ጥቃት ትሰነዝራለች:-አዲሱ ድንጋጌ‼️
የሰሜን ኮሪያ መንግስት በሕገ መንግስቱ ላይ ባደረገው አዲስ ማሻሻያ፣ መሪው ኪም ጆንግ ኡን በጠላት ሃይሎች ከተገደሉ ወይም የግድያ ሙከራ ከተፈጸመባቸው ወታደራዊ ሃይሉ አውቶማቲክ የሆነ የኒውክሌር አጸፋዊ ጥቃት እንዲሰነዝር አዝዟል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የአይሑድ እና የአሜሪካ ጥምረት በቴሕራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት የኢራኑ የበላይ መሪ አሊ ካሜኒ እና የቅርብ አማካሪዎቻቸው መገደላቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
ኪም ጆንግ ኡንም ተመሳሳይ “የአመራር ማጥፋት” (Decapitation Strike) ጥቃት ሊሰነዘርብኝ ይችላል በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ መውደቃቸው ተነግሯል።
በፒዮንግያንግ በተካሄደው 15ኛው የሰሜን ኮሪያ የሕዝብ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ በጸደቀው የኒውክሌር ፖሊሲ ሕግ አንቀጽ 3 ላይ እንደሰፈረው፣ የአገሪቱ የኒውክሌር ሃይል ዕዝ እና ቁጥጥር ስርዓት በጠላት ሃይሎች ጥቃት አደጋ ላይ ከወደቀ፣ የኒውክሌር ጥቃት “በአውቶማቲክ መንገድ እና ወዲያውኑ” ይፈጸማል።
ይህ ማለት መሪው ኪም ጆንግ ኡን ትዕዛዝ መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ ቢሆኑ ወይም ቢገደሉ፣ ወታደራዊ መኮንኖቹ ያለምንም ተጨማሪ ትዕዛዝ አጸፋውን እንዲመልሱ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
seledadotio
seledadotio
የሰሜን ኮሪያ መንግስት በሕገ መንግስቱ ላይ ባደረገው አዲስ ማሻሻያ፣ መሪው ኪም ጆንግ ኡን በጠላት ሃይሎች ከተገደሉ ወይም የግድያ ሙከራ ከተፈጸመባቸው ወታደራዊ ሃይሉ አውቶማቲክ የሆነ የኒውክሌር አጸፋዊ ጥቃት እንዲሰነዝር አዝዟል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የአይሑድ እና የአሜሪካ ጥምረት በቴሕራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት የኢራኑ የበላይ መሪ አሊ ካሜኒ እና የቅርብ አማካሪዎቻቸው መገደላቸውን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
ኪም ጆንግ ኡንም ተመሳሳይ “የአመራር ማጥፋት” (Decapitation Strike) ጥቃት ሊሰነዘርብኝ ይችላል በሚል ከፍተኛ ስጋት ውስጥ መውደቃቸው ተነግሯል።
በፒዮንግያንግ በተካሄደው 15ኛው የሰሜን ኮሪያ የሕዝብ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ በጸደቀው የኒውክሌር ፖሊሲ ሕግ አንቀጽ 3 ላይ እንደሰፈረው፣ የአገሪቱ የኒውክሌር ሃይል ዕዝ እና ቁጥጥር ስርዓት በጠላት ሃይሎች ጥቃት አደጋ ላይ ከወደቀ፣ የኒውክሌር ጥቃት “በአውቶማቲክ መንገድ እና ወዲያውኑ” ይፈጸማል።
ይህ ማለት መሪው ኪም ጆንግ ኡን ትዕዛዝ መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ ቢሆኑ ወይም ቢገደሉ፣ ወታደራዊ መኮንኖቹ ያለምንም ተጨማሪ ትዕዛዝ አጸፋውን እንዲመልሱ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአለም የፕሬስ ነፃነት ኢንዴክስ ኢትዮጵያ 148ተኛ እንዲሁም ኤርትራ 180ኛ ደረጃን አገኙ፡፡ ሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ ወይንም አርኤስኤፍ የ2026 የአለም የፕሬስ ነፃነት ኢንዴክስን ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ ኢንዴክስ ላይ እንደተገለፀው አለም ላይ ዘንድሮ የሁሉም አገራት የፕሬስ አያያዝ ዝቅተኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
እንዲሁም ካለፉት 25 አመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ያህሉ የአለም አገራት ውስጥ የፕሬስ ነፃነት ‹‹አስቸጋሪ›› ወይንም ‹‹የከፋ›› ሆኖ መገኘቱን አስረድቷል፡፡ ይህንን ኢንዴክስ ለማውጣት እንደመስፈርትነት የተጠቀመው ለጋዜጠኞች ያለውን የኢኮኖሚ፣ የህግ፣ የደህንነት፣ የፖለቲካና የማህበራዊ ሁኔታዎች መሆኑን የገለፀው አርኤስኤፍ፣ ዘንድሮ አሜሪካ ደረጃዋ በ7 ደረጃዎች መውረዱን አስታውቋል፡፡ እንደኢንዴክሱ ከሆነ ኖርዌይ በዝርዝሩ ውስጥ ለጋዜጠኞች የተመቸች አገር በመሆን ዘንድሮ ለ10ረኛ ተከታታይ አመት በቀዳሚነት ተቀምጣለች፡፡
ኤርትራ ደግሞ ለ3ተኛ ተከታታይ አመት የመጨረሻው ረድፍ ላይ መገኘቷን አስታውቋል፡፡ የ180 አገራት ደረጃ በተቀመጠበት በዚህ ኢንዴክስ ጎረቤት አገር ኤርትራ በ180ኛ ቦታ ላይ ስትቀመጥ ከእሷ ከፍ ብላ በ179ነኛ ደረጃ ያለችው ሰሜን ኮሪያ ናት፡፡ 178ተኛ ላይ ደግሞ ቻይናን አስቀምጧል፡፡ እንዲሁም ኢራንን በ177ኛ ደረጃና ሩሲያን በ172ተኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጠው ይህ ኢንዴክስ ለኢትዮጵያ ደግሞ የ148ተኛ ደረጃን ሰጥቷል፡፡ በኢንዴክሱ ላይ ኢትዮጵያ 4 ጋዜጠኞችን ላለፉት 3 አመታት የሽብርተኝነት ክስ መስርታ በእስር ላይ ማቆየቷንም አስታውቋል፡፡
እንዲሁም ካለፉት 25 አመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ያህሉ የአለም አገራት ውስጥ የፕሬስ ነፃነት ‹‹አስቸጋሪ›› ወይንም ‹‹የከፋ›› ሆኖ መገኘቱን አስረድቷል፡፡ ይህንን ኢንዴክስ ለማውጣት እንደመስፈርትነት የተጠቀመው ለጋዜጠኞች ያለውን የኢኮኖሚ፣ የህግ፣ የደህንነት፣ የፖለቲካና የማህበራዊ ሁኔታዎች መሆኑን የገለፀው አርኤስኤፍ፣ ዘንድሮ አሜሪካ ደረጃዋ በ7 ደረጃዎች መውረዱን አስታውቋል፡፡ እንደኢንዴክሱ ከሆነ ኖርዌይ በዝርዝሩ ውስጥ ለጋዜጠኞች የተመቸች አገር በመሆን ዘንድሮ ለ10ረኛ ተከታታይ አመት በቀዳሚነት ተቀምጣለች፡፡
ኤርትራ ደግሞ ለ3ተኛ ተከታታይ አመት የመጨረሻው ረድፍ ላይ መገኘቷን አስታውቋል፡፡ የ180 አገራት ደረጃ በተቀመጠበት በዚህ ኢንዴክስ ጎረቤት አገር ኤርትራ በ180ኛ ቦታ ላይ ስትቀመጥ ከእሷ ከፍ ብላ በ179ነኛ ደረጃ ያለችው ሰሜን ኮሪያ ናት፡፡ 178ተኛ ላይ ደግሞ ቻይናን አስቀምጧል፡፡ እንዲሁም ኢራንን በ177ኛ ደረጃና ሩሲያን በ172ተኛ ደረጃ ላይ ያስቀመጠው ይህ ኢንዴክስ ለኢትዮጵያ ደግሞ የ148ተኛ ደረጃን ሰጥቷል፡፡ በኢንዴክሱ ላይ ኢትዮጵያ 4 ጋዜጠኞችን ላለፉት 3 አመታት የሽብርተኝነት ክስ መስርታ በእስር ላይ ማቆየቷንም አስታውቋል፡፡
3 months ago
ሰሜን ኮርያ የጎረቤቷን የደቡብ ኮርያን ድራማዎችን የተመለከቱ ሰዎችን በሞት መቅጣት መቀጠሏ ተሰማ
በሰሜን ኮሪያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በተከሰተበት ወቅት የሞት ቅጣት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ሲል ሴኡል ላይ የተመሰረተዉ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ገልጿል።ከጃንዋሪ 2020 እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ ቢያንስ 153 ሰዎች ተገድለዋል ወይም ሞት ተፈርዶባቸዋል፡፡ወረርሽኙ ከመከሰቱ በፊት በነበሩት አምስት ዓመታት ውስጥ 44 ሰዎች ተቀጥተዉ እንደነበረ የሽግግር ፍትህ የስራ ቡድን አስታዉቋል።
በጣም ከተለመዱት ጥፋቶች መካከል አንዳንዶቹ ከሃይማኖት፣ ከአጉል እምነት እና ከውጪ የባህል ይዘት ጋር የተያያዙ ሲሆን የደቡብ ኮርያ ድራማዎን መመልከት ለቅጣቱ ምክንያት ሆኗል፡፡ እ.ኤ.አ. በ 2015 እስከ በ 2019 መካከል ባሉት ዓመታት የሞት ቅጣት ቁጥሩ ቀንሶ ነበር፡፡ ለመቀነሱም ዋና ምክንያቱ ዓለም አቀፍ ጫናዎች የመንግስታቱ ድርጅት ጥያቄን ተከትሎ ነዉ። ነገር ግን ፒዮንግያንግ ድንበሯን ከዘጋች በኋላ በ2020 ግድያ ጨምሯል ሲል የሽግግር ፍትህ የስራ ቡድን አስታዉቋል።
መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት በሰሜን ኮሪያ በኪም የግዛት ዘመን መጀመሪያ ላይ የሞት ፍርድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱንና በ2013 ከ80 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ሲል አስታዉሷል።ፒዮንግያንግ ስልታዊ በሆነ መንገድ የሰብአዊ መብት ረገጣ እየፈፀመች መሆኑን ያረጋገጠውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባደረገው ጥናት መሰረት ቁጥሩ እየቀነሰ የመጣ ይመስላል።በ2020 ግን ቢያንስ 54 ሰዎች ተገድለዋል ፣በ2021 ደግሞ 45 ሰዎች ሲገደሉ በአንድ ዓመት ከፍተኛ አመዘጋገብ የተፈጸመበት ነዉ፡፡
seledadotio
seledadotio
በሰሜን ኮሪያ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በተከሰተበት ወቅት የሞት ቅጣት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ሲል ሴኡል ላይ የተመሰረተዉ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ገልጿል።ከጃንዋሪ 2020 እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ ቢያንስ 153 ሰዎች ተገድለዋል ወይም ሞት ተፈርዶባቸዋል፡፡ወረርሽኙ ከመከሰቱ በፊት በነበሩት አምስት ዓመታት ውስጥ 44 ሰዎች ተቀጥተዉ እንደነበረ የሽግግር ፍትህ የስራ ቡድን አስታዉቋል።
በጣም ከተለመዱት ጥፋቶች መካከል አንዳንዶቹ ከሃይማኖት፣ ከአጉል እምነት እና ከውጪ የባህል ይዘት ጋር የተያያዙ ሲሆን የደቡብ ኮርያ ድራማዎን መመልከት ለቅጣቱ ምክንያት ሆኗል፡፡ እ.ኤ.አ. በ 2015 እስከ በ 2019 መካከል ባሉት ዓመታት የሞት ቅጣት ቁጥሩ ቀንሶ ነበር፡፡ ለመቀነሱም ዋና ምክንያቱ ዓለም አቀፍ ጫናዎች የመንግስታቱ ድርጅት ጥያቄን ተከትሎ ነዉ። ነገር ግን ፒዮንግያንግ ድንበሯን ከዘጋች በኋላ በ2020 ግድያ ጨምሯል ሲል የሽግግር ፍትህ የስራ ቡድን አስታዉቋል።
መንግሥታዊ ያልሆነው ድርጅት በሰሜን ኮሪያ በኪም የግዛት ዘመን መጀመሪያ ላይ የሞት ፍርድ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱንና በ2013 ከ80 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ሲል አስታዉሷል።ፒዮንግያንግ ስልታዊ በሆነ መንገድ የሰብአዊ መብት ረገጣ እየፈፀመች መሆኑን ያረጋገጠውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባደረገው ጥናት መሰረት ቁጥሩ እየቀነሰ የመጣ ይመስላል።በ2020 ግን ቢያንስ 54 ሰዎች ተገድለዋል ፣በ2021 ደግሞ 45 ሰዎች ሲገደሉ በአንድ ዓመት ከፍተኛ አመዘጋገብ የተፈጸመበት ነዉ፡፡
seledadotio
seledadotio
3 months ago
የሞስኮ እና ፒዮንግያንግ ድርና ማግ ሆነናል አሉ
#ethiopia | የሩሲያው መከላከያ ሚኒስትር አንድሬ ቤሎሶቭ ከሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የሁለቱ ሀገራት ወታደራዊ ትብብር ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል።
ይህ ጉብኝት በቃላት ደረጃ ከሚገለጽ ዲፕሎማሲ ባለፈ፣ በተግባር የሚታይ ስልታዊ ዝግጅት የታየበት ነው።
ሁለቱ ሀገራት ከ2027 እስከ 2031 የሚዘልቅ የጋራ ወታደራዊ ግንኙነት ፍኖተ ካርታ ላይ ተስማምተዋል። ይህም ትብብራቸው ለረጅም ጊዜ የሚቆይ መሆኑን ያሳያል።
በሰኔ 2024 የተፈረመው ስምምነት አንዱ ሀገር ጥቃት ቢሰነዘርበት ሌላኛው ወታደራዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ያስገድዳል። ይህም ሰሜን ኮሪያን የሩሲያ ቀጥተኛ የጦር አጋር አድርጓታል።
ቤሎሶቭ ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ጦርነት ወቅት ለሩሲያ ላሳየችው "ወንድማዊ ድጋፍ" እና በኩርስክ ክልል ለተሳተፉት የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና ሰጥተዋል።
ይህ ጥምረት በ"እጅ በእጅ" ግብይት ላይ የተመሰረተ ይመስላል። ምዕራባውያን እንደሚሉት ከሆነ፦
