13 hours ago
ኬንያ ወደ ሀገሯ ለሚገቡ የውጭ ዜጎች የጤና ኢንሹራንስ ግዴታ አደረገች
የኬንያ ጤና ሚኒስቴር ከኬንያ ውጭ የሚመጡ ማንኛውም ሀገር ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመግባታቸው በፊት ሕጋዊ የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ ሊኖራቸው እንደሚገባ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አወጣ።
በካቢኔ ሴክሬታሪ አደን ዱአሌ በተፈረመው በዚህ ይፋዊ ሰነድ መሠረት፣ የኬንያ ዜጋ ያልሆኑ እና ለተለያዩ ጉዳዮች ከ12 ወራት ላነሰ ጊዜ ወደ ኬንያ የሚገቡ የትኛውንም ሀገር ጎብኚዎችና መንገደኞች ይህ መመሪያ ይመለከታቸዋል ተብሏል።
መንገደኞች ከገዛ ሀገራቸው የገዙት የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ በኬንያ መንግሥት የወጣውን የመድህን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ፣ በኬንያ የኤሌክትሮኒክ የጉዞ ፈቃድ (eTA) ስርዓት ላይ ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
ከጉዞ በፊት ኢንሹራንስ ያልያዙ መንገደኞች ደግሞ ኬንያ አየር መንገድ ወይም የድንበር በር ሲደርሱ በኬንያ ሕግ ከተፈቀደላቸው የኢንሹራንስ ተቋማት ገዝተው ማቅረብ ይኖርባቸዋልም ተብሏል።
የኬንያ ኢሚግሬሽን አገልግሎት የጉዞ ፈቃድ በሚሰጥበት ወቅት እና በሁሉም የድንበር በሮች ላይ የጤና ኢንሹራንስ ማረጋገጫውን በጥብቅ የሚቆጣጠር ሲሆን፣ ይህንን ማረጋገጫ ሳያቀርቡ ወደ ሀገሪቱ መግባት እንደማይቻል ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
የኬንያ ጤና ሚኒስቴር ከኬንያ ውጭ የሚመጡ ማንኛውም ሀገር ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ከመግባታቸው በፊት ሕጋዊ የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ ሊኖራቸው እንደሚገባ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አወጣ።
በካቢኔ ሴክሬታሪ አደን ዱአሌ በተፈረመው በዚህ ይፋዊ ሰነድ መሠረት፣ የኬንያ ዜጋ ያልሆኑ እና ለተለያዩ ጉዳዮች ከ12 ወራት ላነሰ ጊዜ ወደ ኬንያ የሚገቡ የትኛውንም ሀገር ጎብኚዎችና መንገደኞች ይህ መመሪያ ይመለከታቸዋል ተብሏል።
መንገደኞች ከገዛ ሀገራቸው የገዙት የጉዞ ጤና ኢንሹራንስ በኬንያ መንግሥት የወጣውን የመድህን መስፈርት የሚያሟላ ከሆነ፣ በኬንያ የኤሌክትሮኒክ የጉዞ ፈቃድ (eTA) ስርዓት ላይ ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
ከጉዞ በፊት ኢንሹራንስ ያልያዙ መንገደኞች ደግሞ ኬንያ አየር መንገድ ወይም የድንበር በር ሲደርሱ በኬንያ ሕግ ከተፈቀደላቸው የኢንሹራንስ ተቋማት ገዝተው ማቅረብ ይኖርባቸዋልም ተብሏል።
የኬንያ ኢሚግሬሽን አገልግሎት የጉዞ ፈቃድ በሚሰጥበት ወቅት እና በሁሉም የድንበር በሮች ላይ የጤና ኢንሹራንስ ማረጋገጫውን በጥብቅ የሚቆጣጠር ሲሆን፣ ይህንን ማረጋገጫ ሳያቀርቡ ወደ ሀገሪቱ መግባት እንደማይቻል ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
14 hours ago
የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል፡፡ ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ አምነው ለሚጠሩት ረዳት ነው፡፡ በመዝሙር 33÷7 እደተጻፈው ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል፡፡ እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳንኤል እንደተናገረው ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው፡፡ ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ ይህንን ድንቅ ተአምር መስከረም ዘጠኝ ቀን መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን ትመሰክራለች፡፡ በቀድሞው የሮም ግዛት 'ሩፍምያ' የምትባል ከተማ ነበረች፡፡
ይህች ከተማ በእምነታቸው ጠንካሮች የሆኑ ጥቂት ክርስቲያኖችና በርካታ ኢአማንያን ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት፡፡ በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ፍጹም የእምነት ሰው ነበር፡፡ በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረግ ስለነበር ተበለጥን የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ “ዮናናውያን”ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ፡፡ በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን መከሩና ወሰኑ፡፡ በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ አለ፡፡ በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር፡፡ ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን መንገድ ዘግተው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት ከቀናት በኋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ፡፡
ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ፡፡ በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በስተቀር ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ሲወጣ ወንዙ እየደነፋ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው፡፡ ከደቂቃዎች በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ እንደሚሆን የተረዳው መጋቢ በታላቅ ድንግጤ ውስጥ ወደቀ፡፡ እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ በመላዕክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ምስለ ስዕል ፊት ወድቆ ተማጸነ፡፡ ታላቁ ወንዝ ቤተ ክርስቲያኑን ጠርጎ የሚወወስደው ከሆነም የሚሆነውን ነገር ለመቀበልና ከዚያም ላለመውጣትም ወሰነ፡፡ ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ፡፡ በዚህ ጊዜ የመላዕክት ሁሉ አለቃቸው ለጠራውም ፈጥኖ የሚደርሰው ቅዱስ ሚካኤል በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ፡፡
መጋቢውንም "ጽና አትፍራ፣ እኔ ካንተ ጋር ነኝና" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት፡፡ በዚያች ቅጽበትም ትልቅ ሸለቆ ተፈጠረ፡፡ በአስፈሪ ሁኔታ ሲመጣ የነበረው ወንዝም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ፡፡ የሚገርመው ነገር የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሸለቆው የተፈጠረው ከቤተ ክርስቲያኑ በታች መሆኑ ነው፡፡ ቤተክርስቲያኑ ግን ጸንቶ ቆመ፡፡ መጋቢውም እግዚአብሔርንና ቅዱስ ሚካኤልን አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ፡፡ በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው፣ መልአኩንም አከበሩት፣ አሕዛብ ግን አፈሩ፡፡
ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ያስገዙ ገዳማውያንና ቅዱሳን ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል፡፡ ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ አምነው ለሚጠሩት ረዳት ነው፡፡ በመዝሙር 33÷7 እደተጻፈው ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል፡፡ እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ዳንኤል እንደተናገረው ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው፡፡ ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ ይህንን ድንቅ ተአምር መስከረም ዘጠኝ ቀን መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን ትመሰክራለች፡፡ በቀድሞው የሮም ግዛት 'ሩፍምያ' የምትባል ከተማ ነበረች፡፡
ይህች ከተማ በእምነታቸው ጠንካሮች የሆኑ ጥቂት ክርስቲያኖችና በርካታ ኢአማንያን ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት፡፡ በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ፍጹም የእምነት ሰው ነበር፡፡ በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረግ ስለነበር ተበለጥን የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ “ዮናናውያን”ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ፡፡ በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን መከሩና ወሰኑ፡፡ በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ አለ፡፡ በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር፡፡ ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን መንገድ ዘግተው ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት ከቀናት በኋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ፡፡
ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ፡፡ በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ ቤተ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በስተቀር ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ሲወጣ ወንዙ እየደነፋ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው፡፡ ከደቂቃዎች በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ እንደሚሆን የተረዳው መጋቢ በታላቅ ድንግጤ ውስጥ ወደቀ፡፡ እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ በመላዕክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ምስለ ስዕል ፊት ወድቆ ተማጸነ፡፡ ታላቁ ወንዝ ቤተ ክርስቲያኑን ጠርጎ የሚወወስደው ከሆነም የሚሆነውን ነገር ለመቀበልና ከዚያም ላለመውጣትም ወሰነ፡፡ ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ፡፡ በዚህ ጊዜ የመላዕክት ሁሉ አለቃቸው ለጠራውም ፈጥኖ የሚደርሰው ቅዱስ ሚካኤል በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ፡፡
መጋቢውንም "ጽና አትፍራ፣ እኔ ካንተ ጋር ነኝና" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት፡፡ በዚያች ቅጽበትም ትልቅ ሸለቆ ተፈጠረ፡፡ በአስፈሪ ሁኔታ ሲመጣ የነበረው ወንዝም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ፡፡ የሚገርመው ነገር የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሸለቆው የተፈጠረው ከቤተ ክርስቲያኑ በታች መሆኑ ነው፡፡ ቤተክርስቲያኑ ግን ጸንቶ ቆመ፡፡ መጋቢውም እግዚአብሔርንና ቅዱስ ሚካኤልን አመሰገነ፡፡ ቅዱስ ሚካኤል መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ፡፡ በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው፣ መልአኩንም አከበሩት፣ አሕዛብ ግን አፈሩ፡፡
ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ያስገዙ ገዳማውያንና ቅዱሳን ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
22 hours ago
የኦሮሞ ሕዝብ የትግል ጥያቄዎች በለውጡ ዓመታት ምላሽ አግኝተዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦቢኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ውስጥ የኦሮሞ ሕዝብ የዘመናት የትግል ጥያቄዎች ምን ያህል ምላሽ እንዳገኙ በሦስት ዋና ዋና ነጥቦች አብራርተዋል።
የነፃነት ጥያቄ (አዕምሮአዊ እና አካላዊ ነፃነት)
አዕምሮአዊ ነፃነት፡ የዛሬው ትውልድ በቋንቋው ሲናገር እና ማንነቱን ሲገልጽ የሚያፍርበት እና የሚሸማቀቅበት የትላንቱ ጊዜ ማብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የማይቀለበስ ነፃነት፡ የኦሮሞ ሕዝብ አካላዊም ሆነ ሥነ-ልቦናዊ ነፃነቱን መጎናጸፉን፣ ከዚህ በኋላ ሕዝቡን እንደ ቀድሞው ልግዛው፣ መሬቱን ልቀማው ወይም ልዝረፈው ብሎ ማሰብ ፍጹም "ሞኝነት" መሆኑን እና ሕዝቡ ዳግም ለባርነት የማይመችበት ከፍታ ላይ መድረሱን አስገንዝበዋል።
የዴሞክራሲ እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ፡-
መቶ በመቶ ራስን ማስተዳደር፦ የኦሮሞ ሕዝብ የራሱ ሕግ አውጪ በመሆን፣ የቋንቋ፣ የባህል እና የማንነት መብቱን አረጋግጦ ራሱን በራሱ ማስተዳደር መጀመሩን አብራርተዋል።
ከገዳ ሥርዓት ጋር ያለው ትሥሥር፦ ይህ ራስን የማስተዳደር እና መሪን የመምረጥ ሂደት አባቶች በገዳ ሥርዓት (በአባ ቦኩ፣ አባ ዱላ እና ሲንቄ) ይጠቀሙበት የነበረውን የሥራ ክፍፍል፣ መመካከር እና የሕዝብ ተሳትፎ የሚያንጸባርቅ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን የዴሞክራሲ ሥርዓት በሂደት እየዘመነ እና እያደገ የሚሄድ ቢሆንም፣ መሠረታዊ የሆነው ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ በኦሮሚያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ምላሽ ማግኘቱን አረጋግጠዋል።
የኢኮኖሚ እና የመሬት ጥያቄ
ከሁሉ በላይ የኢኮኖሚ ጥያቄው ወሳኝ መሆኑን አንሥተው፣ በተለይም አራሹ ገበሬ ከመሬቱ ሳይፈናቀል በላቡ ሠርቶ ያገኘውን ፍሬ ራሱ የሚጠቀምበትን እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ የሚረጋገጥበትን ሥርዓት ማስፈን ዋነኛ ትኩረት መሆኑን አመላክተዋል።
በዮናስ በድሉ
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
*******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦቢኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ውስጥ የኦሮሞ ሕዝብ የዘመናት የትግል ጥያቄዎች ምን ያህል ምላሽ እንዳገኙ በሦስት ዋና ዋና ነጥቦች አብራርተዋል።
የነፃነት ጥያቄ (አዕምሮአዊ እና አካላዊ ነፃነት)
አዕምሮአዊ ነፃነት፡ የዛሬው ትውልድ በቋንቋው ሲናገር እና ማንነቱን ሲገልጽ የሚያፍርበት እና የሚሸማቀቅበት የትላንቱ ጊዜ ማብቃቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
የማይቀለበስ ነፃነት፡ የኦሮሞ ሕዝብ አካላዊም ሆነ ሥነ-ልቦናዊ ነፃነቱን መጎናጸፉን፣ ከዚህ በኋላ ሕዝቡን እንደ ቀድሞው ልግዛው፣ መሬቱን ልቀማው ወይም ልዝረፈው ብሎ ማሰብ ፍጹም "ሞኝነት" መሆኑን እና ሕዝቡ ዳግም ለባርነት የማይመችበት ከፍታ ላይ መድረሱን አስገንዝበዋል።
የዴሞክራሲ እና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ፡-
መቶ በመቶ ራስን ማስተዳደር፦ የኦሮሞ ሕዝብ የራሱ ሕግ አውጪ በመሆን፣ የቋንቋ፣ የባህል እና የማንነት መብቱን አረጋግጦ ራሱን በራሱ ማስተዳደር መጀመሩን አብራርተዋል።
ከገዳ ሥርዓት ጋር ያለው ትሥሥር፦ ይህ ራስን የማስተዳደር እና መሪን የመምረጥ ሂደት አባቶች በገዳ ሥርዓት (በአባ ቦኩ፣ አባ ዱላ እና ሲንቄ) ይጠቀሙበት የነበረውን የሥራ ክፍፍል፣ መመካከር እና የሕዝብ ተሳትፎ የሚያንጸባርቅ መሆኑን ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን የዴሞክራሲ ሥርዓት በሂደት እየዘመነ እና እያደገ የሚሄድ ቢሆንም፣ መሠረታዊ የሆነው ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ በኦሮሚያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ምላሽ ማግኘቱን አረጋግጠዋል።
የኢኮኖሚ እና የመሬት ጥያቄ
ከሁሉ በላይ የኢኮኖሚ ጥያቄው ወሳኝ መሆኑን አንሥተው፣ በተለይም አራሹ ገበሬ ከመሬቱ ሳይፈናቀል በላቡ ሠርቶ ያገኘውን ፍሬ ራሱ የሚጠቀምበትን እና የኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱ የሚረጋገጥበትን ሥርዓት ማስፈን ዋነኛ ትኩረት መሆኑን አመላክተዋል።
በዮናስ በድሉ
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #currentaffairs
1 day ago
በሁለቱ የኢሕአፓ ፖለቲከኞች እና በተቃዋሚዎች ጠበቃው አበራ ንጉሥ ላይ 12 የምርመራ ቀናት ተፈቀደ
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት "በሽብር ወንጀል" የተጠረጠሩት ፖለቲከኞቹ አበበ አካሉ እና ይሳቅ ወልዳይ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ ላይ የ12 የምርመራ ቀናት መፍቀዱን ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።
ዛሬ አርብ ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም. ረፋድ ላይ የተሰየመው ችሎት የመርማሪ ፖሊስን ጥያቄ የተቀበለው፣ ፍርድ ቤቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ለተነሳው ጥርጣሬ በማስረጃነት የቀረቡት ቃለ መጠይቆች ላይ "የሽብር መነሻ ሐሳብ በማግኘታቸው" እንደሆነ ጠበቃው ገልጸዋል።
ሁለቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ፖለቲከኞች እና ለተቃዋሚዎች ጥብቅና በመቆም የሚታወቁት አበራ በቁጥጥር ስር የዋሉት ሰኞ ሐምሌ 27 ነበር። በፌደራል ፖሊስ አባላት በተያዙ ሁለተኛው ቀን ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።
መርማሪ ፖሊስ ሦስቱ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ "በመንግሥት የፀጥታ ተቋማት እና በመንግሥትት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የሽብር ጥቃት" ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለፍርድ ቤት ገልጿል።