ወደ 14,000 የሚጠጉ ወታደሮችን እና የጦር መሣሪያዎችን ለሩሲያ ግንባር አሰልፋለች።
ሩሲያ ምን ትሰጣለች? በምላሹ ዘመናዊ የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ድጋፍ፣ የምግብ ዋስትና እና የኃይል (ኢነርጂ) አቅርቦትን ለሰሜን ኮሪያ ታረጋግጣለች።
ይህ ጥምረት በምዕራባውያን ዘንድ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረው ሰሜን ኮሪያ በምትገኝበት ቀጠና (ምስራቅ እስያ) ያለውን የኃይል ሚዛን ሊያናጋ ስለሚችል እና የዩክሬን ጦርነትን መልክ ሊቀይር ስለሚችል ነው።
የሩሲያ ቴክኖሎጂ እና የሰሜን ኮሪያ የሰው ኃይል መቀላቀል ለኔቶ (NATO) አባላት ቀላል የማይባል የቤት ስራ ሆኖባቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #ሰሜንኮሪያ #ወታደራዊትብብር #ኪምጆንግኡን #አንድሬቤሎሶቭ #የዓለምፖለቲካ #ዩክሬን #ዜና
#ethiopia | የሩሲያው መከላከያ ሚኒስትር አንድሬ ቤሎሶቭ ከሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የሁለቱ ሀገራት ወታደራዊ ትብብር ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል።
ይህ ጉብኝት በቃላት ደረጃ ከሚገለጽ ዲፕሎማሲ ባለፈ፣ በተግባር የሚታይ ስልታዊ ዝግጅት የታየበት ነው።
ሁለቱ ሀገራት ከ2027 እስከ 2031 የሚዘልቅ የጋራ ወታደራዊ ግንኙነት ፍኖተ ካርታ ላይ ተስማምተዋል። ይህም ትብብራቸው ለረጅም ጊዜ የሚቆይ መሆኑን ያሳያል።
በሰኔ 2024 የተፈረመው ስምምነት አንዱ ሀገር ጥቃት ቢሰነዘርበት ሌላኛው ወታደራዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ያስገድዳል። ይህም ሰሜን ኮሪያን የሩሲያ ቀጥተኛ የጦር አጋር አድርጓታል።
ቤሎሶቭ ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ጦርነት ወቅት ለሩሲያ ላሳየችው "ወንድማዊ ድጋፍ" እና በኩርስክ ክልል ለተሳተፉት የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና ሰጥተዋል።
ይህ ጥምረት በ"እጅ በእጅ" ግብይት ላይ የተመሰረተ ይመስላል። ምዕራባውያን እንደሚሉት ከሆነ፦
ወደ 14,000 የሚጠጉ ወታደሮችን እና የጦር መሣሪያዎችን ለሩሲያ ግንባር አሰልፋለች።
ሩሲያ ምን ትሰጣለች? በምላሹ ዘመናዊ የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ድጋፍ፣ የምግብ ዋስትና እና የኃይል (ኢነርጂ) አቅርቦትን ለሰሜን ኮሪያ ታረጋግጣለች።
ይህ ጥምረት በምዕራባውያን ዘንድ ከፍተኛ ስጋት የፈጠረው ሰሜን ኮሪያ በምትገኝበት ቀጠና (ምስራቅ እስያ) ያለውን የኃይል ሚዛን ሊያናጋ ስለሚችል እና የዩክሬን ጦርነትን መልክ ሊቀይር ስለሚችል ነው።
የሩሲያ ቴክኖሎጂ እና የሰሜን ኮሪያ የሰው ኃይል መቀላቀል ለኔቶ (NATO) አባላት ቀላል የማይባል የቤት ስራ ሆኖባቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ሩሲያ #ሰሜንኮሪያ #ወታደራዊትብብር #ኪምጆንግኡን #አንድሬቤሎሶቭ #የዓለምፖለቲካ #ዩክሬን #ዜና
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የአለምን የኃይል ሚዛን የሚቀይረው የሰሜን ኮሪያ እና የኢራን ሚስጥራዊ ስምምነት
በአሜሪካ እና በአጋሮቿ ከፍተኛ ማዕቀብ የተጣለባቸው ሰሜን ኮሪያ እና ኢራን በምስጢር የፈጠሩት ወታደራዊ ጥምረት በዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ መድረክ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሯል።
የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ከተራ የንግድ ልውውጥ ባለፈ እጅግ የላቁ የባለስቲክ ሚሳኤል ቴክኖሎጂዎችን፣ የከባድ መሳርያዎችን እና የስትራቴጂክ መረጃዎችን ማጋራት ላይ ያተኮረ መሆኑን የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ የምስጢር ትብብር ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያላትን ወታደራዊ የበላይነት በከፍተኛ ፍጥነት እንድታሳድግ የረዳት ሲሆን፣ ሰሜን ኮሪያ በበኩሏ ከኢራን የምታገኘውን የገንዘብ እና የኢነርጂ ድጋፍ ተጠቅማ ማዕቀቦችን የምትጥስበት አዲስ መንገድ ቀርጻለች።
የምዕራባውያን ሀገራት የጣሉት ማዕቀብ የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ አቅም ከመገደብ ይልቅ ይበልጥ እንዲቀራረቡ እና አደገኛ ጥምረት እንዲፈጥሩ ማድረጉ ለብዙዎች ስጋት ሆኗል።
ይህ አዲስ የኃይል ሚዛን ከቀጠናው አልፎ መላውን ዓለም ሊያናውጥ እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
በአሜሪካ እና በአጋሮቿ ከፍተኛ ማዕቀብ የተጣለባቸው ሰሜን ኮሪያ እና ኢራን በምስጢር የፈጠሩት ወታደራዊ ጥምረት በዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ መድረክ ላይ ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሯል።
የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ከተራ የንግድ ልውውጥ ባለፈ እጅግ የላቁ የባለስቲክ ሚሳኤል ቴክኖሎጂዎችን፣ የከባድ መሳርያዎችን እና የስትራቴጂክ መረጃዎችን ማጋራት ላይ ያተኮረ መሆኑን የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
ይህ የምስጢር ትብብር ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያላትን ወታደራዊ የበላይነት በከፍተኛ ፍጥነት እንድታሳድግ የረዳት ሲሆን፣ ሰሜን ኮሪያ በበኩሏ ከኢራን የምታገኘውን የገንዘብ እና የኢነርጂ ድጋፍ ተጠቅማ ማዕቀቦችን የምትጥስበት አዲስ መንገድ ቀርጻለች።
የምዕራባውያን ሀገራት የጣሉት ማዕቀብ የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ አቅም ከመገደብ ይልቅ ይበልጥ እንዲቀራረቡ እና አደገኛ ጥምረት እንዲፈጥሩ ማድረጉ ለብዙዎች ስጋት ሆኗል።
ይህ አዲስ የኃይል ሚዛን ከቀጠናው አልፎ መላውን ዓለም ሊያናውጥ እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት ለሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ወዳጅነታቸውን የሚያጠናክር የጠመንጃ ስጦታ አበረከቱላቸው
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በፒዮንግያንግ የጓደኝነት ስምምነት በተፈራረሙበት ወቅት ለሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጠመንጃ በስጦታ ማበርከታቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሁለቱም መሪዎች ሩሲያ በዩክሬን የምታካሂደው ጦርነት ቁልፍ ደጋፊዎች ሲሆኑ፤በቅርበት ለመተባበር እና ከምዕራባውያን የሚመጣባቸውን ጫና ለመቋቋም ተስማምተዋል።
የቤላሩስ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በለቀቁት ቪዲዮ፤ሉካሼንኮ ለኪም አውቶማቲክ ጠመንጃውን ሲያበረክቱ ‹‹ጠላቶች ቢመጡ በሚል ነው›› ሲሉ በቀልድ መልክ ተናግረዋል።
በምላሹም ኪም ለሉካሼንኮ ሰይፍ እና የቤላሩስ መሪ ምስል ያለበት የአበባ ማስቀመጫ በስጦታ ሰጥተዋል።
ሉካሼንኮ ለኪም እንደተናገሩት፤"እንደ ጓደኛ በዚህ ዓለም ውስጥ ሁሉንም ነገር እንዳየ ሰው ልነግርህ የምችለው ነገር ቢኖር፤ ይህንን ታታሪ እና ስነ-ስርዓት ያለው ህዝብ ይዘህ ሀገርህን ታላቅ ታደርጋታለህ " ማለታቸውን የቤላሩስ ዜና አገልግሎት ቤልታ ዘግቧል።
አክለውም "የዓለም አቀፍ ህግጋት በኃያላን መንግስታት በግልጽ ችላ በሚባሉበት እና በሚጣሱበት በዚህ ወቅት ሀገራት ሉዓላዊነታቸውን ለመጠበቅ እና የዜጎቻቸውን ደህንነት ለማሻሻል መተባበር አለባቸው ብለዋል።
ሉካሼንኮ የጓደኝነት ስምምነቱን ‹‹መሰረታዊ›› ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ኪም በበኩላቸው ስምምነቱ "የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የተረጋጋ እድገት እንዲኖረው ዋስትና ይሰጣል" ማለታቸውን ቤልታ ዘግቧል።
በተጨማሪም ሁለቱ መሪዎች ከግብርና እስከ መረጃ ቴክኖሎጂ እና የህዝብ ጤና ባሉ ዘርፎች ላይ ለመተባበር ተስማምተዋል።
ሰሜን ኮሪያ እና ቤላሩስ በሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ሩሲያን በዩክሬን ጦርነት በመደገፋቸው በምዕራባውያን ከባድ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል።
በዚህ ወቅት ፒዮንግያንግ ለሩሲያ ጦር ወታደሮችን እያቀረበች ሲሆን፤ ባለፈው ዓመት የምዕራባውያን ባለስልጣናት ለቢቢሲ እንደተናገሩት በዩክሬን ጦርነት የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ 1 ሺህ የሚገመቱ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ተገድለዋል።
ዩክሬን በበኩሏ ሩሲያ በዩክሬን ኢላማዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የቤላሩስን ግዛት እንደ ጦር ሰፈር ትጠቀማለች ስትል ከሳለች።
ሀና ሰይፉ
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በፒዮንግያንግ የጓደኝነት ስምምነት በተፈራረሙበት ወቅት ለሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጠመንጃ በስጦታ ማበርከታቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ሁለቱም መሪዎች ሩሲያ በዩክሬን የምታካሂደው ጦርነት ቁልፍ ደጋፊዎች ሲሆኑ፤በቅርበት ለመተባበር እና ከምዕራባውያን የሚመጣባቸውን ጫና ለመቋቋም ተስማምተዋል።
የቤላሩስ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በለቀቁት ቪዲዮ፤ሉካሼንኮ ለኪም አውቶማቲክ ጠመንጃውን ሲያበረክቱ ‹‹ጠላቶች ቢመጡ በሚል ነው›› ሲሉ በቀልድ መልክ ተናግረዋል።
በምላሹም ኪም ለሉካሼንኮ ሰይፍ እና የቤላሩስ መሪ ምስል ያለበት የአበባ ማስቀመጫ በስጦታ ሰጥተዋል።
ሉካሼንኮ ለኪም እንደተናገሩት፤"እንደ ጓደኛ በዚህ ዓለም ውስጥ ሁሉንም ነገር እንዳየ ሰው ልነግርህ የምችለው ነገር ቢኖር፤ ይህንን ታታሪ እና ስነ-ስርዓት ያለው ህዝብ ይዘህ ሀገርህን ታላቅ ታደርጋታለህ " ማለታቸውን የቤላሩስ ዜና አገልግሎት ቤልታ ዘግቧል።
አክለውም "የዓለም አቀፍ ህግጋት በኃያላን መንግስታት በግልጽ ችላ በሚባሉበት እና በሚጣሱበት በዚህ ወቅት ሀገራት ሉዓላዊነታቸውን ለመጠበቅ እና የዜጎቻቸውን ደህንነት ለማሻሻል መተባበር አለባቸው ብለዋል።
ሉካሼንኮ የጓደኝነት ስምምነቱን ‹‹መሰረታዊ›› ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ኪም በበኩላቸው ስምምነቱ "የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የተረጋጋ እድገት እንዲኖረው ዋስትና ይሰጣል" ማለታቸውን ቤልታ ዘግቧል።
በተጨማሪም ሁለቱ መሪዎች ከግብርና እስከ መረጃ ቴክኖሎጂ እና የህዝብ ጤና ባሉ ዘርፎች ላይ ለመተባበር ተስማምተዋል።
ሰሜን ኮሪያ እና ቤላሩስ በሰብዓዊ መብት ጥሰት እና ሩሲያን በዩክሬን ጦርነት በመደገፋቸው በምዕራባውያን ከባድ ማዕቀብ ተጥሎባቸዋል።
በዚህ ወቅት ፒዮንግያንግ ለሩሲያ ጦር ወታደሮችን እያቀረበች ሲሆን፤ ባለፈው ዓመት የምዕራባውያን ባለስልጣናት ለቢቢሲ እንደተናገሩት በዩክሬን ጦርነት የመጀመሪያዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ 1 ሺህ የሚገመቱ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ተገድለዋል።
ዩክሬን በበኩሏ ሩሲያ በዩክሬን ኢላማዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር የቤላሩስን ግዛት እንደ ጦር ሰፈር ትጠቀማለች ስትል ከሳለች።
ሀና ሰይፉ
4 months ago
⚠️ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን አሜሪካን "የሽብርተኛ ሀገር" ሲሉ ወነጀሉ!
የሰሜን ኮሪያው ከፍተኛ መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቅርቡ በሰጡት መግለጫ አሜሪካን "የሽብርተኛ ሀገር" (Terrorist State) በማለት የጠሩ ሲሆን፣ ዋሽንግተን በመላው ዓለም ሰላምን እያደፈረሰች መሆኗን በጽኑ ተችተዋል። መሪው አክለውም አሜሪካ በዓለም ዙሪያ የምታደርገው ጣልቃ ገብነት እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለዓለም አቀፋዊ ሰላምና ደህንነት ትልቅ ስጋት እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን ጠንካራ መግለጫ የመጣው በፒዮንግያንግ እና በዋሽንግተን መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት ወቅት ነው። ሰሜን ኮሪያ አሜሪካ በኮሪያ ልሳነ ምድር የምታደርገውን ወታደራዊ ልምምድ እና የምትጥለውን ማዕቀብ እንደ ጠብ ጫሪነት እንደምትመለከተው በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች። አሁን የቀረበው ክስም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የጂኦ-ፖለቲካ ባለሙያዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
መሪው በንግግራቸው ወቅት አሜሪካ የራሷን ጥቅም ለማስጠበቅ ስትል የተለያዩ ሀገራትን ሉዓላዊነት እየጣሰች እንደሆነ እና ይህ ድርጊቷም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የሰላም መደፍረስ እያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ ንግግር ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና ሚሳኤል አቅሟን እያሳደገች ባለችበት ወቅት መሰማቱ፣ በምስራቅ እስያ ቀጠና ያለውን የኃይል ሚዛን እና የጸጥታ ሁኔታ ይበልጥ አሳሳቢ እንዲሆን አድርጎታል።
seledadotio
seledadotio
የሰሜን ኮሪያው ከፍተኛ መሪ ኪም ጆንግ ኡን በቅርቡ በሰጡት መግለጫ አሜሪካን "የሽብርተኛ ሀገር" (Terrorist State) በማለት የጠሩ ሲሆን፣ ዋሽንግተን በመላው ዓለም ሰላምን እያደፈረሰች መሆኗን በጽኑ ተችተዋል። መሪው አክለውም አሜሪካ በዓለም ዙሪያ የምታደርገው ጣልቃ ገብነት እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለዓለም አቀፋዊ ሰላምና ደህንነት ትልቅ ስጋት እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን ጠንካራ መግለጫ የመጣው በፒዮንግያንግ እና በዋሽንግተን መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት ወቅት ነው። ሰሜን ኮሪያ አሜሪካ በኮሪያ ልሳነ ምድር የምታደርገውን ወታደራዊ ልምምድ እና የምትጥለውን ማዕቀብ እንደ ጠብ ጫሪነት እንደምትመለከተው በተደጋጋሚ ስትገልጽ ቆይታለች። አሁን የቀረበው ክስም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የጂኦ-ፖለቲካ ባለሙያዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
መሪው በንግግራቸው ወቅት አሜሪካ የራሷን ጥቅም ለማስጠበቅ ስትል የተለያዩ ሀገራትን ሉዓላዊነት እየጣሰች እንደሆነ እና ይህ ድርጊቷም በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ የሰላም መደፍረስ እያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።
ይህ ንግግር ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና ሚሳኤል አቅሟን እያሳደገች ባለችበት ወቅት መሰማቱ፣ በምስራቅ እስያ ቀጠና ያለውን የኃይል ሚዛን እና የጸጥታ ሁኔታ ይበልጥ አሳሳቢ እንዲሆን አድርጎታል።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
ሉካሼንኮ ለኪም ጆንግ ኡን የጦር መሳሪያ በስጦታ አበረከቱ
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ ባደረጉት ጉብኝት ለሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን አውቶማቲክ ጠመንጃ በስጦታ አበረከቱ።
ሉካሼንኮ ስጦታውን ሲያስረክቡ "ጠላቶች ቢመጡ ትጠቀምበታለህ" በማለት በቀልድ መልክ መናገራቸው ተዘግቧል። ኪም ጆንግ ኡንም በምላሹ የራሳቸው ምስል ያለበትና ከባህር ዛጎል የተሰራ ትልቅ የአበባ ማስቀመጫ ሰጥተዋል።
ሁለቱ መሪዎች በምዕራባውያን ላይ ያላቸውን ተቃውሞ በመግለጽ የ"ወዳጅነትና ትብብር" ስምምነት ተፈራርመዋል።
ቤላሩስና ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ጦርነት ሩሲያን በግልጽ የሚደግፉ ሲሆን፣ ጉብኝታቸውም አዲስ የትብብር ምዕራፍ መክፈቻ መሆኑ ተገልጿል።
ስምምነቱ ከግብርና እስከ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ያሉ ዘርፎችን ያጠቃልላል።
ምንጭ፦ AFP
የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ ባደረጉት ጉብኝት ለሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን አውቶማቲክ ጠመንጃ በስጦታ አበረከቱ።
ሉካሼንኮ ስጦታውን ሲያስረክቡ "ጠላቶች ቢመጡ ትጠቀምበታለህ" በማለት በቀልድ መልክ መናገራቸው ተዘግቧል። ኪም ጆንግ ኡንም በምላሹ የራሳቸው ምስል ያለበትና ከባህር ዛጎል የተሰራ ትልቅ የአበባ ማስቀመጫ ሰጥተዋል።
ሁለቱ መሪዎች በምዕራባውያን ላይ ያላቸውን ተቃውሞ በመግለጽ የ"ወዳጅነትና ትብብር" ስምምነት ተፈራርመዋል።
ቤላሩስና ሰሜን ኮሪያ በዩክሬን ጦርነት ሩሲያን በግልጽ የሚደግፉ ሲሆን፣ ጉብኝታቸውም አዲስ የትብብር ምዕራፍ መክፈቻ መሆኑ ተገልጿል።
ስምምነቱ ከግብርና እስከ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ያሉ ዘርፎችን ያጠቃልላል።
ምንጭ፦ AFP
5 months ago
ኪም ጆንግ ኡን እና ልጃቸው በአዲሱ የጦር ታንክ ልምምድ ላይ
#ethiopia | የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ታዳጊ ሴት ልጃቸውን ጁ ኤን አስከትለው አዲስ የተመረተውን ዘመናዊ የጦር ታንክ ሲያስመርቁና ሲያስፈትኑ ታይተዋል። የሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን (KCNA) ዛሬ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ ታዳጊዋ ጁ ኤ አባቷ በቅርብ ርቀት ሆኖ እየተከታተላት የጦር ታንኩን በብቃት ስታሽከረክር ታይታለች።
የአዲሱ ታንክ ልዩ ባህሪያት
ይህ አዲስ ታንክ የሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ምን ያህል እንደገፋ የሚያሳይ ነው ተብሏል። ዋና ዋናዎቹም፦
* የላቀ የመንቀሳቀስ ብቃት፦ በማንኛውም አስቸጋሪ መሬት ላይ በፍጥነት መጓዝ የሚችል፤
* ከፍተኛ የተኩስ ኃይል፦ ኢላማዎችን በከፍተኛ ጥራት መምታት የሚያስችል ቴክኖሎጂ የታጠቀ፤
* የመከላከያ ዘዴ፦ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን የመመከት ልዩ አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።
የጊዜው ስልታዊ መልዕክት
ይህ ወታደራዊ ትርኢት በአጋጣሚ የተከናወነ አይደለም። አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ "Freedom Shield" የተሰኘውን መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ልምምድ ባጠናቀቁ ማግስት የተደረገ በመሆኑ፣ ፒዮንግያንግ ለጠላቶቿ የሰጠችው ቀጥተኛ ማስጠንቀቂያ እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ።
የጁ ኤ መገኘት ምን ያሳያል?
ታዳጊዋ ጁ ኤ በጦር ሜዳ ልምምዶች እና በከፍተኛ ወታደራዊ ዝግጅቶች ላይ በብዛት መታየቷ፣ የሰሜን ኮሪያ ቀጣይ መሪ ለመሆን እየተዘጋጀች እንደሆነ ፍንጭ ይሰጣል። መሪው ኪም ጆንግ ኡን ልጃቸው በታንክ አሽከርካሪነት መቀመጫ ላይ ሆና ልምምድ ስታደርግ በኩራት ሲመለከቱ የሚያሳዩት ምስሎች፣ የቤተሰቡን የሥልጣን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ተምሳሌታዊ ትርጉም አለው ተብሎ ይታመናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሰሜንኮሪያ #ኪምጆንግኡን #ጁኤ #የጦርታንክ #ወታደራዊልምምድ #ጂኦፖለቲካ #northkorea #kimjongun
#ethiopia | የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ታዳጊ ሴት ልጃቸውን ጁ ኤን አስከትለው አዲስ የተመረተውን ዘመናዊ የጦር ታንክ ሲያስመርቁና ሲያስፈትኑ ታይተዋል። የሀገሪቱ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን (KCNA) ዛሬ ባወጣው መረጃ መሰረት፣ ታዳጊዋ ጁ ኤ አባቷ በቅርብ ርቀት ሆኖ እየተከታተላት የጦር ታንኩን በብቃት ስታሽከረክር ታይታለች።
የአዲሱ ታንክ ልዩ ባህሪያት
ይህ አዲስ ታንክ የሰሜን ኮሪያ ወታደራዊ ቴክኖሎጂ ምን ያህል እንደገፋ የሚያሳይ ነው ተብሏል። ዋና ዋናዎቹም፦
* የላቀ የመንቀሳቀስ ብቃት፦ በማንኛውም አስቸጋሪ መሬት ላይ በፍጥነት መጓዝ የሚችል፤
* ከፍተኛ የተኩስ ኃይል፦ ኢላማዎችን በከፍተኛ ጥራት መምታት የሚያስችል ቴክኖሎጂ የታጠቀ፤
* የመከላከያ ዘዴ፦ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን የመመከት ልዩ አቅም ያለው መሆኑ ተገልጿል።
የጊዜው ስልታዊ መልዕክት
ይህ ወታደራዊ ትርኢት በአጋጣሚ የተከናወነ አይደለም። አሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ "Freedom Shield" የተሰኘውን መጠነ ሰፊ ወታደራዊ ልምምድ ባጠናቀቁ ማግስት የተደረገ በመሆኑ፣ ፒዮንግያንግ ለጠላቶቿ የሰጠችው ቀጥተኛ ማስጠንቀቂያ እንደሆነ ተንታኞች ይገልጻሉ።
የጁ ኤ መገኘት ምን ያሳያል?