ድርጊቱን ሊፈጽሙ የነበሩት "ከህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ድብቅ ግንኙነት በማድረግ" እንደሆነ የገለጸው ፖሊስ፤ "ጽምዶ [ተ]ብሎ ከሚጠራው ኃይል ጋር በቀናጀት" ምልመላ እና ስለላ ሲያከናውኑ እንደነበር በመጥቀስም ወንጅሏል።
በዚህ ጉዳይ ላይ "ሥራውን አጠናቅቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የሕግ አካል ለመላክ" እንዲችልም 14 የምርመራ ቀናት እንዲፈቀድለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ፣ በሦስቱ ግለሰቦች ላይ የቀረበውን ውንጀላ ለማስረዳት በቀረቡት በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ የተደረጉ ቃለ መጠይቆች 'የሽብር ይዘት አላቸው ወይስ የላቸውም' የሚለውን ለመወሰን ለዛሬ አርብ ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት በመርማሪ ፖሊስ ቀረቡትን "የሐሰት ፕሮፓጋንዳ" ቪድዮ ሊንኮች መመልከቱን እንደገለጸ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ዳኞች በቀረቡላቸው የቪዲዮ ሊንኮች ላይ "የሽብር ይዘት" የሚያገኙ ከሆነ ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ሊፈቀድ እንደሚችል፤ ካልሆነ ደግሞ በዋስትና ሊወጡ ይችሉ እንደነበር ጠበቃው አስረድተዋል።
እንደ ጠበቃው ገለጻ፣ ቪዲዮዎቹን የተመለከቱን ዳኞች ለፖሊስ ጥርጣሪ "መነሻ የሚሆኑ ይዘቶችን አግኝተናል" ብለዋል።
ዳኞች "በሰማነው ድምፅ ላይ ድርጊቱ የሽብር ሊመስል የሚችል የመነሻ ሀሳብ አግኝተናል። በተወሰነ መልኩ የመነሻ ሀሳብ ስላገኘን ለፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መስጠቱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል" እንዳሉ ጠበቃው አስረድተዋል።
በዚህም መሠረት መርማሪ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት ውስጥ ተጠርጣሪዎቹ "ፍርድ ቤት ከቀረቡበት ቀን ጀምሮ የሚታሰብ የ12 ቀን የምርመራ ጊዜ" መፍቀዳቸውን ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ በቀጣዩ በሚኖረው ቀጠሮ ላይ "ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ" እንዲቀርብ ትዕዛዝ መሰጠቱንም ጠበቃ ሰለሞን ተናግረዋል።
BBC Amharic
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ዳሽቦርድ ይፋ ተደረገ
#ethiopia | የትምባሆ ምርቶችን ጎጂነት ለመግታትና በዘርፉ የሚከናወኑ የሕግ ማስከበር ሥራዎችን በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ለማድረግ ያለመው የትምባሆ ቁጥጥር ዳታ ኢኒሼቲቭ ዳሽቦርድ ይፋ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ፣ የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማኅበር እንዲሁም የመቋሚያ የማኅበረሰብ ልማት ድርጅት በጋራ በመሆን ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ የትምባሆ አጠቃቀምንና የኢንዱስትሪዎችን ተፅዕኖ ለመግታት መረጃን በአንድ ማዕከል ማሰባሰብ ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህ አዲስ የተበገገው ዳሽቦርድ በተለይም መረጃዎችን በሀገራችን የሥራ ቋንቋ በአማርኛ አካቶ ማዘጋጀቱ መረጃው ለፖሊሲ አውጪዎች ብቻ ሳይሆን ለሚዲያዎች፣ ለተመራማሪዎችና ለሰፊው ሕብረተሰብ ያለ ምንም የቋንቋ መሰናክል በቀላሉ እንዲደርስ ያስችላል።
በውስጡም የትምባሆ ተጠቃሚነት ስርጭትን፣ የሕገ-ወጥ ንግድ ሁኔታዎችን እንዲሁም ታክስ በጤና እና በሀገር ገቢ ላይ የሚያመጣውን አወንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳዩ አገራዊ የምርምር ውጤቶችን ያካተተ ነው።
ከዚህም በተጨማሪ ዜጎች ከትምባሆ ሱስ የሚላቀቁበትንና ከምልሰተ-ሱስ የሚጠበቁበትን መንገድ የሚያመቻቹ መረጃዎች በውስጡ ተካተውበታል።
የትምባሆ ኢንዱስትሪዎችን የተቀናጀ እንቅስቃሴ በወቅቱ ለመቆጣጠር መረጃዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ የማዘመን፣ ዳሽቦርዱን እስከ ታችኛው የመዋቅር ደረጃ ድረስ የማድረስና አቅም የመገንባት ሥራዎች በቀጣይ ትኩረት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።
ባለድርሻ አካላትም ይህንን ዝግጁ መረጃ በመጠቀም ሕግ የማስከበር፣ የግንዛቤ ማስጨበጥ እና ተጨማሪ የምርምር ሥራዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።
#tobaccocontrol #publichealthethiopia #efda #tdi #tobaccodatainitiative #healthdevantimalaria
#ethiopia | የትምባሆ ምርቶችን ጎጂነት ለመግታትና በዘርፉ የሚከናወኑ የሕግ ማስከበር ሥራዎችን በመረጃ ላይ የተመሠረቱ ለማድረግ ያለመው የትምባሆ ቁጥጥር ዳታ ኢኒሼቲቭ ዳሽቦርድ ይፋ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ፣ የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማኅበር እንዲሁም የመቋሚያ የማኅበረሰብ ልማት ድርጅት በጋራ በመሆን ባዘጋጁት በዚህ መድረክ ላይ፣ የትምባሆ አጠቃቀምንና የኢንዱስትሪዎችን ተፅዕኖ ለመግታት መረጃን በአንድ ማዕከል ማሰባሰብ ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተመልክቷል።
ይህ አዲስ የተበገገው ዳሽቦርድ በተለይም መረጃዎችን በሀገራችን የሥራ ቋንቋ በአማርኛ አካቶ ማዘጋጀቱ መረጃው ለፖሊሲ አውጪዎች ብቻ ሳይሆን ለሚዲያዎች፣ ለተመራማሪዎችና ለሰፊው ሕብረተሰብ ያለ ምንም የቋንቋ መሰናክል በቀላሉ እንዲደርስ ያስችላል።
በውስጡም የትምባሆ ተጠቃሚነት ስርጭትን፣ የሕገ-ወጥ ንግድ ሁኔታዎችን እንዲሁም ታክስ በጤና እና በሀገር ገቢ ላይ የሚያመጣውን አወንታዊ ተፅዕኖ የሚያሳዩ አገራዊ የምርምር ውጤቶችን ያካተተ ነው።
ከዚህም በተጨማሪ ዜጎች ከትምባሆ ሱስ የሚላቀቁበትንና ከምልሰተ-ሱስ የሚጠበቁበትን መንገድ የሚያመቻቹ መረጃዎች በውስጡ ተካተውበታል።
የትምባሆ ኢንዱስትሪዎችን የተቀናጀ እንቅስቃሴ በወቅቱ ለመቆጣጠር መረጃዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ የማዘመን፣ ዳሽቦርዱን እስከ ታችኛው የመዋቅር ደረጃ ድረስ የማድረስና አቅም የመገንባት ሥራዎች በቀጣይ ትኩረት እንደሚሰጣቸው ተገልጿል።
ባለድርሻ አካላትም ይህንን ዝግጁ መረጃ በመጠቀም ሕግ የማስከበር፣ የግንዛቤ ማስጨበጥ እና ተጨማሪ የምርምር ሥራዎችን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።
#tobaccocontrol #publichealthethiopia #efda #tdi #tobaccodatainitiative #healthdevantimalaria
1 day ago
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ወሰነ።
የተላለፈው መግለጫ ከዩቲዩብ እንዲወርድ እና ይቅርታ እንዲጠየቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ዐቃቤ ሕግ አርቲስቶቹ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ በመስጠታቸው የዋስትና መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።
ዛሬ ነሀሴ 01 2018 ዓ/ም ጠዋት በነበረው ችሎት ተጠርጣሪ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ለዐቃቤ ሕግ አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ለምን መግለጫ እንደሰጡም ለችሎቱ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
አርቲስቶቹ በማብራሪያቸው ድርጊቱን የፈጸሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚደርስባቸው ስም ማጥፋትና መልካም ስም ከማጉደፍ ራሳቸውን ለመከላከል አስበው እንደሆነ አስረድተዋል።
ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለከሰዓት 9:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍርድ ቤቱ፤ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠትና ማብራሪያ ማቅረብ ጥፋት መሆኑን አመልክቷል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚጠፋ ስም መልስ ለመስጠት እንኳን ቢሆን ድርጊቱን ፈጽሟል የሚሉትን አካል በሕግ መጠየቅ ሲገባ መግለጫ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቁሟል።
ሆኖም «በጥቃቅን ጥፋቶች የዋስትና መብትን ማገድ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም» ሲል ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።
በተጨማሪም አርቲስቶቹና ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣ ወይም በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
በዚህም መሠረት መግለጫ የሰጡት አርቲስቶች ሌላ ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ውሳኔ ተሰጥቷል።
በሌላ በኩል «እግረኛው» በተሰኘው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ እንዲተላለፍ ያደረገው አቶ ተክለሃይማኖት አዳነ ቪዲዮውን ከዩቲዩብ (YouTube) ላይ እንዲያወርድና ይቅርታ እንዲጠይቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
የመደበኛው የሕግ ሂደት ቀጠሮ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም የተቀጠረ መሆኑ ታውቋል።
ገዛ ጌታሁን
የተላለፈው መግለጫ ከዩቲዩብ እንዲወርድ እና ይቅርታ እንዲጠየቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
ዐቃቤ ሕግ አርቲስቶቹ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ መግለጫ በመስጠታቸው የዋስትና መብታቸው ተነስቶ በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል።
ዛሬ ነሀሴ 01 2018 ዓ/ም ጠዋት በነበረው ችሎት ተጠርጣሪ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ለዐቃቤ ሕግ አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ለምን መግለጫ እንደሰጡም ለችሎቱ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
አርቲስቶቹ በማብራሪያቸው ድርጊቱን የፈጸሙት በማኅበራዊ ሚዲያ ከሚደርስባቸው ስም ማጥፋትና መልካም ስም ከማጉደፍ ራሳቸውን ለመከላከል አስበው እንደሆነ አስረድተዋል።
ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለከሰዓት 9:00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው ፍርድ ቤቱ፤ በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠትና ማብራሪያ ማቅረብ ጥፋት መሆኑን አመልክቷል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ለሚጠፋ ስም መልስ ለመስጠት እንኳን ቢሆን ድርጊቱን ፈጽሟል የሚሉትን አካል በሕግ መጠየቅ ሲገባ መግለጫ መስጠቱ ተገቢ እንዳልሆነ ጠቁሟል።
ሆኖም «በጥቃቅን ጥፋቶች የዋስትና መብትን ማገድ ተገቢ ሆኖ አላገኘነውም» ሲል ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ያቀረበውን ጥያቄ ውድቅ አድርጎታል።
በተጨማሪም አርቲስቶቹና ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣ ወይም በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን አቤቱታ ፍርድ ቤቱ አልተቀበለውም።
በዚህም መሠረት መግለጫ የሰጡት አርቲስቶች ሌላ ጊዜ ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ በከባድ ማስጠንቀቂያ እንዲታለፉ ውሳኔ ተሰጥቷል።
በሌላ በኩል «እግረኛው» በተሰኘው የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ እንዲተላለፍ ያደረገው አቶ ተክለሃይማኖት አዳነ ቪዲዮውን ከዩቲዩብ (YouTube) ላይ እንዲያወርድና ይቅርታ እንዲጠይቅ ፍርድ ቤቱ አዟል።
የመደበኛው የሕግ ሂደት ቀጠሮ ለጥቅምት 02 ቀን 2019 ዓ.ም የተቀጠረ መሆኑ ታውቋል።
ገዛ ጌታሁን
1 day ago
በአርባምንጭ ከተማ የኮሪደር ልማት የመብራት ምሰሶ ላይ ጉዳት ያደረሰው አሽከርካሪ 1 ሚሊዮን ብር ተቀጣ
በአርባምንጭ ከተማ በኮሪደር ልማት ሥራ የተተከለ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ምሰሶ (ፖል) በመግጨት ውድመት ያደረሰ አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ 1 ሚሊዮን ብር እንዲቀጣና የወደመውን ሀብት በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተወሰነ።
በከተማዋ ሲቀላ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪው ተሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ ባልተፈቀደ ቦታ ላይ በማሽከርከር በከፍተኛ ወጪ የተተከለውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በመግጨት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የአርባምንጭ ከተማ ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ከከተማው ትራፊክ ፖሊስ ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ጥፋተኛውን አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
የከተማው ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰራዊት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት፣ በቸልተኝነት በሚፈጸሙ ጥፋቶች የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት እንዳይባክን እና አስተማሪ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ሲባል የተሰበረውንና የወደመውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ።
ጥፋተኛውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ከነዋሪዎች የተገኘው የጥቆማ ትብብር ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የገለጹት አቶ ሰራዊት፣ ለኅብረተሰቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኃላፊው አክለውም ለከተማዋ እድገትና ለነዋሪዎች ምቾት በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚያበላሹ ወይም ሕግ በሚተላለፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በአርባምንጭ ከተማ በኮሪደር ልማት ሥራ የተተከለ ዘመናዊ የመንገድ ዳር መብራት ምሰሶ (ፖል) በመግጨት ውድመት ያደረሰ አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ውሎ 1 ሚሊዮን ብር እንዲቀጣና የወደመውን ሀብት በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ ተወሰነ።
በከተማዋ ሲቀላ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪው ተሽከርካሪ ለማንቀሳቀስ ባልተፈቀደ ቦታ ላይ በማሽከርከር በከፍተኛ ወጪ የተተከለውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በመግጨት ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የአርባምንጭ ከተማ ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ከከተማው ትራፊክ ፖሊስ ጋር ባደረጉት የተቀናጀ ክትትል ጥፋተኛውን አሽከርካሪ በቁጥጥር ሥር ማዋል ተችሏል።
የከተማው ደንብ አስከባሪ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰራዊት ገዛኸኝ እንዳስታወቁት፣ በቸልተኝነት በሚፈጸሙ ጥፋቶች የመንግሥትና የሕዝብ ሀብት እንዳይባክን እና አስተማሪ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ሲባል የተሰበረውንና የወደመውን ስማርት የመብራት ምሰሶ በራሱ ወጪ ወደ ነበረበት እንዲመልስ።
ጥፋተኛውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ከነዋሪዎች የተገኘው የጥቆማ ትብብር ከፍተኛ ሚና እንደነበረው የገለጹት አቶ ሰራዊት፣ ለኅብረተሰቡ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኃላፊው አክለውም ለከተማዋ እድገትና ለነዋሪዎች ምቾት በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የኮሪደር ልማት ሥራዎችንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን በሚያበላሹ ወይም ሕግ በሚተላለፉ አካላት ላይ የሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ማጭበርበር የተጠረጠሩ አርቲስቶች ላይ ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት ቀጠሮ ተሰጠ።
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ሽፋን በተፈጸመ መጠነ ሰፊ የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 2 ቀን 2019 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
ነገር ግን ተከሳሾቹ "እግረኛው" በተሰኘ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጽ ላይ ቀርበው መግለጫ መስጠታቸውን ተከትሎ፣ ዐቃቤ ሕግ ባለ 5 ገጽ የክስ አቤቱታ አቅርቦ ስለነበር ጉዳዩ ከሰዓት በኋላ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተደርጎ ፣ ለዛሬ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጠዋት 4፡00 ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር።
ጠዋት በነበረው ችሎት ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነን ጨምሮ አርቲስቶቹ በጠበቆቻቸው አማካኝነት ዐቃቤ ሕግ ላቀረበው አቤቱታ በጽሑፍ ምላሽ ሰጥተዋል።