ታዳጊዋ ጁ ኤ በጦር ሜዳ ልምምዶች እና በከፍተኛ ወታደራዊ ዝግጅቶች ላይ በብዛት መታየቷ፣ የሰሜን ኮሪያ ቀጣይ መሪ ለመሆን እየተዘጋጀች እንደሆነ ፍንጭ ይሰጣል። መሪው ኪም ጆንግ ኡን ልጃቸው በታንክ አሽከርካሪነት መቀመጫ ላይ ሆና ልምምድ ስታደርግ በኩራት ሲመለከቱ የሚያሳዩት ምስሎች፣ የቤተሰቡን የሥልጣን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ተምሳሌታዊ ትርጉም አለው ተብሎ ይታመናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ሰሜንኮሪያ #ኪምጆንግኡን #ጁኤ #የጦርታንክ #ወታደራዊልምምድ #ጂኦፖለቲካ #northkorea #kimjongun
5 months ago
ኪም ጆንግ ኡን እንዲህ ብለዋል‼️
"ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ኢራንን የሚወጋው ያቺ ሀገር ልትቋቋመው እንደማትችል ስላመነ ነው። የእኔን ሀገር ሰሜን ኮሪያን፣ ቻይናን ወይም ሩሲያን ለመተንኮስ የማይደፍረውም ለዚህ ነው፤ ምክንያቱም የእኛን ኃይልና ሚሳኤሎቻችንን በሚገባ ያውቃል።
እኛ መላዋን አሜሪካ በአንድ ሚሳኤል ብቻ ከምድረ-ገጽ ማጥፋት እንችላለን። እሱ ግጭት የሚፈልገው አጸፋ መመለስ እንደማይችሉ ከሚያምንባቸው አገራት ጋር ነው።
ነገር ግን ኢራን በእውነት ከፈለገች አብዛኛውን የአሜሪካ ክፍል በቦምብ መደብደብ ትችላለች። ጥቃት የማታደርሰው ግን የብዙ አሜሪካውያን ንጹሐን ዜጎች ሕይወት እንዳይጠፋ በመፍራት ብቻ ነው።"
ዛቻ ኃይልን አያረጋግጥም። የአንድ ሀገር እውነተኛ ታላቅነት የሚታየው በሰላም፣ በፍትህ እና ለሰው ልጅ ሕይወት በሚሰጥ ክብር ነው"ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
"ዶናልድ ትራምፕ ዛሬ ኢራንን የሚወጋው ያቺ ሀገር ልትቋቋመው እንደማትችል ስላመነ ነው። የእኔን ሀገር ሰሜን ኮሪያን፣ ቻይናን ወይም ሩሲያን ለመተንኮስ የማይደፍረውም ለዚህ ነው፤ ምክንያቱም የእኛን ኃይልና ሚሳኤሎቻችንን በሚገባ ያውቃል።
እኛ መላዋን አሜሪካ በአንድ ሚሳኤል ብቻ ከምድረ-ገጽ ማጥፋት እንችላለን። እሱ ግጭት የሚፈልገው አጸፋ መመለስ እንደማይችሉ ከሚያምንባቸው አገራት ጋር ነው።
ነገር ግን ኢራን በእውነት ከፈለገች አብዛኛውን የአሜሪካ ክፍል በቦምብ መደብደብ ትችላለች። ጥቃት የማታደርሰው ግን የብዙ አሜሪካውያን ንጹሐን ዜጎች ሕይወት እንዳይጠፋ በመፍራት ብቻ ነው።"
ዛቻ ኃይልን አያረጋግጥም። የአንድ ሀገር እውነተኛ ታላቅነት የሚታየው በሰላም፣ በፍትህ እና ለሰው ልጅ ሕይወት በሚሰጥ ክብር ነው"ብለዋል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
5 months ago
ሰሜን ኮሪያ 10 የሚደርሱ ሚሳዔሎችን ወደ ጃፓን አስወነጨፈች።
ሚሳዔሎቹ ከሰናን ግዛት ተነስተው 350 ኪሎሜትር በመጓዝ በጃፓን ባህር አርፈዋል።
ፒዮንግያንግ ሚሳዔልቹን ያስወነጨፈችው አሜሪካ እና ጃፓን የሚያካሂዱትን የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በመቃወም ነው።
ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ከሳምንታት በፊት ፓርቲያቸው ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ሰሜን ኮሪያ ከአሜሪካ ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኗን ጠቁመዋል።
ኪም ዋሽንግተን ለድርድር የፒዮንግያንግን ብሄራዊ ጥቅም አምና መቀበል እንዳለባት አሳስበዋል። #trtworld
seledadotio
seledadotio
ሚሳዔሎቹ ከሰናን ግዛት ተነስተው 350 ኪሎሜትር በመጓዝ በጃፓን ባህር አርፈዋል።
ፒዮንግያንግ ሚሳዔልቹን ያስወነጨፈችው አሜሪካ እና ጃፓን የሚያካሂዱትን የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በመቃወም ነው።
ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ከሳምንታት በፊት ፓርቲያቸው ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ሰሜን ኮሪያ ከአሜሪካ ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆኗን ጠቁመዋል።
ኪም ዋሽንግተን ለድርድር የፒዮንግያንግን ብሄራዊ ጥቅም አምና መቀበል እንዳለባት አሳስበዋል። #trtworld
seledadotio
seledadotio
5 months ago
ሰሜን ኮሪያ 10 የሚጠጉ የባሊስቲክ ሚሳይሎችን መተኮሷ ተነገረ
የደቡብ ኮሪያ ጦር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ ሰሜን ኮሪያ 10 የሚጠጉ አጫጭር ርቀት ተኳሽ የባሊስቲክ ሚሳይሎችን ወደ ምስራቃዊ የባሕር ጠረፏ መተኮሷን አስታውቋል።
አል አረቢያ የደቡብ ኮሪያን የጦር ኃይሎች ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ሚሳይሎቹ የተተኮሱት ከሰሜን ኮሪያ ዋና ከተማ ፒዮንግያንግ አቅራቢያ ካለው የሱናን አካባቢ ነው።
እነዚህ ሚሳይሎች ወደ 350 ኪሎ ሜትር የሚጠጋ ርቀት ከተጓዙ በኋላ በምስራቃዊው የባሕር ክፍል (የጃፓን ባሕር) ላይ ማረፋቸውን የደቡብ ኮሪያ የጋራ ኤታማዦር ሹም ገልጸዋል።
የደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ድርጊቱን "ግልጽ ትንኮሳ" ሲሉ የጠሩት ሲሆን፤ ጥቃቱን ተከትሎ ከጃፓን እና ከአሜሪካ ጋር በመተባበር ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ መጠነ ሰፊ የሚሳይል ሙከራ የተደረገው፤ ሰሜን ኮሪያ ከጥቂት ቀናት በፊት ወታደራዊ የሰላዮች ሳተላይት ወደ ህዋ ለማምጠቅ ያደረገችው ሙከራ መክሸፉን ተከትሎ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
ፒዮንግያንግ በቅርቡ በቆሻሻ የተሞሉ ፊኛዎችን ወደ ደቡብ ኮሪያ ድንበር በመላክ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሳው እንደነበር ይታወሳል።
የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሚዮ ኪሺዳ በበኩላቸው፤ ሰሜን ኮሪያ የባሊስቲክ ሚሳይል በመተኮስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጥሳለች ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።
ልዑል ወልዴ
የደቡብ ኮሪያ ጦር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ ሰሜን ኮሪያ 10 የሚጠጉ አጫጭር ርቀት ተኳሽ የባሊስቲክ ሚሳይሎችን ወደ ምስራቃዊ የባሕር ጠረፏ መተኮሷን አስታውቋል።
አል አረቢያ የደቡብ ኮሪያን የጦር ኃይሎች ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ሚሳይሎቹ የተተኮሱት ከሰሜን ኮሪያ ዋና ከተማ ፒዮንግያንግ አቅራቢያ ካለው የሱናን አካባቢ ነው።
እነዚህ ሚሳይሎች ወደ 350 ኪሎ ሜትር የሚጠጋ ርቀት ከተጓዙ በኋላ በምስራቃዊው የባሕር ክፍል (የጃፓን ባሕር) ላይ ማረፋቸውን የደቡብ ኮሪያ የጋራ ኤታማዦር ሹም ገልጸዋል።
የደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ድርጊቱን "ግልጽ ትንኮሳ" ሲሉ የጠሩት ሲሆን፤ ጥቃቱን ተከትሎ ከጃፓን እና ከአሜሪካ ጋር በመተባበር ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ መጠነ ሰፊ የሚሳይል ሙከራ የተደረገው፤ ሰሜን ኮሪያ ከጥቂት ቀናት በፊት ወታደራዊ የሰላዮች ሳተላይት ወደ ህዋ ለማምጠቅ ያደረገችው ሙከራ መክሸፉን ተከትሎ መሆኑ ትኩረት ስቧል።
ፒዮንግያንግ በቅርቡ በቆሻሻ የተሞሉ ፊኛዎችን ወደ ደቡብ ኮሪያ ድንበር በመላክ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ውጥረት ይበልጥ አባብሳው እንደነበር ይታወሳል።
የጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሚዮ ኪሺዳ በበኩላቸው፤ ሰሜን ኮሪያ የባሊስቲክ ሚሳይል በመተኮስ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎችን ጥሳለች ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።
ልዑል ወልዴ
5 months ago
መጀመሪያ ቬንዙዌላ አሁን ደግሞ ኢራን፦ ቻይና አጋሮቿን ለምን አትከላከልም?