በተጨማሪም በሕግ በተያዘ ጉዳይ ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ለምን መግለጫ እንደሰጡ የቃል ማብራሪያ አቅርበዋል።
ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ፦ "እኛ የኪነ ጥበብ ሰዎች ነን፤ ነገር ግን በመልካም ስማችን ላይ በማኅበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ስለተከፈተብንና ስማችን በመጥፋቱ ሥራችን ስለተበላሸ ነው ምላሽ ለመስጠት የተገደድነው" ብለዋል።
"ለምሳሌ በዚህ ምክንያት አምስት የሥራ ውሎች ተቋርጠውብኛል፤ እኔና ጓደኛዬ የምንሰራው የቴሌቪዥን ፕሮግራምም እንዲቋረጥ ተደርጓል" ሲል አርቲስት ይገረም ደጀኔ ለችሎቱ አብራርቷል።
በነበረው መግለጫ የፍርድ ቤቱን የሕግ ሂደት እንዳያስተጓጉሉ ጥንቃቄ ማድረጋቸውንም ተናግረዋል።
አርቲስቶቹን በማኅበራዊ ሚዲያ አናግሮ መግለጫቸውን ያስተላለፈው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በበኩሉ፦ "እኔ ይህን ፕሮግራም ሳቀርብ የመጀመሪያዬ አይደለም፤ አርቲስቶቹ በሕግ ከመያዛቸው አስቀድሞ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬን በፊንቴክ ዙሪያ ተገልጋዮች ስለሚያነሱት ቅሬታ ጠይቄ ሰርቻለሁ፤ ከዚያ በኋላም አርቲስቶቹን ጥፋተኛ አድርገው በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች የሚዘግቡትን መረጃዎች መነሻ በማድረግ የጠየቅኋቸው ሰዎች አሉ። አሁን እነሱን ያናገርኩት ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፣ የፍትሕ ሂደቱን እንደማይጎዳ የሕግ ባለሙያ አማክሬ ነው" ሲል ለችሎቱ አስረድቷል።
ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የተሰጠው መግለጫ ከፍርድ ቤት ውጭ ውሳኔ መስጠት እንደሆነና በሕግ ሂደት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ መግለጫ መስጠት በሕግ ወንጀል መሆኑ መደነገጉን አብራርቷል።
ቀጥሎም "ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ የአርቲስቶችን ጠበቃ ስለ መዝገቡ ጠይቆ ጠበቃው 'በዚህ ጉዳይ ላይ ማብራሪያ አልሰጥም' ሲሉ 'ፈሪ ነህ ማለት ነው?' በማለት ተናግሯል፤ ይህም የተሳሳተ አካሄድ ነው።
ማንም ቢሆን መግለጫ መስጠት በሕግ ተጠያቂ እንደሚያደርግ አያውቅም ተብሎ አይገመትም፤ “የመጣው ይምጣ” በሚል ስሜት የተሰጠ መግለጫ እንደሆነ ስለምናምን፣ ፍርድ ቤቱ በአቤቱታው ላይ የተጠቀሱትን መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እንዲሰጥልን" ሲል ጠይቋል።
ዐቃቤ ሕግ ከትላንት በፊቱ ችሎት በጽሑፍ ባቀረበው አቤቱታ፦
• የተከሳሾች የዋስትና መብት ተነስቶ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ፣
• የወንጀል ድርጊቱን ሆን ብለው የፈጸሙት በመሆኑ፣ ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖትን ጨምሮ ድርጊቱን ለምን እንደፈጸሙ ተጠይቀው በወንጀል ሕግ አንቀጽ 457 መሠረት እንዲቀጡ፣
• ፍርድ ቤቱ ቀጥታ የማይቀጣቸው ከሆነ፣ ዐቃቤ ሕግ በቁጥጥር ሥር ውለው ክስ እንዲመሠረትባቸው እንዲያደርግ፣
• በተላለፈው ቪዲዮ ላይ ይቅርታ ተጠይቆ ከማኅበራዊ ሚዲያ እንዲወርድ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት፣ የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ግራ ቀኙን ያደመጠው ችሎቱ የቀረቡትን አቤቱታዎች መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ከሰዓት 9፡00 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ገዛ ጌታሁን
1 day ago
የኢራን ፓርላማ አሜሪካ እና እስራኤል በሆርሙዝ ወሽመጥ እንዳያልፉ የሚከለክል ረቂቅ ሕግ አቀረበ
የኢራን ፓርላማ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ በኩል የሚያልፉ መርከቦች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠብቅ ረቂቅ ሕግ ላይ ተወያየ።
ረቂቅ ሕጉ ከአሜሪካ፣ እስራኤል እና ቴህራን ጠብ አጫሪ ናቸው ስትል ከምትፈርጃቸው አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦችን ማገድ እንደሚያካትት ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
ታስኒም የፓርላማ አባል የሆኑትን አባስ ሳሊሚን ጠቅሶ እንደዘገበው የፓርላማው ብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ በወሽመጡ እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ ላይ አገሪቱ የሚኖራትን ቁጥጥር በሚመለከት ተወያይቷል።
በረቂቅ ሕጉ መሠረት አሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን ጠብ አጫሪ ብላ ከፈረጀቻቸው ሌሎች አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸውን መርከቦች በወሽመጡ እንዳያልፉ ይከለከላከሉ።
በረቂቅ ሕጉ በተጨማሪም ከእስራኤል ገር ግንኙነት ያላቸው ወታደራዊ እና የሲቪል የጭነት መርከቦች እንዲሁም በኢራን ላይ በተከፈተው ዘመቻ ድጋፍ ያደረጉ እንዳያልፉ ይከለከላሉ።
በተጨማሪም በኢራን ላይ ጉዳት በማድረስ ረገድ ኃላፊነት አለባቸው ተብለው የሚታመኑ አገራትና ግለሰቦች፣ ካሳ እስኪከፍሉ ድረስ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እና በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በኩል የማለፍ ፈቃድ አይሰጣቸውም።
ረቂቅ ሕጉ ለሚፈጸሙ ጥሰቶች ከባድ ቅጣቶችን፤ ከእነዚህም መካከል በመርከብ ላይ የተጫነው ሸቀጥ ካለው ዋጋ እስከ 20 በመቶ የሚደርስ የገንዘብ ቅጣትን አካትቷል።
በሕጉ መሠረት፣ መንግሥት በፋርስ ባህረ ሰላጤ ውስጥ የአሰሳ ስራን ለመቆጣጠር፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ ለመከታተል እንዲሁም ደህንነትን እና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከጦር ኃይሎች ጋር በጋራ እንዲሰራ ይጠበቅበታል።
ሳሊም ሕጉ በባለሙያዎች እየታየ መሆኑን እና ከመጽደቁ በፊት የማሻሻያ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢራን ፓርላማ ረቂቅ ሕጉ ላይ የተወያየው አገሪቱ ከኦማን ጋር በወሽመጡ አስተዳደር ላይ እየተነጋገረች ባለችበት እና ከሥምምነት ይደረሳል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው።
BBC
የኢራን ፓርላማ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ በኩል የሚያልፉ መርከቦች ላይ ያለውን ቁጥጥር የሚያጠብቅ ረቂቅ ሕግ ላይ ተወያየ።
ረቂቅ ሕጉ ከአሜሪካ፣ እስራኤል እና ቴህራን ጠብ አጫሪ ናቸው ስትል ከምትፈርጃቸው አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸው መርከቦችን ማገድ እንደሚያካትት ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
ታስኒም የፓርላማ አባል የሆኑትን አባስ ሳሊሚን ጠቅሶ እንደዘገበው የፓርላማው ብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ በወሽመጡ እና በፐርዢያ ባሕረ ሰላጤ ላይ አገሪቱ የሚኖራትን ቁጥጥር በሚመለከት ተወያይቷል።
በረቂቅ ሕጉ መሠረት አሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን ጠብ አጫሪ ብላ ከፈረጀቻቸው ሌሎች አገራት ጋር ግንኙነት ያላቸውን መርከቦች በወሽመጡ እንዳያልፉ ይከለከላከሉ።
በረቂቅ ሕጉ በተጨማሪም ከእስራኤል ገር ግንኙነት ያላቸው ወታደራዊ እና የሲቪል የጭነት መርከቦች እንዲሁም በኢራን ላይ በተከፈተው ዘመቻ ድጋፍ ያደረጉ እንዳያልፉ ይከለከላሉ።
በተጨማሪም በኢራን ላይ ጉዳት በማድረስ ረገድ ኃላፊነት አለባቸው ተብለው የሚታመኑ አገራትና ግለሰቦች፣ ካሳ እስኪከፍሉ ድረስ በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ እና በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በኩል የማለፍ ፈቃድ አይሰጣቸውም።
ረቂቅ ሕጉ ለሚፈጸሙ ጥሰቶች ከባድ ቅጣቶችን፤ ከእነዚህም መካከል በመርከብ ላይ የተጫነው ሸቀጥ ካለው ዋጋ እስከ 20 በመቶ የሚደርስ የገንዘብ ቅጣትን አካትቷል።
በሕጉ መሠረት፣ መንግሥት በፋርስ ባህረ ሰላጤ ውስጥ የአሰሳ ስራን ለመቆጣጠር፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ ለመከታተል እንዲሁም ደህንነትን እና የአካባቢ ጥበቃን ለማረጋገጥ ከጦር ኃይሎች ጋር በጋራ እንዲሰራ ይጠበቅበታል።
ሳሊም ሕጉ በባለሙያዎች እየታየ መሆኑን እና ከመጽደቁ በፊት የማሻሻያ ሃሳባቸውን እንዲያቀርቡ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢራን ፓርላማ ረቂቅ ሕጉ ላይ የተወያየው አገሪቱ ከኦማን ጋር በወሽመጡ አስተዳደር ላይ እየተነጋገረች ባለችበት እና ከሥምምነት ይደረሳል ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ነው።
BBC
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የኤርትራ ወታደራዊ አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው መግባታቸውን አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ
የኤርትራ መንግሥት ከፍተኛ የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ዛላምበሳ ከተማ በግልጽ መግባታቸው እና የኤርትራን ሰንደቅ ዓላማ መስቀላቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የክልል አንድነት በግልጽ የጣሰ ድርጊት መሆኑን በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ።
አምባሳደር ባጫ ደበሌ ባሰፈሩት ጽሑፍ እንደገለጹት፣ ይህ ክስተት በተናጥል የተከሰተ ሳይሆን በኤርትራ አገዛዝ እና "ጽምዶ" በተባለው የሕወሓት ቡድን መካከል ሲካሄድ የቆየው ስውርና ግልጽ ቅንጅት ውጤት ነው።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የኤርትራ ጦር ታንኮችንና ከባድ መሣሪያዎችን ወደ ትግራይ ክልል በማስገባት በኢፌዴሪ መንግሥትና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ ያቀደውን ግልጽና ኃይል የተቀላቀለበት እንቅስቃሴ ማፋጠኑን ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጣናው ሰላም ሲል ከፍተኛ ስልታዊ ታጋሽነት ማሳየቱን ያብራሩት አምባሳደር ባጫ፣ የኤርትራ መንግሥት ግን የቀረቡለትን የዲፕሎማሲያዊ ውይይት ጥሪዎች በሙሉ ውድቅ ማድረጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም የኤርትራ አገዛዝ የትግራይ ወጣቶችን በግዴታ በመልመልና ለሱዳን ጦርነት በቅጥረኝነት በመሸጥ ለገዛ ፖለቲካዊ ፍላጎቱ መጠቀሚያ እያደረጋቸው እንደሚገኝ አጋልጠዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኤርትራ መንግሥት ላይ የጣለው ማዕቀብ አሁናዊ ለውጥ ያላመጣ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ሲባል በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ራስን የመከላከል ሕጋዊ መብቱን ተጠቅሞ እርምጃ ለመውሰድ ሊገደድ እንደሚችል አምባሳደር ባጫ ደበሌ አስጠንቅቀዋል።
የኤርትራ መንግሥት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚያንቀሳቅሰውን ኃይል በአስቸኳይ ካላወጣና ከጣልቃ ገብነት ካልተቆጠበ፣ የሚፈጠረው ቀጣናዊ አለመረጋጋት በራሷ በኤርትራ ሕልውና፣ በቀይ ባሕር አካባቢና በሙሉ የአፍሪካ ቀንድ ላይ የከፋ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መዘዝ እንደሚያስከትል ማሳሰባቸውን ከሆርን ሪቪው ያገኘነው የአምባሳደሩ መልዕክት ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የኤርትራ መንግሥት ከፍተኛ የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ዛላምበሳ ከተማ በግልጽ መግባታቸው እና የኤርትራን ሰንደቅ ዓላማ መስቀላቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የክልል አንድነት በግልጽ የጣሰ ድርጊት መሆኑን በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ።
አምባሳደር ባጫ ደበሌ ባሰፈሩት ጽሑፍ እንደገለጹት፣ ይህ ክስተት በተናጥል የተከሰተ ሳይሆን በኤርትራ አገዛዝ እና "ጽምዶ" በተባለው የሕወሓት ቡድን መካከል ሲካሄድ የቆየው ስውርና ግልጽ ቅንጅት ውጤት ነው።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የኤርትራ ጦር ታንኮችንና ከባድ መሣሪያዎችን ወደ ትግራይ ክልል በማስገባት በኢፌዴሪ መንግሥትና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ ያቀደውን ግልጽና ኃይል የተቀላቀለበት እንቅስቃሴ ማፋጠኑን ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጣናው ሰላም ሲል ከፍተኛ ስልታዊ ታጋሽነት ማሳየቱን ያብራሩት አምባሳደር ባጫ፣ የኤርትራ መንግሥት ግን የቀረቡለትን የዲፕሎማሲያዊ ውይይት ጥሪዎች በሙሉ ውድቅ ማድረጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም የኤርትራ አገዛዝ የትግራይ ወጣቶችን በግዴታ በመልመልና ለሱዳን ጦርነት በቅጥረኝነት በመሸጥ ለገዛ ፖለቲካዊ ፍላጎቱ መጠቀሚያ እያደረጋቸው እንደሚገኝ አጋልጠዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኤርትራ መንግሥት ላይ የጣለው ማዕቀብ አሁናዊ ለውጥ ያላመጣ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ሲባል በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ራስን የመከላከል ሕጋዊ መብቱን ተጠቅሞ እርምጃ ለመውሰድ ሊገደድ እንደሚችል አምባሳደር ባጫ ደበሌ አስጠንቅቀዋል።
የኤርትራ መንግሥት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚያንቀሳቅሰውን ኃይል በአስቸኳይ ካላወጣና ከጣልቃ ገብነት ካልተቆጠበ፣ የሚፈጠረው ቀጣናዊ አለመረጋጋት በራሷ በኤርትራ ሕልውና፣ በቀይ ባሕር አካባቢና በሙሉ የአፍሪካ ቀንድ ላይ የከፋ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መዘዝ እንደሚያስከትል ማሳሰባቸውን ከሆርን ሪቪው ያገኘነው የአምባሳደሩ መልዕክት ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
መጥፎውን አዙሪት እንስበር፡ በሌብነት ላይ የሚደረግ የጋራ ትግል
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ሀገር የምታድገው፣ የምትበለፅገው እና የዜጎቿን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የምትችለው በንፁህ እጆች እና በቅን ልቦች ስትመራ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና እና የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ እንደ ትልቅ ካንሰር እና ማነቆ የተጋረጠው አሳሳቢ ፈተና ሌብነት እና የሙስና ተግባር ነው። ይህ እኩይ ድርጊት በግለሰቦች፣ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች እና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ እንደ ምስጥ በመሰግሰግ የሀገርን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመመዝበር ላይ ይገኛል።
ሙስና እና ሌብነት የሀገርን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ከማድማት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ እና የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲስፋፋ ያደርጋል። በመሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት ፈጥሮ የዋጋ ንረት እንዲባባስ በማድረግ ኅብረተሰቡን ለከፋ ችግር እያጋለጠው ይገኛል። ይህን የጥፋት ተግባር ከሥረ መሠረቱ ነቅሎ ማውጣት አሁን ላይ የሀገር ህልውና፣ ሰላም እና ደህንነት ጉዳይ ሆኗል።
ይህንኑ አሳሳቢ ሀገራዊ ፈተና አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የችግሩን ሥር-ሰደድነት ሲያብራሩ፤ "የተንዛዛ አሰራር ጉቦ ሰጭ ይፈጥራል። ጉቦ ሰጭ ጉቦ ተቀባይ ይፈጥራል። ጉቦ ተቀባይ የተንዛዛ አሰራር ይፈጥራል። ይህ መጥፎ አዙሪት ነው፤ በቀላሉ አንወጣውም። ጉቦኞች እና ሌቦች ባሉበት ሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት ማምጣት ቀርቶ አብሮ መኖርም አስቸጋሪ ይሆናል፤ ካልተረባረብን ያጠፋናል" በማለት አስገንዝበዋል።
ይህን በሽታ ለማከም መንግሥት አሁን ላይ በማያዳግም ሁኔታ ሰፊ የማጽዳት ዘመቻ እና የሕግ ማስከበር እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ በነበሩ አካላት፣ እንዲሁም በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር መዋቅር ውስጥ በተሰገሰጉ ሌቦች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው።
በተለይም በነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ፣ በማዕድን ዘርፍ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ በፋይናንስ ተቋማት እና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም ከአፈር ማዳበሪያ ግዢ እና ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ላይ ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የሕዝብን ሀብት በመመዝበር በተገኙ አመራሮች፣ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና የውጭ ዜጎች ጭምር ላይ የማያዳግም የሕግ ተጠያቂነት እየሰፈነ መሆኑ፤ ሕገ-ወጥ የንግድ ድርጅቶች እና መጋዘኖች እየታሸጉ፣ የተጭበረበሩ የባንክ ሒሳቦች እየታገዱ መሆኑ እንዲሁም አሻጥሩን ከመሰረቱ ለማጋለጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ይበል የሚያሰኝ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ተግባር ነው።
ይሁን እንጂ ሌብነትን የማጥፋቱ እና ግልጽነት ያለው ዘመናዊ አሠራርን የመዘርጋቱ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም። መንግሥት የጀመረው ይህ ጠንካራ የሕግ ማስከበር እርምጃ ግቡን እንዲመታ እና ሀገርን ከሕገ-ወጥነት ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ እና የማይተካ ሚና አለው።
ስለሆነም እያንዳንዱ ዜጋ ሕጋዊ መብቱን ለማስከበርም ሆነ አገልግሎት ለማግኘት ጉቦ ከመስጠት መቆጠብ፣ ሌቦችን እና አሻጥር ፈጻሚዎችን ያለ አንዳች ይሉኝታ እና ፍርሃት ማጋለጥ እንዲሁም ከሕገ-ወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በጽናት ሊቆም ይገባል።
በተጨማሪም በጅምላ ከመወነጃጀል ወጥተን፣ ሌባውን ለይተን ሌባ በማለት፣ በተቃራኒው በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግለውን ሠራተኛ ደግሞ በማክበርና በማበረታታት ሀገራዊ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል።
ካልተረባረብን አብሮ መኖርን ጭምር አደጋ ላይ የሚጥለውን ይህን የሙስና እና የሌብነት ደዌ፣ በጋራ ትግላችን፣ በቁርጠኝነታችን እና በማይናወጥ ጽናታችን ማሸነፍ ግድ ይለናል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ሀገር የምታድገው፣ የምትበለፅገው እና የዜጎቿን ተጠቃሚነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የምትችለው በንፁህ እጆች እና በቅን ልቦች ስትመራ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጀመረችው የብልጽግና እና የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ እንደ ትልቅ ካንሰር እና ማነቆ የተጋረጠው አሳሳቢ ፈተና ሌብነት እና የሙስና ተግባር ነው። ይህ እኩይ ድርጊት በግለሰቦች፣ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች እና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ እንደ ምስጥ በመሰግሰግ የሀገርን ሀብት በከፍተኛ ደረጃ በመመዝበር ላይ ይገኛል።
ሙስና እና ሌብነት የሀገርን አጠቃላይ ኢኮኖሚ ከማድማት ባለፈ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንዲባባስ እና የኮንትሮባንድ ንግድ እንዲስፋፋ ያደርጋል። በመሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት ፈጥሮ የዋጋ ንረት እንዲባባስ በማድረግ ኅብረተሰቡን ለከፋ ችግር እያጋለጠው ይገኛል። ይህን የጥፋት ተግባር ከሥረ መሠረቱ ነቅሎ ማውጣት አሁን ላይ የሀገር ህልውና፣ ሰላም እና ደህንነት ጉዳይ ሆኗል።
ይህንኑ አሳሳቢ ሀገራዊ ፈተና አስመልክቶ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የችግሩን ሥር-ሰደድነት ሲያብራሩ፤ "የተንዛዛ አሰራር ጉቦ ሰጭ ይፈጥራል። ጉቦ ሰጭ ጉቦ ተቀባይ ይፈጥራል። ጉቦ ተቀባይ የተንዛዛ አሰራር ይፈጥራል። ይህ መጥፎ አዙሪት ነው፤ በቀላሉ አንወጣውም። ጉቦኞች እና ሌቦች ባሉበት ሀገር ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት ማምጣት ቀርቶ አብሮ መኖርም አስቸጋሪ ይሆናል፤ ካልተረባረብን ያጠፋናል" በማለት አስገንዝበዋል።
ይህን በሽታ ለማከም መንግሥት አሁን ላይ በማያዳግም ሁኔታ ሰፊ የማጽዳት ዘመቻ እና የሕግ ማስከበር እርምጃ መውሰድ ጀምሯል። ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዓቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ በነበሩ አካላት፣ እንዲሁም በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር መዋቅር ውስጥ በተሰገሰጉ ሌቦች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ ነው።
በተለይም በነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ፣ በማዕድን ዘርፍ የኮንትሮባንድ ንግድ፣ በፋይናንስ ተቋማት እና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር እንዲሁም ከአፈር ማዳበሪያ ግዢ እና ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዙ ወንጀሎች ላይ ጠንካራ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የሕዝብን ሀብት በመመዝበር በተገኙ አመራሮች፣ ነጋዴዎች፣ ደላሎች እና የውጭ ዜጎች ጭምር ላይ የማያዳግም የሕግ ተጠያቂነት እየሰፈነ መሆኑ፤ ሕገ-ወጥ የንግድ ድርጅቶች እና መጋዘኖች እየታሸጉ፣ የተጭበረበሩ የባንክ ሒሳቦች እየታገዱ መሆኑ እንዲሁም አሻጥሩን ከመሰረቱ ለማጋለጥ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ ይበል የሚያሰኝ እና ተጠናክሮ ሊቀጥል የሚገባው ተግባር ነው።
ይሁን እንጂ ሌብነትን የማጥፋቱ እና ግልጽነት ያለው ዘመናዊ አሠራርን የመዘርጋቱ ኃላፊነት ለመንግሥት ብቻ የሚተው አይደለም። መንግሥት የጀመረው ይህ ጠንካራ የሕግ ማስከበር እርምጃ ግቡን እንዲመታ እና ሀገርን ከሕገ-ወጥነት ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ እና የማይተካ ሚና አለው።
ስለሆነም እያንዳንዱ ዜጋ ሕጋዊ መብቱን ለማስከበርም ሆነ አገልግሎት ለማግኘት ጉቦ ከመስጠት መቆጠብ፣ ሌቦችን እና አሻጥር ፈጻሚዎችን ያለ አንዳች ይሉኝታ እና ፍርሃት ማጋለጥ እንዲሁም ከሕገ-ወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በጽናት ሊቆም ይገባል።
በተጨማሪም በጅምላ ከመወነጃጀል ወጥተን፣ ሌባውን ለይተን ሌባ በማለት፣ በተቃራኒው በቅንነትና በታማኝነት የሚያገለግለውን ሠራተኛ ደግሞ በማክበርና በማበረታታት ሀገራዊ ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል።
ካልተረባረብን አብሮ መኖርን ጭምር አደጋ ላይ የሚጥለውን ይህን የሙስና እና የሌብነት ደዌ፣ በጋራ ትግላችን፣ በቁርጠኝነታችን እና በማይናወጥ ጽናታችን ማሸነፍ ግድ ይለናል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
2 days ago
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
2 days ago
ጤና ልማትና ፀረ‐ወባ ማህበር በአማርኛ የተዘጋጀ የመጀመሪያውን የትምባሆ ቁጥጥር ዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ አደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ በትምባሆ ቁጥጥር ዙሪያ ያሉ የተበታተኑ መረጃዎችን በአንድ ማዕከል ለማደራጀትና ተደራሽነታቸውን ለማስፋት ያለመው «የትምባሆ ቁጥጥርዳታ ኢኒሺዬቲቭ» (TCDI Ethiopia) ዳሽቦርድ፣ የአማርኛ ገጾቹን በይዘት በማበልፀግ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመረቀ።
ይህ አገራዊ የዲጂታል ዳሽቦርድ ይፋ የተደረገው የጤና፣ ልማት እና ፀረ-ወባ ማህበር (HDAMA) ከኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ጋር በመተባበር ባዘጋጁት ልዩ የመክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ ነው፡፡
የዳሽቦርዱ በይፋ መከፈት በኢትዮጵያ የትምባሆ ቁጥጥር ፖሊሲዎችን፣ ስትራቴጂዎችን እና ሕጋዊ ውሳኔዎችን ሙሉ በሙሉ በምርምርና በፅኑ መረጃ (Data-driven decision making) ላይ የተመሰረቱ ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተገልጿል።
ቀደም ሲል በተለያዩ ተቋማት እና ተመራማሪዎች ዘንድ ተበታትነው ይገኙ የነበሩ መረጃዎች በአንድ ቋት መደራጀታቸው፣ ፖሊሲ አውጪዎችና የሕብረተሰብ ጤና ባለሙያዎች ትክክለኛ አገራዊ ስታቲስቲክሶችን በመጠቀም ፈጣንና ውጤታማ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸዉ ተገልጿል።
የቋንቋ ተደራሽነትና የባለድርሻ አካላት ምክክር የዳሽቦርዱ ገጾች በአማርኛ ቋንቋ ተበልፅገው መቅረባቸው የመረጃ ተደራሽነትን ከመጨመሩ ባለፈ፣ ለመገናኛ ብዙኃን፣ ለተመራማሪዎችና ለመላው ህብረተሰብ የግንዛቤ ማሳደጊያ ቁልፍ መሳሪያ ሆኖ እንደሚያገለግል ታውቋል።
በማስጀመርያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የየዘርፉ ባለድርሻ አካላት የዳሽቦርዱን መመረቅ ተከትሎ በስፋት ዉይይት የተካሄደባቸዉ ሲሆን በውይይቱም ዳሽቦርዱ የሚያቀርባቸውን ዳታዎች ለሕግና ፖሊሲ ማሻሻያ አግባብነት ባለው መልኩ ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ አስተያየቶችን ተለዋውጠዋል።
ይህንን ጠቃሚ ዳሽቦርድ ወደ አማርኛ በመተርጎም፣ በማበልፀግ እና ለዛሬው ማስተዋወቂያ መድረክ የቴክኒክና የመረጃ ማዕከል ድጋፍ ላደረጉት የኢትዮጵያ የምግብ እና መድኃኒት ባለስልጣን፣ HDAMA፣ Development Gateway (DG) A Center for the Study of the Economies of Africa (CSEA) እንዲሁም ለሌሎች አጋር አካላት ምስጋና ቀርቧል።
2 days ago
በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
3 days ago
በትግራይ በዘውዱ ሀፍቱ ግድያ እድሜ ልክ ተፈርዶባቸው የነበሩ ግለሰቦች ከእስር መፈታታቸውን 'ይኾኖ' ማህበር አስታወቀ
በትግራይ ክልል ወጣት ዘውዱ ሀፍቱን በመግደል ወንጀል በእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ከእስር መፈታታቸውን በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅት 'ይኾኖ' (Yikhono) አስታወቀ።
እንደ ማህበሩ ገለፃ፣ ሁለቱ ግለሰቦች በፈጸሙት ዘግናኝ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የጽኑ እስራት ውሳኔ ከተላለፈባቸው ገና አንድ ወር ያህል እንኳ ሳይሞላው ነው ከእስር ነፃ የወጡት።
ዕድሜዋ 32 የነበረችው ዘውዱ ሀፍቱ፣ ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በታቀደ ጥቃት በህዝብ ፊት በደረሰባት ከፍተኛ ድብደባ እና በመኪና በመጨፈለቋ ህይወቷ ማለፉ ይታወሳል።
ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ፦
በዳኞች ላይ ይደርስ የነበረ ዛቻ እና በችሎት ውስጥ የተፈጠሩ ረብሻዎች ሂደቱን ሲያስተጓጉሉት መቆየታቸው ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ጥፋተኝነታቸውን በማረጋገጥ ያለ ምንም ይቅርታ (ይግባኝ) የዕድሜ ልክ እስራት ውሳኔ አሳልፎ ነበር።
ከእስር ተፈተዋል የተባሉት ተከሳሾች ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ሲሆኑ፣ ያሬድ በወቅቱ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት የ22ኛ ሰራዊት አዛዥ ሆነው የሚያገለግሉት የኮሚሽነር ገብረሥላሴ በላይ ልጅ እንደሆነ ተገልጿል።
የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ቤተሰቦች እንደሚያስረዱት፣ በምርመራው እና በፍትህ ሂደቱ ወቅት የባለስልጣናት ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት እንደነበር ጠቁመዋል።
የግለሰቦቹ ከእስር መፈታት በክልሉ የፍትህ ስርዓት እና በሕግ የበላይነት ላይ ትልቅ ጥያቄ ማስነሳቱን የጠቆመው 'ይቅኖ' ማህበር፣ ውሳኔው የሴቶችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ #justiceforzewdu በሚሉ ሃሽታጎች ለወጣት ዘውዱ ሀፍቱ ፍትህ እንዲረጋገጥ፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጣልቃ በሚገቡ ባለስልጣናት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር ጥሪዎች በመቅረብ ላይ ይገኛሉ።
Via ጉርሻ page
በትግራይ ክልል ወጣት ዘውዱ ሀፍቱን በመግደል ወንጀል በእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩት ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ከእስር መፈታታቸውን በክልሉ የሚንቀሳቀሰው የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅት 'ይኾኖ' (Yikhono) አስታወቀ።
እንደ ማህበሩ ገለፃ፣ ሁለቱ ግለሰቦች በፈጸሙት ዘግናኝ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተው የጽኑ እስራት ውሳኔ ከተላለፈባቸው ገና አንድ ወር ያህል እንኳ ሳይሞላው ነው ከእስር ነፃ የወጡት።
ዕድሜዋ 32 የነበረችው ዘውዱ ሀፍቱ፣ ነሐሴ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በታቀደ ጥቃት በህዝብ ፊት በደረሰባት ከፍተኛ ድብደባ እና በመኪና በመጨፈለቋ ህይወቷ ማለፉ ይታወሳል።
ጉዳዩ በፍርድ ቤት ሲታይ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ውስጥ፦
በዳኞች ላይ ይደርስ የነበረ ዛቻ እና በችሎት ውስጥ የተፈጠሩ ረብሻዎች ሂደቱን ሲያስተጓጉሉት መቆየታቸው ተገልጿል።
ፍርድ ቤቱ ጥፋተኝነታቸውን በማረጋገጥ ያለ ምንም ይቅርታ (ይግባኝ) የዕድሜ ልክ እስራት ውሳኔ አሳልፎ ነበር።
ከእስር ተፈተዋል የተባሉት ተከሳሾች ያሬድ ገብረሥላሴ እና አንገሶም ኃይለማርያም ሲሆኑ፣ ያሬድ በወቅቱ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት የ22ኛ ሰራዊት አዛዥ ሆነው የሚያገለግሉት የኮሚሽነር ገብረሥላሴ በላይ ልጅ እንደሆነ ተገልጿል።
የሴቶች መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ቤተሰቦች እንደሚያስረዱት፣ በምርመራው እና በፍትህ ሂደቱ ወቅት የባለስልጣናት ተፅዕኖ እና ጣልቃ ገብነት እንደነበር ጠቁመዋል።
የግለሰቦቹ ከእስር መፈታት በክልሉ የፍትህ ስርዓት እና በሕግ የበላይነት ላይ ትልቅ ጥያቄ ማስነሳቱን የጠቆመው 'ይቅኖ' ማህበር፣ ውሳኔው የሴቶችን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ገልጿል።
በአሁኑ ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ #justiceforzewdu በሚሉ ሃሽታጎች ለወጣት ዘውዱ ሀፍቱ ፍትህ እንዲረጋገጥ፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጣልቃ በሚገቡ ባለስልጣናት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ እና የህግ የበላይነት እንዲከበር ጥሪዎች በመቅረብ ላይ ይገኛሉ።
Via ጉርሻ page
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት የሰረቀው የሆስፒታሉ ጥበቃ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
መዝሙረ ሄላም ላይ የተደረገ አጭር ኂሳዊ ንባብ
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
ከቢኒያም አቡራ
#ethiopia | አዳም ረታ ታሪክን ከነገሥታት፣ ከመሪዎች፣ ማኅበረሰቡ ባበጀው ድልድል ውስጥ ‹ላዕላይ› ከሚባሉት ደረጃዎች አንጻር አያስመለክተንም። ታሪካዊ ከሚባሉ አጋጣሚዎች ውስጥ የተዘነጉትን ጥቃቅን የታሪክ ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ይመርጣል። ይወስዳል መንገድ ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ፍንዳታውን ከሚሞት ዘመድ፣ ከሚደነግጥ ለማኝ፣ ከሚሰነጠቅ የወፍ እንቁላል፣ ከሚፈስ የእናት ወተት ጋር Micro-Macro Connection በመፍጠር የትልቁ ቀዳዳ መፈጠርን ከሚጢጢዬ ሽንቁሮች ጋር ያስተሳስርልናል። እንዲህ ያሉ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕሪያትን ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጻሕፍቱ ውስጥ በተለያየ መጠን እናገኛለን።
Adam Reta አዳም ረታ "መዝሙረ ሄላም" በተሰኘው በዐዲሱ መጽሐፉ ላይም በኢትዮጵያ ታሪካዊ-ፖለቲካዊ አጋጣሚ ውስጥ እንደ ዐውራ የሚታዩትን የእድገት በኅብረት ዘመቻን እንደነ-አሮን፣ እንደነቃል … ባሉ ገጸባሕርያት በኩል፣ የሰባ ሰባቱን ድርቅ በሄላም ጡት በኩል፣ “ጥላሁን ለምን ለምን ሞተ” እየተባለ ኢዮቤልዩ ቤተመንግሥት ጋር የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ በሡልጣን በኩል፣ የከተማ መሬት ዐዋጅን በተለያዩ ግለሰቦች በኩል … እናያለን። በዚህም የታሪክን ትልቅ ካርታ ለመረዳት የተረሱና የጠለሉ ታሪኮችን ይመረምራል። ስለዚህ ነቁጣዊ ማኅበራዊ ክስተቶችን ወደ ታሪክ ምኩራብ በማምጣት ከትልቁ የታሪክ ምሥል ጎን ያስተያያል። ይህ ደግሞ የኒው ሂስቶሪሲዝም ኹነኛ ማጠንጠኛ ነው።
ልክ “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ባለው “የመንግሥቱ ጊዜ” በሚለው ድርሰት ውስጥ፣ ትልቁን “የታኅሣሥ ግርግር”ን እንደ መቼት አምጥቶ የተጻፈውና የተተኮረው ግን ኹነተ-ደቂቅ (micro-events) ላይ ነው። ስለግርማሜ ንዋይ፣ ስለኮሌኔል ወርቅነህ ገበየሁ፣ ሰለጄነራል ሙልጌታ ቡሊ አይደለም የሚያትተው። ስለአንድ ብላቴና ከእንቅልፍ መነሳት፣ ስለገበጣ ጨዋታ፣ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሕፃናትን አሰብስቦ ‹ኪራላይሶን› የሚያስብል ካሕን፣ ስለመንደር ውስጥ ሐሜቶች፣ ስለግለሰቦች ፍርሃት፣ በአጋጣሚ ስላየው አስደናቂ አሞራ … ያወጋል። የታሪክ አጋጣሚ አምጥቶ በታሪክ ውስጥ ግለሰቦች ላይ ስለሚረብበው የታሪክ መንፈስ ያትታል። ልክ እንደዚሁ መዝሙረ ሄላም ላይም ጽሑፉ ታሪክን አያብራራም፤ ነገር ግን ታሪክ እንዴት በሰው ልብ ውስጥ እንደሚኖር ያሳያል። በዚህ ኹነተ-ደቂቅ (micro-event) ምክንያት በዘመኑ ላይ ያገነገነውን ባሕላዊ እምነትን፣ የሥልጣን መዋቅርን፣ የወል ግንዛቤን አጨንቁረን እንድንመለከት ያስችለናል።
ከመንግሥት ሼልፍ ላይ ሳይኾን ከግለሰብ ጀርባ ላይ የተወሰደው የአዳም የአጻጻፍ መንገድ ከኒው ሂስቶሪስዝም ጽንሰ-ሐሳቦች ጋር በአንድ መም ላይ የሚሄዱ ናቸው። መዝሙረ ሄላም የተሰኘው ዐዲሱ የአዳም ረታ መጽሐፍ የኒው ሂስቶሪሲዝም ባሕርያትን ይጋራል። አንዳንድ ነገሮችን በዓይን መመልከት ባይቻልም በግብሩ (ቁስ ላይ በሚያደርገው ግፊት) ግን ይታወቃል። በመዝሙረ ሄላም መጽሐፍ ውስጥም አንዳንድ ነገሮችን በቀጥታ ማየት ባንችልም ቅሉ እነርሱን የሚያሳይልንን ነገሮች ግን እንቃኛለን። ዘማች ወጣት ተማሪዎችን እናያለን፤ መንግሥትን፣ ሕግንና ኃይልን ግን በቀጥታ አንመለከትም። የተማከለ ኃይል አናይም ግን የገጸባሕርያቱ የፍርሃት ምንጭ ከተማከለ ኃይል ጋር የተያያዘ ቀጭን መስመር መኖሩን እናያለን። መንግሥትም ቢኾን በቀጥታ አይገባም፤ ነገር ግን ፍርሃት እንደ ሥርዓት ዘዋሪ (system driver) ይኾናል። እንደ ሚሸል ፉኮ አገላለጽ ኃይል ከተማከለ ሥርዓት የሚመነጭ ሳይኾን በየትኛውም ቦታና ጊዜ በፍርሃት፣ በልማድ፣ በንግግር … ሊከሰት የሚችል ሂደት አይደል?
መዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ “circulation of social energy” ቀርቧል። መዝሙረ ሄላም ላይ መረጃ ከመንግሥት አይመጣም፤ ከግለሰብ እንጂ። የከተማ መሬት ዐዋጅም ኾነ የተማሪዎች ዘመቻ በገጸባሕርያቱ ወሬ ውስጥ ነው የሚንቀረቀበው። ይህ የመረጃ ሥርዓት ኃይል ማን እንዳለው ማን እንደሌለው ያሳያል። እንግዲህ ይህ በፉኮኛ micro-power መኾኑ ነው። በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክ እንደ ወሬ እንጂ እንደ ሰነድ አይቀርብም።
ወሬ የፍርሃት ቤንዚን ነው … ፍርሃት ደግሞ በዝምታ መሸበብን ይፈጥራል … የዝምታ አፈ-ሙቅ ደግሞ ኃይለኛው እንዳይታይ ያደርጋል … የተደራጀው ኃይል ጥፋትን ሊያደርስ ባሰበ ቁጥር የወሬ ቤንዚን ይጨምራል። ሰዎች በዕቅብተ-ንግግር ራሳቸውን ሲሸብቡ ደርዝ ያለው ሙግት ይኮሰምናል፣ ንግግር ሲጠፋ ያልታወቀ አደጋ ይከሰታል፣ ፍርሃትም ይጨምራል። ያልታወቀ አደጋ ደግሞ ከታወቀ አካል ይመጣል። ስለዚህ ጥንስሱ የሚጀምረው ከወሬ እንደኾነ ያስመለክተናል። አዳም በመዝሙረ ሄላም ላይ ታሪክን እንደ “circulation of social energy” ሲያቀርብ ፕሬዝዳንት፣ ጀነራል፣ ፕሮፌሰር የኾኑ ታሪክ ከላዕላይ ያስቀመጣቸው ሰዎች አያስፈልጉትም። በአንጻሩ ሄላም ለማን እንደሳመችው ተደርጎ ብርሃኔ ያስወራው ወሬ፣ የሄላም አባት ወታደር በመኾኑ ምክንያት በካሱ፣ በሄኖክ እናት የተነዛው ወሬ እና ሄላም ከሄኖክ ጋር የተቆራረጠችበት መንገድ እንዲሁም የሄላምን የጡት ወተት በተመለከተ የተነዛው ወሬን ይጠቀማል።
መዝሙረ ሄላምን ከድኅረ-ቅኝ-አገዛዝ የኂስ መንገድ አንጻር እንመልከተው።
እውን ቅኝ-ግዛት ተረት ኾኖ ቀርቷል? በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በሥነልቦና ረገድ የቅኝ አገዛዝ ዳናው ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል? አዳም በመዝሙረ ሄላም ጽሑፍ ውስጥ ከቅኝ-ግዛት በተወረሰ መዋቅር ምክንያት የተሰናከለን ሕይወት ሊያስመለክተን ይኾን?
“ከተሞች ከቅኝ ግዛት በኋላ ሁለት ዓይነት መልክ ይኖራቸዋል፤ ለጥቂቱ የተድላ፣ ለተቀረው ደግሞ የአሳር መንደር ይኾናሉ” ይላል ፍራንዝ ፋኖን። በመዝሙረ ሄላም ላይ እና “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላሞት” የተሰኘው ድርሰት ላይም ይህንን ነው የምንመለከተው። “ይወስዳል መንገድ ያመጣል መንገድ …” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ ካሉ ጽሑፎች መካከል “የቢሾፍቱ ልጆች ጥላ ሞት” አንዱ ነው። የቢሾፍቱ ልጆች ሆቴሉን ያዩታል፤ ግን አይገቡበትም። ሆቴሉ የሀገራቸው መሬት ላይ ነው፤ እነርሱ ግን ከሆቴሉ ውጭ ናቸው። መናፈሻው ውስጥ አንዲት የፈረንጅ ልጅ ጠግባ ለልጆቹ እንደ ውሻ ዳቦ ትወረውርላቸዋለች። አፈር ላይ የወደቀን ዳቦ አራግፈው ይመገባሉ። በገዛ ሐይቃቸው ዳር ላይ ናቸው፤ ሌሎች ግን በጀልባ እየተንሸራሸሩ ይንፈላሰሳሉ። ለፈረንጆቹ ያደረው ሞገስ የላንድሮቨር ተፈናጣጭ ኾኗል። ሌሎቹ ግን ከመኪናው ውጪ ናቸው። ሞገስ እንደ እነርሱ ሕጻን ቢኾንም ለፈረንጅ በማሸርገዱ የትምህርት ቤቱ ባለቤት ሲመስል ሌሎች ልጆች ግን በገዛ መምህራቸው ይብጠለጠላሉ። የቢሾፍቱ ልጆች፣ ነጻ በተባለች ሀገር እየኖሩ በቅኝ ግዛት ጥላ ይተዳደራሉ። የቢሾፍቱ ልጆች በገዛ መንደራቸው አካሉ በማይታይ የቅኝ ግዛት እጅ ይገፋሉ። ሞገስ አይናገርም፤ የሚናገርለት አለ። ልክ የቢሾፍቱ ልጆች ላይ በአንድ ከተማ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንደምናገኘው ሁሉ “የስንብት ቀለማት” ላይም በአዲስ አበባ ውስጥ ሁለት የከተማ ምሥል እንመለከታለን። እንደ ዘድሬክ፣ ሳተርን፣ ከተስፋዬ ወደ አሸናፊ የተቀየሩ የድሎት ምሥሎች እና የእነምትክ ጉልት፣ የእትየ እልልታ የጉርሻ መሸጫ መስኮት ያሉ የእጦት ሥዕል እናገኛለን። መዝሙረ ሄላም ላይም እንዲህ ያለ በአንድ ከተማ ላይ የሁለት ምሥሎች አደባባይ እጀግ ብዙ ቦታ ይገኛል።
በሌላኛው የድኅረ-ቅኝ-ግዛት ኂስ (postcolonial criticism) መዝሙረ ሄላምን ስንመለከት መጀመሪያ ላይ “ፈረንጅ ሲያደንቀኝና ሲገረምብኝ የሰሙ የአገሬ ደነዞች በየተራ “ካላስ የኔ ጎሳ ናት” … እያሉ መሻማት ጀመሩ ትላለች - ሄላም። በኋላ ደግሞ በተነዛባት አጓጉል ወሬ … የሄላምን ጡት ንቀው፣ አንጓጥጠው፣ አባረዋት ሲያበቁ የፈረንጅ የዱቄት ወተትን ይመርጣሉ። ይህ በባሕላዊ ማንነትና በዘመናዊነት መካከል የሚዋልል ማኅበረሰብን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የድኅረ-ቅኝ-ግዛት አካል ነው። በሌሎቹ የአዳም ሥራዎች ውስጥ ድኅረ-ቅኝ-ግዛት አተያይ በቋንቋና በኪነ-ጥበብ ምርጫ ውስጥ እንዴት እንደሚንፀባረቅ ያሳያል። በመዝሙረ ሄላም ላይ ደግሞ ምዕራባዊው ዓለም ለአገር በቀል መፍትኼ-ሥራይ የሚሰጠው ዋጋ ዝቅተኛ መኾኑንና የኢኮኖሚ ብዝበዛው አሁንም በረቂቅ መንገድ መቀጠሉን ያሳያል። እዚህ ላይ ሥዕለማርያም የተባለችዋን ገጸባሕርይ እና በውጭ ሀገራት የተነዙ ወሬዎችን ስንጨማምር ደግሞ የበለጠ ብዙ ለማለት ያስችላል።
መዝሙረ ሄላም ላይ እጅግ ብዙ ማኅበረሰባዊ ኂስ እናገኛለን። ለአብነት ያህል አንድ ሁለቱን እንቃኝ።
“መዝሙረ ሄላም” ላይ ማኅበረሰቡ በችላ-ባይነት አልያም በኾን ተብሎነት ልጆቹን ምን ያህል ተጠቂ እንዳደረጋቸው የሚያሳይ መልክ ተንጸባርቆበታል ማለት ይቻላል። ጋሽ ክብካብና ዘመናይ ኾን ብለው ቴዲና ሄላም ላይ የሚያደርሱትን፣ ተክለማርያም የወላጁን(የዘሪቱን) ችላ-ባይነት ለአብነት ማቅረብ ይቻላል። ማኅበረሰቡ ልጆችን “የነገ ተስፋዎች” ይላል፤ ነገር ግን ዛሬያቸው ላይ አይሠራም።
ማኅበረሰብ የመማጸኛ ከተማዎችን ወደ ተጨማሪ ግፍ መሥሪያ ቦታዎች እንደሚቀይር በአዳም መጻሕፍት ላይ በብዛት እንመለከታለን። “ይወስዳል መንገድ …” ላይ … “ቀዳዳ” በተሰኘው ታሪክ ላይ ማርታ ለደበበ በምትሰጠው ፍቅር ሳቢያ የሚሠራበትን ግፍ የምታስረሳ ብትኾንም ማኅበረሰቡ ግን ተጨማሪ ግፍ የሚሠራበት መሣሪያ ኾናለች። የስንብት ቀለማት ላይ ምኒልክ ከዚያ ሁሉ እስርና እንግልት በኋላ፣ “በፊያሜታ አርፋለሁ” ብሎ ቤቷ ሲሄድ ተጨማሪ ሕመም በጆሮው በኩል ጭንቅላቱ ላይ ይሻጥበታል። መዝሙረ ሄላም ላይም፣ ሄላም “ሙዚቃዬን ከሕዝብ ጆሮ ያደርስልኛል … ያሳርፈኛል …” ብላ የተመካችበት ምናሴ እንጦሮጦስ ይጨምራታል። ማኅበረሰባችን የመስቀል ተ ሠላጢን ግብር እንዳለው፣ ከላይ አሳልሞ ከታች በአንካሴው ጉድጓድ እንደሚምስ ያሳያል። ይህም የመልእክትን ወጭት ሰብሮ የወጣ ጥበባዊ አጻጻፍ ነው። በፈጣጣው የቀረበ የትችት ኮሶ አይደለም። ድንቅ ነው!
መዝሙረ ሄላም ላይ ከምናገኛቸው ዋና ዋና ገጸባሕርያት የተወሰኑት (አሮን፣ ቃል፣ ምናሴ፣ ሄላም) ላይ መጠነኛ ቅኝት እናድርግ።
auto-fiction ዓይነት አጻጻፍ ባለው የአሮን አተራረክ ውስጥ አሮን “system observer” መኾኑን እንገነዘባለን። ሥርዓቱን ያያል፣ ዘማቹን ያስተውላል፣ ቃለጉባኤ ይይዛል፣ ችግሩን ይመለከታል፣ ይጽፋል። አሮን የተገፋ ታሪክ ድምፅ ነው፤ ንቃት አለው፣ ግን የታሪክ ሂደትን የሚቀይር ኃይል የለውም፤ ስለዚህም ያ ሁሉ የጻፈውን ጽሑፍን ያጣል። የንቃት ችግር የለበትም፤ የማኅበራዊ ንቃት ድምፅነቱን ከዘመነ አባት ጋር ባደረገው ውይይት ውስጥ ተመልክተናል። ግን ደግሞ ይህ ብቻውን የቆመ ነጠላ ነገር ነው፤ ምክንያቱም ማኅበራዊ ተሳትፎ የለበትም። ቃል የተሰኘችው ገጸባሕርይም እንደ አሮን ናት፤ ንቃት ያላት፣ system observer ናት። ማኅበራዊ ንቃት ማኅበራዊ እንቅስቃሴ ካላገዘው ግንጥል ጌጥ ነው። ቃልና አሮን ንቃት አላቸው፤ ግን ንቃታቸውን ተግባር አላገዘውም፤ ንቃቱን የሚተገብር አደረጃጀት የላቸውም። ስለዚህ ዕጣ-ፈንታቸው ውድቀት ይኾናል። በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ይህን የድግግሞሽ አዙሪት መዝሙረ ሄላም ላይ ደራሲ አዳም ረታ በሰላ ብዕር አስቀምጧል።
የደራሲና የአርታኢ ትስስር በተንጸባረቀበት በሄላም አተራረክ ውስጥ ምናሴ የተሰኘ ገጸባሕርይ እናገኛለን። ምናሴ የ-false collective consciousness ትእምርት ነው። ምናሴዎች ለሥልጣን ይሠራሉ፣ ራሳቸውን እንደ ነጻ ያስባሉ፤ ነገር ግን የሥርዓቱ የመጠቀሚያ መሣሪያ (system functionary) ናቸው። ምናሴዎች የኦልቪቴዎች ጥይት ናቸው። ምናሴዎች የሔላምዎች ስኬት ሳይኾን የገዛ ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ የማኅበረሰቡ አካል ናቸው። ምናሴ በሌላ መነጽር ብናየው የመንግሥት ቢሮክራት የመካከለኛው መደብ ውክል ነው። ሀገሩ ከንጉሣዊ ሥርዓት ወደ ወታደራዊ ሥርዓት ቢቀየርም፤ ከወታደራዊ ሥርዓት ወደ ሌላ ሥርዓት ቢለወጥም ምናሴያውያን ግን አይቀየሩም። ሥርዓት ይቀየራል - ምናሴያውያን አይቀየሩም፣ ትእዛዝ ይፈጽማሉ፣ ይከድራሉ። ይህ በኢትዮጵያ ፖለቲካል-ታሪክ ውስጥ የተደጋገመ፣ ግን ደግሞ ያልተስተዋለ እውነት ነው።
ሄላም የወታደር ልጅ ናት፤ እንዲያሳድጋት በአደራ የተሰጠው ቤተሰብ የሚበድላት። የሷ ዓይነት ዕጣ ከደረሰው እንደ ወንድሟ ከምታየው ቴዲ ከሚባል ልጅ ጋር ታድጋለች። መጀመሪያ የሚልዮን፣ የኋላ ኋላ የምናሴ ፍቅረኛ የምትኾን ድምፀ-መረዋ ሴት ናት። ሁሉ ነገሯን ባጣችበት ወቅት ጡቷ ተአምር ያመርታል።
በመዝሙረ ሄላም ላይ የሄላም የጡት ወተት የአንዳች ነገር ውክል ይመስለኛል። ሻዕቢያ ለታጋይ ወጣቶች ማሳደጊያ ፈልጓት ሊሰርቃት መፈለጉ በቀላሉ የሚዘለል ነገር ነው? ወተት እና ጡት በመጀመሪያ እይታ የሕፃናት ትዝታ፣ የእናትነት ምሥል፣ የእምነት እና የጾታ መነሳሳት የተዋሃዱበትም አይደል? ወተት ሕይወት ነው? የመጀመሪያ ምግብ፣ ከእናት ወደ ልጅ የሚፈስም አይደል? በክርስቲያናዊ ምልክት ንጹሕነትን አይወክልም? ወተት ከ“ቅዱስ” ወደ “ሥጋዊ” የሚያስተላልፍ ድልድይ ነው ማለት እንችል ይኾን? የሄላምን ጡት የጠባ ታማሚ ልጅ እንዴት ጤናማ ሊኾን ቻለ? የምን ትእምርት ነው? ሄላም ከብዙ ወንድ ጋር የወጣች እንደመኾኗ ለዚህ ሰናይ ግብር ለምን የሷ ጡት ተመረጠ?