ከላ ናሲዮን ጋዜጣ ከቀረበ ፅሁፍ ላይ የተወሰደ
በሁለቱም አጋጣሚዎች የኤዥያው ግዙፍ ሀገር ራሱን "በጥንካሬ ማውገዝ" ላይ ብቻ ገድቧል።
የቻይናውያንን አካሄድ ለመረዳት አንዳንድ ጥንታዊ አባባሎቻቸው ሊረዱ ይችላሉ። የቻይና የኢኮኖሚ ዘመናዊነት ቁልፍ መሪ የነበሩት ዴንግ ዚያኦፒንግ (1904-1997) እንዲህ ብሎ መደጋገም ይወዱ ነበር፦ "ተራራ ላይ ተቀምጠህ ነብሮች ሲጣሉ ተመልከት።"
ባለፉት ሁለት ወራት ቻይና በአጋሮቿ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ባሳደሩ ሁለት ግጭቶች ላይ ከሩቅ ሆና ያለ ፍላጎት የምትመለከት ትመስል ነበር። በተከታታይ በተከሰቱ ፈጣን ክስተቶች፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቬንዙዌላውን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን ከስልጣን አንስተው በቁጥጥር ስር ውለው ወደ አሜሪካ እንዲወሰዱ አድርገዋል። ከአንድ ወር ተኩል በኋላ ደግሞ ከእስራኤል ጋር በመተባበር መንፈሳዊ መሪውን አሊ ካሜኒን ጨምሮ ትላልቅ ባለ ስልጣናት ተገድልዋል።
ቻይና የቬንዙዌላ እና የኢራን ነዳጅ ዋና የንግድ አጋር እና ገዢ ብትሆንም፣ እንዲሁም በዓለም ላይ ካሉ በጣም ጠንካራ ወታደሮች አንዱ ቢኖራትም፣ በሁለቱም ሁኔታዎች የሰጠችው ምላሽ "በጥንካሬ ማውገዝ" እና ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች እንዲቀጥሉ በመምከር ብቻ የተገደበ ነበር። ማዱሮ ወይም ካሜኒ ከቤጂንግ የበለጠ ነገር ጠብቀው ከሆነ፣ የዚህን ልዩ አጋር ታሪክ በሚገባ ስላላወቁ ነው።
የሲኖ-አርጀንቲና ኦብዘርቫቶሪ ዳይሬክተር እና ከዚጂያንግ ዩኒቨርሲቲ በቻይና ጥናት የማስተርስ ድግሪ ያላቸው ፓትሪሲዮ ጁስቶ ለላ ናሲዮን ሲናገሩ፦ "ቻይና የኑክሌር እና የወታደራዊ ልዕለ ኃያል ሀገር ናት፣ ነገር ግን ባለፉት 4,000 ዓመታት ውስጥ ከድንበሯ ውጭ በማንኛውም ጦርነት ውስጥ ጣልቃ ገብታ አታውቅም።
እ.ኤ.አ. በ1979 የካምቦዲያ ክሜር ሩዥ ቬትናምን በወረረበት ወቅት ብቻ ነው ጣልቃ የገባችው፣ ያኔም ቢሆን እንደ ውስጣዊ ስጋት ስላየቻቸው ብቻ ነበር። ቻይና በወታደራዊ ኃይሏ የምትታመነው ራሷን ለመከላከል እንጂ ሌሎችን ለመከላከል ወይም ሌሎች አገሮችን ለመቆጣጠር አይደለም" ብለዋል።
ጁስቶ አክለውም "ስለ እነዚህ ነገሮች ስታወራ አንድ ሰው 'ይህ የኮምኒስት ፕሮፓጋንዳ ነው' ሊል ይችላል። ነገር ግን የቻይናን አገዛዝ ወታደራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች እና ጥልቅ ፍላጎቶች ለመረዳት ታሪክን እና የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ማየት ብቻ በቂ ነው" ብለዋል።
ከ2015 እስከ 2019 በቻይና የቀድሞ የአርጀንቲና አምባሳደር የነበሩት ዲዬጎ ጉላር፣ የኤዥያው ግዙፍ ሀገር በሌሎች ሀገራት አስቸኳይ ሁኔታዎች ወይም በዚህ ሁኔታ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያልተጠበቁ ውሳኔዎች ምክንያት በኮሚኒስት ፓርቲ የተቀረጸውን የመንግስት ፕሮግራም እንደማይቀይር ይስማማሉ።
"እ.ኤ.አ. በ2017 በተካሄደው የፓርቲ ኮንግረስ፣ ቻይናውያን በ2049 የዓለም ትልቁ ኢኮኖሚ የመሆን ግብ አስቀምጠዋል። አሁን ደግሞ በሚቀጥለው አስርት ዓመት አጋማሽ ላይ ያንን ግብ ለማሳካት በሚያስችል ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ዛሬ ቻይና ከ190 ሀገራት ውስጥ የ140ዎቹ ዋና የንግድ አጋር ናት። ስለዚህ በትራምፕ ወታደራዊ ዛቻ አይረበሹም" ሲሉ ጉላር ገልጸዋል።
ዴንግ ዚያኦፒንግ ይደግሙት የነበረው እና የቻይናውያንን የጊዜ አረዳድ እና የስልጣን አያያዝ ለመረዳት የሚረዳው ሁለተኛው አባባል እንዲህ ይላል፦ "ችሎታህን ደብቅ እና አመቺውን ጊዜ ጠብቅ፤ መሪነትን በፍጹም አትጠይቅ።"
የኢኮኖሚ ኃይል
የኢኮኖሚ ሁኔታዋን ስንመለከት፣ ማኦ ዜዱንግ በ1949 ወደ ስልጣን ሲመጡ ቻይና በድህነት የተዘፈቀች እና በጦርነት የወደመች ተራ ሀገር ነበረች። አሁን ግን በ2037 አሜሪካን በጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (Nominal GDP) በመብለጥ እና የዓለም የማኑፋክቸሪንግ ምርትን 35% በመሸፈን (የአሜሪካን እጥፍ) የዓለም ቀዳሚ የኢኮኖሚ ኃይል ትሆናለች ተብሎ ይገመታል።
ጉላር ሲያስረዱ "ቤጂንግ አብዛኛውን ጊዜ ከኢኮኖሚ ግቦቿ አታፈነግጥም። በትራምፕ የታሪፍ ማዕቀብ ምክንያት ቻይናውያን 29% የሚሆነውን የወጪ ንግዳቸውን አጥተዋል።
ነገር ግን በቻይናውያን ትዕግስት፣ ግንኙነቶችን መልሰው በመገንባት በአንድ ዓመት ውስጥ ያንኑ የወጪ ንግድ ደረጃ መልሰው አግኝተዋል። በቬንዙዌላ ለቻቪስታ አገዛዝ 65 ቢሊዮን ዶላር አበድረዋል። ማዱሮ ከወደቁ በኋላም፣ ከመንገዳቸው እና ከግብቸው ሳይወጡ ያንን ብድር እንደ 'ኪሳራ' ቆጥረው ትተውታል።
በእነዚህ ቀናት ኢራን የሆርሙዝን ሰርጥ ከዘጋች በኋላ፣ ቻይና ለመርከቦቿ ያ እገዳ እንዲነሳ ማድረግ ችላለች" ብለዋል።
ቻይና ሌሎች ሀገራትን በኢኮኖሚ ለመቆጣጠር የምትሞክር "ጣልቃ ገብ" ሀገር ተብላ ልትፈረጅ ትችላለች ወይ ተብለው ሲጠየቁ ጁስቶ እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ "ከአርጀንቲና በስተቀር በክልሉ ያሉ ሁሉም ሀገራት ከቻይና ጋር የንግድ ትርፍ (Surplus) አላቸው፣ እንዲሁም ከፍተኛ ኢንቨስትመንት አግኝተዋል።"
አክለውም "ብራዚልን እንደ ምሳሌ ብንወስድ፣ 30 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ አላት። ብራዚላውያን ከቻይና ከሚገዙት በላይ ለቻይና ይሸጣሉ። ለአንድ ብራዚላዊ ስለ ቻይና የኢኮኖሚ 'ጣልቃ ገብነት' ብታወራበት ፊትህ ላይ ይስቅብሃል። እንደ አጋር ወደድንም ጠላንም፣ ግዙፉ የሀገር ውስጥ ገበያዋ የማይተካ የኢኮኖሚ አጋር ነው፣ አብዛኞቹ ሀገራትም የሚያዩት በዚህ መንገድ ነው። በተጨማሪም ቻይና የንግድ አጋሮቿን በርዕዮተ ዓለም፣ በሃይማኖት፣ በአምባገነንነት ወይም በዲሞክራሲ ላይ ተመስርታ አትመርጥም። ቅድሚያ የምትሰጠው ለኢኮኖሚ እድገቷ ነው" ብለዋል።
ወታደራዊ ኃይል
ከወታደራዊ ጥንካሬ አንጻር የቻይና ጦር በግምት ሁለት ሚሊዮን ንቁ አባላት ያሉት ሲሆን በዓለም ትልቁ ነው። ታዲያ ጥያቄው እንደ ኔቶ (NATO) ወይም እንደ ቀድሞው የዋርሶው ስምምነት (Warsaw Pact) ከሌሎች ኃይሎች ጋር ወታደራዊ ጥምረት በመፍጠር ከርዕዮተ ዓለም አጋሮቿ ጋር ለጋራ መከላከያ ለምን አትቆምም የሚል ነው።
"እነዚያ ሁሉ ጥምረቶች አጋር ሀገር በሶስተኛ ወገን ከተጠቃ የመከላከል ግዴታን ያካትታሉ። ይህ ደግሞ ቻይና በፍጹም የማታደርገው ነገር ነው። ኃይሏ የራሷን ግዛት ለመከላከል ነው፣ ይህም እንደ ቻይናውያን አመለካከት የራቀችውን 'ክፍለ ሀገር' ታይዋንን ይጨምራል። ቻይና ከሰሜን ኮሪያ ወይም ከፓኪስታን ጋር አንዳንድ ወታደራዊ ስምምነቶች ያሏት ከድንበሯ አጠገብ ያሉ የኑክሌር ኃይሎች ስለሆኑ ብቻ ነው" ሲሉ ጁስቶ መለሱ።
የኤዥያው ግዙፍ ሀገር ለመከላከያ የምታውለው ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርቷ 1.7% ያህል ሲሆን፣ ይህም ከዓለም አማካይ 2.4% በታች ነው።
"ቻይናውያን የመከላከያ ፖሊሲያቸውን እንዴት እንደሚረዱ ለማወቅ፣ ከ1954 ጀምሮ የውጭ ፖሊሲያቸውን የሚመሩትን እና ላለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ያልለወጡትን 'አምስቱ የሰላማዊ አብሮ መኖር መርሆዎች' ማየት ያስፈልጋል" ሲሉ ጁስቶ ተናግረዋል።
እነዚህ መርሆዎች፦ የሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የጋራ መከባበር፣ እርስ በእርስ አለመወራረር፣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ እኩልነት እና የጋራ ጥቅም፣ እንዲሁም ሰላማዊ አብሮ መኖር ናቸው።
ዴንግ ዚያኦፒንግ ደጋግመው የተናገሩትን አስፈሪ ሀረግ ማስታወስ ብቻ ይበቃል፦ "ጥንካሬህን ደብቅ፣ አመቺውን ጊዜ ጠብቅ።"
ከላ ናሲዮን ጋዜጣ ከቀረበ ፅሁፍ ላይ የተወሰደ
በሁለቱም አጋጣሚዎች የኤዥያው ግዙፍ ሀገር ራሱን "በጥንካሬ ማውገዝ" ላይ ብቻ ገድቧል።
የቻይናውያንን አካሄድ ለመረዳት አንዳንድ ጥንታዊ አባባሎቻቸው ሊረዱ ይችላሉ። የቻይና የኢኮኖሚ ዘመናዊነት ቁልፍ መሪ የነበሩት ዴንግ ዚያኦፒንግ (1904-1997) እንዲህ ብሎ መደጋገም ይወዱ ነበር፦ "ተራራ ላይ ተቀምጠህ ነብሮች ሲጣሉ ተመልከት።"
ባለፉት ሁለት ወራት ቻይና በአጋሮቿ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ባሳደሩ ሁለት ግጭቶች ላይ ከሩቅ ሆና ያለ ፍላጎት የምትመለከት ትመስል ነበር። በተከታታይ በተከሰቱ ፈጣን ክስተቶች፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቬንዙዌላውን ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮን ከስልጣን አንስተው በቁጥጥር ስር ውለው ወደ አሜሪካ እንዲወሰዱ አድርገዋል። ከአንድ ወር ተኩል በኋላ ደግሞ ከእስራኤል ጋር በመተባበር መንፈሳዊ መሪውን አሊ ካሜኒን ጨምሮ ትላልቅ ባለ ስልጣናት ተገድልዋል።
ቻይና የቬንዙዌላ እና የኢራን ነዳጅ ዋና የንግድ አጋር እና ገዢ ብትሆንም፣ እንዲሁም በዓለም ላይ ካሉ በጣም ጠንካራ ወታደሮች አንዱ ቢኖራትም፣ በሁለቱም ሁኔታዎች የሰጠችው ምላሽ "በጥንካሬ ማውገዝ" እና ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች እንዲቀጥሉ በመምከር ብቻ የተገደበ ነበር። ማዱሮ ወይም ካሜኒ ከቤጂንግ የበለጠ ነገር ጠብቀው ከሆነ፣ የዚህን ልዩ አጋር ታሪክ በሚገባ ስላላወቁ ነው።
የሲኖ-አርጀንቲና ኦብዘርቫቶሪ ዳይሬክተር እና ከዚጂያንግ ዩኒቨርሲቲ በቻይና ጥናት የማስተርስ ድግሪ ያላቸው ፓትሪሲዮ ጁስቶ ለላ ናሲዮን ሲናገሩ፦ "ቻይና የኑክሌር እና የወታደራዊ ልዕለ ኃያል ሀገር ናት፣ ነገር ግን ባለፉት 4,000 ዓመታት ውስጥ ከድንበሯ ውጭ በማንኛውም ጦርነት ውስጥ ጣልቃ ገብታ አታውቅም።
እ.ኤ.አ. በ1979 የካምቦዲያ ክሜር ሩዥ ቬትናምን በወረረበት ወቅት ብቻ ነው ጣልቃ የገባችው፣ ያኔም ቢሆን እንደ ውስጣዊ ስጋት ስላየቻቸው ብቻ ነበር። ቻይና በወታደራዊ ኃይሏ የምትታመነው ራሷን ለመከላከል እንጂ ሌሎችን ለመከላከል ወይም ሌሎች አገሮችን ለመቆጣጠር አይደለም" ብለዋል።
ጁስቶ አክለውም "ስለ እነዚህ ነገሮች ስታወራ አንድ ሰው 'ይህ የኮምኒስት ፕሮፓጋንዳ ነው' ሊል ይችላል። ነገር ግን የቻይናን አገዛዝ ወታደራዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች እና ጥልቅ ፍላጎቶች ለመረዳት ታሪክን እና የቅርብ ጊዜ ክስተቶችን ማየት ብቻ በቂ ነው" ብለዋል።