ሌላው፣ መዝሙረ ሄላም ላይ ኦልቬቲን እናገኛታለን። ኦልቬቲ የግራጫ ቃጭልዋ። መዝገቡ ንፋስ መውጫ ሳለ፣ ባልንጀራው ኤልያስ የብልግና ሀሁ ሊያስተምረው እፊቱ ያቆማት ቀይ ሰሌዳ ነበረች ኦልቬቲ። መዝሙረ ሄላም ላይ ምናሴን እና ቤተሰቡን የምታሾር ዐውራ ገጸባሕርይ ኾና ትከሰታለች። መዝሙረ ሄላም እና ግራጫ ቃጭሎች በጋለሞታይቱ በኦልቬቲ ብቻ ሳይኾን በዘመነ እንድርያስ እና በመዝገቡ ዱባለም ይገናኛሉ። ነጋ ዳቦ ጋጋሪውም በ-typological space መዝሙረ ሄላም ላይ እናገኘዋለን።
መዝሙረ ሄላምን ከህላዌነት (Existentialism) አንጻር እንመልከተው። ሄላም ትርጉም በማይሰጥ ዓለም ውስጥ እንዴት እንደምትኖር እናነባለን። የሀገሯ ዳር ድንበር እንዳይነካ አባት ብታዋጣም አሳዳጊዎቿ ግን የወላጅን ፍቅር አዋጥተው አይለግሷትም። ወርቅ አበድራ ጠጠር ትነፈጋለች። ዕቃ ለማገዝ ቤቷ ድረስ ለመጣው ሚልዮን ልቧን ትሰጣለች። ሀና የሸነቆረችውን ክፍተት ለሞላችበት ውለታዋ ክፍያ ይኾን ዘንድ ሚልዮን ለሄላም የወለፈንዴ ቡጢ ያሳርፍባታል። ለሕይወት ትርጉም ለመስጠት ባስ ውስጥ ካገኘችው ሄኖክ ጋር ብትሞክርም የበለጠ የሕይወት ትርጉም ይዛባባታል። የወታደር ልጅ መኾኗ ሄላምነቷን በዜሮ ያባዘዋል። የመጨረሻው ስንብትም ከሄኖክ ጓደኛ አፎት በሚወጣ ሰይፍ መቀላት ይኾናል። ከሄኖክ ጓደኛ ጀርባ የሚውለበለበው ባንዲራ ደግሞ የሄኖክ ሸሚዝ መኾኑ ደግሞ ቁስሉን እንደ አቡሰዲቅ ያደርገዋል። ለሕይወቷ ትልቅ ትርጉም ያለውን የሙዚቃ ሥራዋን፣ “ትርጉም ወዳለው
ነገር ይቀይርልኛል” ብላ በምትተማመንበት በምናሴ ትነጠቃለች። ተአምር በሚያስብለው በጡት ወተት ምክንያት ለሕይወቷ ትርጉም ለመስጠት ትታትራለች። የጡት ወተቷን ምርምር በማድረግ ለትልቅ ዓለምአቀፍ በጎ ተፅዕኖ ታደርጋለች ተብላ የተቆጠረችው ሥዕለማርያም የዓለም አቀፍ መሳለቂያና ትችት ምንጭ ትኾንባታለች። ይህ ሁሉ ትርጉም የሌለው ድግግሞሽ ነው። ይህ ደግሞ በሳርተር የተገለጸውን “existence without essence”-ን ያሳያል።
የህላዌነት መሠረታዊ ሐሳብ ነጻነት ነው፤ ግን ነጻነት ፍርሃትን ይወልዳል። ሄላም ለአሮን ፍቅሯን መናገር ትችላለች፤ ነገር ግን ዝምታን መርጣለች። የግራጫው መዝገቡ፣ የእንጀራ እናቱ የምታደርስበትን በደል እንደሚያውቀው ሁሉ ሄላምም ክብካብና ዘበናይ የሚያደርሱባትን አድሎ ታውቃለች፤ ግን ለረዥም ጊዜ ዝም ብላለች። ሄላም፣ ሙዚቃዋን ካጣች በኋላ ወደ ባንዱ ሄዳ መጋፈጥ ትችላለች፤ ነገር ግን አትሄድም … ይህ በሳርተርኛ bad faith ነው።
የሄላም ምርጫ ዝምታ ኾነ እንጂ ደካማ ናት ማለት አይደለም። “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል ዝምታ ነው ያላት። በሌላ ጎኑ ደግሞ ዝምታዋ፣ የለመደችውን ግፍ ከማታውቀው ዐዲስ ግፍ የመምረጥ ኹኔታ ነው። ዐዳዲስ ግፎችን ለመሸሽ በዝምታ አላዋቂነት ዛጎል ውስጥ የመደበቅ ብቃት ነው። የለመደችውን ግፍ የመከላከል አቅም ስላላት ባለመደችው ግፍ እንዳያጠፏት ሠግታ በውስጣዊ ንቃተ ሕሊና የዘየደችው ብልሃት ሊኾን ይችላል። ዝምታዋ የመቆየቷ ምሥጢር ነው። ደበበ ቀዝቃዛ ገለልተኛ ነኝ የሚለው ሰው ለመኖር ሲል ሳይታወቀው ስሜቱን የሚቆጣጠርበት መንገድን ለማስታወስ ነው።
“የስንብት ቀለማት” ገጸባሕርይ የኾነው ዮሴፍም ብዙ ነገር ያውቃል፤ ግን ዝም ይላል … ፊያሜታ ቂል መስሏት ትዘባርቃለች … እሱ ግን “አልተናገርኩም ማለት አላውቀውም ማለት አይደለም” የሚል የዝምታ መልስ ይመልስላታል። እሷ ግን ዝምታው አይገባትም። የ“ቀዳዳ”ው ደበበ እና “የስንብት …” ዮሴፍ ቀዳዳውን አይሞሉትም፤ እያዩት ይኖራሉ። ዶነሮች ጥሩ ፈንድ ሲለቁ ፊያሜታ ፕሮጀክቱን ለአሳምነው ትሰጠውና ዮሴፍን “ምን ዶነሮች እኮ ጠፉ ትለዋለች” … ዝም ይላል፤ ይታዘባል።
ቃል መሣሪያ ነበር፤ በዘመነ ደበበ፣ በዘመነ ዮሴፍ፣ በዘመነ ሄላም እና በዘመነ መዝገቡ ዱባለ ግን ቃል አደገኛ ኾኗል፤ ዝምታ ኹነኛ መጠጊያ ነው … ይህ ከደርግ በኋላ የተፈጠረ “traumatized literary silence” ማሳያ ነው። ስለኾነም ተራኪዎቹ (ደበበ፣ መዝገቡ፣ ዮሴፍ እና ሄላም) ለምን ዝም አሉ ሳይኾን "ዝምታን የሚያመነጭ ሥርዓት ምን ይኾን?" ብለን እንድንጠይቅ ያደርጋል። ግለሰብ ዝም ሲል፤ ሕዝብ በጸጥታ ይዋጣል፤ የዚያኔ የተማከለው ኃይል አፍ ያወጣል።
የአዳምን ዐዲሱን መጽሐፍ "በንባብ ይለቅ" ብለን መርቀናል።
ቢኒያም አቡራ
ሐምሌ 25 / 2018 ዓ.ም
4 days ago
እስራኤል አሽከርካሪ አልባ የታክሲ አግልግሎት ልትጀምር ነው
#ethiopia | እስራኤል በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎችን በ2027 አገልግሎቱን በይፋ ልታስጀምር ነው።
እስራኤል ይህንን አገልግሎት አስቀድማ ለማስጀመር ከባለፉት አምስት አመታት ጀምራ ጥረት ስታደርግ ነበር ሲል ዘ ጀሩሳሌም ፖስት የዘገበው።
የመንግስት መስሪያ ቤቶች የራሳቸውን የህግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ባለፉት አምስት ዓመታት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ቢሆንም ወጥ የሆነ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂና የደህንነት ስታንዳርድ ባለመኖሩ ምክንያት ሂደቱ ሲጓተት ቆይቷል ነው የተባለው።
ነገር ግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሽከርካሪዎች ህግ አውጪ አካል በቅርቡ ያጸደቀው አዲስ የደህንነትና የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎቱ ለማስጀመር ረድቷል ተብሏል።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎች ከሰው አሽከርካሪ ያላነሰ ወይም የተሻለ የደህንነት ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት አዲሱ የአውሮፓ ስታንዳርድ እስራኤል ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ የሚሆን ይሆናል።
የእስራኤል የትራንስፖርት ሚኒስቴር ያለ አሽከርካሪ የሚሰሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ለአስመጪዎች ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያፋጠነ ይገኛል ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #israel #taxi #transport #technology
#ethiopia | እስራኤል በራሳቸው የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎችን በ2027 አገልግሎቱን በይፋ ልታስጀምር ነው።
እስራኤል ይህንን አገልግሎት አስቀድማ ለማስጀመር ከባለፉት አምስት አመታት ጀምራ ጥረት ስታደርግ ነበር ሲል ዘ ጀሩሳሌም ፖስት የዘገበው።
የመንግስት መስሪያ ቤቶች የራሳቸውን የህግ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት ባለፉት አምስት ዓመታት ጥረት ሲያደርጉ የቆዩ ቢሆንም ወጥ የሆነ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂና የደህንነት ስታንዳርድ ባለመኖሩ ምክንያት ሂደቱ ሲጓተት ቆይቷል ነው የተባለው።
ነገር ግን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሽከርካሪዎች ህግ አውጪ አካል በቅርቡ ያጸደቀው አዲስ የደህንነትና የቁጥጥር መመሪያ አገልግሎቱ ለማስጀመር ረድቷል ተብሏል።
አዲሱ የሕግ ማዕቀፍ አሽከርካሪ አልባ ተሽከርካሪዎች ከሰው አሽከርካሪ ያላነሰ ወይም የተሻለ የደህንነት ብቃት ሊኖራቸው እንደሚገባ ያስገድዳል።
በዚህም መሰረት አዲሱ የአውሮፓ ስታንዳርድ እስራኤል ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ የሚሆን ይሆናል።
የእስራኤል የትራንስፖርት ሚኒስቴር ያለ አሽከርካሪ የሚሰሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ለአስመጪዎች ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት እያፋጠነ ይገኛል ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #israel #taxi #transport #technology
4 days ago
በተቋማዊ ሪፎርሙ ሕዝባዊነቱን ያጠናከረው ሠራዊት
**************
የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነት፣ የሕዝብ ደኅንነት እና የጽናት ታላቅ ምሰሶ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት በሠራዊቱ ውስጥ የተተገበሩት ጥልቀት ያላቸው የሪፎርም እና የተቋማዊ መዋቅር ማሻሻያዎች ሠራዊቱን ወደ አዲስ የልህቀት ደረጃ ያሸጋገሩ ናቸው።
ይህ የሪፎርም ሂደት የሠራዊቱን ሕዝባዊነት የበለጠ ያጠናከረ፣ ሙያዊ ገለልተኝነቱን ያረጋገጠ እና መዋቅራዊ አደረጃጀቱን በዘመናዊ ወታደራዊ ሳይንስ መርሆዎች ላይ ያቆመ ነበር።
ተቋሙን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት በማፅዳት እና አደረጃጀቱን በማዘመን የአየር ኃይል፣ የባሕር ኃይል እንዲሁም የሳይበር ደኅንነት ክፍሎች ዘመኑ የሚጠይቀውን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዝግጁነት ደረጃ እንዲላበሱ አስችሏቸዋል።
በተቋማዊ ሪፎርሙ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ውጤቶች መካከል በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በሰው ኃይል ግንባታ ላይ የታየው የላቀ ዕድገት ይጠቀሳል።
ሠራዊታችን ዘመናዊ የክትትል ቴክኖሎጂዎችን፣ የሰው አልባ አየር (ድሮን) ሥርዓቶችን እና የተራቀቁ የመረጃ መረቦችን በመታጠቅ ተቋማዊ ቁመናውን አዳብሯል።
በየደረጃው ባሉ ወታደራዊ አካዳሚዎች የተሰጡት የላቁ የስልጠና መርሐ-ግብሮች የሠራዊቱን ሥነ-ልቦናዊና ቴክኒካዊ አቅም በማሳደግ፣ አደጋዎችን በሳይንሳዊ ስልት፣ አነስተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ጉዳት በሚያስከትል መልኩ የመከላከልና የማክሸፍ ብቃቱን አጎልብተውለታል።
በሀገራችን ያጋጠሙ ውስብስብ የውስጥ ደኀንነት ፈተናዎችን በማረጋጋት ሂደት ሠራዊቱ ያሳየው አስተዋይነት እና ሕዝባዊ ወገንተኝነት ጎልቶ የወጣበት ነው።
የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የትዕግሥት እና የሰላም መንገዶችን በማስቀደም፣ የሲቪሎችን ሕይወት ከጉዳት በመጠበቅ እና የሀገር ሀብት የሆኑ መሠረተ-ልማቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል።
ይህም ሠራዊቱ የኃይል አጠቃቀምን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ የሰላም እና የሕግ ሥርዓት ዋስትና መሆኑን ያስመሰከረበት ነው።
ከሀገር ውስጥ ተልዕኮ ባሻገር፣ ሠራዊታችን በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ለሚከናወኑ የሰላም ማስከበር ሥራዎች የጸና አለኝታ ሆኖ ዘልቋል።
በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተልዕኮዎች የሚያሳየው የላቀ ሙያዊ ሥነ-ምግባር፣ ለሕዝብ ያለው ቅርበት እና የተላበሰው ሕዝባዊነት የሀገራችንን በጎ ገፅታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተገነቡት ዘመናዊ አቅሞች እና ተቋማዊ ነፃነት፣ ሠራዊታችን ወደፊትም የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝብን አደራ በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥለዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopiandefenseforce #endf #ethiopianarmy #heroesofethiopia #militarypower #ethiopiandiplomacy
**************
የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገር ሉዓላዊነት፣ የሕዝብ ደኅንነት እና የጽናት ታላቅ ምሰሶ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት በሠራዊቱ ውስጥ የተተገበሩት ጥልቀት ያላቸው የሪፎርም እና የተቋማዊ መዋቅር ማሻሻያዎች ሠራዊቱን ወደ አዲስ የልህቀት ደረጃ ያሸጋገሩ ናቸው።
ይህ የሪፎርም ሂደት የሠራዊቱን ሕዝባዊነት የበለጠ ያጠናከረ፣ ሙያዊ ገለልተኝነቱን ያረጋገጠ እና መዋቅራዊ አደረጃጀቱን በዘመናዊ ወታደራዊ ሳይንስ መርሆዎች ላይ ያቆመ ነበር።
ተቋሙን ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት በማፅዳት እና አደረጃጀቱን በማዘመን የአየር ኃይል፣ የባሕር ኃይል እንዲሁም የሳይበር ደኅንነት ክፍሎች ዘመኑ የሚጠይቀውን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የዝግጁነት ደረጃ እንዲላበሱ አስችሏቸዋል።
በተቋማዊ ሪፎርሙ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ውጤቶች መካከል በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በሰው ኃይል ግንባታ ላይ የታየው የላቀ ዕድገት ይጠቀሳል።
ሠራዊታችን ዘመናዊ የክትትል ቴክኖሎጂዎችን፣ የሰው አልባ አየር (ድሮን) ሥርዓቶችን እና የተራቀቁ የመረጃ መረቦችን በመታጠቅ ተቋማዊ ቁመናውን አዳብሯል።
በየደረጃው ባሉ ወታደራዊ አካዳሚዎች የተሰጡት የላቁ የስልጠና መርሐ-ግብሮች የሠራዊቱን ሥነ-ልቦናዊና ቴክኒካዊ አቅም በማሳደግ፣ አደጋዎችን በሳይንሳዊ ስልት፣ አነስተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ጉዳት በሚያስከትል መልኩ የመከላከልና የማክሸፍ ብቃቱን አጎልብተውለታል።
በሀገራችን ያጋጠሙ ውስብስብ የውስጥ ደኀንነት ፈተናዎችን በማረጋጋት ሂደት ሠራዊቱ ያሳየው አስተዋይነት እና ሕዝባዊ ወገንተኝነት ጎልቶ የወጣበት ነው።
የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች የትዕግሥት እና የሰላም መንገዶችን በማስቀደም፣ የሲቪሎችን ሕይወት ከጉዳት በመጠበቅ እና የሀገር ሀብት የሆኑ መሠረተ-ልማቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ረገድ ውጤታማ ሥራ ሠርቷል።
ይህም ሠራዊቱ የኃይል አጠቃቀምን የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ የሰላም እና የሕግ ሥርዓት ዋስትና መሆኑን ያስመሰከረበት ነው።
ከሀገር ውስጥ ተልዕኮ ባሻገር፣ ሠራዊታችን በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ለሚከናወኑ የሰላም ማስከበር ሥራዎች የጸና አለኝታ ሆኖ ዘልቋል።
በአፍሪካ ኅብረት እና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተልዕኮዎች የሚያሳየው የላቀ ሙያዊ ሥነ-ምግባር፣ ለሕዝብ ያለው ቅርበት እና የተላበሰው ሕዝባዊነት የሀገራችንን በጎ ገፅታ በዓለም አቀፍ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተገነቡት ዘመናዊ አቅሞች እና ተቋማዊ ነፃነት፣ ሠራዊታችን ወደፊትም የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝብን አደራ በላቀ ብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አስተማማኝ መሠረት ጥለዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopiandefenseforce #endf #ethiopianarmy #heroesofethiopia #militarypower #ethiopiandiplomacy
4 days ago
ይህን እሽግ እንደተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ ወንጀል ነው!