ከ2015 እስከ 2019 በቻይና የቀድሞ የአርጀንቲና አምባሳደር የነበሩት ዲዬጎ ጉላር፣ የኤዥያው ግዙፍ ሀገር በሌሎች ሀገራት አስቸኳይ ሁኔታዎች ወይም በዚህ ሁኔታ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያልተጠበቁ ውሳኔዎች ምክንያት በኮሚኒስት ፓርቲ የተቀረጸውን የመንግስት ፕሮግራም እንደማይቀይር ይስማማሉ።
"እ.ኤ.አ. በ2017 በተካሄደው የፓርቲ ኮንግረስ፣ ቻይናውያን በ2049 የዓለም ትልቁ ኢኮኖሚ የመሆን ግብ አስቀምጠዋል። አሁን ደግሞ በሚቀጥለው አስርት ዓመት አጋማሽ ላይ ያንን ግብ ለማሳካት በሚያስችል ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ዛሬ ቻይና ከ190 ሀገራት ውስጥ የ140ዎቹ ዋና የንግድ አጋር ናት። ስለዚህ በትራምፕ ወታደራዊ ዛቻ አይረበሹም" ሲሉ ጉላር ገልጸዋል።
ዴንግ ዚያኦፒንግ ይደግሙት የነበረው እና የቻይናውያንን የጊዜ አረዳድ እና የስልጣን አያያዝ ለመረዳት የሚረዳው ሁለተኛው አባባል እንዲህ ይላል፦ "ችሎታህን ደብቅ እና አመቺውን ጊዜ ጠብቅ፤ መሪነትን በፍጹም አትጠይቅ።"
የኢኮኖሚ ኃይል
የኢኮኖሚ ሁኔታዋን ስንመለከት፣ ማኦ ዜዱንግ በ1949 ወደ ስልጣን ሲመጡ ቻይና በድህነት የተዘፈቀች እና በጦርነት የወደመች ተራ ሀገር ነበረች። አሁን ግን በ2037 አሜሪካን በጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (Nominal GDP) በመብለጥ እና የዓለም የማኑፋክቸሪንግ ምርትን 35% በመሸፈን (የአሜሪካን እጥፍ) የዓለም ቀዳሚ የኢኮኖሚ ኃይል ትሆናለች ተብሎ ይገመታል።
ጉላር ሲያስረዱ "ቤጂንግ አብዛኛውን ጊዜ ከኢኮኖሚ ግቦቿ አታፈነግጥም። በትራምፕ የታሪፍ ማዕቀብ ምክንያት ቻይናውያን 29% የሚሆነውን የወጪ ንግዳቸውን አጥተዋል።
ነገር ግን በቻይናውያን ትዕግስት፣ ግንኙነቶችን መልሰው በመገንባት በአንድ ዓመት ውስጥ ያንኑ የወጪ ንግድ ደረጃ መልሰው አግኝተዋል። በቬንዙዌላ ለቻቪስታ አገዛዝ 65 ቢሊዮን ዶላር አበድረዋል። ማዱሮ ከወደቁ በኋላም፣ ከመንገዳቸው እና ከግብቸው ሳይወጡ ያንን ብድር እንደ 'ኪሳራ' ቆጥረው ትተውታል።
በእነዚህ ቀናት ኢራን የሆርሙዝን ሰርጥ ከዘጋች በኋላ፣ ቻይና ለመርከቦቿ ያ እገዳ እንዲነሳ ማድረግ ችላለች" ብለዋል።
ቻይና ሌሎች ሀገራትን በኢኮኖሚ ለመቆጣጠር የምትሞክር "ጣልቃ ገብ" ሀገር ተብላ ልትፈረጅ ትችላለች ወይ ተብለው ሲጠየቁ ጁስቶ እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ "ከአርጀንቲና በስተቀር በክልሉ ያሉ ሁሉም ሀገራት ከቻይና ጋር የንግድ ትርፍ (Surplus) አላቸው፣ እንዲሁም ከፍተኛ ኢንቨስትመንት አግኝተዋል።"
አክለውም "ብራዚልን እንደ ምሳሌ ብንወስድ፣ 30 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ አላት። ብራዚላውያን ከቻይና ከሚገዙት በላይ ለቻይና ይሸጣሉ። ለአንድ ብራዚላዊ ስለ ቻይና የኢኮኖሚ 'ጣልቃ ገብነት' ብታወራበት ፊትህ ላይ ይስቅብሃል። እንደ አጋር ወደድንም ጠላንም፣ ግዙፉ የሀገር ውስጥ ገበያዋ የማይተካ የኢኮኖሚ አጋር ነው፣ አብዛኞቹ ሀገራትም የሚያዩት በዚህ መንገድ ነው። በተጨማሪም ቻይና የንግድ አጋሮቿን በርዕዮተ ዓለም፣ በሃይማኖት፣ በአምባገነንነት ወይም በዲሞክራሲ ላይ ተመስርታ አትመርጥም። ቅድሚያ የምትሰጠው ለኢኮኖሚ እድገቷ ነው" ብለዋል።
ወታደራዊ ኃይል
ከወታደራዊ ጥንካሬ አንጻር የቻይና ጦር በግምት ሁለት ሚሊዮን ንቁ አባላት ያሉት ሲሆን በዓለም ትልቁ ነው። ታዲያ ጥያቄው እንደ ኔቶ (NATO) ወይም እንደ ቀድሞው የዋርሶው ስምምነት (Warsaw Pact) ከሌሎች ኃይሎች ጋር ወታደራዊ ጥምረት በመፍጠር ከርዕዮተ ዓለም አጋሮቿ ጋር ለጋራ መከላከያ ለምን አትቆምም የሚል ነው።
"እነዚያ ሁሉ ጥምረቶች አጋር ሀገር በሶስተኛ ወገን ከተጠቃ የመከላከል ግዴታን ያካትታሉ። ይህ ደግሞ ቻይና በፍጹም የማታደርገው ነገር ነው። ኃይሏ የራሷን ግዛት ለመከላከል ነው፣ ይህም እንደ ቻይናውያን አመለካከት የራቀችውን 'ክፍለ ሀገር' ታይዋንን ይጨምራል። ቻይና ከሰሜን ኮሪያ ወይም ከፓኪስታን ጋር አንዳንድ ወታደራዊ ስምምነቶች ያሏት ከድንበሯ አጠገብ ያሉ የኑክሌር ኃይሎች ስለሆኑ ብቻ ነው" ሲሉ ጁስቶ መለሱ።
የኤዥያው ግዙፍ ሀገር ለመከላከያ የምታውለው ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርቷ 1.7% ያህል ሲሆን፣ ይህም ከዓለም አማካይ 2.4% በታች ነው።
"ቻይናውያን የመከላከያ ፖሊሲያቸውን እንዴት እንደሚረዱ ለማወቅ፣ ከ1954 ጀምሮ የውጭ ፖሊሲያቸውን የሚመሩትን እና ላለፉት ሰባት አስርት ዓመታት ያልለወጡትን 'አምስቱ የሰላማዊ አብሮ መኖር መርሆዎች' ማየት ያስፈልጋል" ሲሉ ጁስቶ ተናግረዋል።
እነዚህ መርሆዎች፦ የሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የጋራ መከባበር፣ እርስ በእርስ አለመወራረር፣ በውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባት፣ እኩልነት እና የጋራ ጥቅም፣ እንዲሁም ሰላማዊ አብሮ መኖር ናቸው።
ዴንግ ዚያኦፒንግ ደጋግመው የተናገሩትን አስፈሪ ሀረግ ማስታወስ ብቻ ይበቃል፦ "ጥንካሬህን ደብቅ፣ አመቺውን ጊዜ ጠብቅ።"
5 months ago
ድላችን ሐውልት
የካራማራ ድል መታሰቢያ ሐውልት
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት የሚገኘውና "ድላችን" ተብሎ የሚጠራው ሐውልት በ1970 ዓ.ም በምስራቅ ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የዚያድ ባሬን ወራሪ ጦር ድል ለማድረግ መስዋዕት ለሆኑት የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ሲሆን፣ የድሉን አራተኛ ዓመት በማክበር በ1974 ዓ.ም ተመርቋል።
የሐውልቱ ስነ-ጥበባዊ ንድፍ በወቅቱ በነበሩ የኢትዮጵያና የሰሜን ኮሪያ (Mansudae Art Studio) ባለሙያዎች ትብብር የተሰራ ነው።
የግንባታው ዘይቤ "ሶሻሊስት ሪአሊዝም" የተከተለ በመሆኑ፣ የሐውልቱ ግዝፈትና የወታደሮቹ አቋቋም የጥንካሬና የድል አድራጊነት ስሜትን በጉልህ ያንጸባርቃል።
በሐውልቱ አናት ላይ የሚታዩት ሶስት ወታደሮች የመደበኛ ጦርን፣ የአየር ኃይልን እና የክብር ዘበኛን ወይም የሚሊሻን ተወካዮች ሲሆኑ፣ የለበሱት ወታደራዊ ልብስና የያዟቸው የኤኬ-47 (AK-47) ጠመንጃዎች በወቅቱ የነበረውን ትክክለኛ ወታደራዊ ትጥቅ የሚወክሉ ናቸው።
በሐውልቱ የታችኛው ክፍል በሚገኘው ሰፊ ግድግዳ ላይ የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች ጎን ለጎን ሆነው ሲዋጉ የሚያሳይ ምስል ተቀርጾ ይገኛል። በተጨማሪም በጦርነቱ ህይወታቸውን ያጡ የ160 ኩባውያን ወታደሮች ፎቶግራፍ በሐውልቱ ግራና ቀኝ ባሉት ግንቦች ላይ በሴራሚክ ተሰርቶ ተለጥፎ ይታያል።
ይህ ሐውልቱ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስከበር የተከፈለውን መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ በወቅቱ የነበረውን ጥልቅ የኢትዮ-ኩባ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቁርኝት እንዲሁም የሶቪየት ህብረትን የርዕዮተ ዓለም ተጽዕኖ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ምንም እንኳን በ1983 ዓ.ም የደርግ መንግስት መውደቅን ተከትሎ ሐውልቱ የፖለቲካ ምልክት ተደርጎ በመወሰዱ የኩባ ወታደሮች ፎቶግራፎች ተነስተውና ጥገና ተነፍጎት ለዓመታት ቢቆይም፣ ቆይቶ ግን በሁለቱ አገራት ስምምነት መሰረት ዳግም ታድሷል።
በአሁኑ ወቅት ሐውልቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነት የተከበረበትን ታሪክ የሚዘክር ብሄራዊ ቅርስ ተደርጎ ይወሰዳል።
በየዓመቱ የካቲት 26 ቀን የሚከበረው የካራማራ ድል ቀንም በዚህ ስፍራ በታላቅ ስነ-ስርዓት ይታሰባል።
#ethiopia #cuba #karamaramonument #addisababa #history #victorymonument #ethiopianhistory #militaryheritage #coldwarhistory
የካራማራ ድል መታሰቢያ ሐውልት
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት የሚገኘውና "ድላችን" ተብሎ የሚጠራው ሐውልት በ1970 ዓ.ም በምስራቅ ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የዚያድ ባሬን ወራሪ ጦር ድል ለማድረግ መስዋዕት ለሆኑት የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ሲሆን፣ የድሉን አራተኛ ዓመት በማክበር በ1974 ዓ.ም ተመርቋል።
የሐውልቱ ስነ-ጥበባዊ ንድፍ በወቅቱ በነበሩ የኢትዮጵያና የሰሜን ኮሪያ (Mansudae Art Studio) ባለሙያዎች ትብብር የተሰራ ነው።
የግንባታው ዘይቤ "ሶሻሊስት ሪአሊዝም" የተከተለ በመሆኑ፣ የሐውልቱ ግዝፈትና የወታደሮቹ አቋቋም የጥንካሬና የድል አድራጊነት ስሜትን በጉልህ ያንጸባርቃል።
በሐውልቱ አናት ላይ የሚታዩት ሶስት ወታደሮች የመደበኛ ጦርን፣ የአየር ኃይልን እና የክብር ዘበኛን ወይም የሚሊሻን ተወካዮች ሲሆኑ፣ የለበሱት ወታደራዊ ልብስና የያዟቸው የኤኬ-47 (AK-47) ጠመንጃዎች በወቅቱ የነበረውን ትክክለኛ ወታደራዊ ትጥቅ የሚወክሉ ናቸው።
በሐውልቱ የታችኛው ክፍል በሚገኘው ሰፊ ግድግዳ ላይ የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች ጎን ለጎን ሆነው ሲዋጉ የሚያሳይ ምስል ተቀርጾ ይገኛል። በተጨማሪም በጦርነቱ ህይወታቸውን ያጡ የ160 ኩባውያን ወታደሮች ፎቶግራፍ በሐውልቱ ግራና ቀኝ ባሉት ግንቦች ላይ በሴራሚክ ተሰርቶ ተለጥፎ ይታያል።
ይህ ሐውልቱ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስከበር የተከፈለውን መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ በወቅቱ የነበረውን ጥልቅ የኢትዮ-ኩባ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቁርኝት እንዲሁም የሶቪየት ህብረትን የርዕዮተ ዓለም ተጽዕኖ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ምንም እንኳን በ1983 ዓ.ም የደርግ መንግስት መውደቅን ተከትሎ ሐውልቱ የፖለቲካ ምልክት ተደርጎ በመወሰዱ የኩባ ወታደሮች ፎቶግራፎች ተነስተውና ጥገና ተነፍጎት ለዓመታት ቢቆይም፣ ቆይቶ ግን በሁለቱ አገራት ስምምነት መሰረት ዳግም ታድሷል።
በአሁኑ ወቅት ሐውልቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነት የተከበረበትን ታሪክ የሚዘክር ብሄራዊ ቅርስ ተደርጎ ይወሰዳል።