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከባድ የምግብ እጥረት የተጎዱ ሕፃናትን ሕይወት ለማዳን የሚሰጠው አጣዳፊ የምግብ መድኃኒት (RUTF) ወይ በተለምዶ ስሙ ፕላምፕሌት በገበያ ላይ ለንግድ መቅረቡና ለክብደት መጨመሪያ መዋሉ ከፍተኛ የሞራልና የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ወንጀል መሆኑ ተገለጸ።
በሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ሕፃናትን ለማዳን በልዩ ሁኔታ የተዘጋጀውን ይህን ሕይወት አድን እሽግ እንደ ተራ መክሰስ ለገበያ ማቅረብ በእርግጥም ህክምናው ለሚገባቸው ሕፃናት የሚደርሰውን እርዳታ በመንጠቅ ሕይወታቸውን ለሞት አደጋ የሚያጋልጥ ተግባር ነው።
በሌላ በኩል ይህ ምርት በካሎሪ፣ በቅባትና በቫይታሚኖች እጅግ የበለፀገ በመሆኑ ጤናማ ሰዎች ሳያስፈልጋቸው ሲመገቡት ለከፍተኛ የኩላሊትና የጉበት ጫና፣ ለደም ስኳርና ቅባት መዛባት እንዲሁም ለቫይታሚን መርዝነት ያጋልጣቸዋል።
በመሆኑም በነፃ ወይም በሕክምና ተቋማት በኩል ለተቸገሩ ሕፃናት የተላከን እርዳታ መሸጥም ሆነ መግዛት በሕግ የሚያስጠይቅ ወንጀል በመሆኑ፣ ሕይወት አድን መድኃኒቶች የንግድ ዕቃ አለመሆናቸውን ተረድቶ ኅብረተሰቡ ከዚህ ድርጊት ሊቆጠብ እንደሚገባ መልእክት ተላልፏል።
(via ጤና)
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
5 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
6 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅ ሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅ ሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
6 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
8 days ago
#usa #immigration
በአሜሪካ ጥገኝነት ጠያቂዎች ያለ ቃለ-መጠይቅ ወደ ፍርድ ቤት የሚላኩበት መመሪያ ጸደቀ።
የትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ጥገኝነት የጠየቁ ስደተኞችን የሚመለከት አዲስ መመሪያ አውጥቷል።
ይህን ተከትሎ በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው ሳይሰማ ቀጥታ ሊባረሩ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
አዲሱ አሰራር ከ1.4 ሚሊዮን በላይ የተከማቹ የጥገኝነት ማመልከቻዎችን ለማቃለል የታሰበ ነው ተብሏል።
ቀደም ሲል የነበረው አሰራር አመልካቾች መጀመሪያ ጉዳያቸውን ለኢሚግሬሽን ኦፊሰር አቅርበው ጥያቄያቸው ውድቅ ከተደረገ ብቻ ወደ ፍርድ ቤት እንዲመሩ የሚያደርግ ነበር።
በአዲሱ መመሪያ በርካታ የጥገኝነት አመልካቾች ከኢሚግሬሽን ኦፊሰሮች ጋር የሚደረገውን የመጀመሪያ ደረጃ ቃለ-መጠይቅ ሳያደርጉ ጉዳያቸው በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት ሊመራ ይችላል።
444,724 ያህል መዝገቦችን ይነካል የተባለው ይህ ውሳኔ የሕግ ባለሙያዎችና የኢሚግሬሽን ተከራካሪዎች አሰራሩ የስደተኞችን የመሰማትና የፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳና ውሳኔዎችን በማፋጠን ሰዎችን በፍጥነት ለማባረር ያለመ ነው በማለት ተችተውታል።
በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ መንግሥት በሀገሪቱ በሚማሩ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ላይ እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ማቀዱ ተሰምቷል።
የታቀደው እርምጃ በተለይ ትምህርታቸውን አጠናቀው በአሜሪካ ለመቆየት ለሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ፈተና ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።
መንግሥት እርምጃው የቪዛ አጠቃቀምን ለማጥበቅና የሀገር ውስጥ የሥራ ገበያን ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ሲገልጽ፣ ተቃዋሚዎች ግን የውጭ ተማሪዎች ለአሜሪካ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አስተዋፅኦ ሊጎዳ ይችላል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የትራምፕ አስተዳደር ከስደተኞች ጋር በተያያዝ እጅግ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑ ተደጋግሞ መገለጹ ይታወሳል።
Seledadotio
Seledadotio
በአሜሪካ ጥገኝነት ጠያቂዎች ያለ ቃለ-መጠይቅ ወደ ፍርድ ቤት የሚላኩበት መመሪያ ጸደቀ።
የትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ጥገኝነት የጠየቁ ስደተኞችን የሚመለከት አዲስ መመሪያ አውጥቷል።
ይህን ተከትሎ በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው ሳይሰማ ቀጥታ ሊባረሩ የሚችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
አዲሱ አሰራር ከ1.4 ሚሊዮን በላይ የተከማቹ የጥገኝነት ማመልከቻዎችን ለማቃለል የታሰበ ነው ተብሏል።
ቀደም ሲል የነበረው አሰራር አመልካቾች መጀመሪያ ጉዳያቸውን ለኢሚግሬሽን ኦፊሰር አቅርበው ጥያቄያቸው ውድቅ ከተደረገ ብቻ ወደ ፍርድ ቤት እንዲመሩ የሚያደርግ ነበር።
በአዲሱ መመሪያ በርካታ የጥገኝነት አመልካቾች ከኢሚግሬሽን ኦፊሰሮች ጋር የሚደረገውን የመጀመሪያ ደረጃ ቃለ-መጠይቅ ሳያደርጉ ጉዳያቸው በቀጥታ ወደ ፍርድ ቤት ሊመራ ይችላል።
444,724 ያህል መዝገቦችን ይነካል የተባለው ይህ ውሳኔ የሕግ ባለሙያዎችና የኢሚግሬሽን ተከራካሪዎች አሰራሩ የስደተኞችን የመሰማትና የፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳና ውሳኔዎችን በማፋጠን ሰዎችን በፍጥነት ለማባረር ያለመ ነው በማለት ተችተውታል።
በሌላ በኩል ፥ የአሜሪካ መንግሥት በሀገሪቱ በሚማሩ የውጭ ሀገር ተማሪዎች ላይ እስከ 100,000 ዶላር የሚደርስ አዲስ ክፍያ ለመጣል ማቀዱ ተሰምቷል።
የታቀደው እርምጃ በተለይ ትምህርታቸውን አጠናቀው በአሜሪካ ለመቆየት ለሚፈልጉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ፈተና ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።
መንግሥት እርምጃው የቪዛ አጠቃቀምን ለማጥበቅና የሀገር ውስጥ የሥራ ገበያን ለመጠበቅ ያለመ መሆኑን ሲገልጽ፣ ተቃዋሚዎች ግን የውጭ ተማሪዎች ለአሜሪካ የትምህርትና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አስተዋፅኦ ሊጎዳ ይችላል በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።
የትራምፕ አስተዳደር ከስደተኞች ጋር በተያያዝ እጅግ ጠንካራ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑ ተደጋግሞ መገለጹ ይታወሳል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
"ዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ከአማራና ኦሮሞ ውህደት ውጭ ማየት አይቻልም"
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
8 days ago
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለት የሚዲያ ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
ባለሥልጣኑ በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚዲያ ተቋማት ሕግና የሙያ ሥነ ምግባርን አክብረው መስራታቸውን እየተከታተለ ድጋፍና እርምት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት፦
• አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና
• አርትስ ቴሌቪዥን
የተሰጣቸውን የይዘት ግዴታዎች በመተላለፍ፣ ለተከታታይ ጊዜ ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እንዲሁም የሕዝብን ጥቅም የሚጎዳ መረጃ በማሰራጨታቸው የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ በባለስልጣኑ ተሰጥቷቸዋል።
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከሬድዮ እና ከቴሌቪዥን ጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ጋር በተስተዋሉ ተደጋጋሚ የህግና የሙያ ጥሰቶች ላይ ውይይቶች ያደረገ ቢሆንም ጉልህ ለውጥ ሳይታይ በመቅረቱ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ያስታውቃል፡፡
ስለሆነም ጣቢያዎቹ በቀጣይ ሥራቸውን በሕግና በሙያ ሥነ ምግባር መሠረት እንዲያከናውኑ በጥብቅ ለማሳሰብ ይወዳል።
ባለስልጣኑ ማስጠንቀቂያው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጽ 74/ሠ መሠረት የተሰጠ መሆኑን እየገለፀ ሚዲያዎቹ ተመሳሳይ የህግ መተላለፍ እና ጥሰት እየፈፀሙ የሚቀጥሉ ከሆነ በህጉ መሠረት ቀጣይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ባለሥልጣኑ ያስታውቃል።
ባለስልጣኑ የሚዲያ ተቋማት በሁሉም የዘገባ ስራዎቻቸው ላይ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና የሀገሪቱን ሕጎች እንዲሁም የዘርፉን የሙያ ሥነ ምግባር አክብሮ መስራት የሁሉም ግዴታ መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጉት እንደማይገባ ያሳስባል።
Seledadotio
Seledadotio
ባለሥልጣኑ በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚዲያ ተቋማት ሕግና የሙያ ሥነ ምግባርን አክብረው መስራታቸውን እየተከታተለ ድጋፍና እርምት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት፦
• አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና
• አርትስ ቴሌቪዥን
የተሰጣቸውን የይዘት ግዴታዎች በመተላለፍ፣ ለተከታታይ ጊዜ ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እንዲሁም የሕዝብን ጥቅም የሚጎዳ መረጃ በማሰራጨታቸው የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ በባለስልጣኑ ተሰጥቷቸዋል።
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከሬድዮ እና ከቴሌቪዥን ጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ጋር በተስተዋሉ ተደጋጋሚ የህግና የሙያ ጥሰቶች ላይ ውይይቶች ያደረገ ቢሆንም ጉልህ ለውጥ ሳይታይ በመቅረቱ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ያስታውቃል፡፡
ስለሆነም ጣቢያዎቹ በቀጣይ ሥራቸውን በሕግና በሙያ ሥነ ምግባር መሠረት እንዲያከናውኑ በጥብቅ ለማሳሰብ ይወዳል።
ባለስልጣኑ ማስጠንቀቂያው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጽ 74/ሠ መሠረት የተሰጠ መሆኑን እየገለፀ ሚዲያዎቹ ተመሳሳይ የህግ መተላለፍ እና ጥሰት እየፈፀሙ የሚቀጥሉ ከሆነ በህጉ መሠረት ቀጣይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ባለሥልጣኑ ያስታውቃል።
ባለስልጣኑ የሚዲያ ተቋማት በሁሉም የዘገባ ስራዎቻቸው ላይ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና የሀገሪቱን ሕጎች እንዲሁም የዘርፉን የሙያ ሥነ ምግባር አክብሮ መስራት የሁሉም ግዴታ መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጉት እንደማይገባ ያሳስባል።
Seledadotio
Seledadotio
9 days ago
የ«ሁሉ ስፖርት» የፈቃድ ስረዛ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሻረ፤ አገልግሎቱ ግን አሁንም ታግዷል
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ አስተላልፈውት የነበረውን የንግድ ፈቃድ ስረዛ ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው ተቋማቱ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት ሕግን ሳይከተሉ እና የተቋሙን የመሰማት መብት ጥሰው ፈቃድ መሰረዛቸውን በመግለፅ ነው።
መንግሥት ድርጅቶቹ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ሰውረዋል ቢልም፣ ፍርድ ቤቱ ይህ በወንጀል ሕግ የሚታይ እንጂ በደፈናው ለአስተዳደራዊ ፈቃድ ስረዛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በውሳኔው ላይ ይግባኝ ማቅረቡን ተከትሎ፣ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ከሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ቀናት እንዲታገድ ተደርጓል።
በመሆኑም ጉዳዩ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ «ሁሉ ስፖርት» ወደ ሥራ አይመለስም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሎተሪ አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ምንም ዓይነት የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ድርጅት እንደሌለ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት እና የገቢዎች ሚኒስቴር በ«ሁሉ ስፖርት» ላይ አስተላልፈውት የነበረውን የንግድ ፈቃድ ስረዛ ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው ተቋማቱ የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት ሕግን ሳይከተሉ እና የተቋሙን የመሰማት መብት ጥሰው ፈቃድ መሰረዛቸውን በመግለፅ ነው።
መንግሥት ድርጅቶቹ ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር ሰውረዋል ቢልም፣ ፍርድ ቤቱ ይህ በወንጀል ሕግ የሚታይ እንጂ በደፈናው ለአስተዳደራዊ ፈቃድ ስረዛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ብሏል።
ሆኖም የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በውሳኔው ላይ ይግባኝ ማቅረቡን ተከትሎ፣ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ከሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ15 ቀናት እንዲታገድ ተደርጓል።
በመሆኑም ጉዳዩ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ «ሁሉ ስፖርት» ወደ ሥራ አይመለስም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሎተሪ አገልግሎቱ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ምንም ዓይነት የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) ድርጅት እንደሌለ አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
10 days ago
ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ
"...ምን ማለት ነው?"
(ሙሼ ሰሙ)
#ethiopia | "ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ" የሚል ዜና በስፋት እየተዘገበ ነው። ከፍተኛ ግብር ሰበሰቡ ማለት ምን ማለት ነው ?! አንጻሩስ ምንድን ነው ? በጀት ነው ? ኮታ ነው? ወይስ የትም ፍጪው ዲቄቱን አምጭው ነው ? ከበጀት በላይ ማትረፍ እንጂ ከበጀት በላይ ግብር መሰብሰብስ እንዴት ይቻላል? ይህ አዲስ ግኝት ነው?
በደሞዝ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰራተኛ "ውጤታማ ሲሆን" ጉርሻ ( Bonus) ከመስጠትና ደሞዙን ከማሳደግ አልፎ ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል ቢሆንም በየዓመቱ ተሽከርካሪ መለወጥ የትኛው መንግስታዊ አሰራርና ደንብ እንደሚፈቅድ የውጭ ኦዲተር መጠየቅ የሚገባው ጉዳይ ይመስለኛል ?
ወደ ዋነኛ ጉዳዬ ልመለስ ።
እርግጥ ነው። ነጋዴ ንብረቱን ላለማጣትና ድርጅቱን ላለመዝጋት ሲል ጥሪቱንና አቅሙን አሟጦ እስኪጨርስና ቤቱ እስኪከረቸም ድረስ ከበጀትም ከኮታም በላይ እጥፍ ድርብ ግብር በማስከፈል ከበጀት በላይ ገንዘብ መሰብሰብ ይቻላል። ተችሏልም። ጥያቄው ግን እስከመቼ የሚለው ነው ?!
በዚህ መንገድ የመንግስት ገቢ አንድ ሺ ፐርሰንት ሊያድግና ሊመነደግ ይችላል። በኮታና በነሲብ ግብር የመሰብሰብ ዘመቻ በሂደት የነጋዴውን ገቢ እያዳከመና ትርፉን እያቀጨጨ ከመሄድ ውጭ ጤናማ የንግድ፣ የግብይይትና የግብር ስርዓት ሊፈጥር አይችልም። ንግድ ፈቃዱን በሰልፍ የሚመልሰውና ድብብቆሽ የሚጫወተው ነጋዴም ለዚህ ክስተት ሕያው ምስክር ነው። ለምን ቢባል ንግድ ለጽድቅ የሚሰራ ስራ አይደለም።
ለማንም ግልጽ እንደሚሆነው በጤናማ መንገድና በሕግ አግባብ የሚነግድ፣ የሚሰራና የሚያመርት ሰው (ካልከሰረ በስተቀር) ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ከትርፉ ጥሪት በመቋጠርና አቅሙን በማጎልበት ንግዱን በማስፋፋት፣ የስራ እድል መፍጠርና ወደ ሚቀጥለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መደብ ( Economic Class) መሸጋገር መቻል አለበት።
ጤናማ የኢኮኖሚ እድገትና ሽግግር፣ የንግድና የግብር ስርዓት መስተጋብር ማለት ይህው ብቻ ነው። ነጋዴውን አሟጦ በማስገበር ማቀጨጭና በሂደት ከገበያ እንዲወጣ ማድረግ የልማት፣ የእድገትና የምርታማነት እንቅፋት ከመሆን ባሻገር ሕገ ወጥነትና የጓሮ በር ድርድር እንዲስፋፋ በር መክፈት ብቻ ነው። በገሃዱ ዓለምም እየሆነ ያለውም ይህው ነው።
ጤናማ የግብር ስርዓት ንግድና ነጋዴው እንዲያብቡ አመቺ ሁኔታን በመፍጠር አምራቹን፣ ባለኢንዱስትሪውን፣ ቸርቻሪውን አከፋፋዩንና አስመጭውን በቁጥርም በአቅምም እንዲጎለብቱ በማገዝ ከሚፈጠረው ሰፊ የንግድ አቅምና ከሚሳለጠው የምርትና የግብይይት ስርዓት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ ተመጣጣኝ ግብር በመሰብሰብ በቅንጅት እንደ ሀገር ማደግ ይቻላል።
ይህ እውን መሆን የሚቻለው ነጋዴው በቂ ትርፍ አትርፎና ጥሪት ቋጥሮ የማምረት አቅሙን በማጎለብት ፣ ፋብሪካውንና ኢንዱስትሪውን በማሳድግ፣ የስራ እድልና አቅርቦትን በማስፋፋት እምቅ ሃይሉንና አቅሙን መጠቀም የማይገድበው፣ በተለይ ከገቢው ጋር የሚመጣጠን ግብር መገበር ሲችል ብቻ ነው።
በጥቅሉ በነሲብ፣ በጅምላና በኮታ የሚጣል ግብር የነጋዴውን ማህበረሰብ አቅም በማሟጠጥና ኪሱን በማራቆት በሂደት ተያይዞ መውደቅን እንጂ ተያይዞ ማደግን አያመጣም። "በነጻ ውድድር ገበያ የሚመራ" ነገር ግን ነጋዴ የሌለበት ወይም ሕገ ወጥነትና ጥገኛ ነጋዴ የተንሰራፋበት ሀገር መፍጠር ነው።
በተደጋጋሚ የሚነሳው የመንግስት ገቢና የሀገሪቱ አጠቃላይ ምርት አለመጣጣም መንስኤ ነጋዴው በቂ ግብር ባለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን ሳይቀረጥ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሕገ ወጥ የገቢ ሸቀጥ መበራከት፣ ቫት የማይጎበኘው አቅርቦት መስፋፋት፣ መንግስት ማግኘት የሚገባው ነገር ግን በአስፈጻሚ አካላት ሙሰኝነት ባክኖ የሚቀር ገቢና በሕገ ወጥ ነጋዴዎችና በሙሰኞች መመሳጠር አየር ላይ ተበልቶ የሚቀረው ገቢ ከሚከፈለው ግብር እጅግ የላቀ መሆን ነው ። ( ማብቂያ የሌለው የገቢ የሚያቀጣጥሉ በገቢ አቅም በላይ ወጭ መልመድ፣ ብክነት፣ ዝርክርከነትና በአቅም አለመኖር ብቻውን ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ ነው)
የመንግስት አስፈጻሚዎች ላይ የነሲብ አስገዳጅ ኮታ በመጣል ኮታቸውን ለመሟላት በየሱቁ፣ በየድርጅቱና በየፋብሪካው እየዞሩ ነጋዴውን ያልሸጠከውን ሸጠሃል። ያላመረትከውን አምርተሃል። ያላገኘውን ትርፍት አግኝተሃል በማለት አቅሉን በመሳት ወደ ሕገ ወጥነት እንዲያመራ ከመግፋት ይልቅ መንግስት የራሱን ጓዳ (የገቢዎችንና የጉምሩክን) አሰራር በመመርመርና በሙስና ተድበስብሶ አየር ላይ የሚቀረውን ግብር በመታደግ ገቢውን ማሳደግ፣ ወጭውን በመቆጣጠርና ቁጠባ በመለማመድ ገቢውን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይችላል።
ነጋዴውንም ከመዋከብ፣ ከመሳደድ በመታደግ ተስፋ ከመቁረጥና የሙሰኞች መጫወቻ ከመሆን ተገላግሎ እፎይታ አግኝቶና ተረጋግቶ አዕምሮውን ለስራ፣ ጊዜውንና ጉልበቱን ለፈጠራና ለምርታማነት፣ ገንዘቡን ለእድገት እንዲጠቀም በማገዝ እየተፈራሩና እየተጠራጠሩ በጨለማ ከመዳከር ይልቅ የስራ ጊዜን ውጤታማ፣ የነጋዴውም ሆነ የሸማቹን ህይወት በተስፋ የተሞላና ብሩህ ማድረግ ይቻላል።
"...ምን ማለት ነው?"
(ሙሼ ሰሙ)
#ethiopia | "ከፍተኛ ግብር የሰበሰቡ ተሸለሙ" የሚል ዜና በስፋት እየተዘገበ ነው። ከፍተኛ ግብር ሰበሰቡ ማለት ምን ማለት ነው ?! አንጻሩስ ምንድን ነው ? በጀት ነው ? ኮታ ነው? ወይስ የትም ፍጪው ዲቄቱን አምጭው ነው ? ከበጀት በላይ ማትረፍ እንጂ ከበጀት በላይ ግብር መሰብሰብስ እንዴት ይቻላል? ይህ አዲስ ግኝት ነው?
በደሞዝ ተቀጥሮ የሚሰራ ሰራተኛ "ውጤታማ ሲሆን" ጉርሻ ( Bonus) ከመስጠትና ደሞዙን ከማሳደግ አልፎ ለተቋሙ አገልግሎት የሚውል ቢሆንም በየዓመቱ ተሽከርካሪ መለወጥ የትኛው መንግስታዊ አሰራርና ደንብ እንደሚፈቅድ የውጭ ኦዲተር መጠየቅ የሚገባው ጉዳይ ይመስለኛል ?
ወደ ዋነኛ ጉዳዬ ልመለስ ።
እርግጥ ነው። ነጋዴ ንብረቱን ላለማጣትና ድርጅቱን ላለመዝጋት ሲል ጥሪቱንና አቅሙን አሟጦ እስኪጨርስና ቤቱ እስኪከረቸም ድረስ ከበጀትም ከኮታም በላይ እጥፍ ድርብ ግብር በማስከፈል ከበጀት በላይ ገንዘብ መሰብሰብ ይቻላል። ተችሏልም። ጥያቄው ግን እስከመቼ የሚለው ነው ?!
በዚህ መንገድ የመንግስት ገቢ አንድ ሺ ፐርሰንት ሊያድግና ሊመነደግ ይችላል። በኮታና በነሲብ ግብር የመሰብሰብ ዘመቻ በሂደት የነጋዴውን ገቢ እያዳከመና ትርፉን እያቀጨጨ ከመሄድ ውጭ ጤናማ የንግድ፣ የግብይይትና የግብር ስርዓት ሊፈጥር አይችልም። ንግድ ፈቃዱን በሰልፍ የሚመልሰውና ድብብቆሽ የሚጫወተው ነጋዴም ለዚህ ክስተት ሕያው ምስክር ነው። ለምን ቢባል ንግድ ለጽድቅ የሚሰራ ስራ አይደለም።
ለማንም ግልጽ እንደሚሆነው በጤናማ መንገድና በሕግ አግባብ የሚነግድ፣ የሚሰራና የሚያመርት ሰው (ካልከሰረ በስተቀር) ማትረፍ ብቻ ሳይሆን ከትርፉ ጥሪት በመቋጠርና አቅሙን በማጎልበት ንግዱን በማስፋፋት፣ የስራ እድል መፍጠርና ወደ ሚቀጥለው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መደብ ( Economic Class) መሸጋገር መቻል አለበት።
ጤናማ የኢኮኖሚ እድገትና ሽግግር፣ የንግድና የግብር ስርዓት መስተጋብር ማለት ይህው ብቻ ነው። ነጋዴውን አሟጦ በማስገበር ማቀጨጭና በሂደት ከገበያ እንዲወጣ ማድረግ የልማት፣ የእድገትና የምርታማነት እንቅፋት ከመሆን ባሻገር ሕገ ወጥነትና የጓሮ በር ድርድር እንዲስፋፋ በር መክፈት ብቻ ነው። በገሃዱ ዓለምም እየሆነ ያለውም ይህው ነው።
ጤናማ የግብር ስርዓት ንግድና ነጋዴው እንዲያብቡ አመቺ ሁኔታን በመፍጠር አምራቹን፣ ባለኢንዱስትሪውን፣ ቸርቻሪውን አከፋፋዩንና አስመጭውን በቁጥርም በአቅምም እንዲጎለብቱ በማገዝ ከሚፈጠረው ሰፊ የንግድ አቅምና ከሚሳለጠው የምርትና የግብይይት ስርዓት ከእያንዳንዱ ነጋዴ ላይ ተመጣጣኝ ግብር በመሰብሰብ በቅንጅት እንደ ሀገር ማደግ ይቻላል።
ይህ እውን መሆን የሚቻለው ነጋዴው በቂ ትርፍ አትርፎና ጥሪት ቋጥሮ የማምረት አቅሙን በማጎለብት ፣ ፋብሪካውንና ኢንዱስትሪውን በማሳድግ፣ የስራ እድልና አቅርቦትን በማስፋፋት እምቅ ሃይሉንና አቅሙን መጠቀም የማይገድበው፣ በተለይ ከገቢው ጋር የሚመጣጠን ግብር መገበር ሲችል ብቻ ነው።
በጥቅሉ በነሲብ፣ በጅምላና በኮታ የሚጣል ግብር የነጋዴውን ማህበረሰብ አቅም በማሟጠጥና ኪሱን በማራቆት በሂደት ተያይዞ መውደቅን እንጂ ተያይዞ ማደግን አያመጣም። "በነጻ ውድድር ገበያ የሚመራ" ነገር ግን ነጋዴ የሌለበት ወይም ሕገ ወጥነትና ጥገኛ ነጋዴ የተንሰራፋበት ሀገር መፍጠር ነው።
በተደጋጋሚ የሚነሳው የመንግስት ገቢና የሀገሪቱ አጠቃላይ ምርት አለመጣጣም መንስኤ ነጋዴው በቂ ግብር ባለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን ሳይቀረጥ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ሕገ ወጥ የገቢ ሸቀጥ መበራከት፣ ቫት የማይጎበኘው አቅርቦት መስፋፋት፣ መንግስት ማግኘት የሚገባው ነገር ግን በአስፈጻሚ አካላት ሙሰኝነት ባክኖ የሚቀር ገቢና በሕገ ወጥ ነጋዴዎችና በሙሰኞች መመሳጠር አየር ላይ ተበልቶ የሚቀረው ገቢ ከሚከፈለው ግብር እጅግ የላቀ መሆን ነው ። ( ማብቂያ የሌለው የገቢ የሚያቀጣጥሉ በገቢ አቅም በላይ ወጭ መልመድ፣ ብክነት፣ ዝርክርከነትና በአቅም አለመኖር ብቻውን ሊነሳ የሚገባው ጉዳይ ነው)
የመንግስት አስፈጻሚዎች ላይ የነሲብ አስገዳጅ ኮታ በመጣል ኮታቸውን ለመሟላት በየሱቁ፣ በየድርጅቱና በየፋብሪካው እየዞሩ ነጋዴውን ያልሸጠከውን ሸጠሃል። ያላመረትከውን አምርተሃል። ያላገኘውን ትርፍት አግኝተሃል በማለት አቅሉን በመሳት ወደ ሕገ ወጥነት እንዲያመራ ከመግፋት ይልቅ መንግስት የራሱን ጓዳ (የገቢዎችንና የጉምሩክን) አሰራር በመመርመርና በሙስና ተድበስብሶ አየር ላይ የሚቀረውን ግብር በመታደግ ገቢውን ማሳደግ፣ ወጭውን በመቆጣጠርና ቁጠባ በመለማመድ ገቢውን በእጥፍ ድርብ ማሳደግ ይችላል።
ነጋዴውንም ከመዋከብ፣ ከመሳደድ በመታደግ ተስፋ ከመቁረጥና የሙሰኞች መጫወቻ ከመሆን ተገላግሎ እፎይታ አግኝቶና ተረጋግቶ አዕምሮውን ለስራ፣ ጊዜውንና ጉልበቱን ለፈጠራና ለምርታማነት፣ ገንዘቡን ለእድገት እንዲጠቀም በማገዝ እየተፈራሩና እየተጠራጠሩ በጨለማ ከመዳከር ይልቅ የስራ ጊዜን ውጤታማ፣ የነጋዴውም ሆነ የሸማቹን ህይወት በተስፋ የተሞላና ብሩህ ማድረግ ይቻላል።
10 days ago
ከግንባታ ቦታ የወጡ ተሽከርካሪዎች መንገድን በጭቃ በማበላሸታቸው 55 ሺህ ብር ተቀጡ
#ethiopia | በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 በሚገኘው አሮጌ ቄራ አካባቢ የሚገኘው TNT Construction የግንባታ ፕሮጀክት ተሽከርካሪዎች መንገድን በጭቃ በማበላሸታቸው 55 ሺህ ብር ቅጣት እንደተጣለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታውቋል።
እንደ ባለሥልጣኑ መረጃ፣ የድርጅቱ ተሽከርካሪዎች ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ በወቅቱ የነበረውን ዝናብ ተገን በማድረግ ከቦታው ለመሰወር ቢሞክሩም፣ የአራዳ ደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት ከልደታ ትራፊክ ማኔጅመንት ጋር በመተባበር ተሽከርካሪዎቹን በመለየት 55 ሺህ ብር የአስተዳደራዊ ቅጣት ጥሏል።
ባለሥልጣኑ ተቋማት ሥራቸውን ሲያከናውኑ የሕዝብ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የመንገድ መሠረተ ልማቶች፣ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስቧል።
በተጨማሪም የክረምት ወቅት በመሆኑ ለማህበረሰቡ አደጋ የሚያስከትሉ ወይም የመሠረተ ልማት ጥበቃን ችላ የሚሉ የግልና የመንግሥት ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ የሕግ ማስከበር እርምጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
#ethiopia | በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 በሚገኘው አሮጌ ቄራ አካባቢ የሚገኘው TNT Construction የግንባታ ፕሮጀክት ተሽከርካሪዎች መንገድን በጭቃ በማበላሸታቸው 55 ሺህ ብር ቅጣት እንደተጣለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን አስታውቋል።
እንደ ባለሥልጣኑ መረጃ፣ የድርጅቱ ተሽከርካሪዎች ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ በወቅቱ የነበረውን ዝናብ ተገን በማድረግ ከቦታው ለመሰወር ቢሞክሩም፣ የአራዳ ደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት ከልደታ ትራፊክ ማኔጅመንት ጋር በመተባበር ተሽከርካሪዎቹን በመለየት 55 ሺህ ብር የአስተዳደራዊ ቅጣት ጥሏል።
ባለሥልጣኑ ተቋማት ሥራቸውን ሲያከናውኑ የሕዝብ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የመንገድ መሠረተ ልማቶች፣ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን በጥንቃቄ በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስቧል።
በተጨማሪም የክረምት ወቅት በመሆኑ ለማህበረሰቡ አደጋ የሚያስከትሉ ወይም የመሠረተ ልማት ጥበቃን ችላ የሚሉ የግልና የመንግሥት ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ የሕግ ማስከበር እርምጃዎች በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
11 days ago
በምስራቅ አርሲ ዞን በታጣቂዎች የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፋ ሆኑ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
Comments