በየዓመቱ የካቲት 26 ቀን የሚከበረው የካራማራ ድል ቀንም በዚህ ስፍራ በታላቅ ስነ-ስርዓት ይታሰባል።
#ethiopia #cuba #karamaramonument #addisababa #history #victorymonument #ethiopianhistory #militaryheritage #coldwarhistory
5 months ago
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ቀጭን ማስጠንቀቂያ ሰጡ
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በአሁኑ ወቅት በኢራን ውስጥ በሚገኙ ዜጎቻቸው ላይ ማንኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስ ሀገራቸው በቀጥታ ወደ ጦርነቱ እንደምትገባ ለአለም አቀፉ ጥምረት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። መሪው የዜጎቻቸው በሰላም መመለስ "ለድርድር የማይቀርብ" ጉዳይ መሆኑን ገልጸውንይህም ቀጣናዊ ግጭቱን ወደ ኑክሌር ኃያላን ፍጥጫ ሊቀይረው የሚችል አደገኛ ሁኔታ መፍጠሩ ተነግሯል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰማው የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ "ኢራን ማለት 50 ሰሜን ኮሪያ ማለት ናት" በማለት የቀጣናውን ስጋት ከገለጹ በኋላ ነው ይህ አባባል በተፋላሚ ወገኖች መካከል ያለውን ጥልቅ የርዕዮተ-ዓለም ልዩነት በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ቀውሶች
የዓለም ጦርነት ስጋት እያየለ በመጣበት በዚህ ወቅት
* ኳታር፦ በሀገሪቱ የድንገተኛ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን የጋዝ ምርት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል።
* ስፔን፦ ከአሜሪካ ጋር ለትብብር የተስማማችው በንግድ ታሪፍ (tariffs) ከፍተኛ ጫና ከደረሰባት በኋላ እንደሆነ ተገልጿል።
* ወታደራዊ ኪሳራ፦ በኢራን የባህር ኃይል ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ቀጥሏል። በተለይም የኢራን የጦር መርከብ እና IRIS Fateh የተሰኘችው ሰርጓጅ መርከብ መጥለቃቸው ወታደራዊ ውጥረቱን ጣሪያ አስነክቶታል።
*ምንም እንኳን የአሜሪካ ኮንግረስ ተጨማሪ ጥቃቶችን ለማገድ ድምጽ ቢሰጥም ፔንታጎን ለደረሰበት የ2 ቢሊዮን ዶላር የመሳሪያ ኪሳራ ማካካሻ 50 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ በጀት እየጠየቀ ይገኛል።
የሩሲያ እና የናቶ (NATO) እንቅስቃሴ
ሩሲያ ከቴህራን መሪዎች ጋር ያላት ግንኙነት በመቋረጡ የኢራንን የኑክሌር ጣቢያዎች ለመቆጣጠር ዝግጅት እያደረገች መሆኑ ተሰምቷል። በሌላ በኩል በቱርክ የሚገኘው የናቶ የአየር መከላከያ ሥርዓት የባሊስቲክ ሚሳኤል ካከሸፈ በኋላ ከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" ከቀጣናዊ ጣልቃ ገብነት ወደ ዓለም አቀፋዊ ግጭት የመሸጋገር አዝማሚያ እያሳየ ነው። በኢራን የሚገኙ የሰሜን ኮሪያ ዜጎች ጉዳይ ለዚህ ግዙፍ ጦርነት መቀስቀሻ ሊሆን እንደሚችል ተሰግቷል።
የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን በአሁኑ ወቅት በኢራን ውስጥ በሚገኙ ዜጎቻቸው ላይ ማንኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስ ሀገራቸው በቀጥታ ወደ ጦርነቱ እንደምትገባ ለአለም አቀፉ ጥምረት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። መሪው የዜጎቻቸው በሰላም መመለስ "ለድርድር የማይቀርብ" ጉዳይ መሆኑን ገልጸውንይህም ቀጣናዊ ግጭቱን ወደ ኑክሌር ኃያላን ፍጥጫ ሊቀይረው የሚችል አደገኛ ሁኔታ መፍጠሩ ተነግሯል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰማው የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ "ኢራን ማለት 50 ሰሜን ኮሪያ ማለት ናት" በማለት የቀጣናውን ስጋት ከገለጹ በኋላ ነው ይህ አባባል በተፋላሚ ወገኖች መካከል ያለውን ጥልቅ የርዕዮተ-ዓለም ልዩነት በግልጽ ያሳየ ሆኗል።
ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ቀውሶች
የዓለም ጦርነት ስጋት እያየለ በመጣበት በዚህ ወቅት
* ኳታር፦ በሀገሪቱ የድንገተኛ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን የጋዝ ምርት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል።
* ስፔን፦ ከአሜሪካ ጋር ለትብብር የተስማማችው በንግድ ታሪፍ (tariffs) ከፍተኛ ጫና ከደረሰባት በኋላ እንደሆነ ተገልጿል።
* ወታደራዊ ኪሳራ፦ በኢራን የባህር ኃይል ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ቀጥሏል። በተለይም የኢራን የጦር መርከብ እና IRIS Fateh የተሰኘችው ሰርጓጅ መርከብ መጥለቃቸው ወታደራዊ ውጥረቱን ጣሪያ አስነክቶታል።
*ምንም እንኳን የአሜሪካ ኮንግረስ ተጨማሪ ጥቃቶችን ለማገድ ድምጽ ቢሰጥም ፔንታጎን ለደረሰበት የ2 ቢሊዮን ዶላር የመሳሪያ ኪሳራ ማካካሻ 50 ቢሊዮን ዶላር ተጨማሪ በጀት እየጠየቀ ይገኛል።
የሩሲያ እና የናቶ (NATO) እንቅስቃሴ
ሩሲያ ከቴህራን መሪዎች ጋር ያላት ግንኙነት በመቋረጡ የኢራንን የኑክሌር ጣቢያዎች ለመቆጣጠር ዝግጅት እያደረገች መሆኑ ተሰምቷል። በሌላ በኩል በቱርክ የሚገኘው የናቶ የአየር መከላከያ ሥርዓት የባሊስቲክ ሚሳኤል ካከሸፈ በኋላ ከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" ከቀጣናዊ ጣልቃ ገብነት ወደ ዓለም አቀፋዊ ግጭት የመሸጋገር አዝማሚያ እያሳየ ነው። በኢራን የሚገኙ የሰሜን ኮሪያ ዜጎች ጉዳይ ለዚህ ግዙፍ ጦርነት መቀስቀሻ ሊሆን እንደሚችል ተሰግቷል።
5 months ago
ጦርነቱን እቀላቀላለሁ:-ኪም ጆንግ‼️
"አንድም የሰሜን ኮሪያ ዜጋ ቢነካ ጦርነቱን እቀላቀላለሁ!" __የኪም ጆንግ ኡን‼️
የዓለምን ፖለቲካ እጅግ አስደንጋጭ በሆነ መልኩ የለወጠ መግለጫ ከሰሜን ኮሪያ ተሰምቷል። የሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ጣልቃ ለመግባት የሚያስችል እጅግ አደገኛና ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
መሪው በይፋዊ መግለጫቸው እንዳሳወቁት፣ በኢራን ምድር የሚገኙ የሰሜን ኮሪያ ዜጎች ደህንነት ላይ ምንም ዓይነት ድርድር እንደማያደርጉና "አንድም የሀገሬ ዜጋ ላይ ጉዳት ከደረሰ ሰሜን ኮሪያ ያለምንም ማመንታትና ቅድመ ሁኔታ ወደ ጦርነቱ ትገባለች" ሲሉ ዓለምን ያስደነገጠ ዛቻ ሰንዝረዋል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን ንግግር በቀጠናው ያለውን ውጥረት ወደ ሦስተኛው የዓለም ጦርነት ሊቀይረው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ፈጥሯል።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የፒዮንግያንግ ቁጣ ለኢራን ትልቅ ወታደራዊ የጀርባ አጥንት ሊሆን የሚችል ሲሆን፣ አሜሪካና አጋሮቿን ደግሞ ወደ ከፋ ወታደራዊ አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት ነው።
seledadotio
seledadotio
"አንድም የሰሜን ኮሪያ ዜጋ ቢነካ ጦርነቱን እቀላቀላለሁ!" __የኪም ጆንግ ኡን‼️
የዓለምን ፖለቲካ እጅግ አስደንጋጭ በሆነ መልኩ የለወጠ መግለጫ ከሰሜን ኮሪያ ተሰምቷል። የሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ጣልቃ ለመግባት የሚያስችል እጅግ አደገኛና ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
መሪው በይፋዊ መግለጫቸው እንዳሳወቁት፣ በኢራን ምድር የሚገኙ የሰሜን ኮሪያ ዜጎች ደህንነት ላይ ምንም ዓይነት ድርድር እንደማያደርጉና "አንድም የሀገሬ ዜጋ ላይ ጉዳት ከደረሰ ሰሜን ኮሪያ ያለምንም ማመንታትና ቅድመ ሁኔታ ወደ ጦርነቱ ትገባለች" ሲሉ ዓለምን ያስደነገጠ ዛቻ ሰንዝረዋል።
ይህ የኪም ጆንግ ኡን ንግግር በቀጠናው ያለውን ውጥረት ወደ ሦስተኛው የዓለም ጦርነት ሊቀይረው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ፈጥሯል።
ተንታኞች እንደሚሉት፣ የፒዮንግያንግ ቁጣ ለኢራን ትልቅ ወታደራዊ የጀርባ አጥንት ሊሆን የሚችል ሲሆን፣ አሜሪካና አጋሮቿን ደግሞ ወደ ከፋ ወታደራዊ አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት ነው።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
5 months ago
ሰሜን ኮሪያ በኢራን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አወገዘች፤ የኪም ጆንግ ኡን “አወዛጋቢ” ንግግር ግን ውሸት ሳይሆን አልቀረም
የሰሜን ኮሪያ መንግሥት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን ወታደራዊ ጥቃት “ሉዓላዊነትን የጣሰ የጥቃት ድርጊት” ሲል በጽኑ አውግዟል።
የፒዮንግያንግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሜሪካን ለአለም ሰላም ጠንቅ የሆነች “ቀስቃሽ” ብሏታል።
ይሁን እንጂ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በኢንተርኔት ላይ የተሰራጨውና የኪም ጆንግ ኡን ነው የተባለው “አንድ ሚሳይል እስራኤልን ከካርታ ለማጥፋት ይበቃል” የሚለው ንግግር በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠም።
የሰሜን ኮሪያ መንግሥታዊ የዜና ወኪል (KCNA) እንዲህ ያለ መግለጫ አላወጣም።
እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ሰሜን ኮሪያ ለኢራን ያላትን ድጋፍ ብትገልጽም፣ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ላለመግባት በመጠኑ “የተገደበ” የቃላት አጠቃቀም መምረጧ ተስተውሏል።
ይህም በክልሉ ያለውን ውጥረት ከማባባስ ይልቅ ሁኔታውን በንቃት ለመከታተል የፈለገች ይመስላል።
የሰሜን ኮሪያ መንግሥት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን ወታደራዊ ጥቃት “ሉዓላዊነትን የጣሰ የጥቃት ድርጊት” ሲል በጽኑ አውግዟል።
የፒዮንግያንግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አሜሪካን ለአለም ሰላም ጠንቅ የሆነች “ቀስቃሽ” ብሏታል።
ይሁን እንጂ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በኢንተርኔት ላይ የተሰራጨውና የኪም ጆንግ ኡን ነው የተባለው “አንድ ሚሳይል እስራኤልን ከካርታ ለማጥፋት ይበቃል” የሚለው ንግግር በገለልተኛ ወገን አልተረጋገጠም።
የሰሜን ኮሪያ መንግሥታዊ የዜና ወኪል (KCNA) እንዲህ ያለ መግለጫ አላወጣም።
እንደ እውነቱ ከሆነ፣ ሰሜን ኮሪያ ለኢራን ያላትን ድጋፍ ብትገልጽም፣ በቀጥታ ግጭት ውስጥ ላለመግባት በመጠኑ “የተገደበ” የቃላት አጠቃቀም መምረጧ ተስተውሏል።
ይህም በክልሉ ያለውን ውጥረት ከማባባስ ይልቅ ሁኔታውን በንቃት ለመከታተል የፈለገች ይመስላል።
5 months ago
ከሳህ እስከ ካሜኒ ግድያ : የአሜሪካ እና ኢራን የ80 ዓመታት የጥላቻና የሴራ ታሪክ
ከኮስታስ ቡሩሲስ ፅሁፍ የተወሰደ
የአሜሪካ እና የኢራን ግንኙነት ላለፉት 80 ዓመታት በዓለም ፖለቲካ ውስጥ እጅግ አስገራሚ፣ አስፈሪ እና መርዛማ ከሚባሉ የታሪክ ምዕራፎች አንዱ ነው።
ይህ ግንኙነት በ1940ዎቹ በሳህ (Shah) ቤተ መንግሥት ውስጥ በደስታና በወዳጅነት ተጀምሮ፣ በኒውክሌር ቴክኖሎጂ ስጦታ ታጅቦ፣ በመጨረሻም በ2026 የአሊ ካሜኒን ግድያ ተከትሎ ወደ ተሟላ ጦርነትና ውዝግብ አምርቷል። ይህን ረጅም ጉዞ በዝርዝር እንመልከተው።
እ.ኤ.አ በ1943 ፍራንክሊን ሩዝቬልት፣ ቸርችል እና ስታሊን በቴህራን ተገናኙ። በወቅቱ ኢራን "የድል ድልድይ" ተብላ ትታወቅ ነበር። አጋሮቹ የቀድሞውን ንጉሥ አባረው ወጣቱንና ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚመቸውን መሐመድ ሬዛ ፓህላቪን በዙፋን ላይ አቆዩት። አሜሪካውያን ለወጣቱ ንጉሥ ምዕራባዊ የአኗኗር ዘይቤን በማስተዋወቅና ድጋፍ በመስጠት ኢራንን በመካከለኛው ምስራቅ ታማኝ ወኪላቸው አደረጓት።
በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ የኢራን ጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ሞሳዴቅ የኢራንን የነዳጅ ሀብት ወደ መንግሥት ለማዞር ወሰኑ። ይህ ውሳኔ ብሪታንያንና አሜሪካን ክፉኛ አስቆጣ።
በ1953 የሲአይኤ "ኦፕሬሽን አጃክስ" በተባለ ሴራ ሞሳዴቅን ከሥልጣን አወረደ። ንጉሡ ሳህ ወደ ሥልጣን ተመለሰ።
በ1957 አሜሪካ ለሳህ ልዩ ስጦታ አበረከተች። "Atoms for Peace" በተባለው ፕሮግራም አማካኝነት የመጀመሪያውን የኒውክሌር ሬአክተር ለቴህራን ሰጠች። ዛሬ አሜሪካን እያስጨነቀ ያለው የኢራን ኒውክሌር መሠረቱ በአሜሪካ እጅ የተጣለ መሆኑ የታሪክ ምፀት ነው።
በ1960ዎቹ ሳህ ኢራንን ወደ ምዕራባዊ ሥልጣኔ ለመቀየር "ነጭ አብዮት" አወጀ። ይሁን እንጂ ይህ ለውጥ በሃይማኖታዊ መሪዎችና በድሆች ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም።
በ1970ዎቹ መጀመሪያ አሜሪካ ኢራንን "የባህረ ሰላጤው ፖሊስ" አድርጋ ሾመቻት። ፕሬዝዳንት ኒክሰን "ከኒውክሌር ውጭ የፈለገውን መሣሪያ ሽጡለት" በማለት ለኢራን ቢሊዮኖችን አፈሰሱ።
ሆኖም በኢራን ውስጥ የነበረው ሙስና እና የሳህ የደህንነት መስሪያ ቤት (SAVAK) የሚያደርሰው ግፍ ሕዝቡን አሰለቸው።
በ1979 አያቶላ ሆሜኒ ከስደት ተመልሰው እስላማዊ አብዮቱን መሩ። ሳህ አገር ጥሎ ፈረጠጠ። በዚያው ዓመት ህዳር ወር ላይ ኢራናውያን ተማሪዎች የአሜሪካን ኤምባሲ በመውረር 52 አሜሪካውያንን ለ444 ቀናት ታገቱ። ይህ ክስተት በአሜሪካና በኢራን መካከል የነበረውን ግንኙነት ለዘላቂ ጥላቻ ዳረገው። አሜሪካ "ታላቁ ሰይጣን" ተብላ ተጠራች።
በ1980ዎቹ አጋማሽ አሜሪካ ለኢራን በድብቅ መሣሪያ የሸጠችበት "ኢራን-ኮንትራ" የተባለው ቅሌት ተከሰተ። ይሁን እንጂ በ1988 የአሜሪካ የጦር መርከብ በስህተት የኢራን የመንገደኞች አውሮፕላን (Flight 655) መትቶ በመጣሉ 290 ንጹሐን ሞቱ። ይህ ቁስል እስካሁን አልሻረም።
በ2002 ፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ ኢራንን ከሰሜን ኮሪያና ኢራቅ ጋር በመፈረጅ "የጥፋት ዘንግ" (Axis of Evil) ብለው ጠሯት። ይህ በቴህራን በኩል ትልቅ ክህደት ተደርጎ ተቆጠረ።
በ2015 ፕሬዝዳንት ኦባማ በዲፕሎማሲያዊ ጥረት የታሪክ ለውጥ አመጡ። የኢራን የኒውክሌር ስምምነት (JCPOA) ተፈረመ። ሆኖም በ2017 ዶናልድ ትራምፕ ሥልጣን ሲይዙ ከዚህ ስምምነት ወጥተው በኢራን ላይ "ከፍተኛ ጫና" አሳደሩ።
በ2020 የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱሌይማኒ በአሜሪካ ድሮን መገደል ሁኔታውን ወደ ጦርነት አቀረበው።
እ.ኤ.አ. የ2025 የዶናልድ ትራምፕ ዳግም መመረጥ ለኢራን አገዛዝ የመጨረሻው መጀመሪያ ነበር። በሰኔ 2025 አሜሪካና እስራኤል "Midnight Hammer" በሚባል ዘመቻ የኢራንን የኒውክሌር ማዕከላት ደበደቡ። ኢራንም በኳታር በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በሚሳኤል ምላሽ ሰጠች።
በመጨረሻም በየካቲት 2026 (እ.ኤ.አ) አሜሪካና እስራኤል በወሰዱት የተቀናጀ ወታደራዊ እርምጃ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አሊ ካሜኒ እና የኢራን አብዮታዊ ዘብ አመራሮች ተገደሉ። ይህ ክስተት በቴህራን ጎዳናዎች ላይ ትልቅ ውዝግብና ለውጥን ፈጥሯል።
የአሜሪካና የኢራን ግንኙነት ከወዳጅነት ወደ ደም አፋሳሽ ጠላትነት የተቀየረበት ታሪክ ለዓለም ትልቅ ትምህርት ነው። በ1943 በፈገግታ የተጀመረው ጉዞ በ2026 በሚሳኤል ድምፅ ደምድሟል።
ዛሬ ኢራን አዲስ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች፤ የመካከለኛው ምስራቅ የወደፊት ዕጣ ፈንታም ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳሳቢ ሆኗል።
ከኮስታስ ቡሩሲስ ፅሁፍ የተወሰደ
የአሜሪካ እና የኢራን ግንኙነት ላለፉት 80 ዓመታት በዓለም ፖለቲካ ውስጥ እጅግ አስገራሚ፣ አስፈሪ እና መርዛማ ከሚባሉ የታሪክ ምዕራፎች አንዱ ነው።
ይህ ግንኙነት በ1940ዎቹ በሳህ (Shah) ቤተ መንግሥት ውስጥ በደስታና በወዳጅነት ተጀምሮ፣ በኒውክሌር ቴክኖሎጂ ስጦታ ታጅቦ፣ በመጨረሻም በ2026 የአሊ ካሜኒን ግድያ ተከትሎ ወደ ተሟላ ጦርነትና ውዝግብ አምርቷል። ይህን ረጅም ጉዞ በዝርዝር እንመልከተው።
እ.ኤ.አ በ1943 ፍራንክሊን ሩዝቬልት፣ ቸርችል እና ስታሊን በቴህራን ተገናኙ። በወቅቱ ኢራን "የድል ድልድይ" ተብላ ትታወቅ ነበር። አጋሮቹ የቀድሞውን ንጉሥ አባረው ወጣቱንና ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚመቸውን መሐመድ ሬዛ ፓህላቪን በዙፋን ላይ አቆዩት። አሜሪካውያን ለወጣቱ ንጉሥ ምዕራባዊ የአኗኗር ዘይቤን በማስተዋወቅና ድጋፍ በመስጠት ኢራንን በመካከለኛው ምስራቅ ታማኝ ወኪላቸው አደረጓት።
በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ የኢራን ጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ሞሳዴቅ የኢራንን የነዳጅ ሀብት ወደ መንግሥት ለማዞር ወሰኑ። ይህ ውሳኔ ብሪታንያንና አሜሪካን ክፉኛ አስቆጣ።
በ1953 የሲአይኤ "ኦፕሬሽን አጃክስ" በተባለ ሴራ ሞሳዴቅን ከሥልጣን አወረደ። ንጉሡ ሳህ ወደ ሥልጣን ተመለሰ።
በ1957 አሜሪካ ለሳህ ልዩ ስጦታ አበረከተች። "Atoms for Peace" በተባለው ፕሮግራም አማካኝነት የመጀመሪያውን የኒውክሌር ሬአክተር ለቴህራን ሰጠች። ዛሬ አሜሪካን እያስጨነቀ ያለው የኢራን ኒውክሌር መሠረቱ በአሜሪካ እጅ የተጣለ መሆኑ የታሪክ ምፀት ነው።
በ1960ዎቹ ሳህ ኢራንን ወደ ምዕራባዊ ሥልጣኔ ለመቀየር "ነጭ አብዮት" አወጀ። ይሁን እንጂ ይህ ለውጥ በሃይማኖታዊ መሪዎችና በድሆች ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም።
በ1970ዎቹ መጀመሪያ አሜሪካ ኢራንን "የባህረ ሰላጤው ፖሊስ" አድርጋ ሾመቻት። ፕሬዝዳንት ኒክሰን "ከኒውክሌር ውጭ የፈለገውን መሣሪያ ሽጡለት" በማለት ለኢራን ቢሊዮኖችን አፈሰሱ።
ሆኖም በኢራን ውስጥ የነበረው ሙስና እና የሳህ የደህንነት መስሪያ ቤት (SAVAK) የሚያደርሰው ግፍ ሕዝቡን አሰለቸው።
በ1979 አያቶላ ሆሜኒ ከስደት ተመልሰው እስላማዊ አብዮቱን መሩ። ሳህ አገር ጥሎ ፈረጠጠ። በዚያው ዓመት ህዳር ወር ላይ ኢራናውያን ተማሪዎች የአሜሪካን ኤምባሲ በመውረር 52 አሜሪካውያንን ለ444 ቀናት ታገቱ። ይህ ክስተት በአሜሪካና በኢራን መካከል የነበረውን ግንኙነት ለዘላቂ ጥላቻ ዳረገው። አሜሪካ "ታላቁ ሰይጣን" ተብላ ተጠራች።
በ1980ዎቹ አጋማሽ አሜሪካ ለኢራን በድብቅ መሣሪያ የሸጠችበት "ኢራን-ኮንትራ" የተባለው ቅሌት ተከሰተ። ይሁን እንጂ በ1988 የአሜሪካ የጦር መርከብ በስህተት የኢራን የመንገደኞች አውሮፕላን (Flight 655) መትቶ በመጣሉ 290 ንጹሐን ሞቱ። ይህ ቁስል እስካሁን አልሻረም።
በ2002 ፕሬዝዳንት ጆርጅ ደብልዩ ቡሽ ኢራንን ከሰሜን ኮሪያና ኢራቅ ጋር በመፈረጅ "የጥፋት ዘንግ" (Axis of Evil) ብለው ጠሯት። ይህ በቴህራን በኩል ትልቅ ክህደት ተደርጎ ተቆጠረ።
በ2015 ፕሬዝዳንት ኦባማ በዲፕሎማሲያዊ ጥረት የታሪክ ለውጥ አመጡ። የኢራን የኒውክሌር ስምምነት (JCPOA) ተፈረመ። ሆኖም በ2017 ዶናልድ ትራምፕ ሥልጣን ሲይዙ ከዚህ ስምምነት ወጥተው በኢራን ላይ "ከፍተኛ ጫና" አሳደሩ።
በ2020 የኢራኑ ጄኔራል ቃሲም ሱሌይማኒ በአሜሪካ ድሮን መገደል ሁኔታውን ወደ ጦርነት አቀረበው።
እ.ኤ.አ. የ2025 የዶናልድ ትራምፕ ዳግም መመረጥ ለኢራን አገዛዝ የመጨረሻው መጀመሪያ ነበር። በሰኔ 2025 አሜሪካና እስራኤል "Midnight Hammer" በሚባል ዘመቻ የኢራንን የኒውክሌር ማዕከላት ደበደቡ። ኢራንም በኳታር በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ በሚሳኤል ምላሽ ሰጠች።
በመጨረሻም በየካቲት 2026 (እ.ኤ.አ) አሜሪካና እስራኤል በወሰዱት የተቀናጀ ወታደራዊ እርምጃ የኢራን መንፈሳዊ መሪ አሊ ካሜኒ እና የኢራን አብዮታዊ ዘብ አመራሮች ተገደሉ። ይህ ክስተት በቴህራን ጎዳናዎች ላይ ትልቅ ውዝግብና ለውጥን ፈጥሯል።
የአሜሪካና የኢራን ግንኙነት ከወዳጅነት ወደ ደም አፋሳሽ ጠላትነት የተቀየረበት ታሪክ ለዓለም ትልቅ ትምህርት ነው። በ1943 በፈገግታ የተጀመረው ጉዞ በ2026 በሚሳኤል ድምፅ ደምድሟል።
ዛሬ ኢራን አዲስ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች፤ የመካከለኛው ምስራቅ የወደፊት ዕጣ ፈንታም ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳሳቢ ሆኗል።
5 months ago
‹‹ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች›› የኔታንያሁ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews
Comments